TIKVAH-MAGAZINE
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያና የመረጃ መለዋወጫ መድረክ ነው። በ +251913134524 ላይ ያግኙን። ለማስታወቂያ @tikvahmagbot ላይ መረጃ ይጠይቁ።
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام TIKVAH-MAGAZINE
کانال TIKVAH-MAGAZINE (@tikvahethmagazine) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 192 450 مشترک است و جایگاه 880 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 97 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 192 450 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 29 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 89 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 54 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 14.74% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 8.73% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 28 368 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 16 795 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 76 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያና የመረጃ መለዋወጫ መድረክ ነው።
በ +251913134524 ላይ ያግኙን።
ለማስታወቂያ @tikvahmagbot ላይ መረጃ ይጠይቁ።”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 30 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 30 ژوئن | +17 | |||
| 29 ژوئن | +59 | |||
| 28 ژوئن | +4 | |||
| 27 ژوئن | 0 | |||
| 26 ژوئن | +37 | |||
| 25 ژوئن | +10 | |||
| 24 ژوئن | +26 | |||
| 23 ژوئن | +30 | |||
| 22 ژوئن | +23 | |||
| 21 ژوئن | +14 | |||
| 20 ژوئن | +27 | |||
| 19 ژوئن | +8 | |||
| 18 ژوئن | +22 | |||
| 17 ژوئن | +17 | |||
| 16 ژوئن | +10 | |||
| 15 ژوئن | +23 | |||
| 14 ژوئن | +16 | |||
| 13 ژوئن | +30 | |||
| 12 ژوئن | +28 | |||
| 11 ژوئن | +9 | |||
| 10 ژوئن | +8 | |||
| 09 ژوئن | +5 | |||
| 08 ژوئن | +43 | |||
| 07 ژوئن | +7 | |||
| 06 ژوئن | +27 | |||
| 05 ژوئن | +21 | |||
| 04 ژوئن | +22 | |||
| 03 ژوئن | 0 | |||
| 02 ژوئن | +5 | |||
| 01 ژوئن | +6 |
| 2 | #WhatsApp 🟩
ዋትስአፕ ከ3 ቢሊዮን በላይ ለሚሆኑ ተጠቃሚዎቹ የስልክ ቁጥራቸውን ሳያጋሩ ልክ እንደ ቴሌግራም የግል መለያ ስም የማስያዝ እና የመቀየር አገልግሎት በይፋ መፍቀዱን አስታውቋል።
አዲሱ የዋትስአፕ ማሻሻያ በተለይም የስልክ ቁጥርን ለሌላ ሰው አሳልፎ ለመስጠት ለሚቸገሩ እና ለግል ዲጂታል ደኅንነታቸው ከፍተኛ ትኩረት ለሚሰጡ ዜጎች ትልቅ መፍትሔ ሆኖ ቀርቧል።
ዋትስአፕ አገልግሎቱን ደረጃ በደረጃ ለሁሉም ተጠቃሚዎች ተደራሽ ለማድረግ እየሠራ መሆኑን የጠቀሰ ሲሆን ለዋትስአፕ ቢዝነስ እና ለተወሰኑ የቤታ ተጠቃሚዎች ቀርቧል።
@TikvahethMagazine | 13 097 |
| 3 | #DRC 🇨🇩
የኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ መንግሥት በአገሪቱ እንደገና እያቀረረ የመጣውን የኢቦላ ወረርሽኝ ስርጭት ለመግታት እና ለመቆጣጠር ሲል በዋና ከተማዋ ኪንሻሳ ጨምሮ በሦስት ከፍተኛ ተጋላጭ በሆኑ ግዛቶች ህዝባዊ ስብሰባዎች ላይ እገዳ ተላልፏል።
ይህ አስቸኳይ እገዳ የተጣለው በነዚህ አካባቢዎች አዲስ የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ መሆኑ ነው የተገለጸው።
ነዋሪዎችም አስፈላጊውን የንጽህና መጠበቂያ መመሪያዎችን እንዲተገብሩና ምልክቱ የሚታይባቸውን ሰዎች በአቅራቢያ ለሚገኙ የጤና ተቋማት በፍጥነት እንዲያሳውቁ ጥሪ ቀርቧል።
ኮንጎ በኢቦላ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 1 ሺ 307 መድረሱን እና ከእነዚህ ውስጥ 377 ያህሉ መሞታቸውን አስታውቃለች።
@TikvahethMagazine | 11 687 |
| 4 | “በሳቅዎ ይክፈሉ” ምንድን ነው ?
