የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe
﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student |
إظهار المزيد📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe
تُعد قناة የሕያ ኢብኑ ኑህ | Yahya Ibnu Nuhe (@yahyanuhe) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 21 224 مشتركاً، محتلاً المرتبة 3 706 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 1 587 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 21 224 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 06 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 293، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 11، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 20.79%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 9.23% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 412 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 959 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 95.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student |”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 07 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 06 يوليو | +11 | |||
| 05 يوليو | +2 | |||
| 04 يوليو | +10 | |||
| 03 يوليو | +5 | |||
| 02 يوليو | +5 | |||
| 01 يوليو | +3 |
| 2 | لا يوجد نص... | 990 |
| 3 | ሀምዛ ዞርትዚስ ከታዋቂው የሞሪታንያ ዓሊም ሸይኽ ዶ/ር ሙስጠፋ አል-ሸይባኒ ጋር ያደረጉትን እጅግ ጠቃሚ ውይይት ተመልክቼ ነበር። በተለይ በዚህ ዲጂታል ዘመን ዳዕዋ ስናደርግ ስለሚገጥሙን እንደ ኢጎ (እኔነት) እና የታዋቂነት ፈተናዎች እንዴት ማለፍ እንደምንችል ያነሱት ሀሳብ ልብ ይነካል። ቪዲዮውን እያየሁ የተወሰነ ማስታወሻ ለመያዝ የሞከርኩ ቢሆንም በመሀል የራሱ AI ሰመራይዝ ያደረገውን ስመለከት ግን ሀሳቤን በጥቅሉ ስለገለጸው እሱን በቡሌት ተርጉሞ ማስቀመጡን መርጫለሁ።
የውይይታቸው ዋና ዋና ነጥቦች እነሆ፡-
• ወደ አደባባይ እና ዲናዊ ስራ ከመውጣታችን በፊት በሌሊት ሶላት (ቂያሙል ለይል) እና በኢኽላስ (ቅንነት) ራሳችንን ማነፅ እና ከአላህ ጋር ያለንን ሚስጥራዊ ግንኙነት ማጠናከር አለብን።
• ቁርኣንን ለበረካ ብቻ ሳይሆን አስተሳሰባችንን ለመቅረፅ እና ራሳችንን ለመለወጥ ልንጠቀምበት ይገባል።
• ለዳዒ ትልቁ ጠላት ታዋቂነት ነው። ከተከታዮቻችን (followers) ቁጥር ይልቅ በዋናው አላማችን ላይ ብቻ ማተኮር አለብን፤ ስኬት ሁሌም ቢሆን የአላህ ስጦታ ነውና።
• ሱረቱ ዩሱፍ እንደሚያስተምረን ውጤታማ ዳዕዋ የረጅም ጊዜ እቅድን፣ ሰዎችን መረዳትን እና ትችትና ውድቀቶችን በትዕግስት ለማለፍ "ትልቅ ልብ" ሊኖረን ይገባል።
