🇪🇹 ኢትዮ Students
📈 تحلیل کانال تلگرام 🇪🇹 ኢትዮ Students
کانال 🇪🇹 ኢትዮ Students (@ethiostudents) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 48 493 مشترک است و جایگاه 3 536 را در دسته آموزش و رتبه 591 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 48 493 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 27 آوریل, 2025، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -699 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 0 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 12.72% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 5.56% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 6 170 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 2 698 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 50 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“Our Bot :
@EthioExamBot
Contact : @ethioexamsupport
Or
@Etssupport”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 18 مارس, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 25 آوریل | 0 | |||
| 24 آوریل | 0 | |||
| 23 آوریل | 0 | |||
| 22 آوریل | 0 | |||
| 21 آوریل | 0 | |||
| 20 آوریل | 0 | |||
| 19 آوریل | 0 | |||
| 18 آوریل | 0 | |||
| 17 آوریل | 0 | |||
| 16 آوریل | 0 | |||
| 15 آوریل | 0 | |||
| 14 آوریل | 0 | |||
| 13 آوریل | 0 | |||
| 12 آوریل | 0 | |||
| 11 آوریل | 0 | |||
| 10 آوریل | 0 | |||
| 09 آوریل | 0 | |||
| 08 آوریل | 0 | |||
| 07 آوریل | 0 | |||
| 06 آوریل | 0 | |||
| 05 آوریل | 0 | |||
| 04 آوریل | 0 | |||
| 03 آوریل | 0 | |||
| 02 آوریل | 0 | |||
| 01 آوریل | 0 |
| 2 | ልጅ የሚወልዱ 5000 ዶላር‼️
ፕሬዝዳንት ትራምፕ አዲስ ለሚወለዱ ህጻናት 5,000 ዶላር እንደሚሰጡ ቃል ገቡ‼️
ትራምፕ የእናቶችን የወሊድ መጠን ለማበረታታት አዋጭ ያሏቸውን እርምጃዎች እየወሰዱ ነው ተብሏል፡፡
ውሳኔው፣ "አሜሪካን እንደገና ጤናማ ማድረግ" ከሚለው የቀድሞው ፕሬዝዳንት ጆን ኤፍ ኬኔድ እቅድ አካል መሆኑ ተገልጿል።
የወቅቱ የአሜሪካ መንግስት አሜሪካውያን እንዲያገቡና ብዙ ልጆች እንዲወልዱ እያበረታታ እንደሚገኝ FOX ዘግቧል፡፡
@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS | 2 688 |
| 3 | ህንድ የፓኪስታን አሸባሪዎች በሂንዱ ቱሪስቶች ላይ ያደረሱትን አስከፊ የሽብር ጥቃት ተከትሎ በፓኪስታን ላይ ጠንከር ያለ እርምጃ እንደምትወስድ አስታወቀች
👉 በተፈፀመው የሽብር ጥቃት 26 ህንዳውያን ቱሪስቶች ተገድለዋል።
ህንድ እያንዳንዱ የፓኪስታን ዜጋ በ48 ሰአታት ውስጥ ህንድን ለቆ እንዲወጣ አዛለች። የሽብር ጥቃቱን ተከትሎ ህንድ በፓኪስታን ለመውሰድ ካቀደቻቸው እርምጃዎችም፤ የሁሉም ፓኪስታናዊያን ዜጎች ቪዛ መሰረዝ፣ በህንድ እና ፓኪስታን በ1960 የተፈረመውን የኢንደስ ውሃ ስምምነትን ማገድና የቫጋ (wagah) ድንበር መሻገሪያ መዝጋትን ያካትታል ሲል መቀመጫውን በፖላንድ ያደረገው ቪሴግራድ 24 የተሰኘው የዜና ድረገፅ ዘግቧል።
