ETHIO-MEREJA®
News & Media Channel® Addisababa, Ethiopia🇪🇹 ውድ የኢትዮ መረጃ ቤተሰቦች ከዚህ የቴሌግራም ቻናል ውጪ ሌላ መረጃ የምናቀርብበት ምንም አይነት የዩቲዩብ፣ የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆች እንደሌለን ለማሳወቅ እንወዳለን፣ ስለሆነም በተመሳሳይ ስም በተከፈቱ ገፆች እንዳይሸወዱ ጥንቃቄ እንድታደርጉ እናሳስባለን። ለጥቆማና ማስታወቂያ ለማሰራት 👉 @ethio_merejabot
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ETHIO-MEREJA®
کانال ETHIO-MEREJA® (@ethio_mereja) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 101 179 مشترک است و جایگاه 2 511 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 291 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 101 179 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 22 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -1 183 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -30 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 12.85% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 8.18% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 13 006 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 8 277 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 61 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“News & Media Channel®
Addisababa, Ethiopia🇪🇹
ውድ የኢትዮ መረጃ ቤተሰቦች ከዚህ የቴሌግራም ቻናል ውጪ ሌላ መረጃ የምናቀርብበት ምንም አይነት የዩቲዩብ፣ የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆች እንደሌለን ለማሳወቅ እንወዳለን፣ ስለሆነም በተመሳሳይ ስም በተከፈቱ ገፆች እንዳይሸወዱ ጥንቃቄ እንድታደርጉ እናሳስባለን።
ለጥቆማና ማስታወቂያ ለማሰራት
👉 @ethio_mere...”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 23 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 23 ژوئیه | 0 | |||
| 22 ژوئیه | 0 | |||
| 21 ژوئیه | 0 | |||
| 20 ژوئیه | 0 | |||
| 19 ژوئیه | 0 | |||
| 18 ژوئیه | 0 | |||
| 17 ژوئیه | 0 | |||
| 16 ژوئیه | 0 | |||
| 15 ژوئیه | 0 | |||
| 14 ژوئیه | 0 | |||
| 13 ژوئیه | 0 | |||
| 12 ژوئیه | 0 | |||
| 11 ژوئیه | 0 | |||
| 10 ژوئیه | 0 | |||
| 09 ژوئیه | 0 | |||
| 08 ژوئیه | 0 | |||
| 07 ژوئیه | 0 | |||
| 06 ژوئیه | 0 | |||
| 05 ژوئیه | 0 | |||
| 04 ژوئیه | 0 | |||
| 03 ژوئیه | +2 | |||
| 02 ژوئیه | +4 | |||
| 01 ژوئیه | 0 |
| 2 | ጄኤፍኤም 106.7 ሬድዮ ሞገድ ለስድስት ወራት ታገደ!
የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በጄኤፍኤም 106.7 ሬድዮ ጣቢያ ላይ የስድስት ወራት የስርጭት እግድ ጣለ
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የጄኤፍኤም (JFM 106.7) ሬድዮ ጣቢያ የብሮድካስት ስርጭት ከሐምሌ 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት ሙሉ ለሙሉ እንዲታገድ መወሰኑን አስታወቀ። ባለሥልጣኑ ውሳኔውን ያስ አስተላለፈው ጣቢያው በተደጋጋሚ የተሰጡትን የቃልና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያዎች ሳይቀበል በመቅረቱ እና በአዋጅ ቁጥር 1238/2013 የተጣሉበትን የፈቃድ ውል ግዴታዎች ባለመወጣቱ እንደሆነ ገልጿል።
ባለሥልጣኑ ባደረገው የይዘት ክትትልና የአካል ኢንስፔክሽን ምልከታ ጣቢያው በህግ የተጣለበትን የሀገራዊ ይዘት ሽፋን አለማካተቱን፣ ህዝብን የሚያስተምሩና የሚያዝናኑ ፕሮግራሞችን ከማቅረብ መቆጠቡን እንዲሁም ለሀገራዊ እሴቶችና ለፖለቲካዊ-ኢኮኖሚያዊ እድገት አስተዋጽኦ የማድረግ ግዴታውን አለመወጣቱን አረጋግጧል። በውሳኔው መሰረት የኢትዮጵያ ኮሚዩኒኬሽን ባለሥልጣንም ጣቢያው የተመደበለትን 106.7 የሬድዮ ሞገድ በእግዱ ወቅት እንዳይጠቀም ማሳሰቢያ የሰጠ ሲሆን፣ ጣቢያው ለሕግ ተገዢ በመሆን ስርጭቱን በአስቸኳይ እንዲያቆም ታዟል። | 7 336 |
| 3 | አሜሪካ በኢራን ላይ ጥቃት ሰነዘረች፤ የጦርነቱ ወጪ 37.5 ቢሊዮን ዶላር መድረሱ ተገለጸ!!