• ስኬት ከቤት ይጀምራል፦ የትዳር አጋራችን እና ቤተሰባችን ከውጭ ለሚገጥመንን ጫና መቋቋሚያ ትልቁ "መልህቃችን" ናቸው። ስለዚህ ጠንካራ እና አፍቃሪ የቤተሰብ ግንኙነት መገንባት ለስኬታችን ወሳኝ ነው።
በመጨረሻም ሀምዛ በራሱ ህይወት ተሞክሮ እንዳጠቃለለው፤ ምንም ያህል የተማርን እና የአካዳሚክ እውቀት ቢኖረንም፣ በዳዕዋ ስራችን ላይ ቁርኣን ሁሌም ቀዳሚ፣ ሀይለኛ እና ውጤታማው መመሪያችን ነው።
ሙሉ ውይይቱን በዚህ ሊንክ ማግኘት ትችላላችሁ፦ | 1 638 |
| 4 | لا يوجد نص... | 1 542 |
| 5 | رسالة صوتية | 335 |
| 6 | https://youtu.be/lVB7tDEdrFw | 341 |
| 7 | ‹‹እፎይ›› የተባለው ግለሰብ ሰሞኑን ያልጠበቀው አረንቋ ውስጥ ገብቶ እፎይታ ያጣ ይመስላል። ላለፉት ጊዜያት የራሱን ጓዳ (የገዛ ሃይማኖቱን) አቧራ የረሳው ይሄው ሰው፣ የእስልምናን አስተምህሮ ለመተቸት "አላህ እጅ አለው፣ እግር አለው ይላሉ" እያለ በማላገጥ የቲኦሎጂ "ሊቅ" ሆኖ ሲመጻደቅ ከርሟል። ሆኖም የሰው ቤት ሲሰልሉ መዋል የገዛ ቤትን ቃጠሎ አያጠፋምና፣ ዛሬ የገዛ ወንድሞቹና ሊቃውንቱ ከእግዚአብሔር አካላት ተሻግረው "እግዚአብሔር የመራቢያ አካል አለው ወይስ የለውም?" በሚል እጅግ አሳፋሪና ቀፋፊ አጀንዳ ላይ ሲተናነቁ አፉን ይዞ ከመደነቅ ውጪ ሌላ አማራጭ አላገኘም።
የገዛ ቴሌግራም ገጹ ላይ "ለሥላሴ የክፍል አካላት የሚሰጡ አንዳንድ መምህራን መኖራቸው ሲያስገርመን የነበረ ቢሆንም ጭራሽ ጾታ አላቸው የሚሉ... በመስማታችን አስደንግጦናል" እያለ የገዛ ቤቱን ጉድ አደባባይ አውጥቶታል። የፌዝ አዙሪት ማለት ይሄ ነው! ፈጣሪን ከፍጡር ጋር በማይመሳሰል፣ ልዕልናውንና ክብሩን በሚመጥን መልኩ የተገለጹትን የአላህን (ሱ.ወ) መለኮታዊ ባህሪያት በራሳቸው ጠባብ የሰውኛ ልክ ሰፍረው ለማላገጥ ሲሞክሩ፣ የራሳቸው የሥነ-መለኮት ግድግዳ ግን ፈርሶ መዓት መጣባቸው።
እኛ ከዚህ ቀደም "ሃይማኖተ አበው"ን እና መሰል የቤተክርስቲያኒቱን መጻሕፍት ዋቢ አድርገን፣ ፈጣሪ ጥፍር፣ ጸጉርና መሰል የሰውነት ክፍሎች እንዳሉት የሚገልጸውን የገዛ ትምህርታቸውን ስናወያያቸው፣ እውነታውን ለመጋፈጥ ድፍረት አጥተው ጆሮ ዳባ ልበስ ብለው ነበር። አሁን ግን ጉዳዩ ከጥፍርና ከጣት አልፎ፣ "ፈጣሪ የመራቢያ አካል አለው? ወንድ ነው ወይስ ሴት?" ወደሚል ከፈጣሪ ክብርና ልዕልና ጋር ፈጽሞ ወደማይገናኝ፣ እጅግ የወረደና ስንኩል አስተሳሰብ ውስጥ ተዘፍቀዋል። ከዚህ በላይ አዋራጅ ነገር ከየት ይመጣል? የሰው ዓይን ውስጥ ያለውን ጉድፍ ለማውጣት ሲታገሉ፣ የራሳቸውን መዋቅራዊ ግንድ ማየት የተሳናቸው ዕውር-ድንብሮች መሆናቸውን በተግባር አረጋገጡልን።
የእነ "እፎይ" እና የመሰሎቹ ትልቁ ችግር እውቀት ማነስ ብቻ ሳይሆን፣ አእምሯዊ ስንፈት ጭምር ነው። የራሳቸውን መሠረታዊ እምነት፣ ሥርዓተ-አምልኮ እና የሊቃውንቶቻቸውን መጻሕፍት እንኳ በቅጡ ሳያነቡ፣ በጭፍን ጥላቻ ብቻ የሌላውን እምነት ለማጥላላት ይሯሯጣሉ። የሰው እምነት ላይ ድንጋይ ለመወርወር ከመሞከር በፊት የራስን የመስታወት ቤት መፈተሽ እንደሚገባ አላወቁትም።
እውነትን በትክክል ሳያውቁና የገዛ ቤታቸውን ቆሻሻ ሳያጸዱ ለክርክር መነሳት የሚያመጣው የውርደት ካባ ይህ ነው። "እፎይ" ዛሬ የራሱ ቤት በሥነ-መለኮት ቀውስ ሲታመስና ጣዖት አምልኮን በሚያስንቅ ትርክት ሲበከል ማየቱ፣ የገዛ ድንቁርናውና የጥላቻው ፍሬ የሰጠው የክብር ሜዳሊያ ነው። የሌላውን ከማንቋሸሽ በፊት ቢያንስ የራስን አምላክ "ጾታ" እና "የመራቢያ አካል" ጉዳይ ከሊቃውንቶቻቸው ጋር ተወያይተው አንድ መቋጫ ላይ ቢደርሱ ይቀድም ነበር!
⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
https://t.me/Yahyanuhe | 4 425 |
| 8 | لا يوجد نص... | 3 380 |
| 9 | ኢትዮጵያ ፌደራላዊ ስርዓት መከተል ከጀመረችበት ጊዜ አንስቶ፣ የኢትዮጵያ ሙስሊም የመብት ጥያቄዎች አፈታት እጅግ በጣም ዘገምተኛ እና አሰልቺ ሆኗል። ለዓመታት የጮኽንለትና የታገልንለት መሰረታዊ መብት አሁንም መፍትሄ አልባ ሆኖ እየተንከባለለ ይገኛል።
በጣም የሚያሳዝነው ደግሞ፣ ትላንትና ከመዋቅሩ ውጪ ሆነው ለህዝብ ሲታገሉ የነበሩ ሰዎች፣ ዛሬ የመጅሊሱን መንበር አግኝተው የተሻለ የመፍትሄ አካል እንዲሆኑ ሲጠበቁ የሚናቸው መደብዘዝ ግን እጅግ አሳዛኝ ነው።
ችግሮችን ከስር መሰረታቸው ቀድሞ ከመፍታት ይልቅ፣ አደጋ ሲከሰት ብቻ ከወቀሳ ለመዳን በሚመስል መልኩ ችግሩ ቦታ እየተገኙ መሯሯጥ የተለመደ ተግባር ሆኗል።
ህዝቡ እና ተማሪዎች በእንደዚህ አይነት ከባድ የማንነት ፈተና ውስጥ እያሉ፣ የመጅሊስ አመራሮቹ መኖራቸውን እራሱ የምናውቀው በሚታደሙበት የበዛ ድግስ ላይ በሚኖር ምስላቸው ነው። ያለ ቅጥ ከፍተኛ በጀት እየተያዘላቸው ከሚከወኑ ድግሶች ብዛት የተነሳ ለህዝብ ብሶት ጆሮ የሚሰጡበት ጊዜ ያገኙም አይመስሉም። ይህ አካሄድ ከእስልምና የአመራርና የአማና መርህ ጋር ፍፁም የሚጣረስ ነው።
ታላቁ ጌታችን አላህ ይህንን ከባድ የኃላፊነት ሚዛን በቅዱስ ቁርኣን እንዲህ ሲል ያስጠነቅቃል፡-
"እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህንና መልክተኛውን አትክዱ፡፡ እናንተ የምታውቁ ስትኾኑ አደራዎቻችሁንም አትክዱ፡፡" (አል-አንፋል 8፥27)
መሪነት ምቾት ሳይሆን ከባድ ፈተና ነው። በኃላፊነት ላይ ተቀምጦ ህዝብን ችላ ማለት የሚያስከትለውን አደጋ፣ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ በማለት አብራርተውታል፡-
"ማንኛውም አላህ የህዝብ መሪ ያደረገው ሰው፣ ህዝቡን በቅንነት ሳያገለግልና ሳይመክር (እያታለላቸው) ከሞተ፤ አላህ በርሱ ላይ ጀነትን እርም ያደርግበታል።" (ሰሒሕ አል-ቡኻሪ 7150)
መሪነት አገልጋይነት እንጂ የሰርክ ድግስ ታዳሚነት አይደለም። አመራሮች ወደ ህሊናቸው ተመልሰው፣ የተቀመጡበት ወንበር የህዝብ አደራ መሆኑን ተገንዝበው እውነተኛ መፍትሄ ሊያመጡ ይገባል። ጊዜያዊ ወቀሳን ለማምለጥ ከመሯሯጥ ይልቅ፣ ዘላቂ የሆነ የህዝብን እንባ የሚያብስ ጠንካራ ስራ ሊሰራ ይገባል!