ሐረር ቢራ «ሳቅፔ» (SAQPay) የተሰኘ መተግበሪያ ይፋ አድርጓል። መተግበሪያው እውነተኛ ሳቅን በመለየት ነጥብ የሚሰጥ ሲሆን በተጠራቀሙ ነጥቦች ሐረር ቢራን በተመረጡ ቦታዎች በቅናሽ መጠቀም የሚያስችል ነው።
"ለእኛ ለሐረሮች፣ ከገንዘብ ልውውጥ ይልቅ እጅግ ትርጉም ያለው ነገር አብረን የምንጋራው ደስታ እና በእውነተኛ ሳቅ ውስጥ የሚፈጠረው አብሮነት እንደሆነ እናምናለን። «በሳቅዎ ይክፈሉ» ይሄንኑ እውነት በተግባር የምናሳይበት መንገዳችን ነው። ምክንያቱም መዝናናት ለሁሉም ክፍት ሲሆን፣ ሰዎች በአንድ ላይ ከመሰባሰብ አልፈው የእርስ በርስ ትስስራቸው ይበልጥ ይጠነክራልና!" ሲሉ የሃይኒከን ኢትዮጵያ የማርኬቲንግ ዳይሬክተር ካሳሁን ፈለቀ ገልጸዋል።
ሁሉም «በሳቅዎ ይክፈሉ» ላይ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች በተመረጡ ቦታዎች ብቻ የሚካሄዱ ናቸው የተባለ ሲሆን ህጋዊ የእድሜ ገደብን እና ኃላፊነት የተሞላበት መጠጥ አጠቃቀም መመሪያዎችን ሙሉ በሙሉ ያከበሩ ስለመሆናቸውም በመግለጫው ጠቅሷል።
@TikvahethMagazine | 10 713 |
| 5 | ስልኮትን ለመቀየር አስበዋል?
አዳዲስ እንዲሁም በመጠኑ ያገለገሉ ስልኮችን ከተሟላ ዋስትና እና ጥገና ጋር ይዘን ቀርበናል📱ለበለጠ መረጃ ቻናላችንን ይጎበኙ
https://t.me/phonehub27
📞 0996544119
📩 inbox @kidaa3535
📍አድራሻ- ቦሌ ከሸገር ህንፃ አጠገብ
📨 ክፍለ ሀገር ላላቸሁ ደንበኞችቻችንም በ DHL መላክ ጀምረናል | 9 637 |
| 6 | ተ/ሀይማኖት ላይ ለጥቂት ሱቆች ብቻ 15% ቅናሽ
☎️ 09 47 77 11 62
💥💥የከተማችን ታላቁ የንግድ ማዕከል መርካቶ በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኝ
💥💥G+ 4 Mall - 6784 ካሬ ላይ የሚያርፍ
11ካሬ, 16ካሬ ,22ካሬና 32 ካሬ አማራጭ
ከ 3,300,000 ብር ጠቅላላ ክፍያ
ከ 1,155,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ
💥በ 4ቱም አቅጥቅጫ የመንገድ አማራጮች ያሉት
💥 በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ የሚረከቡት
💥 በ Net area የሚሸጥ
ለበለጠ መረጃ - ☎️09-47-77-11-62
Telegram @Novi_03 | 10 517 |
| 7 | የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ሳምንታዊ ግበይት 31.3 ሚሊዮን ብር ሆኖ ተመዝግቧል።
የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ (ESX) ሳምንታዊ ግብይቱን ባጠናቀቀበት የመዝጊያ ደውል ላይ የ31.3 ሚሊዮን ብር አጠቃላይ የሰነዶች ዝውውር አስመዝግቧል።
ይህ የግብይት መጠን ባለፈው ሳምንት ከተመዘገበውና ጊዜያዊ የገበያ መነቃቃት ከነበረው የ1 ቢሊዮን ብር ታሪካዊ ዝውውር አንጻር ዝቅ ያለ ቢሆንም ገበያው በተረጋጋ መዋቅር ላይ መቀጠሉን ያሳያል።
📊 የተፈጸሙ ግብይቶች ብዛት - በአጠቃላይ 149 ግብይቶች (Transaction) ተከናውነዋል።
📶 ባለቤት የቀየሩ አክሲዮኖች ብዛት - 14,590 ገደማ አክሲዮኖች ከአንድ ባለሀብት ወደ ሌላ ተላልፈዋል።
በገበያው ላይ ከተንቀሳቀሰው አጠቃላይ የገንዘብ መጠን ውስጥ የአዋሽ ባንክ እና ገበያውን አዲስ የተቀላቀለው የአባይ ባንክ አክሲዮኖች ብቻቸውን የ95 በመቶ ድርሻን ተቆጣጥረዋል።
#AWAB (አዋሽ ባንክ)
📶 6,700 አክሲዮኖች የተገበያዩ ሲሆን፣ ይህም በሳምንቱ ባለቤት ከቀየሩት አጠቃላይ አክሲዮኖች የ46 በመቶ ድርሻ አለው።
📊 20.3 ሚሊዮን ብር ግብይት የተፈጸመበት ሲሆን፣ ይህም ከጠቅላላው የገበያ የገንዘብ ዝውውር (Value) 64.9% ድርሻ አለው።
📊 በሳምንቱ በተከናወኑ የግብይቶች ብዛት (Transactions) ረገድ የ60% ድርሻ ነበረው።
