ETHIO-MEREJA®
News & Media Channel® Addisababa, Ethiopia🇪🇹 ውድ የኢትዮ መረጃ ቤተሰቦች ከዚህ የቴሌግራም ቻናል ውጪ ሌላ መረጃ የምናቀርብበት ምንም አይነት የዩቲዩብ፣ የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆች እንደሌለን ለማሳወቅ እንወዳለን፣ ስለሆነም በተመሳሳይ ስም በተከፈቱ ገፆች እንዳይሸወዱ ጥንቃቄ እንድታደርጉ እናሳስባለን። ለጥቆማና ማስታወቂያ ለማሰራት 👉 @ethio_merejabot
Ko'proq ko'rsatish📈 Telegram kanali ETHIO-MEREJA® analitikasi
ETHIO-MEREJA® (@ethio_mereja) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 101 636 obunachidan iborat bo'lib, Yangiliklar & Media toifasida 2 471-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 290-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 101 636 obunachiga ega bo‘ldi.
12 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -1 090 ga, so‘nggi 24 soatda esa -52 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 18.96% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 7.38% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 0 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 7 500 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 0 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“News & Media Channel®
Addisababa, Ethiopia🇪🇹
ውድ የኢትዮ መረጃ ቤተሰቦች ከዚህ የቴሌግራም ቻናል ውጪ ሌላ መረጃ የምናቀርብበት ምንም አይነት የዩቲዩብ፣ የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆች እንደሌለን ለማሳወቅ እንወዳለን፣ ስለሆነም በተመሳሳይ ስም በተከፈቱ ገፆች እንዳይሸወዱ ጥንቃቄ እንድታደርጉ እናሳስባለን።
ለጥቆማና ማስታወቂያ ለማሰራት
👉 @ethio_mere...”
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 13 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Yangiliklar & Media toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 13 Iyul | 0 | |||
| 12 Iyul | 0 | |||
| 11 Iyul | 0 | |||
| 10 Iyul | 0 | |||
| 09 Iyul | 0 | |||
| 08 Iyul | 0 | |||
| 07 Iyul | 0 | |||
| 06 Iyul | 0 | |||
| 05 Iyul | 0 | |||
| 04 Iyul | 0 | |||
| 03 Iyul | +2 | |||
| 02 Iyul | +4 | |||
| 01 Iyul | 0 |
| 2 | የመክፈያ አማራጮች፦
💰 50% ለሚከፍል፦ በካሬ ከ 70,000 ብር ጀምሮ!
📉 በ10% ቅድመ ክፍያ ፦ በካሬ ከ 80,000 ብር ጀምሮ!
ወደፊት ቦሌን በምታስንቀውና በፈጣን እድገት ላይ በምትገኘው "ቡልጋሪያ"! 🌆
ቃሉን በተግባር እየከወነ የመጣው አዲስ ላይፍ ሪል እስቴት (Addis Life Real Estate)፣ የሚያስረክበውን ድንቅ አፓርታማ በኮንዶሚኒየም ዋጋ ይዞላችሁ ቀርቧል!
⚠️ ልብ ይበሉ፦ ይህ ወርቃማ ዕድል የተለቀቀው ለ10 ቤቶች ብቻ በተዘጋጀ ልዩ ቅናሽ ነው። የቀደመ በእጅጉ ያተርፋል!
ለበለጠ መረጃ ☎️ 0937867901
☎️ 0717840668 ይደዉሉልን። | 1 883 |
| 3 | ብሔራዊ ባንክ የብድር ገደብ ሙሉ ለሙሉ አነሳ!
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በባንኮች ላይ ጥሎት የነበረውን ጊዜያዊ የብድር ገደብ ሙሉ በሙሉ ማንሳቱን አስታወቀ።
ባንኩ ይህንን የወሰነው ወደ ገበያ መር የገንዘብ ፖሊሲ ሥርዓት ለመሸጋገር ያስቀመጠው ግብ በመሳካቱ እንደሆነ ገልጿል።
ይሁን እንጂ የብድር ገደቡ መነሳት የገንዘብ ፖሊሲው መላላኩን እንደማያሳይ የገለጸው ባንኩ፣ የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር የፖሊሲ ወለድ ምጣኔውን በአንድ በመቶ እንዲጨምር አድርጓል። በተጨማሪም ባንኮች ከልክ ያለፈ ብድር እንዳይሰጡ የሚቆጣጠር አዲስ የጥበቃ ማዕቀፍ አስተዋውቋል።
በሌላ በኩል የወጪ ንግድ ወጪን ለመቀነስና ላኪዎችን ለማበረታታት፣ የውጭ ምንዛሬ ኮሚሽን ምጣኔ ከ2.5 በመቶ ወደ 1.5 በመቶ ዝቅ እንዲል ተደርጓል። የወጪ ንግድ ገቢን ለባንክ የማስረከብ ግዴታም ከ50 በመቶ ወደ 30 በመቶ ዝቅ ብሏል። | 5 950 |
| 4 | ደቡብ አፍሪካ ከ53 ሺህ በላይ የውጭ ሀገር ዜጎችን ማባረሯን ገለጸች!!
