ETHIO-MEREJA®
News & Media Channel® Addisababa, Ethiopia🇪🇹 ውድ የኢትዮ መረጃ ቤተሰቦች ከዚህ የቴሌግራም ቻናል ውጪ ሌላ መረጃ የምናቀርብበት ምንም አይነት የዩቲዩብ፣ የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆች እንደሌለን ለማሳወቅ እንወዳለን፣ ስለሆነም በተመሳሳይ ስም በተከፈቱ ገፆች እንዳይሸወዱ ጥንቃቄ እንድታደርጉ እናሳስባለን። ለጥቆማና ማስታወቂያ ለማሰራት 👉 @ethio_merejabot
显示更多📈 Telegram 频道 ETHIO-MEREJA® 的分析概览
频道 ETHIO-MEREJA® (@ethio_mereja) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 99 454 名订阅者,在 新闻与媒体 类别中位列第 2 525,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 324 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 99 454 名订阅者。
根据 31 八月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -1 229,过去 24 小时变化为 -56,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 17.19%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.55% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 17 103 次浏览,首日通常累积 8 508 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 48。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“News & Media Channel®
Addisababa, Ethiopia🇪🇹
ውድ የኢትዮ መረጃ ቤተሰቦች ከዚህ የቴሌግራም ቻናል ውጪ ሌላ መረጃ የምናቀርብበት ምንም አይነት የዩቲዩብ፣ የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆች እንደሌለን ለማሳወቅ እንወዳለን፣ ስለሆነም በተመሳሳይ ስም በተከፈቱ ገፆች እንዳይሸወዱ ጥንቃቄ እንድታደርጉ እናሳስባለን።
ለጥቆማና ማስታወቂያ ለማሰራት
👉 @ethio_mere...”
凭借高频更新(最新数据采集于 01 九月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 新闻与媒体 类别中的关键影响点。
数据加载中...
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 01 九月 | 0 |
| 2 | ቀረጥ ሳይከፈልባቸው ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ ከ700 በላይ ተንቀሳቃሽ ስልኮችና ልዩ ልዩ ቁሳቁሶች ተያዙ፡፡
ተገቢውን የጉምሩክ ሂደት ያላለፉና በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሀገር ውስጥ የገቡ የተለያዩ ዓይነትና መጠን ያላቸው ከ700 መቶ በላይ የሞባይል ቀፎዎች፣ ከሁለት ሺህ በላይ የቻርጀር ገመዶች፣ ልዩ ልዩ የኤሌክትሮኒክስ መለዋወጫዎችና አልበሳት በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡
በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የመሣለሚያ አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ/ም በክ/ከተማው ወረዳ 8 ልዩ ቦታው አዲስ አበባ የገበያ ማዕከል ከምሽቱ 1፡00 ሠዓት ሲሆን አሰፋ ጸጋ እና አማኑኤል ብርሀኑ የተባሉ ተጠርጣሪዎች የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹን የሠሌዳ ቁጥር B-77746 አ.አ በሆነ ሱዙኪ የጭነት ተሽከርካሪ ይዘው ሲንቀሳቀሱ ስራ ላይ በነበሩ የፖሊስ አባላት በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
የክ/ከተማው ፖሊስ ዋና መምሪያ በተጠርጣሪዎቹ ላይ ተገቢውን የሰውና የሰነድ ማስረጃ በማደራጀት ክስ እንደሚያስመሰርት የገለፀ ሲሆን ህብረተሰቡም መሰል የወንጀል ድርጊት በሀገር ምጣኔ ሀብትና በህጋዊ ነጋዴዎች ላይ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተፅዕኖ በመረዳት የመረጃ የመስጠት ባህሉን ሊያጠናክር እንደሚገባም የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡
(ምንጭ ፣ አዲስ አበባ ፖሊስ) | 8 980 |
| 3 | ⭐️⭐️⭐️የአዲስ አመት 30% ልዪ ቅናሽ በመሀል ካሳንችስ ዘመናዊ የህይወት ዘይቤን ይቀላቀሉ! ኢንተርሌግዠሪ ሆቴል ፊትለፊት
በካሬ #77ሺ ብር ብቻ
🏠 የቤት አማራጮች
🔹 1 መኝታ: 72.99 ካሬ ጀምሮ
🔹 2መኝታ: 127 ካሬ ጀምሮ
🔹 3 መኝታ: 158ካሬ ጀምሮ
በተጨማሪም ብስራተ ገብርኤል ላፍቶ ሞል ላይ
🏠 የቤት አማራጮች
🔹 1 መኝታ: 89.9ካሬ ጀምሮ
🔹 2 መኝታ: 105 ካሬ ጀምሮ
🔹 3 መኝታ: 173ካሬ ጀምሮ
💳 ቀላል የክፍያ አማራጭ
⭐️በ10 ዙር የግንባታ ሂደት መሰረት የሚከፈል
⭐️ያለ ምንም የዋጋ ጭማሪ ክፍያዎን ማጠናቀቅ ይችላሉ።
📈 ለኢንቨስትመንት ፍጹም አማራጭ!
