ETHIO-MEREJA®
News & Media Channel® Addisababa, Ethiopia🇪🇹 ውድ የኢትዮ መረጃ ቤተሰቦች ከዚህ የቴሌግራም ቻናል ውጪ ሌላ መረጃ የምናቀርብበት ምንም አይነት የዩቲዩብ፣ የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆች እንደሌለን ለማሳወቅ እንወዳለን፣ ስለሆነም በተመሳሳይ ስም በተከፈቱ ገፆች እንዳይሸወዱ ጥንቃቄ እንድታደርጉ እናሳስባለን። ለጥቆማና ማስታወቂያ ለማሰራት 👉 @ethio_merejabot
إظهار المزيد📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ETHIO-MEREJA®
تُعد قناة ETHIO-MEREJA® (@ethio_mereja) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 100 773 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 554 في فئة الأخبار والوسائط والمرتبة 292 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 100 773 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 30 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -1 327، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -45، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 13.02%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 8.27% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 13 123 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 8 338 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 49.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“News & Media Channel®
Addisababa, Ethiopia🇪🇹
ውድ የኢትዮ መረጃ ቤተሰቦች ከዚህ የቴሌግራም ቻናል ውጪ ሌላ መረጃ የምናቀርብበት ምንም አይነት የዩቲዩብ፣ የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆች እንደሌለን ለማሳወቅ እንወዳለን፣ ስለሆነም በተመሳሳይ ስም በተከፈቱ ገፆች እንዳይሸወዱ ጥንቃቄ እንድታደርጉ እናሳስባለን።
ለጥቆማና ማስታወቂያ ለማሰራት
👉 @ethio_mere...”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 31 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الأخبار والوسائط.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 31 يوليو | 0 | |||
| 30 يوليو | 0 | |||
| 29 يوليو | 0 | |||
| 28 يوليو | 0 | |||
| 27 يوليو | 0 | |||
| 26 يوليو | 0 | |||
| 25 يوليو | 0 | |||
| 24 يوليو | 0 | |||
| 23 يوليو | 0 | |||
| 22 يوليو | 0 | |||
| 21 يوليو | 0 | |||
| 20 يوليو | 0 | |||
| 19 يوليو | 0 | |||
| 18 يوليو | 0 | |||
| 17 يوليو | 0 | |||
| 16 يوليو | 0 | |||
| 15 يوليو | 0 | |||
| 14 يوليو | 0 | |||
| 13 يوليو | 0 | |||
| 12 يوليو | 0 | |||
| 11 يوليو | 0 | |||
| 10 يوليو | 0 | |||
| 09 يوليو | 0 | |||
| 08 يوليو | 0 | |||
| 07 يوليو | 0 | |||
| 06 يوليو | 0 | |||
| 05 يوليو | 0 | |||
| 04 يوليو | 0 | |||
| 03 يوليو | +2 | |||
| 02 يوليو | +4 | |||
| 01 يوليو | 0 |
| 2 | ወደ ስዊድን ያቀኑ 20 የእግርኳስ ቡድን አባላት መጥፋታቸው ተሰማ
ወደ ስዊድን ያቀኑ ዕድሜያቸው ከ 14 እስከ 17 የሚገመት 20 ታዳጊ የእግርኳስ ተጫዋቾች ከ መሪያቸው ጋር መጥፋታቸውን ስዊድን ሄራልድ ዘግቧል።
"ጎቲያካፕ" ለተሰኘ የእግር ኳስ ውድድር ከኢትዮጵያ የሔዱት ታዳጊዎች ካረፉበት ትምሕርት ቤት ሳያሳውቁ በመውጣት መሰወራቸውን የስዊድን ፖሊስ አስታውቋል።እግር ኳስ ተጫዋቾቹ ወደ ኢትዮጵያ እንዳልተመለሱ ያረጋገጠው ፖሊስ፤ በራሳቸው ፍላጎት ጠፍተው ሊሆን እንደሚችል አመላክቷል።
በጉዳዩ ዙርያ ምላሽ የሰጠው ፌደሬሽኑ የቡድኑ አባላት መጥፋት እንዳሳዘነው እና ታዳጊዎቹ በመሰል ውድድሮች ላይ በራሳቸው ጥረት በሚያገኙት እድል ወደ ውድድሩ ማምራታቸውን አሳውቋል።