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አሜሪካ እስካሁን 37.5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ያስወጣትን የኢራን ጦርነት «አልጨረስኩም» ሲሉ ካስጠነቀቁ በኋላ፥ በዛሬው ረቡዕ ዕለት የዋሺንግተን አዳዲስ ጥቃቶች በቴህራን የሚገኙ የአየር መከላከያዎችን አንቀሳቅሰዋል።
ሁለቱ ተፋላሚዎች በስትራቴጂካዊው ሆርሙዝ ወሽመጥ ዙሪያ ባካሄዱት ውጊያ ምክንያት የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነቱ መፍረሱን ተከትሎ፥ የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ለዓለም አቀፍ የነዳጅ አቅርቦት ቁልፍ የሆኑትን የቀጣናውን ሌሎች መተላለፊያዎች ወደ ማካተት አድጓል።
ሆኖም የዩናይትድ ስቴትስ ከፍተኛ ዲፕሎማት ማርኮ ሩቢዮ ዋሺንግተን ከቴህራን ጋር ስምምነት ላይ ለመድረስ ዲፕሎማሲን ለመጠቀም ፈቃደኛ መሆኗን ደግመው አረጋግጠዋል። ሩቢዮ በማኒላ በተካሄደው የደቡብ ምስራቅ እስያ ሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ እንደተናገሩት «በአሁኑ ወቅት እያጋጠመን ያለው ችግር የድርድር ሂደቱን በቁም ነገር አለመውሰዳቸው ነው» ብለዋል።
የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እስማኤል ባቃኢ በበኩላቸው በአሸማጋዮች በኩል ከዋሽንግተን ጋር የሚደረጉ የዲፕሎማሲ ልውውጦች መቀጠላቸውን ገልጸዋል።
በመካከለኛው ምስራቅ የተካሄደው የቅርብ ጊዜ የጥቃት ማዕበል የአሜሪካ ጦር እንደ «ወታደራዊ ሎጂስቲክስ መሰረተ ልማት» ያሉ ኢላማዎችን መምታትን ያካተተ ሲሆን፥ የኢራን መንግሥት መገናኛ ብዙኃን ደግሞ የኑክሌር የኃይል ማመንጫ በሚገኝበት ቡሼህርን ጨምሮ በመላ አገሪቱ ጥቃቶች መፈጸማቸውን ዘግበዋል። | 9 336 |
| 4 | በሆሊውድ ዝነኛ የብሎክባስተር ፊልሞች "Godzilla vs. Kong" እና "Godzilla x Kong: The New Empire" ላይ “ጂያ” የተሰኘውን ቁልፍ ገጸ-ባህሪ በመወከል የምትታወቀው የ18 ዓመቷ መስማት የተሳናት ወጣት ተዋናይት ኬይሊ ሆትል ማክሰኞ ጠዋት በደረሰባት ድንገተኛ የመኪና አደጋ ሕይወቷ ማለፉን ፎክስ ኒውስ ዲጂታል አረጋግጧል።
የተዋናይቷ አባት ጆሹዋ ሆትል በሜሪላንድ ግዛት ውስጥ ስለደረሰው አደጋ በሰጠውና በፌስቡክ በኩል ባስተላለፈው የ23 ደቂቃ የአሜሪካ የምልክት ቋንቋ (ASL) ቀጥታ ስርጭት መግለጫ፣ ልጁ ወደ ሆስፒታል በመጓዝ ላይ እያለች ልቧ መቆሙን በለቅሶ አስታውቋል።
ከተከታታይ መስማት የተሳናቸው ትውልዶች በተገኘችውና የቨርጂኒያ ተወላጅ በሆነችው ኬይሊ ሆትል ሞት ሳቢያ መላው የሆሊውድ የኪነ-ጥበብ ማኅበረሰብ በከባድ ሐዘን ውስጥ ወድቋል።
ይህንን ልብ ሰባሪ ክስተት እና የተዋናይቷን አጭር የሕይወት ጉዞ በጥልቀት ስንመለከተው ኬይሊ በሆሊውድ ውስጥ በገንዘብና በጥቅም ብቻ በሚመራው የፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ መስማት ለተሳናቸው አካላት እውነተኛና ተጨባጭ የውክልና መድረክ የፈጠረች ስልታዊ ተፅዕኖ ፈጣሪ መሆኗን ያሳያል። በ2021 ዓ.ም. “ጎድዚላ ቨርሰስ ኮንግ” በተሰኘው ታላቅ ፊልም ላይ ከግዙፉ “ኮንግ” ጋር ልዩ የልብ ትስስር ያላትን የጂያን ገጸ-ባህሪ ወክላ ስትወጣ፣ በሆሊውድ ታሪክ ውስጥ መስማት የተሳናቸው ተዋናዮች በትልልቅ የሳይንስ ልብወለድ ፊልሞች ላይ የመሪነት ሚና መጫወት እንደሚችሉ በተግባር ያሳየች ድንቅ ተሰጥኦ ነበረች።
በ2024 ዓ.ም. በወጣው ሁለተኛው ፊልም ላይም የምልክት ቋንቋን በፊልሙ ውስጥ በስፋት በማስተዋወቅ የራሷን ደማቅ አሻራ አኑራለች። | 9 582 |
| 5 | ዩክሬናዊያን ለፕሬዝደንት ዘለንስኪ እስከ አርብ ቀነ ገደብ ሰጡ፡፡
የዩክሬይኑ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ የመከላከያ ሚኒስትራቸውን ማባረራቸው ከፍተኛ ተቃውሞ አስከትሎባቸዋል፡፡
ሚኒስትሩን ሚካኤሎ ፌርዶቭን ከስልጣን ማንሳታቸውን ካስታወቁበት ካለፈው ሳምንት ማለትም ጁላይ 16 አንስቶ በከተሞች የተቃውሞ ሰልፎች እየተደረጉ ነው፡፡ በኬይቭ ከሚገኘው ኢቫን ፍራንኮ አደባባይ የተጀመረው ይህ ሰልፍ አሁን ወደ16 ግዛቶች ተዛምቷል፡፡
ተቃዋሚዎቹ በጦርነቱ ከፍተኛ ሚናና አስተዋፅኦ የነበራቸውን መከላከያ ሚኒስትር ከስልጣን ማንሳት አያስፈልግም የሚሉ ናቸው፡፡ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ ሚኒስትሩን ለምን ማንሳት እንደፈለጉ የሰጡት ምክንያት ባይኖርም የአገሪቱ ሚዲያዎች ግን ምክንያቱ በፕሬዝደንቱና በሚኒስትሩ መካከል የተፈጠረው ፀብ እንደሆነ በመግለፅ ላይ ናቸው፡፡ በሚኒስትሩ ከስልጣን መነሳት የተቆጡት ዩክሬናዊያን ቁጥር ከእለት ወደእለት እየጨመረ መምጣቱ ደግሞ ጉዳዩን አሳሳቢ አድርጎታል፡፡