የሕያ ኢብኑ ኑህ | 5 595 |
| 10 | لا يوجد نص... | 4 023 |
| 11 | በአማራ ክልል በሙስሊሙ ማኅበረሰብ ላይ የሚፈጸመው ግፍ፣ ሰቆቃና አፈና ማብቂያ ያጣ ይመስላል። ትናንት ምሽት በዳንግላ ከተማ የዒሻ ሶላትን አሰግደው ወደ ቤታቸው በመመለስ ላይ ሳሉ፣ በታጣቂዎች ተደብቀው የተገደሉት የሼኽ ሱፍያን አደም ሕልፈት፣ የዚህ መሪርና ቋሚ ሐዘናችን ቀጣይ ምዕራፍ ነው።
ሼኽ ሱፍያን ከ20 ዓመታት በላይ በመስጂድ ኢማምነት ያገለገሉ፣ ከሙስሊሙም ሆነ ሙስሊም ካልሆነው ወገን ጋር በሰላም የኖሩ የመስጂድ ኢማም ናቸው። ታዲያ እንዲህ ዓይነቱን የሰላም ሰው በጨለማ ደብቆ መግደል ከጀርባው ያለው መልእክት ምንድን ነው?
እውነታው አፍረጥርጦ የሚናገረው አንድ ነገር አለ፦ በክልሉ ውስጥ ሆን ተብሎ የሃይማኖት ግጭት ለማስነሳት፣ ሙስሊሙን ከማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ህልውናው ለማፈናቀል፣ እንዲሁም ማኅበረሰቡን መሪ አልባ ለማድረግ የሃይማኖት አባቶችን ነጥሎ የማጥቃት አደገኛ ዘመቻ በስፋት እየተተገበረ ይገኛል።
ይህ በታጣቂዎች የሚተገበረው እኩይ ተግባር፣ በአጋጣሚ የሚፈጸም ወንጀል አይደለም። ይልቁንም በተለያዩ የኦርቶዶክስ አክቲቪስቶችና ጽንፈኛ የሚዲያ አካላት፣ ለወራትና ለዓመታት ሲያረግዙትና ሲያቀነባብሩት የነበረው የጥላቻ ትርክትና የዘር ማጥፋት ፕሮፓጋንዳ የወለደው የትግበራ ውጤት ነው።
እነዚህ አካላት ዛሬ ለሚፈሰው የንጹሐን የሃይማኖት መሪዎች ደም የመጀመሪያ ተጠያቂዎች ናቸው። የሼኽ ሱፍያንን ንጹሕ ደም አላህ አይተወውም! ለቤተሰቦቻቸው፣ ለዳንግላ ሙስሊሞችና ለመላው የሀገራችን ሙስሊም ማኅበረሰብ አላህ መጽናናትን ይስጠን።
የዳንግላው ኢማም ግድያ | 5 029 |
| 12 | ለንግድ፣ ለህክምና ወይም ለጉብኝት ወደ ቱርክ፣ ዱባይ እና የተለያዩ ሀገራት ለመጓዝ ካሰባችሁ ፈሲሩ ትራቭል የትኬት ጉዳያችሁን በኃላፊነት ያጠናቅቃል። እንግልት የሌለበት ጉዞ ለማድረግ ስትፈልጉ በዋትስአፕ አግኙን፦
https://wa.me/qr/5CWCIMYBZLCJB1
+251911762080 | 4 568 |
| 13 | ለንግድ፣ ለህክምና ወይም ለጉብኝት ወደ ቱርክ፣ ዱባይ እና የተለያዩ ሀገራት ለመጓዝ ካሰባችሁ ፈሲሩ ትራቭል የትኬት ጉዳያችሁን በኃላፊነት ያጠናቅቃል። እንግልት የሌለበት ጉዞ ለማድረግ ስትፈልጉ በዋትስአፕ አግኙን፦
+251911762080 | 1 |
| 14 | ለንግድ፣ ለህክምና ወይም ለጉብኝት ወደ ቱርክ፣ ዱባይ እና የተለያዩ ሀገራት ለመጓዝ ካሰባችሁ ፈሲሩ ትራቭል የትኬት ጉዳያችሁን በኃላፊነት ያጠናቅቃል። እንግልት የሌለበት ጉዞ ለማድረግ ስትፈልጉ በዋትስአፕ አግኙን፦
+251911762080 | 1 |
| 15 | "በሰዎች ላይ ጥገኛ በሆንክ ቁጥር፣ በእነርሱ ዘንድ ያለህ ክብርም ልክ ጥገኛ በሆንክበት መጠን ይቀንሳል፤ የምትለምናቸው አንዲት ጉንጭ ዉሃ እንኳን ብትሆን።"
