የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe
﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student | ለንግድ፣ ለህክምና ወይም ለጉብኝት ወደ ቱርክ፣ ዱባይ እና የተለያዩ ሀገራት ለመጓዝ ካሰባችሁ ፈሲሩ ትራቭል የትኬት ጉዳያችሁን በኃላፊነት ያጠናቅቃል። እንግልት የሌለበት ጉዞ ለማድረግ ስትፈልጉ በዋትስአፕ አግኙን፦ https://wa.me/qr/5CWCIMYBZLCJB1
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe
Channel የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe (@yahyanuhe) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 21 254 subscribers, ranking 3 695 in the Religion & Spirituality category and 1 588 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 21 254 subscribers.
According to the latest data from 16 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 180 over the last 30 days and by 5 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 18.41%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.20% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 3 911 views. Within the first day, a publication typically gains 1 742 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 69.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student |
ለንግድ፣ ለህክምና ወይም ለጉብኝት ወደ ቱርክ፣ ዱባይ እና የተለያዩ ሀገራት ለመጓዝ ካሰባችሁ ፈሲሩ ትራቭል የትኬት ጉዳያችሁን በኃላፊነት ያጠናቅቃል። እንግልት የሌለበት ጉዞ ለማድረግ ስትፈልጉ በዋትስአፕ አግኙን፦
https://wa.me/qr/5CWCIMYBZLCJB1”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 17 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 17 July | +5 | |||
| 16 July | +7 | |||
| 15 July | +1 | |||
| 14 July | +9 | |||
| 13 July | +8 | |||
| 12 July | 0 | |||
| 11 July | +16 | |||
| 10 July | +3 | |||
| 09 July | 0 | |||
| 08 July | +2 | |||
| 07 July | +11 | |||
| 06 July | +11 | |||
| 05 July | +2 | |||
| 04 July | +10 | |||
| 03 July | +5 | |||
| 02 July | +5 | |||
| 01 July | +3 |
| 2 | No text... | 128 |
