ETHIO-MEREJA®
News & Media Channel® Addisababa, Ethiopia🇪🇹 ውድ የኢትዮ መረጃ ቤተሰቦች ከዚህ የቴሌግራም ቻናል ውጪ ሌላ መረጃ የምናቀርብበት ምንም አይነት የዩቲዩብ፣ የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆች እንደሌለን ለማሳወቅ እንወዳለን፣ ስለሆነም በተመሳሳይ ስም በተከፈቱ ገፆች እንዳይሸወዱ ጥንቃቄ እንድታደርጉ እናሳስባለን። ለጥቆማና ማስታወቂያ ለማሰራት 👉 @ethio_merejabot
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ETHIO-MEREJA®
کانال ETHIO-MEREJA® (@ethio_mereja) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 102 836 مشترک است و جایگاه 2 497 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 287 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 102 836 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 10 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -1 869 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -60 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 21.46% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.09% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 22 072 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 9 347 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 67 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“News & Media Channel®
Addisababa, Ethiopia🇪🇹
ውድ የኢትዮ መረጃ ቤተሰቦች ከዚህ የቴሌግራም ቻናል ውጪ ሌላ መረጃ የምናቀርብበት ምንም አይነት የዩቲዩብ፣ የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆች እንደሌለን ለማሳወቅ እንወዳለን፣ ስለሆነም በተመሳሳይ ስም በተከፈቱ ገፆች እንዳይሸወዱ ጥንቃቄ እንድታደርጉ እናሳስባለን።
ለጥቆማና ማስታወቂያ ለማሰራት
👉 @ethio_mere...”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 11 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 11 ژوئن | 0 | |||
| 10 ژوئن | 0 | |||
| 09 ژوئن | 0 | |||
| 08 ژوئن | 0 | |||
| 07 ژوئن | 0 | |||
| 06 ژوئن | 0 | |||
| 05 ژوئن | 0 | |||
| 04 ژوئن | 0 | |||
| 03 ژوئن | 0 | |||
| 02 ژوئن | 0 | |||
| 01 ژوئن | 0 |
| 2 | በአርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ የደረሰውን የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች በተመለከተ ኢሰመኮ የሰጠው መግለጫ!!
መንግሥት ተገቢውን ምርመራ በማካሄድ ተጠያቂነትን የማረጋገጥ እና ተጎጂዎችን ለመካስና ለማቋቋም የሚያስችሉ እርምጃዎችን ሊወስድ ይገባል
. . . . .
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ግንቦት 23 እና 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተፈጸመውን ጥቃት በተመለከተ ክትትል እና ምርመራ እያከናወነ ይገኛል፡፡ ኢሰመኮ ይህ መግለጫ ይፋ እስከተደረገበት ጊዜ ድረስ በአካባቢው በአካል በመገኘት ከዐይን እማኞች፣ ከተጎጂዎች፣ ከተጎጂ ቤተሰቦች፣ እና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ባሰባሰባቸው መረጃዎችና ማስረጃዎች ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው “በተለምዶ ኦነግ ሸኔ” ታጣቂ ቡድን በፈጸመው ጥቃት የመንግሥት የጸጥታ ኃይል አባላትና ሲቪል ሰዎች መገደላቸውን፣ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን፣ የንብረት ውድመት እና ቃጠሎ መድረሱን ለማረጋገጥ ችሏል።
ኢሰመኮ በምርመራ ሂደቱ እንዳረጋገጠው በአሰኮ ወረዳ ደለተ ጫፋ ቀበሌ አካባቢ ከግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ የታጣቂዎች እንቅስቃሴ በመስተዋሉ የአካባቢው ሚሊሻዎችና የኦሮሚያ ጸረ ሽምቅ ውጊያ ፖሊስ አባላት በስፍራው በመሰማራታቸው “በተለምዶ ኦነግ ሸኔ” ተብሎ በሚጠራው ታጣቂ ቡድን እና በተሰማሩ የጸጥታ አካላት መካከል ግጭት ተፈጥሯል። ግጭቱን ተከትሎ የአካባቢው ነዋሪ የሆኑ ሰዎች ላይ ታጣቂ ቡድኑ ባደረሰው ጥቃት ከአካባቢው መሸሽ ባልቻሉ ኃይሉ ንጉሴ እና ሰሙ አባይነህ በተባሉ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንዲሁም በአካባቢው ከብቶች በመጠበቅ ላይ የነበረ ባቶ ሰፈኖ የተባለ የእስልምና እምነት ተከታይ በአጠቃላይ የሦስት ሲቪል ሰዎች ሕይወት ሊያልፍ ችሏል።
