ETHIO-MEREJA®
News & Media Channel® Addisababa, Ethiopia🇪🇹 ውድ የኢትዮ መረጃ ቤተሰቦች ከዚህ የቴሌግራም ቻናል ውጪ ሌላ መረጃ የምናቀርብበት ምንም አይነት የዩቲዩብ፣ የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆች እንደሌለን ለማሳወቅ እንወዳለን፣ ስለሆነም በተመሳሳይ ስም በተከፈቱ ገፆች እንዳይሸወዱ ጥንቃቄ እንድታደርጉ እናሳስባለን። ለጥቆማና ማስታወቂያ ለማሰራት 👉 @ethio_merejabot
Mostrar más📈 Análisis del canal de Telegram ETHIO-MEREJA®
El canal ETHIO-MEREJA® (@ethio_mereja) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 100 668 suscriptores, ocupando la posición 2 573 en la categoría Noticias y medios y el puesto 293 en la región Etiopía.
📊 Métricas de audiencia y dinámica
Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 100 668 suscriptores.
Según los últimos datos del 02 agosto, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -1 386, y en las últimas 24 horas de -32, conservando un alto alcance.
- Estado de verificación: No verificado
- Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 13.38%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 8.76% de reacciones respecto al total de suscriptores.
- Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 13 469 visualizaciones. En el primer día suele acumular 8 815 visualizaciones.
- Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 42.
📝 Descripción y política de contenido
El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“News & Media Channel®
Addisababa, Ethiopia🇪🇹
ውድ የኢትዮ መረጃ ቤተሰቦች ከዚህ የቴሌግራም ቻናል ውጪ ሌላ መረጃ የምናቀርብበት ምንም አይነት የዩቲዩብ፣ የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆች እንደሌለን ለማሳወቅ እንወዳለን፣ ስለሆነም በተመሳሳይ ስም በተከፈቱ ገፆች እንዳይሸወዱ ጥንቃቄ እንድታደርጉ እናሳስባለን።
ለጥቆማና ማስታወቂያ ለማሰራት
👉 @ethio_mere...”
Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 03 agosto, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Noticias y medios.
Carga de datos en curso...
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 02 agosto | 0 | |||
| 01 agosto | 0 |
| 2 | አሜሪካዊ አጋር ያገኘው የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከ60 ሺሕ በላይ ሯጮችን ሊያሳትፍ ነው
የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ለ26ኛ ጊዜ የሚዘጋጀው ዓመታዊው ውድድር በመጪው ኅዳር 13 ቀን 2019 ዓ.ም. የሚካሄድ ሲሆን፣ በአዲስ ዋና ስፖንሰር በከፍተኛ ጥራት ለማከናወን መዘጋጀቱን ከትናንት በስቲያ በሐያት ሬጀንሲ ሆቴል በተዘጋጀ የምዝገባ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተገልጿል።
በታሪኩ ከፍተኛውን ቁጥር ከ60 ሺሕ በላይ ተሳታፊዎች ለመቀበል በታሰበበት የሩጫ መድረኩ፣ በአሜሪካው «ባንክ ኦፍ አሜሪካ» ዋና አጋርነትና የስያሜ መጠሪያ ጋር የሚካሄድ ነው፡፡
ባንኩ ከዚህ ቀደም በተደረገው ስምምነት መሠረት እስከ 2030 ድረስ በአጋርነት ይሠራል። ከዋናው የ10 ኪሎ ሜትር ሩጫ ባሻገርም የሴቶቹን የ5 ኪሎ ሜትር «ቅድሚያ ለሴቶች» ውድድር በዋና አጋርነት ይቀጥላል።
የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር ዳግማዊት አማሩ እንዳስታወቁት፣ ይህ ትብብር በአገሪቱ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ትልቅ ዕድል የሚፈጥርና ማኅበረሰቡን ከማስተዋወቅ ባለፈ በርካታ አዳዲስ ዕድሎችን የሚፈጥር ነው። ውድድሩ ከ2017 ዓ.ም. ጀምሮ የዓለም አትሌቲክስ ደረጃን ያገኘና በየጊዜውም አዳዲስ ተሰጥዖዎችን እያፈራ መምጣቱንም አስታውሰዋል።
የ2019 የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የ10 ኪሎ ሜትር ሩጫ ምዝገባ ከትናንት በስቲያ የተጀመረ ሲሆን፣ ምዝገባው በቴሌብር መተግበሪያ ብቻ እንደሚከናወን ተገልጿል። የሩጫው ዋና መሪ ቃልም «ሩጫዬ፣ ቀለሜ» መሆኑ ይፋ ሆኗል።
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!