| 3 | ጌታቸው ሽፈራው አሁን ምን አድርጉ ነው የሚለን? አህመዲን ጀበል ድንገት ወልቃይት ገብቶ ከጌች አለቆች የሰሊጥ እርሻ ንግድ ጋር ፉክክር ገጥሞ ከሆነ በግልጽ ይንገረን! ካልሆነ ግን፣ ጌታቸው “የአለቆቹ የሰሊጥ እርሻ የክብር ዘብ” የሆነውን ቋሚ ተልዕኮውን ወደ ጎን ትቶ አህመዲን ላይ እንዲህ ነጋ ጠባ ብዕሩን የሚስልበት ምክንያት ፈጽሞ ሊገባኝ አልቻለም።
ዘዴው እጅግ አርጅቷል! የሙስሊሙን ፍትሐዊ የእኩልነት ጥያቄ ጠቅልሎ በአህመዲን ጀበል ጫንቃ ላይ በመጫን፣ እሱን በተለየ መልኩ ፍሬም በማድረግና እሱን ኮርነር ማድረግ ትልቁን ጥያቄ ለማዳፈን የሚደረገው ልፋት የተነቃበት ቀሽም ትግል ነው። ጤነኛ አእምሮ ያለው ሰው ሁሉ የሚቀበለውንና የሚጋራውን የመብት ጥያቄ፣ ዛሬ ላይ አስር ዓይነት የፕሮፓጋንዳ ዱቄት ቢነሰነሱበትም ሊደበቅ አይችልም።
የሚገርመው ደግሞ የጌታቸው ትጋት ነው! እዚያው እስራኤል ተቀምጦ፣ ከኢራን ሚሳኤሎች ሩምታ በተረፈበት የትርፍ ሰዓቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ያረጀ የፕሮፓጋንዳ ለመንዛት እንደ መስቀል ወፍ ብቅ እያለ በመጻፉ ትልቅ ለውጥ እንደሚፈጥር ያስባል። አህመዲን የሰጠው የሚዲያ ፍሬሚንግ (Media Framing) ስልጠና እኮ አደባባይ ላይ በግልጽ የተሰጠ፣ ዓለም አቀፍ መርህን የተከተለ ትምህርት ነው።
ታዲያ ጌታቸው ለምን እንዲህ አንጨረጨረው? መልሱ ቀላል ነው። “እንኳን እናንተ እኛም አውቀናል” የሚለው ጭንቀት ነው! ገና ከሰማያዊ ፓርቲ ዘመን ጀምሮ፣ በኋላም በጋዜጦቹ፣ እንዲሁም “ለአማራ ሕዝብ ቴሌቪዥን ልናቋቁም ነው” በሚል ስም ሕዝብ ያዋጣውን የአስራት ሚዲያን ገንዘብ ተከፋፍለው ከመሰወራቸው በፊት ሲያቅዷቸው የነበሩ የፍሬሚንግ ሴራዎች በነሱ ብቻ ታውቀው እንዲተገበሩ ይፈልጋል።
አለማየሁ ገላጋይ ስለ ንባብ በሚያወራበት አንድ ኢንተርቪው ላይ ፈላስፋው ኒቼ ሰዎች መጽሀፍ እንዲያነቡ ብዙም ፍላጎት እንደሌለው ይገልጻል። ለዚህ ምክንያቱ ፈላስፋው የሚያቀርበው የረባ መልስ ባይኖረውም ሰዎች ግን የዚህ ፍላጎቱ ምንጭ ሌላው ሰው የስራዎቹን ምንጮች በንባብ እንዳይደርስበት ስለሚሰጋ እንደሆነ የተሰጠውን አስተያየት ገልጾ ይናገራል። የሚዲያ ሰው የሆነው ጌታቸው ጭንቀትም“እኛን ብቻ ልናውቀው የሚገባውን እቅድ ሌላው አውቆት ለምን አስተማረው?”ይመስላል።
የራሱን ሕዝብ ስም እየሸጠ ገንዘብ ይዞ የጠፋ አካል፣ ሙስሊሙ ላይ ሲሰራ የነበረው የሚዲያ ደባ ሲነቃበትና ማኅበረሰቡ ራሱን ከፕሮፓጋንዳ የሚከላከልበት ስልጠና ሲሰጠው በዚህ ደረጃ የሚያንጨረጭረው ከሆነ፤ ጌታቸው ማንነቱንና የቆመበትን መሠረት በተዘዋዋሪ በደንብ እየነገረን ነው ማለት ነው።
ሀሳብዎትን ለማጋራት | 818 |
| 4 | No text... | 1 |
| 5 | በአላህ ፈቃድ ሦስተኛ ልጃችንን "ሙኒብ"ን በሰላም ታቅፈናል!አልሐምዱሊላህ። | 2 038 |
| 6 | ህንድ ሀገር የሚኖር አስቸኳይ የተፈለገ መድሀኒት በመግዛት ሊተባበረንና ሊልክልንና የሚችል Abu Yusra በግል ልታናግሩት ትችላላችሁ። መረጃውን ሼር በማድረግ አግዙን። | 3 124 |
| 7 | ህንድ ሀገር የሚኖር አስቸኳይ የተፈለገ መድሀኒት በመግዛት ሊተባበረንና ሊልክልንና የሚችል Abu Yusra በግል ልታናግሩት ትችላላችሁ። መረጃውን ሼር በማድረግ አግዙን። | 1 |
