☀ሁዳ መልቲሚዲያ |HUDA MULTIMEDIA
☀ሁዳ መልቲሚዲያ - 🇭🇺🇩🇦 🇲🇺🇱🇹🇮🇲🇪🇩🇮🇦 -قناة هدى الاسلامية ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ንፁህ ኢስላማዊ እውቀት ይደርሳቸው ዘንድ እንሰራለን! ለአስተያየት @nuugaa
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ☀ሁዳ መልቲሚዲያ |HUDA MULTIMEDIA
کانال ☀ሁዳ መልቲሚዲያ |HUDA MULTIMEDIA (@huda4eth) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 21 911 مشترک است و جایگاه 3 602 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 1 524 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 21 911 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 07 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -201 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 0 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 11.15% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 6.46% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 2 443 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 1 415 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 12 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“☀ሁዳ መልቲሚዲያ - 🇭🇺🇩🇦 🇲🇺🇱🇹🇮🇲🇪🇩🇮🇦 -قناة هدى الاسلامية
ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ንፁህ ኢስላማዊ እውቀት ይደርሳቸው ዘንድ እንሰራለን!
ለአስተያየት @nuugaa”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 08 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 08 ژوئن | 0 | |||
| 07 ژوئن | +7 | |||
| 06 ژوئن | +2 | |||
| 05 ژوئن | +7 | |||
| 04 ژوئن | +4 | |||
| 03 ژوئن | 0 | |||
| 02 ژوئن | 0 | |||
| 01 ژوئن | 0 |
| 2 | https://vt.tiktok.com/ZSQNVPG5M/ | 1 316 |
| 3 | ምርጫ ቦርድ ሰብዓዊ መብቷን አክብሮ፣ ነፃነቷን በመጠበቅ ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን ጋር በእኩልነት ቀጥሮ ታስመርጥ ዘንድ የቀጠራትን ኒቃቢስት ሙስሊም ኢትዮጵያዊ ተመልከቱ ... ይህ ኒቃብን በመመሪያ ከልክሎ ሙስሊም ተማሪዎችን ከመማር ማስተማሩ እያደናቀፈ ላለው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እና መሠል ተቋማት ትልቅ ትምህርት ይሆናል። ኒቃብ እሴታችን፣ ባህላችን፣ ማንነታችን፣ እምነታችን ነው። ከመማር፣ ከመስራት አያግድም። እንደለበሱ ይማራሉ፤ እንደለበሱ ይሰራሉ፤ እንደለበሱ ሀገርን ያገለግላሉ።
አትልበሱ፣ አይለብሱም ለሚሉት ጥያቄ አለን፤ ፍትሐዊ መልስ እስኪሰጡ ጥያቄ አለን!
@aaumsu | 3 688 |
| 4 | ሙስሊም ሴቶች ሒጃባቸውን (ኒቃብ) እንደለበሱ መንግስታቸውን ሲመርጡ የሚያሳይ ምስል ነው። ምርጫ ቦርድ የሁሉንም ሀይማኖት እና ባህል ባማከለ መልኩ አግላይ ያልሆነን የምርጫ ስርዓት መዘርጋቱ የሚበረታታ ነው።
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጀምሮ ሒጃብ (ኒቃብ) ለባሽ ሙስሊም ዜጎችን ባገለለ መልኩ የትምህርት ስርዓታቸውን ለመዘርጋት የሚሞክሩ ተቋማት ከዚህ መማር አለባቸው።
መንግስቷን ስትመርጥ ኒቃብ ስለለበሽ ተብላ ያልተከለከለች ኢትዮጵያዊ በመንግስት ተቋም ልትማር ስትሄድ ኒቃብ ስለለበሽ ተብላ የምትከለከለው በየትኛው አመክንዮ ነው?! ከዚህ ታልፎ ይህንን መድሎ ሕጋዊ ለማድረግ የሚሞክር ሕገ-ወጥ መመሪያ ማውጣትስ ምን ማለት ነው?! ሊታረም ይገባል!!