-ETHIO-MEREJA-
T.me/ethio_mereja | 3 658 |
| 3 | 👉Studio 32ካሬ 1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ 2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና 3 መኝታ ከ 118ካሬ ጀምሮ
👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት
👉100% ለሚከፍሉ እስከ 35% ቅናሽ
👉20% ከፍለው ቀሪውን በ 16 ዙር ከፍለው የሚጨርሱት
👉 በመገናኛ ዲያስፖራ አደባባይ ፊት ለፊት(BELLEVUE) ሆቴል አጠገብ (የካ ክፍለ ከተማ ጀርባ) ከቴምር ሪልስቴት
👉በተጨማሪም በቡልጋሪያ(አፍሪካ ህብረት ፊት ለፊት) እና በአዋሬ(ቤተመንግስት አጠገብ) አፓርትመንቶች አሉን
💥 የንግድ ሱቆች
#ቡልጋሪያ ላይ ከ900ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ፒያሳ ላይ ከ1.4ሚሊዮን ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ቃሊቲገላን ላይ ከ500ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ።
#ሳር ቤት አዳምስ አጠገብ ከ 900ሺ ብር ቅድመ ክፍያ
🎯ልብይበሉ
# ያለምንም ወለድና የግንባታ እቃዎች ጭማሪ በኢትዮጵያ ብር ከፍለው የሚጨርሱት ነው
#ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
👇👇👇👇👇👇
+251939770177
+251996856273
https://t.me/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp. https://wa.me/251939770177
Telegram :@KalTemerRealEstate | 6 358 |
| 4 | ተራዝሟል!!
የመኖሪያ ቤት አከራይ ተከራይ ውል እድሳት እስከ ነሀሴ 30 /2018 ዓ.ም ድረስ ተራዘመ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የዜጎችን የኑሮ ጫና ለመቀነስ እና በኪራይ ገበያው ላይ የሚስተዋሉ ህገ-ወጥና ዘፈቀዳዊ አሰራሮችን በዘላቂነት ለመግታት እየወሰደ ባለው እርምጃ የቤት ኪራይ ጭማሪ ጣሪያ 11.5% ሆኖ መወስኑን ተከትሎ የውል እድሳት ምዝገባም ከ ሐምሌ 1 / 2018 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል፡፡
ይህንን ተከትሎ በመላው ከተማዋ የሚገኙ የግል መኖሪያ ቤቶች የአከራይ-ተከራይ የውል እድሳት ምዝገባ ግዜ እስከ እስከ ሀምሌ 30 /2018 ዓ.ም የነበረው እስከ ነሀሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ መራዘሙን የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ አሳውቋል።
የውል እድሳት ግዜው በህብረተሰቡ ጥያቄ መስረት የተራዘመ ሲሆን ነዋሪው ያለምንም መጨናነቅ እንዲዋዋል ታሳቢ ያደረገ መሆኑንም ቢሮው ገልጿል።
ህብረተሰቡ በሁሉም ክፍለ ከተማ ቤቶች አስተዳደር ፅ/ቤት ፤ በየወረዳው በተዘጋጁ የውል ቦታዎች እና በሁሉም ክፍለ ከተማ አዲስ መሶብ አስፈላጊውን መረጃ ይዞ በመገኘት አገልግሎቱን ማግኘት የሚቻል መሆኑን ቢሮው በድጋሚ ያሳውቃል፡፡
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ | 6 423 |
| 5 | የቀድሞው የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት እና በአሁኑ ወቅት የጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ አማካሪ የሆኑት አቶ ጌታቸው ረዳ፣ የትግራይ ሰራዊት አመራሮችና አባላት በጥቂት የህወሓት ፖለቲከኞች ተገፋፍተው ክልሉን ዳግም ወደ እልቂት ከመክተት እንዲቆጠቡ አሳሰቡ።
አቶ ጌታቸው በኤክስ ገጻቸው የደብረ ጽዮንን ንግግር አያይዘው ባሰራጩት እጅግ ነቀፋ የበዛበት መልእክት፣ የህወሓት አመራሮች የትግራይን ህዝብ አንድነት በመበተን እንዲሁም በፋኖ፣ በሱዳኑ ጄኔራል አል-ቡርሃን እና በኤርትራ መንግስት (ሻዕቢያ) ላይ ተማምነው ዳግም ጦርነት ለመክፈት የሚያደርጉት ፉከራ የሚያመጣው ለውጥ እንደሌለ ገልጸዋል። በዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል፣ በወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር (ሞንጆሪኖ) እና በቀድሞው የደህንነት ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ መሪነት፣ በጉልበት "አራት ኪሎ እንመለሳለን" በማለት የሚያልሙትን "ቅዠት" በአስቸኳይ እንዲያቆሙ አስጠንቅቀዋል።
