የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe
﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student |
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe
کانال የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe (@yahyanuhe) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 21 005 مشترک است و جایگاه 3 803 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 1 605 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 21 005 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 11 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 829 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 28 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 21.39% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 8.48% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 4 493 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 781 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 93 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student |”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 12 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 11 ژوئن | +28 | |||
| 10 ژوئن | +12 | |||
| 09 ژوئن | +20 | |||
| 08 ژوئن | +18 | |||
| 07 ژوئن | +1 | |||
| 06 ژوئن | +6 | |||
| 05 ژوئن | +11 | |||
| 04 ژوئن | +15 | |||
| 03 ژوئن | +34 | |||
| 02 ژوئن | +6 | |||
| 01 ژوئن | +166 |
| 2 | በአርሲ የተፈጸመውን አሰቃቂ የንጹሐን ግድያ ሁሉም ወገን በጋራ እያወገዘው ይገኛል። በእርግጥም የንጹሐን ዜጎች ግድያ እጅግ አሳዛኝና አስነዋሪ ድርጊት ነው። ከሰሜን እስከ ደቡብ፣ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ መሞትን ክፉኛ ተላምደነው፣ የንጹሐን ሞት ከተራ የዜና ማሟያነት ማለፍ ያቃተበት አሳዛኝ ዘመን ላይ ደርሰናል።
በዚህ መሃል፣ ያለምንም የዘርና የእምነት ልዩነት ሁሉም ኢትዮጵያዊ ግድያውን እያወገዘ ባለበት በአሁኑ ወቅት፣ የአንዳንዶች አካሄድ ግን እጅግ እንግዳና አስገራሚ ሆኖ እናገኘዋለን። "ለምን አላወገዛችሁም?" ብለው ሲወርፉ የነበሩ ሰዎች፣ ተገቢውን ውግዘት ሲሰሙ ደግሞ መልሰው "እናንተ ራሳችሁ ናችሁ ገዳዮቹ!" በማለት፣ ማኅበራዊ ሚዲያውን በንጹሐን ደም በሚነግድ ጸያፍ የፖለቲካ ትርክት ሊሞሉት ይሞክራሉ። በእርግጥ የእነዚህ ሰዎች ዋና ዓላማና ፍላጎት ምንድን ነው?
በእነዚህ ንጹሐን ዜጎች ደም እና መከራ የፌስቡክ ላይክ እና ሼር ለመሰብሰብ ስትሽቀዳደሙ ጥቂት እንኳ አታፍሩም? አንድ ሰው ለወገኑ ያለውን ልባዊ ሐዘኔታ ለመግለጽ የእናንተን ፈቃድና ይሁንታ የሚጠብቅ የሚመስላችሁ፣ ራሳችሁን በምን ዓይነት የሥነ-ልቦና ልዕልና ውስጥ አስቀምጣችሁት ነው? እውነታው ሲፈተሽ፣ ስለሟቾች ጉዳይ "በእምነት ይመስሉናል" ከማለት ባለፈ፣ መሞታቸው ትዝ የሚላችሁ ፌስቡክ ላይ ስትገቡ ብቻ መሆኑን ሕሊናችሁ ጠንቅቆ ያውቀዋል።
እባካችሁ በንጹሐን ደም መነገድ ነውር ነውና ከዚህ እኩይ ምግባራችሁ ታቀቡ! በዚህ የሐዘን ወቅት ሆን ብለው በንጹሐን ሞት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘትና መከፋፈልን ለመፍጠር የሚጥሩ አካላትን "ተው!" ማለትና ማውገዝ፣ ከጤናማና ሰላም ወዳድ ዜጎች ሁሉ የሚጠበቅ ኃላፊነት ነው።
⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
https://t.me/Yahyanuhe | 3 596 |
| 3 | በዚህ ፈታኝ ወቅት ለዳዕዋ ሥራችን የቴክኒክ ባለሙያዎች እገዛ እንሻለን!