በተጨማሪም ቁጥራቸው ለጊዜው በውል ባልታወቁ ቤቶች ላይ ቃጠሎ መድረሱን፣ የጠለታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን መቃጠሉን፤ ቢዮ ቡጡሌ የሼክ ሙስተፋ መስጅድ አጥር ላይ ጉዳት መድረሱን፣ በድለተ ጫፋ ጤና ጣቢያ፣ በነዋሪዎች መኖሪያ ቤቶችና የንግድ መደብሮች ላይ በመደዳ ዘረፋ መፈጸሙን እንዲሁም ከ2,650 በላይ የሚገመቱ የአካባቢው ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ኢሰመኮ አረጋግጧል።
ኢሰመኮ በአርሲ ዞን በሽርካ፣ በአሰኮ፣ በአንቆሎ ዋቤ፣ ጉና እና መርቲ ወረዳዎች ላይ በታጣቂዎቹ ሲፈጸሙ የነበሩ ጥቃቶች ዳግም እንዳይከሰቱ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደረግ እና ጥቃት ፈጻሚዎች ላይ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ በተለያዩ ጊዜያት ማሳሰቡ ይታወሳል። መንግሥት በአካባቢው ላይ በተደጋጋሚ መሰል ጥቃቶች እና የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች መከሰት መቀጠላቸው አሳሳቢ መሆኑን ከግምት በማስገባት ጥቃት በተፈጸመባቸው አካባቢዎች የጀመራቸውን ጥረቶች በማጠናከር በአስቸኳይ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እንዲሰማሩ እና ሰላምና ደኅንነትን በማረጋገጥ ነዋሪዎችን ወደ ተረጋጋ ሕይወት የመመለስ ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም በመንግሥትና በሌሎች አጋር አካላት በጥቃቶቹ ምክንያት ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ነዋሪዎች በቂ የሆነ የአስቸኳይ የሰብአዊ ድጋፍ እንዲቀርብና ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው ተመልሰው በዘላቂነት የሚቋቋሙበት ሁኔታ እንዲመቻች ኢሰመኮ ያሳስባል። በሌላ በኩል ኢሰመኮ ጉዳዩን አስመልክቶ ዝርዝር የምርመራ ሪፖርት ይፋ የሚያደርግ መሆኑን እየገለጸ፤ የተፈጸሙ ጥቃቶችን በአግባቡ ሳያረጋግጡ የሚሰነዘሩ ፍረጃዎችና ቅስቀሳዎች ተጨማሪ ግጭት እንዲፈጠር የማነሳሳት ዕድላቸው ሰፊ በመሆኑ ማናቸውም ተቋማትም ሆኑ ግለሰቦች ከዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ጥሪ ያቀርባል።
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ ኢሰመኮ በዜጎች ላይ ለደረሰው ሞትና ጉዳት ማዘኑን ገልጸው በሲቪል ሰዎች ላይ የተፈጸሙት የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች አሳሳቢ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ አክለውም መንግሥት ሁኔታውን ለማረጋጋት እና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ ያከናወናቸው ተግባራት መቀጠል ያለባቸው መሆኑን ጠቅሰው፤ በማንኛውም ጊዜ የጸጥታ ሥጋት ባለባቸው አካባቢዎች ሁሉ በቂ የጸጥታ ኃይሎች በመመደብና ተመሳሳይ ጥቃቶችን የመከላከል ሥራ በመሥራት የነዋሪዎች በሕይወት የመኖር፣ የአካል ደኅንነት እና የንብረት መብቶች ለአደጋ እንዳይጋለጡ እንዲያደርግ፣ ተገቢውን ምርመራ በማካሄድ ተጠያቂነትን የማረጋገጥ እና ተጎጂዎችን ለመካስና ለማቋቋም የሚያስችሉ እርምጃዎችን እንዲወስድ እንዲሁም ሁሉም አካላት የተፈጠሩ ችግሮችን ከማውገዝ ባሻገር ግጭት ቀስቃሽ ከሆኑ መግለጫዎች እና ድርጊቶች እንዲታቀቡ ጥሪ አቅርበዋል። | 14 440 |
| 3 | بدون متن... | 13 301 |
| 4 | ሰላም የአዲስ ላይፍ ቤተሰቦች እስካሁን በ3ቱ ጵሮጀክቶች የሰጣችሁንን እምነት ይዘን ፣ አዲስና እጅግ ዘመናዊ የሆነዉን 4ተኛዉን ጵሮጀክታችንን በቡልጋሪያ ይዘንላቹ መምጣታችንን ስንገልፅ በታላቅ ደስታ ነዉ።
ታዲያ ይህን ድንቅ ኪነ ህንፃ ላይ ለመኖር ቀድሞ ለወሰነ ደንበኛ የቅድመ ጵርጀክት ማሰጀመሪያ ልዩ ጥቅምን አዘጋጅተን በካሬ ከ80,750ጀምሮ እየሸጥን እንገኛለን።
ልብ ይበሉ አዲስ ላይፍ ሰርቶ በማሰረከብ እና በግንባታ ጥራት የማይታማ ድርጅት መሆኑን ሳይዘነጉ ይህን እድል አሁኑኑ ይጠቀሙ።
ለበለጠ መረጃ በ0937867901
ይደዉሉ። | 21 773 |
| 5 | ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናችን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት እንደሚከተለው ነው፦
መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።››
(መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪)
በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው።
የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል።
በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።
በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት | 22 769 |
| 6 | بدون متن... | 20 386 |
| 7 | የምርጫ ውጤት መቼ ይፋ ይሆናል ?
በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የተረጋገጠ የመጨረሻ ውጤት ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ ይፋ እንደሚደረግ አርትስ ቴሌቪዥን ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሠሌዳ ተመልክቷል።
በዚህም መሠረት የሂደቱ አፈጻጸም በሚከተለው መልኩ ይከናወናል፦
✔️ጊዜያዊ ውጤቶች በምርጫ ጣቢያዎች፡ ከዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያዎቹ የጊዜያዊ ውጤቶች በይፋ ተለጥፈው ለሕዝብ ይፋ ይደረጋሉ።
✔️የምርጫ ክልል ጊዜያዊ ውጤቶች፡ ከግንቦት 25 እስከ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ በምርጫ ክልሎች ደረጃ ጊዜያዊ ውጤቶች ይፋ ይደረጋሉ።
✔️የውጤት መረከብ ሂደት፡ ምርጫ ቦርድ ከምርጫ ክልሎች ውጤቶችን የመረከብና የመገምገም ሥራውን ከግንቦት 26 እስከ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ያከናውናል።
✔️የመጨረሻ ውጤት፡ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የተረጋገጠ የመጨረሻ ውጤት ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ በይፋ ይገለጻል።
✔️ቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜ፡ ከምርጫው ዕለት (ግንቦት 24) ጀምሮ እስከ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ ማንኛውም የምርጫ ቅሬታዎች ተቀባይነት አግኝተው በቦርዱ ምላሽ ይሰጥባቸዋል።
የምርጫ ቦርድ ይህን የውጤት አሰጣጥ ሂደት በታቀደው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት በግልጽነትና በታማኝነት ለማከናወን ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል። | 22 852 |
| 8 | በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ከ10 በላይ ኦርቶዶክሳውያን ሲገደሉ የ101 ዓመት እድሜ ያለው የቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወድሟል።
የመድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይም ዘረፋ የተካሄደ ሲሆን ምእመናን ጽላቱን ይዘው ተሰደዋል፤ መኖሪያ ቤታቸውም ተቃጥሏል።
ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት፣ አሰኮ ወረዳ፣ ጠላታ ጨፋ ቀበሌ እና ካራ ኩፍቴና በሚባሉ አካባቢዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ ያነጣጠረ አሰቃቂ ግድያ ተፈጽሟል።
በአሰኮ ወረዳ ጠላታ ጨፋ ቀበሌ ብቻ በታጣቂ ኃይሎች በተፈጸመ ሰብአዊነት በጎደለው ጥቃት ከ10 በላይ ንጹሃን ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል።
በአካባቢው 101 ዓመታትን ዕድሜ ያስቆጠረው፣ የጠላታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወውደሙ ተገልጿል።
በተመሳሳይ ጥቃት በካራ ኩፍቴና መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ላይ ጥቃት የተሰነዘረ ሲሆን፣ የቤተክርስቲያኑ ንብረት የሆኑ ቤቶች በመቃጠላቸው ምእመናን የመድኃኔዓለምን ቅዱስ ጽላት ይዘው በእግራቸው ወደሌላ አካባቢ መሸሻቸው ታውቋል።
በዚሁ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በሺርካ ወረዳ በሁለት ወጣት ኦርቶዶክሳውያን ላይ ዘግናኝ ግድያ መፈጸሙ ተሰምቷል።
