ar
Feedback
ETHIO-MEREJA®

ETHIO-MEREJA®

الذهاب إلى القناة على Telegram

News & Media Channel® Addisababa, Ethiopia🇪🇹 ውድ የኢትዮ መረጃ ቤተሰቦች ከዚህ የቴሌግራም ቻናል ውጪ ሌላ መረጃ የምናቀርብበት ምንም አይነት የዩቲዩብ፣ የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆች እንደሌለን ለማሳወቅ እንወዳለን፣ ስለሆነም በተመሳሳይ ስም በተከፈቱ ገፆች እንዳይሸወዱ ጥንቃቄ እንድታደርጉ እናሳስባለን። ለጥቆማና ማስታወቂያ ለማሰራት 👉 @ethio_merejabot

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ETHIO-MEREJA®

تُعد قناة ETHIO-MEREJA® (@ethio_mereja) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 102 583 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 488 في فئة الأخبار والوسائط والمرتبة 286 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 102 583 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 16 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -1 796، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -27، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 22.58‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 8.55‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 23 167 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 8 773 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 65.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
News & Media Channel® Addisababa, Ethiopia🇪🇹 ውድ የኢትዮ መረጃ ቤተሰቦች ከዚህ የቴሌግራም ቻናል ውጪ ሌላ መረጃ የምናቀርብበት ምንም አይነት የዩቲዩብ፣ የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆች እንደሌለን ለማሳወቅ እንወዳለን፣ ስለሆነም በተመሳሳይ ስም በተከፈቱ ገፆች እንዳይሸወዱ ጥንቃቄ እንድታደርጉ እናሳስባለን። ለጥቆማና ማስታወቂያ ለማሰራት 👉 @ethio_mere...

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 17 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الأخبار والوسائط.

102 583
المشتركون
-2724 ساعات
-3077 أيام
-1 79630 أيام

جاري تحميل البيانات...

سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
يونيو '26
يونيو '260
في 5 قنوات
مايو '260
في 2 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+10
في 6 قنوات
Get PRO
مارس '26
+127
في 7 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+16
في 4 قنوات
Get PRO
يناير '26
+15
في 8 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+3
في 5 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+33
في 8 قنوات
Get PRO
أكتوبر '25
+35
في 8 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+65
في 4 قنوات
Get PRO
أغسطس '25
+23
في 3 قنوات
Get PRO
يوليو '25
+4
في 5 قنوات
Get PRO
يونيو '25
+49
في 8 قنوات
Get PRO
مايو '25
+35
في 7 قنوات
Get PRO
أبريل '25
+7
في 7 قنوات
Get PRO
مارس '25
+26
في 3 قنوات
Get PRO
فبراير '25
+3
في 11 قنوات
Get PRO
يناير '25
+71
في 7 قنوات
Get PRO
ديسمبر '24
+196
في 7 قنوات
Get PRO
نوفمبر '24
+183
في 10 قنوات
Get PRO
أكتوبر '24
+464
في 9 قنوات
Get PRO
سبتمبر '24
+557
في 10 قنوات
Get PRO
أغسطس '24
+594
في 14 قنوات
Get PRO
يوليو '24
+221
في 8 قنوات
Get PRO
يونيو '24
+39
في 9 قنوات
Get PRO
مايو '24
+248
في 10 قنوات
Get PRO
أبريل '24
+495
في 10 قنوات
Get PRO
مارس '24
+808
في 12 قنوات
Get PRO
فبراير '24
+449
في 9 قنوات
Get PRO
يناير '24
+427
في 13 قنوات
Get PRO
ديسمبر '23
+249
في 8 قنوات
Get PRO
نوفمبر '23
+245
في 11 قنوات
Get PRO
أكتوبر '23
+987
في 19 قنوات
Get PRO
سبتمبر '23
+233
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '23
+435
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '23
+582
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '23
+410
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '23
+327
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '23
+578
