የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe
﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student | ለንግድ፣ ለህክምና ወይም ለጉብኝት ወደ ቱርክ፣ ዱባይ እና የተለያዩ ሀገራት ለመጓዝ ካሰባችሁ ፈሲሩ ትራቭል የትኬት ጉዳያችሁን በኃላፊነት ያጠናቅቃል። እንግልት የሌለበት ጉዞ ለማድረግ ስትፈልጉ በዋትስአፕ አግኙን፦ https://wa.me/qr/5CWCIMYBZLCJB1
Показати більше📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe
Канал የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe (@yahyanuhe) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 21 233 підписників, посідаючи 3 709 місце в категорії Релігія і духовність та 1 588 місце у регіоні Ефіопія.
📊 Показники аудиторії та динаміка
З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 21 233 підписників.
За останніми даними від 08 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 288, а за останні 24 години на 1, загальне охоплення залишається високим.
- Статус верифікації: Не верифікований
- Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 22.32%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 8.90% реакцій від загальної кількості підписників.
- Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 4 740 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 889 переглядів.
- Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 99.
📝 Опис та контентна політика
Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
“﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student |
ለንግድ፣ ለህክምና ወይም ለጉብኝት ወደ ቱርክ፣ ዱባይ እና የተለያዩ ሀገራት ለመጓዝ ካሰባችሁ ፈሲሩ ትራቭል የትኬት ጉዳያችሁን በኃላፊነት ያጠናቅቃል። እንግልት የሌለበት ጉዞ ለማድረግ ስትፈልጉ በዋትስአፕ አግኙን፦
https://wa.me/qr/5CWCIMYBZLCJB1”
Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 09 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.
Триває завантаження даних...
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 09 липня | 0 | |||
| 08 липня | +2 | |||
| 07 липня | +11 | |||
| 06 липня | +11 | |||
| 05 липня | +2 | |||
| 04 липня | +10 | |||
| 03 липня | +5 | |||
| 02 липня | +5 | |||
| 01 липня | +3 |
| 2 | Немає тексту... | 576 |
| 3 | ተዋሕዶን ለመከላከል ስትለፉ፣ አባቶቻችሁ ባወገዙት በንስጥሮስ ትምህርት ውስጥ መውደቃችሁን ግን አስተውላችኋል?
ሰሞኑን "እግዚአብሔር ጾታ የለውም" በሚለው መከላከያ ስም፣ የገዛ ቤታችሁን መሠረት እያፈረሳችሁ ነው። የኤፌሶን ጉባኤ ያወገዘው ትምህርት ዛሬ በየገጾቻችሁ ላይ እየተንሸራሸረ መሆኑን ብዙዎቻችሁ ያወቃችሁ አይመስለኝም።
"ክርስቶስ ወንድ የሆነውና የተገረዘው በሰብእናው እንጂ በመለኮቱ አይደለም፤ መለኮትና ሥጋ አይገናኙም" የሚለው አባባል ላዩን ሲታይ እንደ ሥላሴ አማኝነታችሁ አምላካችሁን የሚከላከል ቢመስልም፣ በነገረ-መለኮት ሚዛን ግን ቀጥተኛ የንስጥሮስ ኑፋቄ ወይንም ክህደት ተብሎ የሚጠራው ነው።
የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ መሠረታዊ የዶክትሪን መመሪያ የሆነው "ሃይማኖተ አበው" ትልቁን የተዋሕዶ ሕግ "የባሕርያት መለዋወጥ" (Communicatio Idiomatum) እንደሆነ ያስተምራል። መጽሐፉ "መለኮት የሥጋን ገንዘብ የራሱ አደረገ፤ ሥጋም የመለኮትን ገንዘብ የራሱ አደረገ" በማለት አበክሮ ይደነግጋል።
ተዋሕዶ (አንድ መሆን) ከተፈጸመ በኋላ "ይህ የሥጋ ሥራ ነው፣ ይህ ደግሞ የመለኮት ሥራ ነው" እያሉ ባሕርይን መነጣጠል፣ በ431 ዓ.ል በኤፌሶን ጉባኤ የተወገዘው የንስጥሮስ ዋነኛ "ኑፋቄ" መሆኑን ዘንግታችሁታል?