ፓኪስታን ቀደም ሲል የኢንደስ ውሃ ስምምነትን (IWT) ማቋረጥ የጦርነት ድርጊት ሊሆን እንደሚችል ገልጻለች። በአለም ባንክ አደራዳሪነት የተደረሰው ይህ ስምምነት በኢንደስ ተፋሰስ የሚገኙ 6 ወንዞችን ያካትታል። ህንድ ምስራቃዊ ወንዞችን (ሱትሌጅ፣ ቤያስ እና ራቪ) ያለገደብ አጠቃቀም ትቆጣጠራለች፣ ፓኪስታን ግን በምዕራብ ወንዞች (ኢንደስ፣ ጄለም፣ ቼናብ) ላይ ቀዳሚ መብቶች ያላት ቢሆንም ህንድ ደግሞ እንደ የውሃ ሃይል ላልሆኑ ፍጆታዎች ልትጠቀምባቸው ትችላለች።
ህንድ ከ6ቱም ወንዞች የውሃ አቅርቦትን መከልከል ከጀመረች ፓኪስታን በውሃ እጥረት ቀውስ ውስጥ ትገባለች። 70% የፓኪስታን የውሃ ፍላጎት በእነዚህ ወንዞች የተሸፈነ በመሆኑ ኢኮኖሚዋ ከባድ ችግር ውስጥ ይወድቃል።
የፓኪስታን ፑንጃብ እና ሲንድ አውራጃዎች ቁልፍ የግብርና ማዕከሎች ሲሆኑ ከፍተኛ የውሃ እጥረት እና የሰብል ምርት መቀነስ፣ የምግብ ዋስትና እጦት እና የኢኮኖሚ ኪሳራ ይገጥማቸዋል።
በአምሪሳር (ህንድ) እና በላሆር (ፓኪስታን) አቅራቢያ የሚገኘው ቫጋህ ድንበር ቁልፍ የንግድ መስመር ነው። የቫጋህ የንግድ መስመር መዘጋት በተለይ በግብርና ምርቶች እና በሲሚንቶ ንግድ ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ ይኖረዋል።
ታድያ ህንድ ይህን እርምጃ ከወሰደች ፓኪስታን በምትኩ በሶስተኛ አገሮች ወይም ወደቦች በኩል ለመጠቀም ትገደዳለች፤ ይህም አላስፈላጊ ወጪን እና የዋጋ ግሽበትን ይጨምራል። የፓኪስታን ላሆር ክልል ከፍተኛ የኢኮኖሚ ችግር፣ ስራ አጥነት እና ማህበራዊ ቀውስ ይገጥመዋል።
@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS | 2 815 |
| 4 | ሩሲያ እና ዩክሬን ከ500 በላይ የጦር እስረኞችን ተለዋወጡ
ሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነቱ ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ትልቅ ነው የተባለውን ከ500 በላይ የጦር እስረኞችን መለዋወጣቸው ተገለፀ።
የእስረኞች ለውውጡ የተከናወነው የሩስያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጊዜያዊ የፋሲካ የተኩስ አቁም ባወጁበት ወቅት ነው፡፡
የሩስያ መከላከያ ሚኒስቴር 246 የሚሆኑ የሩሲያ ወታደሮች በልውውጡ መመለሳቸውን ገልጿል፡፡
የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ በበኩላቸው 277 የሚሆኑ የዩክሬን ወታደሮች መፈታታቸውን አረጋግጠዋል።
@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS | 3 796 |
| 5 | ፖፕ ፍራንሲስ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ
ሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል፡፡
@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS | 4 370 |
| 6 | ከ14 ዓመት መለያየት በኃላ አርቲስት ገነት ንጋቱ እና አርቲስት ሙሉጌታ ጀዋሬ በድጋሚ ተሞሸሩ‼️
ሁሉቱም በማልቀስ ደስታቸውን የገለፁ ሲሆን ሁሉንም ነገር ለፈጣሪ ሰጥተን ድጋሚ ትዳርን አንድ ብለን ጀምረናል ያሉት ጥንዶች መልካም ምኞታችሁን ተመኙልን ብለዋል::
@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS | 5 257 |
| 7 | ሮቦት ማራቶን ሮጠ
በቤጂንግ ታሪክ ተሰርቷል።
ቲያንጎንግ አልትራ የተሰኘ ሮቦት የቤጂንግ ግማሽ ማራቶንን ሮጦ ማጠናቀቁ ተዘግቧል።
ሮቦቱ 2፡40፡42 በሆነ ሰዓት በመግባት ነዉ የግማሽ ማራቶን ሩጫን ያጠናቀቀው።