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '23
+123
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '23
+1 206
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '23
+2 730
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '22
+261
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '22
+333
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '22
+381
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '22
+809
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '22
+1 206
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '22
+403
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '22
+288
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '22
+329
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '22
+160
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '22
+2 643
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '22
+101
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '22
+649
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '21
+598
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '21
+2 509
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '21
+2 433
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '21
+1 050
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '21
+2 889
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '21
+3 399
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '21
+1 218
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '21
+1 229
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '21
+1 659
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '21
+1 269
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '21
+1 388
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '21
+2 540
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '20
+253 170
في 0 قنوات
التاريخ
نمو المشتركين
الإشارات
القنوات
17 يونيو0
16 يونيو0
15 يونيو0
14 يونيو0
13 يونيو0
12 يونيو0
11 يونيو0
10 يونيو0
09 يونيو0
08 يونيو0
07 يونيو0
06 يونيو0
05 يونيو0
04 يونيو0
03 يونيو0
02 يونيو0
01 يونيو0
منشورات القناة
የሟቾች ቁጥር 31 ደረሰ🕯🕯 በተከሰተው የመኪና አደጋ የሟቾች ቁጥር 31 መድረሱን የኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ። ዛሬ ጠዋት በደሴ እና ኮምቦልቻ መካከል ሐረጎ በተባለ ሥፍራ
+3
የሟቾች ቁጥር 31 ደረሰ🕯🕯 በተከሰተው የመኪና አደጋ የሟቾች ቁጥር 31 መድረሱን የኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ። ዛሬ ጠዋት በደሴ እና  ኮምቦልቻ መካከል ሐረጎ በተባለ ሥፍራ በደረሰ የመኪና አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉን መዘገባችን ይታወሰል። አሁን ደግሞ  የሟቾች ቁጥር መጨመሩን ፖሊስ አስታውቋል። የኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ እንደገለጸው  በአደጋው ሕይወታቸው ያለፉ ሰዎች 31 ደርሷል። አደጋው የደረሰው በተለምዶ ከደሴ ወደ ኮምቦልቻ በሚወስደው ሐረጎ "S" መንገድ መታጠፊያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ከንጋቱ 12:00 መኾኑን የኮምቦልቻ ከተማ አሥተዳደር ፖሊስ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር ጌታቸው ሙህዬ ተናግረዋል። ተሽከርካሪው ከ100 ሜትር በላይ ርዝመት ያለው ገደል ውስጥ በመግባቱ ሹፌሩን ጨምሮ የ31 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ በ33 ሰዎች ላይ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱንም ኮማንደር ጌታቸው ለአሚኮ ገልጸዋል።  ተሽከርካሪው 64 ሰዎችን አሳፍሮ በመጓዝ ላይ እንደነበር ያነሱት ኮማንደር ጌታቸው ተጎጅዎች በደሴ እና በኮምቦልቻ ሆስፒታሎች  ሕክምና እየተደረገላቸው እንደኾነም  አንስተዋል። የአደጋው  መንስኤም  እየተጣራ መኾኑን አስታውቀዋል። ለተጎጅ ቤተሰቦችም መጽናናትን እንመኛለን።

2
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው የተለያ
ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው (ሰሜ ባላገሩ) ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው የተለያዩ ባህላዊ እና ሌሎች ይዘቶቸ ያሏቸው የሙዚቃ ሥራዎችን ለአድማጭ ተመልካች አበርክቷል፡፡ ድምጻዊው ለሕዝብ ካበረከታቸው የሙዚቃ ሥራዎች መካከል ነይ ዘመድዬ፣ እንዴት ነሽ፣ ደቦት እንስራ፣ ዘና በይ፣ ባላገር እና ሌሎች ይገኙበታል፡፡ ድምጻዊ ሰማኸኝ በለው ባለትዳር እና የአራት ልጆች አባት እንደነበር ፋና ዲጂታል ከቤተሰቦቹ ያገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡ ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለአድናቂዎቹ መጽናናትን ይመኛል፡፡
11 531
3
አሳዛኝ አደጋ🕯🕯🕯 ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት አለፈ። ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕ+1
አሳዛኝ አደጋ🕯🕯🕯 ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት አለፈ። ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ በነበረ ተሽከርካሪ በደረሰ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታውቋል። አደጋው የደረሰው ከደሴ እና ኮምቦልቻ ከተሞች መካከል በሚገኘው የሐረጎ መንገድ ላይ ነው። ዛሬ ሰኔ 08/10/18ዓ.ም ማለዳ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ የሕዝብ አውቶቡስ በተለምዶ ሐረጎ እየተባለ በሚጠራው መንገድ ላይ በደረሠበት አደጋ እስካሁን የ28 ሰው ሕይወት ሲያልፍ በርካቶች ቀላልና ከባድ ጉዳት ደርሶባተቸዋል። የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪው በግምት100 ሜትር ጥልቀት ወዳለው ገደል ገብቶ ነው አደጋው የደረሠው። በሕይወት የተረፉትን ወደ ሕክምና ቦታ ለማድረስ አሁንም ርብርብ እየተደረገ መኾኑን የገለጸው ፓሊስ የአደጋውን ምክንያት በመጣራት ላይ መኾኑን አስታውቋል።
12 226
4
ደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ የሚገኘውን የግብፅ ወታደራዊ ጣቢያ ዘጋች ደቡብ ሱዳን በላይኛው ናይል ግዛት፣ በፓጋክ አካባቢ ሲንቀሳቀስ የቆየውን የግብፅ ወታደራዊ ጣቢያ እንዲዘጋ ትዕዛዝ አ
ደቡብ ሱዳን በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ የሚገኘውን የግብፅ ወታደራዊ ጣቢያ ዘጋች ደቡብ ሱዳን በላይኛው ናይል ግዛት፣ በፓጋክ አካባቢ ሲንቀሳቀስ የቆየውን የግብፅ ወታደራዊ ጣቢያ እንዲዘጋ ትዕዛዝ አስተላለፈች። የኢትዮጵያ ድንበርን አዋሳኝ በሆነው በዚህ አካባቢ የነበረው ጣቢያ፣ ግብፅ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ያላትን ጥቅም ለማስጠበቅ ትጠቀምበት የነበረ ስትራቴጂያዊ የክትትል ማዕከል እንደነበር ተገልጿል። ይህ የደቡብ ሱዳን ውሳኔ በአካባቢው የኃይል ሚዛን ላይ ትልቅ ለውጥ የሚያመጣ እንደሆነ የፓለቲካ ተንታኞች የገለፁ ሲሆን፣ ሀገሪቱ በሱዳን የእርስ በርስ ግጭት ሳቢያ የተስተጓጎለውን የነዳጅ ንግድ ለማካካስ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የኢኮኖሚና የመሠረተ ልማት ትስስር ለማጠናከር ያላት ፍላጎት መገለጫ እንደሆነ ይስማሙበታል። በፓጋክ የነበረው የግብፅ ወታደራዊ ጣቢያ የቴክኒክና የሎጀስቲክስ ባለሙያዎችን ጨምሮ ወደ 260 የሚጠጉ ግብጻውያን ይገኙበት እንደነበር ተጠቅሷል። የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ባለፉት ሳምንታት ውጥረት ውስጥ እንደነበር የሚነገር ሲሆን፣ የደቡብ ሱዳን ወቅታዊ ውሳኔ በቀጠናው የፖለቲካ አሰላለፍ ላይ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኗል።
15 764
5
በምሽት ክበብ ውስጥ በተነሳ ግጭት የሰው ህይወት ማለፉን ተከትሎ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊስ ገለጸ በአዲስ አበባ ከተማ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ቱሉ ዲምቱ በሚገኝ ሆልስቴ
በምሽት ክበብ ውስጥ በተነሳ ግጭት የሰው ህይወት ማለፉን ተከትሎ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን ፖሊስ ገለጸ በአዲስ አበባ ከተማ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ቱሉ ዲምቱ በሚገኝ ሆልስቴ ሆቴል ውስጥ ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት ላይ በሰዎች መካከል ጠብ ተነስቶ ነበር። በዚህ ግጭት ወቅት አቡሽ ባዩ የተባለ ግለሰብ በሽጉጥ ተመትቶ ህይወቱ ሊያልፍ ችሏል። የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ እንደታወቀው ከድርጊቱ ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ 12 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራውን በስፋት እየገፋበት ይገኛል። ከተያዙት ግለሰቦች መካከል በፀቡ ላይ በቀጥታ የተሳተፈ አንድ ሰው፣ ከዋናው ገዳይ ጋር አብሮ ሲዝናና የነበረ ሌላ ተጠርጣሪ እንዲሁም ለግጭቱ መነሻ እንደሆነች የተጠረጠረች አንዲት አስተናጋጅ ይገኙበታል። በወቅቱ በነበረው አለመግባባት ሳቢያ በሰዎችና በንብረት ላይ ጉዳት የደረሰ ሲሆን፣ ወንጀሉን የፈጸመው ግለሰብ ሟች ታጥቆት የነበረውን ሽጉጥ ቀምቶ እንደተኮሰበት የሚያሳዩ ፍንጮችን ማግኘቱን ፖሊስ ጠቁሟል። የጉዳዩን ዝርዝር የምርመራ ውጤት ወደፊት ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግም አስታውቋል። በሌላ በኩል ፖሊስ ከዚህ ድርጊት ጋር ተያይዞ በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የከተማዋን ነባራዊ የሰላም ሁኔታ የማይገልጽ የተዛባ መረጃ እየተሰራጨ መሆኑን ገልጿል። ህብረተሰቡ የሀሰት ወሬዎችንና አሉባልታዎችን ወደ ጎን በመተው ትክክለኛውን መረጃ ከታማኝ የመረጃ ምንጮች ብቻ የመቀበል ልምዱን ሊያሳድግ እንደሚገባ ያሳሰበው መምሪያው፣ የስጋት ድባብ ለመፍጠር የሚሰሩ አካላትን በተባበረ ክንድ ለማክሸፍ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርቧል። የአዲስ አበባ ፖሊስ
