TIKVAH-MAGAZINE
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያና የመረጃ መለዋወጫ መድረክ ነው። በ +251913134524 ላይ ያግኙን። ለማስታወቂያ @tikvahmagbot ላይ መረጃ ይጠይቁ።
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام TIKVAH-MAGAZINE
کانال TIKVAH-MAGAZINE (@tikvahethmagazine) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 192 649 مشترک است و جایگاه 917 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 98 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 192 649 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 06 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 420 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 30 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 12.90% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 8.79% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 24 855 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 16 933 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 71 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያና የመረጃ መለዋወጫ መድረክ ነው።
በ +251913134524 ላይ ያግኙን።
ለማስታወቂያ @tikvahmagbot ላይ መረጃ ይጠይቁ።”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 07 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 07 ژوئیه | +32 | |||
| 06 ژوئیه | +35 | |||
| 05 ژوئیه | +18 | |||
| 04 ژوئیه | +27 | |||
| 03 ژوئیه | +40 | |||
| 02 ژوئیه | +60 | |||
| 01 ژوئیه | +27 |
| 2 | አሜሪካ ለሶማሊያው ሰላም አስከባሪ ልዑክ የምትሰጠውን የሎጂስቲክስ ድጋፍ ልታቋርጥ ነው።
በሶማሊያ ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ወደ 12 ሺህ የሚጠጉ ወታደሮችን ይዞ ለመሰማራት የታቀደው አዲሱ የአፍሪካ ኅብረት የድጋፍና ማረጋጊያ ተልዕኮ (AUSSOM) በአሜሪካ ምክንያት መስተጓጎል ሊገጥመው ይችላል ተብሏል።
አሜሪካ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) የሚያደርገውን የሎጂስቲክስ ድጋፍ ልታቋርጥ በመወሰኗ ምክንያት የመፍረስ አደጋ እንደተጋረጠበት ሮይተርስ የዲፕሎማሲ ሰነዶችን ዋቢ በማድረግ ዘግቧል።
በተመድ የሶማሊያ ድጋፍ ሰጪ ቢሮ (UNSOS) በኩል ለሚቀርቡት እንደ ምግብ፣ ነዳጅ፣ ሕክምና እና ማመላለሻ ላሉ የሎጂስቲክስ አቅርቦቶች የአሜሪካ ድጋፍ ከፍተኛ ድርሻ ያለው ነው።
ይሁን እንጂ ዋሽንግተን ለአፍሪካ ኅብረት በላከችው ዲፕሎማሲያዊ ማስታወሻ፥ ከ2026 ማብቂያ በኋላ ይህንን የሎጂስቲክስ ድጋፍ እንደማትደግፍ ያስታወቀች ያስታወቀችው።