የአዲስ አበባ የንግድና የዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው በካሳንችስ እና ብስራተ ገብርኤል አከባቢዎች የራስዎን አፓርታማ ባለቤት ይሁኑ። ለቤት ፈላጊዎች እና ለኢንቨስትመንት የሚሆን አውራ ምርጫ!
2% ብቻ ከጠቅላላ የቤቱ ዋጋ በመክፈል፣ ቤቱን ለ3ኛ ወገን (Resale) ማስተላለፍ ወይም መሸጥ ይችላሉ። ይህም ከፍተኛ የመዋዕለ ንዋይ እድገትና ትርፍ የሚያስገኝ እድል ነው።
🌟 የፕሮጀክቱ አሜኒቲዎች
✅ 24/7 ጥበቃ እና CCTV
✅ ዘመናዊ ሊፍት
✅ ሰፊ የመኪና ማቆሚያ
✅ ባክአፕ ጀነሬተር
✅ የውሃ ማጠራቀሚያ
✅ ዘመናዊ ጂም
🏊 የመዋኛ ገንዳ
🛝 የልጆች መጫወቻ
🌿 የአረንጓዴ መዝናኛ ቦታ
☕ ዘመናዊ Lobby & Lounge
✨ ጥራት፣ ምቾት እና ዋጋ የሚገናኙበት ምርጥ የመኖሪያ ፕሮጀክት!
📞: 0911356543 | 10 293 |
| 4 | የብሔራዊ ባንክ ማሳሰቢያ!!
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለሕዝቡ፣ ለዲያስፖራውና ለመላው የገንዘብ ተጠቃሚ ጠንካራ ማሳሰቢያ አስተላልፏል።
ሕገወጥ የሃዋላ አውታረ መረቦችንና ፈቃድ ያልተሰጣቸውን የገንዘብ ማስተላለፊያ ወኪሎች መጠቀም ከፍተኛ የፋይናንስና የሕግ አደጋ ሊያስከትል እንደሚችል ባንኩ አስጠንቅቋል።
ገንዘብዎ ደህንነት ይገባዋል! በሕገወጥ መንገድ ገንዘብ መላክ ወይም መቀበል የገንዘብ ኪሳራ፣ የክፍያ መዘግየት፣ የሂሳብ መገደብ እና ሕጋዊ እርምጃ ሊያስከትል ይችላል።
በተለይ በዚህ ወቅት የገንዘብ ልውውጥ መጠን እየጨመረ በመሆኑ፣ ደንበኞች፣ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ አባላትና መላው ሕዝብ ገንዘብ ሲልኩም ሆነ ሲቀበሉ በብሔራዊ ባንክ ፈቃድ የተሰጣቸውን ሕጋዊ የገንዘብ ማስተላለፊያ አማራጮች ብቻ እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።
ብሔራዊ ባንክ ፈቃድ የሌላቸው ተብለው የተጠቀሱ የገንዘብ ማስተላለፊያ መንገዶች፦
1. Adulis Money Transfer (ADZ)
2. Amal Express
3. Amal USA
4. Amana Express
5. Avanti
6. Awash Direct
7. Bakaal Money Transfer
8. Jubba Express
9. Rasmy Pay
10. Ramad Pay / Ramada Pay (Kaah)
11. Shgey Money Transfer
12. Taaj Financial Service
13. Tasa Pay
14. Tawakal Money Services
15. USwyre
16. World Direct Link
17. Zola ናቸው። | 11 997 |
| 5 | 460 የሚጠጉ ሰዎችን ሕይወት የታደገው የድልድዩ ጠባቂ!
#Ethiopia | በቻይና የናንጂንግ ያንግትዜ ወንዝ ድልድይ በዓለም ላይ በርካታ ሰዎች ሕይወታቸውን ለማጥፋት የሚመርጡት አስፈሪ ሥፍራ በመባል ይታወቃል።
ነገር ግን ላለፉት 21 ዓመታት በዚህ ድልድይ ላይ አንድ ያልተለመደ ተአምር ሲፈጸም ቆይቷል።
በድልድዩ እራሳቸውን ለማጥፋት የመጡ 469 ሰዎችን በቼን ሲ እርዳታ ከሞት ተርፈዋል።
ቼን በወጣትነቱ በከባድ ድህነትና መከራ ያሳለፈው ሲሆን ከፈረንጆቹ 2003 ጀምሮ ቅዳሜና እሁድ ሙሉ በሙሉ ድልድዩ ላይ በመዘዋወር ወደዚህ ድልይ የሚመጡትን ሰዎች መጠበቅ ጀመረ።
ቼን በሞተር ብስክሌቱና በእግሩ ድልድዩን እያሰሰ የተስፋ መቁረጥ ምልክት የሚያሳይና ተክዞ የሚሄድ ማንኛውንም ሰው በነፃነት ቀርቦ ያናግራል።
የሥነ-ልቦና ትምህርት ሳይማር በራሱ የሕይወት ልምድና ደግነት ብቻ የሰዎችን ጭንቀት ይረዳል።
አንዳንዶቹን በንግግር ሌሎቹን ደግሞ በጉልበቱ እየጎተተ ከሞት አትርፏቸዋል።
የሌሎችን ከባድ ሕመም እና የተወሰኑ ማዳን ያልቻላቸውን ሰዎች ትዝታ በሕልሙ እያየ ለዓመታት ትልቅ የሥነ-ልቦና ጫና አስተናግዷል።
ቼን ሲ እንደሚለው አንዳንዴ ሰዎችን ከከፋ አደጋ ለማዳን ሳይንሳዊ እውቀት ሳይሆን በቦታው ተገኝቶ ሰብአዊ ርህራሄ ማሳየት ብቻ በቂ መሆኑን ተናግሯል።