25 198
6
በአርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ የደረሰውን የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች በተመለከተ ኢሰመኮ የሰጠው መግለጫ!! መንግሥት ተገቢውን ምርመራ በማካሄድ ተጠያቂነትን የማረጋገጥ እና ተጎጂዎችን ለመካስና ለማቋቋም የሚያስችሉ እርምጃዎችን ሊወስድ ይገባል . . . . . የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ግንቦት 23 እና 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተፈጸመውን ጥቃት በተመለከተ ክትትል እና ምርመራ እያከናወነ ይገኛል፡፡ ኢሰመኮ ይህ መግለጫ ይፋ እስከተደረገበት ጊዜ ድረስ በአካባቢው በአካል በመገኘት ከዐይን እማኞች፣ ከተጎጂዎች፣ ከተጎጂ ቤተሰቦች፣ እና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ባሰባሰባቸው መረጃዎችና ማስረጃዎች ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ የሚጠራው “በተለምዶ ኦነግ ሸኔ” ታጣቂ ቡድን በፈጸመው ጥቃት የመንግሥት የጸጥታ ኃይል አባላትና ሲቪል ሰዎች መገደላቸውን፣ ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን፣ የንብረት ውድመት እና ቃጠሎ መድረሱን ለማረጋገጥ ችሏል።   ኢሰመኮ በምርመራ ሂደቱ እንዳረጋገጠው በአሰኮ ወረዳ ደለተ ጫፋ ቀበሌ አካባቢ ከግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ የታጣቂዎች እንቅስቃሴ በመስተዋሉ የአካባቢው ሚሊሻዎችና የኦሮሚያ ጸረ ሽምቅ ውጊያ ፖሊስ አባላት በስፍራው በመሰማራታቸው “በተለምዶ ኦነግ ሸኔ” ተብሎ በሚጠራው ታጣቂ ቡድን እና በተሰማሩ የጸጥታ አካላት መካከል ግጭት ተፈጥሯል። ግጭቱን ተከትሎ የአካባቢው ነዋሪ የሆኑ ሰዎች ላይ ታጣቂ ቡድኑ ባደረሰው ጥቃት ከአካባቢው መሸሽ ባልቻሉ ኃይሉ ንጉሴ እና ሰሙ አባይነህ በተባሉ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንዲሁም በአካባቢው ከብቶች በመጠበቅ ላይ የነበረ ባቶ ሰፈኖ የተባለ የእስልምና እምነት ተከታይ በአጠቃላይ የሦስት ሲቪል ሰዎች ሕይወት ሊያልፍ ችሏል።  በተጨማሪም ቁጥራቸው ለጊዜው በውል ባልታወቁ ቤቶች ላይ ቃጠሎ መድረሱን፣ የጠለታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን መቃጠሉን፤ ቢዮ ቡጡሌ የሼክ ሙስተፋ መስጅድ አጥር ላይ ጉዳት መድረሱን፣ በድለተ ጫፋ ጤና ጣቢያ፣ በነዋሪዎች መኖሪያ ቤቶችና የንግድ መደብሮች ላይ በመደዳ ዘረፋ መፈጸሙን እንዲሁም ከ2,650 በላይ የሚገመቱ የአካባቢው ነዋሪዎች መፈናቀላቸውን ኢሰመኮ አረጋግጧል። ኢሰመኮ በአርሲ ዞን በሽርካ፣ በአሰኮ፣ በአንቆሎ ዋቤ፣ ጉና እና መርቲ ወረዳዎች ላይ በታጣቂዎቹ ሲፈጸሙ የነበሩ ጥቃቶች ዳግም እንዳይከሰቱ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደረግ እና ጥቃት ፈጻሚዎች ላይ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ በተለያዩ ጊዜያት ማሳሰቡ ይታወሳል። መንግሥት በአካባቢው ላይ በተደጋጋሚ መሰል ጥቃቶች እና የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች መከሰት መቀጠላቸው አሳሳቢ መሆኑን ከግምት በማስገባት ጥቃት በተፈጸመባቸው አካባቢዎች የጀመራቸውን ጥረቶች በማጠናከር በአስቸኳይ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እንዲሰማሩ እና ሰላምና ደኅንነትን በማረጋገጥ ነዋሪዎችን ወደ ተረጋጋ ሕይወት የመመለስ ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም በመንግሥትና በሌሎች አጋር አካላት በጥቃቶቹ ምክንያት ከቀያቸው ለተፈናቀሉ ነዋሪዎች በቂ የሆነ የአስቸኳይ የሰብአዊ ድጋፍ እንዲቀርብና ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው ተመልሰው በዘላቂነት የሚቋቋሙበት ሁኔታ እንዲመቻች ኢሰመኮ ያሳስባል።  በሌላ በኩል ኢሰመኮ ጉዳዩን አስመልክቶ ዝርዝር የምርመራ ሪፖርት ይፋ የሚያደርግ መሆኑን እየገለጸ፤ የተፈጸሙ ጥቃቶችን በአግባቡ ሳያረጋግጡ የሚሰነዘሩ ፍረጃዎችና ቅስቀሳዎች ተጨማሪ ግጭት እንዲፈጠር የማነሳሳት ዕድላቸው ሰፊ በመሆኑ ማናቸውም ተቋማትም ሆኑ ግለሰቦች ከዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ ጥሪ ያቀርባል። የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ ኢሰመኮ በዜጎች ላይ ለደረሰው ሞትና ጉዳት ማዘኑን ገልጸው በሲቪል ሰዎች ላይ የተፈጸሙት የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች አሳሳቢ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ አክለውም መንግሥት ሁኔታውን ለማረጋጋት እና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ ያከናወናቸው ተግባራት መቀጠል ያለባቸው መሆኑን ጠቅሰው፤ በማንኛውም ጊዜ የጸጥታ ሥጋት ባለባቸው አካባቢዎች ሁሉ በቂ የጸጥታ ኃይሎች በመመደብና ተመሳሳይ ጥቃቶችን የመከላከል ሥራ በመሥራት የነዋሪዎች በሕይወት የመኖር፣ የአካል ደኅንነት እና የንብረት መብቶች ለአደጋ እንዳይጋለጡ እንዲያደርግ፣ ተገቢውን ምርመራ በማካሄድ ተጠያቂነትን የማረጋገጥ እና ተጎጂዎችን ለመካስና ለማቋቋም የሚያስችሉ እርምጃዎችን እንዲወስድ እንዲሁም ሁሉም አካላት የተፈጠሩ ችግሮችን ከማውገዝ ባሻገር ግጭት ቀስቃሽ ከሆኑ መግለጫዎች እና ድርጊቶች እንዲታቀቡ ጥሪ አቅርበዋል።
23 877
7
+1
لا يوجد نص...