በቅርቡ ሁላችንም እንደምንታዘበው፣ በክርስቲያን ወገኖቻችን በኩል እስልምናን በተመለከተ የሚነሳው ውዝግብ፣ ትችትና ያልተገባ ንግግር ከምንጊዜውም በላይ ጨምሯል። በዚህ ወሳኝ ሰዓት እምነታችንን በዕውቀት መከላከልና ለሚነሱት ማደናገሪያዎች ትክክለኛውን መረጃ ምላሽ ማድረስ እጅግ አስፈላጊ ነው።
ይህን ታላቅ የዳዕዋ ሥራ በሰፊው ለማድረስ ደግሞ፣ ከፍተኛ ተደራሽነት ያለው መድረክ የግድ ይለናል። እንደምታውቁት ከ100 ሺህ በላይ Followers የነበሩትና፣ በሶስት ወራት ውስጥ ብቻ ከ20 ሚሊዮን በላይ ተደራሽነት ወይንም Reach የነበረው ዋነኛው የፌስቡክ ገጼ ከተዘጋ አሁን ከ3 እስከ 4 ወራት አልፈውታል። ይህ ገጽ በነበረን የዳዕዋ እና የንጽጽር ሥራ ላይ ትልቅ ምሽግ የነበረ ሲሆን፣ አሁን ግን በተለይ በዚህ ጫና በበዛበት ወቅት መዘጋቱ የራሱን ክፍተት ፈጥሯል።
ስለዚህ፣ ይህንን ገጽ በማስመለስ በኩል ሊያግዘኝ የሚችል የቴክኒክ ባለሙያ እፈልጋለሁ። በተለይም የፌስቡክ 'ብሉ ባጅ' (Meta Verification) ያለው እና ከፌስቡክ ኮንታክት ሴንተር ጋር በቀጥታ በመነጋገር ገጹን ማስከፈት የሚችል አቅም ያለው ወንድም ወይም እህት ካለ፣ እባካችሁ አግዙኝ። ይህን በማድረግዎ በግልዎ ለዚህ የዳዕዋ መስመር ትልቅ አሻራዎን እያኖሩ ነው።
ይህንን ማድረግ የምትችሉ ባለሙያዎች፣ እባካችሁ በውስጥ መስመር ወይም በዚህ የቴሌግራም አድራሻ አናግሩኝ፦ @Yahyanuhe1
አላህ ለዲኑ የምንለፋበትን አቅም ይስጠን። ሼር በማድረግ ትክክለኛው ሰው ዘንድ እንዲደርስ ተባበሩኝ! | 3 866 |
| 4 | እስልምናን ለተቀበሉ ሙስሊም ወንድምና እህቶች የተዘጋጀ መሠረታዊ ዲን ሥልጠና!
ወደ ውቡ የኢስላም ጎዳና በቅርቡ ለተቀላቀሉ (ለሰለሙ) ወንድሞች እና እህቶች በሙሉ፤ እነሆ ጥራቱን በጠበቀ መልኩ፣ ብቁ በሆኑ አሰልጣኞች የሚሰጥ ልዩ እና ነፃ የሁለት ወራት የአካል ሥልጠና ተዘጋጅቷል።
ቦታ፡ አዲስ አበባ፣ ጦር ኃይሎች አካባቢ
የሥልጠና ጊዜ፡ ለሁለት ወራት (በአካል የሚሰጥ)
በዚህ ሥልጠና የሚዳሰሱ ዋና ዋና የትምህርት ዘርፎች፦
• የቁርኣን ትምህርት፦ መሠረታዊ የቁርኣን አቀራር እና ትርጉም
• ፊቅህ፦ የዕለት ተዕለት ኢስላማዊ ሕግጋት እና አፈጻጸም
• ዐቂዳ፦ መሠረታዊ የሃይማኖቱ እምነት እና ምሰሶዎች
• ሲራ፦ የነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) አርአያነት ያለው የሕይወት ታሪክ
• ሹቡሃት፦ በእስልምና ዙሪያ ለሚነሱ ብዥታዎችና ጥያቄዎች የሚሰጡ ምላሾች
• ሕይወትን በእስልምና፦ እምነትን በዕለት ተዕለት ሕይወት ውስጥ መተግበር (ከቅርብ ክትትልና ሥነ-ልቦናዊ ድጋፍ ጋር የተዋሃደ)
ሥልጠናው ሙሉ በሙሉ ነፃ ሲሆን፣ ቦታው ሳይሞላ ፈጥነው ይመዝገቡ። ይህንን መልእክት ለሌሎች በማካፈልና ሼር በማድረግ አዳዲስ ሙስሊም ወንድምና እህቶቻችን መረጃው እንዲደርሳቸው የበኩልዎን አስተዋጽኦ ያድርጉ!