በነገረ-ክርስቶስ ትምህርታችሁ መሠረት፣ ቃል ሥጋ ሲሆን የተዋሐደው ረቂቅና ጾታ አልባ ሰብእናን ሳይሆን፣ የተሟላ አካልና የወንድነት ጾታ ያለውን ሥጋ ነው። ስለዚህ "ተገረዘ" ወይም "ወንድ ነው" ሲባል፣ ይህ ሁሉ የተፈጸመው ራሱ አምላክ በሆነው ቃል ላይ ነው እንጂ፣ ከመለኮት ተነጥሎ ለብቻው በሚቆም ሌላ ሥጋዊ አካል ላይ አይደለም።
የሰሞኑ ተከራካሪዎች የገዛ ቤታቸውን የሥነ-መለኮት ቀውስ ለመሸፈን ሲሉ፣ "ሥጋ ለብቻው ጾታ አለው፣ መለኮት ግን የለውም" እያሉ ክርስቶስን ለሁለት እየከፈሉት ይገኛሉ። ይህ ማለት ደግሞ ክርስቶስን ሁለት አካል፣ ሁለት ባሕርይ ወደማድረግ ያመራል።
የሶሻል ሚዲያ ክርክርን ለማሸነፍ ሲባል ብቻ የኤፌሶንን ጉባኤ ውሳኔ ማፍረስና የተወገዘውን የንስጥሮስን ትምህርት መልሶ ማንገሥ አማራጭ የጠፋበት መፍትሄ መስሏል። የሰውን እምነት ለመተቸት ከመሯሯጥ በፊት፣ የገዛ መጻሕፍቶቻችሁን አንብባችሁ ቀኖናችሁን ጠንቅቃችሁ ብታውቁ እንዲህ ያለ ታሪካዊ ውርደት ውስጥ አትወድቁም ነበር።
አንድ ጥያቄ ግን ልጠይቃችሁ፦ ክርስቶስን ለሁለት ከፍላችሁ "መገረዝና ጾታ የሥጋ ብቻ ነው" ካላችሁ፣ ለምን ንስጥሮስን አወገዛችሁት? የእርሱና የእናንተ ልዩነት ምንድነው?
© የሕያ ኢብኑ ኑህ | 1 541 |
| 4 | Немає тексту... | 1 421 |
| 5 | የሰሞኑን "ሥላሴ ጾታ አለው" ውዝግብ ተከትሎ የቀረበው ይቅርታና የተደረገው ማስተባበያ፣ አንድ እጅግ መሠረታዊ የሆነ የሥነ-መለኮት ጥያቄን በውስጡ አምቆ ይዟል። "መለኮት ረቂቅ ነው፣ ጾታ የለውም" የሚለውን አጠቃላይ መርህ ለማስጠበቅ ሲባል የሀይማኖት አባቱ በደቦ ቢወገዙም፣ የቤተ ክርስቲያኗ የራሷ የሆነው የነገረ-ክርስቶስ ዶክትሪን ግን ከዚህ ጋር የሚላተም ሌላ ግዙፍ እውነታን እንደሚያነሳ መረሳት የለበትም።
ይኸውም፣ ሥላሴዎች በአንድነታቸው ጾታ የላቸውም ቢባል እንኳ፣ ከሦስቱ አካላት አንዱ የሆነው «ወልድ» ሥጋን በመልበሱ ምክንያት የተሟላ የወንድነት ጾታ እንደነበረውና ግዝረትንም እንደፈጸመ መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያስተምራል።
የክርስትና አስተምህሮ "እግዚአብሔር ቃል (ወልድ) ሰው ሆነ" ብሎ ሲያምን፣ ሰው የሆነው ጾታ በሌለው ረቂቅ ማንነት ሳይሆን፣ በተጨባጭ የወንድነት ተፈጥሮ ነው። ይህንንም የሉቃስ ወንጌል 2፡21 በሚከተለው መልኩ ያረጋግጠዋል፦
"ሊገርዙት ስምንት ቀን በሞላ ጊዜ፥ በማኅፀን ሳይረገዝ በመልአኩ እንደ ተባለ ስሙ ኢየሱስ ተብሎ ተጠራ።"
ይህ አንቀጽ፣ ኢየሱስ (እንደ ክርስትናው እምነት አምላክ የሆነው ወልድ) የተሟላ የሰውነት አካልና የወንድነት ጾታ እንደነበረው ማረጋገጫ ነው። ግዝረት ደግሞ በቀጥታ ከወንድ ልጅ የመራቢያ አካል ጋር የተያያዘ ሥርዓት በመሆኑ፣ የአንዱ የሥላሴ አካል (ወልድ) ጾታ ባለቤትነት ፈጽሞ ሊካድ የማይችል ሃይማኖታዊ እውነታ ነው።
ይህን የሥነ-መለኮት አጣብቂኝ የቀደምት አባቶችና የስኮላስቲክ ሊቃውንት በጥልቀት ተከራክረውበታል። በነገረ-ክርስቶስ ጥናት ውስጥ፣ "የባሕርያት መለዋወጥ" (Communicatio Idiomatum) የሚባል መሠረታዊ መርህ አለ። ይህ መርህ "መለኮት የሥጋን ገንዘብ የራሱ አደረገ፤ ሥጋም የመለኮትን ገንዘብ የራሱ አደረገ" የሚል ነው።