ተቃዋሚዎቹ ዛሬ ባወጡት መግለጫ ዘለንስኪ መከላከያ ሚኒስትሩን እስከ አርብ ድረስ ወደስልጣን እንደሚመልሱ ቀነ ገደብ አስቀምጠውላቸዋል፡፡ ፕሬዝደንት ዘለንስኪ አዲስ መከላከያ ሚኒስትር የሾሙ ቢሆንም የተቃውሞው አስተባባሪ የሆነው ዲሚትሪ ኮዚያቲስኪ በሰጠው ቃለ ምልልስ በ3 ቀናት ውስጥ ፌርዶቭ እንዲመለሱ ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡ ይህ ካልሆነ በመላው አገሪቱ ያልተገደበ ተቃውሞ እንደሚከናወን አስጠንቅቋል፡፡ | 9 994 |
| 6 | #ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
👉Studio 32ካሬ 1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ 2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና 3 መኝታ ከ 118ካሬ ጀምሮ
👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት
👉100% ለሚከፍሉ እስከ 35% ቅናሽ
👉20% ከፍለው ቀሪውን በ 16 ዙር ከፍለው የሚጨርሱት
👉 በመገናኛ ዲያስፖራ አደባባይ ፊት ለፊት(የካ ክፍለ ከተማ ጀርባ) ከቴምር ሪልስቴት
👉በተጨማሪም በቡልጋሪያ(አፍሪካ ህብረት ፊት ለፊት) እና በአዋሬ(ቤተመንግስት አጠገብ) አፓርትመንቶች አሉን
💥 የንግድ ሱቆች
#ቡልጋሪያ ላይ ከ900ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ፒያሳ ላይ ከ1.4ሚሊዮን ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ቃሊቲገላን ላይ ከ500ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ።
#ሳር ቤት አዳምስ አጠገብ ከ 900ሺ ብር ቅድመ ክፍያ
🎯ልብይበሉ
# ያለምንም ወለድና የግንባታ እቃዎች ጭማሪ በኢትዮጵያ ብር ከፍለው የሚጨርሱት ነው
#ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
👇👇👇👇👇👇
+251939770177
+251996856273
https://t.me/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp. https://wa.me/251939770177
Telegram :@KalTemerRealEstate | 10 528 |
| 7 | በአዲስ አበባ ከተማ በአከራይ ተከራይ ውል መፈፀም የተከለከሉ ተግባራት...
👉 የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል ሳያስመዘግቡ መከራየትና ማከራየት
👉 በአከራይ ወይም ተከራይ ቸልተኝነት የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል በአዋጁ የተቀመጠው የጊዜ ገደብ አሳልፎ ማስመዝገብ፤
👉 የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል እድሳት አለማስመዝገብ፤
👉 በአዋጁ ከተፈቀደው አግባብ ውጪ የዋጋ ጭማሪ ማድረግ፤
👉 በአዋጁ ከሚፈቅደው ውጪ የውል ዘመን ሳይጠናቀቅ ከቤት ማስወጣት፤
👉 በአዋጁ የተቀመጠውን የማስታወቂያ ወይም የማስጠንቀቂያ ጊዜ ሳይሰጥ ውል ማቋረጥ፤
👉 አዋጁ ላይ ከተቀመጠው መጠን በላይ የቅድመ ክፍያ እንዲፈፀም ማስገደድ፤
👉 በባንክ ወይም በሌላ ሕጋዊ የሆነ የኤሌክትሪክ መንገድ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ክፍያ አለመፈፀም፤
👉 ቀደም ሲል ሲከራይ የቆየ የመኖሪያ ቤት ወይም ግንባታው ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ አዲስ መኖሪያ ቤት ያለአገልግሎት እንዲቀመጥ ማድረግ፤
👉 በአዋጁ ለአከራይ የተሰጠውን ማበረታቻ ያለአግባብ መጠቀም ሀሰተኛ መረጃ ወይም ማስረጃ ማቅረብ የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ መረጃ ያመላክታል፡፡ | 10 210 |
| 8 | የሰኔ ወር 2018 ዓ.ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት 13.9 በመቶ ሆኖ ተመዘገበ
የሰኔ ወር 2018 ዓ.ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት መጠን 13.9 በመቶ የተመዘገበ ሲሆን ይህም በሰኔ 2017 ዓ.ም ከነበረው 13.9 በመቶ ተመሳሳይ ሆኖ ተመዝገቧል።
የምግብና አልኮል ያልሆኑ መጠጦች ዋጋ 15.1 በመቶ የጨመረ ሲሆን በዋናነት አትክልት፣ ስጋ ፣ የወተት ተዋፅኦዎች፣ እንቁላል፣ ፍራፍሬ፣ ዘይትና ስኳር የመሳሰሉት የምግብ ሸቀጦች ዋጋ በመጨመራቸው የተመዘገበ ጭማሪ መሆኑን መረጃው ያሳያል።