🔗 ለመመዝገብ ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ፦
https://forms.gle/ugsXL6MM2QR1T1k99 | 5 822 |
| 5 | بدون متن... | 3 272 |
| 6 | በኦርቶዶክስ_ቤተ_እምነት_መካከል_ያለው_ልዩነት.pdf | 4 451 |
| 7 | ከሰሞኑ አባቴ በታሪክ ውስጥ አያቶቹ ስላሳለፉት ከባድ የፈተና ዘመን ሲያጫውተኝ ነበር። በአፄ ዮሐንስ አራተኛ ዘመነ መንግሥት፣ የቀደሙት አያቶቻችን እምነታቸውን እንዲቀይሩ (እንዲከፍሩ) ካልሆነ ግን ሕይወታቸውን እንዲያጡ የተደረገበትን ያንን መራር ውጣ ውረድና የታሪክ ጠባሳ በቅርበት ከሰማው በዝርዝር አስታወሰኝ።
ይህ የታሪክ እውነት በቀጥታ የሚያገናኘን በ1870 ዓ.ል ወደተካሄደው የቦሩ ሜዳ ጉባኤ ነው። በዚያ ዘመን "እምነትህን ቀይር፣ ካልሆነ ግን አንገትህን እቀላሃለሁ" በሚል መመሪያ በወሎና በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች ላይ አሰቃቂ ግፍ ተፈጽሟል። እምነታቸውን አንቀይርም ያሉ ወገኖች ንብረታቸው ተወርሷል፣ ሀገር ጥለው እንዲሰደዱ ተደርገዋል፣ አልፎም ለሕይወት መጥፋት ተዳርገዋል።
እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ፣ በቅርቡ የትግራይ ኦርቶዶክስ ሲኖዶስ (መንበረ ሰላም) አፄ ዮሐንስ አራተኛን "ቅዱስና ሰማዕት" በማለት ሰይሟቸዋል። እዚህ ላይ በሰከነ እና በምክንያታዊነት ልንጠይቅ የሚገባው ትልቅ ጥያቄ አለ፦ በአሥር ሺዎች የሚቆጠሩ ሰላማዊ ሙስሊሞችን እምነት በሃይማኖት ነፃነት መርህ ፈንታ በኃይል ለመቀየር የሞከረንና ደም ያፈሰሰን መሪ፣ በምን ዓይነት ሰብአዊ ወይም መንፈሳዊ መመዘኛ ነው "ሰማዕት" ተብሎ ሊጠራ የሚችለው?
ይህ ዓይነቱ አሰያየም በውስጡ እጅግ አደገኛ መልእክት ይዟል። ሰላማዊ ዜጎችን በሃይማኖታቸው ምክንያት ማስገደድና መግደል "ቅድስናን ወይም ሰማዕትነትን ያሰጣል" የሚል ትርክት ማራመድ፣ ለወደፊቱም ቢሆን ተመሳሳይ ተግባራትን እንደ ትክክለኛ መንገድ ማጽደቅ ይመስላል። ይህ ደግሞ ለዘመናት ለኖረችው ሀገራችንና ለሕዝቦች አብሮነት ትልቅ ጠንቅ ነው።
እዚህ ላይ ግን አንድ ትልቅ መሥመር ማስመር ያስፈልጋል። ሰላምና እኩልነትን የሚሻው ሰፊው የትግራይ ሕዝብ የዚህ ዓይነቱ እኩይ እና አስገዳጅ ታሪካዊ ነውር ተጋሪ እንዳልሆነ ምንም ጥርጥር የለውም። ሕዝቡንና ይህንን ውሳኔ ያስተላለፉትን ጥቂት የሃይማኖት መሪዎች ነጥሎ ማየት ግድ ይላል። ይህንን የተሳሳተ ውሳኔ የወሰኑት የሲኖዶሱ አካላት ግን፣ ከታሪክ ስህተት ተምረው የሕዝቦችን ስሜት ከማክበር ይልቅ፣ ዛሬም ድረስ በታሪክ ጠባሳ ላይ መርዝ የሚረጩ መሆናቸውን ማወቅና መረዳት ያስፈልጋል።