አሜሪካ ለዚህ ውሳኔ በምክንያትነት የጠቀሰችው የሶማሊያ መንግሥት የውስጥ የፖለቲካ ሽኩቻ እንዲሁም በዚህ ሁሉ ዓመታት የዓለም አቀፍ እርዳታ አልሸባብን ማሸነፍና የሀገሪቱን የጸጥታ ኃላፊነት ሙሉ በሙሉ መረከብ ባለመቻሉ መሆኑ ነው የተገለጸው።
ዋሽንግተን ባለፉት ዓመታት በቢሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር ብታፈስም የሚጠበቀውን ውጤት አለማግኘቷም ለውሳኔው ምክንያት መሆኑ ነው የገለጸው።
ይህ የአሜሪካ ውሳኔ ሌላ አማራጭ ድጋፍ ካልተገኘ ተልዕኮው ሙሉ በሙሉ እንዲቆም ሊያደርግ እንደሚችል የአፍሪካ ኅብረት እና ዲፕሎማቶች ስጋታቸውን ገልጸዋል።
ይህም በሶማሊያ ውስጥ የአልሸባብ ጥቃቶች እንደገና እንዲያገረሹ እና የሀገሪቱ መንግሥት ይበልጥ እንዲዳከም በር የሚከፍት በመሆኑ በምሥራቅ አፍሪካ የጸጥታ መዋቅር ላይ ከፍተኛ ስጋት የደቀነ ነው።
Credit: Reuters
@TikvahethMagazine | 25 983 |
| 3 | ኢትዮጵያ በቡና ኤክስፖርት ታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ 3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ አስመዘገበች
ኢትዮጵያ በተያዘው በጀት ዓመት ከቡና ኤክስፖርት ለመጀመሪያ ጊዜ 3 ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር ገቢ ማግኘቷ ተገልጿል።
ሀገሪቱ ባለፉት ዓመታት የቡና ኤክስፖርት ገቢ በቋሚነት እያደገ የመጣ ሲሆን በ2015 በጀት ዓመት 1.4 ቢሊዮን ዶላር፣ በ2016 በጀት ዓመት 1.43 ቢሊዮን ዶላር፣ እንዲሁም በ2017 በጀት ዓመት ገቢው ወደ 2.65 ቢሊዮን ዶላር ከፍ ብሎ ነበር።
የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አዱኛ ደበላ ይህ የ3 ቢሊዮን ዶላር ገቢ የረጅም ጊዜ ዕቅድ አካል መሆኑን ባስተላለፉት መልዕክት ገልጸዋል።
@TikvahethMagazine | 23 301 |
| 4 | "ከእያንዳንዱ የምግብ እጥረት አኃዛዊ መረጃ ጀርባ የሚሰቃዩ ሕፃናት እና ቤተሰቦች መኖራቸውን ማስታወስ ይገባል" — ወ/ሮ ቤዛ በሻህ የሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች ዋና ሥራ አስኪያጅ
በጀርመን ሀምበርግ በተካሄደው የ2026ቱ የሃምበርግ ዘላቂ ልማት ኮንፈረንስ (HSC) ላይ የተገኙት የሆፕ ስፓይና ቢፊዳ እና ሃይድሮሴፋለስ (HOPE-SBH) ዋና ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ቤዛ በሻህ ኃይሌ፣ በነርቭ ዘንግ አፈጣጠር ችግሮች መከላከልና በእናቶችና ሕፃናት ጤና ዙሪያ ዓለም አቀፍ ትኩረት እንዲሰጥ ጥሪ አቅርበዋል።
ወ/ሮ ቤዛ በኮንፈረንሱ ማዕቀፍ ውስጥ ባደረጉት ንግግር፥ በሕይወት የመጀመሪያዎቹ 1,000 ቀናት ላይ የተመጣጠነ ምግብን ለማረጋገጥ የሚደረግ ኢንቨስትመንት የእናቶችንና የሕጻናትን ጤና ለማሻሻል፣ ለትምህርት ጥራትና ለኢኮኖሚ ዕድገት ወሳኝ ስትራቴጂ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
በዚህ መድረክ ላይም "ከእያንዳንዱ የምግብ እጥረት አኃዛዊ መረጃ ጀርባ የሚሰቃዩ ሕፃናት እና ቤተሰቦች መኖራቸውን ማስታወስ ይገባል" ሲሉ የገለጹት ዋና ሥራ አስኪያጇ፣ ይህም ለሰው ልጅ ካፒታል እና ለዘላቂ ልማት ትልቅ እንቅፋት እንደሚሆን አስገንዝበዋል።