የደቡብ አፍሪካ መንግስት ከሳምንታት በፊት የጀመረውን ‹‹የስደት አስተዳደር›› ዘመቻ ተከትሎ ከ53 ሺህ በላይ የውጭ ሀገር ዜጎች ከሀገር እንዲወጡ ወይም ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ መደረጉን አስታውቋል።
ባለስልጣናት እንደገለጹት፤ አብዛኞቹ ተባራሪዎች ከማላዊ፣ ከዚምባብዌ እና ከሞዛምቢክ የመጡ ሲሆን ፥ የሀገሪቱ የመልሶ ማቋቋም እና የማባረር ሂደት አሁንም እየቀጠለ በመሆኑ ቁጥሩ ሊጨምር እንደሚችል ተገልጿል።
ደቡብ አፍሪካ ባለፉት ሳምንታት ሁከት፣ ማስፈራራት እና ዝርፊያ የታየባቸውን ፀረ-ስደተኛ ተቃውሞዎች ተከትሎ በህገ-ወጥ ስደተኞች ላይ በቅርብ አመታት ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ እርምጃ እየወሰደች ትገኛለች።
ተቃዋሚዎቹ ስደተኞች ለከፍተኛ የስራ አጥነት ችግር፣ ለወንጀል መጠን መጨመር እና ለህዝብ አገልግሎቶች መበላሸት ምክንያት ናቸው በማለት በመወንጀል፥ ጥብቅ የድንበር ቁጥጥር እንዲደረግና ሰፊ የማባረር እርምጃ እንዲወሰድ እየጠየቁ ነው።
የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ስደተኞችን ለደቡብ አፍሪካ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፈተናዎች ማስተባበያ ከማድረግ እንዲቆጠቡ አስጠንቅቋል።
የፀረ-ስደተኛ አንቀሳቃሾች ፍላጎታቸው እስኪሟላ ድረስ መንግስትን ለመጫን በየሳምንቱ ተቃውሞ እንደሚያደርጉ ያስፈራሩ ሲሆን ፥ይህም ተቃውሞ ወደ ሁከት ሊቀየር ይችላል የሚል ስጋት ፈጥሯል።
አስተያየት ሰጪዎች ህገ-ወጥ ስደተኞች ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ እስከ ሰኔ 30 ድረስ የጊዜ ገደብ ያስቀመጡ ሲሆን፥ይህም በርካታ የውጭ ሀገር ዜጎች ከጥቃት እና ከማስፈራራት ለማምለጥ ሀገሪቱን ለቀው እንዲወጡ አድርጓቸዋል። ጋና፣ ናይጄሪያ፣ ኡጋንዳ እና ኬንያን ጨምሮ በርካታ ሀገራት በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ዜጎቻቸውን ወደ ሀገራቸው መልሰዋል። | 5 731 |
| 5 | የዓለም ባንክ በቀጣዮቹ 10 ዓመታት በኢትዮጵያ ለሚያከናውናቸው ድጋፎች የፖሊሲ ለውጦች አደረገ
የዓለም ባንክ ከ2027 እስከ 2036 ያለውን የ10 ዓመታት የአጋርነት ማዕቀፍ ይፋ ያደረገ ሲሆን፣ በሚቀጥሉት 10ዓመታት ቅድሚያ ይሰጣቸው የነበሩ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን ሙሉ በሙሉ ከዕቅዱ ውጪ ማድረጉን አስታወቀ፡፡
ሪፖርተር የተመለከተው የዓለም ባንክ አዲስ የስትራቴጂ ሰነድ ትኩረቱን በዋናነት በየዓመቱ ወደ ሥራው ዓለም ለሚቀላቀሉ ወደ ሁለት ሚሊዮን ገደማ የሚሆኑ ወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር ላይ አድርጓል፡፡
ግዙፍ በመንግሥት የሚመሩ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶችን፣ ዋና ዋና የአስፋልት መንገዶችንና የቱሪዝም ዘርፍን በቀጣዮቹ አሥር ዓመታት ሙሉ በሙሉ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ፕሮጀክቶች ዝርዝር ውጪ አድርጓቸዋል፡፡
👉የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ከዕቅዱ ውጪ እንዲሆኑ የተደረጉት ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት ባደረገችው ኢንቨስትመንት በቂ የማመንጨት አቅም ስላላት ሲሆን፣ የቱሪዝም ዘርፍ ደግሞ በኢትዮጵያ ያለው የፀጥታና የመሠረተ ልማት ሁኔታ መሻሻል እስከሚታይበት ድረስ ከዝርዝሩ ውጪ እንዲሆን መደረጉን ጠቁሟል፡፡
የከተማ አውራ ጎዳናዎችን የመገንባት ዕቅድም ቀርቶ፣ በተመሳሳይ መልኩ የገጠር መንገዶችን ወደ ማስፋፋት እንዲዞር የተደረገ ሲሆን፣ ይህም አርሶአደሩ ምርቱን በቀላሉ ወደ ገበያ እንዲያቀርብ ለማገዝ፣ የጉምሩክ አሠራርን ለማዘመንና የወጪ ንግድ ወጪን ለመቀነስ ያለመ አዲስ መዋቅራዊ አቅጣጫ መሆኑ ተመልክቷል።
👉ባንኩ በቀጣይ እቅዶቹ የኤሌክትሪክ መስመር ዝርጋታ ማስተካከል፣ የኃይል መቆራረጥን መቀነስና በሚሊዮኖች ለሚቆጠር ሕዝብ የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን አስተማማኝ ማድረግ የሚሉት ይገኙበታል፡፡
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!