| 8 | ከሰሞኑ የሥላሴን የጾታ ጉዳይ በተመለከተ ፌስቡክ ላይ ባካፈልኳቸው ጽሑፎች ሥር የሚሰጡትን አስተያየቶች በቅርበት ስከታተል ቆይቻለሁ። ከሚሰጡት አስተያየቶች ውስጥ በሚያሳዝን ሁኔታ ከ70 እስከ 80 በመቶ የሚሆኑት ስድቦች ናቸው። ይሁንና አብዛኛዎቹን ስድቦች (በቀጥታ እኔ ላይ የተሰነዘሩ ከሆነ) የማጥፋትም ሆነ ሰዎችን ብሎክ የማድረግ ልምዱ የለኝም። ምክንያቱም ሰዎች ለስድብ የሚጋለጡት በተሳሳተ አስተምህሮ ተጽዕኖ ሥር ሲወድቁ መሆኑን ስለማምን፣ በገጹ ላይ ቆይተው በሌሎች ትምህርቶች ይታነጻሉ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።
ከስድቦቹ በተቃራኒ፣ ሐሳቤን በደንብ ተረድተው በምክንያት የሞገቱኝ ጥቂት ሰዎች ግን አሉ። ለእነሱም ጊዜ ባገኘሁ መጠን ተገቢውን ሪፕላይ ለመስጠትና የሰለጠነ ውይይት ለማድረግ ሞክሬያለሁ፤ ብዙዎቻችሁም ከዚሁ የውይይት ክፍል እንደምትማሩበትም ተስፋ አደርጋለሁ። በዚህ ለተሳተፋችሁ የክርስቲያን መምህራን ጨዋ ኮሜንታችሁም ትልቅ ክብር አለኝ።
ይሁን እንጂ፣ "ይህ ሁሉ 80 እና 90 በመቶ የሚሆን መንጋዊ ስድብ ከየት መጣ?" ብዬ ግን ሳስብ ነበር። ለካስ የብዙዎቹ ቲክቶክ መምህራቸው የሆነው የካራ እምነት ተከታዩ እፎይ፣ ጽሑፌን ወስዶ የወረዱ የዱርዬ ቃላትን በማዥጎድጎድ ሲሰድበኝ ከርሟል። ቲክቶክ ላይ ስላልነበርኩ በአጋጣሚ ቪዲዮውን የተመለከትኩት ዩቲዩብ ላይ ነው።
ከ90 በመቶ በላይ የሚሆነው የቪዲዮው ክፍል ስድቦችንና ዘለፋዎችን ያጨቀ ነው። ይህ ዓይነቱ አቀራረብ ትምህርት ከማስተማር ይልቅ ለቲክቶክ አልጎሪዝም ቅርብ የሆነውን የዱርዬ ገጸ ባሕሪን ተላብሶ መታየትን ስለሚመርጥ የተጠናወተው የተለመደ ባሕሪው ሊሆን ስለሚችል ብዙም አልፈርድበትም። የተወሰነ የስድብ "መርሀ ግብሩን" ለጊዜውም ቢሆን እኔ ላይ አውሎ ነቢዩን የሚሰድብበት ምላሱ ቢዚ መሆኑ በርግጥ ለኔ ጥሩ ስሜት የሚፈጥር እንጅ የሚያበሳጭ አይደለም።
እውነት ለመናገር፣ ላለፉት ቀናት ያነሳናቸውን የክርስትና አስተምህሮና የጉባኤያትን ታሪክ በተመለከተ የቀረቡትን ነጥቦች፣ የካራ እምነት ተከታዩ እፎይ አንድ በመቶ እንኳ በቅጡ ይረዳዋል ብዬ አላስብም። ሐሳቡን ለስድብ ከማመቻቸት ውጭ የነገረ መለኮት ግንዛቤው እጅግ አናሳ ነው። ከሱ በተሻለ ኮሜንት ላይ ሲሞግቱኝ የነበሩ ክርስቲያን መምህራን ስለሚወራውም ነገር ስለሚያወሩትም ነገር ከፍ ባለ መልኩ መረዳት አላቸው።
ለማንኛውም ሰማንያም ዘጠናም በመቶ የሆነውን ስድብ እንተወው፤ ለስድብ ምላሽ መስጠት ተገቢም አስፈላጊም አይደለም። ነገር ግን እዚያ ውስጥ ጥቂትም ቢሆን የተናገራቸው ነገሮች እውነት የሚመስለው ሰው ካለ፣ ማብራሪያ የሚሰጥ አጭር የቪዲዮ ፕሮግራም ለመሥራት እሞክራለሁ። ከዚህ ባለፈ ግን፣ ሰሞኑን ስጽፋቸው የነበሩት ጉዳዮች የካራ እምነት ተከታዩ እፎይንም ሆነ ተከታዮቹን በዚህ ደረጃ ነርቫቸውን ይነካዋል ብዬ ፈጽሞ አላሰብኩም ነበር። የሙስሊም ጠል አካላትን የህመም ኤሪያዎችን በዚህ አይነት መልኩ እየሞከሩ ማወቅ ለቀጣይ ስራዎች ስለሚያግዝ ጥሩ ተሞክሮ ነው።
በፌስቡክ የሚደረጉ ውይይቶችን ለመከታተል ይህንን ይጫኑ
© የሕያ ኢብኑ ኑህ | 4 194 |
| 9 | No text... | 3 386 |
| 10 | ተዋሕዶን ለመከላከል ስትለፉ፣ አባቶቻችሁ ባወገዙት በንስጥሮስ ትምህርት ውስጥ መውደቃችሁን ግን አስተውላችኋል?