(ኢብኑ ተይሚያህ፥ መጅሙዕ አል-ፈታዋ 39/1)
የሰው ልጅ በተፈጥሮው ስስ ነው። ደጋግሞ ሲጠየቅ ይሰለቻል፣ ሲደገፉበት ይከብደዋል፣ ሲለምኑትም ንቀትን ያመጣል። የቱንም ያህል የሚወድህ ቢሆን፣ ሁሌ እጅህን ወደ እርሱ ከዘረጋህ "ሸክም" መሆንህ አይቀርም። እውነተኛ የክብር ከፍታ ያለው ሰዎች ዘንድ በመተናነስ ውስጥ ሳይሆን፣ ከሰዎች እጅ በመብቃቃት ውስጥ ነው።
ይህንን የሰው ልጅ ስነ-ልቦናዊ እውነት ታላቁ ጌታችን በቅዱስ ቁርኣን በአንድ ወሳኝ ቃል አጠቃልሎታል፡-
"በአላህም ላይ ተመካ፡፡ መመኪያም በአላህ በቃ፡፡" (አል-አሕዛብ 33፥3)
የሚገርመው የአላህና የሰው ልጅ ተቃራኒ ባህሪ እዚህ ጋ ነው። ሰው ስትለምነው ይንቅሃል፤ አላህ ግን ሳትለምነው ስትቀር ይቆጣል። ነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ለባልደረባቸው ለሰህሉ ብኑ ሰዕድ (ረ.ዐ) የሰጡት አጭርና ወርቃማ የሕይወት ፎርሙላ ይህንኑ የሚያስረግጥ ነው፡-
"ከዚህች ዓለም ድንበር እለፍ (ዙህድ አድርግ) አላህ ይወድሃል፤ በሰዎች እጅ ባለው ነገር ላይም አትመኝ (ተስፋ ቁረጥ) ሰዎች ይወዱሃል።" (ሱነን ኢብኑ ማጀህ 4102)
የውስጥ ነፃነትህ የሚጀምረው "ሰው ምን ይለኛል ወይም ምን ይሰጠኛል" ከሚል ጠባቂነት ራስህን ስታላቅቅ ነው። ግንባርህን ለፈጣሪህ ብቻ አዋርድ፤ ያኔ አላህ በሰዎች ፊት ቀና ብለህ እንድትሄድ ያደርግሃል። ሰዎች ዘንድ ክብርህን ማቆየት ከፈለግክ፣ ከእነርሱ ምንም አለመፈለግን ልመድ።
© የሕያ ኢብኑ ኑህ | 4 536 |
| 16 | ይህ በምስሉ ላይ በድምቀት የምትመለከቱት የ"መልካም ወጣት" ማዕከል ፕሮጀክት፣ የዘመናችን ምርጡ የቢዝነስ እና የፖለቲካ ከቨር ሆኖ ብቅ ብሏል። ጉዳዩን በጥልቀት ለተመለከተው፣ በውስጡ የሚከተሉት አስገራሚ "ተዓምራት" ይፈጸሙበታል፦
የመጀመሪያ ነገር ፕሮጀክቱ ዓለማዊ ሽፋን ያለው 100% ሃይማኖታዊ ፕሮጀክት ነው። ወጣቶችን ከሱስ እና ከብልሹ አሠራር "ማገገም" (Rehabilitation) የሚለው ቃል ለጆሮ እጅግ ጣፋጭ ነው። ይህን ዓለማዊ እና በጎ አድራጎታዊ ሽፋን በመጠቀም ግን የሚሰጠው ቶታሊ ሃይማኖታዊ ዶክትሪን ነው። መንግሥትም ሆነ ሕዝብ "ለወጣቶች እያሰቡ ነው" ብሎ ሲያጨበጭብ፣ ከጀርባ ያለው ዋናው ዓላማ ግን የተቋማቱን የሃይማኖት አጀንዳ ማስፈጸም ነው።
ሌላኛው አላማው መሬት በነፃ የማግኘት "መንፈሳዊ" ጥበብ ነው። ለምን በሚሊዮኖች አውጥተህ መሬት ትገዛለህ? "ለወጣቶች ማገገሚያ" የሚል ፕሮፖዛል ይዘህ፣ በተለይም በደቡብ ክልሎች አካባቢ ብቅ ካልክ፣ የመንግሥት መሬት እንደ መና ከሰማይ ይወርድልሃል። ይህ የ"መልካም ወጣት" ሽፋን፣ ሰፋፊ መሬቶችን ለመቀበል፣ የንግድ ኔትወርኮችን ለመዘርጋት እና የኢኮኖሚ አቅምን ለማሳለጥ የተገኘ የዘመናችን ምርጥ ማስተር ፕላን ሆኗል።