---ETHIO-MEREJA--
T.me/ethio_mereja | 8 816 |
| 6 | #ጤናመረጃ
10 አስገራሚ የሎሚ የጤና ጥቅሞች!
ሎሚን አዘውትሮ መጠቀም ከሚያስገኛቸው ጥቅሞች ዋና ዋናዎቹን አጠር አድርገን እንያለን።
1) በሽታ የመከላከል አቅምን ያሳድጋል፤ በቪታሚን ሲ የበለፀገ በመሆኑ ከጉንፋንና ከተለያዩ ተላላፊ ቫይረሶች ይከላከላል።
2) ለምግብ መፈጨት ሥርዓት፤ ጠዋት በለጋ ውሃ መጠጣት በጉበት ውስጥ ያሉ መርዛማ ነገሮችን ለማስወገድና አንጀትን ለማረጋጋት ይረዳል።
3) የቆዳን ውበት ይጠብቃል፤ የኮላጅን ምርትን በማፋጠን የቆዳ መሸብሸብን ይከላከላል፤ መልክን ያጠራል።
4) የኩላሊት ጠጠርን ይከላከላል፤ በውስጡ ያለው ሲትሪክ አሲድ የካልሲየም ጠጠር እንዳይፈጠርና በሽንት እንዲወገድ ያደርጋል።
5) የደም ማነስን ይከላከላል፤ ሰውነታችን ከምግብ የሚያገኘውን የብረት (Iron) ንጥረ ነገር በቀላሉ እንዲመጥ ያግዛል።
6) ለአፍ ጠረን መፍትሔ ነው፤ በአፍ ውስጥ ያሉ ባክቴሪያዎችን በማጥፋት ጠረንን ያድሳል፤ የጥርስ ሕመምንም ያስታግሳል።
7) ክብደትን ለመቀነስ ያግዛል፤ በውስጡ ያለው የፔክቲን ፋይበር የረሃብ ስሜትን የሚቀንስና ስብን ለማቃጠል የሚረዳ ነው።
8) የልብን ጤንነት ይጠብቃል፤ መጥፎ ኮሌስትሮልን በመቀነስ ለልብ ሕመም እና ለድንገተኛ ስትሮክ የመጋለጥ ዕድልን ያጠባል።
9) ካንሰርን ይከላከላል፤ በውስጡ ያሉ ተፈጥሯዊ ውህዶች (Flavonoids) የካንሰር ሴሎች እንዳይፈጠሩና እንዳይስፋፉ ይረዳሉ።
10) የደም ግፊትን ያስተካክላል፤ በውስጡ የሚገኘው ፖታሲየም የደም ስሮችን በማዝናናት የደም ግፊት ጤናማ እንዲሆን ያደርጋል።
ጠቃሚ ነውና ለወዳጆ ያካፍሉ! ሼር!
---ETHIO-MEREJA--
👉 T.me/ethio_mereja | 11 119 |
| 7 | ሞጅታባ ኻሜኒ የአባታቸውን ግድያ ለመበቀል ቃል ገብተዋል❗️
የኢራን አዲሱ የበላይ መሪ አያቶላ ሞጅታባ ኻሜኒ የተገደሉትን አባታቸውን አሊ ኻሜኒን ደም መበቀል የመላው የኢራን ሕዝብ ፍላጎት በመሆኑ የአጸፋው ርምጃ እንደሚወሰድ አስታወቁ።
👉ሞጅታባ ኻሜኒ የአባታቸው ሥርዓተ ቀብር መፈጸሙን ተከትሎ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ካለአግባብ የንጹሃንን ህይወት የቀጠፉ ወንጀለኛና ክብር የለሽ ነፍሰ ገዳዮችን ለመበቀል ቃል እንገባለን ብለዋል። ለሳምንት ያህል ሲካሄድ የቆየው የሽኝት ሥነ ስርዓት ተጠናቅቆ የኢራን የቀድሞው መሪ ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈጽሟል።
👉አሜሪካና እስራኤል በኢራን ላይ በሰነዘሩት ጥቃት አሊ ኻሜኒ መገደላቸውን ተከትሎ ኢራን ተከታታይ የአጸፋ ርምጃዎችን መውሰዷ ይታወሳል።
በሌላ በኩል ኢራን የአሜሪካውን ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕን ለመግደል አዲስ እቅድ ማውጣቷን የሚያሳዩ መረጃዎች ደርሶኛል ስትል እስራኤል በቅርቡ ለአሜሪካ የደህንነት መረጃ ማጋራቷን ተገልጿል። ይህንን ተከትሎ ፕሬዚዳንት ትራምፕ በማህበራዊ ትሰስር ገጻቸው በኩል ኢራን በእሳቸው ላይ የግድያ ሙከራ ካደረገች በሺዎች የሚቆጠሩ ሚሳኤሎችን በኢራን ላይ እንደሚተኩሱ ማስጠንቀቃቸውን የዘገበው አናዶሉ ነው።
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!