ከፌደራል መንግስቱ ጋር በቅርበት እየሰሩ የሚገኙት አቶ ጌታቸው፣ የትግራይ ሰራዊት ከምንም በላይ የህዝቡን ደህንነት እንዲያስቀድም ጥሪ አቅርበዋል። አቅም እያለ የህዝቡን የህልውና ጥያቄዎች መመለስ የሚቻለው በሰላማዊ መንገድ ብቻ መሆኑን በማስገንዘብ፣ ሰራዊቱ በህይወቱና በአካሉ ላይ እየተቆመረበት ያለውን ኃይል 'ይበቃል' ሊለው እንደሚገባ አሳስበዋል።
በመጨረሻም "በሐውልቲ (የህወሓት ጽህፈት ቤት) የመሸገው የብጥብጥ ቡድን" ሲሉ የጠሯቸው እነዚህ አካላት፣ በፉከራና በውጭ ኃይሎች ድጋፍ ላይ በመተማመን የዲፕሎማሲ በሮችን ከዘጉ በኋላ፣ አሁን መሬት ላይ ያለው እውነት ሲከብዳቸው "ዓለም ይድረስልኝ" እያሉ መጮሃቸው ማመዛዘን የጎደለው የፖለቲካ ኪሳራ መሆኑን በአጽንኦት ተችተዋል። | 10 556 |
| 6 | 👉Studio 32ካሬ 1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ 2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና 3 መኝታ ከ 118ካሬ ጀምሮ
👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት
👉100% ለሚከፍሉ እስከ 35% ቅናሽ
👉20% ከፍለው ቀሪውን በ 16 ዙር ከፍለው የሚጨርሱት
👉 በመገናኛ ዲያስፖራ አደባባይ ፊት ለፊት(BELLEVUE) ሆቴል አጠገብ (የካ ክፍለ ከተማ ጀርባ) ከቴምር ሪልስቴት
👉በተጨማሪም በቡልጋሪያ(አፍሪካ ህብረት ፊት ለፊት) እና በአዋሬ(ቤተመንግስት አጠገብ) አፓርትመንቶች አሉን
💥 የንግድ ሱቆች
#ቡልጋሪያ ላይ ከ900ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ፒያሳ ላይ ከ1.4ሚሊዮን ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ቃሊቲገላን ላይ ከ500ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ።
#ሳር ቤት አዳምስ አጠገብ ከ 900ሺ ብር ቅድመ ክፍያ
🎯ልብይበሉ
# ያለምንም ወለድና የግንባታ እቃዎች ጭማሪ በኢትዮጵያ ብር ከፍለው የሚጨርሱት ነው
#ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
👇👇👇👇👇👇
+251939770177
+251996856273
https://t.me/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp. https://wa.me/251939770177
Telegram :@KalTemerRealEstate | 13 268 |
| 7 | በምክክር ሂደቱ የቀረቡ የአጀንዳ ምክረ ሀሳቦች በ75 በመቶ አባላት ተቀባይነት ካገኙ ከመግባባት እንደተደረሰ ጠቋሚ ነዉ የተባለለት የምክክር ምዕራፍ በመጪዉ ሰኞ ይጀመራል ተባለ
የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በባለፉት ሁለት ቀናት 2መቶ50 ተመካካሪዎች በቡድን በመከፋፈል ዉይይት ሲያደርጉ መቆየታቸዉን ዛሬ በሰጠዉ መግለጫ አሳዉቋል።
በዚህ የምክክር ምዕራፍ የተጀራጁ ምክረ ሀሳቦች 5መቶ አባላት ወዳሉት ቀርበዉ ፤ እነዚህ የ5 መቶ አባላት ተመካካሪዎች ቡድን ለውሳኔ መግባቢያ ሀሳብ ያደራጁታል ተብሏል።
እንደ ኮሚሽኑ መረጃ 5መቶ አባላት ያሏቸው ተመካካሪ ቡድኖች እያንዳንዳቸው በአንድ አጀንዳ ላይ የሚወያዩ ሲሆን፤በአጀንዳው ላይ ከመግባባት ደረሰ የሚባለው በዉይይቱ የመነጩ የመፍትሄ ሀሳቦች በ75 በመቶ አባላቱ ከመግባባት የተደረሰባቸው ወይም ተቀባይነት ያገኙ እንደሆነ ነው።
ሌላዉ የምክክሩ የውሳኔ አሰጣጥ አካል የሆነው አካሄድ ከክልል እና ከፌደራል አባላት ተመርጠዉ የሚዋቀረዉ የክልላዊ ጉባኤ ሲሆን፤በዛሬዉ ዕለት 3 መቶ 30 ተወካዮች እንደተመረጡ ኮሚሽኑ በሰጠዉ መግለጫ ተናግሯል።
12 ክልሎች እና 2 ከተማ አስተዳደሮች እንዲሁም የፌደራል ተቋማት ከእያንዳንዳቸው 22 ተወካዮች ተወጣጥተው የተዋቀረ ቡድን መሆኑን የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ ገልፀዋል።
በዚህ ቡድን 70 በመቶ ድምጽ ባለማግኘቱ ውድቅ በተደረገ የአጀንዳ የምክር ሀሳብ ላይ ቢያንስ ሶስት ክልሎች ቅሬታ ያቀረቡ እንደሆነ ያንን የሚፈቱበት አግባብ የሚኖር ነዉ ተብሏል። በቀደሙት የድምፅ አሰጣጥ ሂደቶች 70 በመቶ ድምጽ ማግኘት ሳይችል የቀረ የአጀንዳ ምክረ ሀሳብ በዚህ ቡድን በድጋሚ ታይቶ የሚጠበቀውን ዝቅተኛ የ70 በመቶ መስፈርት ካሟላ ወደ ሚቀጥለው ምዕራፍ የሚሸጋገር ይሆናል። | 12 770 |
| 8 | የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ለሁለት የሚዲያ ተቋማት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ ሰጠ።
ባለሥልጣኑ በአዋጅ ቁጥር 1238/2013 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት የሚዲያ ተቋማት ሕግና የሙያ ሥነ ምግባርን አክብረው መስራታቸውን እየተከታተለ ድጋፍና እርምት በማድረግ ላይ ይገኛል።