ሔኖክ ወ/ገብርኤል / GetuTemesgen | 11 032 |
| 6 | ⭐️⭐️⭐️የአዲስ አመት 30% ልዪ ቅናሽ በመሀል ካሳንችስ ዘመናዊ የህይወት ዘይቤን ይቀላቀሉ! ኢንተርሌግዠሪ ሆቴል ፊትለፊት
በካሬ #77ሺ ብር ብቻ
🏠 የቤት አማራጮች
🔹 1 መኝታ: 72.99 ካሬ ጀምሮ
🔹 2መኝታ: 127 ካሬ ጀምሮ
🔹 3 መኝታ: 158ካሬ ጀምሮ
በተጨማሪም ብስራተ ገብርኤል ላፍቶ ሞል ላይ
🏠 የቤት አማራጮች
🔹 1 መኝታ: 89.9ካሬ ጀምሮ
🔹 2 መኝታ: 105 ካሬ ጀምሮ
🔹 3 መኝታ: 173ካሬ ጀምሮ
💳 ቀላል የክፍያ አማራጭ
⭐️በ10 ዙር የግንባታ ሂደት መሰረት የሚከፈል
⭐️ያለ ምንም የዋጋ ጭማሪ ክፍያዎን ማጠናቀቅ ይችላሉ።
📈 ለኢንቨስትመንት ፍጹም አማራጭ!
የአዲስ አበባ የንግድና የዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው በካሳንችስ እና ብስራተ ገብርኤል አከባቢዎች የራስዎን አፓርታማ ባለቤት ይሁኑ። ለቤት ፈላጊዎች እና ለኢንቨስትመንት የሚሆን አውራ ምርጫ!
2% ብቻ ከጠቅላላ የቤቱ ዋጋ በመክፈል፣ ቤቱን ለ3ኛ ወገን (Resale) ማስተላለፍ ወይም መሸጥ ይችላሉ። ይህም ከፍተኛ የመዋዕለ ንዋይ እድገትና ትርፍ የሚያስገኝ እድል ነው።
🌟 የፕሮጀክቱ አሜኒቲዎች
✅ 24/7 ጥበቃ እና CCTV
✅ ዘመናዊ ሊፍት
✅ ሰፊ የመኪና ማቆሚያ
✅ ባክአፕ ጀነሬተር
✅ የውሃ ማጠራቀሚያ
✅ ዘመናዊ ጂም
🏊 የመዋኛ ገንዳ
🛝 የልጆች መጫወቻ
🌿 የአረንጓዴ መዝናኛ ቦታ
☕ ዘመናዊ Lobby & Lounge
✨ ጥራት፣ ምቾት እና ዋጋ የሚገናኙበት ምርጥ የመኖሪያ ፕሮጀክት!
📞: 0911356543 | 10 979 |
| 7 | አሜሪካ በትግራይ ጉዳይ ላይ ስምምነት እንዲደረግ ጠየቀች፤ ህወሓት ከአፍሪካ ህብረት ውይይት በፊት ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀመጠ
በአፍሪካ ህብረት ከፍተኛ ተወካይ ኦሉሴጉን ኦባሳንጆ የመቀሌ ጉብኝት ማብቂያ ላይ አሜሪካ በኢትዮጵያ መንግስት እና በትግራይ አመራሮች መካከል እርቅ እንዲወርድ እና ስምምነት ላይ እንዲደረስ ጥሪ አቀረበች።
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ እና የአፍሪካ ህብረት የዩኤስ ሚሲዮን ጉዳይ ፈጻሚ ዎልተር ፓርስ በጋራ ባወጡት መግለጫ፣ የኦባሳንጆ ጥረት እንዳበረታታቸው ገልጸው ውይይቱን እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።
አሜሪካ ቀዳሚ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባው የሰብአዊ እርዳታ አቅርቦት እና ተፈናቃዮችን ወደ ቀደመ ቀያቸው በሰላም የመመለሱ ሂደት እንደሆነ አስታውቃለች።
በሌላ በኩል ህወሓት በሰጠው ምላሽ በቅርቡ ከመቀሌው ውይይት ከአዲስ አበባ በኩል የመጣ "አዲስ ሃሳብ ወይም የእድገት ማሳያ የለም" ሲል ገልጿል።
ድርጅቱ ከመደበኛ ድርድር በፊት መፈታት ያለባቸውን በርካታ ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጧል።
ህወሓት ካቀረቧቸው ቅድመ ሁኔታዎች መካከል፡
👉ወታደራዊ ከበባ እንዲያበቃ እና የኢኮኖሚ ማዕቀብ እንዲነሳ፣
👉አከራካሪ ቦታዎች ነፃ ወጥተው ተፈናቃዮች እንዲመለሱ፣
👉የህወሓት ህጋዊ እና ፖለቲካዊ ህልውና ሙሉ በሙሉ እንዲመለስ የሚሉ ይገኙበታል።
ምንጭ: ዘ ሪፖርተር | 15 333 |
| 8 | ⭐️⭐️⭐️የአዲስ አመት 30% ልዪ ቅናሽ በመሀል ካሳንችስ ዘመናዊ የህይወት ዘይቤን ይቀላቀሉ! ኢንተርሌግዠሪ ሆቴል ፊትለፊት
በካሬ #77ሺ ብር ብቻ
🏠 የቤት አማራጮች
🔹 1 መኝታ: 72.99 ካሬ ጀምሮ
🔹 2መኝታ: 127 ካሬ ጀምሮ
🔹 3 መኝታ: 158ካሬ ጀምሮ
በተጨማሪም ብስራተ ገብርኤል ላፍቶ ሞል ላይ
🏠 የቤት አማራጮች
🔹 1 መኝታ: 89.9ካሬ ጀምሮ
🔹 2 መኝታ: 105 ካሬ ጀምሮ
🔹 3 መኝታ: 173ካሬ ጀምሮ
💳 ቀላል የክፍያ አማራጭ
⭐️በ10 ዙር የግንባታ ሂደት መሰረት የሚከፈል
⭐️ያለ ምንም የዋጋ ጭማሪ ክፍያዎን ማጠናቀቅ ይችላሉ።
📈 ለኢንቨስትመንት ፍጹም አማራጭ!