የእስክንድርያው ሊቅ ቄርሎስ "ተዋሕዶ" በሚለው ጽንሰ-ሐሳቡ፣ ቃል (ወልድ) ሥጋን ሲለብስ የሥጋን ባሕርይ (ጾታን፣ መወለድን፣ መራብን፣ መገረዝን) ሙሉ በሙሉ የራሱ (ገንዘቡ) እንዳደረገ ያስተምራል። በተመሳሳይ፣ እንደ ቶማስ አኩዊናስ ያሉት የኋለኛው ዘመን ስኮላስቲክ ሊቃውንትም፣ ክርስቶስ የተሟላ ሰብዓዊ ተፈጥሮን (ወንድነትን) መላበሱን በስፋት አብራርተዋል። በነዚህ አባቶች ትምህርት መሠረት፣ "ተገረዘ" የተባለው ተራ ሥጋ ሳይሆን፣ ራሱ አምላክ የሆነው ወልድ ነው።
እዚህ ላይ ነው እንግዲህ ትልቁ የሎጂክ እና የሥነ-መለኮት ቀውስ ወይንም ፓራዶክስ የሚፈጠረው። ዛሬ ላይ የሶሻል ሚዲያው መንጋ "እግዚአብሔር እንዴት ጾታ አለው ይባላል?" ብለው የነገረ-መለኮት ቅንዓት ያደረባቸው መስለው ሲቆጡ፣ የራሳቸውን መሠረታዊ ቀኖና በሚገባ ያልተረዱ መሆናቸውን ያሳብቃል።
ሥላሴን በአንድነት "ጾታ አልባ" ብሎ መደምደም፣ "ሰው ሆነ" የተባለውን አንዱን አካል (ወልድ) ተፈጥሮአዊ ማንነት ከመካድ ጋር እኩል ነው። የሃይማኖት አባቱ "ሥላሴ ጾታ አለው" በማለታቸው ቢወገዙም፣ ቢያንስ አንደኛው አካል በምድር ላይ በነበረው ቆይታ የተሟላ የጾታ መገለጫና የመራቢያ አካል (ለግዝረት የበቃ) እንደነበረው መዘንጋት ግን የለበትም።
ስለሆነም ሥላሴ በጅምላ ጾታ የላቸውም ብለህ ስለተናገርክ እግዚአብሔር ጾታ እንደነበረው ከማመን መሸሽና ማምለጥ ግን አትችልም..!
© የሕያ ኢብኑ ኑህ | 2 242 |
| 6 | Немає тексту... | 1 952 |
| 7 | ከሰሞኑ "ሥላሴ ጾታ አላቸው" በማለት ሲያስተምሩ የነበሩ አንድ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባት፣ በማኅበራዊ ሚዲያ በደረሰባቸው ከባድ ዘመቻና ውግዘት ምክንያት "ተሳስቻለሁ" ብለው ይቅርታ መጠየቃቸው ብዙዎቻችንን አስገርሟል ። ይሁን እንጂ ከዚህ ክስተት ጀርባ ልናነሳቸውና ልንመረምራቸው የሚገቡ ማኅበራዊ፣ ሃይማኖታዊ እና ተቋማዊ እውነታዎች ግን አሉ።
ይህንን ጉዳይ በነጻ አእምሮ ስንመዝነው፣ የሚከተሉት አበይት ነጥቦች ፍንትው ብለው ይታዩናል፦
1/ እኚህ አባት ይህንን ትምህርት ለ40 ዓመታት ሲያስተምሩት እንደነበር በገዛ አንደበታቸው መስክረዋል። ጥያቄው ያለው እዚህ ላይ ነው፤ የአንድን ሃይማኖት መሠረታዊ ዶክትሪን (ስለ ፈጣሪ ማንነት) የሚነካ ትልቅ ጉዳይ ለ40 ዓመታት ያህል ያለ ምንም ከልካይ ሲሰበክ፣ ያንን ሁሉ ተማሪ ሲያፈሩበት የነበረ ትምህርት በየትኛውም ሊቅም ሆነ ጉባኤ ሳይወገዙም ሆነ ሳይታረሙ በነጻነት ሲያስተምሩት ቆይተዋል። ይህ ትምህርት በሌላው ላይ ሲሳለቁ በነበሩ የቲክቶክ ጎረምሶች እይታ ውስጥ ባይገባና ሌላውን ሲተቹት ከነበረበት ጉዳይ አንጻር ባክፋየር አድርጎባቸው "ተዋረድን" የሚል ስሜት ፈጥሮ ዘመቻ ባያስከፍት ትምህርቱ ይቀጥል ነበር ማለት ነው።
ከዚህም በተጨማሪ የጾታን የሰዋሰው ፍችዎች በመዘርዘር እሳቸውን ሲከላከሉ የነበሩ ጎንደር አካባቢ የምናውቃቸው የሀይማኖት መምህራን ሳይቀር በጉዳዩ መደናገጣቸው አልቀረም። እውነታዎች የሚመዘኑትና የሚረጋገጡት በዕውቀትና በሊቃውንት ነው ወይስ ነገሩ አደባባይ ወጥቶ የሶሻል ሚዲያ አጀንዳ ሲሆን ብቻ በሚፈጠር ዘመቻ ነው?
