cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል

በሒዳያ ኢስላማዊ ማዕከል ስር በመሆን አስፈላጊና አስተማሪ ንፅፅራዊ ትምህርቶችን፦ - ቪድዬዎችን - ኦድዬዎችን - አጫጭር መጣጥፎችን እያዘጋጀ በሀገርኛ ቋንቋ ያቀርባል፡፡

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
4 960
مشترکین
-124 ساعت
+217 روز
+13530 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

▯▩ ወይይት ▩▯ "ስቅለት በኢስላም" ◍ ወንድም ኢምራን           🆅🆂 ◍ ወገናችን ሳሚ ◍ ወገናችን ሳለህ ◍ ሌሎችም
نمایش همه...
ለምሳሌ፦ አንደኛ በ 50-138 AD የማቴዎስ ተማሪ የነበረው ባስሊዲስ በ 117 AD ላይ ወንጌል አዘጋጅቷል፤ ይህ ወንጌል ላይ፦ "ኢየሱስ ሳይሰቀል ወደ ሰማይ እንዳረገ እና እርሱን እንሰቅላለን ብለው የቀሬናን ስምዖንን እንደሰቀሉት ይናገራል፤ ይህንን ወንጌል በኃላ ላይ የመጡት አበው በ 130-200 AD ይኖር የነበረ ኢራኒየስ፣ በ 150-215 AD ይኖር የነበረ የአሌክሳንድሪያው ክሌመንት ተቃወሙት፤ ብዙ ጊዜ ከባስሊዲስ ወንጌል ላይ 260-340 AD ይኖር የነበረው የቂሳሪያው አውሳቢዮስ ይጠቅስ ነበረ። ሁለተኛ በ 60-135 AD ይኖር የነበረው በርናባስ የበርናባስን ወንጌል፣ የበርናባስን መልእክት እና የበርናባስ ሥራ በ 100–131 AD አዘጋጅቷል፤ በሳይናቲከስ ኮዴክስ ላይ ፓሊካርፕ ለፊሊጵስዩስ በጻፈው ፓሊላርፕ 1፥1 ቀጥሎ የበርናባስ መልእክት 5፥7 ይቀጥልል። እዚህ ወንጌል ላይ፦ "ኢየሱስ ሳይሰቀል ወደ ሰማይ እንዳረገ እና እርሱን እንሰቅላለን ብለው የአስቆሮቱ ይሁዳ እንደሰቀሉት ይናገራል። ሦስተኛ በ 85-160 AD ይኖር የነበረው የሲኖፕ ማርኮይን ወንጌል አዘጋጅቷል፤ ይህ የማርኮናይት ወንጌል በ 1740 AD ከተገኙት የሙራቶሪያን ብጥስጣሽ"Muratorian fragment" አንዱ ነው፤ የካርቴጅ ጉባኤ ከማርኮናይት ግሩፕ ውስጥ የዮሐንስን አፓልካሊፕስ"ራእይ" ተቀብላ በእነርሱ የነበረውን የጳውሎስን አፓልካሊፕስ፣ የጴጥሮስን አፓልካሊፕስ፣ የቶማስን አፓልካሊፕስ፣ የእስጢፋኖስን አፓልካሊፕስ፣ የያዕቆብን አፓልካሊፕስ ደብቃቸዋለች። በማርኮናይት ወንጌል ወንጌል ላይ፦ "ኢየሱስ ሳይሰቀል ወደ ሰማይ እንዳረገ እና እርሱን እንሰቅላለን ብለው የሮማ ወታደር እንደሰቀሉት ይናገራል። አራተኛ በ 36-115 AD ይኖር የነበረው ኤቦን ወንጌል አዘጋጅቷል፤ ይህ የኤቦናይት ወንጌል ላይ፦ "ኢየሱስ ሳይሰቀል ወደ ሰማይ እንዳረገ ይናገራል። በ 347-420 AD ይኖር የነበረው ጄሮም ኤቦን በዮሐንስ ዘመን ይኖር እንደነበረ መስክሯል። ነገር ግን ኤቦንን በ 36-115 AD ይኖር የነበረው የቆሮጵሮሱ ኤጵፋኒየስ አውግዞቷል።
نمایش همه...