ምግብ ነክ ያልሆኑ የዋጋ ግሽበት 12.2 በመቶ የደረሰ ሲሆን ትራንስፖርት 14.3 በመቶ፣ አልኮል መጠጦችና ትምባሆ 14.5 በመቶ፣ በኮሙዩኒኬሸን 8.9 በመቶ ፣ ምግብ ቤቶችና ሆቴሎች 12.0 በመቶ እንዲሁም ሌሎች እቃዎችና አገልግሎቶች 17.9 በመቶ ሆነው ተመዝግበዋል።
የኢትዮጵያ ስታቲስቲክስ አገልግሎት | 10 011 |
| 9 | መንግስት አዲስ የተሽከርካሪ ባለቤትነት ታክስ ሊጥል ነው
መንግስት በ2020 በጀት ዓመት ተግባራዊ የሚሆን አዲስ የተሽከርካሪ ባለቤትነት ታክስ ለመጣል እየተዘጋጀ ነው።
የሚኒስትሮች ምክር ቤት የህግ ረቂቁን በታህሳስ ወር መጨረሻ ለፌዴሬሽን ምክር ቤት እንደሚያቀርብ ካፒታል ያገኘዉ መረጃ ያመለክታል። ታክሱ ከጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት እስከ 0.2 በመቶ ገቢ ያስገኛል ተብሎ ይጠበቃል። | 11 378 |
| 10 | አንድ የቻይና ኩባንያ በኢትዮጵያ የተቀናጀ የቡና ኢንዱስትሪ ፓርክ ለመመስረት ስምምነት ተፈራረመ
የቻይናው ሑይቹዋን ዮንግዩ ሰፕላይ ቼይን ማኔጅመንት ሰርቪስ (Huichuan Yongyu Supply Chain Management Service Co., Ltd.) በኢትዮጵያ የተቀናጀ የቡና ኢንዱስትሪ ፓርክ ለመመስረት ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር የመግባቢያ ስምምነት መፈራረሙን ኮሚሽኑ አስታወቀ።
ስምምነቱ የተፈረመው የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነሮች ዳጋቶ ኩምቤ እና ዚናቡ ይርጋ ከቻይናው ኩባንያ ከፍተኛ ሥራ አስፈጻሚዎች ጋር በኢትዮጵያ የቡና ማቀነባበር ዘርፍ ባሉ የኢንቨስትመንት ዕድሎች ላይ ከተወያዩ በኋላ ነው።
እንደ ኮሚሽኑ ገለጻ፣ አቶ ዳጋቶ የቡና መገኛ የሆነችው ኢትዮጵያ በ2018 የኢትዮጵያ በጀት ዓመት ከ3 ቢሊዮን ዶላር በላይ ዋጋ ያለው ቡና ወደ ውጭ መላኳን ገልጸው፤ ነገር ግን የአገሪቱ የወጪ ንግድ አብዛኛው አሁንም እሴት ሳይጨመርበት በጥሬው የሚላክ መሆኑን ጠቁመዋል።
ኩባንያው ለቡና ብቻ በተዘጋጀ የኢንዱስትሪ ፓርክ ላይ ለመሰማራት ያቀደው ኢንቨስትመንት፣ ኢትዮጵያ እሴት የተጨመረባቸው የቡና ምርቶችን ወደ ውጭ የመላክ ስትራቴጂዋን ለመደገፍ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ገልጸዋል።ኮሚሽኑ እንዳለው፣ አቶ ዚናቡ ፕሮጀክቱን ወደ ሥራ ለማስገባት እንዲረዳ ኮሚሽኑ አስፈላጊውን ድጋፍ እና የኢንቨስትመንት ማመቻቸት እንደሚያደርግ ለኩባንያው ልዑክ አረጋግጠውላቸዋል። | 12 182 |
| 11 | ስፔን የ23ኛው ዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነች
****
በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 በማሸነፍ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ሆናለች።
የጨዋታው መደበኛ ክፍለ ጊዜ ያለ ግብ በመጠናቀቁ አሸናፊውን ለመለየት 30 ደቂቃ ተጨምሯል።
በጭማሪው ክፍለ ጊዜ 106ኛው ደቂቃ ላይ ፌራን ቶሬስ ያስቆጠራት ግብ ስፔንን አሸናፊ አድርጋለች።
በዚህም ስፔን ከ16 ዓመታት በኋላ ውድድሩን አሸንፋ በታሪኳ ለሁለተኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ባለቤት ሆናለች። | 13 655 |
| 12 | የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) በዛሬው ዕለት መግለጫ የሰጡ ሲሆን ካነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች መሀከል፡-
👉 ሀገራዊ መግባባት በክርክርና በአብላጫ ድምጽ የሚወሰን እንዳልሆነ አውቀናል፡፡
👉 ልሂቃንና ማህበረሰቡ አብረው ለመጀመሪያ ጊዜ ተገናኝተው የሚመክሩበት ጊዜ ስለሆነ ሁለቱንም አንድ ወለል ላይ ማምጣቱ በጣም ተገቢ ነው፡፡
👉 ሂደቱን የተሳለጠ ለማድረግ ተጨማሪ ግብአቶች እየሰጠን እንገኛለን፡፡
👉 የሀገራዊ ምክክር ሂደቱ የተዋጣለት መሆኑን ስናስተውል ብዙዎች ወደ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ መጥተዋል፡፡
👉 ከአሁን በፊት ከሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ጋር ያልሰሩ የፖለቲካ ፓርቲዎች መጥተዋል፤ በጣም ደስ ብሎናል፡፡
👉 በስተመጨረሻም ቢሆን መካተት ፈልገው የጠየቁትን እንዲካተቱ አድርገናል፤ ይሄ ደግሞ ለሀገራችን አስፈላጊ ነው፡፡
👉 እስካሁን ያልመጡ ጥቂት የፖለቲካ ፓርቲዎችና ታጣቂዎች አሁንም ወደዚህ እንዲመጡ ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡
👉 ከሚቀጥለው ሰኞ ጀምሮ ከጠዋት እስከ ማታ ስራዎቻችንን በየቦታው ተከፋፍለን የምንሰራበት ጊዜ ሙሉ በሙሉ ይጀምራል፡፡ | 14 463 |
| 13 | #ስለህግ #የህግመረጃ
በዕርቅ_ማለቅ_የሚችሉ_የወንጀል_አይነቶች!