2/ የሃይማኖት አባቱ ወደ ይቅርታ የመጡት የትምህርቱን ስሕተትነት በምክንያት ተረድተውትና አምነውበት ነው ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። የሰሞኑ የሶሻል ሚዲያ መንጋ ውግዘት፣ የሰውየውን ክብር የሚገፍ፣ እዚያው ቸርች ውስጥ በእድሜያቸው፣ ባበረከቱት አገልግሎት ሲያላግጥ እና በደሞዛቸው ጭምር ሲዘበት የነበረበት ጉዳይ ነው። የሰውን ልጅ የኑሮ መሠረትና ማኅበራዊ ክብር በማስፈራራት በሚመጣ ጫና ውስጥ፣ ማንም ሰው "ሆዴ በጀርባዬ" ብሎ ቃሉን ቢውጥ አይፈረድበትም። እዚህ ላይ ያሸነፈው እውነት ሳይሆን፣ የመንጋው ጉልበት ነው።
3/ ከሁሉ በላይ አእምሮን የሚኮረኩረው አስገራሚው ሽግግር ይህ ነው። በታሪክ እንደምናውቀው የቤተ ክርስቲያን የዶክትሪን ልዩነቶችና ውግዘቶች የሚካሄዱት፣ ሊቃውንት ተሰብስበው በሚያደርጉት የሲኖዶስ ጉባኤ ነበር። ዛሬ ግን የቤተ ክርስቲያኒቱ የውሳኔ አሰጣጥ ሥርዓት "ከጉባኤ ውግዘት ወደ ቲክቶክ ውግዘት" ተሸጋግሯል። የኒቅያና የቁስጥንጥንያ ጉባኤዎችን የቲክቶከሮች ‹ላይቭ› ስርጭት ተክቶታል፤ መጽሐፍትን አገላብጦ ከመሞገት ይልቅ፣ በአንድነት በመጮህና በማንቋሸሽ የሥነ-መለኮት ጉዳዮች ላይ የመጨረሻ ውሳኔ እየተሰጠ አየተመለከትን ነው። በዚህ ከቀጠላችሁ መሠረታዊ የሥላሴ ዶግማ ላይም ያልተመቿቹህ ነገሮችን በቀላሉ ማሳየት ከተቻለ ቤተ ክርሰቲያኗን በቀላሏ እጇን መጠምዘዝ የሚከብዳችሁ አይመስለኝም።
ማጠቃለያ፦
የአንድ እምነት መሠረታዊ ዶክትሪን በማህበራዊ ሚዲያ የጋራ ዘመቻ፣ እንዲሁም በመንጋው ጩኸት የሚወሰንና የሚቀየር ከሆነ፣ ሃይማኖታዊ ቀውሱ ምን ያህል ጥልቅ እንደሆነ መገመት አያዳግትም።
በኮሜንት ለሚደረግ ውይይት | 2 176 |
| 8 | Немає тексту... | 1 850 |
| 9 | "ምስጋና ለአላህ ይገባው የዓለማት ጌታ ለኾነው፤"
(الْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ)
(ቁርኣን 1፡2)
ሱረቱል ፋቲሃን በቀን ውስጥ ቢያንስ አስራ ሰባት ጊዜ እንቀራዋለን። ነገር ግን የዚህች ሱራ መክፈቻ የሆነችው "አልሐምዱሊላህ" የሚለው ሐረግ በውስጡ የያዘው ቋንቋዊ፣ ስነ-ልቦናዊ እና ታሪካዊ ሚስጥር እጅግ አስገራሚ ነው።
1. "ሐምድ" ወይስ "መድሕ"? (የቃላት ምርጫ ጥበብ)
በዓረብኛ ቋንቋ "ምስጋና" ወይም "ውዳሴ" የሚለውን ሐሳብ ለመግለጽ "መድሕ" (مَدْح) እና "ሐምድ" (حَمْد) የሚሉ ሁለት ቃላት አሉ። ታዲያ ቁርኣን ለምን "አል-መድሑ ሊላህ" አላለም?