ሰሞኑን "እግዚአብሔር ጾታ የለውም" በሚለው መከላከያ ስም፣ የገዛ ቤታችሁን መሠረት እያፈረሳችሁ ነው። የኤፌሶን ጉባኤ ያወገዘው ትምህርት ዛሬ በየገጾቻችሁ ላይ እየተንሸራሸረ መሆኑን ብዙዎቻችሁ ያወቃችሁ አይመስለኝም።
"ክርስቶስ ወንድ የሆነውና የተገረዘው በሰብእናው እንጂ በመለኮቱ አይደለም፤ መለኮትና ሥጋ አይገናኙም" የሚለው አባባል ላዩን ሲታይ እንደ ሥላሴ አማኝነታችሁ አምላካችሁን የሚከላከል ቢመስልም፣ በነገረ-መለኮት ሚዛን ግን ቀጥተኛ የንስጥሮስ ኑፋቄ ወይንም ክህደት ተብሎ የሚጠራው ነው።
የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መሠረታዊ የዶክትሪን መመሪያ የሆነው "ሃይማኖተ አበው" ትልቁን የተዋሕዶ ሕግ "የባሕርያት መለዋወጥ" (Communicatio Idiomatum) እንደሆነ ያስተምራል። መጽሐፉ "መለኮት የሥጋን ገንዘብ የራሱ አደረገ፤ ሥጋም የመለኮትን ገንዘብ የራሱ አደረገ" በማለት አበክሮ ይደነግጋል።
ተዋሕዶ (አንድ መሆን) ከተፈጸመ በኋላ "ይህ የሥጋ ሥራ ነው፣ ይህ ደግሞ የመለኮት ሥራ ነው" እያሉ ባሕርይን መነጣጠል፣ በ431 ዓ.ል በኤፌሶን ጉባኤ የተወገዘው የንስጥሮስ ዋነኛ "ኑፋቄ" መሆኑን ዘንግታችሁታል?
በነገረ-ክርስቶስ ትምህርታችሁ መሠረት፣ ቃል ሥጋ ሲሆን የተዋሐደው ረቂቅና ጾታ አልባ ሰብእናን ሳይሆን፣ የተሟላ አካልና የወንድነት ጾታ ያለውን ሥጋ ነው። ስለዚህ "ተገረዘ" ወይም "ወንድ ነው" ሲባል፣ ይህ ሁሉ የተፈጸመው ራሱ አምላክ በሆነው ቃል ላይ ነው እንጂ፣ ከመለኮት ተነጥሎ ለብቻው በሚቆም ሌላ ሥጋዊ አካል ላይ አይደለም።
የሰሞኑ ተከራካሪዎች የገዛ ቤታቸውን የሥነ-መለኮት ቀውስ ለመሸፈን ሲሉ፣ "ሥጋ ለብቻው ጾታ አለው፣ መለኮት ግን የለውም" እያሉ ክርስቶስን ለሁለት እየከፈሉት ይገኛሉ። ይህ ማለት ደግሞ ክርስቶስን ሁለት አካል፣ ሁለት ባሕርይ ወደማድረግ ያመራል።
የሶሻል ሚዲያ ክርክርን ለማሸነፍ ሲባል ብቻ የኤፌሶንን ጉባኤ ውሳኔ ማፍረስና የተወገዘውን የንስጥሮስን ትምህርት መልሶ ማንገሥ አማራጭ የጠፋበት መፍትሄ መስሏል። የሰውን እምነት ለመተቸት ከመሯሯጥ በፊት፣ የገዛ መጻሕፍቶቻችሁን አንብባችሁ ቀኖናችሁን ጠንቅቃችሁ ብታውቁ እንዲህ ያለ ታሪካዊ ውርደት ውስጥ አትወድቁም ነበር።
አንድ ጥያቄ ግን ልጠይቃችሁ፦ ክርስቶስን ለሁለት ከፍላችሁ "መገረዝና ጾታ የሥጋ ብቻ ነው" ካላችሁ፣ ለምን ንስጥሮስን አወገዛችሁት? የእርሱና የእናንተ ልዩነት ምንድነው?
© የሕያ ኢብኑ ኑህ | 3 860 |
| 11 | No text... | 2 436 |
| 12 | የሰሞኑን "ሥላሴ ጾታ አለው" ውዝግብ ተከትሎ የቀረበው ይቅርታና የተደረገው ማስተባበያ፣ አንድ እጅግ መሠረታዊ የሆነ የሥነ-መለኮት ጥያቄን በውስጡ አምቆ ይዟል። "መለኮት ረቂቅ ነው፣ ጾታ የለውም" የሚለውን አጠቃላይ መርህ ለማስጠበቅ ሲባል የሀይማኖት አባቱ በደቦ ቢወገዙም፣ የቤተ ክርስቲያኗ የራሷ የሆነው የነገረ-ክርስቶስ ዶክትሪን ግን ከዚህ ጋር የሚላተም ሌላ ግዙፍ እውነታን እንደሚያነሳ መረሳት የለበትም።