የአዲስ አበባ የንግድና የዲፕሎማሲ ማዕከል በሆነችው በካሳንችስ እና ብስራተ ገብርኤል አከባቢዎች የራስዎን አፓርታማ ባለቤት ይሁኑ። ለቤት ፈላጊዎች እና ለኢንቨስትመንት የሚሆን አውራ ምርጫ!
2% ብቻ ከጠቅላላ የቤቱ ዋጋ በመክፈል፣ ቤቱን ለ3ኛ ወገን (Resale) ማስተላለፍ ወይም መሸጥ ይችላሉ። ይህም ከፍተኛ የመዋዕለ ንዋይ እድገትና ትርፍ የሚያስገኝ እድል ነው።
🌟 የፕሮጀክቱ አሜኒቲዎች
✅ 24/7 ጥበቃ እና CCTV
✅ ዘመናዊ ሊፍት
✅ ሰፊ የመኪና ማቆሚያ
✅ ባክአፕ ጀነሬተር
✅ የውሃ ማጠራቀሚያ
✅ ዘመናዊ ጂም
🏊 የመዋኛ ገንዳ
🛝 የልጆች መጫወቻ
🌿 የአረንጓዴ መዝናኛ ቦታ
☕ ዘመናዊ Lobby & Lounge
✨ ጥራት፣ ምቾት እና ዋጋ የሚገናኙበት ምርጥ የመኖሪያ ፕሮጀክት!
📞: 0911356543 | 13 670 |
| 9 | የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ።
የ2018 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ተደርጓል። ተፈታኞችም ውጤታቸው ማየት ጀምረዋል።
ውጤት ለማየት ፦
👉 በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et
👉 ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram
👉 አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms
በአንድ ጊዜ በርካታ ተማሪዎች ውጤታቸውን ለማየት ስለሚሞክሩ የኔትዎርክ መጨናነቅ ሊያጋጥም ስለሚችል ደጋግሞ መሞከር ይገባል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልጋቸው https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ ማቅረብና ምላሹንም በዛው ማስፈንጠሪያ መከታተል እንደሚችሉ ገልጿል። | 19 656 |
| 10 | 🚨 እስከ 35% ቅናሽ! ያለምንም ወለድ እና የዋጋ ጭማሪ በምርጥ ቦታዎች የቤት ባለቤት ይሁኑ! 🚨
ኑሮዎን በአዲስ አበባ ማዕከላዊ እና ውድ ስፍራዎች ለማድረግ አስበዋል? ቴምር ሪል ስቴት (Temer Properties) እጅግ ማራኪ በሆኑ የክፍያ አማራጮች ዘመናዊ አፓርትመንቶችን እና የንግድ ሱቆችን አቅርቦልዎታል።
✅ በየትኛው ቦታ መኖር ይፈልጋሉ?
📍 መገናኛ (ቤልቪው ሆቴል አጠገብ)
📍 ቡልጋሪያ (አፍሪካ ህብረት ፊት ለፊት)
📍 አዋሬ (ቤተመንግስት አጠገብ)
📍 ሳር ቤት (አዳምስ አጠገብ)
💰 ልዩ የክፍያ አማራጮች (በኢትዮጵያ ብር ብቻ)፡
100% ለሚከፍሉ፡ እስከ 35% ታላቅ ቅናሽ!
40% ቅድመ ክፍያ፡ የ 10% ቅናሽ ተጠቃሚ ሲሆኑ፤ ቀሪውን 60% ቤቱን ሲረከቡ ይከፍላሉ።
20% ቅድመ ክፍያ፡ ቀሪውን በ16 ዙር፣ በረጅም ጊዜ ከፍለው ይጨርሳሉ።
🏠 የአፓርትመንት አማራጮች (ከስቱዲዮ እስከ 3 መኝታ)፦
• ስቱዲዮ (ከ 32 ካሬ ጀምሮ)
• 1 መኝታ (ከ 60 ካሬ ጀምሮ)
• 2 መኝታ (ከ 90 ካሬ ጀምሮ)
• 3 መኝታ (ከ 118 ካሬ ጀምሮ)
🎯 ልብ ይበሉ፡ ክፍያው ያለምንም የባንክ ወለድ እና የግንባታ እቃዎች የዋጋ ጭማሪ የሚፈፀም ነው!