ሮቦቱ የመጀመሪያው በሰው ልጅ የተሰራ ሮቦት ሆኗል ማራቶንን በመሮጥ።
@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS | 4 570 |
| 8 | “አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነሥቶአል።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 15፥20
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለእየሱስ ክርስቶስ የትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ!🙏🙏
@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS | 4 257 |
| 9 | 👀የኮሪደር ልማት ጉዳት ያደረሱ ከብቶች ተቀጡ::
13 ከብቶች የኮሪደር ልማት ላይ ጉዳት በማድረሳቸው 65 ሺ ብር በቅጣት የከብቶቹ ባለቤቶች እንዲከፍሉ ተደረገ
በቦሌ ወረዳ 12 አስተዳደር የኮሪደር ልማት ላይ በቸልተኝነት ጉዳት እንዲደርስ አድርገዋል የተባሉ የከብት ባለቤቶች በ13 ከብት እያንዳንዳቸው 5ሺ ብር በጠቅላላ 65 ሺ ብር እንዲቀጡ በዛሬው እለት ተደርጓል።
የወረዳው ደንብ ማስከበር ጽ/ቤት ማህበረሰቡ ከመሰል ድርጊት እንዲቆጠብ አሳስቧል ።
@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS | 5 928 |
| 10 | ✍️ ትንቢተ ኢሳ 53 : 5 እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችን እና ለመድሐኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ።
@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS | 6 846 |
| 11 | ስጋ‼️
ለበዓሉ በሸማች የህብረት ስራ ሉካንዳ ቤቶች አንድ ኪሎ ስጋ ከ460 እስከ 520 ብር ብቻ እንዲሸጡ ተመን ተቀመጠ‼️
ለፋሲካ በዓል 239 የሸማች የህብረት ስራ ሉካንዳ ቤቶች አንድ ኪሎ ስጋ ከ460 እስከ 520 ብር ብቻ እንዲሸጡ ተመን መቀመጡን የአዲስ አበባ ህብረት ስራ ኮሚሽን አስታወቀ።
የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ልእልቲ ግደይ በዓሉን አስመልክቶ በምርት አቅርቦትና የዋጋ ተመን በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል።
በዚህ መሰረት በከተማዋ ከእሁድ ገበያ በተጨማሪ 137 ባዛሮች በልዩ ሁኔታ በየአካባቢው በመክፈት ማህበረሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን እንዲሸምት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
154 መሰረታዊ የህብረት ስራ ማሀበራትና 11 ዩኒየኖች ከተማዋ ላይ ያለውን የኑሮ ውድነት ባማከለ መልኩ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረቡ መሆናቸውን ተናግረዋል።
800 የሚጠጉ የህብረት ስራ ሱቆች ለበዓሉ ሙሉ አቅርቦትን በመያዝ እየሰሩ መሆናቸውን ኮሚሽነሯ ጠቅሰው፥ በዚህ መሰረት የምርት አቅርቦት ችግር እንዳያጋጥም ከክልሎች ጋር በመተሳሰር እየተሰራ መሆኑን አመላክተዋል።
ለበዓሉ የእርድ እንስሳት ወደ ከተማዋ እንዲገቡ በማድረግ 1 ኪሎ ስጋ ከ460 እስከ 520 ብቻ በማህበራቱ ሉካንዳ ቤቶች እንዲሸጥ በጥናት ተወስኗል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪ በሁሉም የመሸጫ ቦታዎች የእንስሳት ተዋጽኦ ደረጃውን በጠበቀና በተመጣጣኝ ዋጋ ይቀርባል ተብሏል።
✍️ ayuzehabesha
@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS | 5 417 |
| 12 | #እግርኳስ
ዩናይትድ 5 ጨዋታ በተከታታይ ካላሸነፈ ጸጉሬን አልቆረጥም ያለዉ ግለሰብ ጸጉሩን ከተቆረጠ 6 ወር አለፈዉ
👉🏼 ግለሰቡ በዉሳኔዉ ይጸጸት ይሆን?
