ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
کانال ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics" (@wahidcom) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 62 465 مشترک است و جایگاه 803 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 533 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 62 465 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 25 اوت, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 15 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 0 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 17.86% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 7.33% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 11 157 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 4 579 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ...”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 28 اوت, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 24 اوت | +22 | |||
| 23 اوت | 0 | |||
| 22 اوت | 0 | |||
| 21 اوت | 0 | |||
| 20 اوت | 0 | |||
| 19 اوت | 0 | |||
| 18 اوت | +1 | |||
| 17 اوت | 0 | |||
| 16 اوت | +3 | |||
| 15 اوت | +28 | |||
| 14 اوت | +34 | |||
| 13 اوت | +1 | |||
| 12 اوت | +20 | |||
| 11 اوت | +5 | |||
| 10 اوت | +8 | |||
| 09 اوت | +13 | |||
| 08 اوت | +7 | |||
| 07 اوت | 0 | |||
| 06 اوت | +5 | |||
| 05 اوت | +16 | |||
| 04 اوت | 0 | |||
| 03 اوت | +20 | |||
| 02 اوت | 0 | |||
| 01 اوت | +15 |
| 2 | ፍዝዝ እና ድንዝዝ ብላችሁ መውቀሱን እና መክሰሱን ትታችሁ በእናንተም መጽሐፍ አምላክ ሰዎች ሁሉ እንዲድኑ እና እውነቱን ወደ ማወቅ እንዲደርሱ ይፈልጋል፦
1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥4 እርሱ ሰዎች ሁሉ እንዲድኑ እና እውነቱን ወደ ማወቅ እንዲደርሱ "ይፈልጋል"። ὃς πάντας ἀνθρώπους θέλει σωθῆναι καὶ εἰς ἐπίγνωσιν ἀληθείας ἐλθεῖν.
በአዲሱ መደበኛ ትርጉም "ይፈልጋል" ለሚለው የገባው ቃል "ቴሌይ" θέλει ሲሆን ሥርወ ቃሉ "ቴሎ" θέλω ነው፥ "ቴሌማ" θέλημά ማለት "ፈቃድ"will" ማለት ሲሆን ቴሌማ እራሱ "ቴሌማ አፖዶሲስ" θέλημά ἀπόδοσις እና "ቴሌማ ፕሮታሲስ" θέλημά πρότᾰσῐς ተብሎ ለሁለት ይከፈላል። "ቴሌማ አፖዶሲስ" θέλημά ἀπόδοσις ማለት "ቀዳማይ ፈቃድ" ማለት ሲሆን ሰዎች ሁሉ እንዲድኑ እና እውነቱን ወደ ማወቅ እንዲደርሱ የአምላክ ቀዳማይ ፈቃድ ነው፥ "ቴሌማ ፕሮታሲስ" θέλημά πρότᾰσῐς ማለት "ደኃራይ ፈቃድ" ማለት ሲሆን ሰዎች ካመፁ ለገሃነም መሆናቸው የአምላክ ደኃራይ ፈቃድ ነው። ዮሐንስ ዘደማስቆ"John of Damascus" ይህንን ነጥብ አፋፍቶ እና አዳብሮ አስቀምጦታል፦
"እንዲሁም የአምላክ የመጀመሪያ ፍላጎት ሁሉም ሰው እንዲድን እና ወደ መንግሥቱ እንዲመጣ መሆኑን ማስታወስ አለብን! 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥4 እርሱ ቸር አምላክ ስለሆነ ከቸርነቱ እንድንካፈል እንጂ ለቅጣት አላዘጋጀንም፥ ነገር ግን እርሱ ፍትሓዊ አምላክ ስለሆነ ኃጢአተኞች ቅጣት እንዲደርስባቸው ፈቃዱ ነው። የመጀመሪያው የአምላክ ቀዳማይ ፈቃድ እና ደስታ፣ ከእርሱ የመነጨ፣ ተብሎ ይጠራል፥ ሁለተኛው ደግሞ የአምላክ ደኃራይ ፈቃድ እና ፍላጎት፣ መነሻው በእኛ ውስጥ ተብሎ ይጠራል"።
Exposition of the Orthodox Faith (John of Damascus) Book II(2) chapter 29
ዮሐንስ ዘደማስቆ ይህንን ያብራራው 1ኛ ጢሞቴዎስ 2፥4 ያለውን ዐውድ በተናገረበት ነው። ዮሐንስ አፈ ወርቅ"John Chrysostom" ይህንን ነጥብ ፊት የማያስመልስ አገንት የማያስቀልስ አድርጎ አስቀምጦታል፦
"ይህ ማለት ግን እርሱ ከምሩ ስለፈቀደ ነው፥ ይህ አንድ ኃያል እንደሚለው የእርሱ ምራዊ ፍላጎት ነው። መልካም ደስታ የሚለው ቃል በሁሉም ቦታ ማለት ቀዳማይ ፈቃድ ማለት ነው፥ ምክንያቱም ሌላ ፈቃድም አለ። ለምሳሌ፦ የመጀመሪያው ፈቃድ ኃጢአተኞች እንዳይጠፉ ነው፥ ሁለተኛው ፈቃድ ሰዎች ክፉ ከሆኑ እንዲጠፉ ነው"።
Homilies on Ephesians (Chrysostom) Homily 1 Ephesians 1፥5
እንግዲህ እነዚህ አበው ከተቀበላችሁ በቁርኣን የተቀመጠውን የአሏህን ፈቃድ ውልግድ እና ውልብድ፣ ወለም እና ዘለም፣ ውልፍጥ እና ዝልፍጥ ሳትሉ በቅጡ እና በአግባብ መረዳት ትችላላችሁ። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይወፍቃችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 11 402 |
| 3 | የአሏህ ፈቃድ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
81፥29 የዓለማቱ ጌታ አሏህ ካልፈቀደ አትፈቅዱም፡፡ وَمَا تَشَاءُونَ إِلَّا أَن يَشَاءَ اللَّهُ رَبُّ الْعَالَمِينَ
"መሺኣህ" مَشِئَة የሚለው ቃል "ሻአ" شَاءَ ማለትም "ፈቀደ" ከሚለው ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ፈቃድ"Will" ማለት ነው፥ የአሏህ ፈቃድ "መሺኣህ ሙቀደማህ" مَشِئَة مُقَدِّمَة እና "መሺኣህ ነቲጃህ" مَشِئَة نَتِيجَة ተብሎ ለሁለት ይከፈላል።
፨ "ሙቀደማህ" مُقَدِّمَة ማለት "ቀዳማይ"Antecedent" ማለት ሲሆን "መሺኣህ ሙቀደማህ" مَشِئَة مُقَدِّمَة ማለት "ቀደማይ ፈቃድ"Antecedent Will" ማለት ነው፥ አምላካችን አሏህ ለዓለማት በደልን የሚሻ አይደለም፡፡ ለባሪያዎቹ ከህደትን አይወድም፦
3፥108 አሏህ ለዓለማት በደልን የሚሻ አይደለም፡፡ وَمَا اللَّهُ يُرِيدُ ظُلْمًا لِّلْعَالَمِينَ
23፥31 አሏህ ለባሮቹ በደልን የሚሻ አይደለም፡፡ وَمَا اللَّهُ يُرِيدُ ظُلْمًا لِّلْعِبَادِ
ሰዎች ቢክዱ አሏህ ከከሓዲዎች የተብቃቃ ነው፥ ለባሪያዎቹም ከህደትን አይወድም። ብናምን ግን እርሱን ይወድልናል፦
39፥7 ብትክዱ አሏህ ከእናንተ የተብቃቃ ነው፥ ለባሪያዎቹም ከህደትን አይወድም። ብታመሰግኑ እርሱን ይወድላችኋል፡፡ إِن تَكْفُرُوا فَإِنَّ اللَّهَ غَنِيٌّ عَنكُمْ ۖ وَلَا يَرْضَىٰ لِعِبَادِهِ الْكُفْرَ ۖ وَإِن تَشْكُرُوا يَرْضَهُ لَكُمْ
አሏህ በሰዎች ገሩን ነገር መሻቱ እና በሰዎች ችግሩን አለመሻቱ የእርሱ ቀደማይ ፈቃድ ነው፦
2፥185 አሏህ በእናንተ ገሩን ነገር ይሻል፥ በእናንተም ችግሩን አይሻም፡፡ يُرِيدُ اللَّهُ بِكُمُ الْيُسْرَ وَلَا يُرِيدُ بِكُمُ الْعُسْرَ
፨ "ነቲጃህ" نَتِيجَة ማለት "ደኃራይ"Consequent" ማለት ሲሆን "መሺኣህ ነቲጃህ" مَشِئَة نَتِيجَة ማለት "ደኃራይ ፈቃድ"Consequent Will" ማለት ነው፥ አምላካችን አሏህ ለሰው የሰጠውን ፈቃድ በአሏህ ደኃራይ ፈቃድ ሥር ነው፦
81፥29 የዓለማቱ ጌታ አሏህ ካልፈቀደ አትፈቅዱም፡፡ وَمَا تَشَاءُونَ إِلَّا أَن يَشَاءَ اللَّهُ رَبُّ الْعَالَمِينَ
አሏህ በደኃራይ ፈቃዱ ለሰው ነጻ ፈቃድ ስለሰጠው ሰው የማመን እና የመካድ ፈቃድ አለው፦
18፥29 «እውነቱም ከጌታችሁ ነው፡፡ የፈቀደ ሰው ይመን፤ የፈቀደ ሰው ይካድ» በላቸው፡፡ وَقُلِ الْحَقُّ مِن رَّبِّكُمْ ۖ فَمَن شَاءَ فَلْيُؤْمِن وَمَن شَاءَ فَلْيَكْفُر
"የፈቀደ" ለሚለው የግሥ መደብ የገባው ቃል "ሻአ" شَاءَ ሲሆን ሰው ኸይር እና ሸር የሆኑ ሁለት አማራጭ መምረጥ የሚችል ፍጡር መሆኑን በቂ ማሳያ ነው፦
72፥14 የሠለሙ ሰዎች እነዚያ ቅንን መንገድ መረጡ፡፡ فَمَنْ أَسْلَمَ فَأُولَـٰئِكَ تَحَرَّوْا رَشَدًا
41፥17 ሰሙዶችማ መራናቸው ዕውርነትንም በቅንነት ላይ መረጡ፡፡ وَأَمَّا ثَمُودُ فَهَدَيْنَاهُمْ فَاسْتَحَبُّوا الْعَمَىٰ عَلَى الْهُدَىٰ
አሏህ ቢሻ ኖሮ በምድር ያሉት ሰዎች ሁሉ አማኝ ያረግ ነበር፥ በተቃራኒው አሏህ ቢሻ ኖሮ ከሓድያንን ባላጋሩ ነበር፦
10፥99 ጌታህም ቢሻ ኖሮ በምድር ያሉት ሰዎች ሁሉም የተሰበሰቡ ሆነው ባመኑ ነበር፡፡ ታዲያ አንተ ሰዎችን አማኞች እንዲኾኑ ታስገድዳለህን?። وَلَوْ شَآءَ رَبُّكَ لَـَٔامَنَ مَن فِى ٱلْأَرْضِ كُلُّهُمْ جَمِيعًا ۚ أَفَأَنتَ تُكْرِهُ ٱلنَّاسَ حَتَّىٰ يَكُونُوا۟ مُؤْمِنِينَ
6፥107 አሏህ ቢሻ ኖሮ ባላጋሩ ነበር፥ በእነርሱ ላይ ጠባቂ አላደረግንህም፡፡ አንተ በእነርሱ ላይ ኃላፊ አይደለህም፡፡ وَلَوْ شَاءَ اللَّهُ مَا أَشْرَكُوا ۗ وَمَا جَعَلْنَاكَ عَلَيْهِمْ حَفِيظًا ۖ وَمَا أَنتَ عَلَيْهِم بِوَكِيلٍ
አሏህ በቀዳማይ ፈቃዱ ሁሉንም አማኝ ቢያደርግ ማስገደድ ስለሆነ ከነጻ ፈቃድ ጋር ይጻረር ነበር፥ በተቃራኒው በቀዳማይ ፈቃዱ ከሓዲያን እንዳይክዱ ቢያደርግ ማስገደድ ስለሆነ ከግብረገባዊ ተጠያቂነት ጋር ይጻረር ነበር። ሰዎች በነጻ ፈቃዳቸው እንዲያምኑ መፍቀዱ እና በነጻ ፈቃዳቸው እንዲክዱ መፈቀዱ ደኃራይ ፈቃዱ ነው፥ አማንያን ወደ ጀነት የሚገቡት በእምነታቸው ምክንያት እና ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ነው፦
10፥9 እነዚያ ያመኑ እና መልካም ሥራዎችን የሠሩ ጌታቸው "በእምነታቸው ምክንያት" የገነትን መንገድ ይመራቸዋል፥ ከሥራቸው ወንዞች ይፈስሳሉ፡፡ በመጠቀሚያ ገነቶች ውስጥ ይኖራሉ፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَعَمِلُوا الصَّالِحَاتِ يَهْدِيهِمْ رَبُّهُم بِإِيمَانِهِمْ ۖ تَجْرِي مِن تَحْتِهِمُ الْأَنْهَارُ فِي جَنَّاتِ النَّعِيمِ
46፥14 እነዚያ የገነት ጓዶች ናቸው፡፡ በእርሷ ውስጥ ዘውታሪዎች ሲኾኑ፡፡ በዚያ "ይሠሩት በነበሩት ምክንያት" ታላቅን ምንዳ ይመነዳሉ፡፡ أُولَـٰئِكَ أَصْحَابُ الْجَنَّةِ خَالِدِينَ فِيهَا جَزَاءً بِمَا كَانُوا يَعْمَلُونَ
"በእምነታቸው ምክንያት" "ይሠሩት በነበሩት ምክንያት" የሚለው ይሰመርበት! በተቃራኒው ከሓዲያን ወደ ጀሀነም የሚገቡት በክህደታቸው ምክንያት እና ይሠሩት በነበሩት ምክንያት ነው፦
6፥30 «ትክዱት በነበራችሁት "ምክንያት" ቅጣቱን ቅመሱ» ይላቸዋል፡፡ قَالَ فَذُوقُوا الْعَذَابَ بِمَا كُنتُمْ تَكْفُرُونَ
10፥8 እነዚያ "ይሠሩት በነበሩት "ምክንያት" መኖሪያቸው በእሳት ውስጥ ነው፡፡ أُولَـٰئِكَ مَأْوَاهُمُ النَّارُ بِمَا كَانُوا يَكْسِبُونَ
"ትክዱት በነበራችሁት ምክንያት" "ይሠሩት በነበሩት ምክንያት" የሚለው ይሰመርበት! ስለዚህ የአሏህ ቀደማይ ፈቃድ ሰው ከጀሀነም እንዲድን ነው፥ ነገር ግን ሰው በምርጫው የጀሀነም መሆን ከፈለገ አሏህ ይህንን ጉዳይ መፍቀዱ የአሏህ ደኃራይ ፈቃዱ ነው። | 8 631 |
| 4 | ኢየሱስ መንገድ ነው!