ይኸውም፣ ሥላሴዎች በአንድነታቸው ጾታ የላቸውም ቢባል እንኳ፣ ከሦስቱ አካላት አንዱ የሆነው «ወልድ» ሥጋን በመልበሱ ምክንያት የተሟላ የወንድነት ጾታ እንደነበረውና ግዝረትንም እንደፈጸመ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያስተምራል።
የክርስትና አስተምህሮ "እግዚአብሔር ቃል (ወልድ) ሰው ሆነ" ብሎ ሲያምን፣ ሰው የሆነው ጾታ በሌለው ረቂቅ ማንነት ሳይሆን፣ በተጨባጭ የወንድነት ተፈጥሮ ነው። ይህንንም የሉቃስ ወንጌል 2፡21 በሚከተለው መልኩ ያረጋግጠዋል፦
"ሊገርዙት ስምንት ቀን በሞላ ጊዜ፥ በማኅፀን ሳይረገዝ በመልአኩ እንደ ተባለ ስሙ ኢየሱስ ተብሎ ተጠራ።"
ይህ አንቀጽ፣ ኢየሱስ (እንደ ክርስትናው እምነት አምላክ የሆነው ወልድ) የተሟላ የሰውነት አካልና የወንድነት ጾታ እንደነበረው ማረጋገጫ ነው። ግዝረት ደግሞ በቀጥታ ከወንድ ልጅ የመራቢያ አካል ጋር የተያያዘ ሥርዓት በመሆኑ፣ የአንዱ የሥላሴ አካል (ወልድ) ጾታ ባለቤትነት ፈጽሞ ሊካድ የማይችል ሃይማኖታዊ እውነታ ነው።
ይህን የሥነ-መለኮት አጣብቂኝ የቀደምት አባቶችና የስኮላስቲክ ሊቃውንት በጥልቀት ተከራክረውበታል። በነገረ-ክርስቶስ ጥናት ውስጥ፣ "የባሕርያት መለዋወጥ" (Communicatio Idiomatum) የሚባል መሠረታዊ መርህ አለ። ይህ መርህ "መለኮት የሥጋን ገንዘብ የራሱ አደረገ፤ ሥጋም የመለኮትን ገንዘብ የራሱ አደረገ" የሚል ነው።
የእስክንድርያው ሊቅ ቄርሎስ "ተዋሕዶ" በሚለው ጽንሰ-ሐሳቡ፣ ቃል (ወልድ) ሥጋን ሲለብስ የሥጋን ባሕርይ (ጾታን፣ መወለድን፣ መራብን፣ መገረዝን) ሙሉ በሙሉ የራሱ (ገንዘቡ) እንዳደረገ ያስተምራል። በተመሳሳይ፣ እንደ ቶማስ አኩዊናስ ያሉት የኋለኛው ዘመን ስኮላስቲክ ሊቃውንትም፣ ክርስቶስ የተሟላ ሰብዓዊ ተፈጥሮን (ወንድነትን) መላበሱን በስፋት አብራርተዋል። በነዚህ አባቶች ትምህርት መሠረት፣ "ተገረዘ" የተባለው ተራ ሥጋ ሳይሆን፣ ራሱ አምላክ የሆነው ወልድ ነው።
እዚህ ላይ ነው እንግዲህ ትልቁ የሎጂክ እና የሥነ-መለኮት ቀውስ ወይንም ፓራዶክስ የሚፈጠረው። ዛሬ ላይ የሶሻል ሚዲያው መንጋ "እግዚአብሔር እንዴት ጾታ አለው ይባላል?" ብለው የነገረ-መለኮት ቅንዓት ያደረባቸው መስለው ሲቆጡ፣ የራሳቸውን መሠረታዊ ቀኖና በሚገባ ያልተረዱ መሆናቸውን ያሳብቃል።
ሥላሴን በአንድነት "ጾታ አልባ" ብሎ መደምደም፣ "ሰው ሆነ" የተባለውን አንዱን አካል (ወልድ) ተፈጥሮአዊ ማንነት ከመካድ ጋር እኩል ነው። የሃይማኖት አባቱ "ሥላሴ ጾታ አለው" በማለታቸው ቢወገዙም፣ ቢያንስ አንደኛው አካል በምድር ላይ በነበረው ቆይታ የተሟላ የጾታ መገለጫና የመራቢያ አካል (ለግዝረት የበቃ) እንደነበረው መዘንጋት ግን የለበትም።
ስለሆነም ሥላሴ በጅምላ ጾታ የላቸውም ብለህ ስለተናገርክ እግዚአብሔር ጾታ እንደነበረው ከማመን መሸሽና ማምለጥ ግን አትችልም..!
