Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
📈 تحلیل کانال تلگرام Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
کانال Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር) (@ibnumunewor) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 109 338 مشترک است و جایگاه 329 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 260 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 109 338 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 03 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 22 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 6 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 17.23% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 8.39% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 18 837 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 9 172 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“كناشة ابن منور”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 04 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 04 ژوئیه | 0 | |||
| 03 ژوئیه | +23 | |||
| 02 ژوئیه | +10 | |||
| 01 ژوئیه | +3 |
| 2 | ለማንኛውም የበኑ ኡመያ መስለም ከነብዩ ﷺ እና ከኸሊፋዎቻቸው ዘንድ የሚጠረጠር አልነበረም። ሂንድን በተመለከተም መስለሟን ነብዩ ﷺ ከተቀበሏት በኋላ እኛ በጥርጣሬ የምናይበት ምንም አይነት ቀዳዳ የለም። ለሐምዛ እኛ ከነብዩ ﷺ በላይ ተቆርቋሪዎች አይደለንም። ያለ አንድ መረጃ የሰዎችን ያውም የሶሐቦችን እስልምና ጥያቄ ውስጥ መክተት የባለ ^ጌዎች ስራ ነው። የሚገርመው ሐምዛን በማስ7ደል እና ጉበቱን በማኘክ ሂንድን የሚያብጠለጥሉ አካላት በቀጥታ ግድያውን የፈፀመውን ወሕሺይን ግን ሲዘምቱበት እና እስልምናውን ጥያቄ ውስጥ ሲያስገቡ አይታዩም።
ስለዚህ ሂንድም በመስለሟ የተነሳ ከነብዩ ﷺ ምርጥ ሶሐብያት ሆናለች ማለት ነው። ስለሆነም ለሶሐቦች አክብሮት እንዲኖረን የተነገረን ትምህርት ሂንድንም ያካትታል። ሶሐቦችን በክፉ እንዳናነሳ የተሰጠን ማሳሰቢያም እንዲሁ ሂንድንም ይመለከታል።
ደግሞም እፈሩ! አቡ ሉእሉአ ማለት ከነብዩ ﷺ በኋላ የኡማው ሁለተኛ ታላቅ ሰው የሆኑትን ኸሊፋው ዑመርን፣ ሱብሒ ሶላት እያሰገዱ በነበሩበት በመርዛማ ስለት ወግቶ የ7ደለ ነው። ይሄ ሰውዬ እሳት አምላኪ መጁሲ ሙሽሪክ ነው። ሺዐዎች ዘንድ ግን ትልቅ የአላህ ወሊይ ነው። ዑመርን መግደሉን ትልቅ ገድል በማድረግ የተንጣለለ መታሰቢያ ዶሪሕ ገንብተውለታል። ለዚያራም ይመላለሱበታል። መግቢያው ላይም አቡበክርን፣ ዑመርንና ዑሥማንን የሚራገም ፅሁፍ በደማቁ አስፍረዋል። እነዚህ የጥመት ቋቶች እና የነዚህ እርጉሞች ደጋፊዎቻቸው ነጋ ጠባ በኑ ኡመያን ሲያብጠለጥሉ ማየት የሚደንቅ ነው። እንጥፍጣፊ ሞራል ቢኖራቸው ኖሮ በዚህ ልክ ርክስ፣ ቁሽሽ ያሉ ፍጥረቶችና የነሱ ደጋፊ ጭፍራዎች ስለ በኑ ኡመያ የማውራት ሞራል አይኖራቸውም ነበር።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 4 396 |
| 3 | እውን ሂንድ የሐምዛን ጉበት አኝካለችን?