ሶስተኛው የሚደንቀኝ ነገር በማይክሮፎን የሚሰጥ "ከፍተኛው ፍርድ ቤት" ውሳኔ የሚመስለው ነገር ነው። የዚህ መድረክ አስቂኝና አሳዛኝ ገጽታ፣ የሕግ የበላይነትን በ"ሃሌሉያ" ማጠቡ ነው። በመድረኩ ላይ የሚወጡ ወጣቶች፤ "ሰው ገድያለሁ፣ ዘርፊያለሁ፣ ደብድቤያለሁ" እያሉ በአደባባይ ከባድ የወንጀል ኑዛዜ ሲያደርጉ፣ ፖሊስ ካቴና ይዞ መምጣት ሲገባው፣ ታዳሚው አሜን ብሎ ያጨበጭባል! መድረኩ የሕግ ተጠያቂነትን የሚያስቀር፣ ነፍስ ላጠፋና ወንጀል ለሠራ ሰው ያለ ስልጣኑ ምሕረት የሚሰጥ የጠቅላይ ፍርድ ቤት ሚናን ተረክቧል።
በአጠቃላይ፣ በ"መልካም ወጣት" ስም በሚታደል የደቡብ ክልል መሬት ለማካካስ የተደረገው ይህ ስትራቴጂ... በእውነትም "የአሥር ዓመት ስኬት" ሊባልለት የሚችል ነው።
© የሕያ ኢብኑ ኑህ | 3 724 |
| 17 | لا يوجد نص... | 3 517 |
| 18 | ኒቃብ ፊትን እንጂ አእምሮን አይሸፍንም!
ዛሬ ከሰመራ ዩኒቨርሲቲ የተሰማው አስደሳች ዜና የተዛቡ ትርክቶችን ከመሰረቱ የሚያፈርስ እና ትልቅ መልእክት ያለው ነው።
ሙተነቂቧ እህታችን ሀስና ኢብራሂም ከሰመራ ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ተመራቂ ሴት ተማሪዎች የላቀ ውጤት በማምጣት የዋንጫ ተሸላሚ ሆናለች። ከዚህም ባለፈ ከጤናና ሕክምና ኮሌጅ ከፍተኛ ውጤት በማስመዝገብ በከፍተኛ ማዕረግ የሜዳሊያ ባለቤት ለመሆን በቅታለች።
ይህ ድንቅ ስኬት አንድ ዐቢይ እውነታን አፍረጥርጦ ይነግረናል፣ ኒቃብ ፀጉርን እና ፊትን ከባዕድ እይታ ይጋርዳል እንጂ፣ አእምሮን፣ ዕውቀትን እና ጥበብን አይሸፍንም።
በተለያዩ ተቋማት ኒቃብን እንደ እንቅፋት የሚቆጥሩ እና እህቶቻችንን ከትምህርት ገበታና ከሥራ ዓለም ለማግለል የሚሞክሩ አካላት መኖራቸው የአደባባይ ምሥጢር ነው። ሆኖም የሀስና ስኬት፣ እነዚህ ክልከላዎች ከጭፍን ጥላቻ የዘለለ አንዳችም ምክንያታዊ መከራከሪያ እንደሌላቸው ሕያው ምስክር ነው። የልብስን ቁመት እና የጨርቅን ቀለም እያዩ የሰውን ልጅ አቅም መመዘን እጅግ ያረጀ ኋላቀርነት መሆኑን በተግባር አሳይታናለች።
ችግሩ ያለው በእህቶቻችን አለባበስ ላይ ሳይሆን፣ የሰዎችን ማንነት በውጫዊ ገጽታቸው ብቻ በሚመዝነው ጠባብ አመለካከት ላይ ነው። ሀስናዎች ፊታቸውን ቢሸፍኑም፣ ብሩህ አእምሯቸው ግን ለሀገርና ለወገን የሚፈነጥቅ ብርሃን መሆኑን አረጋግጠዋል።
እንኳን ደስ አለሽ ሀስና! ይህ ስኬትሽ ለብዙ እህቶቻችን መነቃቂያ፣ መብታቸውን ለሚጋፉ ጠባብ አሳቢዎች ደግሞ ተገቢ እና በሳል ምላሽ ነው።
⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
https://t.me/Yahyanuhe | 4 520 |
| 19 | ውብና ማራቂ ቂርኣቶችን በቴሌግራም ማዳመጥ ስትሹ፣ እነሆ ቻናል!