በስፔን ነዋሪነቱን ያደረገዉ ፍራንክ ኢሌት የተሰኘ የዩናይትድ ደጋፊ ቡድኑ በተከታታይ 5 ጨዋታዎችን ካላሸነፈ ጸጉሩን እንደማይቆረጥ አሳዉቆ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ቻሌንጅ ከጀመረ ዛሬ ላይ 192ኛ ቀኑን ይዟል።
ዩናይትድ የኋልዮሽ ጉዞዉን ቀጥሎ ደጋፊዉም ቀስ በቀስ ወደ ሬጌ ቦይስ ራስታ ስታይል ተከታዮች የሚቀላቀል እየመሰለ ሄዷል።
ከሁሉም አሳሳቢዉ ደግሞ ሊጉ ሊጠናቀቅ እንደመሆኑ ቀጣዩ አመት እስኪመጣ ይህ ደጋፊ ምን ሊሆን ነዉ የሚሉ ጥያቄዎችን ያጭራል።
@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS | 6 180 |
| 13 | " በስህተት የገባልኝን 3.5 ሚሊዮን ብር ለባለቤቱ መልሻለሁ " - አቶ በህጉ ወ/ሚካኤል
በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ በስህተት ወደ አካዉንቱ የገባን 3.5 ሚሊዮን ብር ተመላሽ ያደረገ ግለሰብ ምስጋና እየተቸረው ይገኛል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ዙሪያ በስም ተጠቃሹን ግለሰብ አግኝቶ ያነጋገራቸው ሲሆን የባንክ ባለሙያ አስተያየት እና ምክርም ጠይቋል።
በስህተት የገባላቸዉን 3.5 ሚሊዮን ብር የመለሱት አቶ በህጉ ወ/ሚካኤል ምን አሉ ?
" ከባንክ ወደ ባንክ በሚደረግ የገንዘብ ዝዉዉር ሂደት በተፈጠረ ስህተት ከሌላ ግለሰብ ወደ አካዉንቴ የገባን 3.5 ሚሊዮን ብር ለባለቤቱ ተመላሽ አድርጊያለሁ።
እኔም የስራ ሰዉ ነኝ እንደዚህ አይነት ክስተት ልያጋጥመኝ ይችላል፤ ስለዚህ ገንዘቡ የኔ ስላልሆነና ለባለቤቱ መመለስ ስላለብኝ ሳላቅማማ መልሻለሁ " ሲሉ ጉዳዩን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
አቶ በህጉ አክለዉም " ብዙ ሰዎች ሞኝ እንደሆንኩ፣ መመለስ እንዳልነበረብኝና ብመልስም ከላዩ ቀንሼ መሆን እንደነበረበት አስተያየት ሲሰጡ ሰምቻለሁ፤ ዳሩ ግን ቅድም እንዳልኩት የኔ ያልሆነ ነገር የኔ አይደለም፤ በተለይም እኔም በቢዝነስ አለም ዉስጥ እንዳለ ሰዉ ነግ በኔ እንደሆነ በመረዳት ማድረግ ያለብኝ ነዉ ያደረኩት "ብለዋል።
የባንክ ባለሙያ ስለሁኔታዉ ምን አሉ ?
የአዋሽ ባንክ ፊንፊኔ ቅርንጫፍ ኦፕሬሽንናል ማናጀር አቶ ፉፋ አሰፋ ስለ ጉዳዩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲያስረዱ " ከባንክ ወደ ባንክ በሚደረግ የገንዘብ ዝዉዉር አቶ ቦንሳ ታደለ የተባሉ የባንካችን ደንበኛ ከአንዱ ባንክ አካዉንት ወደ ሌላ ባንክ አካዉንት በአካል ተገኝተዉ በማንዋል ፅፈዉ ሂሳብ ሲያስተላልፉ አንድ ቀጥር ተሳስተዉ ፅፈዉ በመስጠታቸዉ 3.5 ሚሊዮን ብር ወደ አቶ በህጉ ወ/ሚካኤል አካዉንንት ተላልፏል " ሲሉ ገልፀዋል።
ባንኩ ለአቶ በህጉ በመደወል ሁኔታውን ማስረዳቱንና አቶ በህጉም ተባባሪ በመሆን ለባለቤቱ ገንዘቡን ተመላሽ ማድረጋቸውን አስታውቋል።
ለሁሉም የባንክ ተጠቃሚዎች የባንክ ባለሙያዉ ምን አሉ ?