~
ሂንድ ቢንቱ ዑትባህ የአቡ ሱፍያን ባለቤት፣ የሙዓዊየህ እናት ነች። ከመስለሟ በፊት የሐምዛን ጉበት አውጥታ አኝካለኝ በሚል ክስ ዛሬም ድረስ ትብጠለጠላለች። በሺዐዎች በተዘጋጀው አር-ሪሳላህ ፊልም ውስጥ ሂንድን እጅግ ጋጠ ወጥ አድርጎ የሚያሳይ በርከት ያለ ክፍል አለ። በርግጥ ይሄ ከሺዐ የማይጠበቅ አይደለም። ለአቡበክርና ለዑመር ያልተመለሱ ጠማሞች ለሂንድ ይመለሳሉ ተብሎ አይጠበቅም።
የነብዩ ﷺ አጎት የሆኑት የአላህ አንበሳ ሐምዛ ብኑ ዐብዲል ሙጦሊብ ረዲየላሁ ዐንሁ የኡሑድ ጦርነት ጊዜ በሐበሻዊው ወሕሺይ መገ - ደላቸው የሚታወቅ ነው። ከዚያም ሆዳቸው ተቀዶ አካላቸው ተቆራርጦ ነውረኛ ተግባር ተፈፅሞባቸዋል። ታሪኩ እዚህ ድረስ ትክክለኛ መረጃ የመጣበት ነው። ከዚህ ውጭ ግን እንዲህ የሚል ዘገባ አለ።
"ሂንድ ሆዱን ቀዳ ጉበቱን በማውጣት አኘከችው። ልትውጠው ግን አልቻለችም። የአላህ መልክተኛ ﷺ ሲያዩት 'ከእሱ በልታለት ይሆን?' ብለው ጠየቁ። 'አልበላችም' ሲሏቸው 'አላህ የሐምዛን አንድም ክፍል ወደ ጀሃነም እሳት እንዲገባ አይፈቅድም' አሉ።" [ሙስነድ አሕመድ፡ 4414]
ይህንን ዘገባ መነሻ በማድረግ ሂንድን ዛሬም ድረስ ክፉኛ የሚያንቋሽሹ ሰዎች አሉ። ሺዐዎች እንኳ ከዚህም የከፋ ብዙ ነገር ስላላቸው ምንም ቢሉ አይደንቅም። የሚገርመው በነሱ ቅጥፈት ተመርዘው ዛሬም ሂንድን የሚኮንኑ ሰዎች ሁኔታ ነው። ይሄ አካሄድ ስሜትን በሸሪዐ ልጓም አለመቆጣጠር ነው። ሐምዛ ላይ የተፈፀመው ድርጊት እጅግ በጣም የሚያም መሆኑ ግልፅ ነው። ነገር ግን ለሐምዛ ያለን ቁጭትና መቆርቆር መነሻው ኢስላም ከሆነ ኢስላማዊ ህግጋትን ሰው እየመረጥን ልንጥስ አይገባም። በዚህ ክስ ሂንድን የሚያወግዝ አካል ቢያንስ ሁለት መሰረታዊ ነጥቦችን ጥሷል።
#አንደኛው፦ ባልተጨበጠ ዘገባ ላይ ተመርኩዞ ነው ውግዘት ውስጥ የገባው።
ታሪኩ የተላለፈበት ሰነድ ከ0ፋን፣ ከሐማድ፣ ከዐጧእ ብኑ ሳኢብ፣ ከሸዕቢይ፣ ከኢብኑ መስዑድ የሚል ነው። ደረጃው ለማስረጃ የሚበቃ ጥንካሬ የሌለው ደካማ ዘገባ ነው። እንዴት እንደሆነ እንመልከት፦
1. ሸዕቢይ ከኢብኑ መስዑድ አልሰማም። አቡ ሓቲም፣ ዳረቁጥኒይ፣ ሓኪም እና ኢብኑ ሐጀር ይህንን አስረግጠው ተናግረዋል። [አልመራሲል፣ ኢብኑ አቢ ሓቲም ፡ ቁ. 591] [ጃሚዑ ተሕሲል ሊአሕካሚል መራሲል፣ አልዐላኢይ፡ 204] [መዕሪፈቱ ዑሉሚል ሐዲሥ፡ 111] [ተህዚቡ ተህዚብ: 7/419]
2. ዐጧእ ብኑ ሳኢብ ኢኽቲላጥ (የሒፍዝ መደባለቅ) የገጠመው ሰው ነው። ይህንን ኢብኑ መዒን፣ ቡኻሪ፣ ዒጅሊ፣ ኢብኑ ዐዲይ፣ ኢብኑ ቀጧን፣ ኢብኑ ከሢር፣ ኢብኑ ሐጀር ገልፀውታል። [አት-ታሪኹል ከቢር፡ 6/465] [አሥ-ሢቃት፣ ዒጅሊ፡ 332] [አልካሚል፡ 7/72] [ተቅሪቡ ተህዚብ፣ ኢብኑ ሐጀር፡ 1/391] [አድ-ዱዐፋኡል ከቢር፡ 3/398] [አልቢዳያ ወንኒሃያ፡ 5/430] [ተህዚቡ ተህዚብ: 7/207]
ይሄም የዘገባውን ዋጋ ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባ ሌላ ድክመት ነው። የሚከተሉት ሙሐዲሦች ደግሞ ታሪኩ ደካማ እንደሆነ በቀጥታ የገለፁ ናቸው፦