---ETHIO-MEREJA--
T.me/ethio_mereja | 10 785 |
| 8 | #የቤት_ኪራይ ከከ11.5 በመቶ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ በላይ የሚጠይቁ አከራዮች እስከ ሦስት ወር የኪራይ ክፍያ ቅጣት ይጣልባቸዋል - የአዲስ አበባ ከተማ ቤቶች ልማት ቢሮ
👉የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለዘንድሮው በጀት ዓመት የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5 በመቶ እንዲሆን ወስኗል፡፡
ይህንን ሕግ በሚተላለፉ አከራዮች ላይ ከባድ የገንዘብ ቅጣት እንደሚጣል ከኢቢሲ ዶት ስትሪም ጋር ቆይታ ያደረጉት የአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር ቤቶች ልማት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ቅድስት ወ/ጊዮርጊስ ተናግረዋል።
ጥናቱ በገለልተኝነት እና በሳይንሳዊ መንገድ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ተሳትፎ የተደረገ በመሆኑ አከራዮች ከዚህ ጣሪያ በላይ ዋጋ መጨመር እንደማይችሉ ኃላፊዋ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ይሁን እንጂ አከራዮች ከዚህ ጣሪያ በታች በሆነ ዋጋ ማከራየት ወይም ጭራሽ ያለመጨመር ሙሉ መብት እንዳላቸው የገለጹት ወ/ሮ ቅድስት፤ አሠራሩ አከራዮች በተከራዮቻቸው ላይ የዘፈቀደ ጭማሪ እንዳያደርጉ የሚገድብ በመሆኑ ለተከራዮች ትልቅ የደኅንነትና የመረጋጋት ስሜት እንደሚፈጥር አስረድተዋል።
ቤት ቋሚ ንብረት በመሆኑ በየዓመቱ የዋጋ ማሻሻያ ማድረግ ግዴታ አለመሆኑን ያነሱት ኃላፊዋ፣ 11.5 በመቶ ጭማሪው ለተከራዩም አቅም የሚመጥን እንዲሁም ለአከራዩም ቤቱን ለማደስና ለመጠገን የሚያስችል በቂ ምጣኔ ነው ብለዋል።
👉ሕጉን በመተላለፍ ከ11.5 በመቶ በላይ የኪራይ ጭማሪ በሚጠይቁ፣ ውል ሳያድሱ/ሳይመዘግቡ በሚገኙ አከራዮች ላይ የሚወሰደው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።
ውላቸውን ሳያድሱ ለተወሰኑ ወራት የሚቆዩ አከራይ እና ተከራዮች እንደየሁኔታው ከ1ወር እስከ 3ወር የቤት ኪራይ መጠን ቅጣት ይጣልባቸዋል።
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!