" ከባንክ ወደ ባንክ በሚደረግ የገንዘብ ዝዉዉር ሂደት ይህ ዓይነቱ አጋጣሚ የመፈጠር ዕድሉ ሰፊ ነዉ። ሁሉም ሰዉ በብር ዝዉዉርና አጠቃላይ በባንክ አጠቃቀም ወቅት ተገቢዉ ጥንቃቄ ማድረግ አለበት " ሲሉ አሳስበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS | 6 462 |
| 14 | ኢትዮጵያ በአህዮች ብዛት በዓለም የመጀመሪያ ደረጃን ይዛለች ።
በዓለም ላይ 50 ሚሊዮን አህዮች እንዳሉ የ2025 ሪፖርት ያመለክታል። በኢትዮጵያ 10 ሚሊዮን አህዮች እንደሚገኙ ተገልጿል።
ካለፈው አመት ጋር ሲነፃፀር ብዛቱ የጨመረ ሲሆን በዓለማችን ትንሽ አህዮች ያሉባት ሀገር ሱሪናሜ ስትሆን ሰባት አህዮች ብቻ ይገኛሉ። በአሜሪካ 52ሺህ አህዮች ይገኛሉ።
ኢትዮጵያ በ10.6 ሚሊዮን አህዮች ቀዳሚ ስትሆን ጐረቤት ሀገር ሰሜን ሱዳን በ7.6 ሚሊዮን አህዮች ሁለተኛ ሆናለች።
በ 3ኛ ደረጃ ፓኪስታን 5.8 ሚሊዮን
በ 4ኛ ደረጃ ቻድ 4.6 ሚሊዮን
በ 5ኛ ደረጃ ሜክሲኮ 3.3 ሚሊዮን በመከተል ቦታውን ይዘዋል።
✍️ mussesolomon
@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS | 6 479 |
| 15 | ቻይና የክብደት መጠናቸው ከ50 ኪሎ ግራም በታች የሆኑ ዜጎቿ ከመኖሪያቸው እንዳይወጡ አሳሰበች‼️
በቻይና ሰሜናዊ ክፍል ዝናብ የቀላቀለ ከባድ ነፋስ መከሰቱን ተከትሎ የሰውነት ክብደት መጠናቸው ከ50ኪሎ ግራም በታች የሆኑ ዜጎቿ ከመኖሪያቸው እንዳይወጡ አሳስባለች።
ከሀገሪቱ ደቡባዊ አዋሳኝ ሞንጎሊያ መነሻውን ያደረገው ነፋስ በሰዓት 150 ኪሎ ሜትር በመሸፈን ቤጂንግ፣ ቲያንጂንን እና ሄበይን ጨምሮ የቻይናን ሰሜናዊ ክፍሎች እየመታ ይገኛል።
የነፋስ ጥንካሬ ከ1 እስከ 17 ባለ ደረጃ የሚለካ ሲሆን አሁን ላይ የተከሰተው ከባድ ንፋስ ባለፉት 10 ዓመታት ከተመዘገቡት የመጀመሪያው መሆኑ ተገልጿል።
የተከሰተው ከባድ ንፋስ ደረጃ 13 ሲሆን ዝናብ ፣ በረዶ እና ነጎድጓድ የቀላቀለ መሆኑን የቻይና የአየር ትንበያ ኤጀንሲ ጠቁሟል።
በሁነቱ በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ምንም ዓይነት ጉዳት እንደሌለ ያመላከተው ኤጀንሲው፤ ከ300 በላይ ግዙፍ ዛፎች ተገንድሰው መውደቃቸውን ጠቁሟል።
ይህን ተከትሎ የሰውነት ክብደታቸው ከ50 ኪሎ ግራም በታች የሚመዝኑ ዜጎች በንፋሱ እንዳይወሰዱ በማሰብ ነው ከመኖሪያቸው እንዳይወጡ ማስጠንቀቂያው የተሰጠው።
እንዲሁም ንፋሱ የባሰ አደጋ እንዳያስከትል አስቸኳይ እርምጃዎች እየተወሰዱ ይገኛል። ዛፎች በቀላሉ እንዳይነቀሉ ማጠናከር ብሎም መቁረጥ፣ ፓርኮች እንዲዘጉ እንዲሁም ወሳኝ እና አስፈላጊ ያልሆኑ በረራዎች እንዲሰረዙም ተደርጓል።
ክስተቱን ተከትሎ የቤጂንግ እና ሌሎች የቻይና ሰሜናዊ አካባቢ ጎዳናዎች ጭር ብለው መዋላቸውን አርቲ በዘገባው አመላክቷል።
@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS | 6 405 |
| 16 | በህንድ የተከሰተው ምንድን ነው ?