1ኛ፦ ኢብኑ ከሢር [አልቢዳያ ወንኒሃያ፡ 5/430]
2ኛ፦ አልሐይሠሚ
3ኛ፦ አልአልባኒይ [ፊቅሁ ሲራ፡ 279-280]
ታሪኩን ሶሒሕ ወይም ሐሰን በማለት ዋጋ ለመስጠት በሞከሩት አሕመድ ሻኪርና አርነኡጥ ላይ ዘለግ ያለ አጥጋቢ ምላሽ የተሰጠበትን ትንታኔ መመልከት የፈለገ إزاحة الغمة في بيان ضعف قصة أكل هند من كبد حمزة የተሰኘውን ጥናት መመልከት ይችላል።
#ሁለተኛው መሰረታዊ የዘገባው ችግር፦ ከሰነድ ባለፈ መልእክቱ ራሱ ፍፁም የተሳሳተ መሆኑ ነው። ዘገባው ላይ ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል የሚል አለበት:- “አላህ የሐምዛን አንድም ክፍል ወደ ጀሃነም እሳት እንዲገባ አይፈቅድም።”
ይሄ ማለት ሂንድ የእሳት ነች ማለት ነው። ይሄ የተሳሳተ ነው። ሶሒሕ አይደለም እንጂ ሂንድ ድርጊቱን መፈፀሟ ቢረጋገጥ እንኳ ይሄ ተግባር ከመስለሟ በፊት የተፈፀመ ነው። መስለሟ በአስተማማኝ ሰነድ ተረጋግጧል። [ቡኻሪ፡ 3825] [ሙስሊም፡ 1714]
በተለያዩ ሐዲሦች እንደተረጋገጠው ኢስላም የቀደመን ወንጀል ሁሉ ያብሳል። ይህ ከሆነ ድርጊቱን ለመፈጸሟ በቂ መረጃ የለም እንጂ ቢኖርስ ከመስለሟ በፊት በነበረ ጉዳይ እንዴት የእሳት ትሆናለች? ይሄ ከመሰረታዊ የኢስላም አስተምህሮት ጋር የሚቃረን ነው።
በርካታ የምንወዳቸው ሶሐቦችኮ ከመስለማቸው በፊት ሺርክን ጨምሮ ብዙ ከባባድ ወንጀሎችን ፈፅመዋል። ልክ እነዚያ ከመስለማቸው በፊት በተፈፀመ ወንጀል እንደማይወቀሱት ሂንድም ከመስለሟ በፊት በተፈፀመ ድርጊት አትወቀስም። ልክ የሐምዛ ገዳይ የሆነውን ወሕሺይን ከመስለሙ በፊት በፈፀመው ድርጊት ከሰለመ በኋላ እንደማንወቅሰው ማለት ነው። ጌታችን እንዲህ ማለቱ ይታወስ፦
{قُلۡ یَـٰعِبَادِیَ ٱلَّذِینَ أَسۡرَفُوا۟ عَلَىٰۤ أَنفُسِهِمۡ لَا تَقۡنَطُوا۟ مِن رَّحۡمَةِ ٱللَّهِۚ إِنَّ ٱللَّهَ یَغۡفِرُ ٱلذُّنُوبَ جَمِیعًاۚ إِنَّهُۥ هُوَ ٱلۡغَفُورُ ٱلرَّحِیمُ}
"በላቸው 'እናንተ በነፍሶቻችሁ ላይ ድንበር ያለፋችሁ ባሮቼ ሆይ! ከአላህ እዝነት ተስፋ አትቁረጡ፡፡ አላህ ኃጢኣቶችን በመላ ይምራልና፡፡ እነሆ እርሱ መሓሪው አዛኙ ነውና፡፡" [አዝ-ዙመር: 53]
ይህንን ከመሰሉ ሰፋፊ የአላህ የእዝነት አዋጆች ውስጥ ሂንድን ለይተን ልናወጣ ነውን? ለራሳችን ልንፈራ ይገባል። በሌላም ቦታ ጌታችን አላህ ሺርክ የሚፈፅሙ፣ ነፍስ የሚያጠፉ፣ ዝሙት የሚፈፅሙ ሰዎች አሳማሚ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው በዛተበት ላይ ተውበት የሚያደርጉትን ግን እንዲህ ሲል እንደሚምራቸው ገልጿል:-
{إِلَّا مَن تَابَ وَءَامَنَ وَعَمِلَ عَمَلࣰا صَـٰلِحࣰا فَأُو۟لَـٰۤىِٕكَ یُبَدِّلُ ٱللَّهُ سَیِّـَٔاتِهِمۡ حَسَنَـٰتࣲۗ وَكَانَ ٱللَّهُ غَفُورࣰا رَّحِیمࣰا}
