cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

ETHIO-MEREJA®

Addisababa, Ethiopia🇪🇹 News & Media Company® . USA : Washington . . . ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!! 👉 @ethio_merejabot

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
130 480
المشتركون
-1724 ساعات
-1457 أيام
-87130 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

በአውሮፓ ዋንጫ ስፔን እና ፈረንሳይ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅለዋል! ምሽት ላይ በተደረጉ የአውሮፓ ሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ስፔን እና ፈረንሳይ ድል ቀንቷቸዋል፡፡  በ17ኛው የአውሮፓ ዋንጫ ጠንካራ ተወዳዳሪ ሆነው የቀረቡት ስፔኖች ያለምንም ሽፈት ግስጋሴያቸውን ቀጥለዋል፡፡ ከአዘጋጇ ሀገር ጀርመን ጋር ትላንት ባደረጉት ጨዋታ 2ለ1 በሆነ ውጤት ያሸነፉት ስፔኖች ለዋንጫው የሚኖራቸውን ከፍተኛ ተፎካካሪነት በምሽቱ ጨዋታ በግልጽ አሳይተዋል፡፡ የአውሮፓ ዋንጫ ከፍተኛ ጎል አስቆጣሪዎች በሁለቱ ቡድኖች መካከል ጨዋታውን አሸንፎ ለመውጣት ፍጹም የጨዋታ ፉክክር በታየበት ግጥሚያ በፔድሪ ተቀይሮ የገባው ዳኒ አልሞ በ51ኛው ደቂቃ ስፔንን መሪ ያደረገች ጎል ያስቆጠረ ሲሆን፥ ፍሎሪያን ዊርዝ በ89ኛው ደቂቃ ጀርመንን አቻ አድርጓል። ጨዋታው ወደ ጭማሪ ስአት አምርቶ ሚኬል ሜሪኖ ለስፔን ወሳኝ ጎል አስቆጥሮ ሀገሩን ወደ ግማሽ ፍጻሜው በማሳለፍ ውለታን ውሏል። የጀርመን ብሔራዊ ቡድን አማካይ ቶኒ ክሩስ በእግርኳስ ህይወቱ ለብሔራዊ ቡድኑ ያደረገው የመጨረሻ ጨዋታው ሆኗል።የአውሮፓ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ምሽት 4 ስአት ሲቀጥል በሀምቡርግ ከተማ ፈረንሳይን ከፖርቹጋል ጋር አገናኝቷል።  ሁለት በራስ ላይ በተቆጠረ ግብ እና በአንድ ፍጹም ቅጣት ምት ሩብ ፍጻሜ መድረስ የቻለው ተከላካዩ የዲዴር ዴሾ ቡድን ትላንትም የግብ ክልሉን በፖርቹጋል ተጫዋቾች ላለማስደፈር አጥር ሰርቶ ተጫውቷል፡፡በመደበኛው እና በጭማሪ ሰአት ግብ ያልተቆጠረበት የፖርቹጋል እና ፈረንሳይ ጨዋታ ወደ መለያ ምት አምርቶ 5ለ3 በሆነ ውጤት ፈረንሳይ ግማሽ ፍጻሜውን መቀላቀል የቻለችበት ውጤት ተመዝግቧል፡፡  የምሽቱን ጨዋታ ተከትሎ ክርስቲያኖ ሮናልዶ እና ፔፔ ለብሔራዊ ቡድኑ የሚያደርጉት የመጨረሻ ጨዋታ እንደሆነ ተነግሮ ነበር፡፡ ንጋት ላይ የብሄራዊ ቡድኑን አሰልጣኝ ጠቅሰው የወጡ መረጃዎች ደግሞ የተጨዋቾቹ እጣ ፈንታ አለመወሰኑን አመላክተዋል፡፡ አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ የክርስቲያኖ እና ፔፔ በብሄራዊ ቡድኑ የሚኖራቸው ቆይታ ገና አልተወሰነም ብለዋል፡፡ ሮናልዶ በውድድሩ ከየትኛውም ተጫዋች የበለጠ የጎል ሙከራዎችን ቢያደርግም ግብ ማስቆጠር ተስኖት ከውድደሩ ውጭ ሲሆን ፔፔ በአውሮፓ ዋንጫ የተሳተፈ በእድሜ ትልቁ ተጫዋች ሪከርድን ይዟል፡፡  የሩብ ፍጻሜ የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው የሚካሄዱ ሲሆን ምሽት 1 ሰአት ላይ ኔዘርላንድ ከቱርክ ምሽት 4 ሰአት ላይ ደግሞ እንግሊዝ ከሲውዲን ጋር ይጫወታሉ፤ የሁለቱ ጨዋታ አሸናፊዎች ወደ ዋንጫ ለማለፍ የሚፋለሙ ይሆናል፡፡  ትላንት በተደረጉ ጨዋታዎች ግማሽ ፍጻሜውን የተቀላቀሉት ስፔን እና ፈረንሳይ በመጭው ማክሰኞ ፍልሚያቸውን የሚያደርጉ ሲሆን በማጥቃት ላይ ተመስርቶ ለሚጫወተው የስፔን ብሄራዊ ቡድን አጥር ሰርተው የሚከላከሉት ፈረንሳዮች ፈተና ሊሆኑ እንደሚችሉ ይጠበቃል፡፡(ዘገባ-አልአይን)
