Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
📈 تحلیل کانال تلگرام Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
کانال Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር) (@ibnumunewor) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 109 869 مشترک است و جایگاه 310 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 282 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 109 869 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 03 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 483 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 12 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 13.16% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 7.31% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 14 454 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 8 032 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“كناشة ابن منور”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 04 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 04 سپتامبر | +10 | |||
| 03 سپتامبر | +26 | |||
| 02 سپتامبر | +2 | |||
| 01 سپتامبر | +4 |
| 2 | ኢኽወቲ ወአኸዋቲ ፊ'ላህ!
~
አመለካከታችንም፣ ግንዛቤያችንም ስለሚለያይ የምፅፈው ሁሉ ለሁሉ ሰው ይስማማል ተብሎ አይታሰብም። የማንም የግል ፀሐፊ አይደለሁምና የማምንበትን እንጂ ሰው እንዳይከፋ እያልኩ እንደማልፅፍ ማሳወቅ አይጠበቅብኝም። ከዚህ በተቃራኒ፣ ሰው እንደመሆኔ ራሴን ማጥራራት ባልፈልግም፣ ማንንም ለማብሸቅና ለእልህ ከመፃፍም እጠነቀቃለሁ ብዬ አስባለሁ። መነገር አለበት ብዬ የማምንበትን ሃሳብ ሰዎችን እንደሚያስከፋ እያወቅኩም ለመናገር እሞክራለሁ። ይሄ አካሄዴ ለአንዳንዶቻችሁ እልህ፣ ለሌሎች የሒክማ ማጠር፣ ለሌሎች ደግሞ ከፋፋይነት ሊሆን ይችላል። የውስጤን አላህ ያውቃል። በኔ ቤት ለወገኔ ይበጃል የምለውን ማካፈሌ ነው።
የሆነ ሆኖ ሃሳቤ በቀጥታ በፅሁፌ የማሰፍረው ነው። የምደብቀውም የለኝም፣ የምደብቅበትም ምክንያት የለኝም። ይህን የምለው "በዚህ ንግግሩኮ ይህንን ነው የፈለገበት" አይነት ትንታኔ ስለሚገጥመኝ ነው። ተወገዘም፣ ተወደሰም የምፈልገው የፃፍኩትን ነው፣ አለቀ። ሌላ ትርጉም የምትሰጡ ሁሉ! ሆነ ብላችሁ አጣማችሁ ሳይሆን መስሏችሁ ብትሳሳቱብኝ ከየትኛውም ቡድን ብትሆኑ ዐፍው ብያለሁ። ሆነ ብሎ ንግግሬን አጣሞ በመተርጎም ለሚከሰኝ ደግሞ ሂሳባችን ከአላህ ዘንድ ነው።
እኔንም እናንተንም ልባችንን አላህ ለሐቅ ክፍት ያድርግልን። በሐቅ ላይም ይሰብስበን። ኣሚን።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 3 390 |
| 3 | ጥሪ ለሙስሊሙ ኡማ!
(የሃይማኖቱ ጉዳይ ለሚያሳስበው ሃላፊነት ለሚሰማው ሙስሊም ሁሉ!)
~
በአዲስ አበባ እና በአንዳንድ የክልል ከተሞች አሕ^ባሾች ድምፃቸውን አጥፍተው በተጠናከረ መልኩ እየተንቀሳቀሱ ነው፡፡ አካሄዳቸውም ህፃናትን ከተለያዩ አካባቢዎች በመሰብሰብ ረዘም ላለ ጊዜ በማሰልጠን ስለሆነ አደጋውን ይበልጥ የከፋ ያደርገዋል፡፡ በቁርኣን ሒፍዝ ስም በሚሰበስቧቸው ልጆች ልቦና ውስጥ አደገኛ የሆነ መርዝ በመትከል ዐቂዳቸውን እየበከሉ ስለሆነ ወገናችንን ለመታደግ ከወላጆች ዘንድ አስፈላጊውን ግንዛቤ ልንፈጥር፣ የምንችለውን ሁሉ ልናደርግ ይገባናል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በህዝብ እንደተተፉ የገባቸው አሕ^ባሾች መልካቸውን ቀይረው በአንዳንድ አካባቢዎች በተብሊጎች ስም እየተንቀሳቀሱ ነው፡፡ ሰዎችን በኹሩጅ ከሰበሰቡ በኋላ ቀስ በቀስ የራሳቸውን ብልሹ ዐቂዳ ለማስረግ እየተጉ ነው፡፡