አልገደሉትም ገቢር አንድ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው። 4፥157 *«እኛ የአላህን መልክተኛ የመርየምን ልጅ አልመሲሕ ዒሳን ገደልን» በማለታቸውም ረገምናቸው፡፡ አልገደሉትም አልሰቀሉትምም፡፡ ግን ለእነሱ ተመሰለ፡፡ እነዚያም በእርሱ ነገር የተለያዩት ከእርሱ መገደል በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡ ጥርጣሬን ከመከተል በስተቀር በእርሱ ነገር ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ በእርግጥም አልገደሉትም*፡፡ وَقَوْلِهِمْ إِنَّا قَتَلْنَا الْمَسِيحَ عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ رَسُولَ اللَّهِ وَمَا قَتَلُوهُ وَمَا صَلَبُوهُ وَلَـٰكِن شُبِّهَ لَهُمْ ۚ وَإِنَّ الَّذِينَ اخْتَلَفُوا فِيهِ لَفِي شَكٍّ مِّنْهُ ۚ مَا لَهُم بِهِ مِنْ عِلْمٍ إِلَّا اتِّبَاعَ الظَّنِّ ۚ وَمَا قَتَلُوهُ يَقِينًا “ታሪክ”history” ያለፈውን ክስተት የሚተርክ የምርምር ጥናት”study” እና አሰሳ”investigation” ነው፤ በታሪክ ጥናት ውስጥ ለታሪክ ምንጭ የሚሆኑ ሁለት መረጃዎች አሉ፣ አንደኛው ትውፊት”tradition” ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የሥነ-ቅርስ ጥናት”archology” ነው፤ “ትውፊት” ከትውልድ ወደ ትውልድ በቃል የሚተላለፍ ቅብብል ሲሆን “ሥነ-ቅርስ ጥናት” ደግሞ በተለያየ ቁስ ላይ የተጻፉትን ጽሑፎች አስሶና ቆፍሮ የሚያቀርብ የታሪክ ምንጭ ነው፤ ትውፊት ሆነ ሥነ-ቅርስ በባህል”culture” ላይ እና በስልጣኔ”civilization” ላይ መሰረት ያደረጉ ግምት”speculation” ናቸው፤ ስለ ኢየሱስ ማንነት በዓለማችን ላይ አንድ አይነት አቋም ያለው የታሪክ ፍሰት የለም፤ አንዱ ሃሳዌ መሲህ ሲለው ሌላው አምላክ ሲለው፣ አንዱ የፈጣሪ እረዳት ሲለው ሌላው ብቸኛ የፈጣሪ ልጅ ይለዋል፤ አንዳንዶች እንደውም በታሪክ ላይ አልነበረም የሚሉም አልታጡም፤ ስለ እርሱ አራቱ ወንጌል ላይ የምናየውም ትረካም ቢሆን እርስ በእርሱ የተዛባ እና በቅብብል የተገኘ እንጂ ግህደተ-መለኮት አይደለም፤ ታዲያ ይህ ዓለማችንን ያነጋገረ የፈጣሪ ነብይ ትክክለኛ ማንነቱን መናገር ያለበት እራሱ ላኪው ፈጣሪ ነው፤ ኢየሱስን የላከው አላህ ስለ ዒሳ ሲናገር፦ 19፥34 ይህ የመርየም ልጅ ዒሳ ነው፡፡ *ያ “በ”እርሱ የሚከራከሩበት እውነተኛ ቃል ነው*፡፡ ذَٰلِكَ عِيسَى ٱبْنُ مَرْيَمَ ۚ قَوْلَ ٱلْحَقِّ ٱلَّذِى فِيهِ يَمْتَرُونَ “የምተሩነ” يَمْتَرُونَ ማለትም “የሚከራከሩበት” የሚለው የግስ መደብ ይሰመርበት፤ ይህ “መከራከር” የሚለው ቃል “ሚርያህ” مِرْيَة ሲሆን “ጭቅጭቅ” “ንትርክ” ክርክር” ማለት ነው፤ በዒሳ ጉዳይ ሰዎች በመወዛገብ መጨቃጨቃቸውን፣ መነታረካቸውን እና መከራከራቸውን ያሳያል፤ ዒሳ ካረገበ በኃላ ቁርኣን እስከሚወርድበት ጊዜ አራጥቃና በጥራቃ እየተባባሉ መቅኖ ሲያሳጣቸው እንደነበር ታሪክ በወርቃማ ብዕሩ አስፍሮታል። “ያ“ በ”እርሱ የሚከራከሩበት እውነተኛ ቃል ነው” የሚል ነው፤ “እርሱ” በሚለው ቃል ላይ “በ” የሚል መስተዋድድ አለ፤ ይህ የሚያመለክተው ስለ ዒሳ አላህ የነገረን ንግግር ሁሉ እውነተኛ ቃል ነው ማለት ነው፤ “በ” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ፊ” فِي  