إظهار الكل...
👍 20 2👎 1🤔 1
Photo unavailableShow in Telegram
🎧Airpod pro Bluetooth earphone🎧 ✨New(packed) እንደታሸገ! High quality | 💯 Best sound designed by apple / Assembled in Usa 🔹የድምፅ ጥራቱ አስገራሚ እና ኩልል ያለ 📌Compatibility: iOS, Android 📌With wireless charging case 📌Sweat & water resistance 📌24 Hours listening time &Hey Siri always on 📌Touch button &Noise Cancellation control 📌support wireless charger& IN/OFF Ear detection ዋጋ ፣ 1800❌ 1600✅ብር ብቻ! Address :- Megenagna        ☎️ 0901882392        ☎️ 0931448106
إظهار الكل...
1
🌺Electric Hair Steamer Cap          💯 High Quality 👉የፀጉር እስቲመር ትሪትመንት ወይም ቅቤ ተቀብተው በቤቶ ሆነው የሚጠቀሙበት!       💦 Price፦ ✅ 1200 ብር         ☎️ 0901882392         ☎️ 0931448106
إظهار الكل...
👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሕመድ አሊ ተገደሉ የብልጽግና ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል እና በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሕመድ አሊ በታጣቂዎች መገደላቸው ተገለጸ። ከአማራ ክልል መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ እና ከዞኑ ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ እንደሚያሳየው አቶ አሕመድ አሊ የተገደሉት #በከሚሴ ከተማ ከሚገኘው መስጅድ ዛሬ ሰኔ 28 ቀን 2016 ዓ.ም “ጁምአ ሶላት ሰግደው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ከታጣቂዎች በተተኮሰባቸው ጥይት” ነው። የክልሉ ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ እንዳመላከተው ዋና አስተዳዳሪው የተገደሉት “የአንድነት ፀር በሆኑ ፅንፈኞች“ ሲል በጠራቸው ሀይሎች በተተኮሰ ጥይት ነው። በአማራ ክልል የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አሕመድ አሊ “በ39 ዓመታቸው መስዋዕት ሆነዋል” ያለው የአማራ ክልል መንግስት መግለጫ “ፅንፈኝነት መሪዎችን በመግደል የሚያሸንፍ ቢመስልም የበለጠ ትግላችንን እንድናጠናክር የሚያደርግ ነው” ሲል አስታውቋል። አቶ አሕመድ አሊ ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ በዞኑ አስተዳደር በተላያዩ ሃላፊነት ቦታዎች ማገልገላቸውን ከዞኑ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
إظهار الكل...
👍 61🔥 16😱 15 12😁 9👎 3
Photo unavailableShow in Telegram