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu | 2 471 |
| 5 | 'ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ፦ "ይህ የወርቅ ሜዳሊያ ድል የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እና የኮሚቴ አባላት መስዋዕትነት ፍሬ ነው"' ሲሉ ተደምጠዋል :: | 2 778 |
| 6 | ታሪካዊው የ“አልማዝ” የክብር ሽልማት ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ የሐጅ ልዑክ ሀገር ቤት ገባ
የዘንድሮው የ1447 ዓ.ሒ የሐጅ ጉዞ እጅግ በላቀ ሁኔታ በስኬት መጠናቀቁን አስመልክቶ፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ዛሬ ግንቦት 23 ቀን 2018 ዓ.ም በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ታሪካዊ የምስራች አብስረዋል። የኢትዮጵያ የሐጅ ልዑክ ከ160 በላይ ከሚሆኑ የዓለም ሀገራት መካከል ቀዳሚ በመሆን፣ ከፍተኛውን እና ታሪካዊውን የ“አልማዝ” የክብር ሽልማት ማሸነፉን ይፋ አድርገዋል።
ቀደም ባሉት ጊዜያት ወገኖቻችን ጥሪታቸውንና ከብቶቻቸውን እየሸጡ፣ በየበረሃው ወራትን በሚፈጅ መንገድ ይንገላቱበት የነበረው የሐጅ ጉዞ ዛሬ ላይ ታሪክ ሆኗል።
ይህ ታላቅ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፣ በተለይም ከታች እስከ ላይ ያሉ የየደረጃው የኮሚቴ አባላት ሌት ተቀን በከፈሉት ታላቅ መስዋዕትነትና ባደረጉት የጋራ ርብርብ ነው። የሳዑዲ አረቢያ የሐጅ እና ዑምራ ሚኒስቴር “ኺታሙሁ ሚስክ” በተባለው ታላቅ መርሃ-ግብሩ ላይ ሽልማቱን ለኢትዮጵያ በይፋ አስረክቧል።
ክቡር ፕሬዝዳንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ዛሬ በምክር ቤቱ ቅጥር ግቢ በተደረገላቸው ደማቅ አቀባበል ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፦ “ጅማሮውንም መጨረሻውን ላሳመረው አላህ ምስጋና ይገባው፤ ከዚህ በፊት የነበረው የሑጃጆች እንግልት አብቅቶ ለመላው ዓለም አርአያ የሆነ አገልግሎት መስጠት ችለናል!” በማለት ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ እና ለምክር ቤቱ አባላት በሙሉ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በ ሀያት ሁሴን | 2 865 |
| 7 | ለሙስሊሞች ተቆርቋሪዋ ሀገር ኤምባሲ የእንኳን አደረሳችሁ መልክት አስተላልፏል😁
አዞ የውሀ ውስጥ እንስሳቷን አስታወሳችዃት?
ወፈር ያለ እንስሳ እንደ የበግ ግልገል የመሰለ ልትውጥ ስትታገል አይኗ ያለቅሳል አሉ!! አይኗ ያለቀሰው ለግልገሉ እዝነት አይደለም! ነገር ግን የበላችው ነገር ትልቅ ስለሆነ አንቋት ነው! እስከምትውጠው ታለቅሳለች አሉ!!
ኢምባሲውም ስለሚወደን የአዞ እምባ እያነባልን መሆኑ ነው¡¡ | 3 837 |
| 8 | ዒድ ሙባረክ! ተቀበለላሁ ሚና ወሚንኩም 🎈✨
አላህ መልካም ስራችንን ይቀበለን። ይህ ቀን የመብላት፣ የመጠጣትና አላህን በብዛት የማውሳት ቀን ነው።
💬 ከሐዲስ፡
ነቢዩ (ﷺ) ስለ ዒድ እና ከዒድ በኋላ ስላሉት ቀናት (አያመተሽሪቅ) ሲናገሩ እንዲህ ብለዋል፦
"የአያመተሽሪቅ ቀናት (ከዒድ በኋላ ያሉ ሶስት ቀናት) የመብያ፣ የመጠጫና አላህን የማውሻ (የዚክር) ቀናት ናቸው።" (ሶሒህ ሙስሊም)
🤝
የተቀያየማችሁትን ይቅርታ ጠይቁ፣ የታመሙትን ጠይቁ፣ ድሆችንና የቲሞችን በደስታችሁ መሀል አስታውሷቸው። ዒዳችሁን ያማረ ያድርግላችሁ! | 2 851 |
| 9 | https://vt.tiktok.com/ZSxHs4GkS/ይህን ቪዲዮ እስከ መጨረሻ ተመልከቱ 👀🔥
የዛሬው መልእክት ለልብህ… 🤍 | 3 352 |
| 10 | 📌ዙልሂጃ 8: "ለነገው ታላቅ ቀን ተዘጋጅተሃል?"