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
5፥75 የመርየም ልጅ አልመሢሕ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ مَّا الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُلُ
ኢየሱስ ወደ ጌታ አምላክ የሚያደርስ መንገድ ስለሆነ ለፊልጶስ፦ "የእውነት እና የሕይወት መንገድ እኔ ነኝ" አለው፦
ዮሐንስ 14፥6 ኢየሱስም እንዲህ አለው፦ "የእውነት እና የሕይወት መንገድ እኔ ነኝ፥ በእኔ በኩል ካልሆነ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም"።(የ 2000 ዕትም 80 አሓዱ)
ግዕዙም በተመሳሳይ፦ "አነ ውእቱ ፍኖተ ጽድቅ ወሕይወት" እንደሚለው ተመልከት! "መንገድ" ማለት በመነሻ እና በመዳረሻ መካከል ያለ "መካከለኛ"Mediator" ነው፥ ካለ መካከለኛ መልእክተኛ በኩል ወደ ጌታ አምላክ መድረስ አይቻልም፦
1 ጢሞቴዎስ 1፥5 አንድ አምላክ አለና፥ በአምላክ እና በሰዎች መካከል ያለው "መካከለኛው" ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው። εἷς γὰρ Θεός, εἷς καὶ μεσίτης Θεοῦ καὶ ἀνθρώπων, ἄνθρωπος Χριστὸς Ἰησοῦς,
ይህ ጥቅስ በግልጽ እና በማያሻማ መልኩ "መካከለኛ" የተባለው ከአንዱ አምላክ ውጪ "ሰው" እንደሆነ ይናገራል፥ እዚህ አንቀጽ ላይ "መካከለኛ" ለሚለው የገባው ቃል "ሜሲተስ" μεσίτης ነው። ሙሴ ከኢየሱስ መላክ በፊት በብሉይ ኪዳን በአምላክ እና በሕዝቡ መካከል ሆኖ መልእክት ሲያስተላልፍ የነበረ መካከለኛ ነበረ፦
ዘዳግም 5፥5 እኔ የያህዌህን ቃል እነግራችሁ ዘንድ በዚያን ጊዜ በያህዌህ እና በእናንተ መካከል ቆሜ ነበር።
"በያህዌህ እና በእናንተ መካከል" የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! ሙሴ ተስፋው የተሰጠው ዘር መሢሑ እስኪመጣ "መካከለኛ" ነበረ፦
ገላትያ 3፥19 ሕጉ የመጣው በመላእክት በኩል በአንድ "መካከለኛ እጅ" ነበር።(አዲሱ መደበኛ ትርጉም) διαταγεὶς δι’ ἀγγέλων ἐν χειρὶ μεσίτου.
ሕግ የመጣው በመላእክት በኩል ነው፥ በተለይ "በስተ ቀኙም የእሳት ሕግ ነበረላቸው" የሚለውን ስንረዳ የእሳት ሕግ የተባለው ቶራህ ሲሆን ቅዱሳኑ የተባሉት መላእክት ናቸው።
ዘዳግም 33፥2 የሐዋርያት ሥራ 7፥53 ዕብራውያን 2፥2 ተመልከት!
ገላትያ 3፥19 "መካከለኛ" ለሚለው የገባው ቃል "ሜሲቶዩ" μεσίτου ሲሆን "እጅ" የሚለውን ለማገናዘብ የመጣ አገናዛቢ ነው፥ ይህም "መካከለኛ" የሚለው ቃል "ሙሴ" የሚለውን ስም ተክቶ የመጣ ነው። ዘኍልቍ 4፥37 ነህምያ 9፥14 ነህምያ 10፥29 ነህምያ 8፥15 ተመልከት!
"በመካከለኛ እጅ" የሚለው "በሙሴ እጅ" የሚለውን ለመተካት የመጣ እንደሆነ ካየን ዘንዳ ሙሴ "መካከለኛ" መባሉ አስረግጠን እና ረግጠን መናገር እንችላለን። መካከለኛው ሙሴ መካከለኛነቱ ለአንድ ማንነት ሳይሆን ለአዛዥ አምላክ እና ለታዛዥ ሕዝቡ ሲሆን አምላክ ግን አንድ ማንነት ነው፦
ገላትያ 3፥20 መካከለኛውም ለአንድ ብቻ አይደለም፥ አምላክ ግን አንድ ነው። ὁ δὲ μεσίτης ἑνὸς οὐκ ἔστιν, ὁ δὲ Θεὸς εἷς ἐστιν.
ኢዮብ 9፥32 እጁን በሁለታችን ላይ የሚያኖር "መካከለኛ" በመካከላችን ምነው በተገኘ። εἴθε ἦν ὁ μεσίτης ἡμῶν καὶ ἐλέγχων καὶ διακούων ἀνὰ μέσον ἀμφοτέρων·
ኢዮብ ከሙሴ በፊት በእርሱ እና በአምላኩ መካከል "መካከለኛ" እንዲኖር ተመኝቶ ከ 400 ዓመት በኃላ ሙሴ መካከለኛ ሆኖ ተነስቷል። ታዲያ ሙሴ ምን ነበር? ሰው እና ነቢይ ወይስ የአምላክ እና የሰው ውሕደት? "መካከለኛ" ማለት "የአምላክ እና የሰው ውሕደት" ነው" ብለው የሚቀጥፉ ሰዎች ሙሴ "መካከለኛ" መባሉን ሲረዱ ምን ይውጣቸው ይሆን? ኢየሱስም በአዲስ ኪዳን "መካከለኛ" የተባለው ሙሴ በተባለበት ቀመር እና ሒሣብ ነው፥ ይህም ሰው በአምላክ እና በሕዝቡ መካከል በሥራ እና በቃል ብርቱ ነቢይ የነበረው የናዝሬቱ ኢየሱስ ነው። የናዝሬቱ ኢየሱስ ከአምላክ እየሰማ ለሕዝቡ የሚናገር መካከለኛ ሰው ነበር፦
ሉቃስ 24፥19 በአምላክ እና በሕዝቡ ሁሉ ፊት በሥራ እና በቃል ብርቱ ነቢይ ስለ ነበረው ስለ ናዝሬቱ ስለ ኢየሱስ።
ዮሐንስ 8፥40 ነገር ግን አሁን ከአምላክ የሰማሁትን እውነት የነገርኋችሁን ሰው ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ?።
አምላክ ባለቤት ሲሆን ሰው ተሳቢ ነው፥ በባለቤት እና በተሳቢ መካከል "የሰማሁት" የሚል አጫፋሪ ግሥ አለ። ይህ ቁልጭ እና ፍንትው አድርጎ የሚያሳየው በላከው አምላክ እና በተላከው መካከለኛ ሰው ያለውን የማንነት እና የምንነት ልዩነት ነው። እርግጥ ነው! ኢየሱስ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፦
5፥75 የመርየም ልጅ አልመሢሕ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ مَّا الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُلُ
አምላካችን አሏህ በእርሱ መንገድ ከሚጓዙ ባሮቹ ያርገን! ከጥመት መንገድ ይጠብቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 9 389 |
| 5 | የአምልኮ መገዛት
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
3፥51 «አሏህ ጌታዬ እና ጌታችሁ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» አላቸው፡፡ إِنَّ اللَّهَ رَبِّي وَرَبُّكُمْ فَاعْبُدُوهُ ۗ هَـٰذَا صِرَاطٌ مُّسْتَقِيمٌ
"የባሕርይ መገዛዛት"Ontological subordination" ማለት በባሕርይ የማይመሳሰሉ ሆነው ነገር ግን በባሕርይ አንዱ ከሌላው ስለሚበልጥ በመካከላቸው ገዥ እና ተገዥ አለ። ለምሳሌ፦ ሰው እና እንስሳ በምንነት የተለያዩ "ባሕርይ"Essence" ስላላቸው ሰው ገዥ እንስሳ ተገዥ ነው፦
መዝሙር 8፥6 ሁሉን ከእግሮቹ በታች አስገዛህለት። πάντα ὑπέταξας ὑποκάτω τῶν ποδῶν αὐτοῦ,
እዚህ አንቀጽ ላይ ለመገዛት የገባው ሥርወ ቃል "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ሲሆን ገዥው ሰው ተገዥው በጎችን፣ ላሞችን፣ ሁሉ ደግሞም የምድረ በዳውን እንስሶች፣ የሰማይንም ወፎች፣ የባሕርን ዓሦች፣ በባሕር መንገድ የሚሄደውንም ሁሉ ነው፦
ዘፍጥረት 1፥28 የባሕርን ዓሦችና የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ "ግዙአቸው"።
መዝሙር 8፥8 በጎችን፣ ላሞችን፣ ሁሉ ደግሞም የምድረ በዳውን እንስሶች፣ የሰማይንም ወፎች፣ የባሕርን ዓሦች፣ በባሕር መንገድ የሚሄደውንም ሁሉ።
እንስሳ ሰውን የሚገዛው የባሕርይ ቢሆንም የአክብሮት መገዛት እንጂ የአምልኮ መገዛት አይደለም። ነገር ግን ኢየሱስ ፍጡር ስለሆነ ለአምላክ የሚገዛበትን ለማሳየት የገባው ሥርወ ቃል "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ነው፦
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥28 ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን "አምላክ" ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት "ይገዛል"። ὅταν δὲ ὑποταγῇ αὐτῷ τὰ πάντα, τότε καὶ αὐτὸς ὁ Υἱὸς ὑποταγήσεται τῷ ὑποτάξαντι αὐτῷ τὰ πάντα, ἵνα ᾖ ὁ Θεὸς πάντα ἐν πᾶσιν.
"ሆ ቴዎስ" ማለት "አምላክ" ማለት ሲሆን ኢየሱስ ሁሉን ላስገዛለት አምላክ ይገዛል፥ ለአምክ የሚደረግ መገዛት የባሕርይ መገዛት ሲሆን የአምልኮ መገዛት ነው፦
ያዕቆብ 4፥7 እንግዲህ ለአምላክ "ተገዙ"! ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል። ὑποτάγητε οὖν τῷ Θεῷ· ἀντίστητε δὲ τῷ διαβόλῳ, καὶ φεύξεται ἀφ’ ὑμῶν·
እዚህ አንቀጽ ላይ "ተገዙ" ለሚለው የገባው ቃል በተመሳሳይ "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ነው፥ ስለዚህ ኢየሱስ በምንነት ሰው፣ የሰው ልጅ፣ ፍጡር በማንነቱ ነቢይ፣ መልእክተኛ እና መሢሕ ስለሆነ ለአምላኩ የሚገዛው መገዛት የአምልኮ መገዛት ነው። ኢየሱስ በምድራዊ ቆይታው አምላኩን ሲለምን፣ ሲጸልይ፣ ሲሰግድለት፣ ሲጦም እና ሲፈራው ከማየት ባሻገር አሁን ላይ ሰማይ የአምላኩ አገልጋይ ነው፦
ዕብራውያን 8፥2 እርሱ በመቅደስ "አገልጋይ" ነው። τῶν ἁγίων λειτουργὸς
እዚህ አንቀጽ ላይ "ሌይቶሬዎርጎስ" λειτουργός ሲሆን የግሥ መደቡ "ላትሬኦ" λατρεύω ነው፥ "ላትሬያ" λατρεία ማለት "አምልኮ" ማለት ሲሆን ኢየሱስ በሰማይ ባለው መቅደስ "አምላኪ"(አገልጋይ) ሰለሆነ ሰማይ ላይ "አምላካችን" እያለ የሚናገርለት አምላክ አለው፦
ራእይ 19፥5 ድምፅም እንዲህ ሲል ከዙፋኑ ወጣ፦ “ባሪያዎቹ ሁሉ እርሱንም የምትፈሩት ታናናሾችና ታላላቆች ሆይ! "አምላካችንን" አመስግኑ”። καὶ φωνὴ ἀπὸ τοῦ θρόνου ἐξῆλθεν λέγουσα Αἰνεῖτε τῷ Θεῷ ἡμῶν, πάντες οἱ δοῦλοι αὐτοῦ, οἱ φοβούμενοι αὐτόν, οἱ μικροὶ καὶ οἱ μεγάλοι.
"አምላካችን" የሚለው ቃል ይሰመርበት! ከዙፋኑ የወጣው "አምላካችን" የሚል ድምፅ በዙፋኑ መካከል ካለው ከኢየሱስ የወጣ ድምፅ ነው፥ "በዚያን ጊዜ" ማለት በሚመጣበት ጊዜ ለአምላኩ የአምላኮ መገዛት በግልጽ እና በይፋ ይገዛል። የእርሱ አስተምሮት «አሏህ ጌታዬ እና ጌታችሁ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» የሚል ነው፦
3፥51 «አሏህ ጌታዬ እና ጌታችሁ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» አላቸው፡፡ إِنَّ اللَّهَ رَبِّي وَرَبُّكُمْ فَاعْبُدُوهُ ۗ هَـٰذَا صِرَاطٌ مُّسْتَقِيمٌ
ክርስቲያኖች ሆይ! ኢየሱስ ያመለከውን አምላክ እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይወፍቃችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 11 179 |
| 6 | "አባቴ ከሁሉ ይበልጣል" ሲል አብ ሁሉንም የሚበልጠው በባሕርይ ከሆነ ከኢየሱስም የሚበልጠው በባሕርይ ነው፥ "ከእኔ አብ ይበልጣል" ሲል በሰውነቱ ከሆነ አምላክ ሰውን የሚበልጠው በባሕርይ እንጂ በግብር አይደለም። "ክርስቶስ" ማለት "የተቀባ" ማለት ሲሆን የተቀባውን ሰው የቀባው አምላክ በባሕርይ ስለሚበልጠው "የክርስቶስም ራስ አምላክ ነው" ተብሏል።
በእርግጥ መሢሑ ለአሏህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፥ ቀራቢዎች የኾኑት መላእክትም አይጠየፉም፡፡ እርሱን ከመገዛት የሚጠየፍ እና የሚኮራም ሰው አሏህ ሁሉንም ወደ እርሱ በእርግጥ ይሰበስባቸዋል፦
፥172 መሢሑ ለአሏህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፥ ቀራቢዎች የኾኑት መላእክትም አይጠየፉም፡፡ እርሱን ከመገዛት የሚጠየፍ እና የሚኮራም ሰው አሏህ ሁሉንም ወደ እርሱ በእርግጥ ይሰበስባቸዋል፡፡ لَّن يَسْتَنكِفَ الْمَسِيحُ أَن يَكُونَ عَبْدًا لِّلَّهِ وَلَا الْمَلَائِكَةُ الْمُقَرَّبُونَ ۚ وَمَن يَسْتَنكِفْ عَنْ عِبَادَتِهِ وَيَسْتَكْبِرْ فَسَيَحْشُرُهُمْ إِلَيْهِ جَمِيعًا
ሳታመቻምቹ እና ሳታመናፍሱ አንዱን አምላክ አሏህን በብቸኝነት እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 1 |
| 7 | የአምልኮ መገዛት
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
3፥51 «አሏህ ጌታዬ እና ጌታችሁ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» አላቸው፡፡ إِنَّ اللَّهَ رَبِّي وَرَبُّكُمْ فَاعْبُدُوهُ ۗ هَـٰذَا صِرَاطٌ مُّسْتَقِيمٌ
"የባሕርይ መገዛዛት"Ontological subordination" ማለት በባሕርይ የማይመሳሰሉ ሆነው ነገር ግን በባሕርይ አንዱ ከሌላው ስለሚበልጥ በመካከላቸው ገዥ እና ተገዥ አለ። ለምሳሌ፦ ሰው እና እንስሳ በምንነት የተለያዩ "ባሕርይ"Essence" ስላላቸው ሰው ገዥ እንስሳ ተገዥ ነው፦
መዝሙር 8፥6 ሁሉን ከእግሮቹ በታች አስገዛህለት። πάντα ὑπέταξας ὑποκάτω τῶν ποδῶν αὐτοῦ,
እዚህ አንቀጽ ላይ ለመገዛት የገባው ሥርወ ቃል "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ሲሆን ገዥው ሰው ተገዥው በጎችን፣ ላሞችን፣ ሁሉ ደግሞም የምድረ በዳውን እንስሶች፣ የሰማይንም ወፎች፣ የባሕርን ዓሦች፣ በባሕር መንገድ የሚሄደውንም ሁሉ ነው፦
ዘፍጥረት 1፥28 የባሕርን ዓሦችና የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ "ግዙአቸው"።
መዝሙር 8፥8 በጎችን፣ ላሞችን፣ ሁሉ ደግሞም የምድረ በዳውን እንስሶች፣ የሰማይንም ወፎች፣ የባሕርን ዓሦች፣ በባሕር መንገድ የሚሄደውንም ሁሉ።
እንስሳ ሰውን የሚገዛው የባሕርይ ቢሆንም የአክብሮት መገዛት እንጂ የአምልኮ መገዛት አይደለም። ነገር ግን ኢየሱስ ፍጡር ስለሆነ ለአምላክ የሚገዛበትን ለማሳየት የገባው ሥርወ ቃል "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ነው፦
1ኛ ቆሮንቶስ 15፥28 ሁሉ ከተገዛለት በኋላ ግን "አምላክ" ሁሉ በሁሉ ይሆን ዘንድ በዚያን ጊዜ ልጁ ራሱ ደግሞ ሁሉን ላስገዛለት "ይገዛል"። ὅταν δὲ ὑποταγῇ αὐτῷ τὰ πάντα, τότε καὶ αὐτὸς ὁ Υἱὸς ὑποταγήσεται τῷ ὑποτάξαντι αὐτῷ τὰ πάντα, ἵνα ᾖ ὁ Θεὸς πάντα ἐν πᾶσιν.