---ETHIO-MEREJA--
T.me/ethio_mereja | 11 056 |
| 9 | #COC በተለያዩ የማህበራዊ ገጾች "ከ2010 ዓ/ም እስከ 2015 ዓ/ም የዲግሪ ተመራቂዎች በሙሉ የትምህርት ማስረጃቸውን ለማረጋገጥ በድጋሚ ፈተና ሊፈተኑ ነው " ተብሎ የተሰራጨው መረጃ የተሳሳተ ነው።
የኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ያዘጋጀውንና ለህዝብ አስተያየት ይፋ ያዳረገውን አዲስ ረቂቅ መመሪያ በማዛበት፣ " ከ2010 እስከ 2015 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ሳይፈተኑ በመጀመሪያ፣ ሁለተኛና ሶስተኛ ዲግሪ የተመረቁ ተማሪዎች በሙሉ የትምህርት ማስረጃቸውን ለማረጋገጥ ሲባል በድጋሚ ፈተና ሊሰጣቸው ነው " በሚል እየተሰራጨ ያለው መረጃ የተሳሳተ መሆኑን ተገልጿል።
ህዝብ አስተያየት እንዲሰጥበት ይፋ የተደረገው መመሪያ የሚመለከተው፣
👉በቀድሞው ዲፕሎማ (10+3፣ 12+2 ወይም ቴክኒክና ሙያ ደረጃ 4 ስልጠና) ተመርቀው፣ ነገር ግን የደረጃ አራት የብቃት ማዕቀፍ (COC) ሳይኖራቸው የመጀመሪያ ዲግሪ፣ ሁለተኛ ዲግሪ (MA) ወይም ሦስተኛ ዲግሪ (PhD) የያዙትን ብቻ መሆኑን ተገልጿል።
👉በመደበኛው መንገድ የመግቢያ መስፈርቱን አሟልተው (ለምሳሌ #የ12ኛ ክፍል ማለፊያ አምጥተው) የገቡ፣ ወይም ከዲፕሎማ ተነስተው የCOC ፈተና አልፈው ዲግሪ የጫኑ እና የተመረቁ ዜጎችን ይህ መመሪያ አይመለከታቸውም።
👉በአጭሩ የሚመለከተው :-
- ለዲግሪ ትምህርት ከመግባታቸው በፊት የሙያ ብቃት ማረጋገጫ (COC) ፈተና ሳይወስዱ ዲግሪ የተማሩና የተመረቁ።
- የሙያ ብቃት ማረጋገጫ (COC) የወሰዱት ለዲግሪ ትምህርት ከተመዘገቡ በኋላ የሆኑ ተማሪዎች ላይ ነው።
የትምህርት ማስረጃቸውም ያለ ምንም ተጨማሪ ፈተና እንደ ቀድሞው ይረጋገጥላቸዋል።
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!
---ETHIO-MEREJA--
T.me/ethio_mereja | 11 936 |
| 10 | ውድ እና የተከበራችሁ የኢትዮ መረጃ ቻናል ቤተሰቦች፤
ላለፉት 7 ዓመታት ሳናቋርጥ ወቅታዊ እና ታማኝ መረጃዎችን ወደ እናንተ ስናደርስ መቆየታችን ይታወቃል። ሆኖም ግን ላለፉት ጥቂት ሳምንታት (ለአንድ ወር አከባቢ) ከአቅም በላይ በሆኑ የግል ምክንያቶች የተነሳ መረጃዎችን ሳናደርሳችሁ በመቆየታችን ታላቅ ይቅርታ እንጠይቃለን።
በዚህ በጠፋንበት ጊዜ ውስጥ ስለ እኛ ሁኔታ ስትጠይቁ እና ስለ እኛ ስታስቡ ለነበራችሁ ሁሉ ምስጋናችን የላቀ ነው።
አሁን ላይ ያሉብንን ጉዳዮች ሙሉ በሙሉ አስተካክለን፣ ፈጣን እና ታማኝ መረጃዎችን ከመቼውም ጊዜ በላይ በላቀ ጥራት ይዘንላችሁ ተመልሰናል።
⚠️ከዚህ ጋር አያይዘን ልናሳስባችሁ የምንወደው ነጥብ፦
ከዚህ ከምንጠቀመው የቴሌግራም ቻናል ውጪ ሌላ መረጃ የምናቀርብበት ምንም አይነት የዩቲዩብ፣ የፌስቡክም ሆነ ሌላ የቴሌግራም ገጾች እንደሌሉን ለማሳወቅ እንወዳለን።
ስለሆነም በተመሳሳይ ስም በተከፈቱ የሐሰት ገጾች እንዳይሸወዱ እና ተገቢውን ጥንቃቄ እንዳያደርጉ በጥብቅ እናሳስባለን።
ላለፉት 7 ዓመታት ለነበረን ቆይታ እና አሁንም
አብራችሁን ስላላችሁ ከልብ እናመሰግናለን!