በወንጀል ጉዳዮች እርቅ የሚከናወነው በልዩ ሁኔታ ነው፡፡ምክንያቱም በመርህ ደረጃ ወንጀል የህዝብን እና የመንግስትን ጥቅም የሚጉዳ ተግባር ነው ተብሎ ስለሚታመን ነው፡፡
👉ክስም የሚቀርበው መንግስት በወከለው ዐቃቤ ህግ ሲሆን ሙሉ ወጪውም የሚሸፈናው በመንግስት ይሆናል፡፡ስለሆነም በወንጀል ህጎች ስር በእርቅ ማለቅ የሚችሉ ገዳዮች በግልፅ ተደንግገው ይገኛሉ፡፡
ለአብነት ለመጥቀስ ያክል ፡-
1. ታስቦ የሚፈጸም ቀላል የአካል ጉዳት (አንቀጽ 556(1)፣
2. በቸልተኝነት የሚፈጸም ቀላል የአካል ጉዳት (አንቀጽ-559(3))፣
3. የእጅ እልፊት (አንቀጽ-560(1)) ፣
4. የዛቻ ወንጀል (አንቀጽ-580) ፣
5. አመንዝራነት (አንቀጽ-652) ፣
6. የሥድብ እና ማዋረድ (አንቀጽ-615) ፣
7. የስም ማጥፋት ወንጀል (አንቀጽ-618) ፣
8. በቤተዘመድ ንብረት ላይ የተፈጸመ ንብረት ነክ ወንጀል (አንቀጽ-664)
9. ጋብቻን በተንኮል ወይም በማታለል መፈፀም(አንቀጽ-646)፣
10. ቀለብ የመስጠት ግዴታን ያለመወጣት(አንቀጽ-558)፣
11. በሌላ ሰው ሀብት ያለአግባብ መጠቀም(አንቀጽ-678)፣
12. አግኝቶ መደበቅ(አንቀጽ-679)፣
13. በሰው ንብረት ላይ ሁከት ማድረግ(አንቀጽ-686)፣
14. በሌላ ሰው ንብረት ላይ ጉዳት ማድረስ(አንቀጽ-689)…ወዘተ ይገኙበታል፡፡
ወንጀሉ የፈጸመው ሰው ቀደም ሲል ተመሳሳይ ወንጀል የፈጸመ ከሆነ ፣ በሕጻናት ወይም በዕድሜ በገፉ ሰዎች ላይ የተፈጸመ ከሆነተጎጂው በሕግ ፊት የመወሰን አቅም የሌለው ከሆነ እርቅ ላይሰራ ይችላል።
ጠቃሚ ነውና ለወዳጆ ያካፍሉ! ሼር!
---ETHIO-MEREJA--
T.me/ethio_mereja | 12 759 |
| 14 | #ጤናመረጃ
የሀበሻ ጎመን ዋና ዋና የጤና ጥቅሞች!
የሀበሻ ጎመን በቪታሚኖች (C, A, K) በማዕድናት (ካልሲየም፣ ብረት) እና በፀረ-ኦክሲዳንት ንጥረ ነገሮች እጅግ የበለፀገ ነው።
1. ለአጥንት ጥንካሬና ጤንነት፦ የሀበሻ ጎመን እጅግ ከፍተኛ የካልሲየም (Calcium) እና የቪታሚን ኬ (Vitamin K) ይዘት ስላለው፣ ለአጥንት መገንባት፣ ለጥንካሬ እና የአጥንት መሳሳትን ለመከላከል አስተዋጽኦ አለው።
2. በሽታ የመከላከል አቅምን ለማጠናከር፦ በውስጡ ባለው ከፍተኛ የቪታሚን ሲ (Vitamin C) መጠን ምክንያት፣ የሰውነትን በሽታ የመከላከል ሥርዓት በማገዝ ከኢንፌክሽኖች እና ከተለያዩ በሽታዎች ይጠብቃል።
3.የደም ማነስን ለመከላከል፦ ጎመን በውስጡ ከፍተኛ የiron ማዕድን ይዟል። ይህም የሰውነታችንን ቀይ የደም ሴል ምርት በማገዝ የደም ማነስ ችግር እንዳይከሰት ትልቅ እገዛ ያደርጋል።
4.ለምግብ መፈጨት ሥርዓት፦ ልክ እንደ ጥቅል ጎመን ሁሉ፣ የሀበሻ ጎመንም ከፍተኛ የፋይበር (የቃጫ) ይዘት ስላለው የሆድ ድርቀትን ለመከላከል እና የአንጀትን ጤንነት ለመጠበቅ ይረዳል።
5.ለአይን ጤንነትና እይታ፦ በአይን ላይ የሚመጡ የዕድሜ መግፋት ጉዳቶችን እና ሌሎች የዓይን በሽታዎችን የመከላከል አቅም ያላቸውን ሉቲን እና ቪታሚን ኤ በበቂ መጠን ይዟል።
6.ለቆዳና ለፀጉር ውበት፦ በውስጡ የሚገኙት ቪታሚኖች (A,C,E) እና ፀረ-ኦክሲዳንቶች ለቆዳ ጤንነት፣ ለወጣትነት ገጽታ እና ለፀጉር ጥንካሬ አስተዋጽኦ ያደርጋሉ።
ጠቃሚ ምክር :- የሀበሻ ጎመንን ከመጠን በላይ ሳያበስሉ (ሳይሞት) በመጠኑ አብስሎ መመገብ በውስጡ ያሉትን ጠቃሚ ንጥረ ነገሮች ሙሉ በሙሉ ለማግኘት ይረዳል።
ጠቃሚ ነውና ለወዳጆ ያካፍሉ! ሼር!