ሲሆን “ስለ”about” ማለት ነው፦ That is Jesus, son of Mary. ˹And this is˺ a word of truth, “about” which they dispute. “ቀሰስ” قَصَص የሚለው ቃል “ቀሰሰ” قصص “ተረከ” ከሚል ቃል የመጣ ሲሆን “ትረካ” ማለት ነው፤ አላህ ሁሉን የሚያይ፣ ሁሉን የሚሰማና ሁሉን የሚያውቅ ስለሆነ ያለፈውን ክስተት “ነቁስሱ አለይከ” نَقُصُّ عَلَيْكَ “እንተርክልሃለን” በማለት በነብያችን”ﷺ” ላይ ይተርካል፦ 11:120 *ከመልክተኞቹም ወሬዎች* ተፈላጊውን ሁሉንም ልብህን በእርሱ የምናረካበትን “*እንተርክልሃለን*፤ በዚህችም እውነቱ ነገር *ለምእምናን ግሳጼ እና ማስታወሻ* መጥቶልሃል፡፡ وَكُلًّۭا نَّقُصُّ عَلَيْكَ مِنْ أَنۢبَآءِ ٱلرُّسُلِ مَا نُثَبِّتُ بِهِۦ فُؤَادَكَ ۚ وَجَآءَكَ فِى هَٰذِهِ ٱلْحَقُّ وَمَوْعِظَةٌۭ وَذِكْرَىٰ لِلْمُؤْمِنِينَ ስለዚህ ከመልክተኞች ታሪክ አንዱ የዒሳ ታሪክ ስለሆነ ይህ ታሪክ ሲከሰት ነብያችን”ﷺ” በህልውና ደረጃ ስላልነበሩ ሁሉን ዐዋቂው አምላክ ለነብያችን”ﷺ” ይህንን ታሪክ ያወርዳል፤ ይህ ስለ ዒሳ ትረካ በእርግጥ እውነተኛ ታሪክ ነው፦ 3፥62 *”ይህ እርሱ በእርግጥ እውነተኛ ታሪክ ነው”*፡፡ አምላክም ከአላህ በስተቀር ምንም የለም፡፡ አላህም እርሱ በእርግጥ አሸናፊው ጥበበኛው ነው፡፡ إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلْقَصَصُ ٱلْحَقُّ ۚ وَمَا مِنْ إِلَٰهٍ إِلَّا ٱللَّهُ ۚ وَإِنَّ ٱللَّهَ لَهُوَ ٱلْعَزِيزُ ٱلْحَكِيمُ ሰዎች በዒሳ ጉዳይ ከሚወዛገቡበት፣ ከሚጨቃጨቁበት፣ ከሚነታረኩበት፣ ከሚከራከሩበት ነጥብ አንዱ ዒሳ ተሰቅሏል ወይስ አልተሰቀለም ነው፤ አምላካችን አላህ፦ ዒሳን አልገደሉትም አልሰቀሉትምም ግን የገደሉትና የሰቀሉት መስሏቸዋል፦ 4፥157 *«እኛ የአላህን መልክተኛ የመርየምን ልጅ አልመሲሕ ዒሳን ገደልን» በማለታቸውም ረገምናቸው፡፡ አልገደሉትም አልሰቀሉትምም፡፡ ግን ለእነርሱ ተመሰለ፡፡ እነዚያም በእርሱ ነገር የተለያዩት ከእርሱ መገደል በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡ ጥርጣሬን ከመከተል በስተቀር በእርሱ ነገር ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ በእርግጥም አልገደሉትም*፡፡ وَقَوْلِهِمْ إِنَّا قَتَلْنَا الْمَسِيحَ عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ رَسُولَ اللَّهِ وَمَا قَتَلُوهُ وَمَا صَلَبُوهُ وَلَـٰكِن شُبِّهَ لَهُمْ ۚ وَإِنَّ الَّذِينَ اخْتَلَفُوا فِيهِ لَفِي شَكٍّ مِّنْهُ ۚ مَا لَهُم بِهِ مِنْ عِلْمٍ إِلَّا اتِّبَاعَ الظَّنِّ ۚ وَمَا قَتَلُوهُ يَقِينًا "እነዚያም በእርሱ ነገር የተለያዩት ከእርሱ መገደል በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡ ጥርጣሬን ከመከተል በስተቀር በእርሱ ነገር ምንም ዕውቀት የላቸውም" ይህንን መለያየት አስመልክቶ ስለ ወንጌላት ታሪካዊ ዳራና ፍሰት፤ በቁርኣን እና በሐዲስ ያለውን እሳቤ ነጥብ በነጥብ ኢንሻላህ እንቀጥላለን...... ✍ከወንድም ወሒድ ዑመር https://t.me/Wahidcom ወሰላሙ አለይኩም
نمایش همه...