በዚሁ መሠረት፦
• አሐዱ ኤፍ ኤም 94.3 እና
• አርትስ ቴሌቪዥን
የተሰጣቸውን የይዘት ግዴታዎች በመተላለፍ፣ ለተከታታይ ጊዜ ያልተረጋገጠ፣ ሚዛናዊ ያልሆነ እንዲሁም የሕዝብን ጥቅም የሚጎዳ መረጃ በማሰራጨታቸው የመጨረሻ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ በባለስልጣኑ ተሰጥቷቸዋል።
ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ከሬድዮ እና ከቴሌቪዥን ጣቢያዎቹ ኃላፊዎች ጋር በተስተዋሉ ተደጋጋሚ የህግና የሙያ ጥሰቶች ላይ ውይይቶች ያደረገ ቢሆንም ጉልህ ለውጥ ሳይታይ በመቅረቱ ማስጠንቀቂያ መስጠቱን ያስታውቃል፡፡
ስለሆነም ጣቢያዎቹ በቀጣይ ሥራቸውን በሕግና በሙያ ሥነ ምግባር መሠረት እንዲያከናውኑ በጥብቅ ለማሳሰብ ይወዳል።
ባለስልጣኑ ማስጠንቀቂያው በመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 አንቀጽ 74/ሠ መሠረት የተሰጠ መሆኑን እየገለፀ ሚዲያዎቹ ተመሳሳይ የህግ መተላለፍ እና ጥሰት እየፈፀሙ የሚቀጥሉ ከሆነ በህጉ መሠረት ቀጣይ አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወስድ ባለሥልጣኑ ያስታውቃል።
ባለስልጣኑ የሚዲያ ተቋማት በሁሉም የዘገባ ስራዎቻቸው ላይ የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ እና የሀገሪቱን ሕጎች እንዲሁም የዘርፉን የሙያ ሥነ ምግባር አክብሮ መስራት የሁሉም ግዴታ መሆኑን ለአፍታም ሊዘነጉት እንደማይገባ ያሳስባል። | 13 397 |
| 9 | ወደ ስዊድን ያቀኑ 20 የእግርኳስ ቡድን አባላት መጥፋታቸው ተሰማ
ወደ ስዊድን ያቀኑ ዕድሜያቸው ከ 14 እስከ 17 የሚገመት 20 ታዳጊ የእግርኳስ ተጫዋቾች ከ መሪያቸው ጋር መጥፋታቸውን ስዊድን ሄራልድ ዘግቧል።
"ጎቲያካፕ" ለተሰኘ የእግር ኳስ ውድድር ከኢትዮጵያ የሔዱት ታዳጊዎች ካረፉበት ትምሕርት ቤት ሳያሳውቁ በመውጣት መሰወራቸውን የስዊድን ፖሊስ አስታውቋል።እግር ኳስ ተጫዋቾቹ ወደ ኢትዮጵያ እንዳልተመለሱ ያረጋገጠው ፖሊስ፤ በራሳቸው ፍላጎት ጠፍተው ሊሆን እንደሚችል አመላክቷል።
በጉዳዩ ዙርያ ምላሽ የሰጠው ፌደሬሽኑ የቡድኑ አባላት መጥፋት እንዳሳዘነው እና ታዳጊዎቹ በመሰል ውድድሮች ላይ በራሳቸው ጥረት በሚያገኙት እድል ወደ ውድድሩ ማምራታቸውን አሳውቋል።
በመሆኑም ታዳጊዎቹ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የወከሉ አለመሆኑን እየገለፅን በአንዳንድ አካላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ እየተገለጸበት ያለው መንገድ ትክክል አለመሆኑን እናሳውቃለን ብሏል ፌደሬሽንኑ።
ፖሊስ የጠፉት ታዳጊዎች ዕድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሆኑ ወጣቶች ሲሆኑ፣ ከእነሱ ጋር አንድ ወይም ከዚያ በላይ የቡድን መሪዎች አብረው ጠፍተዋል ብሏል። ይህ የታወቀው በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ሲሆን ያረፉበት ትምህርት ቤት አስተዳዳሪ አባላቱ ያለ ምንም ማስታወቂያ ለቀው መሄዳቸውን ካረጋገጠ በኋላ ለፖሊስ ማሳወቁም ተዘግቧል። | 14 798 |
| 10 | በምስራቅ አርሲ ዞን በታጣቂዎች የተፈጸሙ ከባድ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ይፋ ሆኑ
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በታጣቂ ቡድኖች በተፈጸሙ ጥቃቶች ላይ ያከናወነውን የምርመራ ግኝት የያዘ 158ኛ ልዩ መግለጫውን ይፋ አድርጓል። በዞኑ በሚገኙ ሽርካ፣ ሮቤ፣ ጀጁ፣ መርቲ፣ ጉና፣ ሆንቆሎ ዋቤ፣ አርሲ ሲሬ፣ ሙኒሳ እና አሰኮ ወረዳዎች በተፈጸሙት ጥቃቶች በሃይማኖትና ማንነት ላይ ያነጣጠሩ የሰዎች ግ ድያ፣ አካል ጉዳት፣ እገታ፣ መፈናቀል እና የንብረት ውድመት መከሰታቸው ተረጋገጧል።
ኢሰመጉ ከመጋቢት 3 እስከ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረገው የመስክ ምርመራና ከሟች ቤተሰቦች፣ ተጎጂዎች፣ የዓይን እማኞች እና የአርሲ ሀገረ ስብከት ቤተክህነት ጽሕፈት ቤቶች ባሰበሰባቸው መረጃዎች መሰረት በጥቃቱ በርካታ ንጹሃን ዜጎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ዓ.ም የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች የምርመራ ስራን አከናውኗል፡፡
በተሰበሰበው መረጃ መሰረት:-
📌 በሽርካ ወረዳ 116፣
📌 በመርቲ ወረዳ 117፣
📌 በጀጁ ወረዳ 101፣