ይህንን ችግር ለመቅረፍ ድርጅታቸው ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች ላለፉት 10 ዓመታት የሠራባቸውን መፍትሔዎች ያብራሩት ወ/ሮ ቤዛ፥ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በመተግበር ላይ የሚገኘውንና ጨውን በአዮዲን እና በፎሊክ አሲድ በጋራ የማበልጸግ ሂደት (Double Salt Fortification) በሀገር በቀል ጥናትና ምርምር የታገዘ ስኬታማ ተሞክሮ መሆኑን በምሳሌነት አቅርበዋል።
ለዚህ ብሔራዊ የፖሊሲ ስኬትም የመንግሥት ተቋማት፣ የልማት አጋሮች፣ የግሉ ዘርፍ እና የሲቪል ማኅበረሰብ በቅንጅት መሥራታቸው ወሳኝ ሚና እንደነበረው ጠቁመዋል።
በማጠቃለያቸውም፣ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ከአጠቃላይ የፖሊሲ ውይይቶች ባለፈ ተጨባጭና ዘላቂ ውጤት ወደሚያመጡ ተግባራዊ አጋርነቶች መሸጋገር እንዳለበት አሳስበዋል።
(ሆፕ ኤስ.ቢ.ኤች /HOPE-SBH) | 23 419 |
| 5 | #አፋልጉኝ
በመጀመሪያው ፎቶ የምትመለከቱት የ7 ዓመት ህፃን ልጅ ቅዳሜ 20/10/2018 6:00 ሰዓት አካባቢ ኮልፌ አጠናተራ መብራት ሀይል አከባቢ ከቤት እንደወጣ አለመመለሱን ቤተሰቦቹ ገልጸውልናል።
መሀመድ ሁሴን ሻፊ ህጻን ልጅ አወጣጡ የጓደኛዬ ምርቃት ብሎ የወጣ ሲሆን እዛም አለመድረሱንና ፈላጊ አባት ሁሴን ሻፊ ነግረውናል።
ህጻን የየየ የተመለከታችሁ 0911622758
0937657710 አሳውቁን ብለዋል።
በሁለተኛው ፎቶ ላይ የምትመለከቱት ናሆም እንዳልካቸው አራጋው ይባላል በቀን 19/10/2018 ከቀኑ 11:00 ፊጋ ሲ ኤም ሲ አከባቢ እንደወጣ አልተመለሰም።
ፈላጊ ወላጅ አባት +251973137595
@TikvahethMagazine | 32 940 |
| 6 | በጋና በተከሰተ የጎርፍ አደጋ 13 ሰዎች ህይወት አለፈ።
⚫ የውሃ ማስተላለፊያ መስመሮችን የዘጉ ግንባታዎች በሙሉ እንዲፈርሱ ትዕዛዝ ተላልፏል።
በጋና ዋና ከተማ አክራ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት በተከሰተ ከፍተኛ የጎርፍ አደጋ ቢያንስ የ13 ሰዎች ሕይወት አልፏል።
የጎርፉ መጠንም ሀገሪቱ ከ1955 በኋላ ያስመዘገበችው አራተኛው ከባዱ ጎርፍ አደጋ ነው ተብሏል።
የጋናው ፕሬዝዳንት ጆን ማሃማ አደጋውን ተከትሎ የከተማዋን ዘላቂ የጎርፍ አደጋ ችግር ለመፍታት የውሃ ማስተላለፊያ መስመሮችን የዘጉ ግንባታዎች በሙሉ እንድፈርሱ ጥብቅ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።
በተጨማሪም የገንዘብ ሚኒስትሩ የአስቸኳይ ጊዜ መጠባበቂያ ፈንድ እንዲለቅ ያዘዙ ሲሆን፣ ብሄራዊ የአደጋ መከላከልና ማስተባበሪያ ድርጅት ለተጎጂዎች ፈጣን ድጋፍ እንዲያደርግ አዘዋል።
ፕሬዝዳንት ማሃማ አፅንዖት በመስጠት “በአክራ ለሚከሰተው የጎርፍ አደጋ ዘላቂ መፍትሄ መፈለግ አለብን” ብለዋል።
እሁድ ምሽት የጣለው ከባድ ዝናብ ያስከተለው ጎርፍ መድረቅ የጀመረ ቢሆንም፣ በነፍስ አድን ስራ ወቅት የሟቾች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል የጋና ብሄራዊ የእሳት አደጋ አገልግሎት ገልጿል።
ፖሊስን፣ የእሳት አደጋ አገልግሎትን እና ብሄራዊ የአደጋ አስተዳደር ድርጅትን ጨምሮ የአደጋ ጊዜ ምላሽ ሰጪ ቡድኖች በጎርፍ በተጎዳው ቀጠና ተሰማርተዋል።
የጋና ብሄራዊ የእሳት አደጋ አገልግሎት እስካሁን ድረስ ከ470 በላይ ሰዎችን ማዳን መቻሉን አስታውቋል።
መረጃው የቢቢሲ አፍሩካ እና የአልጀዚራ ነው።
@TikvahethMagazine | 33 247 |
| 7 | የኢትዮጵያ መንግሥት እና የዩሮቦንድ አበዳሪዎች አዲስ ስምምነት ምን ይዟል ?