"ሆ ቴዎስ" ማለት "አምላክ" ማለት ሲሆን ኢየሱስ ሁሉን ላስገዛለት አምላክ ይገዛል፥ ለአምክ የሚደረግ መገዛት የባሕርይ መገዛት ሲሆን የአምልኮ መገዛት ነው፦
ያዕቆብ 4፥7 እንግዲህ ለአምላክ "ተገዙ"! ዲያብሎስን ግን ተቃወሙ ከእናንተም ይሸሻል። ὑποτάγητε οὖν τῷ Θεῷ· ἀντίστητε δὲ τῷ διαβόλῳ, καὶ φεύξεται ἀφ’ ὑμῶν·
እዚህ አንቀጽ ላይ "ተገዙ" ለሚለው የገባው ቃል በተመሳሳይ "ሃይፖታሶ" ὑποτάσσω ነው፥ ስለዚህ ኢየሱስ በምንነት ሰው፣ የሰው ልጅ፣ ፍጡር በማንነቱ ነቢይ፣ መልእክተኛ እና መሢሕ ስለሆነ ለአምላኩ የሚገዛው መገዛት የአምልኮ መገዛት ነው። ኢየሱስ በምድራዊ ቆይታው አምላኩን ሲለምን፣ ሲጸልይ፣ ሲሰግድለት፣ ሲጦም እና ሲፈራው ከማየት ባሻገር አሁን ላይ ሰማይ የአምላኩ አገልጋይ ነው፦
ዕብራውያን 8፥2 እርሱ በመቅደስ "አገልጋይ" ነው። τῶν ἁγίων λειτουργὸς
እዚህ አንቀጽ ላይ "ሌይቶሬዎርጎስ" λειτουργός ሲሆን የግሥ መደቡ "ላትሬኦ" λατρεύω ነው፥ "ላትሬያ" λατρεία ማለት "አምልኮ" ማለት ሲሆን ኢየሱስ በሰማይ ባለው መቅደስ "አምላኪ"(አገልጋይ) ሰለሆነ ሰማይ ላይ "አምላካችን" እያለ የሚናገርለት አምላክ አለው፦
ራእይ 19፥5 ድምፅም እንዲህ ሲል ከዙፋኑ ወጣ፦ “ባሪያዎቹ ሁሉ እርሱንም የምትፈሩት ታናናሾችና ታላላቆች ሆይ! "አምላካችንን" አመስግኑ”። καὶ φωνὴ ἀπὸ τοῦ θρόνου ἐξῆλθεν λέγουσα Αἰνεῖτε τῷ Θεῷ ἡμῶν, πάντες οἱ δοῦλοι αὐτοῦ, οἱ φοβούμενοι αὐτόν, οἱ μικροὶ καὶ οἱ μεγάλοι.
"አምላካችን" የሚለው ቃል ይሰመርበት! ከዙፋኑ የወጣው "አምላካችን" የሚል ድምፅ በዙፋኑ መካከል ካለው ከኢየሱስ የወጣ ድምፅ ነው፥ "በዚያን ጊዜ" ማለት በሚመጣበት ጊዜ ለአምላኩ የአምላኮ መገዛት በግልጽ እና በይፋ ይገዛል። የእርሱ አስተምሮት «አሏህ ጌታዬ እና ጌታችሁ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» የሚል ነው፦
3፥51 «አሏህ ጌታዬ እና ጌታችሁ ነው፥ ስለዚህ አምልኩት! ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» አላቸው፡፡ إِنَّ اللَّهَ رَبِّي وَرَبُّكُمْ فَاعْبُدُوهُ ۗ هَـٰذَا صِرَاطٌ مُّسْتَقِيمٌ
ክርስቲያኖች ሆይ! ኢየሱስ ያመለከውን አምላክ እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይወፍቃችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም
አንዱን አምላክነቱ ለሰዎች የባሕርይ ሲሆን ኢየሱስ እራሱን ከሰዎች ጋር አካቶ "አምላካችን" ማለቱ በራሱ ኢየሱስ ለአንዱ አምላክ የሚገዛው የባሕርይ መገዛዛት ነው፦
ኢሳይያስ 61፥2 የተወደደችውን የያህዌን ዓመት "አምላካችን" የሚበቀልበትን ቀን እናገር ዘንድ እና የሚያለቅሱትን ሁሉ አጽናና ዘንድ ልኮኛል። לִקְרֹ֤א שְׁנַת־רָצֹון֙ לַֽיהוָ֔ה וְיֹ֥ום נָקָ֖ם לֵאלֹהֵ֑ינוּ לְנַחֵ֖ם כָּל־אֲבֵלִֽים׃
ራእይ 19፥5 ድምፅም እንዲህ ሲል ከዙፋኑ ወጣ፦ “ባሪያዎቹ ሁሉ እርሱንም የምትፈሩት ታናናሾችና ታላላቆች ሆይ! "አምላካችንን" አመስግኑ”። καὶ φωνὴ ἀπὸ τοῦ θρόνου ἐξῆλθεν λέγουσα Αἰνεῖτε τῷ Θεῷ ἡμῶν, πάντες οἱ δοῦλοι αὐτοῦ, οἱ φοβούμενοι αὐτόν, οἱ μικροὶ καὶ οἱ μεγάλοι.
"አምላካችን" የሚለው ቃል ይሰመርበት! ከዙፋኑ የወጣው "አምላካችን" የሚል ድምፅ በዙፋኑ መካከል ካለው ከኢየሱስ የወጣ ድምፅ ነው። የሥነ መለኮት ምሁር እና ተንታኝ ዮሐንስ ጊል "አምላካችን" የሚለው ኢየሱስ ስለመሆኑ ባብራሩበት የትርጓሜ መጽሐፍ እንዲህ ብለዋል፦
ራእይ 7፥17 "በዙፋኑ መካከል ያለው" በጉ እረኛቸው ይሆናልና። ὅτι τὸ Ἀρνίον τὸ ἀνὰ μέσον τοῦ θρόνου ποιμανεῖ αὐτούς
"ድምፅም እንዲህ ሲል ከዙፋኑ ወጣ" የሚለው በዙፋኑ ላይ ከተቀመጠው ከእግዚአብሔር አብ አይደለም፥ "አምላካችንን አመስግኑ" የሚለው ሐረግ በትክክለኛነት እና በአግባብነት በአብ ሊነገር አይችልም። ይልቁንም መካከለኛ ሆኖ ስለ አብ ለሕዝቡ፦ "አምላኬ እና አምላካችሁ፥ እና አባቴ እና አባታችሁ" ያለው በዙፋኑ መካከል ካለው በግ ከክርስቶስ ነው። Gill's Exposition of the Whole Bible Commentary, Revelation 19:5
ኢየሱስ ወደ አንዱ አምላክ ከሰገደ፣ ከጦመ፣ ከጸለየ እንዲሁ እርሱ ከፈራው እና ካመለከው ለአንድ አምላክ የሚገዛው መገዛት የባሕርይ መገዛዛት ነው። አንዱ አምላክ ከሁሉ ይበልጣል፥ "ሁሉ" በሚል ቃል ውስጥ ኢየሱስ ስለሚካተት ከእርሱ አብ በባሕርይ የሚበልጠው የበላይ ነው፦
ዮሐንስ 10፥29 የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል። ὁ Πατήρ μου ὃ δέδωκέν μοι πάντων μεῖζόν ἐστιν
ዮሐንስ 14፥28 "ከ"እኔ" አብ ይበልጣልና። ὁ Πατὴρ μείζων μού ἐστιν.
1ኛ ቆሮንቶስ 11፥3 የክርስቶስም ራስ አምላክ ነው። κεφαλὴ δὲ τοῦ Χριστοῦ ὁ Θεός. | 1 |
| 8 | በባይብል የገደለ ብቻ ሳይሆን አባቱን ወይም እናቱን የሚሰድብ ፈጽሞ ይገደላል፦
ዘሌዋውያን 27፥17 ሰውንም እስኪሞት ድረስ የሚመታ ፈጽሞ ይገደል።
ዘጸአት 21፥17 አባቱን ወይም እናቱን የሚሰድብ ፈጽሞ ይገደል።
ኢየሱስ ሲመጣ ደግሞ ሕጉ ጠብቆ እና አጥብቆ የሞት ፍርድ የሚገባው የገደለ ብቻ ሳይሆን በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ የሞት ፍርድ እንደሚገባው አበክሮ እና አዘክሮ ተናግሯል፦
ማቴዎስ 5፥21-22 ለቀደሙት፦ አትግደል እንደ ተባለ ሰምታችኋል፤ የገደለም ሁሉ ፍርድ ይገባዋል። እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል።
"የገደለም ሁሉ ፍርድ ይገባዋል" ማለት በዘሌዋውያን 27፥17 "ፈጽሞ ይገደል" የሚለው ከሆነ "በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል" ማለት "ፈጽሞ ይገደላል" ማለት ነው። እንደውም ኢየሱስ እንቅጩን ፍርጥ አርጎ፦ "በሰይፍ የሚገድል ማንም ቢኖር ራሱ በሰይፍ እንዲገደል ይገባዋል" ብሏል፦
ራእይ 13፥10 "በሰይፍ የሚገድል ማንም ቢኖር ራሱ በሰይፍ እንዲገደል ይገባዋል"።
በተጨማሪ ሬካብ እና ወንድሙ በዓና ወደ ኢያቡስቴ ቤት ገብተው ኢያቡስቴን ገድለዉት እራሱን ቆረጡት፥ ዳዊትም ሬካብን እና ወንድሙ በዓናን አስገድሎ እጃቸውን እና እግራቸውን እንዲቆረጥ አድርጓል፦
2 ሳሙኤል 4፥7 ወደ ቤትም በገቡ ጊዜ እርሱ በእልፍኙ በምንጣፉ ላይ ተኝቶ ሳለ መቱት፥ ገደሉትም፤ ራሱንም ቈርጠው ወሰዱት።
ሳሙኤል 4፥12 ዳዊትም ጕልማሶቹን አዘዘ፥ ገደሉአቸውም፤ እጃቸውን እና እግራቸውን ቈርጠው በኬብሮን በውኃ መቆሚያ አጠገብ አንጠለጠሉአቸው።
ኢዮአብ እና ሠራዊቱ በአሞን ከከተማ ይኖሩ የነበሩትን የአሞን ልጆች አውጥተው በመጋዝ ተረተሩአቸው፤ በመጥረቢያም ቈራረጡአቸው። ዳዊትም በአሞን ልጆች ከተሞች ሁሉ እንዲሁ አደረገ፦
1ኛ ዜና መዋዕል 20፥3 በውስጥዋም የነበሩትን ሕዝብ አውጥተው በመጋዝ ተረተሩአቸው፤ በመጥረቢያም ቈራረጡአቸው። ዳዊትም በአሞን ልጆች ከተሞች ሁሉ እንዲሁ አደረገ። ዳዊትም ሕዝቡም ሁሉ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ። καὶ τὸν λαὸν τὸν ἐν αὐτῇ ἐξήγαγε καὶ διέπρισε πρίοσι καὶ ἐν σκεπάρνοις σιδηροῖς καὶ ἐν διασχίζουσι· καὶ οὕτως ἐποίησε Δαυὶδ τοῖς πᾶσιν υἱοῖς ᾿Αμμών. καὶ ἀνέστρεψε Δαυὶδ καὶ πᾶς ὁ λαὸς αὐτοῦ εἰς ῾Ιερουσαλήμ.
"ዳዊትም በአሞን ልጆች ከተሞች ሁሉ እንዲሁ አደረገ" በማለት ዳዊት ልክ እንደ ኢዮአብ የአሞን ልጆችን በመጋዝ ተረተሩአቸው፤ በመጥረቢያም ቈራረጡአቸው፥ ግሪክ ሰፕቱአጀንት በዚህ ልክ ያስቀመጡት ሲሆን የ 2 ሺህ የኦርቶዶክስ ባይብል እና King James Version በዚህ አግባብ ተርጉመውታል፦
1 Chronicles 20፥3 KJV And he brought out the people that were in it, and cut them with saws, and with harrows of iron, and with axes. Even so dealt David with all the cities of the children of Ammon. And David and all the people returned to Jerusalem.
ነቢያችን"ﷺ" በቂሷስ ፍርድ እና ቅጣት ማድረጋቸው ነቢይ ላለመሆናቸው መስፈርት ከሆነ እንግዲያውስ በነካ አፋችሁን "ሙሴ፣ ኢየሱስ፣ ዳዊት የፈጣሪ ነቢይ አይደሉም" በሉና! ምን ይሻላችኃል ግን? ባይብል ሲጠቀስ እንቡር እና ፒርር እንዲሁ ቡፍ እና ኩፍ ከምትሉ ቁርኣንን እና ሐዲስን ለማሳጣት፣ ለማጭሸማቀቅ እና ለማሳቀቅ ፊጥ እና ቁጢጥ የምትሉትን ተዉ! አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 11 168 |
| 9 | የነቢያችን"ﷺ" ቅጣት
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
42፥40 የመጥፎም ነገረ ዋጋ ብጤዋ መጥፎ ናት፡፡ وَجَزَاءُ سَيِّئَةٍ سَيِّئَةٌ مِّثْلُهَا
"ቂሷስ" قِصَاص የሚለው ቃል "ቋሶ" قَاصَّ ማለትም "አመሳሰለ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ማመሳሰል" ማለት ነው፦
2፥179 ባለ አእምሮዎች ሆይ! ለእናንተም በማመሳሰል ሕግ ውስጥ ሕይወት አለላችሁ፡፡ ትጠነቀቁ ዘንድ ገዳይን መግደል ተደነገገላችሁ፡፡ وَلَكُمْ فِي الْقِصَاصِ حَيَاةٌ يَا أُولِي الْأَلْبَابِ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ማመሳሰል" ለሚለው ቃል የገባው "ቂሷስ" قِصَاص መሆኑ ልብ አድርግ! ሰው ጤናማ ሕይወት ይኖር ዘንድ አምላካችን አሏህ ቂሷስን ደንግጓል፥ በቂሷስ ነፍስ ያጠፋ ነፍሱ ይጠፋል፣ ዓይን ያጠፋ ዓይኑ ይጠፋል፣ አፍንጫም ያጠፋ አፍንጫው ይጠፋል፣ ጆሮም ያጠፋ ጆሮው ይጠፋል፣ ጥርስ የሰበረ ጥርሱ ይሰበራል። እነዚህ ቁስሎችን በቂሷስ ይፈታሉ፦
5፥45 በእነርሱም ላይ በውስጧ፦ «ነፍስ በነፍስ ዓይንም በዓይን አፍንጫም በአፍንጫ ጆሮም በጆሮ ጥርስም በጥርስ ይያዛል፥ ቁስሎችንም "ማመሳሰል" አለባቸው» ማለትን ጻፍን፡፡ وَكَتَبْنَا عَلَيْهِمْ فِيهَا أَنَّ النَّفْسَ بِالنَّفْسِ وَالْعَيْنَ بِالْعَيْنِ وَالْأَنفَ بِالْأَنفِ وَالْأُذُنَ بِالْأُذُنِ وَالسِّنَّ بِالسِّنِّ وَالْجُرُوحَ قِصَاصٌ
አሁንም እዚህ አንቀጽ ላይ "ማመሳሰል" ለሚለው ቃል የገባው "ቂሷስ" قِصَاص መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። መጥፎ ለሠሩ ሠዎች መጥፎ ቅጣት መቅጣት ቂሷስ ነው፥ የአሏህ መጽሐፍ ጭብጡ ቂሷስ ነው፦
42፥40 የመጥፎም ነገረ ዋጋ ብጤዋ መጥፎ ናት፡፡ وَجَزَاءُ سَيِّئَةٍ سَيِّئَةٌ مِّثْلُهَا
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 26
አነሥ እንደተረከው፦ “ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "የአሏህ መጽሐፍ ቂሷስ ነው"። أَنَّ أَنَسًا، حَدَّثَهُمْ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ كِتَابُ اللَّهِ الْقِصَاصُ ”.