"እንኳን አደረሳችሁ?" ◍ እኅት ዘሀራ
نمایش همه...
አልገደሉትም ገቢር ሁለት በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው። 4፥157 *«እኛ የአላህን መልክተኛ የመርየምን ልጅ አልመሲሕ ዒሳን ገደልን» በማለታቸውም ረገምናቸው፡፡ አልገደሉትም አልሰቀሉትምም፡፡ ግን ለእነርሱ ተመሰለ፡፡ እነዚያም በእርሱ ነገር የተለያዩት ከእርሱ መገደል በመጠራጠር ውስጥ ናቸው፡፡ ጥርጣሬን ከመከተል በስተቀር በእርሱ ነገር ምንም ዕውቀት የላቸውም፡፡ በእርግጥም አልገደሉትም*፡፡ وَقَوْلِهِمْ إِنَّا قَتَلْنَا الْمَسِيحَ عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ رَسُولَ اللَّهِ وَمَا قَتَلُوهُ وَمَا صَلَبُوهُ وَلَـٰكِن شُبِّهَ لَهُمْ ۚ وَإِنَّ الَّذِينَ اخْتَلَفُوا فِيهِ لَفِي شَكٍّ مِّنْهُ ۚ مَا لَهُم بِهِ مِنْ عِلْمٍ إِلَّا اتِّبَاعَ الظَّنِّ ۚ وَمَا قَتَلُوهُ يَقِينًا ነጥብ አንድ "ታሪካዊ ዳራ" ኢየሱስ ከፈጣሪ የሚናገረውን ትምህርት ተሰቶት ነበር፤ ይህ ትምህርት የፈጣሪ ቃል ነው፤ ከእርሱ የሚሰማው ትምህርት የፈጣሪ ወንጌል ነው፦ ዮሐንስ 17:8 *የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸዋለሁና*፤ እነርሱም ተቀበሉት፥ ዮሐንስ 17:14 እኔ *ቃልህን ሰጥቻቸዋለሁ*፤ ዮሐንስ 14:24 የማይወደኝ ቃሌን አይጠብቅም፤ *የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም*። ዮሐንስ 7፥16 ስለዚህ ኢየሱስ መለሰ እንዲህም አላቸው። *ትምህርቴስ ከላከኝ ነው እንጂ ከእኔ አይደለም*፤ ዮሐንስ 12:49 *እኔ ከራሴ አልተናገርሁምና፤ ነገር ግን የላከኝ አብ እርሱ የምለውን የምናገረውንም ትእዛዝ ሰጠኝ*። ሉቃስ 5፥1 ሕዝቡም *የእግዚአብሔርን ቃል እየሰሙ* ሲያስጠብቡት ሳሉ፥ እርሱ ራሱ በጌንሳሬጥ ባሕር ዳር ቆሞ ነበር፤ ማርቆስ 1፥14 ዮሐንስም አልፎ ከተሰጠ በኋላ ኢየሱስ *የእግዚአብሔርን ወንጌል* እየሰበከና፦ ዘመኑ ተፈጸመ የእግዚአብሔርም መንግሥት ቀርባለች፤ ንስሐ ግቡ፡ *በወንጌልም እመኑ* እያለ ወደ ገሊላ መጣ። "በወንጌልም እመኑ" ሲል ከመለኮት የተሰጠውን ወንጌል ብቻና ብቻ ነው፤ ይህንን ወንጌል ለሃዋርያቱ አስተላልፏል፤ "የሰጠኸኝን ቃል ሰጥቻቸዋለሁና" የሚለው ሃይለ-ቃል ይሰመርበት፤ ኦሪገን የተሰጠው ወንጌል የአስራ ሁለቱ ወንጌል ሲሆን ጠፍቷል ይለናል። ጄሮም ደግሞ የአስራ ሁለቱ ወንጌል የሃዋርያት ወንጌል እንሆሃነ ተናግሯል፤ ሐዋርያቱ ለደቀመዛሙርቶታቸው ሲያስተላልፉ ቀደ መዛሙርቶቻቸው ይህንን ወንጌል ከሚሰሙት ታሪክ ጋር ቀላቅለው ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ሞክረዋል፦ ሉቃስ 1:1-4 የከበርህ ቴዎፍሎስ ሆይ፥ ከመጀመሪያው በዓይን ያዩትና የቃሉ አገልጋዮች የሆኑት እንዳስተላለፉልን፥ በኛ ዘንድ ስለ ተፈጸመው ነገር ብዙዎች ታሪክን በየተራው ለማዘጋጀት ስለ ሞከሩ፥ እኔ ደግሞ ስለ ተማርኸው ቃል እርግጡን እንድታውቅ በጥንቃቄ ሁሉን ከመጀመሪያው ተከትዬ በየተራው ልጽፍልህ መልካም ሆኖ ታየኝ።”
نمایش همه...