በመሆኑም ታዳጊዎቹ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን የወከሉ አለመሆኑን እየገለፅን በአንዳንድ አካላት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አባላት እንደሆኑ እየተገለጸበት ያለው መንገድ ትክክል አለመሆኑን እናሳውቃለን ብሏል ፌደሬሽንኑ።
ፖሊስ የጠፉት ታዳጊዎች ዕድሜያቸው ከ14 እስከ 17 ዓመት የሆኑ ወጣቶች ሲሆኑ፣ ከእነሱ ጋር አንድ ወይም ከዚያ በላይ የቡድን መሪዎች አብረው ጠፍተዋል ብሏል። ይህ የታወቀው በውድድሩ የመጨረሻ ቀን ሲሆን ያረፉበት ትምህርት ቤት አስተዳዳሪ አባላቱ ያለ ምንም ማስታወቂያ ለቀው መሄዳቸውን ካረጋገጠ በኋላ ለፖሊስ ማሳወቁም ተዘግቧል። | 9 935 |
| 3 | በምስራቅ አርሲ ዞን በታጣቂዎች የተፈጸሙ ከባድ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ይፋ ሆኑ
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 2018 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ በታጣቂ ቡድኖች በተፈጸሙ ጥቃቶች ላይ ያከናወነውን የምርመራ ግኝት የያዘ 158ኛ ልዩ መግለጫውን ይፋ አድርጓል። በዞኑ በሚገኙ ሽርካ፣ ሮቤ፣ ጀጁ፣ መርቲ፣ ጉና፣ ሆንቆሎ ዋቤ፣ አርሲ ሲሬ፣ ሙኒሳ እና አሰኮ ወረዳዎች በተፈጸሙት ጥቃቶች በሃይማኖትና ማንነት ላይ ያነጣጠሩ የሰዎች ግ ድያ፣ አካል ጉዳት፣ እገታ፣ መፈናቀል እና የንብረት ውድመት መከሰታቸው ተረጋገጧል።
ኢሰመጉ ከመጋቢት 3 እስከ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ባደረገው የመስክ ምርመራና ከሟች ቤተሰቦች፣ ተጎጂዎች፣ የዓይን እማኞች እና የአርሲ ሀገረ ስብከት ቤተክህነት ጽሕፈት ቤቶች ባሰበሰባቸው መረጃዎች መሰረት በጥቃቱ በርካታ ንጹሃን ዜጎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። ከ2014 ዓ.ም እስከ ግንቦት 24/2018 ዓ.ም ዓ.ም የተፈጸሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች የምርመራ ስራን አከናውኗል፡፡
በተሰበሰበው መረጃ መሰረት:-
📌 በሽርካ ወረዳ 116፣
📌 በመርቲ ወረዳ 117፣
📌 በጀጁ ወረዳ 101፣
📌 በሮቤ ወረዳ 47፣
📌 በጉና ወረዳ 26፣
📌 በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ 20፣
📌 በሙኒሳ ወረዳ 19፣
📌 በአሰኮ ወረዳ 5 ንጹሃን እና 4 የጸጥታ አካላት (ሚሊሻዎች) እንዲሁም
📌 በሲሬ ወረዳ 3 ሰዎች ተገ ድለዋል።
ከግድ ያው በተጨማሪ ከፍተኛ የእገታ ወንጀል የተፈጸመ ሲሆን፣
📍በሮቤ ወረዳ 156 ሰዎች፣
📍በጀጁ ወረዳ 182 ሰዎች፣
📍በመርቲ ወረዳ 29 ሰዎች
📍በሽርካ ወረዳ 39 ሰዎች ታግተው በርካቶቹ በካሳ ክፍያ የተለቀቁ ቢሆንም የበርካታ ታጋቾች የደረሱበት ሁኔታ እስከ አሁን አይታወቅም። እንዲሁም በሕፃናትና አዛውንቶች ላይ የቆሰሉና አካል ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ከቀያቸው ተፈናቅለዋል።
የአሰኮ ወረዳ የጠለታ ጨፋ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያንን ጨምሮ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት መዘረፋቸውና መቃጠላቸው፣ የመኖሪያ ቤቶች መፍረሳቸው እና የቀንድና የጋማ ከብቶች መዘረፋቸው በምርመራው ተረጋግጧል።
ኢሰመጉ መንግስት የዜጎችን በሕይወት የመኖርና የንብረት ጥበቃ የማድረግ ሕገ-መንግሥታዊ ግዴታውን እንዲወጣ፣ በጥሰቱ የተሳተፉ አካላት በሕግ እንዲጠየቁ እና ለተፈናቀሉት ዘላቂ መፍትሔ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል። | 10 405 |
| 4 | #ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
👉Studio 32ካሬ 1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ 2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና 3 መኝታ ከ 118ካሬ ጀምሮ
👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት
👉100% ለሚከፍሉ እስከ 35% ቅናሽ
👉20% ከፍለው ቀሪውን በ 16 ዙር ከፍለው የሚጨርሱት
👉 በመገናኛ ዲያስፖራ አደባባይ ፊት ለፊት(የካ ክፍለ ከተማ ጀርባ) ከቴምር ሪልስቴት
👉በተጨማሪም በቡልጋሪያ(አፍሪካ ህብረት ፊት ለፊት) እና በአዋሬ(ቤተመንግስት አጠገብ) አፓርትመንቶች አሉን
💥 የንግድ ሱቆች
#ቡልጋሪያ ላይ ከ900ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ፒያሳ ላይ ከ1.4ሚሊዮን ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ቃሊቲገላን ላይ ከ500ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ።