የመጥፎም ነገረ ዋጋ ብጤዋ መጥፎ ስለሆነ በአንድ ወቅት ነቢያችን"ﷺ" እረኛቸውን ለዑረይናህ ሰዎች እንዲንከባከባቸው ሰተዋቸው ሳሉ የዑረይናህ ሰዎች ግን በተቃራኒው የነቢያችንን"ﷺ" እረኛ እጅና እግር ቆርጠው እና ዓይን አጥፍተው በመግደላቸው ቂሷስ ተደርጎ እጃቸውንና እግራቸውንም እንዲቆረጥ እና ዓይኖቻቸውም እንዲጠፋ ተደርጓል፦
ሡነን ነሣኢይ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 62
አነሥ እንደተረከው፦ "ሰዎች ከዑክል ወይም ከዑረይናህ ወደ ነቢዩ"ﷺ" መጡ፥ የመዲናህ አየር ንብረት ተጨናንቋል። ነቢዩም"ﷺ" ለእነርሱ፦ "ወደ ግመሎች ሂዱና ወተታቸውን ጠጡ እንዲሁ ሽንታቸውን ለመድኃኒት ተጠቀሙ" ብለው አዘዟቸው፥ እነርሱ ግን እረኛውን ገድለው ግመሎቹን ሰረቁ። ነቢዩም"ﷺ" ከኃላቸው ሰው ልከው እጃቸውን እና እግራቸውንም ቈረጡ፥ ዓይኖቻቸውም አጠፉ"። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ أَتَى النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم نَفَرٌ مِنْ عُكْلٍ أَوْ عُرَيْنَةَ فَأَمَرَ لَهُمْ - وَاجْتَوَوُا الْمَدِينَةَ - بِذَوْدٍ أَوْ لِقَاحٍ يَشْرَبُونَ أَلْبَانَهَا وَأَبْوَالَهَا فَقَتَلُوا الرَّاعِيَ وَاسْتَاقُوا الإِبِلَ فَبَعَثَ فِي طَلَبِهِمْ فَقَطَّعَ أَيْدِيَهُمْ وَأَرْجُلَهُمْ وَسَمَلَ أَعْيُنَهُمْ .
"ሠመለ" سَمَلَ ማለት "አጠፋ" ማለት ነው። አምላካችን አሏህ፦ "ዓይንም በዓይን ይያዛል፥ ቁስሎችንም "ማመሳሰል" አለባቸው" ስላለ እነዚህ ሰዎች የእረኛውን ዓይን ስላጠፉ ዓይናቸው እንዲጠፋ ተደርጓል፦
ሡነን ነሣኢይ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 78
አነሥ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" የእረኛውን ዓይኖች በማጥፋታቸው ምክንያት የእነዚያን ሰዎች ዓይኖች ብቻ አጥፍተው ነበር"። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ إِنَّمَا سَمَلَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم أَعْيُنَ أُولَئِكَ لأَنَّهُمْ سَمَلُوا أَعْيُنَ الرُّعَاةِ .
በኪታቡ አት-ተሕሪሙ አድ-ደም ዐውድ ውስጥ "እነዚያ" የተባሉት የዑረይናህ ሰዎች እንደሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። በባይብልም ቢሆን ዓይን ያጠፋ ዓይኑ እንዲጠፋ ትእዛዝ አለ፦
ዘጸአት 21፥23-25 ጕዳት ግን ቢያገኛት ሕይወት በሕይወት፣ ዓይን በዓይን፣ ጥርስ በጥርስ፣ እጅ በእጅ፣ እግር በእግር፣ መቃጠል በመቃጠል፣ ቍስል በቍስል፣ ግርፋት በግርፋት ይከፈል። | 9 502 |
| 10 | "ዳዊትም በአሞን ልጆች ከተሞች ሁሉ እንዲሁ አደረገ" በማለት ዳዊት ልክ እንደ ኢዮአብ የአሞን ልጆችን በመጋዝ ተረተሩአቸው፤ በመጥረቢያም ቈራረጡአቸው፥ ግሪክ ሰፕቱአጀንት በዚህ ልክ ያስቀመጡት ሲሆን የ 2 ሺህ የኦርቶዶክስ ባይብል እና King James Version በዚህ አግባብ ተርጉመውታል፦
1 Chronicles 20፥3 KJV And he brought out the people that were in it, and cut them with saws, and with harrows of iron, and with axes. Even so dealt David with all the cities of the children of Ammon. And David and all the people returned to Jerusalem.
ነቢያችን"ﷺ" በቂሷስ ፍርድ እና ቅጣት ማድረጋቸው ነቢይ ላለመሆናቸው መስፈርት ከሆነ እንግዲያውስ በነካ አፋችሁን "ሙሴ፣ ኢየሱስ፣ ዳዊት የፈጣሪ ነቢይ አይደሉም" በሉና! ምን ይሻላችኃል ግን? ባይብል ሲጠቀስ እንቡር እና ፒርር እንዲሁ ቡፍ እና ኩፍ ከምትሉ ቁርኣንን እና ሐዲስን ለማሳጣት፣ ለማጭሸማቀቅ እና ለማሳቀቅ ፊጥ እና ቁጢጥ የምትሉትን ተዉ! አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 1 |
| 11 | የነቢያችን"ﷺ" ቅጣት
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
42፥40 የመጥፎም ነገረ ዋጋ ብጤዋ መጥፎ ናት፡፡ وَجَزَاءُ سَيِّئَةٍ سَيِّئَةٌ مِّثْلُهَا
"ቂሷስ" قِصَاص የሚለው ቃል "ቋሶ" قَاصَّ ማለትም "አመሳሰለ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ማመሳሰል" ማለት ነው፦
2፥179 ባለ አእምሮዎች ሆይ! ለእናንተም በማመሳሰል ሕግ ውስጥ ሕይወት አለላችሁ፡፡ ትጠነቀቁ ዘንድ ገዳይን መግደል ተደነገገላችሁ፡፡ وَلَكُمْ فِي الْقِصَاصِ حَيَاةٌ يَا أُولِي الْأَلْبَابِ لَعَلَّكُمْ تَتَّقُونَ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ማመሳሰል" ለሚለው ቃል የገባው "ቂሷስ" قِصَاص መሆኑ ልብ አድርግ! ሰው ጤናማ ሕይወት ይኖር ዘንድ አምላካችን አሏህ ቂሷስን ደንግጓል፥ በቂሷስ ነፍስ ያጠፋ ነፍሱ ይጠፋል፣ ዓይን ያጠፋ ዓይኑ ይጠፋል፣ አፍንጫም ያጠፋ አፍንጫው ይጠፋል፣ ጆሮም ያጠፋ ጆሮው ይጠፋል፣ ጥርስ የሰበረ ጥርሱ ይሰበራል። እነዚህ ቁስሎችን በቂሷስ ይፈታሉ፦
5፥45 በእነርሱም ላይ በውስጧ፦ «ነፍስ በነፍስ ዓይንም በዓይን አፍንጫም በአፍንጫ ጆሮም በጆሮ ጥርስም በጥርስ ይያዛል፥ ቁስሎችንም "ማመሳሰል" አለባቸው» ማለትን ጻፍን፡፡ وَكَتَبْنَا عَلَيْهِمْ فِيهَا أَنَّ النَّفْسَ بِالنَّفْسِ وَالْعَيْنَ بِالْعَيْنِ وَالْأَنفَ بِالْأَنفِ وَالْأُذُنَ بِالْأُذُنِ وَالسِّنَّ بِالسِّنِّ وَالْجُرُوحَ قِصَاصٌ
አሁንም እዚህ አንቀጽ ላይ "ማመሳሰል" ለሚለው ቃል የገባው "ቂሷስ" قِصَاص መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። መጥፎ ለሠሩ ሠዎች መጥፎ ቅጣት መቅጣት ቂሷስ ነው፥ የአሏህ መጽሐፍ ጭብጡ ቂሷስ ነው፦
42፥40 የመጥፎም ነገረ ዋጋ ብጤዋ መጥፎ ናት፡፡ وَجَزَاءُ سَيِّئَةٍ سَيِّئَةٌ مِّثْلُهَا
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 65, ሐዲስ 26
አነሥ እንደተረከው፦ “ነቢዩም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ "የአሏህ መጽሐፍ ቂሷስ ነው"። أَنَّ أَنَسًا، حَدَّثَهُمْ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ كِتَابُ اللَّهِ الْقِصَاصُ ”.
የመጥፎም ነገረ ዋጋ ብጤዋ መጥፎ ስለሆነ በአንድ ወቅት ነቢያችን"ﷺ" እረኛቸውን ለዑረይናህ ሰዎች እንዲንከባከባቸው ሰተዋቸው ሳሉ የዑረይናህ ሰዎች ግን በተቃራኒው የነቢያችንን"ﷺ" እረኛ እጅና እግር ቆርጠው እና ዓይን አጥፍተው በመግደላቸው ቂሷስ ተደርጎ እጃቸውንና እግራቸውንም እንዲቆረጥ እና ዓይኖቻቸውም እንዲጠፋ ተደርጓል፦
ሡነን ነሣኢይ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 62
አነሥ እንደተረከው፦ "ሰዎች ከዑክል ወይም ከዑረይናህ ወደ ነቢዩ"ﷺ" መጡ፥ የመዲናህ አየር ንብረት ተጨናንቋል። ነቢዩም"ﷺ" ለእነርሱ፦ "ወደ ግመሎች ሂዱና ወተታቸውን ጠጡ እንዲሁ ሽንታቸውን ለመድኃኒት ተጠቀሙ" ብለው አዘዟቸው፥ እነርሱ ግን እረኛውን ገድለው ግመሎቹን ሰረቁ። ነቢዩም"ﷺ" ከኃላቸው ሰው ልከው እጃቸውን እና እግራቸውንም ቈረጡ፥ ዓይኖቻቸውም አጠፉ"። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ أَتَى النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم نَفَرٌ مِنْ عُكْلٍ أَوْ عُرَيْنَةَ فَأَمَرَ لَهُمْ - وَاجْتَوَوُا الْمَدِينَةَ - بِذَوْدٍ أَوْ لِقَاحٍ يَشْرَبُونَ أَلْبَانَهَا وَأَبْوَالَهَا فَقَتَلُوا الرَّاعِيَ وَاسْتَاقُوا الإِبِلَ فَبَعَثَ فِي طَلَبِهِمْ فَقَطَّعَ أَيْدِيَهُمْ وَأَرْجُلَهُمْ وَسَمَلَ أَعْيُنَهُمْ .
"ሠመለ" سَمَلَ ማለት "አጠፋ" ማለት ነው። አምላካችን አሏህ፦ "ዓይንም በዓይን ይያዛል፥ ቁስሎችንም "ማመሳሰል" አለባቸው" ስላለ እነዚህ ሰዎች የእረኛውን ዓይን ስላጠፉ ዓይናቸው እንዲጠፋ ተደርጓል፦
ሡነን ነሣኢይ መጽሐፍ 37, ሐዲስ 78
አነሥ እንደተረከው፦ "ነቢዩ"ﷺ" የእረኛውን ዓይኖች በማጥፋታቸው ምክንያት የእነዚያን ሰዎች ዓይኖች ብቻ አጥፍተው ነበር"። عَنْ أَنَسٍ، قَالَ إِنَّمَا سَمَلَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم أَعْيُنَ أُولَئِكَ لأَنَّهُمْ سَمَلُوا أَعْيُنَ الرُّعَاةِ .