በህንድ እና ኔፓል ከባለፈው ረቡዕ አንስቶ በጣለው ከባድ ዝናብ ከ100 በላይ ሰዎች ህይወታቸው ማለፉ ተገለጸ::
በምስራቃዊ ህንድ በምትገኘው ቢሀር 82 የሚደርሱ ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን የሀገሪቱ አደጋ ጊዜ መስሪያ ቤት አስታውቋል፡፡
የህንድ ሚትሮሎጂ ተቋም በምዕራብ እና ምስራቅ ህንድ ያሉ ዜጎች ጥንቃቄ እንዲያደርጉም አሳስቧል፡፡
በተመሳሳይ በደቡብ እስያዋ ሀገር ኔፓል በከባድ ዝናብ ምክንያት 8 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉ ተዘግቧል፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዓለም ላይ የሚከሰቱ የመሬት መንቀጥቀጥ፤ አውሎ ነፋሳት፤ እና ከባድ ዝናብ ዓለማችን ፈታኝ የአየር ንብረት ለውጥ እንዳጋጠማት አመላካች ነው ሲል ኢስተርን አይ ዘግቦታል፡፡ | 5 497 |
| 17 | ማኅበረሰቡ በቴሌግራም አማካኝነት የሚላኩለትን አጠራጣሪ ሊንኮች ከመክፈት እንዲቆጠብ ማሳሰቢያ ተሰጠ
ማኅበረሰቡ በቴሌግራም አማካኝነት የሚላኩለትን አጠራጣሪ ሊንኮች ከመክፈት እንዲቆጠብ የኢንፎርሜሽን መረብ አስተዳደር ኤጄንሲ አሳስቧል።
አስተዳደሩ የኢንተርኔት አጠቃቀም በየቀኑ እየጨመረ በሄደበት በዚህ ዘመን፤ ከዚህ ጋር ተያይዘው የሚመጡ ስጋቶችም እየተስፋፉ መሆናቸውን ገልጿል።
በቅርቡም በርካታ አደገኛ የኢንተርኔት አድራሻዎችን (URLs) መርምሮ፣ እነዚህ አድራሻዎች የኢትዮጵያ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በይበልጥ የቴሌግራም ተጠቃሚዎች አካውንቶችን በመንጠቅ ከፍተኛ ስጋት ሊያስከትሉ እንደሚችሉ ማረጋገጡን አስታውቋል።
እነዚህም ከተለያዩ አካላት በቴሌግራም የሚደርሱ ሊንኮች በርካታ አደጋዎችን የሚይዙ ሲሆን፤ የሚከተሉት አደጋዎች በዋናነት ይገኙበታል።
👉 የግል መረጃ መጠለፍ፦ እንደ የባንክ መለያ ወይም የይለፍ ቃል ያሉ መረጃዎችን መሰረቅ፤
👉የማልዌር ስርጭት፦ ስልኮችን ወይም ኮምፒውተሮችን የሚጎዱ ቫይረሶች፤
👉ማጭበርበሪያ፦ ተጠቃሚዎችን በሀሰተኛ ተስፋዎች (እንደ ውርርድ ወይም ኢንቨስትመንት) መታለል እንደሚገኙበት ገልጿል።
በመሆኑም ማኅበረሰቡ በቴሌግራም አማካኝነት የሚላኩለትን አጠራጣሪ ሊንኮች ከመክፈት እንዲቆጠብ ያሳሰበው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር፤ ሰሞኑን በቴሌግራም ከሚላኩና ማኅበረሰቡ በፍጹም ሊከፍታቸው ከማይገቡ ሊንኮች መካከል ጥቂቶቹን ይፋ አድርጓል፡፡
➮ ሰሞኑን በቴሌግራም ከሚላኩና በፍጹም ልንከፍታቸዉ ከማይገቡ ሊንኮች መካከል ጥቂቶቹ ከላይ በምስሉ ተያይዘዋል። | 7 260 |