---ETHIO-MEREJA--
T.me/ethio_mereja | 13 227 |
| 15 | በውጭ ሀገር ተደብቀው በበርካታ ኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ ኢሰብአዊ ድርጊቶችን ሲፈጽሙ የነበሩ ዳውድ ተፈሪ ለገሰ እና ደስታ ተገኝ አበጋዝ የተባሉ አደገኛ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታወቀ!!
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ዱባይ ፖሊስ ጋር በመቀናጀት በውጭ ሀገር ተደብቀው በበርካታ ኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ ኢሰብአዊ ድርጊቶችን ሲፈጽሙ የነበሩ ዳውድ ተፈሪ ለገሰ እና ደስታ ተገኝ አበጋዝ የተባሉ አደገኛ ሕገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉን አስታውቋል።
ሁለቱ ዋና ተጠርጣሪዎች የተለያዩ የማታለያ ዘዴዎችን በመጠቀም 105 ዜጎችን በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ዱባይ በመውሰድና ከ188 ሚሊዮን ብር በላይ ከተጎጂዎች በመሰብሰብ፣ በበርካታ ዜጎች ላይ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት ሲፈጽሙ የቆዩ በመሆናቸው የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከዱባይ ፖሊስ ጋር በመተባበር በቁጥጥር ሥር ውለው ለሀገራችን ተላልፈው እንዲሰጡ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከተባበሩት አረብ ኢምሬትስ ዱባይ የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል በደረሰው ጥቆማ፣ ተጠርጣሪዎቹ ዱባይ ተቀምጠው ሀገር ውስጥ ባሉ ተባባሪዎቻቸው አማካኝነት ወጣቶችን በመመልመል ወደ ዱባይ በመላክ፣ በተዘጋጀ የማገቻ ቦታ በማቆየት፣ በተለይ በሴቶች ላይ ጥቃት በማድረስና በማሰቃየት ከፍተኛ ወንጀል ሲፈጽሙ የቆዩ መሆናቸው ተረጋግጧል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስም ጉዳዩን ሲያጣራ ቆይቶ በሀገር ውስጥና በውጭ ሆነው በተቀናጀ መንገድ ወንጀሉን ሲፈፅሙ በቆዩ ዳውድ ተፈሪ ለገሰ እና ደስታ ተገኝ አበጋዝ እና በግብረአበሮቻቸው ላይ የፍርድ ቤት መያዣ ትዕዛዝ በማውጣት፣ ውጭ ሀገር ያሉትን ከዱባይ ፖሊስ ጋር በትብብር በመስራት ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ውለው ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ለሀገራችን ተላልፈው እንዲሰጡ አድርጓል።
ተጠርጣሪዎቹ ምንም ዓይነት ሰውን ወደ ውጭ መላክ የሚያስችል ሕጋዊ ፍቃድ ሳይኖራቸው፣ በሀገር ውስጥ ያለው ቡድን ከውጪ ካለው ቡድን ጋር ትስስር በመፍጠርና በተቀናጀ መልኩ "በተለያዩ ካምፓኒዎች ስራ እናስቀጥራችኋለን’’ በማለት ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ በርካታ ዜጎችን ከተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች በመመልመል፣ ሀሰተኛ መረጃዎችን በማሰራጨትና ያልተገባ ተስፋ በመስጠት ከአንድ ሰው ከ320,000 እስከ 600,000 ብር በመቀበል ማታለያ የቱሪስት ቪዛ አዘጋጅተው በመላክ፣ በሀገር ውስጥ ባሉ ተባባሪዎቻቸው በተከፈተ የባንክ አካውንት ገንዘቡን በኢትዮጵያ ብር፣ በድርሃም እና በሪያል ገቢ የሚያስደርጉ መሆናቸውን ፖሊስ ደርሶበታል።
ገንዘቡን የከፈሉ ተጎጂዎች ዱባይ እንደገቡ በጉልበት ሥራ ላይ እንዲሰማሩ በማድረግ፣ ከተጎጂዎች "ኮሚሽን" በሚል ተጨማሪ ገንዘብ በማስከፈል እንዲሁም የሁለት ወር የቱሪስት ቪዛ ሲያልቅ "የሁለት ዓመት የመኖሪያ ፍቃድ እናሰጣችኋለን፤ ካልከፈላችሁ ግን ወደ ኢትዮጵያ ትመለሳላችሁ" በማለት በአንድ ሰው 1 ሺህ 200 ድርሃም እንዲከፍሉ በማድረግ በዜጎች ላይ ከፍተኛ ግፍና ስቃይ ሲያደርሱ ቆይተዋል ብሏል ፖሊስ።
ተጠርጣሪዎቹ ተጎጂዎችን ከዱባይ ኤርፖርት ከተቀበሉ በኋላ ሰዎችን የሚያከማቹበት ቦታ በመውሰድ፣ በአንድ ክፍል ውስጥ በርካታ ወንዶችንና ሴቶችን በማገት፣ ምግብ በስምንት ቀን አንድ ጊዜ ደረቅ ሩዝ በመስጠት ለከፍተኛ ርሃብ እና እንግልት እንዲሁም ሴቶች ላይ ጾታዊ ጥቃት ሲያደርሱባቸው መቆየታቸው ተደርሶበታል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በተጨማሪ ባደረገው ክትትል፣ በሀገር ውስጥ ሆነው ዱባይ ካሉት ግብረ-አበሮቻቸው በሚሰጣቸው ትዕዛዝ ሰዎችን መልምሎ በመላክና የባንክ አካውንት ከፍተው ገንዘብ እያሰባሰቡ የነበሩ 1ኛ ብዙአየሁ አውግቸው በሀይሉ እና 2ኛ ራህመት አበበ እሸቴ የተባሉ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራውን በስፋት በማከናወን ላይ መሆኑን ገልጿል።
ፖሊስ ምርመራውን ዘመኑ ያፈራቸውን ቴክኖሎጂዎች ተጠቅሞ ይህንን ውስብስብና ድንበር ተሸጋሪ ወንጀል ለማጣራት እንዲሁም በእነዚህ ተጠርጣሪዎች አማካኝነት ከሀገር ወጥተው ከፍተኛ ስቃይ ደርሶባቸው ከነበሩ ግለሰቦችና ተጎጂዎች ካሉበት ዱባይ የቀጥታ ቨርቹዋል የምስክርነት ቃላቸውን በመቀበል ላይ ይገኛል።