ነገ 9ኛው ቀን (የአረፋ ቀን) ነው። የአመቱ እጅግ በላጭና ምርጡ ቀን! ሐጅ ላይ የሌለን ሙስሊሞች ነገን በመፆም ከአላህ ትልቅ ምንዳ የምንቀበልበት ቀን ነው።
💬 ነቢዩ (ﷺ) ስለ አረፋ ቀን ፆም ሲጠየቁ እንዲህ አሉ።
"የአለፈውን አመትና የመጪውን አመት (ትናንሽ) ወንጀሎች ያስምራል።" (ሶሒህ ሙስሊም)
🚨 ሼር ያድርጉት፦ ዛሬ ሌሊት ሰሑር ለመነሳት ስልክህን አላርም ሙላ፣ ቤተሰቦችህንም ቀስቅስ። አንተ በላክኸው መልእክት ምክንያት አንድ ሰው ቢፆም፣ የአንተ ምንዳ ሳይቀነስ የሱ አይነት አጅር ታገኛለህ! | 3 569 |
| 11 | ዙልሂጃ 7: የአባታችን ኢብራሂምን ፈለግ መከተል! 🐑🔪
አቅም ላለው ሰው በዙልሒጃህ 10ኛው ቀን (የዒድ እለት) ወይም ከዒድ በኋላ ባሉት ሶስት ቀናት (አያመተሽሪቅ) ኡድሒያ ማረድ ትልቅ አጅር አለው።
📖 ከቁርዓን፡
"ለጌታህ ስገድ፤ እረድም (ኡድሒያ አድርግ)።" (ሱረቱ አል-ከውሰር፡ 2)
💬 ከሐዲስ፡
የአላህ መልክተኛ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
"ኡድሒያ ማረድ ለምትፈልጉ ሰው፤ የዙልሒጃህ ጨረቃ ከታየች ጀምሮ ኡድሒያውን እስኪያርድ ድረስ ከፀጉሩም ሆነ ከጥፍሩ ምንም እንዳይቆርጥ (እንዳይነካ)።" (ሶሒህ ሙስሊም)
⚠️ ማሳሰቢያ፦
እርድ ለማረድ ያሰባችሁ ወንድሞችና እህቶች ጥፍርና ፀጉር ከመቁረጥ ተቆጠቡ። አቅሙ የሌለን ደግሞ አላህ በኒያችን አጅሩን እንዲሰጠን እንለምነው። | 2 122 |
| 12 | መፈታት ጠዋፈል አኢፋደአ እና 3ቱ ቀናቶች (አያመ ተሽሪቅ)
በተቀሩት 3 ቀናት የሚሰሩ ስራዎች
ቪዲዮ ቁ 04
ሸይኽ ኢልያስ አህመድ
ለመካ አያ ሆቴል ሁጃጆች ከተሰጠ ትምህርት የተወሰደ
ሁዳ መልቲሚዲያ
T.me/huda4eth
#hajj #ሐጅ #ሀጅ #ሸይኽ_ኢልያስ_አህመድ@huda4eth | 2 411 |
| 13 | ሙዝደሊፋ ማደር፣ ጀምረተል ዓቀባ እና ነህር (እርድ መፈፀም)
ቪዲዮ ቁ 03
ሸይኽ ኢልያስ አህመድ
ለመካ አያ ሆቴል ሁጃጆች ከተሰጠ ትምህርት የተወሰደ
ሁዳ መልቲሚዲያ
T.me/huda4eth
#hajj #ሐጅ #ሀጅ #ሸይኽ_ኢልያስ_አህመድ@huda4eth | 2 518 |
| 14 | ሚና እና የዓረፋ ቀን ውሎ
ሸይኽ ኢልያስ አህመድ
ለመካ አያ ሆቴል ሁጃጆች ከተሰጠ ትምህርት የተወሰደ
ሁዳ መልቲሚዲያ
T.me/huda4eth
#hajj #ሐጅ #ሀጅ #ሸይኽ_ኢልያስ_አህመድ@huda4eth | 3 195 |
| 15 | የሐጅ ዝግጅት እና የሐጅ ኢህራም ቦታና ግዜ
ሸይኽ ኢልያስ አህመድ
ለመካ አያ ሆቴል ሁጃጆች ከተሰጠ ትምህርት የተወሰደ
ሁዳ መልቲሚዲያ
T.me/huda4eth
#hajj #ሐጅ #ሀጅ #ሸይኽ_ኢልያስ_አህመድ@huda4eth | 3 019 |
| 16 | 1. ሜክሲኮ ተባረክ መስጂድ
2. ስታዲየም
3. ፍልውሃ መስጂድ