"በበይነ መረብ የሚሰጠው የ12ተኛ ክፍል ፈተና እንደቀረ ተደርጎ እየቀረበ ያለው መረጃ ሃሰተኛ ነው" - ትምህርት ሚኒስቴር ************** ከ12ተኛ ብሄራዊ ፈተና ጋር ተያይዞ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የበይነ መረብ ፈተናው እንደቀረ ተደርጎ እየቀረበ ያለው መረጃ በፍጹም ከእውነት የራቀና ሃሰተኛ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ.ም የ12ተኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በበይነ መረብና በወረቀት እንደሚሰጥ መግለጹ ይታወቃል። ሆኖም በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የበይነ መረብ ፈተናው እንደቀረ ተደርጎ እየቀረበ ያለው መረጃ በፍጹም ከእውነት የራቀ ሃሰተኛ መሆኑን የገለጸው ሚኒስቴሩ፤ ፈተናው በሁለቱም በወረቀት እና በኦንላይን እንደሚሰጥ አረጋግጧል። ተማሪዎች ይሄንኑ ተገንዝበው ዝግጅታቸውን እንዲቀጥሉ ያሳሰበው ሚኒስቴሩ፤ ፈተናውን የተሳካ ለማድረግ እንደተለመደው ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በጥምረት እየሰራ መሆኑንና ለዚህም ከፍተኛ ዝግጅት ማድረጉን አስገንዝቧል።
إظهار الكل...
👍 14😁 6 1🤔 1
በፓሪስ ኦሊምፒክ ጨዋታዎች ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች‼️ በፓሪስ 2024 ኦሊምፒክ ጨዋታዎች በአትሌቲክስ ስፖርት ኢትዮጵያን የሚወክሉ የመጨረሻ ተሰላፊ አትሌቶች ከነተጠባባቂያቸው መለየታቸውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታውቋል። ማራቶን በሴቶችና በወንዶች ✍️ አትሌት ትዕግስት አሰፋ፣አትሌት አማኔ በሪሶ፣አትሌት መገርቱ ዓለሙ፣አትሌት ጎይቶቶም ገ/ስላሴ (ተጠባባቂ) ✍️ አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ፣አትሌት ሲሳይ ለማ፣አትሌት ዴሬሳ ገለታ፣ አትሌት ታምራት ቶላ (ተጠባባቂ) 800 ሜትር በሴቶች ✍️ አትሌት ፅጌ ድጉማ፣አትሌት ሐብታም ዓለሙ፣አትሌት ወርቅነሽ መለሰ፣ አትሌት ንግስት ጌታቸው (ተጠባባቂ) 1500 ሜትር በወንዶችና በሴቶች ✍️ አትሌት አብዲሳ ፈይሳ፣አትሌት ሳሙኤል ተፈራ፣አትሌት ኤርሚያስ ግርማ፣አትሌት ታደሰ ለሚ (ተጠባባቂ) ✍️ አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ፣አትሌት ብርቄ ሃየሎም፣አትሌት ድርቤ ወልተጂ፣አትሌት ሂሩት መሸሻ (ተጠባባቂ) 5ሺህ ሜትር ወንዶችና በሴቶች ✍️አትሌት ሀጎስ ገ/ህይወት፣አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ፣አትሌት አዲሱ ይሁኔ፣አትሌት ሰሞን ባረጋ (ተጠባባቂ) ✍️ አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ፣አትሌት መዲና ኢሳ፣አትሌት እጅጋየሁ ታዬ፣አትሌት ፍሬወይኒ ኃይሉ (ተጠባባቂ) 10ሺህ ሜትር ወንዶችና በሴቶች ✍️ አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ፣አትሌት በሪሁ  አረጋዊ፣አትሌት ሰለሞን በረጋ፣አትሌት ቢኒያም መሀሪ (ተጠባባቂ) ✍️ አትሌት ጉዳፍ ፀጋዬ፣አትሌት ፎቴን ተስፋዬ፣አትሌት ፅጌ ገ/ሰላማ፣አትሌት አይናዲስ መብራቱ (ተጠባባቂ) 3ሺህ ሜትር መሠናክል በወንዶች  ✍️ አትሌት ለሜቻ ግርማ፣አትሌት ሳሙኤል ፍሬው፣አትሌት ጌትነት ዋለ፣አትሌት አብርሃም ስሜ (ተጠባባቂ) 20 ኪሎ ሜትር ርምጃ በወንድ አትሌት ምስጋና ዋቁማ ናቸው።
إظهار الكل...
👍 48🤯 2 1