አምስተኛ በ 36-115 AD ይኖር የነበረው ሰርቲዩስ ወንጌል አዘጋጅቷል፤ ይህ የሰርቲዩስ ወንጌል ላይ፦ "ኢየሱስ ሳይሰቀል ወደ ሰማይ እንዳረገ ይናገራል። ስድስተኛ በ 36 AD ጀምረው ይኖሩ የነበሩት ናዝራውያን ወንጌል አዘጋጅተዋል፤ ይህ የናዝራውያን ወንጌል ላይ፦ "ኢየሱስ ሳይሰቀል ወደ ሰማይ እንዳረገ ይናገራል። ናዝራውያን የሙሴን ሕግ ይቀበላሉ፤ የኢየሱስን በድንግና መወለድ ይቀበላሉ፣ የሌሎችን ወንጌላት አይቀበሉም። በግሪክ ኮይኔ የተዘጋጁት ወንጌሎች የትዬለሌ ናቸው፤ እነርሱም፦ የቶማስ ወንጌል፣ የይሁዳ ወንጌል፣ የባስሊዲስ ወንጌል፣ የበርናባስ ወንጌል፣ የማርኮናይት ወንጌል፣ የኤቦናይት ወንጌል፣ የሰርቲዩስ ወንጌል፣ የናዝራውያን ወንጌል፣ የጴጥሮስ ወንጌል፣ የያዕቆብ ወንጌል፣ የፊሊጶስ ወንጌል፣ የበርተሎሜዎስ ወንጌል፣ የመቅደላዊት ማርያም ወንጌል፣ የማቴዎስ ወንጌል፣ የማርቆስ ወንጌል፣ የሉቃስ ወንጌል፣ የዮሐንስ ወንጌል የመሳሰሉት ናቸው፣ በቁጥር ወደ 47 ይደርሳሉ፣ ዛሬ የቀኖና ወንጌሎች የተባሉት ኦርጅናል አራቱ ወንጌሎች የለም፣ አራቱ ወንጌላት ተጻፉ የሚባሉት ከ 60-100 AD ሲሆን የእነርሱ የቅጂ ቅጂ ብጥስጣሽ"fragments" እና ደንገሎቹ"papiruses" የሚያሳዩት ግን ከ 200-250 AD ነው፦ የማቴዎስ ወንጌል ደንገል 45 የሚባለው በ 250 AD፣ የማርቆስ ወንጌል ደንገል 45 የሚባለው በ 250 AD፣ የሉቃስ ወንጌል ደንገል 75 የሚባለው በ 250 AD፣ የዮሐንስ ወንጌል ደንገል 46 የሚባለው በ 200 AD ነው፣ ዛሬ ያሉት 5800 ቀዳማይ የግሪክ እደ-ክታባት ኢየሱስ ካስተማረ ከሶስት መቶ አመት በኋላ የተዘጋጁ ናቸው፤ ዋና ዋናዎቹ ሳይናቲከስ ጥራዝ በ 330 AD፣ ቫቲካነስ ጥራዝ 350 AD፣ አሌክሳንድሪየስ ጥራዝ 400 AD፣ ኤፍሬማይ ጥራዝ 450 AD ላይ የተዘጋጁ ናቸው። ይህ እንዲህ በእንዲህ እንዳለ በ 397 AD የካርቴጅ ጉባኤ ፈላጭ ቆራጭ በመሆን የቅጂዎች ቅጂዎች የሆኑትን አራቱን ወንጌሎች ብቻ ቀኖና"canon" አድርጋ ሌሎችን ወንጌሎች "አፓክራፋ" አድርጋለች፤ "አፓክራፋ" የሚለው ቃል "አፓክራፈስ" ἀπόκρυφος ከሚለው ግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን "ድብቅ" ማለት ነው፤ ለዛ ነው አምላካችን አላህ፦ "የመጸሐፉ ሰዎች ሆይ እዉነቱንም እናንተ የምታወቁ ስትሆኑ ለምን ትደብቃላችሁ?" ብሎ የተናገረው፦ 