#ሳር ቤት አዳምስ አጠገብ ከ 900ሺ ብር ቅድመ ክፍያ
🎯ልብይበሉ
# ያለምንም ወለድና የግንባታ እቃዎች ጭማሪ በኢትዮጵያ ብር ከፍለው የሚጨርሱት ነው
#ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
👇👇👇👇👇👇
+251939770177
+251996856273
https://t.me/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp. https://wa.me/251939770177
Telegram :@KalTemerRealEstate | 9 855 |
| 5 | በቢሸፍቱ አቡሴራ ላይ ለሚገነባው አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጄክት አበዳሪዎች ቃል ስለገቡት የ8.5 ቢሊዮን ዶላር ብድር የመጨረሻ ውሳኔ መገቢት 2019 ዓም እንደሚታወቅ ታወቀ
"የጡረታ ጊዜዬ ስለተጠናቀቀ የመንግስትን ውሳኔ እየጠበቅሁ ነው" አቶ መስፍን ጣሰው
- የኢትዮጵያ አየር መንገድ 9.1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቱን አስታወቀ
- ለ5000 ሠራተኞች ቤት እየገነባ መሆኑን አስታውቋል
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በኦሮሚያ ክልል ቢሸፍቱ አቡሴራ ለሚያስገነባው ግዙፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ ፕሮጄክት 8.5 ቢሊዮን ዶላር ብድር ለመስጠት ቃል የገቡ አበዳሪዎች የመጨረሻ ውጤት የሚታወቀው በቀጣይ ዓመት 2019 ዓም መሆኑን የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አስታወቁ።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን ይህን የተናገሩት ዛሬ ሐምሌ 22 ቀን 2018 ዓ.ም በስካይላይት ሆቴል አመታዊ አፈጻጸሙን አስመልክቶ መግለጫ ሲሰጡ ነው።
ዋና ስራ አስፈጻሚው አየር መንገድ ግሩፑ ያገኘው ገቢ ካለፈው በጀት ዓመት አንጻር በ20 በመቶ ቢያድግም፣ ወጪውም በገልፍ ጦርነትና በሌሎች ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ምክንያት በ25 በመቶ ከፍ ማለቱንም አሳውቀዋል። አየር መንገዱ በዚህ አመት 897ሺህ ቶን ጭነት ያጓጓዘ ሲሆን፣ ይህም ከእቅዱ 16 በመቶ ከፍ ያለ መሆኑን አቶ መስፍን አሳውቀዋል።
አየር መንገድ ግሩፑ በተጠናቀቀው በጀት አመት አራት አዳዲስ አለም አቀፍ በረራዎችን የጀመረ ሲሆን፣ ከእነዚህም መካከል ወደ ፖርቹጋል፣ ቬትናምና አቡዳቢ የተጀመሩት በረራዎች ተጠቃሽ ናቸው። | 10 677 |
| 6 | በጃፓን ኩማሞቶ በሬክተር ስኬል 7.1 የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ
በጃፓን ደቡባዊ የኪዩሹ ደሴት በሚገኘው ኩማሞቶ ግዛት ዛሬ የደረሰው ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጥ በሰዎች ሕይወት፣ በመሠረተ ልማት እና በኢንዱስትሪ ተቋማት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አስከትሏል።
የመጀመሪያ ግምገማዎች መንቀጥቀጡ በ6.8 እስከ 7.1 ማግኒትዩድ መካከል መለካቱን ያሳያሉ፤ ባለሥልጣናት የመጨረሻ ሳይንሳዊ ግምገማ እየተጠበቀ መሆኑን ገልጸዋል።
ከአደጋው በኋላ በካሺማ ከተማ የሚገኘው «ኢዮን ሞል ኩማሞቶ» ውስጥ ከባድ ፍንዳታ ተከስቶ የሕንፃው ክፍል በመፍረሱ በርካታ ሰዎች በፍርስራሹ ስር መቀራቸው ተገልጿል።
እስካሁን ከ20 እስከ 30 የሚደርሱ ሰራተኞች የጠፉ ሲሆን፣ የእሳት አደጋ እና የነፍስ አድን ቡድኖች የማዳን ሥራ እያካሄዱ ነው። ፍንዳታው ከጋዝ መፍሰስ ጋር ሊያያዝ እንደሚችል ጥርጣሬ ቢኖርም፣ ባለሥልጣናት መንስኤውን እያጣሩ ነው።
በሌላ በኩል፣ በአካባቢው በሚገኝ የወረቀት ፋብሪካ ውስጥ የነበሩ በርካታ ሰራተኞች ያሉበት እስካሁን አልታወቀም።
በባቡር መስመሮች፣ በድልድዮች እና በመንገዶች ላይም ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል፤ የባቡር አገልግሎት ተቋርጧል፣ አንዳንድ ባቡሮችም ከሐዲድ ወጥተዋል። በአካባቢው የአየር ማረፊያም ለጊዜው ተዘግቷል።
የኃይል አቅርቦት በአስር ሺዎች ቤቶች ተቋርጧል፤ ከ60 በላይ የተከታታይ ንዝረቶች በመመዝገባቸውም ተጨማሪ የመሬት መንሸራተት እና የሕንፃ መውደቅ አደጋ ስለሚኖር ህዝቡ ከተጎዱ ሕንፃዎች እንዲርቅ ጥሪ ቀርቧል።
የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ሳናኤ ታካኢቺ የመከላከያ ኃይሎችን፣ የእሳት አደጋ ባለሙያዎችን እና ሌሎች የአደጋ ምላሽ ቡድኖችን ወደ ተጎዱ አካባቢዎች መላካቸውን ገልጸዋል።
መረጃው ለሌሎች እንዲደርስ ሼር ያድርጉ!