ታሪክን የምንፈትሸው ለበቀል ሳይሆን፣ ካለፉ ስህተቶች ተምረን የተሻለችና የሁሉንም ዜጎች እምነትና ማንነት የምታከብር ሀገር ለመገንባት ነው። አላህ እውነቱን የምናይበትን ልቦና ይስጠን።
⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
https://t.me/Yahyanuhe | 3 961 |
| 8 | بدون متن... | 3 608 |
| 9 | የዚህ ሥራ መነሻ ከሰባት ዓመታት በፊት የተጻፈ መለስተኛ አርቲክል ነው። በወቅቱ ከወንድሜ ቢላል ሐበሺ ጋር በመሆን በንጽጽር ዳዕዋ እንቅስቃሴ ውስጥ አንድ የተለየ ኃላፊነት ለመውሰድ አስበን ነበር።
የዚህ ጥረት ዋና ዓላማ፣ ልክ አሁን እንደምናየው ከኦርቶዶክስ ወገን ይደርሱ የነበሩ ተደጋጋሚ ትችቶችንና ያልተገቡ ንግግሮችን በተጨባጭ መረጃ ለመመለስ ነበር። ከመጽሐፍ ቅዱስ ንጽጽር ባለፈ፣ በቀጥታ ወደ ውስጣዊ መጻሕፍቶቻቸው (ድርሳናት እና ገድላት) መግባት አስፈላጊ መሆኑን አመንበት።
በንጽጽሩ በኩል ምላሽ የሚሰጡ ሌሎች ወንድሞች ስለነበሩ፣ ይህንን ዘርፍ በተለየ መልኩ መያዙ የተሻለ ነው በሚል ወደ ስራው ተገባ። በአላህ እገዛ፣ ከሁለት መቶ በላይ ድርሳናት ተሰባስበው፣ ከሦስት መቶ እስከ አራት መቶ የሚደርሱ ጽሑፎችን በማዘጋጀት ሰፊ ጥረት ተደርጓል (በዚህም አብዛኛው የድካም ፍሬ የወንድማችን ቢላል ነበር)።
ራሱን በቻለ የፌስቡክ ገጽ እና ቻናሎች ሲሰራጭ የነበረው ትምህርት፣ አልሐምዱሊላህ፣ መልካም ውጤት ነበረው። አብዛኛው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ የራሱን ድርሳናት በደንብ ስለማያውቅ፣ መረጃዎቹ ሰፊ ግንዛቤን የፈጠሩ ነበሩ። ፕሮቴስታንቶች ከሚያነሱት ትችት በተለየ፣ ከእኛ እምነት መነጽር የቀረቡት አዳዲስ ነጥቦች፣ ብዙዎች እምነታቸውን በምክንያት እንዲመረምሩ ሰበብ ሆኗል።
ወንድሜ ቢላል በግል ውሳኔው ከማኅበራዊ ሚዲያ ራሱን ለማራቅ ሲወስን፣ ስራው በመጠኑም ቢሆን ቢዳከምም፣ የተጀመረው በጎ ጥረት እንዳይቋረጥ በማሰብ በወቅቱ የተጻፉትን ጽሑፎች የማረምና የማስፋት ሥራ ለመስራት ሲሞከር ቆይቷል። ከእነዚህም ውስጥ አንዱ የሆነውና በየጊዜው ሲዳብር የቆየው ይህ የኦርቶዶክስ ቤተ እምነትን የውስጥ አስተምህሮና ታሪካዊ ክፍፍል መሠረት ያደረገው ሥራ፣ አልሐምዱሊላህ ዛሬ ላይ በቂ መረጃ መስጠት በሚችል መልኩ ተሰናድቷል።
ሰሞኑን የሚስተዋሉትን ያልተገቡ ንግግሮችና ጥያቄዎች ተከትሎ፣ ጉዳዩን በመረጃ ማሳየትና ግልጽ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፣ የተበታተኑት ጽሑፎች ተሰባስበው ለታሪክ በሚቀመጥ የፒዲኤፍ ሰነድ ተዘጋጅተዋል።
ይህ ሰነድ በዚህ ዙሪያ መሠረታዊ እውቀት ማግኘት ለምትፈልጉ እና በውይይት መድረኮች ለምትሳተፉ ሁሉ፣ እንደ ጠንካራ የሙግት መሣሪያ ሆኖ ያገለግላል ብየ ተስፋ አደርጋለሁ።