3:71 የመጸሐፉ ሰዎች ሆይ! “እዉነቱን በዉሸት” ለምን *ትቀላቅላላችሁ*? “እዉነቱንም” እናንተ የምታወቁ ስትሆኑ ለምን *ትደብቃላችሁ*? يَٰٓأَهْلَ ٱلْكِتَٰبِ لِمَ تَلْبِسُونَ ٱلْحَقَّ بِٱلْبَٰطِلِ وَتَكْتُمُونَ ٱلْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ 5፥15 የመጽሐፉ ባለቤቶች ሆይ! *”ከመጽሐፉ ትሸሽጉት ከነበራችሁት ነገር ብዙውን ለእናንተ የሚገልጽ ከብዙውም የሚተው ሲኾን መልክተኛችን በእርግጥ መጣላችሁ*፡፡ ከአላህ ዘንድ ብርሃንና ገላጭ መጽሐፍ በእርግጥ መጣላችሁ፡፡ يَٰٓأَهْلَ ٱلْكِتَٰبِ قَدْ جَآءَكُمْ رَسُولُنَا يُبَيِّنُ لَكُمْ كَثِيرًۭا مِّمَّا كُنتُمْ تُخْفُونَ مِنَ ٱلْكِتَٰبِ وَيَعْفُوا۟ عَن كَثِيرٍۢ ۚ قَدْ جَآءَكُم مِّنَ ٱللَّهِ نُورٌۭ وَكِتَٰبٌۭ مُّبِينٌۭ “ከብዙውም የሚተው ሲኾን” ማለት የመጽሐፉ ባለቤቶች ከደበቋቸው ሁሉንም አልተናገሩም ማለት ነው፤ በቀኖና ያላካተቷቸው ግን የሸሸጓቸውን እንዳለ ይህ አንቀጽ ይጠቁማል፤ በወንጌሎች ታሪካዊ ዳራና ፍሰት ዋቢ መጽሐፍት ያደረኩት የአዲስ ኪዳን ምሁር የሆኑትን የፕሮፌሰር ባርት ሄርማን መጽሐፍት ነው፦ 1. The Other Gospels: Accounts of Jesus from Outside the New Testament. Oxford University Press, USA. 2013 by Bart D. Ehrman 2. The Orthodox Corruption of Scripture: The Effect of Early Christological Controversies on the Text of the New Testament. Oxford University Press, USA. 2011 3. Lost Scriptures: Books that Did Not Make It into the New Testament. Oxford University Press, USA. 2003 ኢንሻላህ በክፍል ሥስት እንቀጥላለን.... ✍ከወንድም ወሒድ ዑመር https://t.me/Wahidcom ወሰላሙ አለይኩም
نمایش همه...
سورة الكهف كاملة تلاوة هادئة وراحة نفسية في يوم الجمعة تريح الأعصاب محمد ديبيروف Surah al kahf አዳምጡ
نمایش همه...