ስለሆነም ነገ አላህ ፊት ከመጠየቃችን በፊት ዛሬ ፈጥነን ነገሮችን በሚገባ ማጤን እና ዙሪያ ገባችንን ማስተዋል የግድ ይለናል፡፡ በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች በሚገኙ የተለያዩ የቁርኣን የሒፍዝ ማእከላት ልጆቻችሁን ያስገባችሁ ወላጆች ሁሉ፡ ነገ አላህ ፊት ከመጠየቃችሁ በፊት፣ የልጆቻችሁንም ዘላለማዊ ህይወት ከማበላሸታችሁ በፊት ከወዲሁ አስፈላጊውን እርምጃ ውሰዱ። ያስገባችሁበትን መርከዝ ምንነት በሚገባ አስረግጡ፡፡ ያለበለዚያ ነገ ብዙ መስዋእትነት ያስከፍለናል፡፡ ከዚያ በላይ ግን ለዘላለማዊ ፀፀት ይጥለናል፡፡ ከዐርሹ በላይ ያለው ጌታችን እንዲህ ይለናል፡-
يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا قُوا أَنْفُسَكُمْ وَأَهْلِيكُمْ نَارًا وَقُودُهَا النَّاسُ وَالْحِجَارَةُ عَلَيْهَا مَلَائِكَةٌ غِلَاظٌ شِدَادٌ لَا يَعْصُونَ اللَّهَ مَا أَمَرَهُمْ وَيَفْعَلُونَ مَا يُؤْمَرُونَ
“እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ነፍሶቻችሁንና ቤተሰቦቻችሁን መቀጣጠያዋ ሰዎችና ደንጋዮች ከሆነችዋ (የጀሀነም) እሳት ጠብቁ፡፡ በርሷ ላይ ጨካኞች፣ ሃይለኞች የሆኑ መላእክት አልሉ፡፡ አላህን ያዘዛቸውን ነገር (በመጣስ) አያምፁትም፡፡ የሚታዘዙትንም ሁሉ ይሰራሉ፡፡” [አት-ተሕሪም፡ 6]
ነብዩም ﷺ እንዲህ ይላሉ፡-
(كُلُّكُمْ رَاعٍ وَكُلُّكُمْ مَسْؤول عَنْ رَعِيَّتِهِ، الإِمَامُ رَاعٍ وَمَسْؤولٌ عَنْ رَعِيَّتِهِ، وَالرَّجُلُ رَاعٍ فِي أَهْلِهِ وَهُوَ مَسْؤولٌ عَنْ رَعِيَّتِهِ، وَالْمَرْأَةُ رَاعِيَةٌ فِي بَيْتِ زَوْجِهَا وَمَسْؤولَةٌ عَنْ رَعِيَّتِهَا، وَالْخَادِمُ رَاعٍ فِي مَالِ سَيِّدِهِ ومَسْؤولٌ عَنْ رَعِيَّتِهِ، قَالَ: وَحَسِبْتُ أَنْ قَدْ قَالَ: وَالرَّجُلُ رَاعٍ فِي مَالِ أَبِيهِ وَمَسْؤولٌ عَنْ رَعِيَّتِهِ- وَكُلُّكُمْ رَاعٍ وَمَسْؤولٌ عَنْ رَعِيَّتِهِ)
“ሁላችሁም እረኞች ናችሁ፡፡ ሁላችሁም ስለ እረኝነታችሁ (ስለ ሃላፊነታችሁ) ተጠያቂ ናችሁ፡፡ መሪ እረኛ ነው፤ ስለ እረኝነቱም ተጠያቂ ነው፡፡ ወንዱ (ባል) በቤተሰቡ ላይ እረኛ ነው፤ ስለ እረኝነቱም ተጠያቂ ነው፡፡ ሴቷም በባሏ ቤት ውስጥ እረኛ ነች፤ ስለ እረኝነቷም ተጠያቂ ነች፡፡ አገልጋይም በአለቃው ንብረት ላይ ተጠያቂ ነው፤ ስለ እረኝነቱም ተጠያቂ ነው፡፡ ‘አንድ ሰው በአባቱ ንብረት ላይ ተጠያቂ ነው፤ ስለ እረኝነቱም ተጠያቂ ነው’ ያሉም ይመስለኛል ይላል ዘጋቢው፡፡ ሁላችሁም እረኞች ናችሁ፡፡ ሁላችሁም ስለ እረኝነታችሁ ተጠያቂ ናችሁ፡፡” [ቡኻሪና ሙስሊም]
ስለዚህ ከተጠያቂነት ለመዳን፣ እራሳችንን እና ወገናችንን ለማትረፍ ሃላፊነታችንን እንወጣ፡፡ ወገን ለወገኑ ደራሽ ነው፡፡ አላህ በዲናችን የመጣውን ፈተና ያንሳልን፡፡ የተሻለውንም ይምረጥልን፡፡ ኣሚን፡፡ ይህን መልእክት በሰፊው በማሰራጨት የምንችላትን እናድርግ፡፡ የአላህ ፈቃዱ ከሆነ የሚጠቀምበት ሰው ይኖራል፡፡
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ ነሐሴ 29/2007)
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 8 127 |
| 4 | بدون متن... | 5 489 |
| 5 | ዛሬ ጁሙዐ ረቢዑል አወል 22/1448 (ነሐሴ 29/2018) የሉምዐቱል ኢዕቲቃድ ኪታብ ደርስ ይኖራል፣ ኢንሻአላህ።
* የሚሰጥበት ቦታ: - አሸዋ ሜዳ፣ መስጂዱል ዋሊደይን
* ቀን:- ዘወትር ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ጁሙዐ
* ሰዓት፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
* የኪታቡን pdf በዚህ ሊንክ ታገኛላችሁ:- https://t.me/IbnuMunewor/9934
* የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 21
* በቦታው ተገኝታችሁ መከታተል ለማትችሉ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል:- https://t.me/IbnuMunewor | 4 935 |
| 6 | መድ'ኸሊይ እንዳትሆን!