ድርጊቱ የተፈጸመው ሚታና ዋጂ ቀበሌ ሲሆን፣ ታጣቂዎች ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ ወጣቶቹ መኖሪያ ቤት በመግባት በቁጥጥር ስር እንዳዋሏቸውና በመቀጠልም ወጣቶቹን ወደ ሚታና ጋዶ ቀበሌ በመውሰድ፣ አንደኛውን በስለት አር ደው፣ ሁለተኛውን ደግሞ በጥይት በመምታት በጭካኔ ሕይወታቸውን እንዳጠፉት ተገልጿል።
ሕይወታቸውን ያጡት የእነዚህ ወጣቶች ሥርዓተ ቀብር ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በጋዶ ማሕደረ ስብሐት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን፣ ምዕመናንና በቤተሰብ በተገኘበት በአንድ መቃብር ተፈጽሟል።
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በአገልጋዮችና ምእመናን ላይ በተደጋጋሚ ጥቃት እንደሚፈጸምበት ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ለዓመታት መረጃ እያደረሰ ቢሆንም ዛሬም ድረስ ዘላቂ መፍትሔ አልተገኘም።
መረጃው የማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ነው። | 16 645 |
| 9 | بدون متن... | 17 658 |
| 10 | የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ውጤታማ ሆኖ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ከማለዳው 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ድምፃቸውን መስጠታቸውን ገልጸዋል።
እስከ እኩለ ሌሊት የቀጠለው የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል።
የድምፅ ቆጠራ ሂደቱ ታዛቢዎችና የፓርቲ ተወካዮች በተገኙበት እየተከናወነ መሆኑን የገለፁ ሲሆን የድምፅ ቆጠራው ተጠናቆ ውጤቱ ይፋ እንደሚሆን አመላክተዋል።
በዛሬው ዕለት በተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፤ እስከ ምሽቱ ሁለት ሰዓት ድረስ 40 ሚሊዮን መራጮች ድምጽ መስጠታቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ተናግረዋል። የምርጫ ውጤት ቆጠራ ዛሬ በማይጠናቀቅባቸው ቦታዎች፤ በነገው ዕለት እንደሚከናወንም ሰብሳቢዋ ገልጸዋል።
ሜላትወርቅ ይህን የገለጹት ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24፤ 2018 ሲካሄድ የዋለውን ምርጫ መጠቃለል በተመለከተ ለሊት ሰባት ሰዓት ገደማ በሰጡት መግለጫ ነው። የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ በዚሁ መግለጫቸው በጸጥታ ችግር ምክንያት ምርጫ ስላልተካሄደባቸው እና ስለተቋረጠባቸው አካባቢዎች በቅድሚያ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ዋና ሰብሳቢዋ ዛሬ እኩለ ቀን ገደማ በሰጡት መግለጫ በ143 የምርጫ ጣቢያዎች፤ በጸጥታ ችግር ምክንያት የድምጽ መስጠት ሂደቱ አለመካሄዱን ገልጸው ነበር።
በአማራ ክልል በሚገኘው የኩታ በር ምርጫ ክልል በሚገኙ አራት የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ምርጫ ሳይከናወን መቅረቱንም ተናግረዋል። በመኮሳቺ እና ቀርሳ ምርጫ ክልል ያለው የጸጥታ ሁኔታ ባለመሻሻሉ በተመሳሳይ ሁኔታ የድምጽ መስጠት ሂደቱ አለመካሄዱን አብራርተዋል። | 17 861 |
| 11 | አሜሪካ በኢራን ላይ አዲስ የአየር ጥቃት ፈፀመች
አሜሪካ በደቡባዊ ኢራን በሚገኙ የኢራን የሚሳኤል ቤዞች እና ፈንጅ ሲቀብሩ ነበር ባለቻቸው ጀልባዎች ላይ የአየር ጥቃት ፈፅማለች፡፡