እነዚህ ውሱን ቤቶች ከመጠናቀቃቸው በፊት አሁኑኑ ይደውሉልን!
📞 +251939770177
📞 +251996856273
📱 WhatsApp: https://wa.me/251939770177
💬 Telegram: @KalTemerRealEstate | https://t.me/TemerRealEstateSalesConsultant | 15 532 |
| 11 | " ተማሪዎች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸው ማየት ይችላሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆነዋል።
በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን (Link) በመጠቀም ማየት የሚችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
በተያያዘም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጿል።
ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡-
- በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et
- ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram
- አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms
ነሐሴ 19 ቀን 2018 አ.ም | 13 368 |
| 12 | አሜሪካ የ200,000 ሰዎችን ቪዛ ልትሰርዝ ነው
የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በታሪክ ትልቁን የቪዛ ስረዛ እርምጃ ለመውሰድ እየተዘጋጀ መሆኑ ተገለጸ።
እርምጃው በንግድ (B1) እና በቱሪዝም (B2) ቪዛ ወደ አሜሪካ ገብተው የጥገኝነት ጥያቄ ያቀረቡ ወይም በመጠየቅ ላይ ያሉ እስከ 200,000 የሚደርሱ የውጭ ሀገር ዜጎችን ዓላማ ያደረገ ነው።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከሃገር ውስጥ ደህንነት መስሪያ ቤት ጋር በመተባበር ከ2016 እስከ 2026 የተሰጡ ቪዛዎችን ለመሰረዝ ዝግጅቱን አጠናቋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ቶሚ ፒጎት እንደተናገሩት፣ እርምጃው ለአጭር ጊዜ ጉብኝት መጥተው ቪዛውን ለቋሚ መኖሪያነት የተጠቀሙበትን ለመቆጣጠር ታስቦ የተወሰደ ነው።
ይህ የቪዛ ስረዛ ሰዎች ወዲያውኑ ከሀገር እንዲወጡ ባያደርግም፣ ህጋዊ የጉዞ ሁኔታቸውን የሚያሳጣ በመሆኑ ከፍተኛ የህግ ክስና ተቃውሞ እንደሚገጥመው ይገመታል።
የትራምፕ አስተዳደር ከዚህ ቀደምም በቪዛ አመልካቾች ላይ በርካታ ጠንካራ ገደቦችን ሲጥል መቆየቱ ይታወቃል። (AP) | 18 840 |
| 13 | በመዲናዋ በትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት አለፈ
በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ በዛሬው ዕለት በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ6 ሰዎች ህይወት አልፏል፡፡
በክፍለ ከተማው ወረዳ 11 ልዩ ቦታው ቅድስት ኪዳነ ምህረት ቤተክርስቲያን አካባቢ በደረሰው አደጋ ከሟቾች በተጨማሪ ሌሎች ሰዎችም ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው የከተማው ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ ገልጿል፡፡፡
ዛሬ ጠዋት 1 ሰዓት ከ50 ከኮዬ ፈቼ ወደ ጎሮ በመጓዝ ላይ የነበረ ሚኒባስ ተሽከርካሪ በተጠቀሰው አካባቢ በመንገድ ስራ ላይ የነበረ ስካቫተር ማሽን መቆፈሪያው ወድቆበት በታክሲው ውስጥ ከነበሩ ትራንስፖርት ተጠቃሚዎች መካከል የ6ቱ ህይወት አልፏል፡፡
ከሟቾች በተጨማሪ በታክሲ ውስጥ የነበሩ ተሳፋሪዎች ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸው የህክምና ክትትል በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑንም ፖሊስ አስታውቋል፡፡ | 18 478 |
| 14 | የተማሪዎች ውጤት መቼ ይለቀቃል?