ቀደም ሲል ኢትዮጵያ ከግል የቦንድ ባለቤቶች ጋር ደርሳው የነበረው ስምምነት "የአበዳሪዎች እኩልነት መርህን አያሟላም" በሚል በዋና አበዳሪ ሀገራት ኮሚቴ (OCC) ውድቅ መደረጉ ይታወሳል።
ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ የገንዘብ ሚኒስቴር ከግንቦት 28 እስከ ሰኔ 28/2018 ዓ.ም. ባደረገው አዲስ ድርድር፣ ከተቃወሙት አበዳሪዎች ጋር የሚያስማማ አዲስ የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት ላይ መድረሱን አስታውቋል።
ይህንን ማስታወቂያ ተከትሎ የኢትዮጵያ ቦንድ ዋጋ ላለፉት ስድስት ወራት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በለንደን ገበያ እስከ $109.17 ሳንቲም ከፍ ብሏል።
ባለሀብቶቹን አሁን እንዲስማሙ ያደረጋቸው "የገንዘብ ዋስትና" የተሰኘ አዲስ ማካካሻ በስምምነቱ ውስጥ መካተቱ ነው። ይህ አዲስ አሠራር ኢትዮጵያ ወደፊት አዲስ እስከ 1 ቢሊዮን ዶላር የሚደርስ ዩሮቦንድ ለገበያ በምታቀርብበት ወቅት (በ2028 እ.ኤ.አ.) እኚሁ ባለሀብቶች በአሁኑ ቦንድ ባላቸው የገንዘብ መጠን ልክ ድርሻ ቀድመው የመግዛት መብት ይሰጣቸዋል።
አዲሱ ቦንድ የሚከፍለው ዓመታዊ ወለድ ከአሁኑ የሚበልጥ ሲሆን፣ የሚሰላውም በወቅቱ የአሜሪካ መንግሥት የ6 ዓመት የግምጃ ቤት ሰነድ ወለድ ላይ ተጨማሪ 4.6 በመቶ ተደምሮበት ነው።
ይሁን እንጂ መንግሥት እስከ ሰኔ 2020 ዓ.ም. ድረስ አዲስ ቦንድ ማውጣት የማይፈልግ ከሆነ፣ ለባለሀብቶቹ የሰጠውን መብት ወቅታዊ ዋጋ ተምኖ እስከ 90 ሚሊዮን ዶላር በሚደርስ ክፍያ አማራጩን ማቋረጥ ይችላል።
በአዲሱ ስምምነት በጸኑት ዋና ዋና የፋይናንስ ውሎች መሠረት፣ 1 ቢሊዮን ዶላር በነበረው የቦንዱ ዋና ዋጋ ላይ የ12 በመቶ ቅናሽ (Haircut) ተደርጎ ባለሀብቶቹ የሚመለስላቸው 880 ሚሊዮን ዶላር ይሆናል።
ይህ ገንዘብ እስከ ሐምሌ 2021 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ በአራት ዙር የሚከፈል ሲሆን፣ የመጀመሪያው የ180 ሚሊዮን ዶላር ክፍያ ከሁለት ሳምንት በኋላ ይፈጸማል።
እንዲሁም መንግሥት ከታኅሣሥ 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ሳይከፍል ያቆየውን የ99.37 ሚሊዮን ዶላር የወለድ ዕዳ ወዲያውኑ የሚከፍል ሲሆን፣ ቦንዱ እስከሚጠናቀቅበት 2021 ዓ.ም. ድረስም 6.15 በመቶ ዓመታዊ ወለድ መክፈሉን ይቀጥላል።
ከመደበኛው ክፍያ በተጨማሪ መንግሥት የቦንድ ገዢዎቹን የወከለውን ኮሚቴ የሥራ ክፍያ 10 ሚሊዮን ዶላር ጨምሮ ድርጅቱ ያወጣቸውን ወጪዎች ሙሉ በሙሉ ለመሸፈን ተስማምቷል።
በሌላ በኩል፣ የኢትዮጵያን የ2024 ቦንድ ከያዙት አካላት መካከል 45 በመቶ የሚሆነውን የሚወክለው የአበዳሪዎች ኮሚቴ ምንም እንኳ አሁን ከሀገሪቱ ጋር ስምምነት ላይ ቢደርስም፣ ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) ሂደቱን የመራበትን መንገድ አጥብቆ ኮንኗል።
ኮሚቴው ባወጣው መግለጫ የዕዳ ሽግሽግ ሂደቱ ፈጣንም ሆነ ፍትሐዊ እንዳልነበረና አይኤምኤፍ የኢትዮጵያን የዕዳ ቅነሳ ፍላጎት የገመገመበት መንገድ እጅግ ደካማ እንደነበር ጠቅሷል።
አይኤምኤፍ የቀረበበትን ወቀሳ ያስተባበለ ሲሆን፣ ይህ አዲስ ስምምነት ለኢትዮጵያ ከተቀመጡት የዕዳ ዘላቂነት ግቦችና መለኪያዎች ጋር ሙሉ በሙሉ የሚጣጣምና በኢትዮጵያ አጠቃላይ የዕዳ ሽግሽግ ሂደት ውስጥ ትልቅ እርምጃ መሆኑን ገልጿል።