📈 በገዢዎች (2,900 ብር) እና በሻጮች (3,000 ብር) መካከል የ100 ብር ልዩነት እየታየበት ሳምንታዊ አማካይ ዋጋው በ2,998 ብር አካባቢ ረግቶ ውሏል።
#ABAY (አባይ ባንክ)
📶 ግብይት በጀመረባቸው በመጀመሪያዎቹ ሁለት ቀናት ብቻ 5,186 አክሲዮኖች ተገበያይተዋል።
📊 የ9.6 ሚሊዮን ብር ግብይት በማከናወን ከጠቅላላው የገበያ የገንዘብ ዝውውር 30.9% ድርሻ በመያዝ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
📊 በሳምንቱ በተከናወኑ የግብይቶች ብዛት ረገድ የ14% ድርሻ ነበረው።
▶️ አዲሱ አባይ ባንክ በ2,000 ብር መዝጊያ ዋጋ ገበያውን ተቀላቅሏል።
#ETEL (ኢትዮ ቴሌኮም)
📶 2,287 አክሲዮኖች ተገበያይተዋል።
📊 የ879,000 ብር ግብይት የተከናወነበት ሲሆን፣ ይህም የ2.88% የገበያ ድርሻ አለው።
📊 በሳምንቱ በተከናወኑ የግብይቶች ብዛት ረገድ የ20% ድርሻ ነበረው።
📈 የ400 ብር ጣሪያውን ሰብሮ በመውጣት በሳምንቱ መጨረሻ እስከ 450 ብር ከፍተኛ ዋጋ የተሸጡ አክሲዮኖች ነበሩ።
#WGB (ወጋገን ባንክ)
📶 343 አክሲዮኖች ተገበያይተዋል።
📊 የ453,000 ብር ግብይት የተከናወነ ሲሆን፣ በግብይት ብዛት ረገድ የ7% ድርሻ ነበረው።
📈 በሳምንቱ መጀመሪያ ከነበረበት 1,290 ብር ተነሥቶ በሳምንቱ ማብቂያ 1,396 ብር ላይ ደርሷል።
በገበያው ላይ ከተመዘገቡት ኩባንያዎች መካከል የገዳ ባንክ (GDAB) አክሲዮኖች በዚህ ሳምንት ምንም ዓይነት ግብይት ሳይከናወንባቸው ተጠናቀዋል።
Credit : ESX, Nigat-Post
@TikvahethMagazine | 21 759 |
| 8 | #Update 🇻🇪
በቬንዙዌላ በተከሰቱት ሁለት ተከታታይና ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጦች የሟቾች ቁጥር ከ920 በላይ ማለፉን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታወቁ።
በአሁኑ ወቅት ቢያንስ 172 ሰዎች በፍርስራሽ ውስጥ ተቀብረው እንደሚገኙ ሲጠቆም፣ የቆሰሉ ዜጎች ቁጥር 3,360 ደርሷል።
ከ50,000 በላይ የሚሆኑ ዜጎች ያሉበት ሳይታወቅ የጠፉ መሆናቸው የተመዘገበ በመሆኑ የሟቾች ቁጥር አሁንም በከፍተኛ ደረጃ ሊጨምር እንደሚችል ተሰግቷል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) ባወጣው የመጀመሪያ ደረጃ ግምት፣ በሬክተር ስኬል 7.2 እና 7.5 በሆነው በዚህ የመሬት መንቀጥቀጥ የደረሰው ቀጥተኛ የኢኮኖሚ ውድመት 6.7 ቢሊዮን ዶላር ይደርሳል።
የተመድ የስደተኞች ኤጀንሲ (IOM) በበኩሉ በዋና ከተማዋ ካራካስ የሚኖሩ 2 ሚሊዮን ሰዎችን ጨምሮ በአጠቃላይ እስከ 6.76 ሚሊዮን የሚደርሱ ዜጎች በአደጋው በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መጎዳታቸውን ገልጿል።
የሀገሪቱ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ዴልሲ ሮድሪጌዝ ለተጎዱ ሆስፒታሎችና መኖሪያ ቤቶች መልሶ ማቋቋሚያ የሚሆን የ200 ሚሊዮን ዶላር ፈንድ መቋቋሙን አስታውቀዋል።
የአሜሪካ መንግሥትን ጨምሮ ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተውጣጡ ከ1,600 በላይ የዓለም አቀፍ የነፍስ አድን ቡድን አባላት በ17 ልዩ በረራዎች ካራካስ የገቡ ሲሆን የነፍስ አድን ሥራው ላይ እየተረባረቡ ይገኛሉ።
ቪዲዮ 🤩 : የሳተላይት ምስል
Source : Reuters
@TikvahethMagazine | 20 618 |
| 9 | በመዲናዋ 100 ኪዮስኮችን ለመገንባት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ፋውንዴሽንና የተባበሩት መንግሥታት የሰፈራ ፕሮግራም (UN-Habitat) በ300,000 ዶላር 100 ኪዮስኮችን ለመገንባት የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ አደረጉ።