### ራሳችንን ከፖለቲካ ማፅዳትና የተከለከሉ ነገሮች
የፖሊስ ተወካዮች ባደረጉት ንግግር፣ ባለፈው የረመዳን በዓል የታዩ አንዳንድ ክፍተቶችን በማንሳት፣ በበዓሉ ላይ የኢራንና የፍልስጤም ባንዲራዎችን ይዞ መንቀሳቀስ ፍጹም የተከለከለ መሆኑን አስገንዝበዋል።
> "ይሄ ፖለቲካ ነው፣ ልክ አይደለም። እንዲያውም ዱዓ በማድረግ ወገኖቻችንን ማሰብ ነው ያለብን። በፕሮግራሙ ላይ ህፃናትና አዛውንቶች ስለሚገኙ፣ የመጣንበትን ዓላማ ብቻ አሳክተን መመለስ አለብን። ራሳችንን ከፖለቲካ ማፅዳት ይኖርብናል" ሲሉ የጸጥታ አካላቱ አሳስበዋል።
>
በባነርና በቲሸርት ላይ የተዘጋጁ፣ የጸጥታ አካላት ሊረዷቸው የማይችሏቸውን የዓረብኛ ፅሁፎችንም ይዞ መግባት እንደማይቻልና ፍተሻ ላይ እንደማይለፉ ተገልጿል። ይህ ወቅት የበዓል ብቻ ሳይሆን ቀጣዩ ጊዜ የምርጫም ጭምር በመሆኑ፣ የሀገሪቱን ሰላም ሊያውኩ ከሚችሉ ነገሮች ሁሉም ሰው ራሱን እንዲጠብቅ ጥሪ ቀርቧል።
### ፍተሻን፣ ስርዓትንና አጠቃቀምን የተመለከቱ መመሪያዎች
በዕለቱ የሚከናወኑ የፍተሻና የአስተናገጃ ስራዎችን ስኬታማ፣ ፈጣንና ከሕግ አግባብ ውጭ እንዳይሆኑ ለማድረግ የሚከተሉት ውሳኔዎች ተላልፈዋል፦
* የመግቢያ ሰዓትና ቅድመ-ዝግጅት፦ ስራው ለጸጥታ አካላትና ለአስተባባሪዎች አመቺ ይሆን ዘንድ አስተባባሪዎች ከሕዝቡ ቀድመው በጠዋት በቦታው መገኘት አለባቸው።
* የፍተሻና የአስተናገጃ አቅጣጫ፦ የፍተሻ ስራውን ለማቀላጠፍና ስርዓትን ለመጠበቅ ሴቶች በአንድ አቅጣጫ፣ ወንዶች ደግሞ በሌላ አቅጣጫ በተለየ መስመር እንዲስተናገዱ ይደረጋል።
* የሴቶች ፍተሻ እና ቦርሳዎች፦ ሴቶች በቦርሳቸው ውስጥ በርካታ ቁሳቁሶችን ስለሚይዙ ፍተሻውን አዳጋች እንዳያደርገው የያዙትን ዕቃ መጠን እንዲቀንሱ ወይም አነስተኛ እንዲያደርጉ ተጠይቋል። ፍተሻው በሴትና በወንድ ፈታሾች በጋራ የሚከናወን ሲሆን፣ የሴት አስተባባሪዎች እገዛ ከፍተኛ እንደሆነ ተገልጿል።
* የኮስሞቲክስ ዕቃዎች፦ ሴቶች የሚይዟቸውን የኮስሞቲክስ ዕቃዎች ከመቀማት ይልቅ እራሳቸው ላይ ሞክረው (ፈትሸው) እንዲያልፉ ይደረጋል።
* የካኪ መያዣ ክልከላ፦ ከተማዋን ሊያቆሽሽ የሚችል ማንኛውንም ነገር መያዝ አይቻልም። ካኪን ለዕቃና ለጫት መተቅለያነት የሚጠቀሙበት ወገኖች በመኖራቸው ወደ መስገጃ ቦታ ይዞ መግባት ፍጹም የተከለከለ ሲሆን፣ ምዕመናን የራሳቸውን ንፁህ መስገጃ ብቻ መያዝ ይችላሉ።
* የስታዲየም አጠቃቀም፦ በዓሉ በሚከበርበት ስታዲየም ውስጥ ያለው ቦታ ሙሉ በሙሉ ሳይሞላ፣ ወደ ውጭ ሰው እንዳይቀመጥ አስተባባሪዎች ጥብቅ ቁጥጥር እንዲያደርጉ ታዟል።
### ከጸጥታ አመራሮች የተሰጠ ምላሽና ማረጋገጫ
የጸጥታ አካላትና ከፍተኛ አመራሮች ከአስተባባሪዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽ የሰጡ ሲሆን፣ የሚከተሉትን ዋና ዋና ማረጋገጫዎች ሰጥተዋል፦