📌 በሮቤ ወረዳ 47፣
📌 በጉና ወረዳ 26፣
📌 በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 20፣
📌 በሙኒሳ ወረዳ 19፣
📌 በአሰኮ ወረዳ 5 ንጹሃን እና 4 የጸጥታ አካላት (ሚሊሻዎች) እንዲሁም
📌 በሲሬ ወረዳ 3 ሰዎች ተገ ድለዋል።
ከግድ ያው በተጨማሪ ከፍተኛ የእገታ ወንጀል የተፈጸመ ሲሆን፣
📍በሮቤ ወረዳ 156 ሰዎች፣
📍በጀጁ ወረዳ 182 ሰዎች፣
📍በመርቲ ወረዳ 29 ሰዎች
📍በሽርካ ወረዳ 39 ሰዎች ታግተው በርካቶቹ በካሳ ክፍያ የተለቀቁ ቢሆንም የበርካታ ታጋቾች የደረሱበት ሁኔታ እስከ አሁን አይታወቅም። እንዲሁም በሕፃናትና አዛውንቶች ላይ የቆሰሉና አካል ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ከቀያቸው ተፈናቅለዋል።
የአሰኮ ወረዳ የጠለታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያንን ጨምሮ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት መዘረፋቸውና መቃጠላቸው፣ የመኖሪያ ቤቶች መፍረሳቸው እና የቀንድና የጋማ ከብቶች መዘረፋቸው በምርመራው ተረጋግጧል።
ኢሰመጉ መንግስት የዜጎችን በሕይወት የመኖርና የንብረት ጥበቃ የማድረግ ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታውን እንዲወጣ፣ በጥሰቱ የተሳተፉ አካላት በሕግ እንዲጠየቁ እና ለተፈናቀሉት ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል። | 15 325 |
| 11 | #ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
👉Studio 32ካሬ 1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ 2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና 3 መኝታ ከ 118ካሬ ጀምሮ
👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት
👉100% ለሚከፍሉ እስከ 35% ቅናሽ
👉20% ከፍለው ቀሪውን በ 16 ዙር ከፍለው የሚጨርሱት
👉 በመገናኛ ዲያስፖራ አደባባይ ፊት ለፊት(የካ ክፍለ ከተማ ጀርባ) ከቴምር ሪልስቴት
👉በተጨማሪም በቡልጋሪያ(አፍሪካ ህብረት ፊት ለፊት) እና በአዋሬ(ቤተመንግስት አጠገብ) አፓርትመንቶች አሉን
💥 የንግድ ሱቆች
#ቡልጋሪያ ላይ ከ900ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ፒያሳ ላይ ከ1.4ሚሊዮን ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ቃሊቲገላን ላይ ከ500ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ።
#ሳር ቤት አዳምስ አጠገብ ከ 900ሺ ብር ቅድመ ክፍያ
🎯ልብይበሉ
# ያለምንም ወለድና የግንባታ እቃዎች ጭማሪ በኢትዮጵያ ብር ከፍለው የሚጨርሱት ነው
#ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
👇👇👇👇👇👇
+251939770177
+251996856273
https://t.me/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp. https://wa.me/251939770177
Telegram :@KalTemerRealEstate | 14 943 |
| 12 | በቢሸፍቱ አቡሴራ ላይ ለሚገነባው አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጄክት አበዳሪዎች ቃል ስለገቡት የ8.5 ቢሊዮን ዶላር ብድር የመጨረሻ ውሳኔ መገቢት 2019 ዓም እንደሚታወቅ ታወቀ
"የጡረታ ጊዜዬ ስለተጠናቀቀ የመንግስትን ውሳኔ እየጠበቅሁ ነው" አቶ መስፍን ጣሰው
- የኢትዮጵያ አየር መንገድ 9.1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ
- ለ5000 ሠራተኞች ቤት እየገነባ መሆኑን አስታውቋል
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኦሮሚያ ክልል ቢሸፍቱ አቡሴራ ለሚያስገነባው ግዙፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ፕሮጄክት 8.5 ቢሊዮን ዶላር ብድር ለመስጠት ቃል የገቡ አበዳሪዎች የመጨረሻ ውጤት የሚታወቀው በቀጣይ ዓመት 2019 ዓም መሆኑን የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አስታወቁ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን ይህን የተናገሩት ዛሬ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በስካይላይት ሆቴል አመታዊ አፈጻጸሙን አስመልክቶ መግለጫ ሲሰጡ ነው።