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንትኮም) እንዳስታወቀው፥ ጥቃቱ በአካባቢው የሚገኙ የአሜሪካ ወታደሮችን ከጥቃት ለመከላከል የተደረገ እና የኢራንን ወታደራዊ ጫና ለመቀነስ ያለመ ነው።
በአሜሪካ እና ኢራን መካከል ያለውን ጦርነት ለማቆም ስምምነት ለማድረግ ድርድር እየተደረገ መሆኑን የገለፀው የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ከስምምነት እስከሚደረስ የአሜሪካ ወታደራዊ ሃይል በሆርሙዝ ሰርጥ የጣለውን ክልከላ አጠናክሮ ይቀጥላል ብሏል።
እስካሁን የአሜሪካን የአየር ጥቃት አስመልክቶ ኢራን የሰጠችው ይፋዊ ምላሽ የለም።
ይሁን እንጂ የኢራን መገናኛ ብዙኃን በሆርሙዝ ሰርጥ አቅራቢያ በምትገኘው የባንደር አባስ ከተማ ፍንዳታ መሰማቱን እና የፍንዳታው ምንጭ እየተጣራ መሆኑን ዘግበዋል፡፡
ጥቃቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል እየተካሄደ የሚገኘውን ድርድር ተፅዕኖ ውስጥ ሊከተው እንደሚችል ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
ጥቃቱ ከተፈፀመ በኋላ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ አሁንም ድርድሩ እንደሚቀጥል ጠቁመው፥ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በዛሬው እለት የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ከኳታሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ገልጸዋል። | 29 428 |
| 12 | የአውሮፓ ህብረት ከ2 ዓመት በፊት በኢትዮጵያ ላይ ጥሎት የነበረውን የቪዛ ገደብ አነሳ
የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ከሁለት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ላይ ጥሎት የነበረውን ጥብቅ የቪዛ ማዕቀብና ገደብ ሙሉ በሙሉ ለማንሳት መወሰኑን አስታዉቋል።
ምክር ቤቱ እ.ኤ.አ. በ2024 በኢትዮጵያ ላይ የተወሰኑ የቪዛ ሕጎችን አግዶ የቆየው፣ የኢትዮጵያ መንግስት በአውሮፓ አገራት በሕገ-ወጥ መንገድ የሚኖሩ ዜጎቹን በፈቃደኝነት መልሶ የመቀበል ሂደት ላይ በቂ ትብብር እንዲያደርግ ግፊት ለመፍጠር እንደነበር ይታወሳል።
የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ባደረገው የቅርብ ጊዜ ግምገማ መሠረት፣ ባለፉት ወራት የኢትዮጵያ መንግስት በአውሮፓ አገራት ውስጥ በሕገ-ወጥ መንገድ የሚገኙ ዜጎቹን ማንነት በመለየት፣ የድንገተኛ ጊዜ የጉዞ ሰነዶችን በመስጠት እንዲሁም መደበኛ የመልሶ ማረፍ ስራዎችን በማደራጀት ረገድ ያሳየው ዲፕሎማሲያዊ እና አስተዳደራዊ ትብብር በከፍተኛ ደረጃ መሻሻሉን አረጋግጧል።
የቪዛ ገደቡ መነሳቱን ተከትሎ፣ ውሳኔው ለአባል አገራቱ በግል ከቀረበበትና ማሳወቂያ ከተሰጠበት ዕለት ጀምሮ በይፋ ተግባራዊ መሆን እንደሚጀምር ምክር ቤቱ ጠቁሟል።
የአውሮፓ ህብረት የቪዛ ሕግ መሠረት፣ ኮሚሽኑ ከአውሮፓ ውጭ ያሉ አገራት ስደተኞችን መልሶ በመቀበል ረገድ የሚያሳዩትን ትብብር በየጊዜው ይገመግማል።
በዚህ ግምገማ መሠረት በቂ ትብብር የማያደርጉ አገራት ላይ ህብረቱ የቪዛ አሰጣጥ ሂደቱን የሚያጠብቁና መብቶችን የሚያግዱ ውሳኔዎችን ያስተላልፋል።
ይህ አሁን የተወሰነው የቪዛ ገደብ መነሳት ውሳኔ፣ በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት፣ የዜጎችን የጉዞ ነጻነት እንዲሁም ሕጋዊ የስደት ቁጥጥር ስራዎችን ይበልጥ ያጠናክራል ተብሎ ይጠበቃል። (ካፒታል-ጋዜጣ) | 32 557 |
| 13 | #ንግድባንክ መልእክት!