ቀደም ሲል ስምምነቱን ውድቅ አድርገውት የነበሩትና የዕዳ ሽግሽግ አበዳሪ አገራት ኮሚቴን (OCC) የሚመሩት ፈረንሳይ እና ቻይናም በአሁኑ አዲስ ስምምነት ላይ ተቃውሞ እንዳላሰሙ የተገለጸ ሲሆን፣ ይህም ኢትዮጵያ ከአበዳሪ አገራት ጋር ያላትን አጠቃላይ የዕዳ ሽግሽግ ሂደት ቶሎ እንድታጠናቅቅ ትልቅ በር ይከፍታል ተብሏል።
Credit: Bloomberg, BBC Amharic
@TikvahethMagazine | 29 017 |
| 8 | #WhatsApp 🟩
ዋትስአፕ ከ3 ቢሊዮን በላይ ለሚሆኑ ተጠቃሚዎቹ የስልክ ቁጥራቸውን ሳያጋሩ ልክ እንደ ቴሌግራም የግል መለያ ስም የማስያዝ እና የመቀየር አገልግሎት በይፋ መፍቀዱን አስታውቋል።
አዲሱ የዋትስአፕ ማሻሻያ በተለይም የስልክ ቁጥርን ለሌላ ሰው አሳልፎ ለመስጠት ለሚቸገሩ እና ለግል ዲጂታል ደኅንነታቸው ከፍተኛ ትኩረት ለሚሰጡ ዜጎች ትልቅ መፍትሔ ሆኖ ቀርቧል።
ዋትስአፕ አገልግሎቱን ደረጃ በደረጃ ለሁሉም ተጠቃሚዎች ተደራሽ ለማድረግ እየሠራ መሆኑን የጠቀሰ ሲሆን ለዋትስአፕ ቢዝነስ እና ለተወሰኑ የቤታ ተጠቃሚዎች ቀርቧል።
@TikvahethMagazine | 31 588 |
| 9 | #DRC 🇨🇩
የኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ መንግሥት በአገሪቱ እንደገና እያቀረረ የመጣውን የኢቦላ ወረርሽኝ ስርጭት ለመግታት እና ለመቆጣጠር ሲል በዋና ከተማዋ ኪንሻሳ ጨምሮ በሦስት ከፍተኛ ተጋላጭ በሆኑ ግዛቶች ህዝባዊ ስብሰባዎች ላይ እገዳ ተላልፏል።
ይህ አስቸኳይ እገዳ የተጣለው በነዚህ አካባቢዎች አዲስ የቫይረሱ ተጠቂዎች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ መሆኑ ነው የተገለጸው።
ነዋሪዎችም አስፈላጊውን የንጽህና መጠበቂያ መመሪያዎችን እንዲተገብሩና ምልክቱ የሚታይባቸውን ሰዎች በአቅራቢያ ለሚገኙ የጤና ተቋማት በፍጥነት እንዲያሳውቁ ጥሪ ቀርቧል።
ኮንጎ በኢቦላ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 1 ሺ 307 መድረሱን እና ከእነዚህ ውስጥ 377 ያህሉ መሞታቸውን አስታውቃለች።
@TikvahethMagazine | 24 138 |
| 10 | “በሳቅዎ ይክፈሉ” ምንድን ነው ?
ሐረር ቢራ «ሳቅፔ» (SAQPay) የተሰኘ መተግበሪያ ይፋ አድርጓል። መተግበሪያው እውነተኛ ሳቅን በመለየት ነጥብ የሚሰጥ ሲሆን በተጠራቀሙ ነጥቦች ሐረር ቢራን በተመረጡ ቦታዎች በቅናሽ መጠቀም የሚያስችል ነው።
"ለእኛ ለሐረሮች፣ ከገንዘብ ልውውጥ ይልቅ እጅግ ትርጉም ያለው ነገር አብረን የምንጋራው ደስታ እና በእውነተኛ ሳቅ ውስጥ የሚፈጠረው አብሮነት እንደሆነ እናምናለን። «በሳቅዎ ይክፈሉ» ይሄንኑ እውነት በተግባር የምናሳይበት መንገዳችን ነው። ምክንያቱም መዝናናት ለሁሉም ክፍት ሲሆን፣ ሰዎች በአንድ ላይ ከመሰባሰብ አልፈው የእርስ በርስ ትስስራቸው ይበልጥ ይጠነክራልና!" ሲሉ የሃይኒከን ኢትዮጵያ የማርኬቲንግ ዳይሬክተር ካሳሁን ፈለቀ ገልጸዋል።
ሁሉም «በሳቅዎ ይክፈሉ» ላይ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች በተመረጡ ቦታዎች ብቻ የሚካሄዱ ናቸው የተባለ ሲሆን ህጋዊ የእድሜ ገደብን እና ኃላፊነት የተሞላበት መጠጥ አጠቃቀም መመሪያዎችን ሙሉ በሙሉ ያከበሩ ስለመሆናቸውም በመግለጫው ጠቅሷል።
@TikvahethMagazine | 22 287 |
| 11 | ስልኮትን ለመቀየር አስበዋል?
አዳዲስ እንዲሁም በመጠኑ ያገለገሉ ስልኮችን ከተሟላ ዋስትና እና ጥገና ጋር ይዘን ቀርበናል📱ለበለጠ መረጃ ቻናላችንን ይጎበኙ
https://t.me/phonehub27
📞 0996544119
