cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ETHIO-MEREJA®

Addisababa, Ethiopia🇪🇹 News & Media Company® . USA : Washington . . . ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!! 👉 @ethio_merejabot

نمایش بیشتر
Advertising posts
132 655مشترکین
-324 ساعت
-87 روز
-3330 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

የአማራ ክልል መንግስት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ሀገሪቱን ና ሁለቱን ክልሎች ወደ ቀውስ ከሚያስገቡ ተግባራቶቹ እንዲቆጠብ አስጠነቀቀ። የአማራ ክልል መንግስት ዛሬ ባወጣው መግለጫ “የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በትናንትናው እለት ማለትም መጋቢት 18 ቀን 2016 ዓ.ም የራያ አላማጣ ወረዳ ቀበሌዎችን በመያዝ ነዋሪዎችን በመግደልና በማሰቃየት ላይ ይገኛል” ሲል ከሷል። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም ባወጣው መግለጫው፤ የአማራ ክልል መንግስት “የትግራይ መሬቶችን የግዛቱ አካል በማድረግ” በክልሉ ካርታ ላይ አስፍሯል፤ የትግራይ ክልል መሬቶች የሰፈሩበትን ካርታ በትምህርት ካሪኩለሙ በማካተት እያስተማረበት እንደሚገኝ ተረድቻለሁ” ማለቱ ይታወሳል። የአማራ ክልል መንግስት ይህንን ተከትሎ ባወጣው መግለጫ፤ “የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ባወጣው መግለጫ በተሳሳተ ካርታ ወደ አማራ ክልል ተካተዋል ያላቸውን አካባቢ ሕዝቦች ታሪካዊ እውነታን፣ ተጨባጭ ማስረጃዎችን እና ነባራዊ ሐቅን የካደ፣ አሳሳችና የጠብ አጫሪነት ፍላጎትን የተሸከመ መግለጫ ነው” ብሎታል። “የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የአማራ ክልል የተማሪዎች የመማሪያ መጻሕፍ ውስጥ የተሳሳተ ካርታ ተሰርቷል ሲል ባወጣው መግለጫ ሊያመላክታቸው የተፈለጉት አካባቢዎች ካለፉት 30 ዓመታት በፊት ጀምሮ የወልቃይት ጠገዴ፤ ጠለምት እንዲሁም የወፍላ ወረዳዎች እና የራያ የማንነት ጥያቄ ያለባቸው ወረዳዎች የማንነትና ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄዎችን ሲያቀርቡባቸው በነበሩ ቦታዎች ናቸው” ብሏል የአማራ ክልል በመግለጫው። “ህወሓት የሠሜን ዕዝ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትን አሰቃቂ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ የማንነትና የአስተዳደር ጥያቄዎቹ ለዘመናት የታፈኑበት ሕዝብ ከማዕከላዊው መንግስት ጎን ተሰልፎ የበኩሉን አስተዋጽዖ ከማበርከቱ ባሻገር በሂደቱ ህወሓት በኃይል ተገፍፎባቸው የነበረውን የማንነትና ጥያቄና ራስን በራስ የማስተዳደር ነጻነት የተቀዳጁበት ሁኔታ ተፈጥሯል” ብሏል የአማራ ክልል መንግስት። የአማራ ክልል በመግለጫው “የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ መጋቢት 16 ቀን 2016 ዓ.ም ከመማሪያ መጽሃፍ ካርታ ጋር በተያያዘ በአማራ ክልል ላይ ጥቃት ከመፈጸም የማይመለስ መሆኑን የሚገልጽ የጠብ አጫሪ መግለጫ ማውጣቱ ካለፉት ድርብርብ ውድቀቶች ትምህርት አለመውሰድን ከማሳየት የዘለለ ፋይዳ አይኖረውም” ብሏል። የተፈጠሩ ችግሮችን በህግ አግባብ እንዲፈታ እተደረገ ያለውን ጥረት የአማራ ክልል መንግስት የራሱን ድርሻ እየተወጣ ባለበት ሁኔታ በህዝብ መጎሳቆልና በወጣቶች እልቂት ትምህርት አለመወሰዱና የተለመደ ትንኮሳ በማድረግ ላይ መሆኑ እንዳሳዘነውም ገልጿል። የትግራይ ክልል ግዜያዊ አስተዳደር ለሀገሪቱ ቋሚ ቀውስ ምንጭ ከሚያደርጉት ተግባራት እንዲታቀብ፣ ሀገራችንንና ሁለቱን ክልሎች ወደ ቀውስ ከሚያስገቡ ተግባራት እንዲቆጠብም የአማራ ክልል መንግስትአስጠንቅቋል።እንዲሁም ጊዚያዊ አስተዳደሩ ከለመደው አጓጉል የካርታ ፖለቲካ ጨዋታ እንዲወጣና የህዝብን ፍላጎት ማዕከል ባደረጉ ውይይቶች ላይ እንዲያተኩር መክሯል። የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ የአማራ ክልል በመማሪያ መጽሐፍት ላይ ያውጣው የተሳሳተ ካርታ ላይ በአስቸኳይ ማስተካከያ እንዲያደርግ በመግለጫው አስተጠንቅቆ ነበር።ይህ የማይሆን ከሆነ ግን “ይህን ተከትሎ ለሚመጣው ነገር ሁሉ ሃላፊነቱን የሚወስደው የአማራ ክልል መሆኑን ልናሳውቅ እንወዳለን” ብሏል።
نمایش همه...