ለዚህ ፕሮጀክትም ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ እና ከመስሪያ ቦታዎች ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ጋር የአራትዮሽ ስምምነት ተደርጓል።
የሚገነቡት ኪዮስኮች በከተማዋ በሚገኙ 11ዱም ክፍለ ከተሞች በተመረጡ ወረዳዎች ውስጥ ለሚገኙ 200 ከስደት ተመላሽ ለሆኑ ዜጎችና የከተማዋ ነዋሪዎች የሥራ ዕድል ለማመቻቸት ታቅዷል።
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ፋውንዴሽን ለዚህ ፕሮጀክት 200 ሺ ዶላር ፈሰስ ሲያደርግ የተመድ የሰፈራ ፕሮግራም 100 ሺውን ሸፍኗል።
@TikvahethMagazine | 17 740 |
| 10 | ቀጣዩ የሪል እስቴት ሽያጮ እኛ ጋር ነው - ጃካ CRM ን እናስተዋውቅዎ።
ጃካ ምን ይሰጥዎታል?
👥 Leads— ዝግጁ ደንበኞች
ከ2 ዓመት በላይ ባደረግነው ጥናት ከ17,000 በላይ የተረጋገጡ ሊዶች::
📊 CRM — ሽያጭዎን በስርዓት ያስተዳድሩ
ሁሉንም ደንበኞችዎን፣ ቀጠሮዎችዎን፣ እና የሽያጭ ሂደትዎን በአንድ ቦታ ይከታተሉ።
ዋጋ — ከ1500 ብር ጀምሮ
🚀 ለመጀመሪያዎቹ 20 ተጠቃሚዎች ልዩ የ33% ቅናሽ እየሰጠን ነው። https://t.me/jakkacrm | 16 124 |
| 11 | ተ/ሀይማኖት ላይ ለጥቂት ሱቆች ብቻ 15% ቅናሽ
☎️ 09 47 77 11 62
💥💥የከተማችን ታላቁ የንግድ ማዕከል መርካቶ በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኝ
💥💥G+ 4 Mall - 6784 ካሬ ላይ የሚያርፍ
11ካሬ, 16ካሬ ,22ካሬና 32 ካሬ አማራጭ
ከ 3,300,000 ብር ጠቅላላ ክፍያ
ከ 1,155,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ
💥በ 4ቱም አቅጥቅጫ የመንገድ አማራጮች ያሉት
💥 በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ የሚረከቡት
💥 በ Net area የሚሸጥ
ለበለጠ መረጃ - ☎️09-47-77-11-62
Telegram @Novi_03 | 17 528 |
| 12 | #Update 🇻🇪: በቬንዙዌላ የሟቾች ቁጥር 589 ደረሰ።
በቬንዙዌላ በተከሰተው አስከፊ የመሬት መንቀጥቀጥ የሟቾች ቁጥር 589 መድረሱን የሀገሪቱ ፕሰዚዳንት ዴልሲ ሮድሪጌዝ አስታውቀዋል።
ከአደጋው ጋር ተያይዞ የቆሰሉ ዜጎች ቁጥርም 2,980 መድረሱ ነው የተገለጸው።
የነፍስ አድን ቡድኖች አደጋው ከተከሰተ በኋላ ባሉት ወሳኝ የ72 ሰዓታት "ወርቃማ የምሕረት ሰዓታት" ውስጥ በፍርስራሾች ሥር የተቀበሩ ሰዎችን በሕይወት ለማውጣት ከፍተኛ ርብርብ እያደረጉ ነው።
የፍለጋ ቡድኖቹ ተጨማሪ ተጎጂዎችን እያገኙ በመሆናቸው የሟቾች ቁጥር አሁንም በከፍተኛ ሁኔታ ሊጨምር እንደሚችል ተገልጿል።
ቪዲዮ 🤩 : በነፍስ አድን ሥራው ወቅት አንዲት እናት በፍርስራሾች መካከል ልጇን ስትገላገል።
@TikvahethMagazine | 24 863 |
| 13 | የሶማሊያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ከኬንያ ተባረሩ
የሶማሊያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር በናይሮቢ ጀሞ ኬንያታ አየር ማረፊያ በደረሱበት ወቅት በኢሚግሬሽን መቆጣጠሪያ ላይ በተፈጠረ የቪዛ/ፕሮቶኮል አለመግባባት ምክንያት ኬንያን ለቀው እንዲወጡ መደረጋቸው ተነግሯል።
ባለስልጣኑ የዲፕሎማቲክ ፓስፖርት ይዘው የነበረ ቢሆንም፣ የኬንያ የኢሚግሬሽን ህግ በሚጠይቀው መሰረት ቅድመ ዝግጅት ወይም የዲፕሎማቲክ ፕሮቶኮል አለመሟላቱ ለክርክሩ መነሻ ሆኗል ነው የተባለው።
ዘገባው የሂራን ኦላይን ነው።
@TikvahethMagazine | 25 858 |
| 14 | በሮቻችን ተከፍተዋል
የንግድዎን ዕድገት የሚያፋጥኑበት፣ በዓይነቱ ለየት ያለው 8ኛው አግሮፉድ ፕላስትፕሪንትፓክ፣ 2ኛው ኢትዮፒካ ኮፊ ሾው እና ኢትዮጵያ ፉድ ሾው ዛሬ በይፋ በሮቹን ከፍቶ የዘርፉን ባለሙያዎችና ጎብኚዎች በመቀበል ላይ ይገኛል!
