የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe
﷽ | Muslim | Theology | Comparative Religion | Philosophy | Student | Teacher |
Ko'proq ko'rsatish14 453
Obunachilar
+924 soatlar
+377 kunlar
+35830 kunlar
- Kanalning o'sishi
- Post qamrovi
- ER - jalb qilish nisbati
Ma'lumot yuklanmoqda...
Obunachilar o'sish tezligi
Ma'lumot yuklanmoqda...
ቁሳዊ ፊትና - መስፈርታችን
ከሰሞኑ ፕ/ር ዋዒል ኻላቅ በነበራቸው አንድ ኢንተርቪው ላይ የ"ዘመናዊ አለም" ሁለት አካላት/Components/ እንዳሉት ይጠቅሳሉ። እነዚህም Essential እና Accidental ሲሉ ይከፍሏቸዋል። Essential/አስፈላጊ የሚባለው አካል ልብና አእምሮው Capital/ ካፒታሊዝም አይደለም/ እና በዚያ ላይ የተመረኮዘ ስርአት እንደሆነ ያብራራሉ። በአጭሩም ሲያብራሩት የሰው ልጅ ዋጋውና ክብሩ የሚለካው ባለው የቁስ አካል መጠን መሆኑን ይጠቅሳሉ።
"ዘመናዊ አለም" ካመጣብን ጉድለቶች መካከል የሰው ልጅ ሚዛኑ በዘመኑ ያገኘው ገንዘብና መሠል ቁሶችን አድርጎ ማስቀመጡ ነው። የሰው ልጅም ክብር ሊሰጥህ ዘንድ የመጀመሪያው ጥያቄ ስራህንና የገቢ መጠንህን ያማከለ ነው። የክብሩ መጠን ከዚህ መልስ በኃላ የሚወሰን ነው። ጥሩ ገንዘብ ካለህ ክብሩ አለ፣ ካልሆነ ግን በዚያው ቅጽበት በህሊናቸው ለሚስሉት "ያልተከበረ ሰው" ራስክን ማዘጋጀት ሊኖርብህ ይገባል።
ይሄ የዘመናዊነት ዳፋ ቁሳዊ/Materialistic/ ማኅበረሰብ እንዲፈጠር ዳርጎታል። በመተሳሰብ የሚሰሩ ስራዎች ሳይቀር ዋጋ ተተምኖላቸው ንግድ ሁነዋል። ከሰሞኑ የተመለከትኩት ጃፓናውያንን የተመለከተ አንድ ዶክመንትሪ ለዚህ ማሳያ ነው። ጃፓናውያኑ ብቸኛ ለሆኑ ሰዎች ራሳቸውን በማከራየት የጉዞና መሠል አጋር በመሆን የከፋዮቻቸውን ሀሳብ በመስማትና ጓደኛ በመሆን ገንዘብ ያገኛሉ። የቀና መተሳሰብ የሞላበት ጓደኝነት እና ወንድማማችነትም በሒደት ገመዱ እየላላ ለመሄዱ ማሳያ ነው። በምዕራቡ አለም ለማያቁት ሰው ማህጸን እያከራዩ ገንዘብ በማግኘት እናትነት የሚባለውን ልዩ ስሜት ወደጎን በማድረግ የገቢ ማስገኛ አድርገው የሚተዳደሩ ሳይቀር ተፈጥረዋል።
የአሏህ መልዕክተኛ "ﷺ" እንደተናገሩት አማና ሲጠፋ ቂያማ ለመቃረቡ ማሳያ ነው። አማና አንድ ነገር ነው፣ አሁን ግን በቁስ አለም ተመዝነው በርካታ የመልካም ስነ ምግባር ገመዶች እየተበጣጠሱ ነው። ኢማም ማሊክ رحمه الله ስለ እውቀታቸው ሲናገሩ "ይህንን እውቀት ለራሳቸው ሲሉ (እራሳቸውን ለማስተካከል) ሲሉ ብቻ እንደተማሩት ይገልጻሉ። ለኛ የተረፈው የእግረ መንገድ ትጋት ውጤት እንጅ ዋና ልፋታቸው እራሳቸውን ለማነጽ ነበር። ዘመኑ በተቃራኒው ዋጀንና ለራስ መማር ቅድሚያ ለራስ መሆኑን እየዘነጋን መጣን። የዲን ወንድማማችነትና ሙሐባ በጥቅምና በሰጥቶ መቀበል ካልሆነ ዘመናዊ በተባለው አለም ለማግኘት ቸጋራ ሁኗል። ወዳጅነት የሚገኝን ጥቅም ተሰልቶበት እንጅ የማይፈለግ ንብረትም ሁኗል።
የ"ዘመናዊው አለም" የፈጠራቸው መሠል የግብረ ገብነት ንግዶች በተቻለ መጠን በዲን ልጓም ማላላት ካልተቻለ እንደ ዑማ መጭያችን አስጊ ነው። አሏህ በንጹህ ልቦና ያዋደን..!