~
ሸይኽ ረቢዕ አልመድ'ኸሊይ - ረሒመሁላህ - እንደማንኛውም ዓሊም ናቸው። ይሄ ደረጃቸውን ዝቅ ማድረግ አይደለም። ከሳቸው የሚበልጡ ታላላቅ ዑለማኦችን በጭፍን መከተል አይፈቀድም ስንል ደረጃቸውን ዝቅ ማድረግ እንደማይሆነው ማለት ነው። ረቢዕ ልክ እንደሌሎቹ ዓሊሞች በየትኛውም ርእስ ላይ ቢሆን ፍፁም አይደሉም። በትንሽ በትልቁ በሸይኽ ረቢዕ ንግግር የሚያስፈራራ ቢኖር ራሱን ነው የሚሸውደው። ሱናን እከተላለሁ የሚል አካል በየትኛውም ዓሊም ላይ ያለው ምልከታ ለከት ሊኖረው ይገባል። አንድን ዓሊም መለኪያም፣ መስፈሪያም፣ መቁረጫም ማድረግ አይገባም። ሸይኽ ዐብዱልዐዚዝ አራጂሒይ - ሐፊዞሁላህ - የሌሎች ዓሊሞችን ንግግር ገሸሽ በማድረግ የሸይኽ ረቢዕን ንግግር በተለዬ የሚይዙ ስለሆኑ ሰዎች ሲጠየቁ እንዲህ ነበር ያሉት፦
يعني جعلوه رسولا، جعلوا ربيع رسولا، جعلوه رسولا، وهذا باطل، هذا باطل، ربيع ... يخطيء و يصيب و لا هو المييزان، الميزان: كلام الله و كلام الرسول، فمن قال: الميزان ربيع، هذا باطل.
"መልእክተኛ አደረጉት ማለት ነው?! ረቢዕን መልእክተኛ አደረጉት?! ይሄ ውድቅ ነው። ይሄ ውድቅ ነው። ረቢዕ ... ይስታል፣ ያገኛል። ሚዛን አይደለም። ሚዛኑ የአላህ ንግግር እና የመልእክተኛው ንግግር ነው። ሚዛኑ ረቢዕ ነው የሚል ይሄ ውድቅ ንግግር ነው።" [ከድምፅ ቅጅ የተወሰደ ነው።]
ስለዚህ የአልባኒይ፣ የኢብኑ ባዝ፣ የኢብኑ ዑሠይሚን፣ ወዘተ ንግግር በጭፍን እንደማይወሰደው የረቢዕ ንግግርም በጭፍን አይወሰድም። ረቢዕ በሌሎች መሻይኾች ላይ የሚናገሩትም በማስረጃ የተደገፈ ሲሆን ይወሰዳል፣ ካልሆነ ይጣላል። እንጂ ተናጋሪው ረቢዕ በመሆናቸው ብቻ ይወሰዳል ማለት አይደለም። አልባኒያ፣ ባዚያ፣ ዑሠይሚኒያ፣ ፈውዛኒያ፣ ... የሚባል መዝሀብ እንደሌለው መድ'ኸሊያ የሚባል መዝሀብም የለም። ስለዚህ አኢማዎችን በጭፍን የሚከተል ሐነፊይ፣ ማሊኪይ፣ ሻፊዒይ፣ ሐንበሊይ፣ ... መሆን እንደሌለብህ ሁሉ ረቢዕን በጭፍን የሚከተል መድ'ኸሊይ ልትሆንም አይገባም። እዚህ ላይ በቃል ደረጃ ችግር የለም። በተግባር ግን በተለያዩ መሻይኾች ላይ ድንበር ማለፍ ስላለ ጥንቃቄ እንዲኖረን ማስታወስ ነው የፈለግኩት። (ለጥጠው ሌላ ትርጉም ከሰጡ በኋላ በራሳቸው ምናብ ላይ ነብር ሆነው ለረድ የሚነሱ እንደሚኖሩ እጠብቃለሁ።)
በተረፈ የኢኽ'ዋን ጀሌዎች እዚህ እንዳትመጡ። የዚህ ፅሑፍ ጭብጥ በቅርብም በሩቅም ከናንተ ጋር የሚገናኝ አይደለም። የኢኽ'ዋን ቡድን ዘንድ የአንጃቸውን ጥመት ከተናገርክ፣ የነ ሐሰን አልበና፣ ሰይድ ቁጥብ፣ ቀርዷዊይ፣ ... ጥፉ አካሄዶች ካስጠነቀቅክ፣ ... በኢኽ'ዋን ቫይረስ በተጠቁ አካላት ዘንድ አንተ መድ'ኸሊይ ወይም ጃ'ሚይ ነህ። ልክ የሙታን አምልኮን፣ በአላህ ሲፋት ላይ ማራቆትን ስታወግዝ "ወሃ'ቢይ" እንደምትባለው ማለት ነው። ለነዚህ ሸይኽ ዒምራን ዐሊይ ሪድዋን አልፋሪሲይ - ረሒመሁላህ - እንዳሉት እንላለን፦
قُـلْ لِلَّذِي اتَّـخَـذَ الـتَّـجَـهُّـمَ مَـرْكَـبًـا
وَ رَآهُ دِيـنًـا و ارْتَــضَـاهُ مَـذْهَــــبًـا
وَ لِـمَـذهَبِ الأَبـــرَارِ صَارَ مُـكَـذِّبـًـا
إنْ كَانَ تَـابِـعُ أَحـمَــــدٍ مُـتَـوَهِّــبًـا *** فَـأَنـا الـمُــــقِـرُّ بِـأَ نَّـنِـي وَهَّـــابِي
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥር 17/2016)
=
* የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 6 711 |
| 7 | بدون متن... | 5 991 |
| 8 | الـرد على أبي مُحمـدٍ ابن حـزمٍ(ت456)
في (إنكاره معاني أسمـاء الله)، و(إنكاره أن يُقال: صفةُ الله)
وفي الـخـاتـمـة: خُلاصـةُ البحث في (ثلاثين) نُقطـةً مُـهـمـةً جـدا
قناة الشيخ أبو العباس الشحري
https://t.me/aleabaas | 6 741 |
| 9 | ደርስ፦
~
* ሉምዐቱል ኢዕቲቃድ
* ክፍል፦ 08
* የኪታቡን pdf በዚህ ሊንክ ታገኛላችሁ:- https://t.me/IbnuMunewor/9934
* የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 16 | 7 881 |
| 10 | ዛሬ ሐሙስ ረቢዑል አወል 21/1448 (ነሐሴ 28/2018) የሉምዐቱል ኢዕቲቃድ ኪታብ ደርስ ይኖራል፣ ኢንሻአላህ።
* የሚሰጥበት ቦታ: - አሸዋ ሜዳ፣ መስጂዱል ዋሊደይን
* ቀን:- ዘወትር ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ጁሙዐ
* ሰዓት፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
* የኪታቡን pdf በዚህ ሊንክ ታገኛላችሁ:- https://t.me/IbnuMunewor/9934
* የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 16
* በቦታው ተገኝታችሁ መከታተል ለማትችሉ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል:- https://t.me/IbnuMunewor | 9 399 |
| 11 | خطبة الجمعة - – 22 ربيع الأول 1448هـ بصفحتين
📌 #خطبة_مكتوبة -٢٢ (٢٢-٣-١٤٤٨هـ)
بعنوان:”دُعَاةٌ عَلَى أَبْوَابِ جَهَنَّمَ“
✏️ كتبها:
أبو مسلم عمر بن حسن العروسي
📥📥📥
https://t.me/AbumuslimArabicDuroos/9256
#العقيدة_خطبة_الجمعة
#منهج_السلف_الخطبة
#التحذير_من_البدع_الخطبة | 8 800 |
| 12 | 3️⃣0️⃣ ቀዳሜ ነሐሴ 3️⃣0️⃣
🟩🟩🟩🟩🟩🟩
➡️ መርከዝ አቡ ሙሳ አል አሽዐሪ የቁርአን ሂፍዝና የተርቢያ ማእከል በበጋና በክረምት በአዳሪ መርሀግብር ሲያስተምራቸው የቆዩ ወንድና ሴት ተማሪዎችን የፊታችን ቅዳሜ ነሐሴ 30 አጠና ተራ እፎይታ የገቢያ ማእከል በሚገኘው ትልቁ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ ያስመርቃል ። ኢንሻአላህ
➡️ በፕሮግራሙ ከተመራቂ ተማሪዎች የተለያዩ ማራኪ ዝግጅቶች ይጠብቋቹሀላ ።
➡️ በፕሮግራሙም ላይ የተለያዩ መሻይኾችና ኡስታዞች አጫጭር ሙሐደራዎች ይኖሯቸዋል ።
ተጋባዥ እንግዶች ⤵️
➡️ሸይኽ ሙሐመድ አወል ባህርዳር
➡️ኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር
➡️ኡስታዝ ሙሐመድ ሲራጅ
➡️ኡሰታዝ ሳዳት ከማል
➡️ኡስታዝ አቡ ሙስሊም
ማሳሰቢያ:
➡️ ፕሮግራሙ የሚጀመረው ከጠዋቱ 2:30 ስለሆነ ፈጥነው እንዲደርሱ ለማሳሰብ እንወዳለን ።
➡️ ለሴቶችም በቂ ቦታ ያለ ሲሆን ፕሮግራሙንም በላይቭ ቀጥታ ስርጭት የሚከታተሉ ይሆናል ።
ነሐሴ 3⃣0⃣
★★★
Telegram : -
https://t.me/merkezabumussa1
https://t.me/merkezabumussa1 | 10 663 |
| 13 | 3️⃣0️⃣ ቀዳሜ ነሐሴ 3️⃣0️⃣
🟩🟩🟩🟩🟩🟩