ተማሪዎች ውጤታቸውን ከሰኞ ጠዋት ወይም ማክሰኞ ከሰዓት ጀምሮ መመልከት ይችላሉ።
በውጤታቸው ላይ ቅሬታ የሚኖራቸው ከሆነም 5/6 ቀናት ቅሬታ የማቅረቢያ ጊዜ የሚሰጣቸው ይሆናል። | 20 061 |
| 15 | #NationalExam
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ስለ 12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት መግለጫ እየሰጡ ነው።
በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና 563 ሺ 960 ተማሪዎች ተመዝግበው 550 ሺ 210 ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል።
ፈተናውን ከወሰዱት ውስጥ 12.8 በመቶ የሚሆኑት ተማሪዎች 50 በመቶ እና ከዚያ በላይ ማምጣት ችለዋል።
ዘንድሮ በአጠቃላይ ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል ማለፍ የቻሉት 70 ሺ 544 ናቸው።
ካለፉት መካከል በተፈጥሮ ሳይንስ 16.5 በመቶ ሲሆኑ በማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ 8.33 በመቶ ናቸው። | 20 228 |
| 16 | ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ በዕጩነት ያቀረባቸው ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሹመት በብሔራዊ ባንክ ውድቅ ሆነ
ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የቀድሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚውን እንዲተኩ በተጠባባቂነት የሰየማቸውን ዋና ሥራ አስፈጻሚ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ውድቅ ማድረጉ ተሰማ፡፡
በግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ውስጥ ተፈጥሮ በነበረው ችግር ሳቢያ የባንኩ ዳይሬክተሮች ቦርድ ዋና ሥራ አስፈጻሚውን ጨምሮ 18 የባንኩ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ከኃላፊነታቸው ማንሳቱና ይህንንም ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክም የባንኩን የቀድሞ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ለአምስት ዓመት በየትኛውም የፋይናንስ ተቋማት እንዳያገለግሉ እንዳገደ መዘገባችን ይታወሳል፡፡
ይህንን ውሳኔ ተከትሎ የግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ቦርድ አዲስ ተጠባባቂ ዋና ሥራ አስፈጻሚ በመሰየም ሹመቱን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እንዲያፀድቅለት ቢልክም፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሹመቱን ሳያፀድቅ ቀርቷል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የተጠባባቂ ዋና ሥራ አስፈጻሚውን ሹመት ያልተቀበለውና ሹመቱንም የማያፀድቅ መሆኑን ለግሎባል ኢትዮጵያ ባንክ ቦርድ በጽሑፍ ማሳወቁንም ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
ብሔራዊ ባንክ ሹመቱን ያላፀደቀበትን ምክንያት በደብዳቤው ማሳወቁ የተመለከተ ሲሆን፣ በዋናነት የጠቀሰው ምክንያትም በባንክ ሥራ አዋጅ አንድ የባንክ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሊያሟላ ይገባል ተብሎ የተዘረዘሩትን መሥፈርቶች ለዋና ሥራ አስፈጻሚነት የታጩት ግለሰብ አያሟሉም የሚል ነው፡፡ ባንኩ ለዋና ሥራ አስፈጻሚነት ያጫቸው አቶ ሳህለ ሚካኤል መኮንን መሆናቸውን ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል። | 21 135 |
| 17 | በአቶ ታዬ ደንደአ ላይ ተጥሎ የነበረው የአራት ዓመት የጽኑ እስራት ውሳኔ በሰበር ሰሚ ችሎት ጸደቀ
#Ethiopia | የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የቀድሞው የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር ደኤታ አቶ ታዬ ደንደአ ላይ የታዘዘውን የአራት ዓመታት የእስር ቅጣት ሙሉ በሙሉ ማጸናቱን አስታወቀ።
ችሎቱ በአዲስ አበባ በዋለው ሰበር ችሎት በአቶ ታዬ ደንደአ በኩል የቀረበውን አቤቱታ ውድቅ በማድረግ በታችኛው ፍርድ ቤት ተበይኖ የነበረውን ውሳኔ አጽንቶታል።
አቶ ታዬ በመጀመሪያ ደረጃ በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያ ይዞ መገኘት በሚል በተመሠረተባቸው ክስ የሰባት ዓመት እስር ተፈርዶባቸው የነበረ ቢሆንም ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ባቀረቡት ይግባኝ ቅጣቱ ወደ አራት ዓመት ዝቅ እንዲል ተደርጎ ነበር።