-ETHIO-MEREJA-
T.me/ethio_mereja | 11 784 |
| 7 | አንቀጽ 39 እስከ መገንጠል የሚለው እስከ መዋሃድ ተብሎ እንዲስተካከል ሐሳብ ቀረበ
የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ቀርቶ ሕብረ ብሔራዊ አንድነት ኮሚሽን የሚል ተቋም እንዲቋቋም ተጠይቋል
በአገራዊ ምክክር ጉባዔ በአሥርና በ50 ተመካካሪ ቡድን ሲወያዩ የቆዩ ተመካካሪዎች ያጠናከሩትን የአጃንዳ ሐሳብ፣ 250 አባላት ላሉት የምክክር ቡድን ማቅረብ ሲጀምሩ፣ በኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት የብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መብት "እስከ መገንጠል" በሚለው አንቀጽ 39 ስር የተቀመጠው ሐረግ "እስከ መዋሃድ" ተብሎ እንዲስተካከል የሚል ሐሳብ ዛሬ ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ቀረበ።
ሀሳቡ የቀረበው፣ አሥርና 50 አባላት ባላቸው ንዑሳን ቡድኖች ስር ሲወያዩ የቆዩ ተመካካሪዎች፣ 250 አባላት ላሉት ሥልታዊ ቡድን ያጠናቀሩትን የአጀንዳ ሐሳብ ሲያቀርቡ ነው።
በዚህም ሐሳብ ከቀረበባቸው አጀንዳዎች መካከል፣ የመንግሥት አደረጃጀትና ቅርጽ፣ እንዲሁም የፖለቲካ ሥርዓት፣ የፖለቲካ ውክልናና የምርጫ ሥርዓትን የተመለከተው አንዱ ሲሆን፣ በሥሩም የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት (የብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መብት አንቀጽ 39) ንዑስ አጀንዳ መሆኑ ይታወቃል።
ይህ ንዑስ አጀንዳ(አንቀጽ 39)፣ የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት የሚሰጥ በመሆኑ፣ ሙሉ ለሙሉ ሳይሻር "እስከ መገንጠል" የሚለው ሐረግ ብቻ ከድንጋጌው እንዲወጣና ባለበት እንዲቀጥል የሚጠይቁ ሐሳቦች ከአሥርና ከ50ዎቹ ንዑስ ብድኖች በአብዛኛው ቀርበዋል። | 13 002 |
| 8 | #ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
👉Studio 32ካሬ 1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ 2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና 3 መኝታ ከ 118ካሬ ጀምሮ
👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት
👉100% ለሚከፍሉ እስከ 35% ቅናሽ
👉20% ከፍለው ቀሪውን በ 16 ዙር ከፍለው የሚጨርሱት
👉 በመገናኛ ዲያስፖራ አደባባይ ፊት ለፊት(የካ ክፍለ ከተማ ጀርባ) ከቴምር ሪልስቴት
👉በተጨማሪም በቡልጋሪያ(አፍሪካ ህብረት ፊት ለፊት) እና በአዋሬ(ቤተመንግስት አጠገብ) አፓርትመንቶች አሉን
💥 የንግድ ሱቆች
#ቡልጋሪያ ላይ ከ900ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ፒያሳ ላይ ከ1.4ሚሊዮን ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ቃሊቲገላን ላይ ከ500ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ።
#ሳር ቤት አዳምስ አጠገብ ከ 900ሺ ብር ቅድመ ክፍያ
🎯ልብይበሉ
# ያለምንም ወለድና የግንባታ እቃዎች ጭማሪ በኢትዮጵያ ብር ከፍለው የሚጨርሱት ነው
#ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
👇👇👇👇👇👇
+251939770177
+251996856273
https://t.me/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp. https://wa.me/251939770177
Telegram :@KalTemerRealEstate | 12 770 |
| 9 | በኢትዮጵያ በመጪዎቹ ዓመታት ሥራ አጥነት ፈታኝ እንደሚሆን የዓለም የሥራ ድርጅት ገለጸ
የዜጎች ማኅበራዊ ጥበቃ አገልግሎት እንዲጨምር ጠይቋል
በትምህርት ያልገፉና የሥራ ልምድ የሌላቸው ወጣቶች በክህሎት ማነስና በራሳቸው ሥራ ለመጀመር በሚገጥማቸው የፋይናንስ ችግር የሥራ ዕድል ዕጦት እንደሚያጋጥማቸው፣ የዓለም የሥራ ድርጅት (ILO) ገለጸ፡፡
የዓለም የሥራ ድርጅት ከሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከዩናይትድ ኪንግደም ተራድኦ ድርጅት (ዩኤአይድ) እና ከሌሎች ተቋማት በጋራ በመሆን፣ በማኅበራዊ ጥበቃ ላይ ያዘጋጀውን ሪፖርት ይፋ ሲያደርግ ነው ይህንን የገለጸው፡፡በሪፖርቱ መሠረት ቁጥራቸው እያደገ ያለው ሥራ ፈላጊ ወጣቶች፣ በክህሎት ክፍተትና የራስን ቢዝነስ ለመጀመር በሚገጥማቸው የፋይናንስ ዕጦት ከፍተኛ ተግዳሮት ይገጥማቸዋል፡፡