በአላህ ፈቃድ፣ ዛሬ ማታ 3፡00 ሰዓት ላይ በቴሌግራም ቻናል ይለቀቃል። የቴሌግራሙን ሊንክ በመጀመሪያው ኮሜንት ላይ ታገኙታላችሁ።
ተቀላቀሉ፣ አመሰግናለሁ።
⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
https://t.me/Yahyanuhe | 4 226 |
| 10 | بدون متن... | 2 957 |
| 11 | በሙስሊሙ የውስጥ አጀንዳ ዙሪያ በሰፊው የምትናገሩ ኦርቶዶክሳውያን ወገኖቼ በመካከላችሁ ስላለው የካራ (ተዋሕዶ)፣ ቅባት እና ጸጋ አስተምህሮታዊ ልዩነቶችና ታሪካዊ ሒደቶች ምን ያክል ታውቃላችሁ? ደጀ ሰላም ላይ ከመምህራኖቻችሁ የማትሰሟቸውን እስከ መጋደል ያደረሱትን የልዩነት ነጥቦች ጥንታዊ መጽሀፍቶቻችሁን መሠረት በማድረግ እለቃለሁና ጠብቁኝ።፣ በጨዋነት እንወያይባቸዋለን።
⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
https://t.me/Yahyanuhe | 3 230 |
| 12 | ከተማ ለምሁሩ፣ ገጠር ለገበሬው - ስልታዊ የቦታ አመራረጥ
የሚሽነሪዎች እንቅስቃሴ በዘፈቀደ የሚደረግ የጉዞ ታሪክ አይደለም፤ ልክ እንደ ቼዝ ጨዋታ እያንዳንዱ እንቅስቃሴ በጥልቀት የታሰበበት ነው። በስትራቴጂ ሰነዶቻቸው ላይ በግልጽ እንደሰፈረው፣ ሚሽነሪዎች ከተማን እና ገጠርን የሚቆጣጠሩበት መንገድ ፈጽሞ የተለያየ ነው። በከተሞች ውስጥ የትምህርት ተቋማትን በማስፋፋት፣ የባለስልጣናትንና የሀብታሞችን ልጆች ኢላማ ያደርጋሉ። ይህም ወደፊት ሀገሪቱን የሚመራውን ምሁራዊና ፖለቲካዊ መደብ በሃሳብ ለመቆጣጠር የሚያስችል የረጅም ጊዜ ስልት ነው።
በገጠር ደግሞ አካሄዳቸው ይቀየራል። የገጠሩን ማህበረሰብ የሚቀርቡት በነገረ-መለኮት ክርክር ሳይሆን፣ በመሰረታዊ ፍላጎቶች ማለትም በግብርና ልማት፣ በውሃ ቁፋሮ እና በጤና ጣቢያዎች በኩል ነው። ከተማውን በአእምሮ፣ ገጠሩን ደግሞ በሆድ የመያዝ ይህ የተቀናጀ ስልት፣ የሙስሊሙን ዓለም ከሁለት አቅጣጫ አጣብቆ ለመያዝ የተነደፈ ነው። ምሁሩን በስልጣኔ ስም፣ ድሃውን ደግሞ በእርዳታ ስም የርዕዮተ-ዓለማቸው ተገዥ የማድረግ ይህ ስልታዊ ምህንድስና፣ ያለምንም የጦር መሳሪያ ሀገርን የመቆጣጠር ረቂቅ ጥበብ ነው።
በቀጣዩ ክፍል የምንዳስሰው አጀንዳ፡
የህክምና ማዕከላትን እንደ ስነ-ልቦናዊ ማደንዘዣ የመጠቀም ሚስጥርን በቀጣይ ክፍል - 13 በአላህ ፍቃድ እንመለከተዋለን።
የመረጃ ምንጮች፦
• The Mission Thinking of the Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus, Thesis.
• Donald Crummey, "Priests and Politicians: Protestant and Catholic Missions".