ይሁን እንጂ በተሰጠው ውሳኔ ላይ ቅሬታ የነበራቸው አቶ ታዬ አምስት የመከራከሪያ ነጥቦችን በማንሳት ለፌዴራል ሰበር ሰሚ ችሎት አቤቱታቸውን ቢያቀርቡም ችሎቱ የቀረበውን ጥያቄ ሳይቀበለው ቀርቷል።
የአቶ ታዬ ደንደአ ባለቤት ወይዘሮ ስንታየሁ ዓለማየሁ ለዶቼ ቬለ በሰጡት ቃል ባለቤታቸው የመሣሪያውን መገኘት ባያስተባብሉም ከሌሎች ዜጎች እኩል የመዳኘት መብት እንደተከለከሉ እና ካቀረቧቸው አምስት ተከላካይ ምስክሮች መካከል የሁለቱ ብቻ ቃል ተሰምቶ ውሳኔ መሰጠቱን በቅሬታነት ማቅረባቸውን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል አቃቤ ሕግ ይግባኝ ባሰማበት ተጓዳኝ የክስ ነጥብ ላይ ፍርድ ቤቱ ለጥቅምት 17 ቀን 2019 ዓ.ም. ቀጣይ ቀጠሮ ሰጥቷል። | 18 307 |
| 18 | አዲስ አበባ የፌዴራል መንግስት ተጠሪ እንድትሆን ከስምምነት ሲደረስ፣ "የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ ትሁን" ለሚለው ሁለት አማራጮች ቀርበው የአዘጋጅ ቡድኑ ቃለጉባዔ ተነበበ።
35ኛ ቀኑን ባስቆጠረው ዋናው የምክክር ጉባዔ በ10፣ 50፣ 250፣ 500 ሰዎች በያዙ ቡድኖች ተመካካሪዎች ሲመክሩባቸው የነበሩ ምክረ ሀሳቦች 500 ሰዎች ከያዘው ቡድን ከደረሱ በኋላ ቡድኑ ተመካክሮባቸው ከስምንቱም ቡድኖች ለተመረጡ 120 አባላት ላሉት ምክረ ሀሳቦች አዘጋጅ ቡድን መቅረባቸው ይታወሳል።
120 አባላት ያሉት ምክረ ሀሳብ አዘጋጅ ቡድን ከባለ 500ው ቡድን የተቀበላቸውን የተመካካሪዎች ምክረ ሀሳቦች ካጣጣመ፣ የሚያቃረኑ ነገሮች እንዳይኖሩ ከተጠነቀቀ፣ ወደ አንድ ወጥ ምክረ ሀሳብ እንዲመጡ ካደረገ በኋላ 500 ሰዎች ለያዙ ለእያንዳንዱ 8 ቡድኖች አቅርቦ ከተመካካሪዎች ሰሞኑን ግብዓት ሰብስቧል።
በዛሬው መርሃ ግብር ደግሞ፣ 120 አባላት ያሉት ቡድን ያዘጋጀውና ግብዓት የሰበሰበበት ቃለጉባዔ ለእያንዳንዱ 500 ሰዎች ለያዙ 8 ቡድኖች ተነቧል። እያንዳንዱ 8 ቡድኖች ሲመክሩ የቆዩት በአንድ፣ አንድ አጀንዳ ሲሆን፣ ዛሬ በተነበባቸው ቃለጉባዔ የተመካከሩበትን አጀንዳ ጨምሮ ያልተመካከሩባቸው የ7ቱ አጀንዳ ምክረ ሀሳቦችም በአዘጋጅ ቡድኑ ተዘጋጅተው ቀርበውላቸዋል።
አከራካሪ ሆኖ በቆየው የአዲስ አበባ ጉዳይ ዛሬ በተነበበው ቃለጉባዔ ምን ተባለ ?
ስምንቱ ዝርዝር ሀሳቦች ከያዙ ዋና አጀንዳዎች መካከል በፌዴራል ከተሞች ጉዳይ፥ የአዲስ አበባ እና የድሬዴዋ ጉዳይ አንዱ ነው። በዚህም በተለይ የአዲስ አበባ ህጋዊ ጉዳይ በተመካካሪዎች በኩል ብርቱ ክርክር፣ ጭቅጭቅ፣ ምክክር ሲያስተናግድ ሰንብቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ ከምክክሩ ተሳታፊዎች እንደተረዳው፣ አዲስ አበባ ተጠሪነቷ የፌዴራል ከተማ ይሁን የሚለው ጉዳይ ተመካካሪዎችን ያስማማ በሚል በቃለባዔው ተቀምጧል።
ልዩ ጥቅም የሚለው ደግሞ "የጋራ ጥቅም" በሚለው ተተክቶ አስማምቶ ቀርቧል። ከተማዋ የፌዴራል ከተማ መሆኗ እንዳ ሆኖ፣ ሌሎች ከተሞች ይጨመሩ የሚል ምክረ ሀሳብም ተቀምጧል።
የኦሮሚያ ክልልን የወከሉ ተሳታፊዎች "አዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ እንድትሆን ሕገመግስቱ እውቅና ይስጥ" ሲሉ፣ ሌሎች ተመካካሪዎች ደግሞ፣ "አዲስ አበባ የብሔር ብሔረሰቦች ናት። ለአንድ ክልል ብቻ አትሰጥም" በሚል ተከራክረው ሀሳቡ በልዩነት ተይዞ እንደነበር ይታወቃል።
ዛሬ በተነበበው የስምንቱንም አጀንዳ ምክረ ሀሳቦች አጣጥሞ የቀረበው ቃለጉባዔ፥ "አዲስ አበባ ከተማ የኦሮሚያ ክልል ዋና መቀመጫ" እንድትሆን በቀረበው ምክረ ሀሳብ ሁለት አማራጭ ምክረ ሀሳቦች እንደተቀመጡለት ተገልጿል።
አንደኛው፥ "ሁሉም ክልሎች ርዕሰ ከተማቸውን መምረጥ ይችላሉ" የሚለው በሕግ ይደንገግ የሚል ነው።
ሁለተኛው፥ በአንቀጽ 49/5 አዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልል መቀመጫ ከመሆኗ ጋር ተያይዞ በከተማዋና በክልሉ መካከል ያለው ግንኙነት በሕግ ይደንገግ የሚል መሆኑ ተመልክቷል።
የድሬዳዋ ከተማን ጉዳይ በተመለከተ ደግሞ፣ ተጠሪነቷ ለፌዴራል መንግስቱ እንዲሆን፣ ሕገመንግስቱ እውቅና በሰጠው ቻርተው እንድትተዳደር በቃለጉባዔው ተነቧል።
ዛሬ የተነበበው የተነበበው ቃለ ጉባዔ ነገ በ4ሺሕ ጉባያኞች ይጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል። | 21 847 |
| 19 | 🚨 እስከ 35% ቅናሽ! ያለምንም ወለድ እና የዋጋ ጭማሪ በምርጥ ቦታዎች የቤት ባለቤት ይሁኑ! 🚨
ኑሮዎን በአዲስ አበባ ማዕከላዊ እና ውድ ስፍራዎች ለማድረግ አስበዋል? ቴምር ሪል ስቴት (Temer Properties) እጅግ ማራኪ በሆኑ የክፍያ አማራጮች ዘመናዊ አፓርትመንቶችን እና የንግድ ሱቆችን አቅርቦልዎታል።
✅ በየትኛው ቦታ መኖር ይፈልጋሉ?