19 177
8
ሰላም የአዲስ ላይፍ ቤተሰቦች እስካሁን በ3ቱ ጵሮጀክቶች የሰጣችሁንን እምነት ይዘን ፣ አዲስና እጅግ ዘመናዊ የሆነዉን 4ተኛዉን ጵሮጀክታችንን በቡልጋሪያ ይዘንላቹ መምጣታችንን ስንገልፅ በታላቅ ደስታ+1
ሰላም የአዲስ ላይፍ ቤተሰቦች እስካሁን በ3ቱ ጵሮጀክቶች የሰጣችሁንን እምነት ይዘን ፣ አዲስና እጅግ ዘመናዊ የሆነዉን 4ተኛዉን ጵሮጀክታችንን በቡልጋሪያ ይዘንላቹ መምጣታችንን ስንገልፅ በታላቅ ደስታ ነዉ። ታዲያ ይህን ድንቅ ኪነ ህንፃ ላይ ለመኖር ቀድሞ ለወሰነ ደንበኛ የቅድመ ጵርጀክት ማሰጀመሪያ ልዩ ጥቅምን አዘጋጅተን በካሬ ከ80,750ጀምሮ እየሸጥን እንገኛለን። ልብ ይበሉ አዲስ ላይፍ ሰርቶ በማሰረከብ እና በግንባታ ጥራት የማይታማ ድርጅት መሆኑን ሳይዘነጉ ይህን እድል አሁኑኑ ይጠቀሙ። ለበለጠ መረጃ በ0937867901 ይደዉሉ።
27 527
9
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናችን እና በኦርቶዶክሳውያን ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ መልእክት አስተላለፉ። ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ ቅዱስነታቸው ያስተላለፉት አባታዊ የኀዘን መልእክት እንደሚከተለው ነው፦ መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡ ‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።›› (መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪) በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው። የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው። የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል። በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን። በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን። በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን። እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!! ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!! አሜን። አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም. አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ © የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት
31 885
10
+2
لا يوجد نص...
26 068
11
የምርጫ ውጤት መቼ ይፋ ይሆናል ? በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የተረጋገጠ የመጨረሻ ውጤት ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ ይ
የምርጫ ውጤት መቼ ይፋ ይሆናል ? በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የተረጋገጠ የመጨረሻ ውጤት ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ ይፋ እንደሚደረግ አርትስ ቴሌቪዥን ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጊዜ ሠሌዳ ተመልክቷል። በዚህም መሠረት የሂደቱ አፈጻጸም በሚከተለው መልኩ ይከናወናል፦ ✔️ጊዜያዊ ውጤቶች በምርጫ ጣቢያዎች፡ ከዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያዎቹ የጊዜያዊ ውጤቶች በይፋ ተለጥፈው ለሕዝብ ይፋ ይደረጋሉ። ✔️የምርጫ ክልል ጊዜያዊ ውጤቶች፡ ከግንቦት 25 እስከ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ በምርጫ ክልሎች ደረጃ ጊዜያዊ ውጤቶች ይፋ ይደረጋሉ። ✔️የውጤት መረከብ ሂደት፡ ምርጫ ቦርድ ከምርጫ ክልሎች ውጤቶችን የመረከብና የመገምገም ሥራውን ከግንቦት 26 እስከ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ያከናውናል። ✔️የመጨረሻ ውጤት፡ የሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ የተረጋገጠ የመጨረሻ ውጤት ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ በይፋ ይገለጻል። ✔️ቅሬታ ማቅረቢያ ጊዜ፡ ከምርጫው ዕለት (ግንቦት 24) ጀምሮ እስከ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ ማንኛውም የምርጫ ቅሬታዎች ተቀባይነት አግኝተው በቦርዱ ምላሽ ይሰጥባቸዋል። የምርጫ ቦርድ ይህን የውጤት አሰጣጥ ሂደት በታቀደው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት በግልጽነትና በታማኝነት ለማከናወን ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።
26 347
12
በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት ከ10 በላይ ኦርቶዶክሳውያን ሲገደሉ የ101 ዓመት እድሜ ያለው የቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወድሟል። የመድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ላይም ዘረፋ የተካሄደ ሲሆን ምእመናን ጽላቱን ይዘው ተሰደዋል፤ መኖሪያ ቤታቸውም ተቃጥሏል። ከግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት፣ አሰኮ ወረዳ፣ ጠላታ ጨፋ ቀበሌ እና ካራ ኩፍቴና በሚባሉ አካባቢዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ ያነጣጠረ አሰቃቂ ግድያ ተፈጽሟል። በአሰኮ ወረዳ ጠላታ ጨፋ ቀበሌ ብቻ በታጣቂ  ኃይሎች  በተፈጸመ ሰብአዊነት በጎደለው ጥቃት ከ10 በላይ ንጹሃን ኦርቶዶክሳውያን ተገድለዋል። በአካባቢው 101 ዓመታትን ዕድሜ ያስቆጠረው፣ የጠላታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ወውደሙ ተገልጿል። በተመሳሳይ ጥቃት በካራ ኩፍቴና መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ላይ ጥቃት የተሰነዘረ ሲሆን፣ የቤተክርስቲያኑ ንብረት የሆኑ ቤቶች በመቃጠላቸው ምእመናን የመድኃኔዓለምን ቅዱስ ጽላት ይዘው በእግራቸው ወደሌላ አካባቢ መሸሻቸው ታውቋል። በዚሁ በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት  በሺርካ ወረዳ በሁለት ወጣት ኦርቶዶክሳውያን ላይ ዘግናኝ ግድያ መፈጸሙ ተሰምቷል። ድርጊቱ የተፈጸመው ሚታና ዋጂ ቀበሌ ሲሆን፣ ታጣቂዎች ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም ወደ ወጣቶቹ መኖሪያ ቤት በመግባት በቁጥጥር ስር እንዳዋሏቸውና በመቀጠልም ወጣቶቹን ወደ ሚታና ጋዶ ቀበሌ በመውሰድ፣ አንደኛውን በስለት አር ደው፣ ሁለተኛውን ደግሞ በጥይት በመምታት በጭካኔ ሕይወታቸውን እንዳጠፉት ተገልጿል። ሕይወታቸውን ያጡት የእነዚህ ወጣቶች ሥርዓተ ቀብር ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በጋዶ ማሕደረ ስብሐት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን፣ ምዕመናንና በቤተሰብ በተገኘበት በአንድ መቃብር  ተፈጽሟል። በምሥራቅ አርሲ ሀገረ ስብከት በአገልጋዮችና ምእመናን ላይ በተደጋጋሚ ጥቃት እንደሚፈጸምበት ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ለዓመታት መረጃ እያደረሰ ቢሆንም  ዛሬም ድረስ ዘላቂ መፍትሔ አልተገኘም። መረጃው የማህበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን ነው።
19 576
13
+1
لا يوجد نص...