የሕፃናት ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ወደ ሥራ ሊገባ የሚገባውን የወጣት ቁጥር የሚያሳድገው በመሆኑ፣ ዕድገቱን ከከተሞች የሥራ ገበያ ዕድል ጋር አጣጥሞና አዋህዶ መሄድ ከፍተኛ ፈተና ይሆናል ብሏል፡፡
በአገር አቀፍ ደረጃ የአካል ጉዳተኞች ቁጥር 17.6 በመቶ እንደሚደርስ ጠቅሶ፣ አካታችና ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ ተሳትፎን የሚደግፉ ፖሊሲዎችና መሠረተ ልማቶችን ማስፋፋት እንደሚያስፈልግ ገልጿል፡፡
በአገር አቀፍ ደረጃ ለሥራ ብቁ የሆነው የሕዝብ ቁጥር እ.ኤ.አ. በ2015 ከነበረበት 54.7 ሚሊዮን እ.ኤ.አ. በ2025 74.8 ሚሊዮን፣ እ.ኤ.አ. በ2030 ወደ 85.3 እንደሚደርስ ሪፖርቱ ያመለክታል፡፡ | 13 298 |
| 10 | የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት
ነገ ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን የኃይል የሚቋረጥባቸው አካባቢዎች፦
✅ከጠዋቱ 2፡00-10፡00
👉አያት፣ አይ ሲ ኤም ሲ ሆስፒታል፣ ስኩል ኦፍ ቱሞሮ፣ መሪ መስኪድ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00-12፡00
👉መቀሌ፣ኤስ ኦ ኤስ፣ ቀበሌ 14፣15፣16 እና 17፣ ዓይን ዓለም እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00-10፡00
👉አዋሽ መልኬሳ መግቢያ እና ከተማ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡00-7፡00
👉መቀሌ ቬተርነሪ ካምፓሰ፣ ኤልሻዳይ፣ ሻፋት፣ ዳጋይ እና ገብረ ሰገን ውሃ ግድብ እና አካባቢው፣
✅ከጠዋቱ 2፡30-11፡00
👉ባህርዳር ጊዮን ት/ቤት፣ሞላልኝ ግሮሰሪ እና አካባቢው የኃይል አቅርቦትይቋረጣል።
ስለሆነም በተጠቀሱት አካባቢዎች የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው ተጠናቆ የኃይል አቅርቦቱ እስኪ መለስ ድረስ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን።
#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት
ሐምሌ 18/2018 ዓ.ም | 15 434 |
| 11 | #ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
👉Studio 32ካሬ 1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ 2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና 3 መኝታ ከ 118ካሬ ጀምሮ
👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት
👉100% ለሚከፍሉ እስከ 35% ቅናሽ
👉20% ከፍለው ቀሪውን በ 16 ዙር ከፍለው የሚጨርሱት
👉 በመገናኛ ዲያስፖራ አደባባይ ፊት ለፊት(የካ ክፍለ ከተማ ጀርባ) ከቴምር ሪልስቴት
👉በተጨማሪም በቡልጋሪያ(አፍሪካ ህብረት ፊት ለፊት) እና በአዋሬ(ቤተመንግስት አጠገብ) አፓርትመንቶች አሉን
💥 የንግድ ሱቆች
#ቡልጋሪያ ላይ ከ900ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ፒያሳ ላይ ከ1.4ሚሊዮን ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ቃሊቲገላን ላይ ከ500ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ።
#ሳር ቤት አዳምስ አጠገብ ከ 900ሺ ብር ቅድመ ክፍያ
🎯ልብይበሉ
# ያለምንም ወለድና የግንባታ እቃዎች ጭማሪ በኢትዮጵያ ብር ከፍለው የሚጨርሱት ነው
#ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
👇👇👇👇👇👇
+251939770177
+251996856273
https://t.me/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp. https://wa.me/251939770177
Telegram :@KalTemerRealEstate | 15 390 |
| 12 | ኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ግዙፍ የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ ግንባታ እያጠናቀቀች ነው
ኢትዮጵያ ጥሬ ወርቅን ወደ ዱባይ በመላክ ለብዙ አስርት ዓመታት ስታካሂድ የቆየችውን አሰራር በማቆም የመጀመሪያውን ግዙፍ ሀገር በቀል የወርቅ ማጣሪያ ፋብሪካ ሥራ ለማስጀመር የመጨረሻ ዝግጅቷን እያጠናቀቀች ይገኛል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው አዲስ መመሪያ መሠረት ከእንግዲህ በሀገሪቱ የሚመረተው ማናቸውም ወርቅ ወደ ውጭ አገር ከመላኩ በፊት በሀገር ውስጥ ደረጃቸውን የጠበቁ የወርቅ አሞሌዎች ሆነው መጣራት ይኖርባቸዋል።