📍 መገናኛ (ቤልቪው ሆቴል አጠገብ)
📍 ቡልጋሪያ (አፍሪካ ህብረት ፊት ለፊት)
📍 አዋሬ (ቤተመንግስት አጠገብ)
📍 ሳር ቤት (አዳምስ አጠገብ)
💰 ልዩ የክፍያ አማራጮች (በኢትዮጵያ ብር ብቻ)፡
100% ለሚከፍሉ፡ እስከ 35% ታላቅ ቅናሽ!
40% ቅድመ ክፍያ፡ የ 10% ቅናሽ ተጠቃሚ ሲሆኑ፤ ቀሪውን 60% ቤቱን ሲረከቡ ይከፍላሉ።
20% ቅድመ ክፍያ፡ ቀሪውን በ16 ዙር፣ በረጅም ጊዜ ከፍለው ይጨርሳሉ።
🏠 የአፓርትመንት አማራጮች (ከስቱዲዮ እስከ 3 መኝታ)፦
• ስቱዲዮ (ከ 32 ካሬ ጀምሮ)
• 1 መኝታ (ከ 60 ካሬ ጀምሮ)
• 2 መኝታ (ከ 90 ካሬ ጀምሮ)
• 3 መኝታ (ከ 118 ካሬ ጀምሮ)
🎯 ልብ ይበሉ፡ ክፍያው ያለምንም የባንክ ወለድ እና የግንባታ እቃዎች የዋጋ ጭማሪ የሚፈፀም ነው!
እነዚህ ውሱን ቤቶች ከመጠናቀቃቸው በፊት አሁኑኑ ይደውሉልን!
📞 +251939770177
📞 +251996856273
📱 WhatsApp: https://wa.me/251939770177
💬 Telegram: @KalTemerRealEstate | https://t.me/TemerRealEstateSalesConsultant | 16 955 |
| 20 | በፍቅር ጓደኛው ላይ የመግደል ሙከራ የፈጸመው ግለሰብ ከሦስት ዓመት ክትትል በኋላ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡
ተከሳሽ አሳየው በዛብህ የፍቅር ጓደኛው በነበረችው ግለሰብ ላይ የመግደል ሙከራ ወንጀሉን የፈጸመው ጥቅምት 11 ቀን 2012 ዓ/ም በየካ ክ/ከተማ በድሮው ወረዳ 13 የካ አባዶ አካባቢ ነው።
ተከሳሹ ለዓመታት የፍቅር ጓደኛው አድርጋው ከነበረችው የግል ተበዳይ ጋር ባለ መግባባት ተለያይተው የቆዩ ሲሆን የራሷን የተሻለ ህይወት በመጀመሯ የቅናት መንፈስ ያድርበታል። በዚህም ሳያበቃ ወደ መኖሪያ ቤቷ ሄዶ ሊያናግራት ሲሞክር የግል ተበዳይ አልፈልግህም ከህይወቴ ውጣ ስትለው በቦክስ የጀመረውን ድብደባ የሽንኩርት መክተፊያ ቢላዋ በማንሳት ከጎኗና ከእጇ ላይ በመውጋት ጉዳት አድርሶባት መሰወሩን የየካ ክ/ከተማ ዋና ፖሊስ ዋ/መምሪያ ገልጿል።
ተከሳሹ የወንጀል ድርጊቱን እንደፈጸመ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጥቆማ የደረሰው ፖሊስ ግለሰቡን በቁጥጥር ስር አውሎ በሰውና በህክምና ማስረጃ የተደገፈ መዝገብ በማደራጀት ለአቃቤ ህግ ማስረከቡን ዋና መምሪያው አስታውሷል።
ተከሳሽ በወቅቱ ዋስትና ተፈቅዶለት ጉዳዩን በውጪ ሆኖ እንዲከታተል ቢደረግም በፍ/ቤት ቀጠሮው ቀን ሳይገኝ ቀርቷል።
ተጣርቶ የቀረበለትን የምርመራ መዝገብ የተመለከተው በፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ቦሌ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ጥቅምት 3ቀን 2015 ዓ/ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ አሳየው በዛብህን በሌለበት በ7 ዓመት ከ8 ወር ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፎበታል።
ፍ/ቤቱ ፖሊስ ተከሳሹን ይዞ ለማረሚያ ቤት እንዲያስረክብ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ፖሊስ ብርቱ ክትትልና ማፈላለግ ሲያደርግ ቆይቶ ከ3 ዓመታት በኋላ ነሐሴ 8 ቀን 2018 ዓ/ም በቁጥጥር ስር አውሎ ለማረሚያ ቤት ማስረከቡን የየካ ክ/ከተማ ዋና ፖሊስ ዋና መምሪያ ገልጿል፡፡
| 19 654 |