© የሕያ ኢብኑ ኑህ | 3 174 |
| 13 | No text... | 3 072 |
| 14 | ከሰሞኑ "ሥላሴ ጾታ አላቸው" በማለት ሲያስተምሩ የነበሩ አንድ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባት፣ በማኅበራዊ ሚዲያ በደረሰባቸው ከባድ ዘመቻና ውግዘት ምክንያት "ተሳስቻለሁ" ብለው ይቅርታ መጠየቃቸው ብዙዎቻችንን አስገርሟል ። ይሁን እንጂ ከዚህ ክስተት ጀርባ ልናነሳቸውና ልንመረምራቸው የሚገቡ ማኅበራዊ፣ ሃይማኖታዊ እና ተቋማዊ እውነታዎች ግን አሉ።
ይህንን ጉዳይ በነጻ አእምሮ ስንመዝነው፣ የሚከተሉት አበይት ነጥቦች ፍንትው ብለው ይታዩናል፦
1/ እኚህ አባት ይህንን ትምህርት ለ40 ዓመታት ሲያስተምሩት እንደነበር በገዛ አንደበታቸው መስክረዋል። ጥያቄው ያለው እዚህ ላይ ነው፤ የአንድን ሃይማኖት መሠረታዊ ዶክትሪን (ስለ ፈጣሪ ማንነት) የሚነካ ትልቅ ጉዳይ ለ40 ዓመታት ያህል ያለ ምንም ከልካይ ሲሰበክ፣ ያንን ሁሉ ተማሪ ሲያፈሩበት የነበረ ትምህርት በየትኛውም ሊቅም ሆነ ጉባኤ ሳይወገዙም ሆነ ሳይታረሙ በነጻነት ሲያስተምሩት ቆይተዋል። ይህ ትምህርት በሌላው ላይ ሲሳለቁ በነበሩ የቲክቶክ ጎረምሶች እይታ ውስጥ ባይገባና ሌላውን ሲተቹት ከነበረበት ጉዳይ አንጻር ባክፋየር አድርጎባቸው "ተዋረድን" የሚል ስሜት ፈጥሮ ዘመቻ ባያስከፍት ትምህርቱ ይቀጥል ነበር ማለት ነው።
ከዚህም በተጨማሪ የጾታን የሰዋሰው ፍችዎች በመዘርዘር እሳቸውን ሲከላከሉ የነበሩ ጎንደር አካባቢ የምናውቃቸው የሀይማኖት መምህራን ሳይቀር በጉዳዩ መደናገጣቸው አልቀረም። እውነታዎች የሚመዘኑትና የሚረጋገጡት በዕውቀትና በሊቃውንት ነው ወይስ ነገሩ አደባባይ ወጥቶ የሶሻል ሚዲያ አጀንዳ ሲሆን ብቻ በሚፈጠር ዘመቻ ነው?
2/ የሃይማኖት አባቱ ወደ ይቅርታ የመጡት የትምህርቱን ስሕተትነት በምክንያት ተረድተውትና አምነውበት ነው ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። የሰሞኑ የሶሻል ሚዲያ መንጋ ውግዘት፣ የሰውየውን ክብር የሚገፍ፣ እዚያው ቸርች ውስጥ በእድሜያቸው፣ ባበረከቱት አገልግሎት ሲያላግጥ እና በደሞዛቸው ጭምር ሲዘበት የነበረበት ጉዳይ ነው። የሰውን ልጅ የኑሮ መሠረትና ማኅበራዊ ክብር በማስፈራራት በሚመጣ ጫና ውስጥ፣ ማንም ሰው "ሆዴ በጀርባዬ" ብሎ ቃሉን ቢውጥ አይፈረድበትም። እዚህ ላይ ያሸነፈው እውነት ሳይሆን፣ የመንጋው ጉልበት ነው።
3/ ከሁሉ በላይ አእምሮን የሚኮረኩረው አስገራሚው ሽግግር ይህ ነው። በታሪክ እንደምናውቀው የቤተ ክርስቲያን የዶክትሪን ልዩነቶችና ውግዘቶች የሚካሄዱት፣ ሊቃውንት ተሰብስበው በሚያደርጉት የሲኖዶስ ጉባኤ ነበር። ዛሬ ግን የቤተ ክርስቲያኒቱ የውሳኔ አሰጣጥ ሥርዓት "ከጉባኤ ውግዘት ወደ ቲክቶክ ውግዘት" ተሸጋግሯል። የኒቅያና የቁስጥንጥንያ ጉባኤዎችን የቲክቶከሮች ‹ላይቭ› ስርጭት ተክቶታል፤ መጽሐፍትን አገላብጦ ከመሞገት ይልቅ፣ በአንድነት በመጮህና በማንቋሸሽ የሥነ-መለኮት ጉዳዮች ላይ የመጨረሻ ውሳኔ እየተሰጠ አየተመለከትን ነው። በዚህ ከቀጠላችሁ መሠረታዊ የሥላሴ ዶግማ ላይም ያልተመቿቹህ ነገሮችን በቀላሉ ማሳየት ከተቻለ ቤተ ክርሰቲያኗን በቀላሏ እጇን መጠምዘዝ የሚከብዳችሁ አይመስለኝም።
ማጠቃለያ፦