• "መድሕ" (مَدْح) የሚለው ቃል ዝም ብሎ ማድነቅን ያሳያል። ለምሳሌ አንድን ውብ ተፈጥሮ ወይም የሚያምር ዕንቁ ስናይ እናደንቃለን (መድሕ እናደርጋለን)፤ ነገር ግን ያ ዕንቁ ለእኛ ያደረገልን የውለታ ጥቅም የለም። በተጨማሪም "መድሕ" ከፍርሃት ወይም ከግብዝነት (ለማስመሰል) ሊደረግ ይችላል።
• "ሐምድ" (حَمْد) ግን ከዚህ የተለየ ነው! "ሐምድ" ማለት በፍቅር፣ በክብር፣ እና በአመስጋኝነት ላይ የተመሰረተ ውዳሴ ነው። አንድን አካል "ሐምድ" የምናደርገው ለለራሱ ፍጹምነት እና ለእኛ ላደረገልን ጸጋና ውለታ ነው። ስለዚህ "አልሐምዱሊላህ" ስንል አላህን በፍጹምነቱ እያወደስነው፣ በሰጠን ጸጋ ደግሞ ከልብ እያመሰገነው ነው ማለት ነው።
2. "አል" (ال) - የስዋስው ታላቅነት
በ"ሐምድ" መጀመሪያ ላይ የመጣችው "አል" (ال) የተሰኘችው መስተአምር፣ በቋንቋው ህግ "ኢስቲግ-ራቅ" (الاستغراق) ትባላለች፤ ትርጉሙም "ሁለንተናዊነትን ማካተት" ማለት ነው። ይህች አንዲት ፊደል የምትነግረን፣ ከፊል ምስጋና ሳይሆን፣ በዓለም ላይ ያሉ የተሟሉና ፍጹም ምስጋናዎች ሁሉ በጠቅላላ የሚገቡት ለአላህ ብቻ መሆኑን ነው!
3. የ"ረብ" እና "አል-ዓለሚን" ጥምረት
"ረብ" (رَبّ) ማለት ፈጣሪ፣ ተንከባካቢ፣ አብልቶ አጠጪ እና ሁሉንም ነገር ከጅምሩ እስከ ፍጻሜው የሚያስተዳድር ማለት ነው። አላህ ለምን ምስጋና እንደሚገባው ሲያብራራ፣ "ምክንያቱም እርሱ የዓለማቱ ሁሉ ረብ ነውና" ይለናል።
በተጨማሪም ቁርኣን "አል-ዓለሚን" (عَالَمِينَ) በማለት በአንቀጹ መጨረሻ ላይ 'ኢን' (የኑን እና የሚም ድምጽ) በመጠቀም እጅግ ማራኪ የሆነ የድምጽ ሪትም (ፋሲላ) ይፈጥራል። ይህ የድምጽ አወቃቀር አንቀጹን በልብ ለማስታወስ ቀላል እና ጆሮን የሚማርክ ያደርገዋል።
የ"አልሐምዱሊላህ"ን ክብደት በተመለከተ ታላቁ ነቢይ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) አቡ ማሊክ አል-አሽዐሪይ ባስተላለፉት ትክክለኛ ሐዲስ ላይ እንዲህ ብለዋል፦
"ንጽህና የእምነት ግማሽ ነው፤ 'አልሐምዱሊላህ' ደግሞ ሚዛንን ትሞላለች..." (ሶሒሕ ሙስሊም፥ 223)
አንዲት ቃል፣ በውስጧ በያዘችው ጥልቅ የውዳሴ እና የምስጋና ሚስጥር ምክንያት፣ የቂያማን ቀን የክብደት ሚዛን ሙሉ ለሙሉ መሙላት ትችላለች! አልሐምዱሊላህ!!
ማጣቀሻዎች፦
ይህ ጹሁፍ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የተፍሲር ሥራዎች መሠረት በማድረግ የተጠናቀረ ነው፦
• መፋቲሑል ገይብ (ተፍሲር አል-ረዚ) - (በተለይም በፋቲሃ ዙሪያ ለሰሩት ጥልቅ የቃላት ትንታኔ)
• አት-ተሕሪር ወት-ተንዊር - ሙሐመድ አጥ-ጧሂር ኢብኑ አሹር
• አል-ከሻፍ - በኢማም አዝ-ዘመኽሸሪ
የቀደመውን ክፍል ለማንበብ ይህንን ጹሁፍ ይጫኑ | 2 194 |
| 10 | Немає тексту... | 1 953 |
| 11 | ሀምዛ ዞርትዚስ ከታዋቂው የሞሪታንያ ዓሊም ሸይኽ ዶ/ር ሙስጠፋ አል-ሸይባኒ ጋር ያደረጉትን እጅግ ጠቃሚ ውይይት ተመልክቼ ነበር። በተለይ በዚህ ዲጂታል ዘመን ዳዕዋ ስናደርግ ስለሚገጥሙን እንደ ኢጎ (እኔነት) እና የታዋቂነት ፈተናዎች እንዴት ማለፍ እንደምንችል ያነሱት ሀሳብ ልብ ይነካል። ቪዲዮውን እያየሁ የተወሰነ ማስታወሻ ለመያዝ የሞከርኩ ቢሆንም በመሀል የራሱ AI ሰመራይዝ ያደረገውን ስመለከት ግን ሀሳቤን በጥቅሉ ስለገለጸው እሱን በቡሌት ተርጉሞ ማስቀመጡን መርጫለሁ።