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሠረት በሀገሪቱ በሚገኙ በተመረጡ ከተሞች ላይ የተከፈቱ የባንክ ሂሳቦች እስከ ግንቦት 06 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ ከደንበኞች የፋይዳ መታወቂያ ጋር እንዲተሳሰር የተቀመጠው ቀነ ገደብ መጠናቀቁን ተከትሎ በትዕዛዙ መሰረት ደንበኞች እነዚህን ሂሳቦች ማንቀሳቀስ እንዳይችሉ ተደርጓል፡፡
ይህንን ተከትሎ በከፍተኛ ሁኔታ የማስተሳሰር ጥያቄ ወደ ባንካችን እየቀረበ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ባንካችን ይህንን ጫና በመቋቋም ለደንበኞቻችን በሚፈለገው ፍጥነት ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተለያዩ አሰራሮችን ተግባራዊ አድርጓል፡፡
ለአብነት ከግንቦት 7 እስከ ግንቦት 12 በተለየ ምክንያት እንዳይንቀሳቀሱ ከተደረጉት ሂሳቦች ውጪ የተሳሰሩ ሂሳቦችን ደንበኞች ማንቀሳቀስ እንዲችሉ ተደርጓል፡፡ እንዲሁም ከ ከግንቦት 12 ጀምሮ ደንበኞች ሂሳባቸውን እንዳስተሳሰሩ የመረጃ ስርዓታችን (system) በራሱ ጊዜ ገደቡን እንዲያነሳ ተደርጓል፡፡
መሰል ፈጣን ምላሾን እየሰጠን የደንበኞቻችንን እርካታ እውን ለማድረግ የምንሰራ መሆኑን እያረጋገጥን በዚህ ሂደት ላሳያችሁት ትዕግስት ከልብ እያመሰገንን በደንበኞቻችን ላይ ለተፈጠረው መጉሏሏት ይቅርታ ለመጠየቅ እንወዳለን፡፡
በተጨማሪም እንዳይንቀሳቀስ ከተደረጉ ሂሳቦች እና ከነዚህ ውጭ በተቀሩት የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚገኙ የባንክ ቅርንጫፍ ደንበኞች እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ አስቀድማችሁ የማስተሳሰር ሂደቱን በባንካችን ቅርንጫፎች በመገኘት ወይም በበይነ መረብ (Online) ማስተሳሰሪያ አማራጭ (https://cbefayda.cbe.com.et) ሂሳባችሁን ለማንቀሳቀስ እንድትችሉ በአክብሮት እንጠይቃለን::
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ | 25 499 |
| 14 | ከቅርብ አመታት ወዲ ውበትን ከጥራት ጋር ባለበት ጊዜ ሰርቶ በማስረከብ የሚታወቀዉ አዲስ ላይፍ ሪል እስቴት እንሆ በቡልጋሪያ በታላቅ ዲስካዉንት ቅድሚያ ለሚገዙ በመረጡት ፍሎር ተስማሚ በሆነላቸዉ ቦታ ቅድሚያ እንደሚሰጣቸዉ ሲገልፅ በራሱ በመተማመን ነዉ።
ታዲያ እናተም አዲስ ላይፍን ሲመርጡ ከ10% ቅድሚያ ክፍያ ጀምሮ የምናስተናግዶ ሲሆን ህንፃዉ ተገንብቶ እስኪያልቅ ድረስ ምንም አይነት የዋጋ ግሽፈት ቢከሰት ደንበኛችንን እንደማይመለከት የጋራ መተማመኛ ዉል ላይ በማስቀመጥ እናስረክቦታለን።
100% ለሚከፍል ከ80,750 ጀምሮ
ለበለጠ መረጃ➤በ0937867901 ይደዉሉ። | 24 602 |
| 15 | አርሰናል ከ22 ዓመታት በኋላ የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን ሆነ✅
ማንቸስተር ሲቲ አቻ መውጣቱን ተከትሎ አርሰናል የፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ሆነ
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 37ኛ ሳምንት ማንቸስተር ሲቲ ከበርንማውዝ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ ውጤት አቻ መውጣቱን ተከትሎ የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑን አረጋግጧል።
በቫሊቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ጁኒየር ክሩፒ በመጀመሪያው አጋማሽ 38ኛ ደቂቃ ላይ ሲያስቆጥር ኧርሊንግ ሃላንድ ሲቲን አቻ ያደገውን ግብ አስቆጥሯል።
ፕሪሚየር ሊጉ ሊጠናቀቅ አንድ ጨዋታ ብቻ የቀረ ሲሆን እስካሁን 82 ነጥቦችን የሰበሰበው አርሰናል 78 ነጥቦች ካሉት ተከታዩ ማንቸስተር ሲቲ ጋር የአምስት ነጥቦች ልዩነት ያለው በመሆኑ ሻምፒዮናነቱን አረጋግጧል። | 28 554 |