ከሰኔ 18 እስከ 20 ለ3 ተከታታይ ቀናት የሚቆየው ይህ ታላቅ አውደ ርዕይ፤ ከብራዚል፣ ቻይና፣ ጣሊያን፣ ጀርመን፣ ፈረንሳይ እና ከሌሎች ከ18 በላይ ሀገራት የተወጣጡ የዘርፉ ግዙፍ ኩባንያዎችና የኢንዱስትሪ መሪዎችን በአንድ ጣራ ስር ሰብስቧል።
በፕላስቲክ፣ ፓኬጂንግ (ማሸጊያ)፣ ፕሪንቲንግ (ሕትመት)፣ በምግብና መጠጥ ማቀነባበሪያ፣ በሬስቶራንት፣ ካፌ፣ በቡና ማቀነባበሪያና ላኪነት ላይ የተሰማራችሁ ኩባንያዎችና ሥራ ፈጣሪዎች በሙሉ፤ አዳዲስ የንግድ ትስስሮችን ለመፍጠርና የዓለምን ቴክኖሎጂ ለመገብየት አሁኑኑ ወደ አውደ ርዕዩ ኑ!
👥 ከ150 በላይ ታዋቂ የሀገር ውስጥና የውጭ ኤግዚቢተሮች
📍 ቦታ፦ በአዲሰ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር (AICC)
🎟️ መግቢያው፦ ሙሉ በሙሉ በነፃ ነው!
አሁኑኑ ቀድመው ይመዝገቡና በቀጥታ ይግቡ፡ https://pranaevents.net/apcfvisitor
የወደፊት የንግድ አጋርዎን ዛሬ ያግኙ! | 20 413 |
| 15 | 🔥 ለ5ቤቶች ብቻ የ30% ቅናሽ!
📍 ሳርቤት አደባባይ
💰በ20% ቅድመ ክፍያ በ3አመት ከፍለው የሚያጠናቅቁት
🛌 76ካሬ
በ 9.1ሚ ብር ጠቅላላ ክፍያ
ቅድመ ክፍያ 20% =1.8ሚ ብር
🛌 100 ካሬ
12ሚ ጠቅላላ ክፍያ
ቅድመ ክፍያ 20% =2.4ሚ ብር
🛌 136 ካሬ
16.3ሚ ብር ጠቅላላ ክፍያ
ቅድመ ክፍያ 20% = 3.3ሚ ብር
💵 ሙሉ ክፍያ ለምትከፍሉ ከ30-35% ልዩ ቅናሽ
📍 በአዋሬ, ቡልጋርያና, አያትና, ፒያሳ ላይ ተጨማሪ ቤቶች አሉን
🏬 የንግድ ሱቅ በፒያሳ, ቡልጋርያና ገላን ኮንዶሚኒየም ከ500ሺ ብር ቅድመ ክፍያና ከ2.4ሚ ብር ሙሉክፍያ ጀምሮ
📞0989888382
📞0941376615
Telegram @hanigirma19 | 20 306 |
| 16 | ቪዲዮ 🤩 : ትረፊ ያላት ነፍስ !