የውይይታቸው ዋና ዋና ነጥቦች እነሆ፡-
• ወደ አደባባይ እና ዲናዊ ስራ ከመውጣታችን በፊት በሌሊት ሶላት (ቂያሙል ለይል) እና በኢኽላስ (ቅንነት) ራሳችንን ማነፅ እና ከአላህ ጋር ያለንን ሚስጥራዊ ግንኙነት ማጠናከር አለብን።
• ቁርኣንን ለበረካ ብቻ ሳይሆን አስተሳሰባችንን ለመቅረፅ እና ራሳችንን ለመለወጥ ልንጠቀምበት ይገባል።
• ለዳዒ ትልቁ ጠላት ታዋቂነት ነው። ከተከታዮቻችን (followers) ቁጥር ይልቅ በዋናው አላማችን ላይ ብቻ ማተኮር አለብን፤ ስኬት ሁሌም ቢሆን የአላህ ስጦታ ነውና።
• ሱረቱ ዩሱፍ እንደሚያስተምረን ውጤታማ ዳዕዋ የረጅም ጊዜ እቅድን፣ ሰዎችን መረዳትን እና ትችትና ውድቀቶችን በትዕግስት ለማለፍ "ትልቅ ልብ" ሊኖረን ይገባል።
• ስኬት ከቤት ይጀምራል፦ የትዳር አጋራችን እና ቤተሰባችን ከውጭ ለሚገጥመንን ጫና መቋቋሚያ ትልቁ "መልህቃችን" ናቸው። ስለዚህ ጠንካራ እና አፍቃሪ የቤተሰብ ግንኙነት መገንባት ለስኬታችን ወሳኝ ነው።
በመጨረሻም ሀምዛ በራሱ ህይወት ተሞክሮ እንዳጠቃለለው፤ ምንም ያህል የተማርን እና የአካዳሚክ እውቀት ቢኖረንም፣ በዳዕዋ ስራችን ላይ ቁርኣን ሁሌም ቀዳሚ፣ ሀይለኛ እና ውጤታማው መመሪያችን ነው።
ሙሉ ውይይቱን በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ፦ | 2 646 |
| 12 | Немає тексту... | 2 510 |
| 13 | Голосове повідомлення | 335 |
| 14 | https://youtu.be/lVB7tDEdrFw | 341 |
| 15 | ‹‹እፎይ›› የተባለው ግለሰብ ሰሞኑን ያልጠበቀው አረንቋ ውስጥ ገብቶ እፎይታ ያጣ ይመስላል። ላለፉት ጊዜያት የራሱን ጓዳ (የገዛ ሃይማኖቱን) አቧራ የረሳው ይሄው ሰው፣ የእስልምናን አስተምህሮ ለመተቸት "አላህ እጅ አለው፣ እግር አለው ይላሉ" እያለ በማላገጥ የቲኦሎጂ "ሊቅ" ሆኖ ሲመጻደቅ ከርሟል። ሆኖም የሰው ቤት ሲሰልሉ መዋል የገዛ ቤትን ቃጠሎ አያጠፋምና፣ ዛሬ የገዛ ወንድሞቹና ሊቃውንቱ ከእግዚአብሔር አካላት ተሻግረው "እግዚአብሔር የመራቢያ አካል አለው ወይስ የለውም?" በሚል እጅግ አሳፋሪና ቀፋፊ አጀንዳ ላይ ሲተናነቁ አፉን ይዞ ከመደነቅ ውጪ ሌላ አማራጭ አላገኘም።
የገዛ ቴሌግራም ገጹ ላይ "ለሥላሴ የክፍል አካላት የሚሰጡ አንዳንድ መምህራን መኖራቸው ሲያስገርመን የነበረ ቢሆንም ጭራሽ ጾታ አላቸው የሚሉ... በመስማታችን አስደንግጦናል" እያለ የገዛ ቤቱን ጉድ አደባባይ አውጥቶታል። የፌዝ አዙሪት ማለት ይሄ ነው! ፈጣሪን ከፍጡር ጋር በማይመሳሰል፣ ልዕልናውንና ክብሩን በሚመጥን መልኩ የተገለጹትን የአላህን (ሱ.ወ) መለኮታዊ ባህሪያት በራሳቸው ጠባብ የሰውኛ ልክ ሰፍረው ለማላገጥ ሲሞክሩ፣ የራሳቸው የሥነ-መለኮት ግድግዳ ግን ፈርሶ መዓት መጣባቸው።