ዋና ስራ አስፈጻሚው አየር መንገድ ግሩፑ ያገኘው ገቢ ካለፈው በጀት ዓመት አንጻር በ20 በመቶ ቢያድግም፣ ወጪውም በገልፍ ጦርነትና በሌሎች ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ምክንያት በ25 በመቶ ከፍ ማለቱንም አሳውቀዋል። አየር መንገዱ በዚህ አመት 897ሺህ ቶን ጭነት ያጓጓዘ ሲሆን፣ ይህም ከእቅዱ 16 በመቶ ከፍ ያለ መሆኑን አቶ መስፍን አሳውቀዋል።
አየር መንገድ ግሩፑ በተጠናቀቀው በጀት አመት አራት አዳዲስ አለም አቀፍ በረራዎችን የጀመረ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ወደ ፖርቹጋል፣ ቬትናምና አቡዳቢ የተጀመሩት በረራዎች ተጠቃሽ ናቸው። | 13 683 |
| 13 | በጃፓን ኩማሞቶ በሬክተር ስኬል 7.1 የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
በጃፓን ደቡባዊ የኪዩሹ ደሴት በሚገኘው ኩማሞቶ ግዛት ዛሬ የደረሰው ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ በሰዎች ሕይወት፣ በመሠረተ ልማት እና በኢንዱስትሪ ተቋማት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አስከትሏል።
የመጀመሪያ ግምገማዎች መንቀጥቀጡ በ6.8 እስከ 7.1 ማግኒትዩድ መካከል መለካቱን ያሳያሉ፤ ባለሥልጣናት የመጨረሻ ሳይንሳዊ ግምገማ እየተጠበቀ መሆኑን ገልጸዋል።
ከአደጋው በኋላ በካሺማ ከተማ የሚገኘው «ኢዮን ሞል ኩማሞቶ» ውስጥ ከባድ ፍንዳታ ተከስቶ የሕንፃው ክፍል በመፍረሱ በርካታ ሰዎች በፍርስራሹ ስር መቀራቸው ተገልጿል።
እስካሁን ከ20 እስከ 30 የሚደርሱ ሰራተኞች የጠፉ ሲሆን፣ የእሳት አደጋ እና የነፍስ አድን ቡድኖች የማዳን ሥራ እያካሄዱ ነው። ፍንዳታው ከጋዝ መፍሰስ ጋር ሊያያዝ እንደሚችል ጥርጣሬ ቢኖርም፣ ባለሥልጣናት መንስኤውን እያጣሩ ነው።
በሌላ በኩል፣ በአካባቢው በሚገኝ የወረቀት ፋብሪካ ውስጥ የነበሩ በርካታ ሰራተኞች ያሉበት እስካሁን አልታወቀም።
በባቡር መስመሮች፣ በድልድዮች እና በመንገዶች ላይም ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል፤ የባቡር አገልግሎት ተቋርጧል፣ አንዳንድ ባቡሮችም ከሐዲድ ወጥተዋል። በአካባቢው የአየር ማረፊያም ለጊዜው ተዘግቷል።
የኃይል አቅርቦት በአስር ሺዎች ቤቶች ተቋርጧል፤ ከ60 በላይ የተከታታይ ንዝረቶች በመመዝገባቸውም ተጨማሪ የመሬት መንሸራተት እና የሕንፃ መውደቅ አደጋ ስለሚኖር ህዝቡ ከተጎዱ ሕንፃዎች እንዲርቅ ጥሪ ቀርቧል።
የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ሳናኤ ታካኢቺ የመከላከያ ኃይሎችን፣ የእሳት አደጋ ባለሙያዎችን እና ሌሎች የአደጋ ምላሽ ቡድኖችን ወደ ተጎዱ አካባቢዎች መላካቸውን ገልጸዋል።
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!
-ETHIO-MEREJA-
T.me/ethio_mereja | 14 964 |
| 14 | አንቀጽ 39 እስከ መገንጠል የሚለው እስከ መዋሃድ ተብሎ እንዲስተካከል ሐሳብ ቀረበ
የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ቀርቶ ሕብረ ብሔራዊ አንድነት ኮሚሽን የሚል ተቋም እንዲቋቋም ተጠይቋል
በአገራዊ ምክክር ጉባዔ በአሥርና በ50 ተመካካሪ ቡድን ሲወያዩ የቆዩ ተመካካሪዎች ያጠናከሩትን የአጃንዳ ሐሳብ፣ 250 አባላት ላሉት የምክክር ቡድን ማቅረብ ሲጀምሩ፣ በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት የብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መብት "እስከ መገንጠል" በሚለው አንቀጽ 39 ስር የተቀመጠው ሐረግ "እስከ መዋሃድ" ተብሎ እንዲስተካከል የሚል ሐሳብ ዛሬ ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ቀረበ።
ሀሳቡ የቀረበው፣ አሥርና 50 አባላት ባላቸው ንዑሳን ቡድኖች ስር ሲወያዩ የቆዩ ተመካካሪዎች፣ 250 አባላት ላሉት ሥልታዊ ቡድን ያጠናቀሩትን የአጀንዳ ሐሳብ ሲያቀርቡ ነው።
በዚህም ሐሳብ ከቀረበባቸው አጀንዳዎች መካከል፣ የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ እንዲሁም የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልናና የምርጫ ሥርዓትን የተመለከተው አንዱ ሲሆን፣ በሥሩም የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት (የብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መብት አንቀጽ 39) ንዑስ አጀንዳ መሆኑ ይታወቃል።