#Updtae 🇻🇪
- በቬንዙዌላ በተከሰተው ድርብ የመሬት መንቀጥቀጥ የሞቱት ሰዎች ቁጥር 188 ደርሷል።
- 1,520 ሰዎች የአካል ጉዳት ደርሶባቸው በሕክምና ማዕከላት ውስጥ እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል።
- 157 ሰዎች የት እንዳሉ አልታወቀም።
- ከ200 በላይ ሰዎች ደግሞ በፈረሱ ሕንጻዎች ፍርስራሽ ውስጥ ተከበው እንደሚገኙና እነሱን በሕይወት ለማውጣት የነፍስ አድን ሠራተኞች ርብርብ ላይ ናቸው ተብሏል።
@TikvahethMagazine | 25 593 |
| 17 | ⚫ በያዝነው ዓመት የወርቅ ወጪ ንግድ ከ5.5 ቢሊዮን ዶላር በላይ አልፏል።
⚫ የታንታለም ማዕድንን እሴት ጨምሮ ለገበያ ለማቅረብ መንግስት ከአሜሪካ ኩባንያ ጋር ድርድር ላይ ይገኛል።
የኢትዮጵያ የወርቅ ወጪ ንግድ በያዝነው ዓመት 5.5 ቢሊዮን ዶላር በላይ ማለፉ ሲገለጽ ይህም ከ2010 ዓ.ም ጋር ሲነጻጸር የ5,000 በመቶ ዕድገት ነው ማስመዝገቡን የማዕድን ሚኒስቴር አስታውቋል።
የማዕድን ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሃና ብርሃኑ “ኢትዮጵያ ታከናውናለች” በተሰኘው ብሔራዊ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ገለጻ ባለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ውስጥ የማዕድን ዘርፉ ለአጠቃላይ የሀገር ውስጥ ምርት (GDP) ያበረከተው አስተዋጽኦ ከ0.8 በመቶ በታች መሆኑን አስታውሰዋል።
አክለውም መንግሥት እ.ኤ.አ. በ2030 የማዕድን ወጪ ንግድ ገቢን ከ10 ቢሊዮን ዶላር በላይ ለማድረስ እና ኢትዮጵያን ከአፍሪካ አምስት ቀዳሚ የማዕድን አምራች ሀገራት ተርታ ለማሰለፍ እቅድ ማስቀመጡን ገልጸዋል።
ኢንጂነር ሃና ብርሃኑ በመድረኩ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች ምንድን ናቸው ?
- በየዓመቱ ለከሰል (coal) ምርት ታወጣ የነበረውን 300 ሚሊዮን ዶላር በሀገር ውስጥ ምርት መተካት ተችሏል።
- የሲሚንቶ ምርት ባለፉት ስምንት ዓመታት ውስጥ ከነበረበት 8 ሚሊዮን ቶን አሁን ላይ በዓመት ወደ 14 ሚሊዮን ቶን አድጓል።
- በአዲስ አበባ-ጂቡቲ ኮሪደር ላይ ያሉ ሦስት ጋዝ መሙያ ማደያዎች ተገንብተዋል።
- ከ1,500 በላይ የከተማ አውቶቡሶችን ከናፍጣ ወደ ጋዝ የመቀየር ሥራ እየተሰራ ነው።
- የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (EIH) በዓለም ላይ ካሉ ያልተነኩ ግዙፍ የፖታሽ ክምችት ባለበት አፋር ክልል ላይ የማልማት ፈቃድ አግኝቷል።
- ባለፉት 30 ዓመታት ምንም እሴት ሳይጨመርበት እንዲሁ ይላክ በነበረው ታንታለም የተሰኘውን ማዕድን በሀገር ውስጥ እሴት ጨምሮ ለገበያ ለማቅረብ መንግስት ከአሜሪካ ኩባንያ ጋር ድርድር ላይ ይገኛል።
- በየዓመቱ ለብረት ምርት የሚወጣውን 1 ቢሊዮን ዶላር ለማስቀረት ያለመ ፋብሪካ እየተገነባ ነው።
- የ40 ሚሊዮን ያህል አርሶ አደሮች ፍላጎት ለማሟላት በየዓመቱ ለማዳበሪያ ግዢ ከ2 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ይደረጋል። መንግሥት የ40 በመቶ ድርሻ ያለው የማዳበሪያ ፋብሪካ በሚቀጥሉት 29 እስከ 30 ወራት ውስጥ ተጠናቆ ወደ ሥራ ሲገባ ሙሉ ለሙሉ የሀገር ውስጥ ፍላጎትን ይሸፍናል።
@TikvahethMagazine | 26 494 |
| 18 | ኢትዮጵያን ጨምሮ በ'ኤል ኒኞ' ስጋት ውስጥ ያሉ 22 ሀገራትን ለመታደግ የ202 ሚሊዮን ዶላር አስቸኳይ ጥሪ ቀረበ