👍 7 7👎 1
የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማት ፕሮጀክት “ዲሞግራፊ ለመቀየር” የሚካሄድ አይደለም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስተባበሉ!! በአዲስ አበባ ከተማ እየተከናወነ የሚገኘው የመንገድ እና አካባቢ ልማት ፕሮጀክት፤ “ዲሞግራፊ ለመቀየር” አሊያም “ኦሮሞዎችን ወደ ከተማ ለመመለስ ነው” የሚሉ ወገኖችን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተችተዋል። አዲስ አበባ ውስጥ “ከበቂ በላይ” የኦሮሞ እና የሌሎች ብሔር ተወላጆች መኖራቸውን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “የሌለ ሰው ኖሮ፤ ሰው ለማምጣት የምንቸገርበት አይደለም” ሲሉም አስተባብለዋል።ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ይህን ያሉት የአዲስ አበባ ከተማ የኮሪደር ልማት ስራን ከሚያስፈጽሙ አመራሮች እና የስራ ኃላፊዎች ጋር ትላንት ረቡዕ መጋቢት 18፤ 2016 ባደረጉት ውይይት ነው። እርሳቸው የሚመሩት መንግስት ከዚህ ቀደም ባከናወናቸው የግንባታ ስራዎች “ብዙ ስሞታዎች ነበሩ” ያሉት አብይ፤ ለዚህም የምኒልክ ቤተ መንግስት እና የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት እድሳትን በምሳሌነት አንስተዋል።  “ይሄ ግቢ ሲቀየር ሀገራዊ ፖለቲካ ነበር። የእዚህን ግቢ እድሳትን እና ዩኒቲ ፓርክን ለመቃወም ሰዎች በጣም ብዙ ደክመዋል። በኋላ [የአዲስ አበባ ከተማ] ማዘጋጃ ቤት ሲጠናቀቅ፤ ‘ለምን ተሰራ’ ተብሎ ብዙ ተብሏል። አሁንም ብዙ አሉባልታዎች፤ ብዙ ወሬዎች ይሰማሉ። ‘ዲሞግራፊ ለመቀየር ነው’፤ ‘ኦሮሞዎች ለመመለስ ነው’ [የሚሉ] የተለያዩ ስሞች ይሰጣሉ” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። አብይ መንግስታቸው የአዲስ አበባ ከተማን “ዲሞግራፊ” የመቀየር እቅድ እንደሌለው ያስረዱት፤ የትውልድ ስፍራቸው የሆነችውን የበሻሻ ከተማ በምሳሌነት በመጥቀስ ነው። “ ‘ዲሞግራፊ መቀየር’ የሚባል ነገር የሚመጣው፤ በሻሻ ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች ቋሚ ሰዎች የነበሩ ሆነው፤ ሰዎች ከጅማ፣ ከአጋሮ ከመጡ፤ በሻሻ እንዲገቡ እና እንዲቀላቀሉ ሲፈለግ የሚሰራ ስራ ነው” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህንን ከአዲስ አበባ ከተማ ሁኔታ ጋር አነጻጽረዋል።  “አዲስ አበባ ውስጥ፤ ከበቂ በላይ ኦሮሞ፣ አማራ፣ ጉራጌ፣ ትግሬ፣ ከበቂ በላይ ሁሉም አለበት። የሁለት፣ ሶስት ሚሊዮን ከተማ እኮ አምስት፣ ስድስት [ሚሊዮን] ገባ። የሌለ ሰው ኖሮ፤ ሰው ለማምጣት የምንቸገርበት አይደለም። አዲስ አበባስ የማን ከተማ ሆና ነው፤ ማን ዲሞግራፊ የሚሰቃይባት? አይገባኝም” ሲሉም ተደምጠዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። የአዲስ አበባ የመንገድ ኮሪደር ልማት ዓላማ ከተማይቱ “ የሁሉም እና ውብ” እንድትሆን ማድረግ መሆኑን የጠቀሱት አብይ፤ ከ“ዲሞግራፊ መቀየር” ጋር ተያይዞ የሚሰሙ አስተያየቶችን “ወሬ እና አሉባልታ” ሲሉ አጣጥለዋቸዋል። “ይሄ ወሬ እና አሉባልታ የሚፈርሰው፤ በተግባር ሰርተን ስናሳይ ነው። ከተግባር ውጭ ይህንን ወሬ ሊያፈርስ የሚችል የለም” ያሉት አብይ፤ ፕሮጀክቱ “ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ” የሚተገበር ከሆነ “ሰው ለመገንዘብ አይቸገርም” ሲሉ አጽንኦት ሰጥተዋል። የአዲስ አበባን “አጠቃላይ የመንገድ ሽፋን እና ዘመናዊነት እንዲሁም የትራንስፖርት ፍሰት ወደ ላቀ ደረጃ ሊያሳድግ የሚችል” የተባለለት “የመንገድ ኮሪደር ልማት”፤ በከተማዋ ካቢኔ የጸደቀው ከአንድ ወር በፊት የካቲት 15፤ 2016 ነበር። በዚህ ፕሮጀክት እንዲለሙ ዕቅድ የተያዘላቸው የመንገድ ኮሪደሮች፤ ዓለም አቀፍ “የስማርት ሲቲ” ስታንዳርድን በማሟላት የአዲስ አበባ ከተማን ደረጃ “ከፍ የሚያደርጉ ናቸው” ሲል የከተማይቱ አስተዳደር ከዚህ ቀደም ባወጣው መግለጫ ማስታወቁ አይዘነጋም። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)  
نمایش همه...
👎 35👍 18
Do you enjoy reading this channel? Perhaps you have thought about placing ads on it? To do this, follow three simple steps: 1) Sign up: https://telega.io/c/ethio_mereja 2) Top up the balance in a convenient way 3) Create an advertising post If the topic of your post fits our channel, we will publish it with pleasure.
نمایش همه...
👍 3🥰 2
Come to my channel  link👇👇👇 https://tglink.io/d21fe0ea6c3d
نمایش همه...
👍 9 1
#ጤናመረጃ ፓፓያ ለጤናችን የሚሰጠን 10 አስደናቂ ጥቅሞች! 1) ፓፓያ በሆድ ውስጥ የሚገኙ ትላትሎችን ለማጥፋት እና የጨጓራን አሲድነት ይቀንሳል፡፡ 2) የፓፓያ ጁስ መጠጣትን ልምድ ማድረግ በአንጀት ውስጥ የሚፈጠርን ኢንፌክሽን እና ጎጂ ፈሳሽ ጠርጎ ያወጣል፡፡ የምግብ መፈጨት ሂደትን በማገዝ ብሎም የአንጀት ካንሰር የመከሰት እድልን ይቀንሳል፡፡ 3) ዝቅተኛ የካሎሪ እና ከፍተኛ የጠቃሚ ምግብ ይዘት ስላለው በውፍረት መቀነስ ሂደት ውስጥ ላሉ ሰዎች አስተዋጽዖው የላቀ ነው፡፡ 4) የጸረ ካንሰርና የሰውነት መቆጣትን የሚቀንስ ባህሪ አለው፡፡ ይህ የሰውነት መቆጣትን የሚቀንስ ባህሪ በማንኛውም የሰውነታችን መገጣጠሚያ ላይ ለሚደርስ ህመምና የአጥንት መሳሳት ለመቀነስ ይረዳል፡፡ 5) ፎረፎርን በመከላከል ጤናማ ጸጉር እንዲኖረን ስለሚያግዝ በተጨማሪ ከፓፓያ የተሰሩ የጸጉር ማስዋቢያ ምርቶችን መጠቀም ይመረጣል፡፡ 6) ካለ እድሜ የሚመጣን የቆዳ መሸብሸብን ይከላከላል፡፡ ፓፓያን በቀጥታ ቆዳዎን በመቀባት ወይም በመመገብ የሚያምር ለስላሳ ቆዳን መጎናፀፍ ይቻላሉ፡፡ የተፈጨ ፓፓያ የተሰነጣጠቀ ተረከዝን ለማከም ይጠቅማል፡፡ 7) የሞቱ የቆዳ ሴሎችን ለማስወገድ ይረዳል፣ የቆዳ ድርቀትን ይከላከላል፡፡ ጥሬ ፓፓያ ፊትዎን ለ25 ደቂቃ በመቀባት ፊት ላይ የሚገኙ ጥቃቅን ያበጡ ነጠብጣቦችን በቀላሉ ማስወገድ ይችላሉ፡፡ 8) ፓፓያ አርጀኒን የተባለን ንጥረ ነገር ሲኖረው ይህም የወንድ ልጅን መሀንነት ይከላከላል፡፡ 9) በቫይታሚን ኤ’ ሲ እና ኢ የበለጸገ በመሆኑ የኮሌስትሮል መጠንን ለመቀነስ በተጨማሪም የልብ ህመምን ይከላከላል፡፡ 10) ራሰ በራነትን ይከላከላል፣ የፀጉር እድገትንና ጥንካሬን ይጨምራል፡፡ ጠቃሚ ነውና ለወዳጆ ያካፍሉ! ሼር! T.me/ethio_mereja
نمایش همه...
👍 66 31👏 7👌 3
የ5 አመቷን ታዳጊ የደፈረው ላይ የ6 ወር እስራት የፈረደው ዳኛ ከስራና ከደመወዝ ታገደ። አቶ ሀብታሙ ሙሉነህ ለወንበራ ወረዳ ፍ/ቤት ዳኛ በወንጀል መዝገብ ቁጥር 8429 ተከሳሽ ተክለአብ ገላታ የወንጀል ህግ ቁጥር 622 ድንጋጌን በመተላለፍ የአምስት አመት ህጻን ልጅ አስገድዶ ድፍረት በደል ወንጀል ተከስዉ ጉዳዩን ሲዳኝ የነበረ ሲሆን ተከሳሽን በቀረበበት ክስ ጥፋተኛ ካልክ በኃላ ቅጣቱን 6 ወር ቀላል እስራት በማለት ወስናሀል ይህ ዉሳኔ ለህጻናት መብት ፍ/ቤቱ ትኩረት ሰጥቶ እንዳልሰራና የመንግስትና የህዝብን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥል ዉሳኔ እንደሆነ በሰፊዉ አቤቱታዎች እየቀረቡ ስለሆነ ዉሳኔ ሰጪ ዳኛ በምን ምክንያት ይህን ዉሳኔ እንደሰጠ ማጣርት እና ማስተካከያ እርምጃ መዉሰድ እንደ ተቋም ስለሚያስፈልግ መተከል ዞን ከፍ/ፍ/ቤት ኮሚቴ በመላክ ጉዳዩን በአስቸካይ አጣርቶ እንዲልክልን ሆኖ እስከዛ ድረስ ይህ ዳኛ ስራዉን እየሰራ ይቀጥል ቢባል ሌላ በደል ሊያደርስ ይችላል የሚል እምነት ስላለን ሌላ ተለዋጭ ትእዛዝ እስከሚደርስ ድረስ ዳኛዉ ከስራ እና ከደመወዝ ታግዶ እንዲቆይ ሲል በቤኒሻንጉል-ጉሙዝ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውሳኔ መስጠቱን ከላይ የተያያዘው ደብዳቤ ያመለክታል።
نمایش همه...
👍 152 19👏 1
🪟ዋው የሚያስብሉ የግድግዳ ምስሎች😍 👉Shine laminated(የሚያብረቀርቅ)ናቸው። 👉በውሀ የሚፀዳ እና HD ማራኪ ናቸው! 👉በቀላሉ ባለው ማንጠልጠያ ሚሰቀል!!      በትዛዝ በ3ቀን እናደርሳለን።   ዋጋ :-  1.50*80 - 3500ብር   ዋጋ :-  1.20*60 - 3000ብር 📍አድራሻ 4killo/ቀበና #ቤሊየር አልዘይን ህንፃ 207ቁ      ☎️ 0901882392 /      ☎️ 0931448106 ተጨማሪ T.me/Dinkwallarts ✅ON HAND - የጌታ እራት አለ።
نمایش همه...