➡️ መርከዝ አቡ ሙሳ አል አሽዐሪ የቁርአን ሂፍዝና የተርቢያ ማእከል በበጋና በክረምት በአዳሪ መርሀግብር ሲያስተምራቸው የቆዩ ወንድና ሴት ተማሪዎችን የፊታችን ቅዳሜ ነሐሴ 30 አጠና ተራ እፎይታ የገቢያ ማእከል በሚገኘው ትልቁ አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ ያስመርቃል ። ኢንሻአላህ
➡️ በፕሮግራሙ ከተመራቂ ተማሪዎች የተለያዩ ማራኪ ዝግጅቶች ይጠብቋቹሀላ ።
➡️ በፕሮግራሙም ላይ የተለያዩ መሻይኾችና ኡስታዞች አጫጭር ሙሐደራዎች ይኖሯቸዋል ።
ተጋባዥ እንግዶች ⤵️
➡️ሸይኽ ሙሐመድ ሀሰን ፈድሉ
➡️ሸይኽ ሙሐመድ አወል ባህርዳር
➡️ኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር
➡️ኡስታዝ ሙሐመድ ሲራጅ
➡️ኡሰታዝ ሳዳት ከማል
➡️ኡስታዝ አቡ ሙስሊም
ማሳሰቢያ:
➡️ ፕሮግራሙ የሚጀመረው ከጠዋቱ 2:30 ስለሆነ ፈጥነው እንዲደርሱ ለማሳሰብ እንወዳለን ።
➡️ ለሴቶችም በቂ ቦታ ያለ ሲሆን ፕሮግራሙንም በላይቭ ቀጥታ ስርጭት የሚከታተሉ ይሆናል ።
ነሐሴ 3⃣0⃣
★★★
Telegram : -
https://t.me/merkezabumussa1
https://t.me/merkezabumussa1 | 1 |
| 14 | #SaudiArabia🇸🇦
በሳዑዲ አረቢያ፣ የሰው ህይወት ያጠፋው ግለሰብ በሞት ተቀጣ።
የሳዑዲ ዓረቢያ የውስጥ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ በመካ ክልል በግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ተብሎ የሞት ፍርድ የተፈረደበት የየመን ዜጋ የሞት ቅጣቱ እንደተፈጸመበት አስታወቀ።
ዚያድ ዋሊድ መሐመድ አብዱላህ ሀይደራህ የተባለው ግለሰብ ከሌላ የየመን ዜጋ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት በሹል ነገር ጭንቅላቱን በመምታት ለሞት እንደዳረገው ሚኒስቴሩ ገልጿል።
ጉዳዩ በፍርድ ቤት ታይቶ ጥፋተኛ መሆኑ ከተረጋገጠ በኋላ፣ ተከሳሽ ይግባኝ ቢጠይቅም የሞት ፍርዱ ጸንቷል። ይህንንም ተከትሎ በንጉሳዊ ትዕዛዝ የሞት ፍርዱ ትላንት ተፈጻሚ ሆኗል።
ሚኒስቴር እንዳለው፥ እርምጃው የሀገሪቱን ደህንነት ለማስጠበቅ፣ ፍትሕን ለማስከበር እና በሕይወት የመኖር መብት ላይ ሚፈጸሙ ወንጀሎችን ለመከላከል የሚወሰድ ሕጋዊ እርምጃ ነው።
ተመሳሳይ ወንጀል ለመፈጸም የሚያስቡ ሰዎችም በሕግ የተደነገገውን ከባድ ቅጣት እንደሚጋፈጡ ሚኒስቴሩ አስጠንቅቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
=
በዚህና መሰል ዜናዎች ስር ኢትዮጵያውያን የሚያሳዩትን ከፍተኛ ድጋፍ የተመለከተ ምን ያህል በሀገራችን የወንጀል መንሰራፋትና በቅጣት ህጉ መላላት ቆሽቱ እንዳረረ መረዳት ይቻላል።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 10 598 |
| 15 | ደርስ፦
~
* ሉምዐቱል ኢዕቲቃድ
* ክፍል፦ 07
* የኪታቡን pdf በዚህ ሊንክ ታገኛላችሁ:- https://t.me/IbnuMunewor/9934
* የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 15 | 9 798 |
| 16 | ዛሬ ረቡዕ ረቢዑል አወል 20/1448 (ነሐሴ 27/2018) የሉምዐቱል ኢዕቲቃድ ኪታብ እንጀምራለን፣ ኢንሻአላህ።
* የሚሰጥበት ቦታ: - አሸዋ ሜዳ፣ መስጂዱል ዋሊደይን
* ቀን:- ዘወትር ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ጁሙዐ
* ሰዓት፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
* የኪታቡን pdf በዚህ ሊንክ ታገኛላችሁ:- https://t.me/IbnuMunewor/9934
* የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 15
* በቦታው ተገኝታችሁ መከታተል ለማትችሉ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል:- https://t.me/IbnuMunewor | 13 216 |
| 17 | የ “ዘመን መለወጫ” ኮተቶች
~
ኢትዮጵያ በምትከተለው ክርስቲያናዊው የዘመን አቆጣጠር መሰረት አዲስ አመት ሊገባ የያዝነው አመት እየተጠናቀቀ ነው። በያመቱ በዚህ ሰሞን የሚፈፀሙ ከሃይማኖታችን ጋር የማይሄዱ በርካታ ነገሮ አሉ። ከነዚህም ውስጥ:-
1. ድግምትና ጥንቆላ፦
በሃገራችን የተለያዩ አካባቢዎች ነሐሴ ሊጠናቀቅ ሲል በየጠንቋዩ ቤት የሚልከሰከሱት ብዙ ናቸው። ከዚያም አምስቱ ወይም ስድስቱ የጳጉሜ ቀናት መንገዶች በድግምት ስራዎች ይሞላሉ። በነዚህ ቀናት ማልዶ የወጣ ሰው እንዲረግጣቸው/ እንዲራመዳቸው ታስቦ በጎረቤት መተላለፊያ እና ህዝብ በሚያዘወትራቸው መንገዶች ላይ የሞቱ ፍየሎች፣ ዶሮዎች፣ ድመቶች፣ ጥንቸሎች ወዘተ ታርደው ይጣላሉ። በደም የተነከሩ ሳንቲሞች፣ ብሮች፣ ጌጣ ጌጦች፣ የተለያዩ ቁሳቁሶች እዚህም እዚያም ወድቀው ይታያሉ።
* ጥንቆላና ድግምት ከኢስላም የሚያስወጡ ከባባድ ወንጀሎች ናቸው፡፡
وَاتَّبَعُوا مَا تَتْلُو الشَّيَاطِينُ عَلَى مُلْكِ سُلَيْمَانَ وَمَا كَفَرَ سُلَيْمَانُ وَلَكِنَّ الشَّيَاطِينَ كَفَرُوا يُعَلِّمُونَ النَّاسَ السِّحْرَ
“በሱለይማን ዘመነ-መንግስት ሸይ ^ጧኖች የሚያነቡትንም (ድግምት) ተከተሉ። ሱለይማን ግን አልካደም (ድግምተኛ አልነበረምና።) ግና ሸይ^ጧኖች ሰዎችን ድግምት የሚያስተምሩ ሲሆኑ ካዱ።” [አል-በቀራህ፡ 102]
ነብዩም ﷺ {ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ በሚናገረው ያመነ፣ በሙሐመድ ላይ በወረደው ክዷል} ብለዋል። [አስ-ሶሒሐህ፡ 3387]
* ደጋሚዎችና ከነሱ ዘንድ የሚመላለሱ ሰዎች መቼም ቢሆን ስኬት የላቸውም። ጌታችን “ድግምተኛም በመጣበት ስፍራ ሁሉ አይቀናውም” ብሏል። [ጦሃ፡ 69]
* ጠንቋይና ደጋሚ ዘንድ የሚሄድ ሰው የተነገረውን ባያምን እንኳን ከባድ ቅጣት ይከተለዋል። ነብዩ ﷺ {ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ ስለሆነ ነገር የጠየቀው የአርባ ቀን ሶላቱ ተቀባይነት የለውም} ብለዋል። [ሙስሊም፡ 5957]
2. ሎሚ መምጠጥ እና ፌጦ መብላት:-
በአንዳንድ አካባቢዎች ከድግምትና ጥንቆላ ለመጠበቅ በማሰብ ወላጆች ልጆቻቸውን ጳጉሜ ላይ ሎሚና ፌጦ ይመግባሉ። ድግምትና ጥንቆላ ሸይ^ ጧናዊ ተግባራት ናቸው። መጥጠበቂያ መንገዶቹ አዝካር፣ አየቱል ኩርሲይ፣ ሱረቱል ኢኽላስን (ቁል ሁወላሁ አሐድ)፣ ሙዐዊዘተይን (ቁል አዑዙ ቢረቢል ፈለቅ፣ ቁል አዑዙ ቢረቢናስ) ከሶላት በኋላ እና ጧትና ማታ መቅራት፣ እንዲሁም ከሱረቱል በቀራ የመጨረሻዎቹን ሁለት አንቀፆች መቅራት፣ ሩቅያ ማድረግ ናቸው። አጉል እምነት ላይ የተመሰረቱ ሰበቦችን መጠቀም ከሺርክ ነው።
በተረፈ የተጣለ የድግምት ስራ ቢያጋጥመን ምንም መደናገጥ አያስፈልግም። በአላህ ላይ ጠንካራ እምነት ማሳደር (ተወኩል) ቀዳሚው መከላከያ መንገድ ነው። አጉል መጨናነቅ ለችግር ይዳርጋል። ከዚያም የድግምት ስራውን ሙዐዊዘተይን በመቅራት ማስወገድ ነው (ማቃጠል፣ መቆራረጥ ወይም ቆፍሮ መቅበር)።
3. የጳጉሜ ዱዓእ የሚል ቢድዐ:-