የዓለም የምግብ እና እርሻ ድርጅት እና የዓለም የምግብ ፕሮግራም ኢትዮጵያን ጨምሮ በ22 ሀገራት የሚገኙ ወደ 9 ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎችን ከ'ኤል ኒኖ'' የአየር ንብረት ቀውስ አስቀድሞ ለመታደግ የጋራ 202 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር በአስቸኳይ እንደሚያስፈልግ ድርጅቶቹ አስታውቀዋል።
የሚገኘው የገንዘብ ድጋፍ እንደ የአካባቢው ተጨባጭ ሁኔታ ታይቶ አስቀድሞ መከላከያ እርምጃዎችን ለመተግበር የሚውል ይሆናል ተብሏል።
ሁለቱ ተቋማት በኤል ኒኖ ሳቢያ ጉዳት ሊደርስባቸው ለሚችሉ 1.2 ሚሊዮን ሰዎች የቅድመ-መከላከያ ድጋፍ ለመስጠት አስቀድመው የተዘጋጁ ቢሆንም፤ ተጨማሪ የ167 ሚሊዮን ዶላር ፈንድ ከተገኘ ግን ትኩረት በተሰጣቸው 22 ሀገራት ውስጥ የሚገኙ ሌላ 7.6 ሚሊዮን ሰዎችን ማካተት እንደሚቻል ጠቁመዋል።
የፋኦ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ቤት ቤችዶል፥ "ቀውሶች ከመባባሳቸው በፊት አስቀድሞ እርምጃ መውሰድ፣ አደጋው ከተከሰተ በኋላ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ይበልጥ ውጤታማና ወጪን የሚቀንስ መሆኑን ልምዳችን በተከታታይ አሳይቶናል።
"የኤል ኒኖ ስጋቶችን ለመለየት የሚያስችሉ መረጃዎች፣ መሣሪያዎች እና ማስረጃዎች በአሁኑ ወቅት በእጃችን ላይ አሉ። አሁን ያለው ትልቁ ተግዳሮት እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል የፋይናንስ አቅርቦት ማጣት ነው” ሲሉ ነው የገለጹት።
በኤል ኒኞ ሳቢያ ከፍተኛ የድርቅ ወይም የጎርፍ አደጋ ይደርስባቸዋል ተብለው ከተለዩት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳን፣ ኡጋንዳ፣ ካሜሩን፣ ማዳጋስካር፣ ማላዊ፣ ሞዛምቢክ፣ ናይጄሪያ እና ዚምባብዌ በቀዳሚነት ተጠቅሰዋል።
በሌሎች አህጉራት ደግሞ አፍጋኒስታን፣ ፓኪስታን፣ ፊሊፒንስ፣ ኮሎምቢያ፣ ኤል ሳልቫዶር፣ ጓቲማላ፣ ሄይቲ፣ ሆንዱራስ እና ቬንዙዌላ በስጋት መዝገቡ ውስጥ ይገኛሉ።
መረጃው ከFAO፣ WFP እና UN News የተጠናቀረ ነው።
@TikvahethMagazine | 23 581 |
| 19 | 🔥 ለ5ቤቶች ብቻ የ30% ቅናሽ!
📍 ሳርቤት አደባባይ
💰በ20% ቅድመ ክፍያ በ3አመት ከፍለው የሚያጠናቅቁት
🛌 76ካሬ
በ 9.1ሚ ብር ጠቅላላ ክፍያ
ቅድመ ክፍያ 20% =1.8ሚ ብር
🛌 100 ካሬ
12ሚ ጠቅላላ ክፍያ
ቅድመ ክፍያ 20% =2.4ሚ ብር
🛌 136 ካሬ
16.3ሚ ብር ጠቅላላ ክፍያ
ቅድመ ክፍያ 20% = 3.3ሚ ብር
💵 ሙሉ ክፍያ ለምትከፍሉ ከ30-35% ልዩ ቅናሽ
📍 በአዋሬ, ቡልጋርያና, አያትና, ፒያሳ ላይ ተጨማሪ ቤቶች አሉን
🏬 የንግድ ሱቅ በፒያሳ, ቡልጋርያና ገላን ኮንዶሚኒየም ከ500ሺ ብር ቅድመ ክፍያና ከ2.4ሚ ብር ሙሉክፍያ ጀምሮ
📞0989888382
📞0941376615
Telegram @hanigirma19 | 21 639 |
| 20 | "ያለ ዲሲፕሊን የሚደረግ የመሠረተ ልማት ግንባታ ስብራትን ይፈጥራል" - ብሩክ ታዬ (ዶ/ር)
⚫ የስኳር፣ የባቡር እና የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች በቢሊዮን የሚቆጠር ያልተከፈለ ዕዳ አለባቸው።
⚫ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ አሁን ላይ 8.2 ትሪሊዮን ብር የሚጠጋ ጠቅላላ ሀብት ያስተዳድራል።