https://t.me/Qurantilawas | 4 202 |
| 20 | የቃላት ቁጥጥር እና የትርጉም ፖለቲካ!
ቋንቋ የቃላት ስብስብ ብቻ አይደለም፤ የአንድ ማህበረሰብ የማሰብ አድማስ፣ ዓለምን የሚያይበት እይታው የሚገለጽበት የስነ-ልቦናው ውቅር ነው። አንድን ህዝብ በወታደር ወርሮ ከመግዛት ይልቅ፣ የሚያስብበትን ቋንቋና የሚጠቀምባቸውን ቃላት ትርጉም መቆጣጠር የረጅም ጊዜ የአእምሮ የበላይነትን ያጎናጽፋል።
የ1911ዱ የላክኖው ኮንፈረንስ እና ተከታታይ የሚሽነሪ የቋንቋ ጥናቶች ያረጋገጡት አንድ ትልቅ እውነት አለ፦ “የክርስትናን ዶክትሪን በምዕራባዊ የቃላት ቆዳ ከሸፈንነው ሙስሊሙ እንደ ባዕድ ነቀርሳ ይተፋዋል፤ በገዛ ቋንቋውና በለመደው የቃላት ቃና ከቀመመነው ግን እንደ ማእድ ይመገበዋል።” ይህ ንጹህ የቋንቋ ጥናት የሚመስለው፣ በውስጡ ግን ከባድ የርዕዮተ-ዓለም ዘረፋ የያዘው ስልት በምሁራዊ አጠራሩ "ስነ-ልሳናዊ ጠለፋ" (Linguistic Hijacking) ይባላል።
ይህ ስልት መሬት ላይ ሲተገበር እጅግ አስገራሚ የሆነ የቃላት ስርቆት ይፈጽማል። ሚሽነሪዎች መጽሐፍ ቅዱስን ወይም ስነ-ጽሑፎቻቸውን ወደ አረብኛ ወይም ኦሮምኛ ሲተረጉሙ አዳዲስ ቃላትን አይፈጥሩም፤ ይልቁንም በሙስሊሙ ማህበረሰብ ዘንድ ከፍተኛ የክብር፣ የፍርሃትና የልቅና ስሜት ያላቸውን ነባር ኢስላማዊ ቃላት ይወስዳሉ። ለምሳሌ 'እግዚአብሔር' ለማለት 'አላህ' ወይም 'ረቢ'፣ 'ኢየሱስ' ለማለት 'ዒሳ'፣ 'ምዕራፍ' ለማለት 'ሱራ'፣ እንዲሁም 'ወንጌል' ለማለት 'ኢንጂል' የሚሉትን ቃላት ይጠቀማሉ።
እዚህ ጋ የተፈጸመው የስነ-ልቦና ማጭበርበር ምንድነው? ቃሉ የሙስሊሙ ነው (ለምሳሌ 'አላህ')፣ በዚያ ቃል ውስጥ የተሞላው ትርጉም ግን የሥላሴ ዶክትሪን ነው። ሙስሊሙ አንባቢ ጽሁፉን ሲያነብ የራሱን ቃል ስላገኘ ንቃተ-ህሊናው የጥርጣሬ በሩን ዝግ ያደርጋል፤ በገዛ የቃላት ቋቱ ውስጥ የተሸሸገውን ባዕድ ጽንሰ-ሀሳብም ያለምንም ተቃውሞ ወደ አእምሮው ያስገባል።
በ20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ዩጂን ኒዳ የተባለ የቋንቋ ምሁር ያመጣው "Dynamic Equivalence" (ተለዋዋጭ አቻ ትርጉም) የተሰኘው መርህ ይህንን ስልት ወደ ላቀ የሳይንስ ደረጃ አድርሶታል። በዚህ መርህ መሠረት፣ ዋናው ቁምነገር የጥንታዊውን ጽሑፍ ቃል በቃል መተርጎም ሳይሆን፣ 'አንባቢው ጽሑፉን ሲያነብ ልክ ኦሪጂናል ጸሐፊው በሱ ቋንቋ እንደጻፈው አድርጎ እንዲሰማው ማድረግ' ነው። ለዚህም ሲባል በሚሽነሪዎች የሚዘጋጁ የአረብኛ በራሪ ጽሑፎችና ትራክቶች የሚጀምሩት በምዕራባዊ ሰላምታ ሳይሆን፣ "አሰላሙ ዐለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱሁ... የተወደዳችሁ ወገኖቼ" በሚል ጥልቅ ኢስላማዊ የቃላት ዜማ ነው።