| 4 326 |
| 13 | بدون متن... | 3 633 |
| 14 | የባዕድነትን ገጽታ በማውለቅ ተመሳስሎ መቅረብ (Indigenization)
የማንኛውም ስውር ወረራ ታላቁ ስኬት የሚለካው፣ ተወራሪው ማህበረሰብ ወረራውን እንደራሱ የባህል አካል አድርጎ ሲቀበለው ነው። የሚሽነሪዎች እንቅስቃሴ በታሪክ ውጤታማ ከነበረባቸው መንገዶች አንዱ የባዕድነት መልኩን በመቀየር "ሀገር-በቀል" (Indigenization) የማድረግ ስልቱ ነው። ይህ ስልት የውጭ ጽንሰ-ሀሳቦችን በአካባቢው ቋንቋ፣ ዜማ፣ ባህላዊ ልብስ እና የአስተዳደር መዋቅር ውስጥ በመክተት፣ ማህበረሰቡ አዲሱን ርዕዮተ-ዓለም ያለ ምንም ጥርጣሬ የራሱ አድርጎ እንዲቀበለው የማድረግ ረቂቅ ጥበብ ነው።
በተለይም በኢትዮጵያ የወንጌላውያን እንቅስቃሴ ታሪክ ውስጥ እንደሚታየው፣ ባህላዊ የሙዚቃ ዜማዎችን እና የሀገር በቀል ስልቶችን ለስብከት አገልግሎት ማዋል ዋነኛ ስትራቴጂ ሆኖ አገልግሏል። ማህበረሰቡ በለመደው ቋንቋና ዜማ ሲነገረው፣ በባዕድ እና በሀገር በቀል አስተሳሰቦች መካከል ያለው ልዩነት ይደበዝዝበታል። ይህ ስልታዊ ውህደት፣ አንድ ማህበረሰብ ሳይነቃ በገዛ ልማዱ ማዕቀፍ ውስጥ አዳዲስ እሴቶችን እንዲያስተናግድ የሚያስገድድ ምሁራዊ ንድፍ ነው። ሃይማኖቱ ከውጭ የመጣ ቢሆንም፣ አቀራረቡ ግን የጓዳ እስኪመስል ድረስ በማላመድ የህዝቡን ስነ-ልቦና በቀላሉ መግዛት ተችሏል።
በቀጣዩ ክፍል የምንዳስሰው አጀንዳ፡
የገጠር እና ከተማ ስልታዊ ክፍፍል - ምሁሩን በሃሳብ፣ ገጠሬውን በልማት የመቆጣጠር ስልትን በቀጣይ ክፍል - 12 ላይ በአላህ ፍቃድ እንመለከተዋለን።
የመረጃ ምንጮች፦
• Temesgen Shibru Galla, "The Mission Thinking of the EECMY", 2011.
• Lamin Sanneh, "Translating the Message: The Missionary Impact on Culture".
መረጃውን ሼር በማድረግ ማህበረሰባችንን እናንቃ! የእርስዎ ተሳትፎ ትውልድን ያነቃል!
⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
https://t.me/Yahyanuhe | 4 404 |
| 15 | بدون متن... | 3 351 |
| 16 | ነገ የዓለም ሙስሊሞች የዒድ አል-አድሃ በዓልን በአንድነት ያከብራሉ። ይህ በዓል ግን ከበዓልነቱና ከመሥዋዕቱ ሥርዓት በላይ፣ እጅግ ጥልቅ የሆነ የፍቅር፣ የፈተና እና የታዛዥነት ታሪክ ያለው ነው።
ነቢዩ ኢብራሂም (ዐለይሂ ሰላም) ልጃቸውን እንዲሠዉ ታዘዙ። አልተከራከሩም፣ አልተግደረደሩም፤ ኢምንት አላመነቱም፣ ፈቃዳቸውን ለአላህ ትዕዛዝ አስገዙ። ነቢዩ ኢስማኤልም (ዐለይሂ ሰላም) ለአባታቸው "አባቴ ሆይ፣ የታዘዝከውን ፈጽም" በማለት በታላቅ የሞራል ልዕልና ታዛዥነታቸውን አሳዩ።
ይህ በዓል የሚያከብረው ይህንን ያለማወላወል በአላህ ላይ ያለ እምነት እና ታማኝነት ነው።
አላህ የሚፈልገው የደም መሥዋዕቱን አይደለም፤ ፈጽሞም ይህንን አይፈልግም። አላህ የሚፈልገው ሰዎች "አምኛለሁ" ሲሉ ምን ያህል በቃላቸው እንደሚጸኑ ነው። እውነተኛ እምነት ማለት ልብን ከዓለማዊ ፍቅር ሁሉ አላቅቆ፣ ለአላህ ብቻ ማስገዛት ነው።
በርግጥ ኢብራሒምና ልጃቸው እንደተጠየቁትም ፈጸሙ፣ በርግጥም እነርሱ በቃላቸው የሚኖሩ እውነተኞች ነበሩ።
በዚህ የተቀደሰ ቀን አላህ ዱዓችንን፣ ጾማችንን፣ መሥዋዕታችንን እና ልመናችንን ይቀበለን። በእምነታችን ቃል ላይ የምንጸናበትን አቅምም ይስጠን።
🐏 መልካም የዒድ በዓል ለርስዎና ለቤተሰብዎ!