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ (EIH) ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) “ኢትዮጵያ ታከናውናለች” በተሰኘው ብሔራዊ ጉባኤ ላይ ኢትዮጵያ ባለፉት 2 አስርት ዓመታት ውስጥ ያካሄደችው የስኳር እና የባቡር መስመር ዝርጋታ ፕሮጀክቶች መንግሥትን በቢሊዮን የሚቆጠር የዕዳ ጫና ውስጥ መክተታቸውን ገልጸዋል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው የኩራዝ ስኳር ፕሮጀክት ብቻውን 65 ቢሊዮን ብር ($1.1 ቢሊዮን) ቢወስድም እስካሁን ድረስ አልተጠናቀቀም ያሉ ሲሆን አጠቃላይ የስኳር ማምረቻ ኢንዱስትሪውን ለማስፋፋት የተደረገው ጥረት 144 ቢሊዮን ብር ($2.1 ቢሊዮን) ተጨማሪ የውጭ ዕዳ ያስከተለ ሆኖ አልፏል ሲሉ ነው የገለጹት።
ከእነዚህ ፕሮጀክቶች ጋር የተያያዘ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአሁኑ ወቅት 110 ቢሊዮን ብር ዕዳ ውስጥ ይገኛል ሲሉ ዶ/ር ብሩክ በመድረኩ ላይ በነበራቸው ገለጻ ያቀረቡት።
አክለውም፥ የወልቃይት ስኳር ፋብሪካን ሙሉ በሙሉ አጠናቆ ወደ ሥራ ለማስገባት ተጨማሪ 42 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።
በተጨማሪም፥ ኢትዮጵያ የአዲስ አበባ-ጂቡቲ የባቡር መስመርን ለመገንባት ከ5 ቢሊዮን ዶላር በላይ የተበደረች ቢሆንም፣ አዋጭነቱ ሳይረጋገጥ ሳይረጋገጥ ተጨማሪ 2.2 ቢሊዮን ዶላር የንግድ ብድር መወሰዱን አስታውሰዋል።
በተጨማሪም፣ የዩኒቨርሲቲዎች ማስፋፊያ እና የንግድ አዋጭነታቸው ሳይጠና የተገነቡ የክልል አውሮፕላን ማረፊያዎች ያለ ንግድ ወይም ተቋማዊ መርህ የተከናወኑ ፕሮጀክቶች ማሳያ መሆናቸውን አንስተዋል።
ለዚህም የንጉሳዊው ሥርዓት አዲስ አበባ ላይ ብቻ ያተኮረ ዕድገት፣ የደርግ ሥርዓት በዕዳ የተደገፈና የግሉን ዘርፍ ያገለለ የኢንዱስትሪ ልማት እና የኢሕአዴግ ሥርዓት ከ1991 እስከ 2018 በነበረው ጊዜ ውስጥ በመንግሥት የልማት ድርጅቶች ብድር ላይ ብቻ መደገፉን በምሳሌነት ጠቅሰዋል።
"ያለ ዲሲፕሊን የሚደረግ የመሠረተ ልማት ግንባታ ስብራትን ይፈጥራል። ምርታማነት የሌለው መሠረተ ልማት ይቆማል። ያለ ተቋማት የሚገነባ ፕሮጀክት ዘላቂ ሊሆን አይችልም" ሲሉ ነው ዋና ሥራ አስፈጻሚው ብሩክ ታዬ (ዶ/ር) የገለጹት።
ባለፉት ስምንት ወራት ውስጥ የቴሌኮም ዘርፉ 121 ቢሊዮን ብር ገቢ ማስመዝገቡ፣ እንዲሁም ባለፉት ሰባት ዓመታት 48 ቢሊዮን ችግኞችን ለመትከል እና 20 ብሔራዊ የቱሪዝም ፕሮጀክቶችን ለመገንባት ያስቻለው የመንግሥትና የመንግስት የግል አጋርነት ሞዴል የዚህ የፖሊሲ ሽግግር ውጤቶች መሆናቸውን ጠቁመዋል።
የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን አያያዝ በሙያዊ መንገድ ለመምራት ከነገ ዛሬ አራት ዓመት ተኩል ገደማ በፊት የተቋቋመው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ፣ በአሁኑ ወቅት 8.2 ትሪሊዮን ብር ጠቅላላ ሀብት እንደሚያስተዳድርና 6.9 ትሪሊዮን ብር አጠቃላይ ገቢ ያመነጨ መሆኑን ዶ/ር ብሩክ በሪፖርታቸው አመልክተዋል
ተቋሙ በዚህ የሥራ ዘመን ውስጥ 715 ቢሊዮን ብር የሥራ ግብር እና ታክስ ያበረከተ ሲሆን፣ 3.9 ቢሊዮን ዶላር አዲስ ኢንቨስትመንት መሳብ መቻሉንና እና በሥሩ ካሉ ድርጅቶች 52 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ገቢ እንዲመነጭ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸዋል።
@TikvahethMagazine | 22 373 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