በኪታቡ አት-ተሕሪሙ አድ-ደም ዐውድ ውስጥ "እነዚያ" የተባሉት የዑረይናህ ሰዎች እንደሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። በባይብልም ቢሆን ዓይን ያጠፋ ዓይኑ እንዲጠፋ ትእዛዝ አለ፦
ዘጸአት 21፥23-25 ጕዳት ግን ቢያገኛት ሕይወት በሕይወት፣ ዓይን በዓይን፣ ጥርስ በጥርስ፣ እጅ በእጅ፣ እግር በእግር፣ መቃጠል በመቃጠል፣ ቍስል በቍስል፣ ግርፋት በግርፋት ይከፈል።
በባይብል የገደለ ብቻ ሳይሆን አባቱን ወይም እናቱን የሚሰድብ ፈጽሞ ይገደላል፦
ዘሌዋውያን 27፥17 ሰውንም እስኪሞት ድረስ የሚመታ ፈጽሞ ይገደል።
ዘጸአት 21፥17 አባቱን ወይም እናቱን የሚሰድብ ፈጽሞ ይገደል።
ኢየሱስ ሲመጣ ደግሞ ሕጉ ጠብቆ እና አጥብቆ የሞት ፍርድ የሚገባው የገደለ ብቻ ሳይሆን በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ የሞት ፍርድ እንደሚገባው አበክሮ እና አዘክሮ ተናግሯል፦
ማቴዎስ 5፥21-22 ለቀደሙት፦ አትግደል እንደ ተባለ ሰምታችኋል፤ የገደለም ሁሉ ፍርድ ይገባዋል። እኔ ግን እላችኋለሁ፥ በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል።
"የገደለም ሁሉ ፍርድ ይገባዋል" ማለት በዘሌዋውያን 27፥17 "ፈጽሞ ይገደል" የሚለው ከሆነ "በወንድሙ ላይ የሚቆጣ ሁሉ ፍርድ ይገባዋል" ማለት "ፈጽሞ ይገደላል" ማለት ነው። እንደውም ኢየሱስ እንቅጩን ፍርጥ አርጎ፦ "በሰይፍ የሚገድል ማንም ቢኖር ራሱ በሰይፍ እንዲገደል ይገባዋል" ብሏል፦
ራእይ 13፥10 "በሰይፍ የሚገድል ማንም ቢኖር ራሱ በሰይፍ እንዲገደል ይገባዋል"።
በተጨማሪ ሬካብ እና ወንድሙ በዓና ወደ ኢያቡስቴ ቤት ገብተው ኢያቡስቴን ገድለዉት እራሱን ቆረጡት፥ ዳዊትም ሬካብን እና ወንድሙ በዓናን አስገድሎ እጃቸውን እና እግራቸውን እንዲቆረጥ አድርጓል፦
2 ሳሙኤል 4፥7 ወደ ቤትም በገቡ ጊዜ እርሱ በእልፍኙ በምንጣፉ ላይ ተኝቶ ሳለ መቱት፥ ገደሉትም፤ ራሱንም ቈርጠው ወሰዱት።
ሳሙኤል 4፥12 ዳዊትም ጕልማሶቹን አዘዘ፥ ገደሉአቸውም፤ እጃቸውን እና እግራቸውን ቈርጠው በኬብሮን በውኃ መቆሚያ አጠገብ አንጠለጠሉአቸው።
ኢዮአብ እና ሠራዊቱ በአሞን ከከተማ ይኖሩ የነበሩትን የአሞን ልጆች አውጥተው በመጋዝ ተረተሩአቸው፤ በመጥረቢያም ቈራረጡአቸው። ዳዊትም በአሞን ልጆች ከተሞች ሁሉ እንዲሁ አደረገ፦
1ኛ ዜና መዋዕል 20፥3 በውስጥዋም የነበሩትን ሕዝብ አውጥተው በመጋዝ ተረተሩአቸው፤ በመጥረቢያም ቈራረጡአቸው። ዳዊትም በአሞን ልጆች ከተሞች ሁሉ እንዲሁ አደረገ። ዳዊትም ሕዝቡም ሁሉ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ። καὶ τὸν λαὸν τὸν ἐν αὐτῇ ἐξήγαγε καὶ διέπρισε πρίοσι καὶ ἐν σκεπάρνοις σιδηροῖς καὶ ἐν διασχίζουσι· καὶ οὕτως ἐποίησε Δαυὶδ τοῖς πᾶσιν υἱοῖς ᾿Αμμών. καὶ ἀνέστρεψε Δαυὶδ καὶ πᾶς ὁ λαὸς αὐτοῦ εἰς ῾Ιερουσαλήμ. | 1 |
| 12 | ገድል
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
2፥193 ሁከት እስከማይገኝ እና ሃይማኖት ለአላህ ብቻ እስከሚኾን ድረስ "ተጋደሉዋቸው"። وَقَاتِلُوهُمْ حَتَّىٰ لَا تَكُونَ فِتْنَةٌ وَيَكُونَ الدِّينُ لِلَّهِ
"ገድል" የሚለው የግዕዝ ቃል "ተጋደለ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ውጊያ" "ትግል" "ፍልሚያ" "መዋጋት" "መጋደል" ማለት ነው፦
1ኛ ጢሞቴዎስ 1፥18 በእርሱ መልካም "ጦርነት" ትዋጋ ዘንድ ይህችን ትእዛዝ አደራ እሰጥሃለሁ።
እዚህ አንቀጽ ላይ "ጦርነት"War" ለሚለው በግዕዙ የገባው ቃል "ገድል" ሲሆን የግዕዙ መጽሐፍ "በከመ ተነብዮ ዘላዕሌከ ከመ ትጽናዕ በኵሉ "ገድል" ሠናይ" ይለዋል። ለቅዱሳን ነቢያት እና ሐዋርያት ከጥንት ጀምሮ የተሰጠ ሃይማኖት አንድ ሃይማኖት ሲሆን ለቅዱሳን ነቢያት እና ሐዋርያት ስለ ተሰጠ ሃይማኖት መጋደል ይገባል፦
ይሁዳ 1፥3 ለቅዱሳን አንድ ጊዜ ፈጽሞ ስለ ተሰጠ ሃይማኖት "እንድትጋደሉ" እየመከርኋችሁ እጽፍላችሁ ዘንድ ግድ ሆነብኝ።
ከጥንት የነበሩት ነቢያት በጦርነት ኃይለኞች ሆኑ፥ የባዕድ ጭፍሮችን አባረሩ፦
ዕብራውያን 11፥34 በጦርነት ኃይለኞች ሆኑ፥ የባዕድ ጭፍሮችን አባረሩ።
"ኢትዮጽያዊ ቄርሎስ" በሚል ማዕረግ የሚጠራው የሥነ መለኮት ምሁር አቦ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ሃይማኖትን በካዱት ሰዎች ላይ ያለው ብይን በብሉይ ኪዳን እና በአዲስ ኪዳን የሞት ፍርድ እንደሆነ ተናግሯል፦
መጽሐፈ ምሥጢር 2፥28 "እነሆ ሃይማኖትን በካዱት ላይ በብሉይ ኪዳን እና በአዲስ ኪዳን የሞት ትእዛዝ ወጣ"።
መጽሐፈ ምሥጢር 2፥29 "የሐዋርያት አለቃ ቅዱስ ጴጥሮስ ቀሌሜንጦስን፦ "ፍጽምት ስለምትሆን ሃይማኖት "ሰይፈህን መዘህ በኢየሱስ ክርስቶስ የማያምኑትን ከሀዲዎች እና ጨካኞች በብረት ሰይፍ ተዋጋ" አለው"።
መጽሐፈ ምሥጢር 2፥35 "በኢየሱስ ክርስቶስ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያንን እንድናነሳት እና እንድናጸናት ሥልጣንን አገኘን፥ ይህንንም የተላለፈ ሰይፍ ይለፍበት ብለው አሜን ወአሜን"።
ፍጽምት ስለምትሆን ሃይማኖት የብረት ሰይፍን መዞ መጋደል በብሉይ ኪዳን እና በአዲስ ኪዳን የታዘዘ መሆኑን አበክሮ ይገልጻል። ይህንን ከተረዳን ዘንዳ ዓለም እስኪሰማና እስኪስማማ ድረስ ጂሃድ በሐቅ እና በባጢል መካከል ያለ ትግል ነው፥ እስከ ፍርዱ ቀን ድረስ እውነት ለማንገሥ ሐሠትን ለማርከሥ መጋደል ግዴታ ነው፦
2፥193 ሁከት እስከማይገኝ እና ሃይማኖት ለአላህ ብቻ እስከሚኾን ድረስ "ተጋደሉዋቸው"። وَقَاتِلُوهُمْ حَتَّىٰ لَا تَكُونَ فِتْنَةٌ وَيَكُونَ الدِّينُ لِلَّهِ
አንቀጹን ልብ ብለነው ከሆነ "ተጋደሉ" እንጂ "ግደሉ" አይልም። ልዩነቱን እስቲ እንመልከት፦
2፥244 በአሏህ መንገድ "ተጋደሉ"፡፡ وَقَاتِلُوا فِي سَبِيلِ اللَّهِ
እነዚህ አንቀጽ ላይ ተጋደሉ" ለሚለው የገባው ቃል "ቃቲሉ" قَاتِلُوا ሲሆን "ግደሉ" ለማለት ቢፈልግ "ኡቅቱሉ" اقْتُلُوا ይሆን ነበር፦
2፥191 ባገኛችኋቸውም ስፍራ ሁሉ "ግደሉ"-ዋቸው፡፡ وَاقْتُلُوهُمْ حَيْثُ ثَقِفْتُمُوهُمْ
እነዚህ አንቀጽ ላይ ግደሉ" ለሚለው "ኡቅቱሉ" اقْتُلُوا ሲሆን መከላከል"Defensive" ሳይሆን "ማጥቃት"Offensive" ነው። ተጨማሪ አንድ አንቀጽ እንመልከት፦
9፥111 በአሏህ መንገድ ላይ ይጋደላሉ፣ ይገድላሉ፣ ይገደላሉ"፡፡ يُقَاتِلُونَ فِي سَبِيلِ اللَّهِ فَيَقْتُلُونَ وَيُقْتَلُونَ
አያችሁ? "ይጋደላሉ" ለሚለው የገባው ቃል "ዩቃቲሉነ" يُقَاتِلُونَ ሲሆን፣ "ይገድላሉ" ለሚለው ግን "የቅቱሉነ" يَقْتُلُونَ ነው። "ቀትል" قَتْل ማለት እና "ቂታል" قِتَال ማለት ሁለት ለየቅል ቃላት እና ትርጉም አላቸው፥ "ቂታል" قِتَال ማለት በግዕዝ "ገድል" ማለት ነው። "ተጋደሉ" የግሥ መደብ ሲሆን "ገድል" የስመ መደብ ነው፥ ስለዚህ "ገድል" ማለት ጂሃዱል ቀልቢያህ፣ ጂሃዱል ቀውሊያህ እና ጂሃዱል ዐመሊያህ ተጠቅሞ የአሏህን ንግግር የበላይ ማድረግ ነው። ሁከት እስከማይገኝ እና ሃይማኖት ለአሏህ ብቻ እስከሚኾን ድረስ ከኩፋሮች ጋር እንጋደላለን፥ ዓለም በአሏህ ሸሪዓህ እስክትደዳደር ድረስ መጋደሉ ይቀጥላል። ተወዳጁ ነቢያች"ﷺ" የታዘዙበት መርሕ ይህ ነው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 3 ሐዲስ 18
ኢብኑ ዑመር እንደተረከው፦ የአሏህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “ሰዎችን "ከአሏህ በቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ አለመኖሩን እና ሙሐመድም የአሏህ መልእክተኛ ነው" ብለው እስኪመሰክሩ፣ ሶላትን እስኪቆሙ እና ዘካህን እስኪያወጡ ድረስ "እንድጋደላቸው" ታዝዣለሁ"። عَنِ ابْنِ عُمَرَ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ " أُمِرْتُ أَنْ أُقَاتِلَ النَّاسَ حَتَّى يَشْهَدُوا أَنْ لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ وَأَنَّ مُحَمَّدًا رَسُولُ اللَّهِ، وَيُقِيمُوا الصَّلاَةَ، وَيُؤْتُوا الزَّكَاةَ
እዚህም ሐዲስ ላይ "አን ኡቃቲለ" أَنْ أُقَاتِلَ ማለት "እንድጋደል" ማለት ሲሆን "እንድገድል" ለማለት ቢሆን ኖሮ "አን አቅቱለ" أَنْ أَقْتُلَ ይሆን ነበር፥ "እንድገድል" ቢል ኖሮ "በሃይማኖት መስገደድ የለም" ከሚል መርሕ ጋር ይጋጭ ነበር። ገድል አጠቃላይ ሦስቱንም የጂሃድ ክፍል የሚይዝ ቃል ነው፦
ሪያዱ አስ-ሷሊሒን መጽሐፍ 1, ሐዲስ 184
አቢ ሠዒድ አል-ኹድሪይ”ረ.ዐ.” እንደተረከው፦ “የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ፦ “ከእናንተ ውስጥ እኩይ ነገር ያየ በእጁ ይቀይረው፣ ካልቻለ በምላሱ ያውግዝ፣ ይህንንም ካልቻለ በልቡ ይጥላው። በልብ መጥላት ደካማው ኢማን ነው”። عن أبي سعيد الخدري رضي الله عنه قال: سمعت رسول الله صلى الله عليه وسلم يقول: “من رأى الخد منكرًا فليغيره بيده ، فإن لم يستطع فبلسانه، فإن لم يستطع فبقلبه وذلك أضعف الإيمان
በእጅ፣ በምላስ እና በልቡ ያልታገለ የጎመንዘር ያህል ኢማን የለውም። ምእምናን ማለት በገንዘቦቻቸው እና በነፍሶቻቸውም በአሏህ መንገድ የታገሉት ብቻ ናቸው፥ እነዚያ እነርሱ እውነተኞቹ ናቸው፦
49፥15 ምእምናን እነዚያ በአሏህ እና በመልእከተኛው ያመኑት ከዚያም ያልተጠራጠሩት “በገንዘቦቻቸው እና በነፍሶቻቸውም በአሏህ መንገድ የታገሉት ብቻ ናቸው”፡፡ እነዚያ እነርሱ እውነተኞቹ ናቸው፡፡ إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ الَّذِينَ آمَنُوا بِاللَّهِ وَرَسُولِهِ ثُمَّ لَمْ يَرْتَابُوا وَجَاهَدُوا بِأَمْوَالِهِمْ وَأَنفُسِهِمْ فِي سَبِيلِ اللَّهِ ۚ أُولَـٰئِكَ هُمُ الصَّادِقُونَ
አምላካችን አሏህ በእርሱ መንገድ ከሚጋደሉ ባሮቹ ያርገን! ለነፍሲያ ተብሎ ከሚደረግ የዘር፣ የብሔር፣ የዘውግ ገድል ይጠብቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 13 382 |
| 13 | ምሥጢረ ትዳር
ይህ ወንድ ልጅ አንድ ሚስት አለው፥ ያቺ ሚስቱ በአካል አራት ናቸው። አራቱ ሴቶች በአካል፣ በስም እና በግብር አራት ሲሆኑ በሚስትነት ግን አንድ ናቸው፥ አራቱም ሴቶች ሚስት የሚለውን ቃል ይጋራሉ።
ኸዲጃ ሚስት ናት፣
ዘይነብ ሚስት ናት፣
ሰሚራህ ሚስት ናት፣
አሚራህ ሚስት ናት።
ነገር ግን አራቱ አካላት አንድን ሚስትነት ስለሚጋሩ ለወንድ አንድ ሚስት ናቸው።
ስለዚህ አንድ ወንድ አራት ሴቶች ሲያገባ ሚስቱ ግን አንዲት ናት።
ይህ "ምሥጢረ ትዳር" ካልተገለጸልህ አይገባህም። | 14 604 |
| 14 | እዚህ አንቀጽ ላይ "ብላቴናይት" ለሚለው የገባው ቃል "ፓርቴኖስ" παρθένος ሲሆን ሰባው ሊቃናት "ወጣት ሴት" የሚለውን አስበው እንጂ "ድንግል" የሚለው አስበው ስላልሆነ አኪላስ፣ ቴዎቶዶስ እና ሲማቲከስ የተባሉ ጥንታዊ የግሪክ መተርጉማን ከዕብራይስጥ ወደ ግሪክ የኢሳይያስ 7፥14 ላይ ያለውን አንቀጽ ሲተረጉሙ "ኔአኒደስ" νεάνιδες ማለትም "ኮረዳ" ብለው አስቀምጠውታል። ግሪክ ሰፕቱአጀንት የትርጉም ሥራ እንጂ ሥር እና መሠረት ካለመሆንም ባሻገር ከዕብራይስጡ የተለየ አሳብ ያቀርባል፦
ኢሳይያስ 7፥14 "ስሙንም አማኑኤል "ትለዋለህ"። καὶ καλέσεις τὸ ὄνομα αὐτοῦ ᾿Εμμανουήλ·
"ትለዋለህ" ለወንድ ነጠላ ሲሆን "ትለዋለች" ለሴት ነጠላ ነው፥ የቱን ነው ኢሳይያስ በትክክል ያለው? ትርጉም ሊሳሳት እንደሚችል ተረድተን የማቴዎስ ጸሐፊ ደግሞ ከዕብራይስጡ እና ከግሪክ ሰፕቱአጀንቱ በተለየ መልኩ አስቀምጦታል፦