ይህ ንዑስ አጀንዳ(አንቀጽ 39)፣ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት የሚሰጥ በመሆኑ፣ ሙሉ ለሙሉ ሳይሻር "እስከ መገንጠል" የሚለው ሐረግ ብቻ ከድንጋጌው እንዲወጣና ባለበት እንዲቀጥል የሚጠይቁ ሐሳቦች ከአሥርና ከ50ዎቹ ንዑስ ብድኖች በአብዛኛው ቀርበዋል። | 15 198 |
| 15 | #ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
👉Studio 32ካሬ 1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ 2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና 3 መኝታ ከ 118ካሬ ጀምሮ
👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት
👉100% ለሚከፍሉ እስከ 35% ቅናሽ
👉20% ከፍለው ቀሪውን በ 16 ዙር ከፍለው የሚጨርሱት
👉 በመገናኛ ዲያስፖራ አደባባይ ፊት ለፊት(የካ ክፍለ ከተማ ጀርባ) ከቴምር ሪልስቴት
👉በተጨማሪም በቡልጋሪያ(አፍሪካ ህብረት ፊት ለፊት) እና በአዋሬ(ቤተመንግስት አጠገብ) አፓርትመንቶች አሉን
💥 የንግድ ሱቆች
#ቡልጋሪያ ላይ ከ900ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ፒያሳ ላይ ከ1.4ሚሊዮን ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ቃሊቲገላን ላይ ከ500ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ።
#ሳር ቤት አዳምስ አጠገብ ከ 900ሺ ብር ቅድመ ክፍያ
🎯ልብይበሉ
# ያለምንም ወለድና የግንባታ እቃዎች ጭማሪ በኢትዮጵያ ብር ከፍለው የሚጨርሱት ነው
#ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
👇👇👇👇👇👇
+251939770177
+251996856273
https://t.me/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp. https://wa.me/251939770177
Telegram :@KalTemerRealEstate | 18 282 |
| 16 | በኢትዮጵያ በመጪዎቹ ዓመታት ሥራ አጥነት ፈታኝ እንደሚሆን የዓለም የሥራ ድርጅት ገለጸ
የዜጎች ማኅበራዊ ጥበቃ አገልግሎት እንዲጨምር ጠይቋል
በትምህርት ያልገፉና የሥራ ልምድ የሌላቸው ወጣቶች በክህሎት ማነስና በራሳቸው ሥራ ለመጀመር በሚገጥማቸው የፋይናንስ ችግር የሥራ ዕድል ዕጦት እንደሚያጋጥማቸው፣ የዓለም የሥራ ድርጅት (ILO) ገለጸ፡፡
የዓለም የሥራ ድርጅት ከሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከዩናይትድ ኪንግደም ተራድኦ ድርጅት (ዩኤአይድ) እና ከሌሎች ተቋማት በጋራ በመሆን፣ በማኅበራዊ ጥበቃ ላይ ያዘጋጀውን ሪፖርት ይፋ ሲያደርግ ነው ይህንን የገለጸው፡፡በሪፖርቱ መሠረት ቁጥራቸው እያደገ ያለው ሥራ ፈላጊ ወጣቶች፣ በክህሎት ክፍተትና የራስን ቢዝነስ ለመጀመር በሚገጥማቸው የፋይናንስ ዕጦት ከፍተኛ ተግዳሮት ይገጥማቸዋል፡፡
የሕፃናት ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ወደ ሥራ ሊገባ የሚገባውን የወጣት ቁጥር የሚያሳድገው በመሆኑ፣ ዕድገቱን ከከተሞች የሥራ ገበያ ዕድል ጋር አጣጥሞና አዋህዶ መሄድ ከፍተኛ ፈተና ይሆናል ብሏል፡፡
በአገር አቀፍ ደረጃ የአካል ጉዳተኞች ቁጥር 17.6 በመቶ እንደሚደርስ ጠቅሶ፣ አካታችና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ተሳትፎን የሚደግፉ ፖሊሲዎችና መሠረተ ልማቶችን ማስፋፋት እንደሚያስፈልግ ገልጿል፡፡
በአገር አቀፍ ደረጃ ለሥራ ብቁ የሆነው የሕዝብ ቁጥር እ.ኤ.አ. በ2015 ከነበረበት 54.7 ሚሊዮን እ.ኤ.አ. በ2025 74.8 ሚሊዮን፣ እ.ኤ.አ. በ2030 ወደ 85.3 እንደሚደርስ ሪፖርቱ ያመለክታል፡፡ | 15 955 |
| 17 | የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ከጠዋቱ 2፡00-10፡00
👉አያት፣ አይ ሲ ኤም ሲ ሆስፒታል፣ ስኩል ኦፍ ቱሞሮ፣ መሪ መስኪድ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00-12፡00
👉መቀሌ፣ኤስ ኦ ኤስ፣ ቀበሌ 14፣15፣16 እና 17፣ ዓይን ዓለም እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00-10፡00
👉አዋሽ መልኬሳ መግቢያ እና ከተማ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00-7፡00
👉መቀሌ ቬተርነሪ ካምፓሰ፣ ኤልሻዳይ፣ ሻፋት፣ ዳጋይ እና ገብረ ሰገን ውሃ ግድብ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡30-11፡00