ቀነኒሳ በቀለ ከ12 አመታት በኋላ ኢትዮጵያን ወክሎ በማራቶን ይወዳደራል በፓሪስ ኦሎምፒክ ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶች ይፋ ሆኑ! የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ኢትዮጵያን በፓሪስ ኦሎምፒክ በአትሌትክስ ስፖርት የሚወክሉ የመጨረሻ ተሰላፊ አትሌቶች ከነተጠባባቂያቸው ይፋ አድርጓል። ከቀናት በኋላ #በፓሪስ በሚጀመረው ኦሎምፒክ ውድድር በማራቶን ኢትዮጵያን ወክለው ከሚወዳደሩት መካከል ቀነኒሳ በቀለ ይገኝበታል፤ በኦሎምፒክ ውድድሮች 3 የወርቅ ሜዳልያ ያለው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ ከ12 አመታት በኋላ ኢትዮጵያን በኦሎምፒክ ማራቶን ውድድር የሚወክል ይሆናል ተብሏል። በማራቶን ወንዶች ኢትዮጵያን ከቀነኒሳ በቀለ ጋር በመሆን ወክለው የሚወዳደሩት አትሌት ሲሳይ ለማ፣ አትሌት ዴሬሳ ገለታ ሲሆኑ አትሌት ታምራት ቶላ ተጠባባቂ ሁኖ ተመርጧል። በማራቶን ሴቶች አትሌት ትዕግስት አሰፋ፣ አትሌት አማኔ በሪሶ፣ አትሌት መገርቱ ዓለሙ የተመረጡ ሲሆን አትሌት ጎይቶቶም ገ/ስላሴ ተጠባባቂ ተደርጋ ተመርጣለች።
إظهار الكل...
👍 33 7👏 3
Photo unavailableShow in Telegram
በትግራዩ ጦርነት ወደ #ሱዳን የተሰደዱ ዜጎች አደጋ ላይ መውደቃቸውን አስታወቁ፣ መንግስት በበኩሉ ለመመለስ እየሰራሁ ነው ብሏል! የትግራዩ ጦርነት ተከትሎ ወደ ሱዳን የተሰደዱ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በሱዳኑ የእርስ በርስ ግጭት ምክንያት አደጋ ላይ መውደቃቸውን አስታወቁ። እነዚህ "60 ሺህ ገደማ የሚገመቱ" እና በሱዳን ተነድባ እና ዑምራኩባ የተባሉ መጠልያዎች ያሉ የትግራይ ጦርነት መቀስቀሱ ተከትሎ ወደ ሱዳን የተሰደዱ ስደተኞች #የኢትዮጵያ መንግስት እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት እንዲደርሱላቸው በመጠየቅ ላይ እንደሚገኙ ተጠቁሟል። የጀርመን ድምጽ ያነጋገራቸው በሱዳን ዑምራኩባ እና ተነድባ የተባሉ የስደተኞች መጠልያ ጣብያዎች ያሉ፥ የትግራዩ ጦርነት በመሸሽ ሱዳን የገቡ ዜጎች፥ በሱዳን የተቀሰቀሰው ጦርነት አስጊ ሁኔታ ላይ እንደጣላቸው፣ እርዳታ ለጋሾች ጨምሮ የተለያዩ ተቋማት እንዲሁም የሱዳን ዜጎች አካባቢ ለቀው እየወጡ ቢሆንም እነዚህ ስደተኞች ግን የሚደርስላቸው አጥተው አሳሳቢ ሁኔታ ላይ መሆናቸው አስታውቀዋል። ተነድባ የስደተኞች መጠልያ ተጠልለው የሚገኙ እና ከጦርነቱ በፊት በትግራይ ምዕራባዊ ዞን ራውያን አካባቢ ከልጆቻቸው ጋር ይኖሩ የነበሩት እናት ወይዘሮ ጊቱ አለፈ ጦርነት ሽሽት የገቡባት ሱዳን ወደ እርስ በርስ ግጭት ማምራትዋ ተከትሎ ግን አሁን ላይ እርሳቸው ጨምሮ በሺዎች የሚቆጠር ስደተኛ ለአደጋ መጋለጣቸውን ገልጸዋል። እኛ ብቻ ነን መሄጃ አጥተን እዚህ ቁጭ ብለን ያለነው፣ የሚረዳን ማንም የለም" ብለዋል። ስለ ጉዳዩ የአሜሪካ ድምፅ የጠየቃቸው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢዩ ተድላ፣ የሱዳኑ ጦርነት ከተቀሰቀሰበት ጊዜ ጀምሮ፣ መንግሥት ዜጎችን የማስመለስ ሥራ እያከናወነ መኾኑን ተናግረዋል፡፡
إظهار الكل...
👍 31 6🙏 1
📍አዲስ አበባ እና አቅራቢያ ለምትገኙ በሙሉ!! የTikTokና የOnline እቃዎችን በብዛት ዋጋ👇 👉 https://telegram.me/AddisEka1 (Join) 👉 https://telegram.me/AddisEka1 👉 https://telegram.me/AddisEka1 👉 https://telegram.me/AddisEka1 (Join) ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉ! በቅናሽ ይሸምቱ!   👉ተአማኒነት እና ጥራት መገለጫችን ነው! 🏃‍➡️🏃‍♂‍➡️🏃‍♂‍➡️🏃‍♀‍➡️🏃‍♂‍➡️🏃‍♂‍➡️🏃‍♀‍➡️🏃‍♀‍➡️.... Join us
إظهار الكل...
አዲስ እቃ | Addis Eka