"ተፀፅቶ የተመለሰና ያመነ መልካምንም ሥራ የሠራ ሰው ብቻ ሲቀር፡፡ እነዚያም አላህ መጥፎ ሥራዎቻቸውን በመልካም ሥራዎች ይለውጣል፡፡ አላህም እጅግ መሓሪ አዛኝ ነው።" [አል-ፉርቃን፡ 70]
ታዲያ ሂንድን ከሰለመችም በኋላ ከነዚህ የአላህ የተስፋ ቃል ውጭ ልናደርጋት ይቻላል ወይ? አደብ ሊኖረን ይገባል። ሁሉንም ሶሐቦች አላህ መልካም ስራዎቻቸውን ይውደድላቸው።
ከመስለሟ በፊት በተፈጠረ ክስተት ማብጠልጠል ለምን አስፈለገ?
ምክንያቱ ወዲህ ነው። እነዚህ ባ -ለጌዎች የአቡ ሱፍያንንም፣ የሂንድንም መስለም አይቀበሉም። ሺዐዎች እና እነሱን በጥመት የተከተሉ እንደ ሰይድ ቁጥብ ያሉ የኢኽዋን አፈንጋጮች ዘንድ የበኑ ኡመያ ቤተሰቦች ኢስላምንና የነብዩን ﷺ ቤተሰቦች ለመበቀል ነው የሰለሙ የመሰሉት እንጂ ኢማን ወደ ልባቸው አልገባም። በዚህ ደረጃ የነብዩን ﷺ ሶሐቦች ከእስልምና እያስወጡ እያከ^ ፈሩ ለዘብተኛና ሚዛናዊ መስለው ሲተውኑ ስቅም አይላቸውም። | 3 824 |
| 4 | بدون متن... | 3 614 |
| 5 | ዛሬ ጁሙዐ ሰኔ 26/2018 የሒልየቱ ጧሊቢል ዒልም ኪታብ ደርስ ይኖራል፣ ኢንሻአላህ።
* የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ መስጂደል ዋሊደይን
* ጊዜ:- ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
* ኪታቡን በpdf መልኩ በዚህ ታገኙታላችሁ፦ https://t.me/IbnuMunewor/9421
* የዛሬ ደርስ መነሻ:- ገፅ፡ 68
* ቦታው ላይ መገኘት ለማትችሉ ደርሱ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል፡-
https://t.me/IbnuMunewor | 6 640 |
| 6 | ሰሞኑን ደርሶችን በቀጥታ እያስተላለፍኩ ያልሆንኩት ኔትዎርክ ስላስቸገረኝ ነው። በተቻለኝ ቅጂዎቹን በጊዜ ለማያያዝ እሞክራለሁ ኢንሻአላህ። | 9 467 |
| 7 | ደርስ
~
• ሒልየቱ ጧሊቢል ዒልም
• ክፍል:- 26
• የኪታቡ ፋይል በpdf መልኩ በዚህ ሊንክ ይገኛል:- https://t.me/IbnuMunewor/9421
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 66 | 9 361 |
| 8 | ዛሬ ሃሙስ ሰኔ 25/2018 የሒልየቱ ጧሊቢል ዒልም ኪታብ ደርስ ይኖራል፣ ኢንሻአላህ።
* የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ መስጂደል ዋሊደይን
* ጊዜ:- ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
* ኪታቡን በpdf መልኩ በዚህ ታገኙታላችሁ፦ https://t.me/IbnuMunewor/9421
* የዛሬ ደርስ መነሻ:- ገፅ፡ 66
* ቦታው ላይ መገኘት ለማትችሉ ደርሱ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል፡-
https://t.me/IbnuMunewor | 10 020 |
| 9 | +8 ኢስላምን ስታውቅ.....