በአንዳንድ አካባቢዎች የጳጉሜ ዱዓእ “መቅቡል ነው” (ተቀባይነት ያለው ነው) የሚል እምነት አለ። ይሄ አጉል እምነት ነው። በጣም የሚገርመው ለዱዓእ የሚጣዱት እስልምናን ያውቃሉ ሰዎችን ያስተምራሉ የሚባሉት ሰዎች መሆናቸው ነው። ነብዩ ﷺ “አላህ እውቀትን ከባሪያዎቹ መንጠቅን አይነጥቅም። ይልቁንም ዑለማዎችን በመውሰድ (በመግደል) እውቀትን ይወስዳል። ከዚያም ዓሊም እስከማይቀር ድረስ። በዚያኔ ሰዎች መሀይማንን መሪዎች አድርገው ይይዛሉ። ሲጠየቁም ያለ እውቀት ፈትዋ ይሰጣሉ። በዚህም ይጠማሉ፣ ያጠማሉም” ብለዋል። [ሶሒሕ አልቡኻሪይ፡ 100] [ሶሒሕ ሙስሊም፡ 2673]
4. የጳጉሜ ጸበል (ጥምቀት)፦
ጳጉሜ 3 ቀን በኦርቶዶክስ ክርስትና የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ በዓል ነው ይላሉ። በዚህ ዕለት "የሰማይ ደጆች ይከፈታሉ፣ ዝናቡም የበረከትና የፈውስ ውሃ ሆኖ ይወርዳል" ተብሎ ይታመናል። በዚህም የተነሳ ሕዝቡ ሕፃናትን ጨምሮ ከሰማይ የሚወርደውን ዝናብ (የጳጉሜን ዝናብ) እንደ ጸበል በመቁጠር ሰውነታቸውን ይጠመቁበታል። ሙስሊሞች ከንደዚህ ዓይነት እምነቶችና ተግባራት ሊርቁ ይገባል።
5. እንቁጣጣሽ ማክበር:-
ሌላኛው የ “ዘመን መለወጫን” ተከትሎ የሚፈፀመው ጥፋት መስከረም አንድን ወይም እንቁጣጣሽን ማክበር ነው። ዕለቱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን እምነት መሠረት "ቅዱስ ዮሐንስ" በመባል የሚጠራ ሲሆን፣ የመጥምቁ ዮሐንስ መታሰቢያ እና የቅዱሳን አበው መታሰቢያ ይደረግበታል። በቤተክርስቲያን ደረጃ የማህሌት፣ የቅዳሴ እና የምስጋና ሥርዓት ይፈጸምበታል።
በተጨማሪም የበዓሉ ስም (እንቁጣጣሽ የሚለው) ከንግሥተ ሳባ እና ከንጉሥ ሰሎሞን አፈ ታሪክ ጋር ይያያዛል። ንግሥተ ሳባ ከኢየሩሳሌም ስትመለስ መኳንንቶቿ "እንቁ ለጣጣሽ" (ለጌጥሽ ይሁን) በማለት በዕንቁ ስለተቀበሏት ይህ ስም እንደወጣ ይነገራል።
አቆጣጠሩ ሀገራዊ እንጂ እምነታዊ መሰረት እንደሌለው ሊያሳምኑ የሚሞክሩ ሰዎች አሉ። ነገሩ ግልፅ ቢሆንም ድንገት የሚሰወራቸው ካሉ ለማስታወስ ያህል:-
* አቆጣጠሩ ከግብፅ ኮፕቲክ ቤተክርስቲያን የተቀዳ ነው።
* አመቱ ሲፃፍ መጨረሻ ላይ “ዓመተ ምህረት” የሚባለውም ክርስቲያናዊ ስለሆነ ነው።
* የነብዩ ዒሳን (ሰላም በሳቸው ላይ ይስፈንና) መወለድ መሰረት ያደረገ እንደሆነ የሚታመን ነው።
* በእለቱም የሚፈፀሙት የተለያዩ ሃይማኖታዊ ሥነ-ሥርዓቶችም በዓሉ ክርስቲያናዊ እንደሆነ በሚገባ አጉልተው ያሳያሉ፦
- የዋዜማ ጸሎትና ማኅሌት፦ በበዓሉ ዋዜማ (ጳጉሜን 5 ወይም 6) ሌሊቱን ሙሉ በቤተክርስቲያን ልዩ የቅዱስ ዮሐንስ ማኅሌትና ጸሎት ይቆማል።
- የቅዳሴ ሥነ-ሥርዓት፦ በዕለቱ ጠዋት ምዕመናን አዲስ ልብስ ለብሰው ወደ ቤተክርስቲያን በመሄድ በቅዳሴና በዕለቱ ትምህርተ ወንጌል ላይ ይሳተፋሉ።
- ዘመነ ዮሐንስን መቀበል፦ በቤተክርስቲያን ዘመን መለወጫን አስመልክቶ ልዩ ጸሎት ይደረጋል፤ የወንጌላዊው ዘመንም (ዘመነ ማቴዎስ፣ ማርቆስ፣ ሉቃስ ወይም ዮሐንስ) ይታወጃል። “እንኳን ከዘመነ ማቲዎስ ወደ ዘመነ ማርቆስ፣ ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ፣ ... አደረሳችሁ” ማለታቸው አቆጣጠሩና በዓሉ ሃይማኖታዊ መሆናቸውን አጉልተው የሚያሳዩ ነጥቦች ናቸው፡፡
ይህንን ስንል የሚጎረብጣቸው አሉ። እኛ'ኮ የኛን ዒድ አብራችሁን ካላከበራችሁ አላልንም። ይልቁንም የኛን እምነታዊ መገለጫ ካላንፀባረቃችሁ ብሎ ሌሎችን መወረፍ አክራሪነት ነው። እምነታችን የሌሎች ህዝቦች #መለያ በሆኑ እምነቶችና ልማዶች መመሳሰልን አይፈቅድም። ነብያችን ﷺ “በሰዎች የተመሳሰለ ከነሱው ነው” ብለዋል።
(ኢብኑ ሙነወር፣ 18/11/1436)
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 19 011 |