1. የሚዲያ ሽፋን፦ ሁሉም ሰው መረጃው አስቀድሞ እንዲደርሰውና ግንዛቤ እንዲኖረው ሰፊ የሚዲያ ሽፋን እንዲኖር ይደረጋል።
2. ክፍተቶችን ማረም፦ ከዚህ በፊት የነበሩትን ክፍተቶች በአሁኑ በዓል ለማስተካከል ከፍተኛ ጥረት ይደረጋል። ይህ ኦረንቴሽን ለአስተባባሪዎች ብቻ ሳይሆን ለሚሰማሩት የፖሊስ አባላትም በተመሳሳይ መልኩ የሚሰጥ በመሆኑ የተቀናጀ አሰራር ይፈጠራል።
3. ከአመራሮች ጋር ያለው ቅርበት፦ ከአመራሮች ጋር በጣም ልዩ የሆነ የሥራ ቅርበትና ግንኙነት ስላለ፣ ማንኛቸውም በመስክ ላይ የሚፈጠሩ ችግሮችን ወዲያውኑ እየተነጋገሩ ለመፍታት ዝግጁነት ተፈጥሯል።
4. ሕጋዊነት፦ "የምንሰራው በሕግና በአሰራር ላይ ተመስርተን ስለሆነ፣ ሕግን አንጥስም" በማለት ስራው በሙሉ ስነ-ስርዓት እንደሚመራ አስገንዝበዋል።
### ከፌደራል ፖሊስ የተሰጠ ምስጋና
ከፌደራል ፖሊስ የተገኙት ኮማንደር ጌትነት በአስተባባሪዎች ላይ እስካሁን ምንም አይነት ችግር እንዳላዩ ጠቅሰው፣ ወጣቶቹ ከፖሊስ ባልተናነሰ መልኩ እየሰሩ መሆኑን መስክረዋል።
ኮማንደሩ አክለውም፦ *"የናንተ ፕሮግራም በሰዓት የተገደበ በመሆኑ ለኛ ምቹ ነው፣ ከባድ ሁኔታ አይፈጥርም። አስተባባሪዎች ከፖሊስ እክል ባልተናነሰ መልኩ እገዛችሁን እንፈልጋለን። የተከለከሉ ነገሮችን አስቀድማችሁ በመናገር ምዕመናን ከማድረግ እንዲቆጠቡ ማድረግ ይኖርባችኋል፤ አታድርጉ የተባለውን ነገር 'አያስፈልግም' በማለት አርሟቸው፣ ተባበሩን። በአግባቡ እናስተናግዳለን፤ የጎደለ ነገር ካለ እናንተና ፈጣሪ ይሙላበት"* ብለዋል።
### የተግባራዊ ስራዎች ማጠቃለያ (Action Items)
በኦረንቴሽኑ ማጠቃለያ ላይ አስተባባሪዎች በአስቸኳይ ወደ ስራ ሊገቡባቸው የሚገቡ ዋና ዋና ተግባራት ተለይተዋል፦
* የጠፉ ልጆችን ወደ ሜክሲኮ ተባረክ መስጂድ፣ ስታዲየም እና ፍልውሃ መስጂድ መውሰድ።
* ካኪ መያዝ እንደማይቻል ለሕዝቡ አስቀድሞ ማሳወቅ።
* ባነር፣ ቲሸርት፣ የፍልስጤም እና የኢራን ባንዲራዎችን ይዞ መግባት ክልክል መሆኑን መቆጣጠር።
* ከምዕመናን የሚጠበቀው ኢዳችንን ሰግደው በሰላም መመለስ ብቻ መሆኑን ግንዛቤ መፍጠር።
* የሴቶች ኮስሞቲክስ ዕቃዎች ላይ እራሳቸው ላይ አስሞክሮ ማሳለፍ።
* ወንዶችንና ሴቶችን በተለያዩ መግቢያ አቅጣጫዎች መምራት። | 2 765 |
| 17 | በአረፋ በዓል አከባበርና ጸጥታ ዙሪያ ከአስተባባሪዎች ጋር የኦረንቴሽን መድረክ ተካሄደ
አዲስ አበባ — የ1447ኛው ዓ.ሂ የኢድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላማዊ መንገድ እንዲጠናቀቅ የራሳቸውን የበኩclean አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እና ከፌደራል ፖሊስ የተወከሉ ከፍተኛ የጸጥታ መኮንኖች ለአዘጋጅና አስተባባሪ ወጣቶች የኦረንቴሽን ስልጠና ሰጥተዋል።