አላህ ካልመለሰን ነገራችን የሚያሰጋ ሁኔታ ላይ ነው
ኡስታዝ ሙሐመድ ሲራጅ ሙ/ኑር
ከ" ሙራቀባ " ደርስ የተቆረጠ ....
https://t.me/MerkezulimamiAhmed | 10 149 |
| 10 | +5 ክፍል 1
በሙሐመድሲራጅ ሙሐመድኑር
https://t.me/MerkezulimamiAhmed | 7 961 |
| 11 | https://t.me/MedrestuImamuAhmed | 7 945 |
| 12 | ደርስ
~
• ሒልየቱ ጧሊቢል ዒልም
• ክፍል:- 25
• የኪታቡ ፋይል በpdf መልኩ በዚህ ሊንክ ይገኛል:- https://t.me/IbnuMunewor/9421
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 64 | 9 801 |
| 13 | ዛሬ ረቡዕ ሰኔ 24/2018 የሒልየቱ ጧሊቢል ዒልም ኪታብ ደርስ ይኖራል፣ ኢንሻአላህ።
* የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ መስጂደል ዋሊደይን
* ጊዜ:- ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
* ኪታቡን በpdf መልኩ በዚህ ታገኙታላችሁ፦ https://t.me/IbnuMunewor/9421
* የዛሬ ደርስ መነሻ:- ገፅ፡ 64
* ቦታው ላይ መገኘት ለማትችሉ ደርሱ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል፡-
https://t.me/IbnuMunewor | 11 702 |
| 14 | «አህሉል አሠር» የሞባይል አፕልኬሽን
ይህ መተግበሪያ የተለያዩ ኢስላማዊ ደርሶችን በደረጃና በስርዓት ለመማር እጅግ አመቺ ተደርጎ የተዘጋጀ ሲሆን፣ የሚከተሉትን ጠቃሚ ይዘቶች በአንድ ላይ አካቶ ይዟል፦
ዘርፈ-ብዙ የኪታብ ደርሶች፦ የዐቂዳ፣ የመንሀጅ፣ የሲራ፣ የአደብ፣ የሐዲሥ፣ የፊቅህ፣ የነሕው እና የሶርፍ ትምህርቶች።
እያንዳንዱ የድምፅ ቅጂ (ኦዲዮ) ከኪታቡ ሶፍት ኮፒ (PDF) ጋር አብሮ የተያያዘ ነው።
አፑን ለአጠቃቀም ልዩ እና ምቹ የሚያደርጉት ባህሪያት፦
• ደርሶችን ከጀማሪ ጀምሮ ደረጃ በደረጃ በቅደም-ተከተል የሚያስተምር።
• ትምህርቱን ሲጨርሱ ራሶን የሚፈሹበት ፈተናዎች ያሉት።
• በትምህርቱ መሃል አስፈላጊ ነጥቦችን በቀላሉ መፃፍ የሚያስችል ጥሩ ማስታወሻ መያዣ ያለው።
• የደርሶች ማውጫ በየዘርፉ በጥራት የተከፋፈለበት።
• የፈለጉትን ደርስ በቀላሉ መልሰው ለማግኘት ምልክት ማድረግ የሚያስችል።
• ከቅጅዎቹ መካከል የመረጡትን ለሌሎች ማጋራት (Share) የሚያስችል አማራጭ።
• አፑን ለአጠቃቀም አመቺ የሚያደርጉት ማስተካከያዎች ያሉት።
• ደርሱን አቋርጠው በሌላ ጊዜ ማዳመጥ ቢፈልጉ በትክክል ካቆሙበት ሰከንድ የሚጀምር።
የአፕሊኬሽን አዘጋጅ፦ HUDASOFT
https://t.me/hudasoft
ይህ ስራችን የላቀው አላህን ፊት ብቻ ተፈልጎበት የተሰራ (የጠራ) ይሆን ዘንድ፤ በዚህ ስራ ላይ ለተባበሩትም ሆነ ይህንን ስራ ለሚያሰራጩት በሙሉ አላህ መልካም ስራችንን እንዲቀበለን እንማፀነዋለን።
አፑን አሁኑኑ አውርደው ይጠቀሙበት፦
🔗 የማውረጃ ሊንክ (Google Play Store)፦