| 18 | بدون متن... | 10 057 |
| 19 | ሱብሀነሏህ እንዴት የሚደንቅ የፅናት ታሪክ ነው
------
በ1977 በኢትዮጵያ በነበረው ድርቅ ምክኒያት የተፈጠረውን ርሃብ ተከትሎ የተከሰተውን ይህን አሳዛኝ ታሪክ ሌላ ሰው ቢያወራው ኖሮ ለማመን ይከብድ ነበር ነገር ግን ይህን ታሪክ የሚናገሩት ኩዌይታዊ ሼኸ ዶ/ር አብዱራህማን አስ-ሰሚጥ ናቸውና ለማመን እንገደዳለን አላህ ይማራቸውና በአፍሪካ አህጉር ከ11ሚሊዮን በላይ ሠዎችን ያሰለሙ ሸይኽ ናቸው
ታሪኩ እንዲህ ነው በ1977 አንድ የክርሰትያን በጎ አድራጊ ማህበር ከሰሜን አሜሪካ እርዳታ ለመሰጠት ወደ ኢትዮጵያ ይመጣና በቀጥታ ድርቅና ርሃብ ወደ ተከሰተበት ገጠር ሂደው እርዳታ መሰጠት ይጀምራሉ ከዚያም የመስጂድ ኢማም የሆኑ አንድ ትልቅ ሠው እርዳታ ለመቀበል ይመጣሉ አሜሪካዊው እርዳታ ሰጪ ሲያያቸው የሀይማኖት አባት መሆናቸውን አውቆ ክርሰትያን እንዲሆኑ ጠየቃቸው እሳቸውም «ክርሰትያን አልሆንም የምትሰጠኝ ከሆነ ሰጠኝ» አሉት አሜሪካዊውም «እሺ አሁን በህዝብ ፊት በውሸት ክርሰትያን ሁኜያለሁ በል እና የፈለግከውን እሰጥሃለሁ» አላቸው እሳቸውም «በውሸትም በእውነትም አልልም ሀይማኖቴን አልቀይርም አሉት» ሰውየው ተናደደ እና «በቃ የሚሰጥ የለንም» ብሎ መለሳቸው ኢማሙ ባዶ እጃቸውን ወደ ቤታቸው ተመለሱ የሳቸው ቤተሰብም ጨርሶ እርዳታ ሳያገኝ ቀረ ፥
ከ3 ወራት በኋላ ይህን ታሪክ የሰሙት ኩዌታዊ ሸይኽ አብዱራህማን እንዲህ ይላሉ «ይህን ወሬ ከሰማሁኝ በኋላ በቀጥታ ከኩዌት ወደ ኢትዮጵያ ሄድኩኝ እና እኚህ ኢማም ወደ ሚኖሩባት አካባቢ ተጓዝን እንደ ደርሰን በአካባቢው ሰው የሚባል የለም ሁሉም ድርቁን ሽሽት አካባቢውን ለቀውት ሄደዋል ይዘውኝ የሄዱት ሰዎች የኢማሙን ቤት አሳዩኝና በራቸውን አንኳኳን የሚከፍትልን ስናጣ በሩን ገፋ አድርጌ ገባሁ ያየሁት ነገር እጅግ ዘግናኝ እና አስደንጋጭ ነበር አይኔን ማመን ከበደኝ ኢማሙ ሚሰታቸው እና ልጆቻቸው ሁሉም እንደተኙ በርሃብ ሙተዋል የአጥንታቸው ሃይከል ብቻ ተኝቶ አገኘሁት ፥ «በርሃብ እንሞታለን እንጂ ሀይማኖታችንን አንቀይርም» ብለው የሞቱ የሀበሻ ቤተሰብ አይቼ ተመለሰኩኝ ፥ በተጨማሪ እነዚያ በክርሰትና ስም ይዘውት የመጡት እርዳታ የኛ የአረብ አገሮች እና የሌሎች የመላው የአለም ህዝብ አዋጥተን ለተባበሩት መንግሰታት ድርጅት በሰብአዊነት የሰጠነው እርዳታ ነበር እነርሱ ግን በእንደዚህ አይነት አሳዛኝ ሁኔታ አከፋፍለውታል» ሲሉ ታሪኩን ያጠቃልላሉ
Abdulfetah Mahmud
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 11 993 |
| 20 | ሸይኽ ዐብዱረዛቅ አልበድር - አላህ ከክፉ ይጠበቃቸውና - እንዲህ ብለዋል፦
*إنّ فاقد التوحيد ميّت ولو كان يمشي على الأرض ومحقّق التوحيد هو الذي يحيا الحياة الحقيقية
*يقول الله -جلّ وعلا-: {أَوَ مَن كَانَ مَيْتاً فَأَحْيَيْنَاهُ} [الأنعام:١٢٢]. أي أحييناه بالإيمان والتوحيد"*
“ተውሒድ የሌለው ሰው፣ ምድር ላይ የሚንቀሳቀስ ቢሆን እንኳ፣ የሞተ ነው። እውነተኛውን ህይወት የሚኖረው ተውሒድን ያረጋገጠ ነው። የላቀውና ከፍ ያለው አላህ እንዲህ ብሏል፡-
“ሙት የነበረና ሕያው ያደረግነው ሰው…” [አል-አንዓም፡ 122]
ይህም ማለት፡- “በኢማንና በተውሒድ ሕያው አደረግነው” ማለት ነው።
🎙️[“የተውሒድ ደረጃ በሙስሊም ህይወት ውስጥ” ከሚል ኹጥባ የተወሰደ።]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 12 266 |