የዓኢሻህ"ረ.ዐ." ትዳር በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ 61፥8 *"የአላህን ብርሃን በአፎቻቸው ሊያጠፉ ይሻሉ፡፡ አላህም ከሓዲዎቹ ቢጠሉም እንኳ ብርሃኑን ገላጭ ነው"*፡፡ يُرِيدُونَ لِيُطْفِئُوا نُورَ اللَّهِ بِأَفْوَاهِهِمْ وَاللَّهُ مُتِمُّ نُورِهِ وَلَوْ كَرِهَ الْكَافِرُونَ አንዲት እንስት ወጣት ናት፥ በሙሥሊሞች ዘንድ በአውንታዊ መልኩ በኢሥላም ታሪክ ላይ አሻራዋን ካስተቀመጡ እና ጉልህ ሚና ከተጫወቱት ሰዎች አንዷ ናት። ይህቺ ወጣት ከነቢያችን"ﷺ" ሰምታ ስለ ነቢያችን"ﷺ" ሕይወትና አኗኗር፣ ስለ ውርስ፣ ስለ ጋብቻ፣ ስለ መጨረሻው ዘመን ትምህርት ወዘተ 2,210 የሚደርሱ ሐዲሳትን ተርካለች፥ ቁርኣን የምእመናት እናቶች ከሚላቸው አንዷ ናት፦ 33፥6 *"ነቢዩ በምእምናን ከራሳቸው ይበልጥ ተገቢ ነው፥ ሚስቶቹም እናቶቻቸው ናቸው"*፡፡ النَّبِيُّ أَوْلَىٰ بِالْمُؤْمِنِينَ مِنْ أَنفُسِهِمْ ۖ وَأَزْوَاجُهُ أُمَّهَاتُهُمْ ይህችም ወጣት ሴት "ኡመል ሙእሚኒን" أُمِّ الْمُؤْمِنِين ማለትም "የምእመናን እናት" በሚል ማዕረግ የምትጠራ ዓኢሻህ"ረ.ዐ." ናት፥ በአንድ ወቅት ዝሙት ሠርታለች ተብላ የሐሰት ክስ ቀርቦባት አምላካችን አሏህ ሡረቱ አን-ኑር 24፥11-20 ያለውን አንቀጽ ስለ ንጽህናዋ አውርዷል፦ 24፥15 *"በምላሶቻችሁ በምትቅበባሉት ጊዜ ለእናንተም በእርሱ ዕውቀት በሌላችሁ ነገር በአፎቻችሁ በተናገራችሁና እርሱ አላህ ዘንድ ከባድ ኀጢአት ኾኖ ሳለ ቀላል አድርጋችሁ ባሰባችሁት ጊዜ ከባድ ቅጣት በነካችሁ ነበር*፡፡ إِذْ تَلَقَّوْنَهُ بِأَلْسِنَتِكُمْ وَتَقُولُونَ بِأَفْوَاهِكُم مَّا لَيْسَ لَكُم بِهِ عِلْمٌ وَتَحْسَبُونَهُ هَيِّنًا وَهُوَ عِندَ اللَّهِ عَظِيمٌ ሡነን አቢ ዳውድ መጽሐፍ 43, ሐዲስ 447 ዓኢሻህ"ረ.ዐ." እንደተረከችው፦ "ነቢዩም"ﷺ"፦ *"ዓኢሻህ ሆይ አብሽሪ! አሏህ ስለ ንጽህናሽ ወሕይ አውርዷል፥ ከዚያም ለእርሷ የቁርኣኑን አንቀጽ ቀሩላት። ወላጆቿም፦ "የአሏህ መልእክተኛን"ﷺ" ግንባር ሳሚ!" አሏት፥ እርሷም፦ "ለእናንተ ሳይሆን ለአሏህ ምስጋና ይሁን!" አለች"*። أَنَّ عَائِشَةَ، رضى الله عنها قَالَتْ ثُمَّ قَالَ تَعْنِي النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ أَبْشِرِي يَا عَائِشَةُ فَإِنَّ اللَّهَ قَدْ أَنْزَلَ عُذْرَكِ ‏"‏ ‏.‏ وَقَرَأَ عَلَيْهَا الْقُرْآنَ فَقَالَ أَبَوَاىَ قُومِي فَقَبِّلِي رَأْسَ رَسُولِ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏.‏ فَقَالَتْ أَحْمَدُ اللَّهَ لاَ إِيَّاكُمَا ‏.