የአንድ እምነት መሠረታዊ ዶክትሪን በማህበራዊ ሚዲያ የጋራ ዘመቻ፣ እንዲሁም በመንጋው ጩኸት የሚወሰንና የሚቀየር ከሆነ፣ ሃይማኖታዊ ቀውሱ ምን ያህል ጥልቅ እንደሆነ መገመት አያዳግትም።
በኮሜንት ለሚደረግ ውይይት | 3 805 |
| 15 | No text... | 2 539 |
| 16 | "ምስጋና ለአላህ ይገባው የዓለማት ጌታ ለኾነው፤"
(الْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ)
(ቁርኣን 1፡2)
ሱረቱል ፋቲሃን በቀን ውስጥ ቢያንስ አስራ ሰባት ጊዜ እንቀራዋለን። ነገር ግን የዚህች ሱራ መክፈቻ የሆነችው "አልሐምዱሊላህ" የሚለው ሐረግ በውስጡ የያዘው ቋንቋዊ፣ ስነ-ልቦናዊ እና ታሪካዊ ሚስጥር እጅግ አስገራሚ ነው።
1. "ሐምድ" ወይስ "መድሕ"? (የቃላት ምርጫ ጥበብ)
በዓረብኛ ቋንቋ "ምስጋና" ወይም "ውዳሴ" የሚለውን ሐሳብ ለመግለጽ "መድሕ" (مَدْح) እና "ሐምድ" (حَمْد) የሚሉ ሁለት ቃላት አሉ። ታዲያ ቁርኣን ለምን "አል-መድሑ ሊላህ" አላለም?
• "መድሕ" (مَدْح) የሚለው ቃል ዝም ብሎ ማድነቅን ያሳያል። ለምሳሌ አንድን ውብ ተፈጥሮ ወይም የሚያምር ዕንቁ ስናይ እናደንቃለን (መድሕ እናደርጋለን)፤ ነገር ግን ያ ዕንቁ ለእኛ ያደረገልን የውለታ ጥቅም የለም። በተጨማሪም "መድሕ" ከፍርሃት ወይም ከግብዝነት (ለማስመሰል) ሊደረግ ይችላል።
• "ሐምድ" (حَمْد) ግን ከዚህ የተለየ ነው! "ሐምድ" ማለት በፍቅር፣ በክብር፣ እና በአመስጋኝነት ላይ የተመሰረተ ውዳሴ ነው። አንድን አካል "ሐምድ" የምናደርገው ለለራሱ ፍጹምነት እና ለእኛ ላደረገልን ጸጋና ውለታ ነው። ስለዚህ "አልሐምዱሊላህ" ስንል አላህን በፍጹምነቱ እያወደስነው፣ በሰጠን ጸጋ ደግሞ ከልብ እያመሰገነው ነው ማለት ነው።
2. "አል" (ال) - የስዋስው ታላቅነት
በ"ሐምድ" መጀመሪያ ላይ የመጣችው "አል" (ال) የተሰኘችው መስተአምር፣ በቋንቋው ህግ "ኢስቲግ-ራቅ" (الاستغراق) ትባላለች፤ ትርጉሙም "ሁለንተናዊነትን ማካተት" ማለት ነው። ይህች አንዲት ፊደል የምትነግረን፣ ከፊል ምስጋና ሳይሆን፣ በዓለም ላይ ያሉ የተሟሉና ፍጹም ምስጋናዎች ሁሉ በጠቅላላ የሚገቡት ለአላህ ብቻ መሆኑን ነው!
3. የ"ረብ" እና "አል-ዓለሚን" ጥምረት
"ረብ" (رَبّ) ማለት ፈጣሪ፣ ተንከባካቢ፣ አብልቶ አጠጪ እና ሁሉንም ነገር ከጅምሩ እስከ ፍጻሜው የሚያስተዳድር ማለት ነው። አላህ ለምን ምስጋና እንደሚገባው ሲያብራራ፣ "ምክንያቱም እርሱ የዓለማቱ ሁሉ ረብ ነውና" ይለናል።
በተጨማሪም ቁርኣን "አል-ዓለሚን" (عَالَمِينَ) በማለት በአንቀጹ መጨረሻ ላይ 'ኢን' (የኑን እና የሚም ድምጽ) በመጠቀም እጅግ ማራኪ የሆነ የድምጽ ሪትም (ፋሲላ) ይፈጥራል። ይህ የድምጽ አወቃቀር አንቀጹን በልብ ለማስታወስ ቀላል እና ጆሮን የሚማርክ ያደርገዋል።
የ"አልሐምዱሊላህ"ን ክብደት በተመለከተ ታላቁ ነቢይ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) አቡ ማሊክ አል-አሽዐሪይ ባስተላለፉት ትክክለኛ ሐዲስ ላይ እንዲህ ብለዋል፦
"ንጽህና የእምነት ግማሽ ነው፤ 'አልሐምዱሊላህ' ደግሞ ሚዛንን ትሞላለች..." (ሶሒሕ ሙስሊም፥ 223)
አንዲት ቃል፣ በውስጧ በያዘችው ጥልቅ የውዳሴ እና የምስጋና ሚስጥር ምክንያት፣ የቂያማን ቀን የክብደት ሚዛን ሙሉ ለሙሉ መሙላት ትችላለች! አልሐምዱሊላህ!!