በቴሌግራም እዚህ ይቀላቀሉን! 0931448106 🌺AMAZON - ETHIOPIA🌺 ቤትዎን የሚያዘምኑ ምርጥ እቃዎችን ይዘንላችሁ መጥተናል። አድራሻ፣ መገናኛ ሲሳይ ፕላዛ 1ኛ ፎቅ 1-010ቁ! (ከዘፍነሽ ወረድ ሲሉ ግሬስ ሞል አጠገብ፣ መሶብ ሀበሻ ሆቴል ፊትለፊት 0901882392 ይደውሉ) Contact us - @HabeshaStorechat 👉 👉0901882392 👉👉 0931448106

👍 7 2
📍አዲስ አበባ እና አቅራቢያ ለምትገኙ በሙሉ!! የTikTokና የOnline እቃዎችን በብዛት ዋጋ👇 🌺 https://telegram.me/AddisEka1 (Join) 🌺 https://telegram.me/AddisEka1 🌺 https://telegram.me/AddisEka1 🌺 https://telegram.me/AddisEka1 (Join) ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉ! በቅናሽ ይሸምቱ!   👉ተአማኒነት እና ጥራት መገለጫችን ነው! 🏃‍➡️🏃‍♂‍➡️🏃‍♂‍➡️🏃‍♀‍➡️🏃‍♂‍➡️🏃‍♂‍➡️🏃‍♀‍➡️🏃‍♀‍➡️.... Join us
إظهار الكل...
አዲስ እቃ | Addis Eka

በቴሌግራም እዚህ ይቀላቀሉን! 0931448106 🌺AMAZON - ETHIOPIA🌺 ቤትዎን የሚያዘምኑ ምርጥ እቃዎችን ይዘንላችሁ መጥተናል። አድራሻ፣ መገናኛ ሲሳይ ፕላዛ 1ኛ ፎቅ 1-010ቁ! (ከዘፍነሽ ወረድ ሲሉ ግሬስ ሞል አጠገብ፣ መሶብ ሀበሻ ሆቴል ፊትለፊት 0901882392 ይደውሉ) Contact us - @HabeshaStorechat 👉 👉0901882392 👉👉 0931448106

اختر خطة مختلفة

تسمح خطتك الحالية بتحليلات لما لا يزيد عن 5 قنوات. للحصول على المزيد، يُرجى اختيار خطة مختلفة.