| 18 | ማኅበረሰቡ በቴሌግራም አማካኝነት የሚላኩለትን አጠራጣሪ ሊንኮች ከመክፈት እንዲቆጠብ ማሳሰቢያ ተሰጠ
ማኅበረሰቡ በቴሌግራም አማካኝነት የሚላኩለትን አጠራጣሪ ሊንኮች ከመክፈት እንዲቆጠብ የኢንፎርሜሽን መረብ አስተዳደር ኤጄንሲ አሳስቧል።
አስተዳደሩ የኢንተርኔት አጠቃቀም በየቀኑ እየጨመረ በሄደበት በዚህ ዘመን፤ ከዚህ ጋር ተያይዘው የሚመጡ ስጋቶችም እየተስፋፉ መሆናቸውን ገልጿል።
በቅርቡም በርካታ አደገኛ የኢንተርኔት አድራሻዎችን (URLs) መርምሮ፣ እነዚህ አድራሻዎች የኢትዮጵያ የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በይበልጥ የቴሌግራም ተጠቃሚዎች አካውንቶችን በመንጠቅ ከፍተኛ ስጋት ሊያስከትሉ እንደሚችሉ ማረጋገጡን አስታውቋል።
እነዚህም ከተለያዩ አካላት በቴሌግራም የሚደርሱ ሊንኮች በርካታ አደጋዎችን የሚይዙ ሲሆን፤ የሚከተሉት አደጋዎች በዋናነት ይገኙበታል።
👉 የግል መረጃ መጠለፍ፦ እንደ የባንክ መለያ ወይም የይለፍ ቃል ያሉ መረጃዎችን መሰረቅ፤
👉የማልዌር ስርጭት፦ ስልኮችን ወይም ኮምፒውተሮችን የሚጎዱ ቫይረሶች፤
👉ማጭበርበሪያ፦ ተጠቃሚዎችን በሀሰተኛ ተስፋዎች (እንደ ውርርድ ወይም ኢንቨስትመንት) መታለል እንደሚገኙበት ገልጿል።
በመሆኑም ማኅበረሰቡ በቴሌግራም አማካኝነት የሚላኩለትን አጠራጣሪ ሊንኮች ከመክፈት እንዲቆጠብ ያሳሰበው የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር፤ ሰሞኑን በቴሌግራም ከሚላኩና ማኅበረሰቡ በፍጹም ሊከፍታቸው ከማይገቡ ሊንኮች መካከል ጥቂቶቹን ይፋ አድርጓል፡፡
➮ ሰሞኑን በቴሌግራም ከሚላኩና በፍጹም ልንከፍታቸዉ ከማይገቡ ሊንኮች መካከል ጥቂቶቹ ከላይ በምስሉ ተያይዘዋል። | 1 |
| 19 | “ምን ተፈልጎ እንደሆነ እስካሁን ለራሴም ያልተመለሰልኝ ጥያቄ ነው”:- ሉላ ገዙ
የብርቱካን ያልሆነው የብርቱካን ታሪክ ለምን በዚህ ደረጃ በሀሰት መስራት እንዳስፍለገ እስካሁን ያልተመለሰልኝ ጥያቄ ነው ትላለች በኢቢኤስ ቴሌቪዥን ፕሮግራም አስተዋዋቂዋ ሉላ ገዙ።
ሉላ ገዙ "የብርቱካን ያልሆነው የብርቱካን ታሪክ" በሚል ርእስ በተሰራው የምርመራ ዘገባ ላይ “የሰው ልጅ ለምን በዚህ ልክ ሊሆን ይችላል? በቃ ስጠይቅ የነበረው እንዴት? ለምን? ምን ተፈልጎ ነው? እስካሁንም ያልተመለሰልኝ ጥያቄ ነው ለራሴም” ብላለች።
@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS | 7 927 |
| 20 | የማስጠንቀቂያ መልእክት 🚫
ለቴሌግራም ተጠቃሚዎች በቴሌግራም የሚላኩልንና በፍፁም ልንነካቸው የማይገቡ ሊንኮች
@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS | 6 979 |