‏ ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 64, ሐዲስ 188 አቢ ኢብኑ መለይካህ እንደተረከው፦ *"ዓኢሻህ፦ "በምላሶቻችሁ በምትቅበባሉት ጊዜ" የሚለውን አንቀጽ ትቀራ ነበር፥ "አል-ወልቅ" ቅጥፈት ነው" ትል ነበር። አቢ ኢብኑ መለይካህም፦ "ይህን አንቀጽ ስለ እርሷ እንደሚናገር ከማንም ይልቅ ታውቅ ነበር" አለ"*። حَدَّثَنِي يَحْيَى، حَدَّثَنَا وَكِيعٌ، عَنْ نَافِعِ بْنِ عُمَرَ، عَنِ ابْنِ أَبِي مُلَيْكَةَ، عَنْ عَائِشَةَ ـ رضى الله عنها ـ كَانَتْ تَقْرَأُ ‏{‏إِذْ تَلِقُونَهُ بِأَلْسِنَتِكُمْ‏}‏ وَتَقُولُ الْوَلْقُ الْكَذِبُ‏.‏ قَالَ ابْنُ أَبِي مُلَيْكَةَ وَكَانَتْ أَعْلَمَ مِنْ غَيْرِهَا بِذَلِكَ لأَنَّهُ نَزَلَ فِيهَا‏.‏ ዓኢሻህ"ረ.ዐ." አባቷ አቡበከር አስ-ሲዲቅ እናቷ ኡሙ ሩማን ሲሆኑ የነቢያችን"ﷺ" ባልደረቦች ናቸው፥ ዓኢሻህ ለነቢያችን"ﷺ" ሚስት እንድትሆን ለቤተሰቦቿ አሳቡን ያመጣችው የነቢያችን"ﷺ" ሴት ባልደረባ የነበረችው ኸውላህ ቢንት ሐኪም"ረ.ዐ." ናት። ቅሉ ግን ዓኢሻህ ለነቢያችን"ﷺ" ሚስት እንደምትሆን ነቢያችን"ﷺ" በሕልማቸው ሁለት ጊዜ አይተዋታል፦ ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 67, ሐዲስ 16 ዓኢሻህ እንደተረከችው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"በሕልሜ ሁለት ጊዜ አይቼሻለው፥ አንድ ሰው(ጂብሪል) በሐር ጨርቅ ተሸክሞሽ፦ "ይህቺ የአንተ ሚስት ናት" አለኝ። ስገልጥ እነሆ አንቺ ነበርሽ። እኔም ዓኢሻህ ለራሴ፦ "ይህ ሕልም ከአሏህ ከሆነ ይፈጸማል" አልኩኝ"*። عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ‏ "‏ أُرِيتُكِ فِي الْمَنَامِ مَرَّتَيْنِ، إِذَا رَجُلٌ يَحْمِلُكِ فِي سَرَقَةِ حَرِيرٍ فَيَقُولُ هَذِهِ امْرَأَتُكَ، فَأَكْشِفُهَا فَإِذَا هِيَ أَنْتِ، فَأَقُولُ إِنْ يَكُنْ هَذَا مِنْ عِنْدِ اللَّهِ يُمْضِهِ ዓኢሻህ ለነቢያችን"ﷺ" የተዳረችው በስድስት ዓመቷ ሲሆን ለዐቅመ-ሐዋህ እስክትደርስ ድረስ ለሦስት ዓመት ከተጠበቀ በኃላ በዘጠኝ ዓመቷ ወደ ነቢያችን"ﷺ" ቤት ገብታለች፦ ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 16, ሐዲስ 82 ዓኢሻህ እንደተረከችው፦ *"ነቢዩ"ﷺ" ሲያገቡኝ የስድስት ዓመት እንስት ነበርኩኝ፥ የዘጠኝ ዓመት እንስት ስሆን ወደ ቤቱ ገባሁኝ"*። عَنْ عَائِشَةَ، قَالَتْ تَزَوَّجَنِي النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم وَأَنَا بِنْتُ سِتِّ سِنِينَ وَبَنَى بِي وَأَنَا بِنْتُ تِسْعِ سِنِينَ ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 67, ሐዲስ 69 ዓኢሻህ"ረ.ዐ." እንደተረከችው፦ *"ነቢዩ"ﷺ" ሲያገቧ የስድስት ዓመት ነበረች፥ የዘጠኝ ዓመት እንስት ሲሆናት ደረሱባት"*። عَنْ عَائِشَةَ ـ رضى الله عنها ـ أَنَّ النَّبِيَّ صلى الله عليه وسلم تَزَوَّجَهَا وَهْىَ بِنْتُ سِتِّ سِنِينَ
نمایش همه...
▯▩ ወይይት ▩▯ "መጀመሪያ ቃል ነበረ" ◍ ወንድም እስሚዝ 🆅🆂 ◍ ወገናችን ሳዳም ◍ ወገናችን ሣምሪ
نمایش همه...