ይህ አዲስ አሰራር የሀገሪቱን የኤክስፖርት ገቢ ከፍ የሚያደርግ የውጭ ምንዛሬ ክምችትን የሚያጠናክር እና ሕገ-ወጥ የወርቅ ኮንትሮባንድን በከፍተኛ ደረጃ የሚቀንስ እንደሚሆን ታምኖበታል።
በአሁኑ ወቅት የመጨረሻውን የፍተሻ ምዕራፍ እያጠናቀቀ የሚገኘው ይህ ዘመናዊ ተቋም በበቀጣይ ዓመት ሥራ የሚጀምር ሲሆን እንደ ኩርሙክ የወርቅ ፕሮጀክት ያሉ አበይት የማዕድን ልማቶችን ጨምሮ እያደገ የመጣውን ሀገራዊ የወርቅ ምርት ሙሉ በሙሉ የሚያስተናግድ ይሆናል። | 15 325 |
| 13 | ሂውማን ራይትስ ዎች በዌስት_ባንክ የሰፈሩ የእስራኤል ዜጎች የሚያካሂዱት ጥቃት ትልቅ እልቂት ሊያስከትል እንደሚችል አስጠነቀቀ
የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቹ ሂውማን ራይትስ ዎች በዌስት ባንክ አካባቢዎች የሰፈሩ የእስራኤል ዜጎች የሚያካሂዱት ጥቃት እየጨመረ በመምጣቱ ተጨማሪ እልቂቶችን ሊያስከትል እንደሚችል በማስጠንቀቅ የእስራኤል መንግሥት ጥቃቶችን ከመከላከል መቆጠቡን እና ተጠያቂነት ላለመኖር ድርጊቶች መንገድ መክፈቱን ከሰሰ።
ሐምሌ 17 በወጣው መግለጫ፣ ድርጅቱ ናብሉስ አቅራቢያ በሚገኘው የታል የፍልስጤም መንደር ላይ በተፈጸሙ ሁለት ጥቃቶች የአራት ፍልስጤማውያን እና የሁለት እስራኤላውያን ሕይወት ማለፉን ገልጿል።
የመብት ተሟጋች ቡድኑ እንደገለጸው፣ የቅርብ ጊዜው ጥቃት፤ በአካባቢው የሰፈሩ የታጠቁ እስራኤላውያን በፍልስጤም ማህበረሰቦች ላይ ጥቃት የሚያሰነዝሩበትን፣ የእስራኤል ወታደሮች ደግሞ በጥቃቱ የሚሳተፉበትን ወይም ጣልቃ ከመግባት የሚቆጠቡበትን ሰፊ ክስተት ያመላክታል። በጥቃቶቹ ላይ ኃላፊነት ያለባቸው ሰዎች ብዙ ጊዜ ከእስራኤል መንግሥት የገንዘብ፣ የቁሳቁስ እና የሕግ ድጋፍ እንደሚያገኙ ድርጅቱ አክሎ ገልጿል። | 19 897 |
| 14 | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በዲጂታል ገንዘቦች እና በቨርቹዋል ሀብቶች ዝውውር ላይ ጥብቅ እገዳ ጣለ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በህግ ከተፈቀደው ውጪ በማናቸውም የቨርቹዋል ሀብቶች ግብይት ማድረግ በጥብቅ የተከለከለ መሆኑን አስታወቀ።
እገዳው ቢትኮይንን ጨምሮ ሌሎች ክሪፕቶከረንሲዎችን ብቻ ሳይሆን፣ ለማንኛውም ክፍያና ኢንቨስትመንት የሚያገለግሉ በዲጂታል መልኩ የሚተላለፉ መግለጫዎችንም ያካትታል።
በተለይም የሚከተሉት ተግባራት ሙሉ በሙሉ የተከለከሉ ናቸው ብሏል ባንኩ;
👉በቨርቹዋል ሀብት እና በመደበኛ ገንዘብ መካከል የሚደረግ መመንዘር
👉በቨርቹዋል ሀብቶች መካከል የሚደረግ ልውውጥና ዝውውር
👉የቨርቹዋል ሀብቶችን ማስቀመጥ፣ ማስተዳደር እና የፋይናንስ አገልግሎት መስጠት
ህብረተሰቡ ከህጋዊ ተጠያቂነት፣ ከማጭበርበር፣ ከሳይበር ጥቃት እና ከከባድ የገንዘብ ኪሳራ ለመጠበቅ ከነዚህ እንቅስቃሴዎች እንዲቆጠብ ባንኩ አሳስቧል። | 17 266 |
| 15 | #ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
👉Studio 32ካሬ 1 መኝታ 60ካሬ ጀምሮ 2 መኝታ 90ካሬ ጀምሮ እና 3 መኝታ ከ 118ካሬ ጀምሮ
👉40% ለምትከፍሉ 10% ቅናሽ ቀሪውን 60% ቤቱን ስትረከቡ የምትከፍሉት
👉100% ለሚከፍሉ እስከ 35% ቅናሽ
👉20% ከፍለው ቀሪውን በ 16 ዙር ከፍለው የሚጨርሱት
👉 በመገናኛ ዲያስፖራ አደባባይ ፊት ለፊት(የካ ክፍለ ከተማ ጀርባ) ከቴምር ሪልስቴት
👉በተጨማሪም በቡልጋሪያ(አፍሪካ ህብረት ፊት ለፊት) እና በአዋሬ(ቤተመንግስት አጠገብ) አፓርትመንቶች አሉን
💥 የንግድ ሱቆች
#ቡልጋሪያ ላይ ከ900ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ፒያሳ ላይ ከ1.4ሚሊዮን ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ፣
#ቃሊቲገላን ላይ ከ500ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ።
#ሳር ቤት አዳምስ አጠገብ ከ 900ሺ ብር ቅድመ ክፍያ
🎯ልብይበሉ
# ያለምንም ወለድና የግንባታ እቃዎች ጭማሪ በኢትዮጵያ ብር ከፍለው የሚጨርሱት ነው
#ቴምርሪልስቴት #ቴምርፕሮፐርቲስ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
👇👇👇👇👇👇
+251939770177
+251996856273
https://t.me/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp. https://wa.me/251939770177
Telegram :@KalTemerRealEstate | 15 596 |
| 16 | በፍሊንትስቶንስ አ.ማ እና በ ደንበኞቹ መካከል 2 ዓመት በላይ ሲያከራክር የቆየው ጉዳይ በፌደራል ሰበር ሰሚ ችሎት መቋጫ አገኘ።
👉 በብያኔው መሰረት ፍሊንትስቶንስ አክስዮን ማህበር ለቀድሞ ደንበኞቹ ከ 282 ሚሊየን ብር በላይ የካሳ ክፍያ የሚከፍል ይሆናል።
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በቀን 08/11/18 ዓም በዋለው ችሎት፣ "ፍሊንትስቶንስ አ.ማ) ከድርጅቱ ቤት ገዝተው ግንባታ ርክክብ ባለማግኘታቸው ምክንያት ክስ የመሠረቱ 212 ደንበኞችን በተመለከተ ከዚህ ቀደም በግልግል ዳኝነት ጉባኤ የተሰጠውን ውሳኔ አጽንቷል።
ጉዳዩ የተጀመረው ፍሊንትስቶንስ ኢንጅነሪንግ አ.ማ. ከ2008 እስከ 2009 ዓም ከደንበኞቹ ጋር በገባቸው የቤት ግዥ ውሎች መሠረት፣ ቤቶቹ በተባለው ጊዜ ውስጥ ርክክብ ባለማድረጋቸው ነው። ደንበኞቹ በአዲስ አበባ ከተማ፣ በለሚ ኩራ ክፍለከተማ "ቦሌ በሻሌ" በተባለ ሳይት የጋራ መኖሪያ ቤት ህንጻ ገንብቶ እንዲያስረክባቸው በውል ስምምነት ግዢ ፈጽመዋል።
ከሳሽ ደንበኞች የቤት ግዢውን የፈጸሙት ከ 2008 ዓም እስከ 2009 ዓም ባሉት የተለያዩ ጊዜያት ቢሆንም በውሉ መሠረት የቤት ርክክቡን ደንበኞቹ ግዢ ከፈጸሙበት አመት ጀምሮ በሚታሰብ 28+2 ወራት ውስጥ ሊፈጸም ቢገባም፣ ድርጅቱ ግንባታውን በተደጋጋሚ በማጓተቱ ደንበኞቹ ለረጅም ዓመታት ርክክብ ሳያገኙ ቆይተዋል።
ጉዳዩን የተመለከተው የግልግል ዳኝነት ጉባኤ ከሁለቱም ወገኖች ማስረጃና ክርክር ከሰማ በኋላ ግንቦት 23 ቀን 2016 ዓ.ም ዝርዝር ብይን ሰጥቷል።
ጉባኤው በውሳኔው መሠረት፣ ድርጅቱ በውሉ የተገባውን የግንባታ ማጠናቀቂያ ጊዜ ገደብ (ከውል ፊርማ በኋላ ባሉት የተለያዩ የግንባታ ደረጃዎች ልክ ማለትም መሠረት ስራ 15 ወራት፣ ሁለተኛ ደረጃ ግንባታ ተጨማሪ ወራት፣ እና የመጨረሻ ርክክብ ጊዜ) ማክበር ሲገባው ባለማክበሩ፣ ደንበኞቹ ለደረሰባቸው ጉዳት ካሳ የማግኘት መብት እንዳላቸው አረጋግጧል።
በጉባኤው ፍሊትስቶንስ አክስዮን ማህበር ግንባታውን በኮንትራቱ መሰረት ገንብቶ ማስረከብ ያልቻለው በኮቪድ 19 ወረርሽኝ፣ በሰሜን በነበረው የእርስ በእርስ ጦርነት፣ የብር መግዛት አቅም መቀነስ፣ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እና ሌሎችም ተያያዥ ምክንያቶችን ያቀረበ ቢሆንም በጉባኤው ተቀባይነት አላገኘም።
በዚህም መሠረት፡-
- ለእያንዳንዱ ተከራካሪ ደንበኛ፣ በቤት ስፋት (በካሬ ሜትር) እና በውል ዋጋ ልክ የተሰላ የመዘግየት ካሳ እንዲከፈል፤ አማካይ የካሬ ሜትር ዋጋ ብር 13,700.00 ላይ ተመስርቶ፣ ለእያንዳንዱ ቤት የተለያየ ስፋት (ከ41.08 እስከ 86.23 ካሬ ሜትር የሚደርስ) ተመጣጣኝ ካሳ እንዲሰላ፤
- በአጠቃላይ ለ212ቱም ከሳሾች ሲደመር (282 ሚሊየን 780ሺ ብር በላይ) የሚቆጠር ካሳ ተከሳሽ ድርጅቱ እንዲከፍል፤ እንዲሁም ተጨማሪ ወለድና ተያያዥ ወጪዎች በህግ አግባብ እንዲተኩ ጉባኤው ወስኗል።
የተወሰኑ ከሳሾች በግልግል ጉባኤው ውሳኔ ባለመስማማት፣ ጉዳዩን በሰበር አቤቱታ ወደ ፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ወስደውታል። የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎቱ ተከራካሪ ወገኖችን፣ የግልግል ውሳኔውን መሠረት ያደረጉ ሰነዶችንና ተያያዥ የሕግ ክርክሮችን ከመረመረ በኋላ፣ የግልግል ጉባኤውን ብይን ሙሉ በሙሉ አጽንቶታል። | 14 508 |
| 17 | لا يوجد نص... | 12 378 |
| 18 | በሲአይኤ (CIA) ተቋማት ላይ የተፈጸሙት የኢራን ጥቃቶች የሩሲያ እጅ አለበት የሚሉ ጥያቄዎችን አስነሱ
በፋርስ ባሕረ ሰላጤ በሚገኙ የሲአይኤ ተቋማት ላይ የተፈጸሙት የኢራን የድሮን ጥቃቶች፣ ሩሲያ ለጥቃቱ የሚሆኑ የዒላማ መረጃዎችን ወይም የላቁ የድሮን ቴክኖሎጂዎችን በመስጠት አግዛ እንደሆነ ለማረጋገጥ የአሜሪካ የደህንነት ተንታኞች ምርመራ እንዲጀምሩ መደረጉም ተሰምቷል።
ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁት አራት የደህንነት ሰዎች እንደተናገሩት፣ የአሜሪካ የደህንነት ባለሥልጣናት በሲአይኤ ተቋማት ላይ በተፈጸሙት ጥቃቶች ላይ የሩሲያ እጅ ስላመኖሩ እስካሁን አጠቃላይ ድምዳሜ ላይ አልደረሱም። ነገር ግን የጥቃቶቹን ውጤታማነት እና ግልጽ ትክክለኛነት፣ እንዲሁም ሩሲያ ለኢራን የምታደርገውን ሰፊ ቴክኒካዊ ድጋፍ እንደ ምስክርነት ጠቅሰዋል።