በበዓሉ ስነ-ስርዓት ላይ ስምሪት የተሰጣቸው አስተባባሪዎች ከቦሌ ክፍለ ከተማ፣ ከአራዳ ክፍለ ከተማ እና ከኮልፌ ክፍለ ከተማ የተወጣጡ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች ሲሆኑ፣ በዓሉን ከማንኛውም የፖለቲካ እንቅስቃሴ ነፃ በሆነ መልኩ በሃይማኖታዊ ስርዓቱ ብቻ አክብሮ ማጠናቀቅ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ እንዲሁም ፍተሻን፣ አስተናገድንና ልዩ ጥንቃቄዎችን በተመለከተ ጥብቅ መመሪያዎችና የተግባር አቅጣጫዎች ተላልፈዋል።
### የጠፉ ልጆችን በተመለከተ የተላለፈ ልዩ መመሪያ
በበዓሉ ዕለት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ማህበራዊ እክሎችን አስቀድሞ ለመከላከል የተለየ አቅጣጫ የተቀመጠ ሲሆን፣ አስተባባሪዎችና ምዕመናን በስነ-ስርዓቱ ወቅት የጠፉ ልጆች ካሉ ወዲያውኑ ሰብስበው ወደሚከተሉት አስተማማኝ የእርዳታ ማዕከላት እንዲወስዷቸው በጥብቅ ታዟል፦ | 2 992 |
| 18 | ነገ እሁድ ግንቦት 16/2018 ከአሱር ሶላት በኋላ አስኮ በድር መስጂድ
የአንድነቱ ሜዳ በሚል ርዕስ
ሰፋ ያለ የዳዕዋ ፕሮግራም
በተወዳጁ ዳኢ ኡስታዝ ካሚል ጣሀ
በአካባቢው እና በዙሪያው የምትገኙ ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ተጋብዛችኋል ። | 2 660 |
| 19 | የሐጅ አደራረግ ስልጠና
በሸይኽ ኢልያስ አህመድ
የቀጥታ ስርጭት ከመካ አያ ሆቴል!!
https://www.facebook.com/share/v/17o5TGcPjr/ | 2 574 |
| 20 | 📌 ዙልሂጃ 5፡ ዱዓ እና ልመናን ማብዛት
የልብ ፍላጎቶች የሚመለሱበት ወርቃማ ሰዓታት! 🤲🔥
እነዚህ ቀናት አላህ ዱዓን የሚቀበልባቸው፣ ባሮቹን ከእሳት ነፃ የሚያወጣባቸው ቀናት ናቸው። ፍላጎትህንና የዱንያ የአኺራ ጭንቀትህን ለአላህ የምታቀርብበት ወቅት አሁን ነው።
📖 ከቁርዓን፡
"ጌታችሁም አለ፦ ለምኑኝ እቀበላችኋለሁና..." (ሱረቱ ጋፊር፡ 60)
💬 ከሐዲስ፡
ነቢዩ (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
"በላጩ ዱዓ የአረፋ ቀን የሚደረግ ዱዓ ነው። እኔና ከእኔ በፊት የነበሩት ነቢያት ካልናቸው ቃላት ሁሉ በላጩ፦ 'ላ ኢላሀ ኢለላሁ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ፣ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁዋ ዐላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር' የሚለው ነው።" (ቲርሚዚ)
📣 ትግበራ፦
ለራስህ፣ ለወላጆችህ፣ ለቤተሰብህ እንዲሁም ለኡማው ዱዓ ማድረግን እንዳትረሳ! | 2 815 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