ማቴዎስ 1፥23 እነሆ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል "ይሉታል"። Ἰδοὺ ἡ παρθένος ἐν γαστρὶ ἕξει καὶ τέξεται υἱόν, καὶ καλέσουσιν τὸ ὄνομα αὐτοῦ Ἐμμανουήλ,
"ይሉታል" በብዙ ቁጥር ሲሆን "ትለዋለህ" "ትለዋለች" ከሚለው ቃል እጅጉን ይለያል፥ የቱን ነው ኢሳይያስ በትክክል ያለው? ምነው የማቴዎስ ጸሐፊ ሲኮርጅ በትትክክል ከመኮረጅ ይልቅ ስርዋጽ ያስገባልን? ለሌላ ሴት የተነገረ ጥቅስ ለማርያም ሰቶ ከመሰቃየት ይልቅ በትክክሉ "ማርያም ያለ ወንድ ዘር በድንግልና ፀንሳለች" ብሎ ማስቀመጥ በቂ ነበር። መርየም አሏህን፦ "ጌታዬ ሆይ! "ወንድ ያልነካኝ ስኾን ለእኔ እንዴት ልጅ ይኖረኛል" አለች፦
3፥47 "ጌታዬ ሆይ! "ወንድ ያልነካኝ ስኾን ለእኔ እንዴት ልጅ ይኖረኛል" አለች፡፡ قَالَتْ رَبِّ أَنَّىٰ يَكُونُ لِي وَلَدٌ وَلَمْ يَمْسَسْنِي بَشَرٌ
አሏህም በመልአኩ፦ "ነገሩ እንዳልሽው ነው፡፡ አላህ የሚሻውን ይፈጥራል፡፡ አንዳችን በሻ ጊዜ ለርሱ ኹን ይለዋል፤ ወዲውኑም ይኾናል አላት፦
3፥47 ነገሩ እንዳልሽው ነው፡፡ አሏህ የሚሻውን ይፈጥራል፥ አንዳችን በሻ ጊዜ ለእርሱ "ኹን" ይለዋል ወዲውኑም ይኾናል" አላት፡፡ قَالَ كَذَٰلِكِ اللَّهُ يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ ۚ إِذَا قَضَىٰ أَمْرًا فَإِنَّمَا يَقُولُ لَهُ كُن فَيَكُونُ
አሏህ ያለ ወንድ እና ያለ ሴት ዘር አደም ከአፈር ከፈጠረ እና ሐዋን ያለ ሴት ዘር ከአደም አጥንት ከፈጠረ ዒሣን ካለ ወንድ ዘር ከመርየም ብቻ መፍጠር ይችላል፥ ይህ በድንግል መፅነስ"Parthenogenesis" ተአምር ሲሆን አሏህ በመርየም ብቻ ሳይሆን በተለያየ ፍጡር ያደርጋል።
"ፓርቴኖ ጌኔሲስ" παρθένο γένεσις የሚለው ቃል "የድንግል ልደት" ማለት ሲሆን የድንግል ልደት ካላቸው ፍጡራን መካከል "ኮሞዶ ድራጎን"Komodo Dragon" ተጠቃሽ ናት፥ በአዞ፣ በወፍ፣ በአሳ፣ በሸረሪት፣ በቀንድ አውጣ፣ በሸረሪት ዝርያዎች ውስጥ ያለ ወንድ በድንግና ፀንሰው የሚወልዱ ስላሉ አሏህ መርየምን ያለ ወንድ እንትኣድትፀንስ ማድረጉ የእርሱ ተአምር ነው፦
19፥21 አላት «ነገሩ እንደዚህሽ ነው» ጌታሽ፦ «እርሱ በእኔ ላይ ገር ነው፥ ለሰዎች ተአምር እና ከእኛም ችሮታ ልናደርገው ይህንን ሠራን የተፈረደም ነገር ነው» አለ፡፡ قَالَ كَذَٰلِكِ قَالَ رَبُّكِ هُوَ عَلَيَّ هَيِّنٌ ۖ وَلِنَجْعَلَهُ آيَةً لِّلنَّاسِ وَرَحْمَةً مِّنَّا ۚ وَكَانَ أَمْرًا مَّقْضِيًّا
የእይሁዳውያንን እና የክርስቲያኖችን ውዝግብ አሏህ በዚህ መልኩ ይፈታልናል። አምላካችን አሏህ ሂዳያውን ይወፍቃቸው! ለእኛም ኢሥቲቃማውን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 16 390 |
| 15 | ድንግል ማርያም
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
3፥47 "ጌታዬ ሆይ! "ወንድ ያልነካኝ ስኾን ለእኔ እንዴት ልጅ ይኖረኛል" አለች፡፡ قَالَتْ رَبِّ أَنَّىٰ يَكُونُ لِي وَلَدٌ وَلَمْ يَمْسَسْنِي بَشَرٌ
በዕብራይስጥ "በቱላህ" בְּתוּלָה ማለት "ድንግል" ማለት ነው፥ በታናኽ "በቱላህ" בְּתוּלָה በነጠላ 32 ጊዜ የተጠቀሰ ሲሆን ወንድ የማያውቃት ድንግል ሴት ናት፦
ዘፍጥረት 24፥16 ብላቴናይቱም መልክዋ እጅግ ያማረ፥ ወንድ የማያውቃት "ድንግል" ነበረች። וְהַנַּעֲרָ֗ טֹבַ֤ת מַרְאֶה֙ מְאֹ֔ד בְּתוּלָ֕ה וְאִ֖ישׁ לֹ֣א יְדָעָ֑הּ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ድንግል" ለሚለው የገባው ቃል "በቱላህ" בְּתוּלָה ነው፥ ይህቺ ሴት ርብቃ ስትሆን እርሷ ድንግል ብቻ ሳትሆን ቆንጆ ወጣት ሴት ነበረች፦
ዘፍጥረት 24፥43 ውኃ ልትቀዳ ለምትመጣውም "ቆንጆ" ጥቂት ውኃ ከእንስራሽ አጠጪኝ። וְהָיָ֤ה הָֽעַלְמָה֙ הַיֹּצֵ֣את לִשְׁאֹ֔ב וְאָמַרְתִּ֣י אֵלֶ֔יהָ הַשְׁקִֽינִי־נָ֥א מְעַט־מַ֖יִם מִכַּדֵּֽךְ׃
እዚህ አንቀጽ ላይ "ቆንጆ" ለሚለው የገባው ቃል "አልማህ" עַלְמָה ሲሆን "ወጣት ሴት" "ብላቴናይት" ማለት ነው፦
ዘጸአት 2፥8 "ብላቴናይቱ" ሄዳ የሕፃኑን እናት ጠራች። הָֽעַלְמָ֔ה וַתִּקְרָ֖א אֶת־אֵ֥ם הַיָּֽלֶד׃
በታናኽ "አልማህ" עַלְמָה የሚለው ቃል 7 ጊዜ የተጠቀሰ ሲሆን "ወጣት ሴት" ማለት ነው፦
ኢሳይያስ 7፥14 ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ "ወጣት ሴት" ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።לָכֵן יִתֵּן אֲדֹנָי הוּא, לָכֶם–אוֹת: הִנֵּה הָעַלְמָה, הָרָה וְיֹלֶדֶת בֵּן, וְקָרָאת שְׁמוֹ, עִמָּנוּ אֵל.
የክርስቲያን መተርጉማን፦ 1. NET Bible 2. New American Bible 3. Good News Translation 4. New Revised Standard Version "ወጣት ልጅ"a young woman" ብለው በትክክሉ ተርጉመውታል። በአካዝ ዘመን የሶርያ ንጉሥ ረአሶን እና የእስራኤልም ንጉሥ ፋቁሔ ኢየሩሳሌምን ሊወጉ ሲሉ አካዝ የተሰጠው ምልክት ሕፃኑ ክፉን ለመጥላት መልካሙን ለመምረጥ ሳያውቅ የፈራሃቸው የሁለቱ ነገሥታት አገር ባድማ መሆን ነው፦
ኢሳይያስ 7፥16 ሕፃኑ ክፉን ለመጥላት መልካሙን ለመምረጥ ሳያውቅ የፈራሃቸው "የሁለቱ ነገሥታት" አገር ባድማ ትሆናለች።
ቢኢሳይያስ ዘመን የነበረችው ያቺ ወጣት ሴት ነቢይቱን ሕፃኑን ወለደችው፥ ኢሳይያስም ያ ከወጣቲቱ ሴት የተወለደውን ሕፃን በወቅቱ በሁለተኛ መደብ "አማኑኤል ሆይ" እያለ ያናግረው ነበር፦
ኢሳይያስ 8፥3 ወደ ነቢይቱም ቀረብሁ እርስዋም ፀነሰች ወንድ ልጅንም ወለደች።
ኢሳይያስ 8፥8 አማኑኤል ሆይ! የክንፉ መዘርጋት የአገርህን ስፋት ትሞላለች።
ይህ አማኑኤል የተባለው ሕፃን አባት እና እናት ያለው ሕፃን ሲሆን ሕፃኑ አባቱንና እናቱን መጥራት ሳያውቅ የደማስቆን ሀብት እና የሰማርያን ምርኮ በአሦር ንጉሥ ፊት በመወሰድ ትንቢቱ ተፈጽሟል፦
ኢሳይያስ 8፥4 "ሕፃኑ "አባቱን" እና እናቱን መጥራት ሳያውቅ የደማስቆን ሀብት እና የሰማርያን ምርኮ በአሦር ንጉሥ ፊት ይወስዳልና" አለኝ።
ኢሳይያስ 7፥14 ላይ በግሪክ ሰፕቱአጀንት"LXX" ላይ "ወጣት ሴት" ለሚለው የገባው ቃል "ፓርቴኖስ" παρθένος ሲሆን በትርጉም ደረጃ "ድንግል" ብቻ ሳይሆን "ወጣት ሴት" ማለትም ነው፦
ዘፍጥረት 34፥3 ልቡናውም በያዕቆብ ልጅ በዲና ፍቅር ተነደፈ፥ "ብላቴናይቱንም" ወደዳት፥ ልብዋንም ደስ በሚያሰኛት ነገር ተናገራት። καὶ προσέσχε τῇ ψυχῇ Δείνας τῆς θυγατρὸς ᾿Ιακὼβ καὶ ἠγάπησε τὴν παρθένον καὶ ἐλάλησε κατὰ τὴν διάνοιαν τῆς παρθένου αὐτῇ. | 13 660 |
| 16 | 19፥21 አላት «ነገሩ እንደዚህሽ ነው» ጌታሽ፦ «እርሱ በእኔ ላይ ገር ነው፥ ለሰዎች ተአምር እና ከእኛም ችሮታ ልናደርገው ይህንን ሠራን የተፈረደም ነገር ነው» አለ፡፡ قَالَ كَذَٰلِكِ قَالَ رَبُّكِ هُوَ عَلَيَّ هَيِّنٌ ۖ وَلِنَجْعَلَهُ آيَةً لِّلنَّاسِ وَرَحْمَةً مِّنَّا ۚ وَكَانَ أَمْرًا مَّقْضِيًّا
የእይሁዳውያንን እና የክርስቲያኖችን ውዝግብ አሏህ በዚህ መልኩ ይፈታልናል። አምላካችን አሏህ ሂዳያውን ይወፍቃቸው! ለእኛም ኢሥቲቃማውን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 1 |
| 17 | ድንግል ማርያም
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
3፥47 "ጌታዬ ሆይ! "ወንድ ያልነካኝ ስኾን ለእኔ እንዴት ልጅ ይኖረኛል" አለች፡፡ قَالَتْ رَبِّ أَنَّىٰ يَكُونُ لِي وَلَدٌ وَلَمْ يَمْسَسْنِي بَشَرٌ
በዕብራይስጥ "በቱላህ" בְּתוּלָה ማለት "ድንግል" ማለት ነው፥ በታናኽ "በቱላህ" בְּתוּלָה በነጠላ 32 ጊዜ የተጠቀሰ ሲሆን ወንድ የማያውቃት ድንግል ሴት ናት፦
ዘፍጥረት 24፥16 ብላቴናይቱም መልክዋ እጅግ ያማረ፥ ወንድ የማያውቃት "ድንግል" ነበረች። וְהַנַּעֲרָ֗ טֹבַ֤ת מַרְאֶה֙ מְאֹ֔ד בְּתוּלָ֕ה וְאִ֖ישׁ לֹ֣א יְדָעָ֑הּ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ድንግል" ለሚለው የገባው ቃል "በቱላህ" בְּתוּלָה ነው፥ ይህቺ ሴት ርብቃ ስትሆን እርሷ ድንግል ብቻ ሳትሆን ቆንጆ ወጣት ሴት ነበረች፦
ዘፍጥረት 24፥43 ውኃ ልትቀዳ ለምትመጣውም "ቆንጆ" ጥቂት ውኃ ከእንስራሽ አጠጪኝ። וְהָיָ֤ה הָֽעַלְמָה֙ הַיֹּצֵ֣את לִשְׁאֹ֔ב וְאָמַרְתִּ֣י אֵלֶ֔יהָ הַשְׁקִֽינִי־נָ֥א מְעַט־מַ֖יִם מִכַּדֵּֽךְ׃
እዚህ አንቀጽ ላይ "ቆንጆ" ለሚለው የገባው ቃል "አልማህ" עַלְמָה ሲሆን "ወጣት ሴት" "ብላቴናይት" ማለት ነው፦
ዘጸአት 2፥8 "ብላቴናይቱ" ሄዳ የሕፃኑን እናት ጠራች። הָֽעַלְמָ֔ה וַתִּקְרָ֖א אֶת־אֵ֥ם הַיָּֽלֶד׃
በታናኽ "አልማህ" עַלְמָה የሚለው ቃል 7 ጊዜ የተጠቀሰ ሲሆን "ወጣት ሴት" ማለት ነው፦
ኢሳይያስ 7፥14 ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ "ወጣት ሴት" ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች።לָכֵן יִתֵּן אֲדֹנָי הוּא, לָכֶם–אוֹת: הִנֵּה הָעַלְמָה, הָרָה וְיֹלֶדֶת בֵּן, וְקָרָאת שְׁמוֹ, עִמָּנוּ אֵל.
የክርስቲያን መተርጉማን፦ 1. NET Bible 2. New American Bible 3. Good News Translation 4. New Revised Standard Version "ወጣት ልጅ"a young woman" ብለው በትክክሉ ተርጉመውታል። በአካዝ ዘመን የሶርያ ንጉሥ ረአሶን እና የእስራኤልም ንጉሥ ፋቁሔ ኢየሩሳሌምን ሊወጉ ሲሉ አካዝ የተሰጠው ምልክት ሕፃኑ ክፉን ለመጥላት መልካሙን ለመምረጥ ሳያውቅ የፈራሃቸው የሁለቱ ነገሥታት አገር ባድማ መሆን ነው፦
ኢሳይያስ 7፥16 ሕፃኑ ክፉን ለመጥላት መልካሙን ለመምረጥ ሳያውቅ የፈራሃቸው "የሁለቱ ነገሥታት" አገር ባድማ ትሆናለች።
ቢኢሳይያስ ዘመን የነበረችው ያቺ ወጣት ሴት ነቢይቱን ሕፃኑን ወለደችው፥ ኢሳይያስም ያ ከወጣቲቱ ሴት የተወለደውን ሕፃን በወቅቱ በሁለተኛ መደብ "አማኑኤል ሆይ" እያለ ያናግረው ነበር፦
ኢሳይያስ 8፥3 ወደ ነቢይቱም ቀረብሁ እርስዋም ፀነሰች ወንድ ልጅንም ወለደች።
ኢሳይያስ 8፥8 አማኑኤል ሆይ! የክንፉ መዘርጋት የአገርህን ስፋት ትሞላለች።
ይህ አማኑኤል የተባለው ሕፃን አባት እና እናት ያለው ሕፃን ሲሆን ሕፃኑ አባቱንና እናቱን መጥራት ሳያውቅ የደማስቆን ሀብት እና የሰማርያን ምርኮ በአሦር ንጉሥ ፊት በመወሰድ ትንቢቱ ተፈጽሟል፦
ኢሳይያስ 8፥4 "ሕፃኑ "አባቱን" እና እናቱን መጥራት ሳያውቅ የደማስቆን ሀብት እና የሰማርያን ምርኮ በአሦር ንጉሥ ፊት ይወስዳልና" አለኝ።
ኢሳይያስ 7፥14 ላይ በግሪክ ሰፕቱአጀንት"LXX" ላይ "ወጣት ሴት" ለሚለው የገባው ቃል "ፓርቴኖስ" παρθένος ሲሆን በትርጉም ደረጃ "ድንግል" ብቻ ሳይሆን "ወጣት ሴት" ማለትም ነው፦
ዘፍጥረት 34፥3 ልቡናውም በያዕቆብ ልጅ በዲና ፍቅር ተነደፈ፥ "ብላቴናይቱንም" ወደዳት፥ ልብዋንም ደስ በሚያሰኛት ነገር ተናገራት። καὶ προσέσχε τῇ ψυχῇ Δείνας τῆς θυγατρὸς ᾿Ιακὼβ καὶ ἠγάπησε τὴν παρθένον καὶ ἐλάλησε κατὰ τὴν διάνοιαν τῆς παρθένου αὐτῇ.