📩 inbox @kidaa3535
📍አድራሻ- ቦሌ ከሸገር ህንፃ አጠገብ
📨 ክፍለ ሀገር ላላቸሁ ደንበኞችቻችንም በ DHL መላክ ጀምረናል | 19 634 |
| 12 | ተ/ሀይማኖት ላይ ለጥቂት ሱቆች ብቻ 15% ቅናሽ
☎️ 09 47 77 11 62
💥💥የከተማችን ታላቁ የንግድ ማዕከል መርካቶ በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኝ
💥💥G+ 4 Mall - 6784 ካሬ ላይ የሚያርፍ
11ካሬ, 16ካሬ ,22ካሬና 32 ካሬ አማራጭ
ከ 3,300,000 ብር ጠቅላላ ክፍያ
ከ 1,155,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ
💥በ 4ቱም አቅጥቅጫ የመንገድ አማራጮች ያሉት
💥 በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ የሚረከቡት
💥 በ Net area የሚሸጥ
ለበለጠ መረጃ - ☎️09-47-77-11-62
Telegram @Novi_03 | 25 476 |
| 13 | የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ሳምንታዊ ግበይት 31.3 ሚሊዮን ብር ሆኖ ተመዝግቧል።
የኢትዮጵያ ሰነደ መዋዕለ ንዋይ ገበያ (ESX) ሳምንታዊ ግብይቱን ባጠናቀቀበት የመዝጊያ ደውል ላይ የ31.3 ሚሊዮን ብር አጠቃላይ የሰነዶች ዝውውር አስመዝግቧል።
ይህ የግብይት መጠን ባለፈው ሳምንት ከተመዘገበውና ጊዜያዊ የገበያ መነቃቃት ከነበረው የ1 ቢሊዮን ብር ታሪካዊ ዝውውር አንጻር ዝቅ ያለ ቢሆንም ገበያው በተረጋጋ መዋቅር ላይ መቀጠሉን ያሳያል።
📊 የተፈጸሙ ግብይቶች ብዛት - በአጠቃላይ 149 ግብይቶች (Transaction) ተከናውነዋል።
📶 ባለቤት የቀየሩ አክሲዮኖች ብዛት - 14,590 ገደማ አክሲዮኖች ከአንድ ባለሀብት ወደ ሌላ ተላልፈዋል።
በገበያው ላይ ከተንቀሳቀሰው አጠቃላይ የገንዘብ መጠን ውስጥ የአዋሽ ባንክ እና ገበያውን አዲስ የተቀላቀለው የአባይ ባንክ አክሲዮኖች ብቻቸውን የ95 በመቶ ድርሻን ተቆጣጥረዋል።
#AWAB (አዋሽ ባንክ)
📶 6,700 አክሲዮኖች የተገበያዩ ሲሆን፣ ይህም በሳምንቱ ባለቤት ከቀየሩት አጠቃላይ አክሲዮኖች የ46 በመቶ ድርሻ አለው።
📊 20.3 ሚሊዮን ብር ግብይት የተፈጸመበት ሲሆን፣ ይህም ከጠቅላላው የገበያ የገንዘብ ዝውውር (Value) 64.9% ድርሻ አለው።
📊 በሳምንቱ በተከናወኑ የግብይቶች ብዛት (Transactions) ረገድ የ60% ድርሻ ነበረው።
📈 በገዢዎች (2,900 ብር) እና በሻጮች (3,000 ብር) መካከል የ100 ብር ልዩነት እየታየበት ሳምንታዊ አማካይ ዋጋው በ2,998 ብር አካባቢ ረግቶ ውሏል።
#ABAY (አባይ ባንክ)
📶 ግብይት በጀመረባቸው በመጀመሪያዎቹ ሁለት ቀናት ብቻ 5,186 አክሲዮኖች ተገበያይተዋል።
📊 የ9.6 ሚሊዮን ብር ግብይት በማከናወን ከጠቅላላው የገበያ የገንዘብ ዝውውር 30.9% ድርሻ በመያዝ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል።
📊 በሳምንቱ በተከናወኑ የግብይቶች ብዛት ረገድ የ14% ድርሻ ነበረው።
▶️ አዲሱ አባይ ባንክ በ2,000 ብር መዝጊያ ዋጋ ገበያውን ተቀላቅሏል።
#ETEL (ኢትዮ ቴሌኮም)
📶 2,287 አክሲዮኖች ተገበያይተዋል።
📊 የ879,000 ብር ግብይት የተከናወነበት ሲሆን፣ ይህም የ2.88% የገበያ ድርሻ አለው።
📊 በሳምንቱ በተከናወኑ የግብይቶች ብዛት ረገድ የ20% ድርሻ ነበረው።
📈 የ400 ብር ጣሪያውን ሰብሮ በመውጣት በሳምንቱ መጨረሻ እስከ 450 ብር ከፍተኛ ዋጋ የተሸጡ አክሲዮኖች ነበሩ።
#WGB (ወጋገን ባንክ)