እኛ ከዚህ ቀደም "ሃይማኖተ አበው"ን እና መሰል የቤተክርስቲያኒቱን መጻሕፍት ዋቢ አድርገን፣ ፈጣሪ ጥፍር፣ ጸጉርና መሰል የሰውነት ክፍሎች እንዳሉት የሚገልጸውን የገዛ ትምህርታቸውን ስናወያያቸው፣ እውነታውን ለመጋፈጥ ድፍረት አጥተው ጆሮ ዳባ ልበስ ብለው ነበር። አሁን ግን ጉዳዩ ከጥፍርና ከጣት አልፎ፣ "ፈጣሪ የመራቢያ አካል አለው? ወንድ ነው ወይስ ሴት?" ወደሚል ከፈጣሪ ክብርና ልዕልና ጋር ፈጽሞ ወደማይገናኝ፣ እጅግ የወረደና ስንኩል አስተሳሰብ ውስጥ ተዘፍቀዋል። ከዚህ በላይ አዋራጅ ነገር ከየት ይመጣል? የሰው ዓይን ውስጥ ያለውን ጉድፍ ለማውጣት ሲታገሉ፣ የራሳቸውን መዋቅራዊ ግንድ ማየት የተሳናቸው ዕውር-ድንብሮች መሆናቸውን በተግባር አረጋገጡልን።
የእነ "እፎይ" እና የመሰሎቹ ትልቁ ችግር እውቀት ማነስ ብቻ ሳይሆን፣ አእምሯዊ ስንፈት ጭምር ነው። የራሳቸውን መሠረታዊ እምነት፣ ሥርዓተ-አምልኮ እና የሊቃውንቶቻቸውን መጻሕፍት እንኳ በቅጡ ሳያነቡ፣ በጭፍን ጥላቻ ብቻ የሌላውን እምነት ለማጥላላት ይሯሯጣሉ። የሰው እምነት ላይ ድንጋይ ለመወርወር ከመሞከር በፊት የራስን የመስታወት ቤት መፈተሽ እንደሚገባ አላወቁትም።
እውነትን በትክክል ሳያውቁና የገዛ ቤታቸውን ቆሻሻ ሳያጸዱ ለክርክር መነሳት የሚያመጣው የውርደት ካባ ይህ ነው። "እፎይ" ዛሬ የራሱ ቤት በሥነ-መለኮት ቀውስ ሲታመስና ጣዖት አምልኮን በሚያስንቅ ትርክት ሲበከል ማየቱ፣ የገዛ ድንቁርናውና የጥላቻው ፍሬ የሰጠው የክብር ሜዳሊያ ነው። የሌላውን ከማንቋሸሽ በፊት ቢያንስ የራስን አምላክ "ጾታ" እና "የመራቢያ አካል" ጉዳይ ከሊቃውንቶቻቸው ጋር ተወያይተው አንድ መቋጫ ላይ ቢደርሱ ይቀድም ነበር!
⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
https://t.me/Yahyanuhe | 5 570 |
| 16 | Немає тексту... | 4 144 |
| 17 | ኢትዮጵያ ፌደራላዊ ስርዓት መከተል ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ፣ የኢትዮጵያ ሙስሊም የመብት ጥያቄዎች አፈታት እጅግ በጣም ዘገምተኛ እና አሰልቺ ሆኗል። ለዓመታት የጮኽንለትና የታገልንለት መሰረታዊ መብት አሁንም መፍትሄ አልባ ሆኖ እየተንከባለለ ይገኛል።
በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ፣ ትላንትና ከመዋቅሩ ውጪ ሆነው ለህዝብ ሲታገሉ የነበሩ ሰዎች፣ ዛሬ የመጅሊሱን መንበር አግኝተው የተሻለ የመፍትሄ አካል እንዲሆኑ ሲጠበቁ የሚናቸው መደብዘዝ ግን እጅግ አሳዛኝ ነው።
ችግሮችን ከስር መሰረታቸው ቀድሞ ከመፍታት ይልቅ፣ አደጋ ሲከሰት ብቻ ከወቀሳ ለመዳን በሚመስል መልኩ ችግሩ ቦታ እየተገኙ መሯሯጥ የተለመደ ተግባር ሆኗል።
ህዝቡ እና ተማሪዎች በእንደዚህ አይነት ከባድ የማንነት ፈተና ውስጥ እያሉ፣ የመጅሊስ አመራሮቹ መኖራቸውን እራሱ የምናውቀው በሚታደሙበት የበዛ ድግስ ላይ በሚኖር ምስላቸው ነው። ያለ ቅጥ ከፍተኛ በጀት እየተያዘላቸው ከሚከወኑ ድግሶች ብዛት የተነሳ ለህዝብ ብሶት ጆሮ የሚሰጡበት ጊዜ ያገኙም አይመስሉም። ይህ አካሄድ ከእስልምና የአመራርና የአማና መርህ ጋር ፍፁም የሚጣረስ ነው።
ታላቁ ጌታችን አላህ ይህንን ከባድ የኃላፊነት ሚዛን በቅዱስ ቁርኣን እንዲህ ሲል ያስጠነቅቃል፡-
"እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህንና መልክተኛውን አትክዱ፡፡ እናንተ የምታውቁ ስትኾኑ አደራዎቻችሁንም አትክዱ፡፡" (አል-አንፋል 8፥27)
መሪነት ምቾት ሳይሆን ከባድ ፈተና ነው። በኃላፊነት ላይ ተቀምጦ ህዝብን ችላ ማለት የሚያስከትለውን አደጋ፣ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ በማለት አብራርተውታል፡-
"ማንኛውም አላህ የህዝብ መሪ ያደረገው ሰው፣ ህዝቡን በቅንነት ሳያገለግልና ሳይመክር (እያታለላቸው) ከሞተ፤ አላህ በርሱ ላይ ጀነትን እርም ያደርግበታል።" (ሰሒሕ አል-ቡኻሪ 7150)
መሪነት አገልጋይነት እንጂ የሰርክ ድግስ ታዳሚነት አይደለም። አመራሮች ወደ ህሊናቸው ተመልሰው፣ የተቀመጡበት ወንበር የህዝብ አደራ መሆኑን ተገንዝበው እውነተኛ መፍትሄ ሊያመጡ ይገባል። ጊዜያዊ ወቀሳን ለማምለጥ ከመሯሯጥ ይልቅ፣ ዘላቂ የሆነ የህዝብን እንባ የሚያብስ ጠንካራ ስራ ሊሰራ ይገባል!
የሕያ ኢብኑ ኑህ | 6 371 |
| 18 | Немає тексту... | 4 478 |
| 19 | በአማራ ክልል በሙስሊሙ ማኅበረሰብ ላይ የሚፈጸመው ግፍ፣ ሰቆቃና አፈና ማብቂያ ያጣ ይመስላል። ትናንት ምሽት በዳንግላ ከተማ የዒሻ ሶላትን አሰግደው ወደ ቤታቸው በመመለስ ላይ ሳሉ፣ በታጣቂዎች ተደብቀው የተገደሉት የሼኽ ሱፍያን አደም ሕልፈት፣ የዚህ መሪርና ቋሚ ሐዘናችን ቀጣይ ምዕራፍ ነው።
ሼኽ ሱፍያን ከ20 ዓመታት በላይ በመስጂድ ኢማምነት ያገለገሉ፣ ከሙስሊሙም ሆነ ሙስሊም ካልሆነው ወገን ጋር በሰላም የኖሩ የመስጂድ ኢማም ናቸው። ታዲያ እንዲህ ዓይነቱን የሰላም ሰው በጨለማ ደብቆ መግደል ከጀርባው ያለው መልእክት ምንድን ነው?
እውነታው አፍረጥርጦ የሚናገረው አንድ ነገር አለ፦ በክልሉ ውስጥ ሆን ተብሎ የሃይማኖት ግጭት ለማስነሳት፣ ሙስሊሙን ከማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ህልውናው ለማፈናቀል፣ እንዲሁም ማኅበረሰቡን መሪ አልባ ለማድረግ የሃይማኖት አባቶችን ነጥሎ የማጥቃት አደገኛ ዘመቻ በስፋት እየተተገበረ ይገኛል።
ይህ በታጣቂዎች የሚተገበረው እኩይ ተግባር፣ በአጋጣሚ የሚፈጸም ወንጀል አይደለም። ይልቁንም በተለያዩ የኦርቶዶክስ አክቲቪስቶችና ጽንፈኛ የሚዲያ አካላት፣ ለወራትና ለዓመታት ሲያረግዙትና ሲያቀነባብሩት የነበረው የጥላቻ ትርክትና የዘር ማጥፋት ፕሮፓጋንዳ የወለደው የትግበራ ውጤት ነው።
እነዚህ አካላት ዛሬ ለሚፈሰው የንጹሐን የሃይማኖት መሪዎች ደም የመጀመሪያ ተጠያቂዎች ናቸው። የሼኽ ሱፍያንን ንጹሕ ደም አላህ አይተወውም! ለቤተሰቦቻቸው፣ ለዳንግላ ሙስሊሞችና ለመላው የሀገራችን ሙስሊም ማኅበረሰብ አላህ መጽናናትን ይስጠን።
የዳንግላው ኢማም ግድያ | 5 696 |
| 20 | ለንግድ፣ ለህክምና ወይም ለጉብኝት ወደ ቱርክ፣ ዱባይ እና የተለያዩ ሀገራት ለመጓዝ ካሰባችሁ ፈሲሩ ትራቭል የትኬት ጉዳያችሁን በኃላፊነት ያጠናቅቃል። እንግልት የሌለበት ጉዞ ለማድረግ ስትፈልጉ በዋትስአፕ አግኙን፦
https://wa.me/qr/5CWCIMYBZLCJB1
+251911762080 | 4 899 |