እዚህ አንቀጽ ላይ "ብላቴናይት" ለሚለው የገባው ቃል "ፓርቴኖስ" παρθένος ሲሆን ሰባው ሊቃናት "ወጣት ሴት" የሚለውን አስበው እንጂ "ድንግል" የሚለው አስበው ስላልሆነ አኪላስ፣ ቴዎቶዶስ እና ሲማቲከስ የተባሉ ጥንታዊ የግሪክ መተርጉማን ከዕብራይስጥ ወደ ግሪክ የኢሳይያስ 7፥14 ላይ ያለውን አንቀጽ ሲተረጉሙ "ኔአኒደስ" νεάνιδες ማለትም "ኮረዳ" ብለው አስቀምጠውታል። ግሪክ ሰፕቱአጀንት የትርጉም ሥራ እንጂ ሥር እና መሠረት ካለመሆንም ባሻገር ከዕብራይስጡ የተለየ አሳብ ያቀርባል፦
ኢሳይያስ 7፥14 "ስሙንም አማኑኤል "ትለዋለህ"። καὶ καλέσεις τὸ ὄνομα αὐτοῦ ᾿Εμμανουήλ·
"ትለዋለህ" ለወንድ ነጠላ ሲሆን "ትለዋለች" ለሴት ነጠላ ነው፥ የቱን ነው ኢሳይያስ በትክክል ያለው? ትርጉም ሊሳሳት እንደሚችል ተረድተን የማቴዎስ ጸሐፊ ደግሞ ከዕብራይስጡ እና ከግሪክ ሰፕቱአጀንቱ በተለየ መልኩ አስቀምጦታል፦
ማቴዎስ 1፥23 እነሆ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል "ይሉታል"። Ἰδοὺ ἡ παρθένος ἐν γαστρὶ ἕξει καὶ τέξεται υἱόν, καὶ καλέσουσιν τὸ ὄνομα αὐτοῦ Ἐμμανουήλ,
"ይሉታል" በብዙ ቁጥር ሲሆን "ትለዋለህ" "ትለዋለች" ከሚለው ቃል እጅጉን ይለያል፥ የቱን ነው ኢሳይያስ በትክክል ያለው? ምነው የማቴዎስ ጸሐፊ ሲኮርጅ በትትክክል ከመኮረጅ ይልቅ ስርዋጽ ያስገባልን? ለሌላ ሴት የተነገረ ጥቅስ ለማርያም ሰቶ ከመሰቃየት ይልቅ በትክክሉ "ማርያም ያለ ወንድ ዘር በድንግልና ፀንሳለች" ብሎ ማስቀመጥ በቂ ነበር። መርየም አሏህን፦ "ጌታዬ ሆይ! "ወንድ ያልነካኝ ስኾን ለእኔ እንዴት ልጅ ይኖረኛል" አለች፦
3፥47 "ጌታዬ ሆይ! "ወንድ ያልነካኝ ስኾን ለእኔ እንዴት ልጅ ይኖረኛል" አለች፡፡ قَالَتْ رَبِّ أَنَّىٰ يَكُونُ لِي وَلَدٌ وَلَمْ يَمْسَسْنِي بَشَرٌ
አሏህም በመልአኩ፦ "ነገሩ እንዳልሽው ነው፡፡ አላህ የሚሻውን ይፈጥራል፡፡ አንዳችን በሻ ጊዜ ለርሱ ኹን ይለዋል፤ ወዲውኑም ይኾናል አላት፦
3፥47 ነገሩ እንዳልሽው ነው፡፡ አሏህ የሚሻውን ይፈጥራል፥ አንዳችን በሻ ጊዜ ለእርሱ "ኹን" ይለዋል ወዲውኑም ይኾናል" አላት፡፡ قَالَ كَذَٰلِكِ اللَّهُ يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ ۚ إِذَا قَضَىٰ أَمْرًا فَإِنَّمَا يَقُولُ لَهُ كُن فَيَكُونُ
አሏህ ያለ ወንድ እና ያለ ሴት ዘር አደም ከአፈር ከፈጠረ እና ሐዋን ያለ ሴት ዘር ከአደም አጥንት ከፈጠረ ዒሣን ካለ ወንድ ዘር ከመርየም ብቻ መፍጠር ይችላል፥ ይህ በድንግል መፅነስ"Parthenogenesis" ተአምር ሲሆን አሏህ በመርየም ብቻ ሳይሆን በተለያየ ፍጡር ያደርጋል።
"ፓርቴኖ ጌኔሲስ" παρθένο γένεσις የሚለው ቃል "የድንግል ልደት" ማለት ሲሆን የድንግል ልደት ካላቸው ፍጡራን መካከል "ኮሞዶ ድራጎን"Komodo Dragon" ተጠቃሽ ናት፥ በአዞ፣ በወፍ፣ በአሳ፣ በሸረሪት፣ በቀንድ አውጣ፣ በሸረሪት ዝርያዎች ውስጥ ያለ ወንድ በድንግና ፀንሰው የሚወልዱ ስላሉ አሏህ መርየምን ያለ ወንድ እንትኣድትፀንስ ማድረጉ የእርሱ ተአምር ነው፦ | 1 |
| 18 | የሐሰት ትርክት
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
22፥30 ከጣዖታት እርኩሰት ተጠንቀቁ! የሐሰትን ቃል ራቁ፡፡ فَٱجْتَنِبُوا۟ ٱلرِّجْسَ مِنَ ٱلْأَوْثَٰنِ وَٱجْتَنِبُوا۟ قَوْلَ ٱلزُّورِ
"ኢትዮጵያ" የምትባል አገር ከሦስት ሺህ ዓመት በላይ ታሪክ ያላት አገር መሆኗን በታሪክ ምሁራን ዘንድ ይተረካል፥ ከጥንት ጀምሮ ኢትዮጵያ የራሷ ቋንቋ፣ ፊደል፣ ሥነ ጽሑፍ ያላት አገር ናት። ነገር ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ስለ ኦርቶዶክስ ደሴታውያን፦ "ኦርቶዶክስ ፊደል ቀርጻ፣ ብራና ዳምጣ፣ ቀለም በጥብጣ አገር ገንብታለች" በማለት የሐሰት ትርክት ይተርካሉ፥ እውን ኦርቶዶክስ አገር በቀል እሳቤ ነው ወይስ ከሌላ አገር የመጣ እሳቤ ነው?
እንደ ጎርጎሮሳውያን በመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያዊ ጃንደረባ ከኢትዮጵያ ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ወንጌል ሰምቶ እና አምኖ ወደ አገሩ ተመለሰ፥ ያ ሰው ከእርሱ አልፎ ለኢትዮጵያውያን ያስተላለፈው እና ያስፋፋው ነገር እንደሌለ እሙን እና ቅቡል ነው።
በአራተኛው ክፍለ ዘመን ሊባኖሳዊ ፍሬምናጥስ በማዕረግ ስሙ "አባ ሰላማ" በንጉሥ ዒዛና ዘመነ መንግሥት ክርስትናን በይፋ አስገብቷል፥ በመቀጠል በ 480 ድኅረ ልደት ተስዓቱ(ዘጠኙ) ቅዱሳን ክርስትናን በጽብሓውያን የአስተሳሰብ ውቅር ወደ ኢትዮጵያ አስገብተዋል።
ሙግቱ እንስቲ ጠበብ እናርገውና "ክርስትና የገባው በመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን ነው" እንበል "ኢትዮጵያን የሚባሉ ሕዝቦች ከመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን በፊት የሉም" እያላችሁን ነው? ከመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን በፊት ፊደል፣ ቋንቋ እና ሥነ ጽሑፍ የለምን? ስለዚህ "ኦርቶዶክስ ፊደል ቀርጻ፣ ብራና ዳምጣ፣ ቀለም በጥብጣ አገር ገንብታለች" የሚለው ትርክት የሐሰት ትርክት ነው።
ሌላው ደሴታውያን "ኦርቶዶክስ አገር ናት" የሚል የሐሰት ትርክት አላቸው፥ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አንድ የክርስትና አንጃ"Sect" እና የክርስትና ሃይማኖት ምድብ እንጂ አገር በፍጹም አይደለችም። አገር ኢትዮጵያ እንደመሆኗ መጠን ኢትዮጵያ ዋቄፈታውን፣ አይሁዳውያንን፣ ሙሥሊሙን፣ እንዲሁ የተለያየ የክርስትና አንጃ እና ጎጥ"Denomination" ያካተተች አገር እንጂ ለኦርቶዶክስ እውነተኛ እናት ለተቀረው የእንጀራ እናት አይደለችም።
ዋቄፈታውን፣ አይሁዳውያንን፣ ሙሥሊሙን፣ እንዲሁ የተለያየ የክርስትና አንጃ እና ጎጥ ከጨዋታ ውጪ በማድረግ "ኦርቶዶክስ የአገር ባለቤት ናት" የሚል ትርክርት አሁንም የሐሰት ትርክት ነው፥ አገሪቱ ከሃይማኖት በገለልተኛ አስተሳሰብ"Secularism" መንግሥት እስከተመራች ድረስ አንድ ሰው የአገር ባለቤት ለመሆን ሃይማኖት ላይኖረውም ጭምር ይችላል።
"ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ናት" የሚል የሐሰት ትርክት የተቀበረ እና ደሴታውያን ይህንን የሐሰት ትርክት ሊያንሰራሩ ቢሞክሩም በአገር ግንባታ እና በብሔራዊ መግባባት ትርክቱ እየተደቆሰ ነው። ለማንኛውም እንደ አንድ ሙሥሊም የሐሰት ትርክትን አጋልጠን ትክክለኛውን ንግግር መናገር ይገባናል፦
33፥70 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ፡፡ ትክክለኛውን ንግግር ተናገሩ፡፡ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اتَّقُوا اللَّهَ وَقُولُوا قَوْلًا سَدِيدًا
የሐሰት ትርክት ሲተረክ የሐሰትን ቃል ራቁ! እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አሏህን ፍሩ! ከእውነተኞቹ ጋር ኹኑ፦
22፥30 ከጣዖታት እርኩሰት ተጠንቀቁ! የሐሰትን ቃል ራቁ፡፡ فَٱجْتَنِبُوا۟ ٱلرِّجْسَ مِنَ ٱلْأَوْثَٰنِ وَٱجْتَنِبُوا۟ قَوْلَ ٱلزُّورِ
9፥119 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አሏህን ፍሩ! ከእውነተኞቹ ጋር ኹኑ፡፡ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ ٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ وَكُونُوا۟ مَعَ ٱلصَّٰدِقِينَ
ከላይ የቀረበው መጣጥፍ "ትክክል አይደለም" የሚል ካለ በማስረጃ መሞገት ይቻላል፥ እውነተኞች እንደኾናችሁ ማስረጃችሁን አምጡ እና በዕውቀት ንገሩኝ፦
2፥111 እውነተኞች እንደኾናችሁ ማስረጃችሁን አምጡ" በላቸው፡፡ قُلْ هَاتُوا۟ بُرْهَٰنَكُمْ إِن كُنتُمْ صَٰدِقِينَ
6፥143 እውነተኞች እንደሆናችሁ በዕውቀት ንገሩኝ" በላቸው፡፡ نَبِّـُٔونِى بِعِلْمٍ إِن كُنتُمْ صَٰدِقِينَ
አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 13 087 |
| 19 | የአሏህ ማየት
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
57፥4 እርሱም የትም ብትኾኑ ከእናንተ ጋር ነው፡፡ አሏህ የምትሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነው፡፡ وَهُوَ مَعَكُمْ أَيْنَ مَا كُنتُمْ ۚ وَاللَّهُ بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌ
የሰው ምንነት እና ማንነት የዓይን፣ የጆሮ፣ የእግር፣ የእጅ ወዘተ ቅንብር"Complex" ነው፥ ለምሳሌ፦ እኔ በምንነት እና በማንነት አንድ ብሆንም የእኔ አንድነት የቅንብር አንድነት ነው። "ዑድው" عُضْو ማለት "ብልት"Organ" ወይም "ክፍል"Part" ማለት ሲሆን የሰው ዓይን፣ ጆሮ፣ እግር፣ እጅ ወዘተ የምንነቱ ክፍል ሲሆን ሕዋስ ነው፥ "ሓሣህ" حَاسَّة ማለት "ሕዋስ"Sense" ማለት ሲሆን ዓይን፣ ጆሮ፣ እግር፣ እጅ ወዘተ የሰው ሕዋስ ነው። አምላካችን አሏህ ሰውን ሰሚ ተመልካችም አድርጎ ፈጥሮታል፦
76፥2 እኛ ሰውን የምንፈትነው ስንኾን ቅልቅሎች ከኾኑ የፍትወት ሕዋስ ፈጠርነው፡፡ ሰሚ ተመልካችም አደረግነው፡፡ إِنَّا خَلَقْنَا الْإِنسَانَ مِن نُّطْفَةٍ أَمْشَاجٍ نَّبْتَلِيهِ فَجَعَلْنَاهُ سَمِيعًا بَصِيرًا
"በሲር" بَصِير ማለት "ተመልካች" ማለት ሲሆን የሰው ተመልካችነት በጊዜ እና በቦታ የተወሰነ ሲሆን የሚመለከትበት መመልከቻ ዓይን እራሱ ግዙፍ እና ስሉጥ ነው፥ የሰው ዓይን ያለ ብርሃን በጨለማ የማያይ እና ብርሃን የሚቀበልበት ውኃ"lens" ያለው ነው። "መሕዱድ" مَحْدُود ማለት "ውስን"Limited" ማለት ሲሆን "መሕዱዲያህ" مَحْدُودِيَّة ማለት "ውስንነት"Limitedness" ነው፥ የፍጡራን ዓይን ውስን ነው። አምላካችን አሏህ ግን ከማንም ፍጡር ጋር የማይመሳሰል ሲሆን እርሱ ተመልካች ነው፦
42፥11 የሚመስለው ምንም ነገር የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ لَيْسَ كَمِثْلِهِ شَيْءٌ ۖ وَهُوَ السَّمِيعُ الْبَصِيرُ
እዚህ አንቀጽ ላይ "ሚስል" مِثْل በሚለው ቃል ላይ መነሻ ቅጥያ ሆኖ የገባው "ከ" كَ የሚል መስተዋድድ "በጭራሽ" "በፍጹም" ማለት ነው፥ "ሸይእ" شَيْء በሚለው ቃል ውስጥ ሁሉም ምንነት የሚካተቱ ሲሆኑ ከፍጡራን መካከል እርሱን የሚመስል ብጤ በጭራሽ የለም።
አሏህ ከፍጡራን ጋር በጭራሽ እና በፍጹም የማይመሳሰል የማየት ባሕሪ አለው፥ የእርሱ ማየት ከፍጡራን ማየት ጋር አይመሳሰልም። "ተሽቢህ" تَشْبِيه ማለት "ማመሳሰል" ማለት ሲሆን የአሏህን ማየት ከፍጡራን ማየት ጋር ማመሳሰል "ተሽቢህ" تَشْبِيه ነው፥ አሏህ እንደ ፍጡራን ዓይነት ዓይን በጭራሽ የለውም። የአሏህ ዓይን መለኮታዊ እና አምላካዊ ዓይን እንጂ ሰዋዊ እና ፍጥረታዊ አይደለም፦
52፥48 ለጌታህ ፍርድም ታገሥ! አንተ በ-"ዓይናችን" ሥር ነህና፡፡ ጌታህንም በምትነሳ ጊዜ ከማመስገን ጋር አወድሰው፡፡ وَاصْبِرْ لِحُكْمِ رَبِّكَ فَإِنَّكَ بِأَعْيُنِنَا ۖ وَسَبِّحْ بِحَمْدِ رَبِّكَ حِينَ تَقُومُ
"በሶር" بَصَر ማለት "መመልከቻ" ማለት ሲሆን መመልከቻ በሉገቲል ዐረቢይ "ዐይን" عَيْن ነው፥ አሏህ የራሱ ዓይን እንዳለው ከላይ ያለው ጥቅስ ያሳያል። የተሽቢህ ተቃራኒ "ተንዚህ" تَنْزِيه ሲሆን የአሏህን ባሕሪይ ከፍጡራን ጋር አለማመሳሰል "ተንዚህ" تَنْزِيه ነው፥ የእርሱ ዓይን ረቂቅ እንጂ ግዙፍ ስላልሆነ ከፍጡራን እርሱን ማንጻት "ተንዚህ" تَنْزِيه ነው። "ሙጥለቅ" مُطْلَق ማለት "ያልተወሰነ"Unlimited" ማለት ሲሆን "ሙጥለቃህ" مُطْلَقَة ማለት "ኢ ውስንንነት"Unlimitedness" ማለት ነው፦
57፥4 እርሱም የትም ብትኾኑ ከእናንተ ጋር ነው፡፡ አሏህ የምትሠሩትን ሁሉ ተመልካች ነው፡፡ وَهُوَ مَعَكُمْ أَيْنَ مَا كُنتُمْ ۚ وَاللَّهُ بِمَا تَعْمَلُونَ بَصِيرٌ
የትም ብንሆን አሏህ ሁሉን ነገር ስለሚመለከት የእርሱ ማየት ያልተወሰነ ነው፥ "ወዚፋህ" وَظِيفَة ማለት "ግብር"Function" ማለት ሲሆን ዓይን ለአሏህ ሲወሶፍ ግብር እንጂ እንደ ሰው የሕዋስ ክፍል አይደለም።
ወደ ባይብል ስንገባ ኢዮብ በአንድ ወቅት፦ "በውኑ የሥጋ ዓይን አለህን? ወይስ ሰው እንደሚያይ ታያለህን? በማለት በአጠይቆት አምላክ የሥጋ ዓይን እንደሌለው እና ሰው እንደሚያይ ዓይነት አስተያየት እንደሌለው ጠቁሞ ነበር፦
ኢዮብ 10፥4 በውኑ የሥጋ ዓይን አለህን?