19 659
14
የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ውጤታማ ሆኖ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ ዜጎች በነቂስ
የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ውጤታማ ሆኖ መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ በሰጡት መግለጫ ዜጎች በነቂስ ወጥተው ከማለዳው 12፡00 ሰዓት ጀምሮ ድምፃቸውን መስጠታቸውን ገልጸዋል። እስከ እኩለ ሌሊት የቀጠለው የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታውቋል። የድምፅ ቆጠራ ሂደቱ ታዛቢዎችና የፓርቲ ተወካዮች በተገኙበት እየተከናወነ መሆኑን የገለፁ ሲሆን የድምፅ ቆጠራው ተጠናቆ ውጤቱ ይፋ እንደሚሆን አመላክተዋል። በዛሬው ዕለት በተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ፤ እስከ ምሽቱ ሁለት ሰዓት ድረስ 40 ሚሊዮን መራጮች ድምጽ መስጠታቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ተናግረዋል። የምርጫ ውጤት ቆጠራ ዛሬ በማይጠናቀቅባቸው ቦታዎች፤ በነገው ዕለት እንደሚከናወንም ሰብሳቢዋ ገልጸዋል። ሜላትወርቅ ይህን የገለጹት ዛሬ ሰኞ ግንቦት 24፤ 2018 ሲካሄድ የዋለውን ምርጫ መጠቃለል በተመለከተ ለሊት ሰባት ሰዓት ገደማ በሰጡት መግለጫ ነው። የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ በዚሁ መግለጫቸው በጸጥታ ችግር ምክንያት ምርጫ ስላልተካሄደባቸው እና ስለተቋረጠባቸው አካባቢዎች በቅድሚያ ማብራሪያ ሰጥተዋል። ዋና ሰብሳቢዋ ዛሬ እኩለ ቀን ገደማ በሰጡት መግለጫ በ143 የምርጫ ጣቢያዎች፤ በጸጥታ ችግር ምክንያት የድምጽ መስጠት ሂደቱ አለመካሄዱን ገልጸው ነበር። በአማራ ክልል በሚገኘው የኩታ በር ምርጫ ክልል በሚገኙ አራት የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ምርጫ ሳይከናወን መቅረቱንም ተናግረዋል። በመኮሳቺ እና ቀርሳ ምርጫ ክልል ያለው የጸጥታ ሁኔታ ባለመሻሻሉ በተመሳሳይ ሁኔታ የድምጽ መስጠት ሂደቱ አለመካሄዱን አብራርተዋል።
20 357
15
አሜሪካ በኢራን ላይ አዲስ የአየር ጥቃት ፈፀመች አሜሪካ በደቡባዊ ኢራን በሚገኙ የኢራን የሚሳኤል ቤዞች እና ፈንጅ ሲቀብሩ ነበር ባለቻቸው ጀልባዎች ላይ የአየር ጥቃት ፈፅማለች፡፡ የአሜሪካ ማዕከላዊ
አሜሪካ በኢራን ላይ አዲስ የአየር ጥቃት ፈፀመች አሜሪካ በደቡባዊ ኢራን በሚገኙ የኢራን የሚሳኤል ቤዞች እና ፈንጅ ሲቀብሩ ነበር ባለቻቸው ጀልባዎች ላይ የአየር ጥቃት ፈፅማለች፡፡ የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (ሴንትኮም) እንዳስታወቀው፥ ጥቃቱ በአካባቢው የሚገኙ የአሜሪካ ወታደሮችን ከጥቃት ለመከላከል የተደረገ እና የኢራንን ወታደራዊ ጫና ለመቀነስ ያለመ ነው። በአሜሪካ እና ኢራን መካከል ያለውን ጦርነት ለማቆም ስምምነት ለማድረግ ድርድር እየተደረገ መሆኑን የገለፀው የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ከስምምነት እስከሚደረስ የአሜሪካ ወታደራዊ ሃይል በሆርሙዝ ሰርጥ የጣለውን ክልከላ አጠናክሮ ይቀጥላል ብሏል። እስካሁን የአሜሪካን የአየር ጥቃት አስመልክቶ ኢራን የሰጠችው ይፋዊ ምላሽ የለም። ይሁን እንጂ የኢራን መገናኛ ብዙኃን በሆርሙዝ ሰርጥ አቅራቢያ በምትገኘው የባንደር አባስ ከተማ ፍንዳታ መሰማቱን እና የፍንዳታው ምንጭ እየተጣራ መሆኑን ዘግበዋል፡፡ ጥቃቱ በሁለቱ ሀገራት መካከል እየተካሄደ የሚገኘውን ድርድር ተፅዕኖ ውስጥ ሊከተው እንደሚችል ቢቢሲ ዘግቧል፡፡ ጥቃቱ ከተፈፀመ በኋላ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ አሁንም ድርድሩ እንደሚቀጥል ጠቁመው፥ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ በዛሬው እለት የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ከኳታሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ጋር ውይይት እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
29 428
16