| 16 | የዓለም ጤና ድርጅት በኢቦላ ቫይረስ ምክንያት ዓለማቀፍ የጤና አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀ
የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና በኡጋንዳ በከፍተኛ ሁኔታ እያገረሸ የመጣውን የኢቦላ ቫይረስ ስርጭት ተከትሎ፣ ወረርሽኙን ይፋዊ የዓለማቀፍ የህዝብ ጤና ስጋት አድርጎ አውጇል።
የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው (ኤክስ) ባስተላለፉት መረጃ፣ እስካሁን ባለው ጊዜ ውስጥ በቫይረሱ ሳቢያ የ 88 ሰዎች ህይወት ማለፉንና 300 ያህል ሰዎች ደግሞ በበሽታው መያዛቸውን አረጋግጠዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም የኢቦላ ቫይረስ ልክ እንደ ኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሁሉ የመቀጣጠልና በከፍተኛ ፍጥነት የመስፋፋት አቅም እንዳለው በማስገንዘብ፣ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ አስቸኳይና ጥብቅ የሆኑ የመከላከል ስራዎች በአለም አቀፍ ደረጃ እንዲተገበሩ ጥሪ አቅርበዋል። | 20 907 |
| 17 | የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቤጂንግ ገብተዋል
የዓለማችን ሁለቱ ሀያላን አገራት አሜሪካ እና ቻይና በመሪዎች ደረጃ ለሚያደርጉት ውይይት የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከልዑካን ቡድናቸው ጋር ቤጂንግ ገብተዋል።
ይህ ጉብኝት በሁለቱ ኃያላን ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ብቻ ሳይሆን የዓለምን ጂኦፖለቲካዊ ሚዛን የሚወስን ነው የተባለ ሲሆን ዶናልድ ትራምፕ በቻይና ቆይታቸው በመካከለኛው ምስራቅ በተለይም በኢራን እና በሆርሙዝ ሰርጥ ላይ ከፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር እንደሚወያዩ ይጠበቃል።
በፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የቻይና ጉብኝት እንደ ቴስላው ባለቤት ኢሎን መስክ እና የአፕል ዋና ስራ አስኪያጅ ቲም ኩክ ያሉ የንግድ ዘርፍ መሪዎች በፕሬዚዳንቱ ልዑካን ውስጥ የተካተቱ ሲሆን ይህም፣ የአሜሪካ ኩባንያዎች በቻይና ገበያ ያላቸውን ድርሻ ለማስጠበቅ እና በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የንግድ ጦርነት ለማርገብ ያለመ ውይይት እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።
መሪዎቹ ለዓለም ነዳጅ ንግድ ቁልፍ የሆነው የሆርሙዝ ሰርጥ ዳግም እንዲከፈት እና ኢራን ወደ ሰላም ስምምነት እንድትመጣ እንደሚመክር የዘገበው ሲኤንኤን ነው። | 0 |
| 18 | ማስታወቂያ ለ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኞች በሙሉ
መጪ ሰኔ 24/2018 ዓ/ም ጀምሮ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ ተፈታኞች የተዘጋጀ የመፈተኛ ክፍል መግቢያ ካርድ (Admission Card) በፈተና አስተዳደር ሲስተም (https://exam.eaes.et/) ከ03/09/2018 ዓ/ም ጀምሮ ለክልል ትምህርት ቢሮ፣ ለዞን ትምህርት መምሪያዎች እና ለትምህርት ቤት ተወካዮች ተለቋል።
ስለሆነም፡-
1.እያንዳንዱ ተፈታኝ ተማሪ በአድሚሽን ካርዱ ጀርባ ላይ የተፈታኝ ተማሪው ትምህርት ቤት ወይም የወረዳው አስተዳደር ትምህርት ጽ/ቤት ማህተም የተደረገበትን አድሚሽን ካርድ ከትምህርት ቤቱ ወስዶ በእጁ መያዝ ይጠበቅበታል።
2.በምዝገባ ወቅት በተፈታኙ ወይም በመዝጋቢው የተከሰተ የትምህርት መስክ፣ የጾታ፣ የፎቶ እና መሰል ማስተካከያዎች ካሉ ከግንቦት 30/2018 ዓ.ም በፊት ለትምህርት ቤቱ ማሳወቅና ሂደቱን ጠብቆ መስተካከሉንም ከትምህርት ቤቱ ማረጋገጥ ይጠበቅበታል።