📶 343 አክሲዮኖች ተገበያይተዋል።
📊 የ453,000 ብር ግብይት የተከናወነ ሲሆን፣ በግብይት ብዛት ረገድ የ7% ድርሻ ነበረው።
📈 በሳምንቱ መጀመሪያ ከነበረበት 1,290 ብር ተነሥቶ በሳምንቱ ማብቂያ 1,396 ብር ላይ ደርሷል።
በገበያው ላይ ከተመዘገቡት ኩባንያዎች መካከል የገዳ ባንክ (GDAB) አክሲዮኖች በዚህ ሳምንት ምንም ዓይነት ግብይት ሳይከናወንባቸው ተጠናቀዋል።
Credit : ESX, Nigat-Post
@TikvahethMagazine | 30 745 |
| 14 | #Update 🇻🇪
በቬንዙዌላ በተከሰቱት ሁለት ተከታታይና ኃይለኛ የመሬት መንቀጥቀጦች የሟቾች ቁጥር ከ920 በላይ ማለፉን የሀገሪቱ ባለሥልጣናት አስታወቁ።
በአሁኑ ወቅት ቢያንስ 172 ሰዎች በፍርስራሽ ውስጥ ተቀብረው እንደሚገኙ ሲጠቆም፣ የቆሰሉ ዜጎች ቁጥር 3,360 ደርሷል።
ከ50,000 በላይ የሚሆኑ ዜጎች ያሉበት ሳይታወቅ የጠፉ መሆናቸው የተመዘገበ በመሆኑ የሟቾች ቁጥር አሁንም በከፍተኛ ደረጃ ሊጨምር እንደሚችል ተሰግቷል።
የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) ባወጣው የመጀመሪያ ደረጃ ግምት፣ በሬክተር ስኬል 7.2 እና 7.5 በሆነው በዚህ የመሬት መንቀጥቀጥ የደረሰው ቀጥተኛ የኢኮኖሚ ውድመት 6.7 ቢሊዮን ዶላር ይደርሳል።
የተመድ የስደተኞች ኤጀንሲ (IOM) በበኩሉ በዋና ከተማዋ ካራካስ የሚኖሩ 2 ሚሊዮን ሰዎችን ጨምሮ በአጠቃላይ እስከ 6.76 ሚሊዮን የሚደርሱ ዜጎች በአደጋው በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ መጎዳታቸውን ገልጿል።
የሀገሪቱ ተጠባባቂ ፕሬዚዳንት ዴልሲ ሮድሪጌዝ ለተጎዱ ሆስፒታሎችና መኖሪያ ቤቶች መልሶ ማቋቋሚያ የሚሆን የ200 ሚሊዮን ዶላር ፈንድ መቋቋሙን አስታውቀዋል።
የአሜሪካ መንግሥትን ጨምሮ ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የተውጣጡ ከ1,600 በላይ የዓለም አቀፍ የነፍስ አድን ቡድን አባላት በ17 ልዩ በረራዎች ካራካስ የገቡ ሲሆን የነፍስ አድን ሥራው ላይ እየተረባረቡ ይገኛሉ።
ቪዲዮ 🤩 : የሳተላይት ምስል
Source : Reuters
@TikvahethMagazine | 29 267 |
| 15 | በመዲናዋ 100 ኪዮስኮችን ለመገንባት የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ።
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ፋውንዴሽንና የተባበሩት መንግሥታት የሰፈራ ፕሮግራም (UN-Habitat) በ300,000 ዶላር 100 ኪዮስኮችን ለመገንባት የሚያስችል ፕሮጀክት ይፋ አደረጉ።
ለዚህ ፕሮጀክትም ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ እና ከመስሪያ ቦታዎች ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ጋር የአራትዮሽ ስምምነት ተደርጓል።
የሚገነቡት ኪዮስኮች በከተማዋ በሚገኙ 11ዱም ክፍለ ከተሞች በተመረጡ ወረዳዎች ውስጥ ለሚገኙ 200 ከስደት ተመላሽ ለሆኑ ዜጎችና የከተማዋ ነዋሪዎች የሥራ ዕድል ለማመቻቸት ታቅዷል።
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ፋውንዴሽን ለዚህ ፕሮጀክት 200 ሺ ዶላር ፈሰስ ሲያደርግ የተመድ የሰፈራ ፕሮግራም 100 ሺውን ሸፍኗል።
@TikvahethMagazine | 22 223 |
| 16 | ቀጣዩ የሪል እስቴት ሽያጮ እኛ ጋር ነው - ጃካ CRM ን እናስተዋውቅዎ።
ጃካ ምን ይሰጥዎታል?