ፖሊስ ሕጋዊ ፍቃድን ሽፋን በማድረግ ከሕገ-ወጥ አዘዋዋሪዎች ጋር በመመሳጠር ሕገ-ወጥ ተግባር የሚፈጽሙና በዜጎች ከፍተኛ ኢሰብዓዊ ድርጊት የሚፈጽሙ ኤጀንሲዎችም መኖራቸውን ማረጋገጡን ጠቅሶ በቀጣይ ምርመራውን በእነዚህ አካላት ላይም አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል። | 12 352 |
| 16 | بدون متن... | 12 552 |
| 17 | ነገ በአዲስ አበባ ሰላማዊ ሰልፍ ይደረጋል።
ሰልፉ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።
በትግራይ ክልል እየተባባሰ የመጣውን ቀውስ ለመቃወምና ለማስቆም በሚል እንዲሁም ለፌደራል መንግስትና ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ለማሳወቅ ''አፈሳ ይቁም ሰላም ይስፈን'' በሚል መሪ ቃል ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ/ም ከጥዋቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ በመስቀል አደባባይ ሰላማዊ ሰልፉ እንደሚደረግ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።
ሰልፉ ተጀምሮ እስከ ሚጠናቀቅበት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስዱ መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።
በዚህም መሰረት:-
#ከመገናኛ በ22 አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ ቅ/ዑራኤል አደባባይ
#በቦሌ መንገድ ወደ መስቀል አደባባ ኦሎምፒያ አደባባይ
#ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ
#ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ መስቀል ለገሀር መብራት
#ከለገሀር ቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታዲዮም ለገሀር ቴሌ ማቋረጫ
#ከአራት ኪሎ ወደ መሰቀል አደባባይ ብሔራዊ ቤተ-መንግስት
#ከካሳንቺስ በመቅረዝ ሆስፒታል ወደ መስቀል አደባባይ መቅረዝ ሆስፒታል አጠገብ
#ከአምባሳደር ቴአትር ወደ መሰቀል አደባባይ ሐራምቤ መብራት የሚወስዱ መንገዶች ከንጋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ መንገዶቹ ለተሽከርካሪ ዝግ ይሆናሉ።
ከዛሬ ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ በመስቀል አደባባይና በዙሪያው ባሉ መንገዶች ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ተሽከርካሪ ለአጭርም ሆነ ረዥም ሠዓት ማቆም የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል። | 11 243 |
| 18 | ከ1ሚሊየን ብር በላይ የሚገመቱ ንብረቶችን የሰረቀች የቤት ሰራተኛ በእስራት ተቀጣች፡፡
ተከሳሽ አለም ሲሳይ የስርቆት ወንጀሉን የፈፀመችው በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ልዩ ስሙ አትሌቶች መንደር ነው።
የቤት ሠራተኛዋ በተቀጠረች በ9ኛ ቀን የተለያዩ አልባሳት እና መዋቢያ ጌጣጌጦችን፣ 500 የአሜሪካን ዶላር ፣ የልዩ ልዩ ሀገራት ገንዘቦችን ውድ ጌጣጌጦች በአጠቃላይ 1 ሚሊየን 423 ሺ 192 ብር የሚያወጡ ንብረቶችን በመስረቅ ትሰወራለች።
ግለሰቧ ወንጀሉን ከፈፀመች በኋላ አድራሻዋን በመቀያየር ለመሰወር ብትሞክርም የጎሮ አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ገርጂ ላይ ከእነ ሰረቀችው ንብረት በቁጥጥር አውሏታል።
ፖሊስ መምሪያው ተገቢውን ምርመራ በማድረግ መዝገቡን ለአቃቢ ህግ ልኮ ክስ እንዲመሰረት አድርጓል።
የተከሳሽ አለም ሲሳይን ጉዳይ የተመለከተው የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለሚ ኩራ ምድብ ችሎት ተከሳሽን ያርማል ሌሎችን ያስተምራል በማለት ግለሰቧ በ5 ዓመት ከ10ወር ፅኑ እስራት እንድትቀጣ ወስኗል።
ለተከሳሿ የትራንስፖርት አገልግሎት በመስጠት እና የተወሰኑ ኤግዚቢቶችን በመሸሸግ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3B-95611 አ/አ አሽከርካሪን በፖሊስ ቁጥጥር ስር በማዋል የምርመራ መዝገብ አደራጅቶ በአቃቤ ህግ ክስ እንዲመሰረት አድርጓል፡፡
ግለሰቧ በተቀጠረች በ9ኛ ቀን ወንጀሉን የፈፀመች ሲሆን ተያዥ እንዳልነበራት ታውቋል።
ህብረተሰቡ የቤት ሰራተኛ ሆነ ማንኛውንም ዓይነት ቅጥር ሲፈፅም ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚባ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪ መልእክቱን አስተላልፏል። | 12 836 |
| 19 | አዲስ አስመጪዎችና ላኪዎች የብሔራዊ ባንክ የሂሳብ ቁጥርን በኤሌክትሮኒክ አንድ መስኮት አገልግሎት እንዲያገኙ ተወሰነ!