3.እያንዳንዱ ተፈታኝ አድሚሽን ካርዱን ወደ መፈተኛ ማዕከልም ሆነ መፈተኛ ክፍል ለመግባት የሚጠቀምበት በመሆኑ በአግባቡና በጥንቃቄ መያስ ይገበዋል።
4.ተፈታኞች በፈተና ወቅት ከአድሚሽን ካርድ በተጨማሪ የፋይዳ መታወቂያ መያዝ ይጠበቅባቸዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት | 0 |
| 19 | በ'ፊንቴክ ኢንቨስትመንት' የማጭበርበር ወንጀል የተጠረጠሩ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች በ 400 እና 500 ሺ ብር የገንዘብ ዋስትና ጉዳያቸውን ከውጭ ሆነው እንዲከታተሉ ተወሰነ።
ችሎቱ ሚያዚያ 28/2018 ዓም በተሰየመበት ወቅት ተጠርጣሪዎች ለዋስትና የሚያቀርቡትን የገንዘብ መጠን ለመወሰን ለዛሬ ሰኞ ግንቦት 3/2018 ዓም ቀነ ቀጠሮ መስጠቱ መዘገባችን ይታወሳል።
በ'ፊንቴክ ኢንቨስትመንት' የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ውለው የነበሩ ታዋቂ አርቲስቶች እና ቲክቶከሮች የዋስትና መብታቸው እንዲከበር የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ ችሎት በወሰነው መሰረት እያንዳንዳቸው ከ400 እስከ 500 ሺ ብር በሚደርስ የገንዘብ ዋስትና ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
ፍርድ ቤቱ በዋስትና ጉዳዩ ላይ መርምሮ ባስተላለፈው ውሳኔ መሠረት ፦
ከ1ኛ እስከ 4ኛ ተከሳሾች (አርቲስት ሠራዊት ፍቅሬ፣ አርቲስት ሠለሞን ቦጋለ፣ አርቲስት ይገረም ደጀን እና አርቲስት ዳንኤል ተገኝ) እያንዳንዳቸው በ500 ሺህ ብር የገንዘብ ዋስትና፤
እንዲሁም 6ኛ እና 7ኛ ተከሳሾች (ካሊድ ናስር እና አብርሃም ግዛው) እያንዳንዳቸው በ 400 ሺህ ብር የገንዘብ ዋስትና ከእስር እንዲፈቱ ወስኗል።
ይሁን እንጂ ተጠርጣሪዎቹ ከሀገር እንዳይወጡ የእግድ ትዕዛዝ ተላልፎባቸዋል።
በሌላ በኩል፣ በክስ መዝገቡ 5ኛ ተከሳሽ በሆነው በቲክቶከሩ መንሱር ጀማል ላይ አቃቤ ህግ የዋስትና መብቱን በመቃወሙ ምክንያት ችሎቱ ውሳኔ ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። | 0 |
| 20 | የአሜሪካ እና የፈረንሳይ ዜጎች በሀንታ ቫይረስ መያዛቸው ተረጋገጠ።
ገዳይ በሆነው የሀንታ ቫይረስ ወረርሽኝ ከተመታች የመንገደኞች መርከብ ወጥተው ወደ ሀገራቸው የተመለሱ አንድ አሜሪካዊ እና አንድ የፈረንሳይ ዜጋ በቫይረሱ መያዛቸው መረጋገጡን ባለስልጣናት ገለጹ።
የአሜሪካ የጤና መምሪያ በበኩሉ፣ በዚሁ የሀገር መመለሻ በረራ ላይ የነበሩ ሌላ ሁለተኛ አሜሪካዊ ዜጋም መጠነኛ ምልክቶች እንደታዩባቸው ገልጾ፤ ሁለቱም መንገደኞች ተላላፊ ለጥንቃቄ ሲባል በሽታን በሚከላከሉ (በባዮ-ኮንቴይመንት) ክፍሎች ውስጥ ሆነው መጓዛቸውን አክሏል።
የፈረንሳይ ጤና ሚኒስትር እስቴፋኒ ሪስት እንደተናገሩት፣ አንዲት ሴት በፓሪስ ተገልላ ትገኛለች፤ የጤና ሁኔታዋም እየተባባሰ ነው።
ከዚሁ ጋር ተያይዞም ከእሷ ጋር ንክኪ ነበራቸው የተባሉ 22 ሰዎች ተለይተዋል፤በአሁኑ ወቅት በስፔን የካናሪ ደሴቶች ቆማ በምትገኘው ኤምቪ ሆንድየስ (MV Hondius) መርከብ ላይ ከነበሩት መንገደኞች መካከል ከ90 በላይ የሚሆኑት ወደ ሀገራቸው በመመለስ ላይ ናቸው። በመርከቧ ላይ ተጉዘው ከነበሩ ሶስት መንገደኞች ጥንድ ሆላንዳውያን እና አንዲት ጀርመናዊት ህይወታቸው አልፏል። ከእነዚህ ውስጥ ሁለቱ በቫይረሱ መያዛቸው ተረጋግጧል።
ባለስልጣናት እንደሚሉት ከሆነ ከፍተኛ የሆነ ወረርሽኝ የመከሰቱ ዕድል በጣም ዝቅተኛ ነው፤ የአሜሪካ የጤና እና የሰብአዊ አገልግሎት መምሪያ ሰኞ ማለዳ ላይ ባወጣው መግለጫ፣ በበረራው ላይ የነበሩት 17ቱም የአሜሪካ ዜጎች በነብራስካ በሚገኝ የህክምና ተቋም "ክሊኒካዊ ግምገማ" ይደረግላቸዋል ተብሏል። በሽታው ምልክቶች ትኩሳት፣ ከፍተኛ ድካም፣ የጡንቻ ህመም፣ የሆድ ህመም፣ ማስታወክ፣ ተቅማጥ እና የትንፋሽ ማጠርን ሊያካትቱ ይችላሉ። | 0 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