تَقَبَّلَ ٱللَّهُ مِنَّا وَمِنكُم
(አላህ ከእኛም ከእናንተም ይቀበለን!)
⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
https://t.me/Yahyanuhe | 5 783 |
| 17 | አመቱን ሙሉ የወረፋ ቀን ጠብቃ ትመጣ የነበረች ውሀ ድንገት የሙስሊሙ በኣል ሲደርስ ሆንተብሎ በሚመስል መልኩ ትጠፋለች። ለበአል መዘጋጃ መሠረታዊ የሚባለው ውሀ እንኳን እንደ ቅንጦት ይከለክሉህና ቀንህን የውሀ ቦቲ ግዥ በመፈለግ ታሳልፋለህ (እነሱም በዚህ ሰአት ገበያ ስለሚበዛ በቀላሉ አይገኙም) በየአመቱ ጥያቄያችን ከዚህ መሠረታዊ ፍላጎት እንዳይሻገር ሆኖብሎና አቅዶ የሚሰራ ኃይል ከጀርባ የለም ብሎ ማሰብ ግን ዘበት ነው። | 4 824 |
| 18 | بدون متن... | 5 434 |
| 19 | ሰው እንዴት ኃጢኣቱ ይማርለት ዘንድ ኃጢአቱን ለሌላ ኃጢአተኛ ይናገራል? የንስሀ አባት ነገር ፈጽሞ ከህሊና የራቀ ነው..!
https://t.me/Yahyanuhe | 5 233 |
| 20 | ኢኮኖሚያዊ ጥገኝነትን የመፍጠር ብልኃት!
ለሚሽነሪዎች እንቅስቃሴ ስኬት ዋነኛው ሞተር ከምዕራባውያን ሀገራት የሚፈሰው ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ ነው። ይህ በጀት ትምህርት ቤቶችን፣ ሆስፒታሎችን እና የልማት ድርጅቶችን ለመገንባት ከመዋሉ ባለፈ፣ በአካባቢው የሚገኙ ሰባኪያን እና ሰራተኞች በገንዘብ ኃይል ለምዕራባውያን ርዕዮተ-ዓለም ታማኝ ሆነው እንዲቀጥሉ የሚያደርግ የጥገኝነት መረብ ፈጥሯል። ይህ የገንዘብ ኃይል፣ ማህበረሰቡ የራሱን የቆየ እሴት ትቶ ወደ አዲሱ አስተሳሰብ እንዲመጣ የሚያደርግ "ኢኮኖሚያዊ ጫና" ሆኖም አገልግሏል።
በተለይ በሶስተኛው ዓለም ሀገራት ይህ በገንዘብ የታገዘ ሃይማኖታዊ መስፋፋት፣ ንጹህ መንፈሳዊነት ሳይሆን የምዕራባውያን የኢኮኖሚ የበላይነት ውጤት መሆኑን የስትራቴጂ ሰነዶቻቸው በግልጽ ያሳያሉ። የሰዎችን ችግርና ረሃብ እንደ መግቢያ በር በመጠቀም፣ ሰብዓዊ እርዳታን ለሃይማኖታዊ ስርጭት እንደ ስልታዊ መሳሪያነት ማዋል መቻሉን ምሁራዊ ሰነዶች ያረጋግጣሉ። የኢኮኖሚ ጥገኝነት መፍጠር፣ ያለምንም ቀጥተኛ ግጭት የማህበረሰቡን ስነ-ልቦናዊ መዋቅር የመለወጥ ስልታዊ ስኬት ሆኖ ይመዘገባል።
በቀጣዩ ክፍል የምንዳስሰው አጀንዳ፦
"ሀገር-በቀል" መስሎ በመቅረብ የባዕድነትን ገጽታ አውልቆ የመጣል "ጥበብን" በቀጣይ ክፍል - 11 በአላህ ፍቃድ እንመለከተዋለን።
የመረጃ ምንጮች፦
• Thesis on Mission Thinking, Chapter 4 (Resource Mobilization).
• EECMY Archive regarding Partner Mission Societies.
ጠቃሚ ነው ብለው ካመኑ ሼር ማድረግ አይርሱ!
⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
https://t.me/Yahyanuhe | 9 733 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