ወይስ ሰው እንደሚያይ ታያለህን? הַעֵינֵי בָשָׂר לָךְ אִם־כִּרְאוֹת אֱנוֹשׁ תִּרְאֶה
የሰው ማየት ውስንነት ያለው፣ ያለ ብርሃን ማየት የማይችል፣ በጨለማ ማየት የማይችል ሲሆን ዓይኑ የሥጋ ዓይን ነው፥ የአምላክ ማየት ግን ያለ ብርሃን ማየት የሚችል፣ በጨለማ ማየት የሚችል፣ እይታው ያልተወሰነ የመለኮት ዓይን ነው፦
ምሳሌ 15፥3 የያህዌህ ዓይኖች በስፍራ ሁሉ ናቸው፥ ክፉዎችን እና ደጎችን ይመለከታሉ። בְּכָל־מָקוֹם עֵינֵי יְהוָה צֹפוֹת רָעִים וְטוֹבִים
የአምላክ ዓይኖች በስፍራ ሁሉ ክፉዎችን እና ደጎችን ይመለከታሉ፥ የመለኮት ዓይን ረቂቅ፣ ምጡቅ፣ ምሉዕ ነው። ማንም ሰው ባይብል ላይ "ዓይን" ማለት "ይህ ማለት ነው" ብሎ ተርጉሞ ማስረጃ ማምጣት አይችልም፥ ከዚያ ይልቅ ሠለስቱ ምዕት ወጥ በሆነ ስምምነት ለእግዚአብሔር ምሳሌአዊ ሳይሆን አማናዊ ዓይን እንዳለው ተናግረዋል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 19 ቁጥር 33
“ለእግዚአብሔር ዓይኖች እና ጆሮዎች እንዳሉት መጽሐፍት የተናገሩት እና የቀሩት እንዳሉት ስለ እግዚአብሔር የተነገረው ሁሉ የታመነ እና እውነተኛ እንደሆነ እናምናለን፥ ነገር ግን አይመረመርም አይታሰብም”።
"ሠለስቱ ምዕት" ማለት በ 325 ድኅረ ልደት በኒቂያ ጉባኤ የተሰበሰቡት 318 ሊቃውንት ናቸው፥ ይህ የኒቂያ ጉባኤ ወጥ የአበው ስምምነት"Consensus Patrum" ነው። በኒቅያ ጉባኤ ከነበሩት አበው አንዱ አትናቴዎስ ዘእስክንድሪያ ለእግዚአብሔር ምሳሌአዊ ሳይሆን አማናዊ ዓይን እንዳለው ተናግሯል፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 28 ቁጥር 30
“ለእግዚአብሔር ዓይን፣ ጆሮ፣ እጅ፣ እግር እንዳለው የተነገረው ሁሉ ስለ እግዚአብሔር በከበሩ መጻሕፍት የተጻፈ ሁሉ የታመነ የተረዳ ነው፥ የተናገርነው ሁሉ አለው። ነገር ግን አይመረመርም አይታወቅም”።
ዓይኑ ምን ዓይነት እንደሆነ "አይመረመርም አይታወቅም" ካለ ይህ በኢሥላም ሥነ መለኮት "ተፍዊድ" ይባላል፥ "ተፍዊድ" تَفْوِيض የሚለው ቃል "ፈወደ" فَوَّضَ ማለትም "አስጠጋ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ማስጠጋት"Delegation" ማለት ነው። "ተክዪፍ" تَكْيِيف ማለት "እንዴትነት"Howness" ማለት ሲሆን የአሏህን ባሕርዮት ያለ እንዴትነት "ቢላ ከይፈ" بِلَا كَيْفَ እንዴትነቱን ወደ አሏህ አስጠግቶ መቀበል "ተፍዊድ" تَفْوِيض ይባላል። በኃላ ላይ ግን ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ እና አውግስጢንዮስ ዘሂፓ የኡሲያ ኢኔርጌያ የተባሉትን ዓይን፣ ጆሮ፣ እግር፣ እጅ ከአማናዊ ወደ ምሳሌአዊ ትርጉም በመስጠት ተሕሪፍ አረጉት፥ "ተሕሪፍ" تَحْرِيف ማለት "ትርጉሙን ማዛባት" ማለት ነው።
አምላካችን አሏህ የእርሱን ባሕሪይ ያለ ተሕሪፍ፣ ያለ ተዕጢል፣ ያለ ተሽቢህ፣ ያለ ተክዪፍ የምንቀበል ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 15 579 |
| 20 | የኢየሱስ ፆታ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
5፥17 እነዚያ "አሏህ እርሱ የመርየም ልጅ አል መሢሕ ነው" ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ لَّقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ
እዚህ ዐውድ ላይ "ፆታ" ማለት ኃፍረተ ሥጋ ልዩነት ያለው ወንድ እና ሴትን ያቀፈ "የመራቢያ አካል"Sexual Organ" ማለት ነው፥ "ፅንስ" ማለት ደግሞ "በማኅፀን ውስጥ የተለያየ ሂደት"Process" ያደረገ ፍጡር" ማለት ነው። ድንግል ማርያም በማኅፀኗ ውስጥ የተፀነሰችው ፅንስ እና የወለደችው ልጇ ፆታው "ወንድ" ነው፦
ሉቃስ 1፥31 እነሆም ትፀንሻለሽ "ወንድ ልጅም" ትወልጃለሽ፥ ስሙንም "ኤሱስ" ትዪዋለሽ። καὶ ἰδοὺ συλλήμψῃ ἐν γαστρὶ καὶ τέξῃ υἱόν, καὶ καλέσεις τὸ ὄνομα αὐτοῦ Ἰησοῦν.
"ወንድ" የሚለው የሥጋ መደብ እና የሥጋ አንቀጽ ሲሆን ይህም እልም አርጎ ፍጡርን ያሳያል፥ የወንዱ ልጅ ስሙ በዕብራይስጥ "ያህሹዋ" יְהוֹשֻׁעַ በግሪክ ኮይኔ ደግሞ "ኤሱስ" Ἰησοῦς ሲባል ይህ ስም የናዝሬቱ ኢየሱስ ከመወለዱ እና ከመፈጠሩ በፊት ለፍጡር ሰው የሚውል ስም ነው፦
ሉቃስ 2፥21 ሊገርዙት ስምንት ቀን በሞላ ጊዜ በማኅፀን ሳይረገዝ(ሳይፀነስ) በመልአኩ እንደ ተባለ፥ ስሙ "ኤሱስ" ተብሎ ተጠራ። Καὶ ὅτε ἐπλήσθησαν ἡμέραι ὀκτὼ τοῦ περιτεμεῖν αὐτόν, καὶ ἐκλήθη τὸ ὄνομα αὐτοῦ Ἰησοῦς, τὸ κληθὲν ὑπὸ τοῦ ἀγγέλου πρὸ τοῦ συλλημφθῆναι αὐτὸν ἐν τῇ κοιλίᾳ.
"ሊገርዙት" የሚለው ይሰመርበት! የሚገርዙት የመራቢያ አካሉን ሲሆን ተገርዞ የሚጣለው ሸለፈቱ ነው፥ አምላክ ጅማሮ እና መነሻ የሌለው ሲሆን ይህ ወንድ ልጅ ግን ስምንተኛ ቀን ሆኖት ጅማሮ እና መነሻ አለው። ይህ ወንድ ልጅ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ጥር 6 ቀን በዓመት አንዴ "ግዝረተ ኢየሱስ" ተብሎ የተገዘረበትን ዓመታዊ ክብረ ይዘከራል፥ "ግዝረት” ማለት የግዕዝ ቃል ሲሆን “ግርዘት”Circumcision” ማለት ነው፦
ሃይማኖተ አበው ምዕራፍ 70 ቁጥር 24
"ሰውም እንደ መሆኑ ለሥጋ እንደሚገባ ተገዘረ"።
ድርሳነ መስቀል ምዕራፍ 3 ቁጥር 26
"የኦሪትን ሕግ ይፈጽም ዘንድ በስምንተኛው ቀን እንደ ሕፃናት ተገረዘ"።
ኢየሱስ በስምንተኛው ቀን የተገረዘ ወንድ ልጅ ነው፥ ከተገረዘ እና ወንድ ልጅ ከሆነ ፆታ አለው። መለኮት ግን መንፈስ ነው፥ መንፈስ ደግሞ ሥጋ እና አጥንት ስለሌለው ፆታ የለውም፦
ዮሐንስ 4፥24 አምላክ መንፈስ ነው። Πνεῦμα ὁ Θεός,
ሉቃስ 24፥39 መንፈስ ሥጋ እና አጥንት የለውምና። ὅτι πνεῦμα σάρκα καὶ ὀστέα οὐκ.
እንደ ተዋሕዶ አስተምህሮት መለኮት የትስብእትን ርስት እና ገንዘብ የራሱ ርስት እና ገንዘብ ካደረገ መለኮት የትስብእትን የመራቢያ ፆታን ገንዘቡ አድርጓልን? "አይ" ካላችሁ እንግዲያውስ የተዋሕዶ ተስተምህሮት ዶግ አመድ ይሆናል፥ "አዎ" ካላችሁ እንግዲያውስ "መለኮት የመራቢያ ፆታ አለው" ማለት ነው።
ይህ የተሠግዎት አጣብቂኝ"Incarnation Dilemma" ሲሆን "አዎ" ከተባለ ቀጣይ ይዞ የሚመጣው መዘዝ የመራቢያ ፆታ ያለው የማን መለኮት ነው? የወልድ መለኮት ወይስ የሦስቱም መለኮት? "የወልድ መለኮት" ከተባለ የመራቢያ ፆታ የሌለው የአብ እና የመንፈስ ቅዱስ መለኮት አለን? "የሦስቱም መለኮት" ከተባለ አብ እና መንፈስ ቅዱስ የመራቢያ ፆታ አላቸውን?
አምላክ እና ሰውን እንደ መርፌ እና ቁልፍ፣ እንደ ጭድ እና ጭቃ፣ እንደ መርፍ እና ሞፈር አንድ ለማድረግ በተለያየ የጊዜ ሱባኤ በተለያየ የቦታ ጉባኤ መዳከሩ ምን ይፈይዳል? "መለኮት ነጠላ አንድ ነው"Divine is Simple" ተብሎ ከፍጡር ሰው ጋር ውቅር"Composition" ሆነ ማለትስ "መለኮት ውቅር ነው"Divine is Complex" ማለት አይሆንም? ቅሉ እና ጥቅሉ ግን ሰው ውስን፣ ግዙፍ እና ስሉጥ ሲሆን መለኮት ደግሞ በተቃራኒው ምሉዕ፣ ረቂቅ እና ምጡቅ ነው፦
ሆሴዕ 11፥9 እኔ አምላክ ነኝ እንጂ ሰው አይደለሁምና። διότι Θεὸς ἐγώ εἰμι καὶ οὐκ ἄνθρωπος·
ያ ከፍጥረት ውጪ ያለው አምላክ ፍጡራንን ያካበበ እና በፍጥረት ውስጥ የተወሰነ ስላልሆነ ሰው አይደለም፥ ሰው ግን በአጭር ቁመት እና በጠባብ ደረት ውስን የሆነ ፍጡር ነው። ኢየሱስ ግን በምንነቱ ከአምላክ እየሰማ ሲናገር የነበረ ሰው ብቻ እና ብቻ ነው፦
ዮሐንስ 8፥40 ነገር ግን አሁን ከ-"አምላክ" የሰማሁትን እውነት የነገርኋችሁን "ሰው" ልትገድሉኝ ትፈልጋላችሁ። νῦν δὲ ζητεῖτέ με ἀποκτεῖναι, ἄνθρωπον ὃς τὴν ἀλήθειαν ὑμῖν λελάληκα, ἣν ἤκουσα παρὰ τοῦ Θεοῦ·
እዚህ አንቀጽ ላይ "ቴዎስ" Θεὸς እና "አንትሮፓስ" ἄνθρωπος በሰዋስው አወቃቀር ሁለት የተለያዩ ምንነት"Ontology" ሆነው ተቀምጠዋል፥ "ቴዎስ" Θεὸς ማለት "አምላክ" ማለት ሲሆን "አንትሮፓስ" ἄνθρωπος ማለት "ሰው" ማለት ነው።
"አምላክ" አሰሚ ባለቤት"Subject" ሲሆን "ሰው" ሰሚ ተሳቢ"Object" ነው፥ በአምላክ እና በሰው መካከል "የሰማሁት" የሚል አጫፋሪ ግሥ"Transitive Verb" ስላለ አሰሚው አምላክ እና ሰሚው ሰው ሁለት የተለያዩ ማንነት"metaphysics" እንደሆኑ ቁልጭ እና ፍንትው አርጎ ያሳያል።
ፍጹሙ ሰው ኢየሱስ ከፍጹሙ አምላክ እየሰማ ከተናገረ የተገረዘው እና ወንድ ልጅ የሆነው ፍጹሙ ሰው ከመለኮት በሰዋስው አደረጃጀት ተለይቶ ተቀምጧል፥ ከአምላክ ሰምቶ የሚናገር ሰው ደግሞ በማንነት ነቢይ እና መልእክተኛ ነው። የማርያም ልጅ ኢየሱስ በምንነት ሰው በማንነት መሢሕ ሆኖ ሳለ "አምላክ ነው" ያሉ በእርግጥ ካዱ፦
5፥17 እነዚያ "አሏህ እርሱ የመርየም ልጅ አል መሢሕ ነው" ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ لَّقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ
ይህ በሰው የተፈጠረው ውርክብ ለመግታት ምንም ዓይነት የሥነ መለኮት ዕውቀት፣ የሥነ አመክንዮ ሙግት፣ የሥነ ልቡና ዘይቤ ቢቀርብ እንኳን ከአንጀት ጠብ የሚል መልስ ሊገኝ አልተቻለም።
መፍትሔው ሴት ማኅፀን ውስጥ የተፀነሰ እና የተወለደ፣ የተገረዘ፣ የመራቢያ ፆታ ያለው ወንድ ልጅ ከማምለክ ይልቅ ያንን ወንድ ልጅ በማርያም ማኅፀን የፈጠረውን አንዱን አምላክ አሏህን እንድታመልኩ ጥሪያችን ነው። በአምላክነቱ ሰውነት የሌለበት አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይወፍቃችሁ! ለእኛም ኢሥቲቃማህ ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 15 008 |