👥 Leads— ዝግጁ ደንበኞች
ከ2 ዓመት በላይ ባደረግነው ጥናት ከ17,000 በላይ የተረጋገጡ ሊዶች::
📊 CRM — ሽያጭዎን በስርዓት ያስተዳድሩ
ሁሉንም ደንበኞችዎን፣ ቀጠሮዎችዎን፣ እና የሽያጭ ሂደትዎን በአንድ ቦታ ይከታተሉ።
ዋጋ — ከ1500 ብር ጀምሮ
🚀 ለመጀመሪያዎቹ 20 ተጠቃሚዎች ልዩ የ33% ቅናሽ እየሰጠን ነው። https://t.me/jakkacrm | 20 470 |
| 17 | ተ/ሀይማኖት ላይ ለጥቂት ሱቆች ብቻ 15% ቅናሽ
☎️ 09 47 77 11 62
💥💥የከተማችን ታላቁ የንግድ ማዕከል መርካቶ በቅርብ ርቀት ላይ የሚገኝ
💥💥G+ 4 Mall - 6784 ካሬ ላይ የሚያርፍ
11ካሬ, 16ካሬ ,22ካሬና 32 ካሬ አማራጭ
ከ 3,300,000 ብር ጠቅላላ ክፍያ
ከ 1,155,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ
💥በ 4ቱም አቅጥቅጫ የመንገድ አማራጮች ያሉት
💥 በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ የሚረከቡት
💥 በ Net area የሚሸጥ
ለበለጠ መረጃ - ☎️09-47-77-11-62
Telegram @Novi_03 | 24 506 |
| 18 | #Update 🇻🇪: በቬንዙዌላ የሟቾች ቁጥር 589 ደረሰ።
በቬንዙዌላ በተከሰተው አስከፊ የመሬት መንቀጥቀጥ የሟቾች ቁጥር 589 መድረሱን የሀገሪቱ ፕሰዚዳንት ዴልሲ ሮድሪጌዝ አስታውቀዋል።
ከአደጋው ጋር ተያይዞ የቆሰሉ ዜጎች ቁጥርም 2,980 መድረሱ ነው የተገለጸው።
የነፍስ አድን ቡድኖች አደጋው ከተከሰተ በኋላ ባሉት ወሳኝ የ72 ሰዓታት "ወርቃማ የምሕረት ሰዓታት" ውስጥ በፍርስራሾች ሥር የተቀበሩ ሰዎችን በሕይወት ለማውጣት ከፍተኛ ርብርብ እያደረጉ ነው።
የፍለጋ ቡድኖቹ ተጨማሪ ተጎጂዎችን እያገኙ በመሆናቸው የሟቾች ቁጥር አሁንም በከፍተኛ ሁኔታ ሊጨምር እንደሚችል ተገልጿል።
ቪዲዮ 🤩 : በነፍስ አድን ሥራው ወቅት አንዲት እናት በፍርስራሾች መካከል ልጇን ስትገላገል።
@TikvahethMagazine | 30 122 |
| 19 | የሶማሊያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ከኬንያ ተባረሩ
የሶማሊያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር በናይሮቢ ጀሞ ኬንያታ አየር ማረፊያ በደረሱበት ወቅት በኢሚግሬሽን መቆጣጠሪያ ላይ በተፈጠረ የቪዛ/ፕሮቶኮል አለመግባባት ምክንያት ኬንያን ለቀው እንዲወጡ መደረጋቸው ተነግሯል።
ባለስልጣኑ የዲፕሎማቲክ ፓስፖርት ይዘው የነበረ ቢሆንም፣ የኬንያ የኢሚግሬሽን ህግ በሚጠይቀው መሰረት ቅድመ ዝግጅት ወይም የዲፕሎማቲክ ፕሮቶኮል አለመሟላቱ ለክርክሩ መነሻ ሆኗል ነው የተባለው።
ዘገባው የሂራን ኦላይን ነው።
@TikvahethMagazine | 30 196 |
| 20 | በሮቻችን ተከፍተዋል
የንግድዎን ዕድገት የሚያፋጥኑበት፣ በዓይነቱ ለየት ያለው 8ኛው አግሮፉድ ፕላስትፕሪንትፓክ፣ 2ኛው ኢትዮፒካ ኮፊ ሾው እና ኢትዮጵያ ፉድ ሾው ዛሬ በይፋ በሮቹን ከፍቶ የዘርፉን ባለሙያዎችና ጎብኚዎች በመቀበል ላይ ይገኛል!
ከሰኔ 18 እስከ 20 ለ3 ተከታታይ ቀናት የሚቆየው ይህ ታላቅ አውደ ርዕይ፤ ከብራዚል፣ ቻይና፣ ጣሊያን፣ ጀርመን፣ ፈረንሳይ እና ከሌሎች ከ18 በላይ ሀገራት የተወጣጡ የዘርፉ ግዙፍ ኩባንያዎችና የኢንዱስትሪ መሪዎችን በአንድ ጣራ ስር ሰብስቧል።
በፕላስቲክ፣ ፓኬጂንግ (ማሸጊያ)፣ ፕሪንቲንግ (ሕትመት)፣ በምግብና መጠጥ ማቀነባበሪያ፣ በሬስቶራንት፣ ካፌ፣ በቡና ማቀነባበሪያና ላኪነት ላይ የተሰማራችሁ ኩባንያዎችና ሥራ ፈጣሪዎች በሙሉ፤ አዳዲስ የንግድ ትስስሮችን ለመፍጠርና የዓለምን ቴክኖሎጂ ለመገብየት አሁኑኑ ወደ አውደ ርዕዩ ኑ!
👥 ከ150 በላይ ታዋቂ የሀገር ውስጥና የውጭ ኤግዚቢተሮች
📍 ቦታ፦ በአዲሰ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር (AICC)
🎟️ መግቢያው፦ ሙሉ በሙሉ በነፃ ነው!
አሁኑኑ ቀድመው ይመዝገቡና በቀጥታ ይግቡ፡ https://pranaevents.net/apcfvisitor
የወደፊት የንግድ አጋርዎን ዛሬ ያግኙ! | 23 210 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