ማጣቀሻዎች፦
ይህ ጹሁፍ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የተፍሲር ሥራዎች መሠረት በማድረግ የተጠናቀረ ነው፦
• መፋቲሑል ገይብ (ተፍሲር አል-ረዚ) - (በተለይም በፋቲሃ ዙሪያ ለሰሩት ጥልቅ የቃላት ትንታኔ)
• አት-ተሕሪር ወት-ተንዊር - ሙሐመድ አጥ-ጧሂር ኢብኑ አሹር
• አል-ከሻፍ - በኢማም አዝ-ዘመኽሸሪ
የቀደመውን ክፍል ለማንበብ ይህንን ጹሁፍ ይጫኑ | 3 009 |
| 17 | No text... | 2 412 |
| 18 | ሀምዛ ዞርትዚስ ከታዋቂው የሞሪታንያ ዓሊም ሸይኽ ዶ/ር ሙስጠፋ አል-ሸይባኒ ጋር ያደረጉትን እጅግ ጠቃሚ ውይይት ተመልክቼ ነበር። በተለይ በዚህ ዲጂታል ዘመን ዳዕዋ ስናደርግ ስለሚገጥሙን እንደ ኢጎ (እኔነት) እና የታዋቂነት ፈተናዎች እንዴት ማለፍ እንደምንችል ያነሱት ሀሳብ ልብ ይነካል። ቪዲዮውን እያየሁ የተወሰነ ማስታወሻ ለመያዝ የሞከርኩ ቢሆንም በመሀል የራሱ AI ሰመራይዝ ያደረገውን ስመለከት ግን ሀሳቤን በጥቅሉ ስለገለጸው እሱን በቡሌት ተርጉሞ ማስቀመጡን መርጫለሁ።
የውይይታቸው ዋና ዋና ነጥቦች እነሆ፡-
• ወደ አደባባይ እና ዲናዊ ስራ ከመውጣታችን በፊት በሌሊት ሶላት (ቂያሙል ለይል) እና በኢኽላስ (ቅንነት) ራሳችንን ማነፅ እና ከአላህ ጋር ያለንን ሚስጥራዊ ግንኙነት ማጠናከር አለብን።
• ቁርኣንን ለበረካ ብቻ ሳይሆን አስተሳሰባችንን ለመቅረፅ እና ራሳችንን ለመለወጥ ልንጠቀምበት ይገባል።
• ለዳዒ ትልቁ ጠላት ታዋቂነት ነው። ከተከታዮቻችን (followers) ቁጥር ይልቅ በዋናው አላማችን ላይ ብቻ ማተኮር አለብን፤ ስኬት ሁሌም ቢሆን የአላህ ስጦታ ነውና።
• ሱረቱ ዩሱፍ እንደሚያስተምረን ውጤታማ ዳዕዋ የረጅም ጊዜ እቅድን፣ ሰዎችን መረዳትን እና ትችትና ውድቀቶችን በትዕግስት ለማለፍ "ትልቅ ልብ" ሊኖረን ይገባል።
• ስኬት ከቤት ይጀምራል፦ የትዳር አጋራችን እና ቤተሰባችን ከውጭ ለሚገጥመንን ጫና መቋቋሚያ ትልቁ "መልህቃችን" ናቸው። ስለዚህ ጠንካራ እና አፍቃሪ የቤተሰብ ግንኙነት መገንባት ለስኬታችን ወሳኝ ነው።
በመጨረሻም ሀምዛ በራሱ ህይወት ተሞክሮ እንዳጠቃለለው፤ ምንም ያህል የተማርን እና የአካዳሚክ እውቀት ቢኖረንም፣ በዳዕዋ ስራችን ላይ ቁርኣን ሁሌም ቀዳሚ፣ ሀይለኛ እና ውጤታማው መመሪያችን ነው።
ሙሉ ውይይቱን በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ፦ | 4 142 |
| 19 | No text... | 3 674 |
| 20 | Voice message | 335 |