መረጃዎቻችን ለሌሎችም እንዲደርሱ ይህንን መልዕክት እና ቀጣይ ዜናዎቻችንን ሼር (Share) በማድረግ አጋርነታችሁን እንድታሳዩን በአክብሮት እንጠይቃለን።
[ETHIO MEREJA - ኢትዮ መረጃ]
T.me/ethio_mereja | 14 498 |
| 11 | የሟቾች ቁጥር 31 ደረሰ🕯🕯
በተከሰተው የመኪና አደጋ የሟቾች ቁጥር 31 መድረሱን የኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።
ዛሬ ጠዋት በደሴ እና ኮምቦልቻ መካከል ሐረጎ በተባለ ሥፍራ በደረሰ የመኪና አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉን መዘገባችን ይታወሰል።
አሁን ደግሞ የሟቾች ቁጥር መጨመሩን ፖሊስ አስታውቋል። የኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ እንደገለጸው በአደጋው ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎች 31 ደርሷል።
አደጋው የደረሰው በተለምዶ ከደሴ ወደ ኮምቦልቻ በሚወስደው ሐረጎ "S" መንገድ መታጠፊያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ከንጋቱ 12:00 መኾኑን የኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ጌታቸው ሙህዬ ተናግረዋል።
ተሽከርካሪው ከ100 ሜትር በላይ ርዝመት ያለው ገደል ውስጥ በመግባቱ ሹፌሩን ጨምሮ የ31 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ በ33 ሰዎች ላይ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱንም ኮማንደር ጌታቸው ለአሚኮ ገልጸዋል።
ተሽከርካሪው 64 ሰዎችን አሳፍሮ በመጓዝ ላይ እንደነበር ያነሱት ኮማንደር ጌታቸው ተጎጅዎች በደሴ እና በኮምቦልቻ ሆስፒታሎች ሕክምና እየተደረገላቸው እንደኾነም አንስተዋል።
የአደጋው መንስኤም እየተጣራ መኾኑን አስታውቀዋል።
ለተጎጅ ቤተሰቦችም መጽናናትን እንመኛለን። | 20 150 |
| 12 | ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው የተለያዩ ባህላዊ እና ሌሎች ይዘቶቸ ያሏቸው የሙዚቃ ሥራዎችን ለአድማጭ ተመልካች አበርክቷል፡፡
ድምጻዊው ለሕዝብ ካበረከታቸው የሙዚቃ ሥራዎች መካከል ነይ ዘመድዬ፣ እንዴት ነሽ፣ ደቦት እንስራ፣ ዘና በይ፣ ባላገር እና ሌሎች ይገኙበታል፡፡ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ባለትዳር እና የአራት ልጆች አባት እንደነበር ፋና ዲጂታል ከቤተሰቦቹ ያገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡
ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለአድናቂዎቹ መጽናናትን ይመኛል፡፡ | 17 885 |
| 13 | አሳዛኝ አደጋ🕯🕯🕯
ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት አለፈ።
ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታውቋል።
አደጋው የደረሰው ከደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች መካከል በሚገኘው የሐረጎ መንገድ ላይ ነው።
ዛሬ ሰኔ 08/10/18ዓ.ም ማለዳ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ የሕዝብ አውቶቡስ በተለምዶ ሐረጎ እየተባለ በሚጠራው መንገድ ላይ በደረሠበት አደጋ እስካሁን የ28 ሰው ሕይወት ሲያልፍ በርካቶች ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሶባተቸዋል።
የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪው በግምት100 ሜትር ጥልቀት ወዳለው ገደል ገብቶ ነው አደጋው የደረሠው። በሕይወት የተረፉትን ወደ ሕክምና ቦታ ለማድረስ አሁንም ርብርብ እየተደረገ መኾኑን የገለጸው ፓሊስ የአደጋውን ምክንያት በመጣራት ላይ መኾኑን አስታውቋል። | 17 132 |
| 14 | ደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ የሚገኘውን የግብፅ ወታደራዊ ጣቢያ ዘጋች
ደቡብ ሱዳን በላይኛው ናይል ግዛት፣ በፓጋክ አካባቢ ሲንቀሳቀስ የቆየውን የግብፅ ወታደራዊ ጣቢያ እንዲዘጋ ትዕዛዝ አስተላለፈች። የኢትዮጵያ ድንበርን አዋሳኝ በሆነው በዚህ አካባቢ የነበረው ጣቢያ፣ ግብፅ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ያላትን ጥቅም ለማስጠበቅ ትጠቀምበት የነበረ ስትራቴጂያዊ የክትትል ማዕከል እንደነበር ተገልጿል።
ይህ የደቡብ ሱዳን ውሳኔ በአካባቢው የኃይል ሚዛን ላይ ትልቅ ለውጥ የሚያመጣ እንደሆነ የፓለቲካ ተንታኞች የገለፁ ሲሆን፣ ሀገሪቱ በሱዳን የእርስ በርስ ግጭት ሳቢያ የተስተጓጎለውን የነዳጅ ንግድ ለማካካስ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የኢኮኖሚና የመሠረተ ልማት ትስስር ለማጠናከር ያላት ፍላጎት መገለጫ እንደሆነ ይስማሙበታል።