👍 10 2
ሰበር ዜና!! የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ዳግም በሶማሊያ አየር ላይ ከመጋጨት ለጥቂት መትረፉ ተነገረ የኢትዮጵያ እና የኤምሬትስ አየር መንገድ አውሮፕላኖች በሶማሊያ አየር ላይ ከመጋጨት ለጥቂት መትረፋቸው ተነገረ። ነጻ አገርነቷን ያወጀችው የሶማሊላንድ ሲቪል አቪዬሽን እና ኤርፖርቶች ባለሥልጣን ሁለቱ አውሮፕላኖች አየር ላይ ሊጋጩ ተቃርበው የነበረው በሶማሊያ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች "አሻሚ እና የተሳሳተ" ትዕዛዝ ነው ብሏል። እንደ ባለሥልጣኑ መግለጫ፤ እሁድ መጋቢት 15/2016 ዓ.ም. ምሽት ላይ በሶማሊያ የአየር ክልል ውስጥ ሲበሩ የነበሩት አውሮፕላኖች ከመጋጨት የተረፉት የሶማሊላንድ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ አብራሪዎች በወሰዱት “ፈጣን እና ትክክለኛ እርምጃ” ነው። የበረራ መቆጣጠሪያ ድረ-ገጽ በሆነው ፍላይትራዳር24 ላይ መመልከት እንደሚቻለው ክስተቱ ባጋጠመበት ወቅት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን እና የኤምሬትሱ ቦይንግ 777 አውሮፕላን በ37ሺህ ጫማ ከፍታ ላይ ሲበሩ ነበር። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የበረራ ቁጥር ኢቲ690 በሶማሊያ የአየር ክልል ሲበር ከነበረበት 37ሺህ ጫማ ምሽት 21፡43 (ሌሊት 6፡43) ሲል በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ከፍታውን በፍጥነት ጨምሮ ወደ 39ሺህ ጫማ ከፍ አድርጓል። በዚህም ምክንያት በሁለቱ የመንገደኞች አውሮፕላኖች መካከል ሊከሰት ይችል የነበረን አሰቃቂ አደጋ ለማስቀረት ችሏል ሲል ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል። በቅርቡ በተመሳሳይ መልኩ የኳታር አየር መንገድ አውሮፕላን ከፍታውን እንዲጨምር በሞቃዲሾ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች ከተነገረው በኋላ ከኢትዮጵያ አውሮፕላን ጋር ለመጋጨት ተቃርቦ እንደነበረ መዘገቡ ይታወሳል።
نمایش همه...
👍 74 10👌 2
አዲስ አበባና አቅራቢያ ለምትገኙ በሙሉ!! የTiktokና የOnline እቃዎችን ከኛ ያገኛሉ! እቃዎቹን ለማየት አሁኑኑ ከታች👇 ይጫኑ! https://telegram.me/AddisEka1 https://telegram.me/AddisEka1 https://telegram.me/AddisEka1 https://telegram.me/AddisEka1 ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉ! በቅናሽ ይሸምቱ! 💯High Quality  💯Big Discount      #Amazon_Ethiopia_2023
نمایش همه...
አዲስ እቃ | Addis Eka

በቴሌግራም እዚህ ይቀላቀሉን! 0931448106 🌺AMAZON - ETHIOPIA🌺 ቤትዎን የሚያዘምኑ ምርጥ እቃዎችን ይዘንላችሁ መጥተናል። አድራሻ:- ከ4ኪሎ-መገናኛ መንገድ ቤሊየር(ሜዳ) ጋር አቤኔዘር ፊትለፊት አዲሱ፣ አል-ዘይን ህንፃ 2ኛ ፎቅ 207ቁ በአጭሩ አቧሬ መታጠፊያ መብራቱ ጋር! Contact us - @HabeshaStorechat 👉 👉0901882392 👉👉 0931448106

👍 11 2👏 1
وارد شوید و به اطلاعات مفصل دسترسی پیدا کنید

ما این گنجینه ها را پس از تأیید هویت به شما نشان خواهیم داد. ما وعده می‌دهیم که سریع است!