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.ahlulaser.hs.app | 11 468 |
| 15 | እውነት ለመናገር እንደ ህዝብ በውስጣችን ሰፊ ክፋት ነው ያለብን። ክፋታችን በጣም ስር የሰደደ ከመሆኑ የተነሳ እምነትም፣ ትምህርትም ብዙ አይቀይረንም። ግብይታችን በብዛት በሸፍጥ የተሞላ ነው። የአገልግሎት ቦታዎች ማጉላላትና ማንገለታታት የበዛባቸው ነው። ክፋቱን ሲፈፅም ሁሉም የዳቦ ስም ይፈልግለታል። በአለባበሳቸው ሁሌ አበሳቸውን የሚያዩት ሙስሊም ተማሪዎች የዚህ ክፋት ሰለባ ናቸው። የሚነሱ ነጥቦች ሁሉ ማመሀኛዎች ብቻ ናቸው። ዋናው ምክንያት ክፋት ነው፣ እድሜም፣ መማርም፣ እምነትም የማይቀይረው ምቀኝነት።
በየመንገዱ የምትጠየቁትን መታወቂያ ቀበሌ እንደዋዛ አታገኙትም። ማመሀኛ ሰበቡ ብዙ ነው። ሁላችንም ፖለቲካ እናወራለን። መንግስትን እንተቻለን። እርስ በርስ ያለን ክፋት ግን ተቆጥሮ የሚዘለቅ አይደለም። በየመን፣ በሊቢያ ከሚታገው ወገን ውስጥ አብዛኛው በኢትዮጵያውያን ነው ግፉ የሚደርሰው።
እንዲያውም መከራ እንኳ አያስተምረንም። ተገፋሁ ብሎ የሚያለቅሰው እንዳቅሙ ገፊ ወይም የገፊዎች ደጋፊ ነው። በብሄር፣ በእምነት ብንለያይም ብዙዎቻችንን አንድ የሚያደርገን ብሄራዊ ቅርሳችን ክፋት ነው፣ አንዱ ሌላውን ጠልፎ ለመጣል የሚደረግ ያላሰለሰ ጥረት።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 12 678 |
| 16 | ከማይፈቀዱ የቀልድ አይነቶች ውስጥ
~
የአላህ መልክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
لا يأخذُنَّ أحدُكم متاعَ أخيه لاعبًا ولا جادًّا
“ከናንተ ውስጥ ማናችሁም የወንድሙን ዕቃ በቀልድም ሆነ በምር አይውሰድ።”
አቡ ዳውድ (5003) እና ቲርሚዚይ (2160) ዘግበውታል። [ሶሒሑ ተርጊብ፡ 2808]
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 14 125 |
| 17 | بدون متن... | 12 933 |
| 18 | የኪታቡ ተውሒድ ደርስ
* በሑዘይፋ መስጂድ እየቀረበ ያለ
* ክፍል - 04
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 12 388 |
| 19 | የአላህ መልክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
مَن قال في مؤمنٍ ما ليس فيهِ؛ أسكنَهُ اللهُ رَدغةَ الخَبالِ، حتى يخرُجَ ممَّا قالَ
"በሙዕሚን ላይ የሌለበትን የተናገረበት ሰው፤ ከተናገረው ነገር እስካልወጣ ድረስ አላህ ከጀሃነም ሰዎች አካል በሚወጣ የእዥና የመ^ግል አረንቋ ውስጥ ያኖረዋል።"
[ሶሒሑ ተርጊብ፡ 2845]
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 15 841 |
| 20 | 📌 የጁሙዓ ኹጥባ (ምክር) - 11
🔶 የክረምት ዕረፍት በትርፍ እና በኪሳራ መካከል!!
https://t.me/AbumuslimAlarsi/14209 | 12 450 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