በፓጋክ የነበረው የግብፅ ወታደራዊ ጣቢያ የቴክኒክና የሎጀስቲክስ ባለሙያዎችን ጨምሮ ወደ 260 የሚጠጉ ግብጻውያን ይገኙበት እንደነበር ተጠቅሷል። የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ባለፉት ሳምንታት ውጥረት ውስጥ እንደነበር የሚነገር ሲሆን፣ የደቡብ ሱዳን ወቅታዊ ውሳኔ በቀጠናው የፖለቲካ አሰላለፍ ላይ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኗል። | 19 098 |
| 15 | በምሽት ክበብ ውስጥ በተነሳ ግጭት የሰው ህይወት ማለፉን ተከትሎ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊስ ገለጸ
በአዲስ አበባ ከተማ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ቱሉ ዲምቱ በሚገኝ ሆልስቴ ሆቴል ውስጥ ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት ላይ በሰዎች መካከል ጠብ ተነስቶ ነበር።
በዚህ ግጭት ወቅት አቡሽ ባዩ የተባለ ግለሰብ በሽጉጥ ተመትቶ ህይወቱ ሊያልፍ ችሏል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ እንደታወቀው ከድርጊቱ ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ 12 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራውን በስፋት እየገፋበት ይገኛል።
ከተያዙት ግለሰቦች መካከል በፀቡ ላይ በቀጥታ የተሳተፈ አንድ ሰው፣ ከዋናው ገዳይ ጋር አብሮ ሲዝናና የነበረ ሌላ ተጠርጣሪ እንዲሁም ለግጭቱ መነሻ እንደሆነች የተጠረጠረች አንዲት አስተናጋጅ ይገኙበታል።
በወቅቱ በነበረው አለመግባባት ሳቢያ በሰዎችና በንብረት ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን፣ ወንጀሉን የፈጸመው ግለሰብ ሟች ታጥቆት የነበረውን ሽጉጥ ቀምቶ እንደተኮሰበት የሚያሳዩ ፍንጮችን ማግኘቱን ፖሊስ ጠቁሟል።
የጉዳዩን ዝርዝር የምርመራ ውጤት ወደፊት ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግም አስታውቋል።
በሌላ በኩል ፖሊስ ከዚህ ድርጊት ጋር ተያይዞ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የከተማዋን ነባራዊ የሰላም ሁኔታ የማይገልጽ የተዛባ መረጃ እየተሰራጨ መሆኑን ገልጿል።
ህብረተሰቡ የሀሰት ወሬዎችንና አሉባልታዎችን ወደ ጎን በመተው ትክክለኛውን መረጃ ከታማኝ የመረጃ ምንጮች ብቻ የመቀበል ልምዱን ሊያሳድግ እንደሚገባ ያሳሰበው መምሪያው፣ የስጋት ድባብ ለመፍጠር የሚሰሩ አካላትን በተባበረ ክንድ ለማክሸፍ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ | 27 152 |
| 16 | በአርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ የደረሰውን የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች በተመለከተ ኢሰመኮ የሰጠው መግለጫ!!
መንግሥት ተገቢውን ምርመራ በማካሄድ ተጠያቂነትን የማረጋገጥ እና ተጎጂዎችን ለመካስና ለማቋቋም የሚያስችሉ እርምጃዎችን ሊወስድ ይገባል
. . . . .
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ግንቦት 23 እና 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተፈጸመውን ጥቃት በተመለከተ ክትትል እና ምርመራ እያከናወነ ይገኛል፡፡ ኢሰመኮ ይህ መግለጫ ይፋ እስከተደረገበት ጊዜ ድረስ በአካባቢው በአካል በመገኘት ከዐይን እማኞች፣ ከተጎጂዎች፣ ከተጎጂ ቤተሰቦች፣ እና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ባሰባሰባቸው መረጃዎችና ማስረጃዎች ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው “በተለምዶ ኦነግ ሸኔ” ታጣቂ ቡድን በፈጸመው ጥቃት የመንግሥት የጸጥታ ኃይል አባላትና ሲቪል ሰዎች መገደላቸውን፣ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን፣ የንብረት ውድመት እና ቃጠሎ መድረሱን ለማረጋገጥ ችሏል።
ኢሰመኮ በምርመራ ሂደቱ እንዳረጋገጠው በአሰኮ ወረዳ ደለተ ጫፋ ቀበሌ አካባቢ ከግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ የታጣቂዎች እንቅስቃሴ በመስተዋሉ የአካባቢው ሚሊሻዎችና የኦሮሚያ ጸረ ሽምቅ ውጊያ ፖሊስ አባላት በስፍራው በመሰማራታቸው “በተለምዶ ኦነግ ሸኔ” ተብሎ በሚጠራው ታጣቂ ቡድን እና በተሰማሩ የጸጥታ አካላት መካከል ግጭት ተፈጥሯል። ግጭቱን ተከትሎ የአካባቢው ነዋሪ የሆኑ ሰዎች ላይ ታጣቂ ቡድኑ ባደረሰው ጥቃት ከአካባቢው መሸሽ ባልቻሉ ኃይሉ ንጉሴ እና ሰሙ አባይነህ በተባሉ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንዲሁም በአካባቢው ከብቶች በመጠበቅ ላይ የነበረ ባቶ ሰፈኖ የተባለ የእስልምና እምነት ተከታይ በአጠቃላይ የሦስት ሲቪል ሰዎች ሕይወት ሊያልፍ ችሏል።