👉ባህርዳር ጊዮን ት/ቤት፣ሞላልኝ ግሮሰሪ እና አካባቢው የኃይል አቅርቦትይቋረጣል።
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ሐምሌ 18/2018 ዓ.ም | 17 711 |
| 18 | #ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
👉Studio 32ካሬ 1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ 2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና 3 መኝታ ከ 118ካሬ ጀምሮ
👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት
👉100% ለሚከፍሉ እስከ 35% ቅናሽ
👉20% ከፍለው ቀሪውን በ 16 ዙር ከፍለው የሚጨርሱት
👉 በመገናኛ ዲያስፖራ አደባባይ ፊት ለፊት(የካ ክፍለ ከተማ ጀርባ) ከቴምር ሪልስቴት
👉በተጨማሪም በቡልጋሪያ(አፍሪካ ህብረት ፊት ለፊት) እና በአዋሬ(ቤተመንግስት አጠገብ) አፓርትመንቶች አሉን
💥 የንግድ ሱቆች
#ቡልጋሪያ ላይ ከ900ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ፒያሳ ላይ ከ1.4ሚሊዮን ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ቃሊቲገላን ላይ ከ500ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ።
#ሳር ቤት አዳምስ አጠገብ ከ 900ሺ ብር ቅድመ ክፍያ
🎯ልብይበሉ
# ያለምንም ወለድና የግንባታ እቃዎች ጭማሪ በኢትዮጵያ ብር ከፍለው የሚጨርሱት ነው
#ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
👇👇👇👇👇👇
+251939770177
+251996856273
https://t.me/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp. https://wa.me/251939770177
Telegram :@KalTemerRealEstate | 17 015 |
| 19 | ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ግዙፍ የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ ግንባታ እያጠናቀቀች ነው
ኢትዮጵያ ጥሬ ወርቅን ወደ ዱባይ በመላክ ለብዙ አስርት ዓመታት ስታካሂድ የቆየችውን አሰራር በማቆም የመጀመሪያውን ግዙፍ ሀገር በቀል የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ ሥራ ለማስጀመር የመጨረሻ ዝግጅቷን እያጠናቀቀች ይገኛል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት ከእንግዲህ በሀገሪቱ የሚመረተው ማናቸውም ወርቅ ወደ ውጭ አገር ከመላኩ በፊት በሀገር ውስጥ ደረጃቸውን የጠበቁ የወርቅ አሞሌዎች ሆነው መጣራት ይኖርባቸዋል።
ይህ አዲስ አሰራር የሀገሪቱን የኤክስፖርት ገቢ ከፍ የሚያደርግ የውጭ ምንዛሬ ክምችትን የሚያጠናክር እና ሕገ-ወጥ የወርቅ ኮንትሮባንድን በከፍተኛ ደረጃ የሚቀንስ እንደሚሆን ታምኖበታል።
በአሁኑ ወቅት የመጨረሻውን የፍተሻ ምዕራፍ እያጠናቀቀ የሚገኘው ይህ ዘመናዊ ተቋም በበቀጣይ ዓመት ሥራ የሚጀምር ሲሆን እንደ ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት ያሉ አበይት የማዕድን ልማቶችን ጨምሮ እያደገ የመጣውን ሀገራዊ የወርቅ ምርት ሙሉ በሙሉ የሚያስተናግድ ይሆናል። | 16 681 |
| 20 | ሂውማን ራይትስ ዎች በዌስት_ባንክ የሰፈሩ የእስራኤል ዜጎች የሚያካሂዱት ጥቃት ትልቅ እልቂት ሊያስከትል እንደሚችል አስጠነቀቀ
የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቹ ሂውማን ራይትስ ዎች በዌስት ባንክ አካባቢዎች የሰፈሩ የእስራኤል ዜጎች የሚያካሂዱት ጥቃት እየጨመረ በመምጣቱ ተጨማሪ እልቂቶችን ሊያስከትል እንደሚችል በማስጠንቀቅ የእስራኤል መንግሥት ጥቃቶችን ከመከላከል መቆጠቡን እና ተጠያቂነት ላለመኖር ድርጊቶች መንገድ መክፈቱን ከሰሰ።
ሐምሌ 17 በወጣው መግለጫ፣ ድርጅቱ ናብሉስ አቅራቢያ በሚገኘው የታል የፍልስጤም መንደር ላይ በተፈጸሙ ሁለት ጥቃቶች የአራት ፍልስጤማውያን እና የሁለት እስራኤላውያን ሕይወት ማለፉን ገልጿል።
የመብት ተሟጋች ቡድኑ እንደገለጸው፣ የቅርብ ጊዜው ጥቃት፤ በአካባቢው የሰፈሩ የታጠቁ እስራኤላውያን በፍልስጤም ማህበረሰቦች ላይ ጥቃት የሚያሰነዝሩበትን፣ የእስራኤል ወታደሮች ደግሞ በጥቃቱ የሚሳተፉበትን ወይም ጣልቃ ከመግባት የሚቆጠቡበትን ሰፊ ክስተት ያመላክታል። በጥቃቶቹ ላይ ኃላፊነት ያለባቸው ሰዎች ብዙ ጊዜ ከእስራኤል መንግሥት የገንዘብ፣ የቁሳቁስ እና የሕግ ድጋፍ እንደሚያገኙ ድርጅቱ አክሎ ገልጿል። | 22 957 |