ሩሲያ በባሕረ ሰላጤው ቀጠና በሚገኙ የአሜሪካ ዒላማዎች ላይ ኢራን ለምናካሂዳቸው ጥቃቶች የዒላማ መረጃዎችን እና ሌሎችንም ድጋፎች ማድረጓን ሮይተርስ እና ሌሎች መገናኛ ብዙኃን የዘገቡት ሲሆን የአሜሪካ ባለሥልጣናትም ያመኑበት ጉዳይ ነው። ነገር ግን የደህንነት ተቋማቱ በሲአይኤ ተቋማት ጥቃት ላይ የሩሲያን እጅ አስመልክቶ እያካሄዱት ያለው ምርመራ ቀደም ሲል ይፋ አልተደረገም ነበር።
በመጋቢት ወር ቢያንስ ሁለት የሲአይኤ ተቋማት ጥቃት እንደተፈጸመባቸው ሮይተርስ እና ሌሎች መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል። ከእነዚህ ተቋማት አንደኛው በሪያድ በሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ውስጥ የሚገኘው በሳውዲ ዓረቢያ የሲአይኤ ጣቢያ ሲሆን፣ ሌላኛው ደግሞ በምሥራቅ ኢራቅ የሚገኝ ተቋም ነው። ምንጮች ተጨማሪ የሲአይኤ ተቋማት መመታታቸውን ቢገልጹም ዝርዝር መረጃዎችን ግን ይፋ አላደረጉም። | 14 917 |
| 19 | በሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ላይ የሚቀርቡ አጀንዳዎች ውሳኔ ላይ የሚደረስባቸው፤ በየደረጃው ያሉ ተሳታፊዎች ከ70 እስከ 75 በመቶ ድጋፍ ሲያገኝ እንደሆነ በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የተዘጋጀ ሰነድ አመለከተ።
ሁሉንም የውሳኔ ሂደቶች አልፈው ለጠቅላላ ጉባኤ ከቀረቡ በኋላ “ጠንካራ ተቃውሞ” የሚያጋጥማቸው አጀንዳዎች፤ ወደ ህዝበ ውሳኔ ”ሊመሩ” እንደሚችሉበሰነዱ ላይ ተጠቁሟል።
በ30 ገጾች የተዘጋጀው ይህ ሰነድ ባለፈው ሳምንት በይፋ የተከፈተውን የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ “የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓትን” በዝርዝር የያዘ ነው።
በአጀንዳዎች ላይ የመጀመሪያዎቹ ውሳኔዎች የሚተላለፉት፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤው ባሉት “ባለ ሁለት ደረጃ መዋቅር” እንደሆነ በሰነዱ ላይ ሰፍሯል። የመጀመሪያው ደረጃ “የርዕሰ ጉዳይ ተመካካሪ ቡድን” የሚል መጠሪያ ያለው ሲሆን ሁለተኛው ደረጃ ደግሞ 211 አባል “የክልል ተወካዮች ጉባኤ” የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል።
“የርዕሰ ጉዳይ ተመካካሪ ቡድን” አንድ ርዕሰ ጉዳይ ላይ ተመካክሮ ምክረ ውሳኔ ወይም ምክረ ሃሳብ እንዲያመነጭ ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽኑ የሚያቋቁመው ቡድን ነው። በዚህ ቡድን የታቀፉ አባላት በአንድ አጀንዳ ላይ ከተመካከሩ በኋላ “75 በመቶ ከመግባባት ላይ ለመድረስ እንደሚሞክሩ” የውሳኔ አሰጣጥ ስርዓት ሰነዱ ያስረዳል።
በተነሳው አጀንዳ ላይ መግባባት ላይ ካልተደረሰ ግን የምሁራን ፓነል እና ሽማግሌዎችን በውስጡ ያካተተ “የስምምነት ግብረ-ኃይል” “ጣልቃ እንደሚገባ” በኮሚሽኑ ሰነድ ላይ ተቀምጧል። ይኸው ሰነድ የስምምነት ግብረ-ኃይሉ ጣልቃ ከገባም በኋላ መግባባት ላይ ካልተደረሰ፤ “ልዩ አብላጫ ድምጽ” የተሰኘው አሰራር ተግባራዊ እንደሚደረግም ጨምሮ ገልጿል። | 14 181 |
| 20 | ጄኤፍኤም 106.7 ሬድዮ ሞገድ ለስድስት ወራት ታገደ!
የመገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን በጄኤፍኤም 106.7 ሬድዮ ጣቢያ ላይ የስድስት ወራት የስርጭት እግድ ጣለ
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን የጄኤፍኤም (JFM 106.7) ሬድዮ ጣቢያ የብሮድካስት ስርጭት ከሐምሌ 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚቀጥሉት ስድስት ወራት ሙሉ ለሙሉ እንዲታገድ መወሰኑን አስታወቀ። ባለሥልጣኑ ውሳኔውን ያስ አስተላለፈው ጣቢያው በተደጋጋሚ የተሰጡትን የቃልና የጽሁፍ ማስጠንቀቂያዎች ሳይቀበል በመቅረቱ እና በአዋጅ ቁጥር 1238/2013 የተጣሉበትን የፈቃድ ውል ግዴታዎች ባለመወጣቱ እንደሆነ ገልጿል።
ባለሥልጣኑ ባደረገው የይዘት ክትትልና የአካል ኢንስፔክሽን ምልከታ ጣቢያው በህግ የተጣለበትን የሀገራዊ ይዘት ሽፋን አለማካተቱን፣ ህዝብን የሚያስተምሩና የሚያዝናኑ ፕሮግራሞችን ከማቅረብ መቆጠቡን እንዲሁም ለሀገራዊ እሴቶችና ለፖለቲካዊ-ኢኮኖሚያዊ እድገት አስተዋጽኦ የማድረግ ግዴታውን አለመወጣቱን አረጋግጧል። በውሳኔው መሰረት የኢትዮጵያ ኮሚዩኒኬሽን ባለሥልጣንም ጣቢያው የተመደበለትን 106.7 የሬድዮ ሞገድ በእግዱ ወቅት እንዳይጠቀም ማሳሰቢያ የሰጠ ሲሆን፣ ጣቢያው ለሕግ ተገዢ በመሆን ስርጭቱን በአስቸኳይ እንዲያቆም ታዟል። | 16 145 |