በተጨማሪም ቁጥራቸው ለጊዜው በውል ባልታወቁ ቤቶች ላይ ቃጠሎ መድረሱን፣ የጠለታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን መቃጠሉን፤ ቢዮ ቡጡሌ የሼክ ሙስተፋ መስጅድ አጥር ላይ ጉዳት መድረሱን፣ በድለተ ጫፋ ጤና ጣቢያ፣ በነዋሪዎች መኖሪያ ቤቶችና የንግድ መደብሮች ላይ በመደዳ ዘረፋ መፈጸሙን እንዲሁም ከ2,650 በላይ የሚገመቱ የአካባቢው ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ኢሰመኮ አረጋግጧል።
ኢሰመኮ በአርሲ ዞን በሽርካ፣ በአሰኮ፣ በአንቆሎ ዋቤ፣ ጉና እና መርቲ ወረዳዎች ላይ በታጣቂዎቹ ሲፈጸሙ የነበሩ ጥቃቶች ዳግም እንዳይከሰቱ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደረግ እና ጥቃት ፈጻሚዎች ላይ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ በተለያዩ ጊዜያት ማሳሰቡ ይታወሳል። መንግሥት በአካባቢው ላይ በተደጋጋሚ መሰል ጥቃቶች እና የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች መከሰት መቀጠላቸው አሳሳቢ መሆኑን ከግምት በማስገባት ጥቃት በተፈጸመባቸው አካባቢዎች የጀመራቸውን ጥረቶች በማጠናከር በአስቸኳይ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እንዲሰማሩ እና ሰላምና ደኅንነትን በማረጋገጥ ነዋሪዎችን ወደ ተረጋጋ ሕይወት የመመለስ ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም በመንግሥትና በሌሎች አጋር አካላት በጥቃቶቹ ምክንያት ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ነዋሪዎች በቂ የሆነ የአስቸኳይ የሰብአዊ ድጋፍ እንዲቀርብና ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው ተመልሰው በዘላቂነት የሚቋቋሙበት ሁኔታ እንዲመቻች ኢሰመኮ ያሳስባል። በሌላ በኩል ኢሰመኮ ጉዳዩን አስመልክቶ ዝርዝር የምርመራ ሪፖርት ይፋ የሚያደርግ መሆኑን እየገለጸ፤ የተፈጸሙ ጥቃቶችን በአግባቡ ሳያረጋግጡ የሚሰነዘሩ ፍረጃዎችና ቅስቀሳዎች ተጨማሪ ግጭት እንዲፈጠር የማነሳሳት ዕድላቸው ሰፊ በመሆኑ ማናቸውም ተቋማትም ሆኑ ግለሰቦች ከዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ጥሪ ያቀርባል።
የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ ኢሰመኮ በዜጎች ላይ ለደረሰው ሞትና ጉዳት ማዘኑን ገልጸው በሲቪል ሰዎች ላይ የተፈጸሙት የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች አሳሳቢ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ አክለውም መንግሥት ሁኔታውን ለማረጋጋት እና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ ያከናወናቸው ተግባራት መቀጠል ያለባቸው መሆኑን ጠቅሰው፤ በማንኛውም ጊዜ የጸጥታ ሥጋት ባለባቸው አካባቢዎች ሁሉ በቂ የጸጥታ ኃይሎች በመመደብና ተመሳሳይ ጥቃቶችን የመከላከል ሥራ በመሥራት የነዋሪዎች በሕይወት የመኖር፣ የአካል ደኅንነት እና የንብረት መብቶች ለአደጋ እንዳይጋለጡ እንዲያደርግ፣ ተገቢውን ምርመራ በማካሄድ ተጠያቂነትን የማረጋገጥ እና ተጎጂዎችን ለመካስና ለማቋቋም የሚያስችሉ እርምጃዎችን እንዲወስድ እንዲሁም ሁሉም አካላት የተፈጠሩ ችግሮችን ከማውገዝ ባሻገር ግጭት ቀስቃሽ ከሆኑ መግለጫዎች እና ድርጊቶች እንዲታቀቡ ጥሪ አቅርበዋል። | 24 772 |
| 17 | Matn yo'q... | 19 938 |
| 18 | ሰላም የአዲስ ላይፍ ቤተሰቦች እስካሁን በ3ቱ ጵሮጀክቶች የሰጣችሁንን እምነት ይዘን ፣ አዲስና እጅግ ዘመናዊ የሆነዉን 4ተኛዉን ጵሮጀክታችንን በቡልጋሪያ ይዘንላቹ መምጣታችንን ስንገልፅ በታላቅ ደስታ ነዉ።
ታዲያ ይህን ድንቅ ኪነ ህንፃ ላይ ለመኖር ቀድሞ ለወሰነ ደንበኛ የቅድመ ጵርጀክት ማሰጀመሪያ ልዩ ጥቅምን አዘጋጅተን በካሬ ከ80,750ጀምሮ እየሸጥን እንገኛለን።
ልብ ይበሉ አዲስ ላይፍ ሰርቶ በማሰረከብ እና በግንባታ ጥራት የማይታማ ድርጅት መሆኑን ሳይዘነጉ ይህን እድል አሁኑኑ ይጠቀሙ።
ለበለጠ መረጃ በ0937867901
ይደዉሉ። | 27 715 |
| 19 | ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናችን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ።
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት እንደሚከተለው ነው፦
መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡
‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።››
(መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪)
በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው።
የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል።
በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።
በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት | 31 885 |
| 20 | Matn yo'q... | 26 068 |