የአውሮፓ ህብረት ከ2 ዓመት በፊት በኢትዮጵያ ላይ ጥሎት የነበረውን የቪዛ ገደብ አነሳ የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ከሁለት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ላይ ጥሎት የነበረውን ጥብቅ የቪዛ ማዕቀብና ገደብ
የአውሮፓ ህብረት ከ2 ዓመት በፊት በኢትዮጵያ ላይ ጥሎት የነበረውን የቪዛ ገደብ አነሳ የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ከሁለት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ላይ ጥሎት የነበረውን ጥብቅ የቪዛ ማዕቀብና ገደብ ሙሉ በሙሉ ለማንሳት መወሰኑን አስታዉቋል። ምክር ቤቱ እ.ኤ.አ. በ2024 በኢትዮጵያ ላይ የተወሰኑ የቪዛ ሕጎችን አግዶ የቆየው፣ የኢትዮጵያ መንግስት በአውሮፓ አገራት በሕገ-ወጥ መንገድ የሚኖሩ ዜጎቹን በፈቃደኝነት መልሶ የመቀበል ሂደት ላይ በቂ ትብብር እንዲያደርግ ግፊት ለመፍጠር እንደነበር ይታወሳል። የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን ባደረገው የቅርብ ጊዜ ግምገማ መሠረት፣ ባለፉት ወራት የኢትዮጵያ መንግስት በአውሮፓ አገራት ውስጥ በሕገ-ወጥ መንገድ የሚገኙ ዜጎቹን ማንነት በመለየት፣ የድንገተኛ ጊዜ የጉዞ ሰነዶችን በመስጠት እንዲሁም መደበኛ የመልሶ ማረፍ ስራዎችን በማደራጀት ረገድ ያሳየው ዲፕሎማሲያዊ እና አስተዳደራዊ ትብብር በከፍተኛ ደረጃ መሻሻሉን አረጋግጧል። የቪዛ ገደቡ መነሳቱን ተከትሎ፣ ውሳኔው ለአባል አገራቱ በግል ከቀረበበትና ማሳወቂያ ከተሰጠበት ዕለት ጀምሮ በይፋ ተግባራዊ መሆን እንደሚጀምር ምክር ቤቱ ጠቁሟል። የአውሮፓ ህብረት የቪዛ ሕግ መሠረት፣ ኮሚሽኑ ከአውሮፓ ውጭ ያሉ አገራት ስደተኞችን መልሶ በመቀበል ረገድ የሚያሳዩትን ትብብር በየጊዜው ይገመግማል። በዚህ ግምገማ መሠረት በቂ ትብብር የማያደርጉ አገራት ላይ ህብረቱ የቪዛ አሰጣጥ ሂደቱን የሚያጠብቁና መብቶችን የሚያግዱ ውሳኔዎችን ያስተላልፋል። ይህ አሁን የተወሰነው የቪዛ ገደብ መነሳት ውሳኔ፣ በኢትዮጵያ እና በአውሮፓ ህብረት መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት፣ የዜጎችን የጉዞ ነጻነት እንዲሁም ሕጋዊ የስደት ቁጥጥር ስራዎችን ይበልጥ ያጠናክራል ተብሎ ይጠበቃል። (ካፒታል-ጋዜጣ)
32 557
17
#ንግድባንክ መልእክት! በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሠረት በሀገሪቱ በሚገኙ በተመረጡ ከተሞች ላይ የተከፈቱ የባንክ ሂሳቦች እስከ ግንቦት 06 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ ከደንበኞች የፋይዳ መታ
#ንግድባንክ መልእክት! በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሠረት በሀገሪቱ በሚገኙ በተመረጡ ከተሞች ላይ የተከፈቱ የባንክ ሂሳቦች እስከ ግንቦት 06 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ ከደንበኞች የፋይዳ መታወቂያ ጋር እንዲተሳሰር የተቀመጠው ቀነ ገደብ መጠናቀቁን ተከትሎ በትዕዛዙ መሰረት ደንበኞች እነዚህን ሂሳቦች ማንቀሳቀስ እንዳይችሉ ተደርጓል፡፡ ይህንን ተከትሎ በከፍተኛ ሁኔታ የማስተሳሰር ጥያቄ ወደ ባንካችን እየቀረበ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ባንካችን ይህንን ጫና በመቋቋም ለደንበኞቻችን በሚፈለገው ፍጥነት ለቀረቡ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት የተለያዩ አሰራሮችን ተግባራዊ አድርጓል፡፡ ለአብነት ከግንቦት 7 እስከ ግንቦት 12 በተለየ ምክንያት እንዳይንቀሳቀሱ ከተደረጉት ሂሳቦች ውጪ የተሳሰሩ ሂሳቦችን ደንበኞች ማንቀሳቀስ እንዲችሉ ተደርጓል፡፡ እንዲሁም ከ ከግንቦት 12 ጀምሮ ደንበኞች ሂሳባቸውን እንዳስተሳሰሩ የመረጃ ስርዓታችን (system) በራሱ ጊዜ ገደቡን እንዲያነሳ ተደርጓል፡፡ መሰል ፈጣን ምላሾን እየሰጠን የደንበኞቻችንን እርካታ እውን ለማድረግ የምንሰራ መሆኑን እያረጋገጥን በዚህ ሂደት ላሳያችሁት ትዕግስት ከልብ እያመሰገንን በደንበኞቻችን ላይ ለተፈጠረው መጉሏሏት ይቅርታ ለመጠየቅ እንወዳለን፡፡ በተጨማሪም እንዳይንቀሳቀስ ከተደረጉ ሂሳቦች እና ከነዚህ ውጭ በተቀሩት የኢትዮጵያ ክፍሎች የሚገኙ የባንክ ቅርንጫፍ ደንበኞች እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ አስቀድማችሁ የማስተሳሰር ሂደቱን በባንካችን ቅርንጫፎች በመገኘት ወይም በበይነ መረብ (Online) ማስተሳሰሪያ አማራጭ (https://cbefayda.cbe.com.et) ሂሳባችሁን ለማንቀሳቀስ እንድትችሉ በአክብሮት እንጠይቃለን:: የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