ብሔራዊ ባንክ የአስመጪና ላኪዎችን የሂሳብ ቁጥር አሰጣጥ በዲጂታል አዘምኗል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከጉምሩክ ኮሚሽን ጋር በመተባበር አዲስ ፈቃድ ላወጡ አስመጪና ላኪዎች የባንኩን የሂሳብ ቁጥር (NBE Account Number) በአንድ መስኮት የኤሌክትሮኒክ አገልግሎት (eSW) በኩል በቀላሉ ማግኘት የሚችሉበትን አሰራር ይፋ አደረገ።
ይህ አዲስ የዲጂታል አሰራር የአስተዳደር ውጣ ውረድን በመቀነስ የውጭ ንግድ እንቅስቃሴን ለማቀላጠፍ የተዘረጋ ሲሆን፣ አገልግሎቱ የሚመለከተውም ለመጀመሪያ ጊዜ የሂሳብ ቁጥር የሚያወጡ አዳዲስ የንግድ ተቋማትን ብቻ ነው።
ቀደም ሲል ቁጥሩ ያላቸው ነባር አስመጪና ላኪዎች በነባር አካውንታቸው መጠቀም እንደሚቀጥሉ ተገልጿል።
ይህ ማሻሻያ ብሔራዊ ባንኩ የገቢና ወጪ ንግድ አገልግሎቶችን ለማዘመን፣ የንግድ ከባቢውን ምቹ ለማድረግና የዲጂታል ህዝብ አገልግሎትን ለማጠናከር የጀመረው ቀጣይነት ያለው ጥረት አካል መሆኑ ተመልክቷል። | 12 370 |
| 20 | ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የገነባችው ግዙፍ የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ ሥራ ሊጀምር መሆኑን ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ!!
የወርቅ ግዥን ወደ ንግድ ባንኮች ለማዘዋወር ጥናት እየተደረገ ነው ተብሏል
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) የአገሪቱ የመጀመሪያው የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ፣ በመጪው አንድ ወር ውስጥ ተመርቆ ሥራ እንደሚጀምር አስታወቁ።
ገዥው ይህንን የገለጹት የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ በሰባተኛ ስብሰባው የገመገማቸውን የኢኮኖሚና የፋይናንስ ሁኔታዎች፣ ያቀረባቸውን ምክረ ሐሳቦችና የብሔራዊ ባንክ ቦርድ ያፀደቃቸውን የፖሊሲ ውሳኔዎች አስመልክቶ ሰኞ ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም. ለመገናኛ ብዙኃን ማብራሪያ ሲሰጡ ነው።
ከአፍሪካ አልፎ ከዚያ በላይ በግዙፍነቱ የሚጠቀስ የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ (ሪፋይነሪ) ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት እዮብ (ዶ/ር)፣ ፋብሪካው በመጪው አንድ ወር ውስጥ ተጠናቆ ወደ ሥራ ሲገባ፣ ለአገሪቱ የወርቅ ገበያ እጅግ ከፍተኛ አቅም እንደሚፈጥር አስረድተዋል።
የአገር ውስጥ የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ ወጪን በከፍተኛ ደረጃ ከመቀነሱም በላይ፣ ቀደም ሲል ወርቅ ወደ ውጭ በመላክ እንዲነጠር ተደርጎ ከዚያ በኋላ ለሌሎች ክምችት በዶላር የመሸጠን አሠራር ሙሉ ለሙሉ የሚያስቀር ነው ብለዋል። በመሆኑም ፋብሪካው ለኢትዮጵያ የወርቅ ገበያ ብቻ ሳይሆን ለአጠቃላይ ቀጣናው ትልቅ አቅም ሊሆን ይችላል ሲሉ ገልጸዋል።
ገዥው ይህንን ቢሉም ፋብሪካው የት አካባቢ እየተገነባ እንዳለና ሌሎች ዝርዝር ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ዘገባው የኢትዮጵያ ሪፖርተር ነው፣
https://ethiopianreporter.com/158211/ | 14 093 |