የቁርዓንን የአጻጻፍ ሪትምና ሰዋሰዋዊ ውበት ኮፒ በማድረግ፣ የክርስትናን መልእክት በኢስላማዊ የስነ-ጽሑፍ ሻንጣ ውስጥ አሽገው ያቀርቡታል። አንባቢው 'ይህ መጽሐፍ ከቫቲካን ወይም ከለንደን የመጣ ነው' ብሎ ማሰብ አቁሞ፣ የሰፈሩ ሰው የጻፈው እስኪመስለው ድረስ በቃላት ወጥመድ ይያዛል።
ይህ የቋንቋ ጦርነት በአፍሪካ ቀንድና በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የነበረው ሚና እጅግ ሰፊ ነው። ላሚን ሳኔህ የተባለው ታዋቂው የታሪክ ምሁር "Translating the Message" በተሰኘው መጽሐፉ ላይ እንዳብራራው፣ ሚሽነሪዎች የአካባቢውን ቋንቋዎች በላቲን ወይም በራሳቸው ፊደል መዝገበ-ቃላት ሲያዘጋጁላቸው ዋነኛ አላማቸው ንባብ ማስተማር ብቻ አልነበረም።
ህዝቡ ወደ አረብኛ ቋንቋና ወደ ኢስላማዊ ስነ-ጽሑፍ ከመሳቡ በፊት፣ የቋንቋውን 'የሃይማኖት መዝገበ-ቃላት' (Theological Vocabulary) በክርስትና መነጽር ቀድመው ለመቆለፍ የተደረገ የጊዜ ሩጫ ነበር። ቃላትን የፈጠረ ወይም መዝገበ-ቃላትን ያጠናቀረ አካል፣ ያ ህዝብ በሚቀጥሉት መቶ ዓመታት ስለ 'ኃጢአት'፣ ስለ 'ጽድቅ' እና ስለ 'አምላክ' የሚያስብበትን የአእምሮ ድንበር ይወስናልና። የብዕርን ጦርነት በቋንቋ ሰዋሰው ውስጥ የመሸሸግ ይህ ጥበብ፣ ያለምንም የጦር ሜዳ የህዝብን የማሰብ አቅም በቅኝ ግዛት ስር የማዋረድ የረቀቀ ፖለቲካ ነው።
በቀጣዩ ክፍል የምንዳስሰው አጀንዳ፡
ድብቁ መረብ - "የቤት ውስጥ አብያተ ክርስቲያናት" እና ማህበረሰብን ከጓዳ ጀምሮ የመሸርሸር ስልትን በቀጣይ ክፍል - 15 በአላህ ፍቃድ እንመለከተዋለን።
የመረጃ ምንጮች፦
• Lamin Sanneh, "Translating the Message: The Missionary Impact on Culture".
• Eugene A. Nida, "Toward a Science of Translating" (Dynamic Equivalence Principles).
• Papers and Discussions of Lucknow Missionary Conference, 1911 (Literature & Language Section).
⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻⁻
https://t.me/Yahyanuhe | 4 677 |
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