25 499
18
ከቅርብ አመታት ወዲ ውበትን ከጥራት ጋር ባለበት ጊዜ ሰርቶ በማስረከብ የሚታወቀዉ አዲስ ላይፍ ሪል እስቴት እንሆ በቡልጋሪያ በታላቅ ዲስካዉንት ቅድሚያ ለሚገዙ በመረጡት ፍሎር ተስማሚ በሆነላቸዉ ቦታ+3
ከቅርብ አመታት ወዲ ውበትን ከጥራት ጋር ባለበት ጊዜ  ሰርቶ በማስረከብ የሚታወቀዉ አዲስ ላይፍ ሪል እስቴት  እንሆ በቡልጋሪያ በታላቅ ዲስካዉንት ቅድሚያ ለሚገዙ በመረጡት ፍሎር ተስማሚ በሆነላቸዉ ቦታ ቅድሚያ እንደሚሰጣቸዉ ሲገልፅ በራሱ በመተማመን ነዉ። ታዲያ እናተም አዲስ ላይፍን ሲመርጡ ከ10% ቅድሚያ ክፍያ ጀምሮ የምናስተናግዶ ሲሆን ህንፃዉ ተገንብቶ እስኪያልቅ ድረስ ምንም አይነት የዋጋ ግሽፈት ቢከሰት ደንበኛችንን እንደማይመለከት የጋራ መተማመኛ ዉል ላይ በማስቀመጥ እናስረክቦታለን። 100% ለሚከፍል ከ80,750 ጀምሮ ለበለጠ መረጃ➤በ0937867901 ይደዉሉ።
24 602
19
አርሰናል ከ22 ዓመታት በኋላ የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን ሆነ✅ ማንቸስተር ሲቲ አቻ መውጣቱን ተከትሎ አርሰናል የፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ሆነ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 37ኛ ሳምንት ማንቸስተር ሲቲ ከበ+7
አርሰናል ከ22 ዓመታት በኋላ የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን ሆነ✅ ማንቸስተር ሲቲ አቻ መውጣቱን ተከትሎ አርሰናል የፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን ሆነ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 37ኛ ሳምንት ማንቸስተር ሲቲ ከበርንማውዝ ጋር ያደረገውን ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ ውጤት አቻ መውጣቱን ተከትሎ የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑን አረጋግጧል። በቫሊቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ጁኒየር ክሩፒ በመጀመሪያው አጋማሽ 38ኛ ደቂቃ ላይ ሲያስቆጥር ኧርሊንግ ሃላንድ ሲቲን አቻ ያደገውን ግብ አስቆጥሯል። ፕሪሚየር ሊጉ ሊጠናቀቅ አንድ ጨዋታ ብቻ የቀረ ሲሆን እስካሁን 82 ነጥቦችን የሰበሰበው አርሰናል 78 ነጥቦች ካሉት ተከታዩ ማንቸስተር ሲቲ ጋር የአምስት ነጥቦች ልዩነት ያለው በመሆኑ ሻምፒዮናነቱን አረጋግጧል።
28 554
20
የዓለም ጤና ድርጅት በኢቦላ ቫይረስ ምክንያት ዓለማቀፍ የጤና አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና በኡጋንዳ በከፍተኛ ሁኔታ እያገረሸ የመጣውን የ
የዓለም ጤና ድርጅት በኢቦላ ቫይረስ ምክንያት ዓለማቀፍ የጤና አስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አወጀ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና በኡጋንዳ በከፍተኛ ሁኔታ እያገረሸ የመጣውን የኢቦላ ቫይረስ ስርጭት ተከትሎ፣ ወረርሽኙን ይፋዊ የዓለማቀፍ የህዝብ ጤና ስጋት አድርጎ አውጇል። ​የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው (ኤክስ) ባስተላለፉት መረጃ፣ እስካሁን ባለው ጊዜ ውስጥ በቫይረሱ ሳቢያ የ 88 ሰዎች ህይወት ማለፉንና 300 ያህል ሰዎች ደግሞ በበሽታው መያዛቸውን አረጋግጠዋል። ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም የኢቦላ ቫይረስ ልክ እንደ ኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሁሉ የመቀጣጠልና በከፍተኛ ፍጥነት የመስፋፋት አቅም እንዳለው በማስገንዘብ፣ የከፋ ጉዳት ሳይደርስ አስቸኳይና ጥብቅ የሆኑ የመከላከል ስራዎች በአለም አቀፍ ደረጃ እንዲተገበሩ ጥሪ አቅርበዋል።
20 907