👍 47❤ 16👏 1😢 1
Photo unavailableShow in Telegram
ቁርዓን ከአሏህ ዘንድ ለመሆኑ አሳማኝ ነጥቦች | ክፍል -3 | ኡስታዝ ኢልያህ ማሕሙድ
https://youtu.be/mFFXKkP0YkY?si=oq6QpyVzjHd4Mbkl
👍 25❤ 2
እስራኤልን የሚደግፈው ክርስቲያኑ አለም ዘንድ ያለው ሎጂክ ሲታሰብም ገርሞ የሚያስገርም ነው። እግዚአብሔርን "ከሰቀሉት" አይሁዳውያንና ሮማውያን ይልቅ በታሪኩ ያላመኑ ሙስሊሞችን ይቀጣቸዋል ብለው ያስባሉ..! Logic has left the chat …
👍 148🤷♂ 11🙊 9🤩 5🙉 4
አምባገነኑ ንጉስ 1,000 ሰውና 1 አህያ እንዲገደሉ በተሰበሰበው ህዝብ ፊት አዋጅ አሳወጀ። የተሰበሰበው ህዝብም ግራ በመጋባት "አህያው ለምንድን ነው የሚገደለው?" ሲሉ ጠየቁ። ንገሱ ወደ አማካሪዎቹ ዙሮ "ከ1,000 ሰው ይልቅ ስለ አህያው እንደሚጠይቁ ቀድሜ አልነገርኳችሁም ነበር?" አለ።
...
የሚገጥመን ሌላ የሚጠየቀው ሌላ እየሆነ ግራ ገባነ
👍 106🤩 28🔥 9🥰 8
Photo unavailableShow in Telegram
የሰው ልጅ እዚህ ምድር ላይ ሲኖር በርካታ እንቆቅልሾችን ያሳልፋል። ከመከራ ሸለቆዎች ውስጥ የድርሻውን ይሻገራል። እዚህ ምድር ላይ ሙሉ ደስታን መሻት ለሰው ልጅ የተመቸ እጣፈንታ አይደለም። ግን የሰው ልጅ ብርቱ ነውና ሁሉኑም እንደ አመጣጣቸው ይቀበላቸዋል። በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ገብቶ ለሀዘኑ እጅ መስጠቱ ቀሪውን ዘመኑን ከማጉበጥ የዘለለ የሚፈይድለት አንዳችም ነገር የለም።
ዱንያ የዩሱፍን ውበት፣ የአባቱን ሀዘንና መከራ፣ የወንድሞቹን ክህደትና ክፋት የያዘች ምድር ናት። ዱንያን እንደ ባህሪዋ መቀበል ግድ ነው። አሏህ ምሉዕ ደስታን ሊሰጠን ጀነትን አዘጋጅቶልናል። ከዚህ ውጭ ይህች ምድር ለኛ ምናችን ናት? ልባችን ከምኗ ይጣበቃል?ሁሉም ታይቶ ጠፊና ጊዜያዊ ብቻ ነው።
የጀነቱ ባለቤት ከጸጋው አይከልክለን!
🔖 https://t.me/Yahyanuhe
❤ 100👍 29🥰 3🔥 1
Photo unavailableShow in Telegram
የሶሻል ሚዲያ ተከታይ ብዛት
በዕለተ ትንሳኤ ከሚፈጠሩ ኹነቶች መካከል አንዱን የአሏህ መልዕክተኛ "ﷺ" እንዲህ ሲሉ ይነግሩናል፦
"ምንም ተከታይ የሌለው ነብይ ይመጣል" ቡኻሪ 5752
ይህ ነብይ ምንም ተከታይ አልነበረውም ማለት ተልዕኮውን አልተወጣም ማለት አይደለም። ወደ አሏህ የሚጣሩና ከአሏህ ውጭ ማንም የማያቃቸው ብዙ ሰዎች አሉ። ዋናው ቁምነገር ስኬቱ አይደለም፣ ትግሉና ኒያው ነው። ስኬቱና ሒዳያው በአሏህ ﷻ እጅ ነው። የሰው ልጅ ተልዕኮ ሀሳቦችን ልቦች ውስጥ ለመትከል መጣር ነው። የተዘራውን ሀሳብ ህያው ማድረግ የኛ ኃላፊነት አይደለም።
አንድ ሰው በማኅበራዊ ሚዲያ በርካታ ተከታይና አድማጭ አለው ማለት አሏህ ዘንድ ስራው ተቀባይነት አለው ማለት አይደለም። ኒያና ኢኽላስ ካልተስተካከለ ድካም ሁሉ ከንቱ ነው። ያለውን የተከታይ ብዛት ወደ መልካም አጋጣሚ ተጠቅሞ ሰውን መጥቀም ከቻለ አጅሩ እጥፍ ነው። ባለው ተከታይ ብዛት ታብዮ ኢኽላስን ከዘነጋ ግን ልፋቱ ከንቱ ነው።
አሏህ ይገስጸን..!
📎 https://t.me/Yahyanuhe
👍 104❤ 28
Photo unavailableShow in Telegram
የወንድማችን አህመድን ህይወት ለማትረፍ በሚደረገው ትግል ውስጥ በትንሹ ድጋፋችሁም ቢሆን የወንድማችንን ተስፋ ለማለምለም ሰበብ መሆን ትችላላችሁ። ለህክምና ከሚያስፈልገው ብር ውስጥ ሊሞላ የቀረው ውስን ብር ነው፣ የቀረችውን ተባብረን በአቅማችን እንሙላት።
ድጋፍ ለማድረግ፦
Account name:
muhammed suleiman & or Taju suleiman.
Comercial bank
1000632758638
Zemzm bank
0042125420101
Awash bank
014251356745900
ለበለጠ መረጃ
0910373510 ታጁ ሱለይማን ...ወንድም
0921572121 ሙሀመድ ሱለይማን ...ወንድም
👍 50❤ 3🥰 2
Boshqa reja tanlang
Joriy rejangiz faqat 5 ta kanal uchun analitika imkoniyatini beradi. Ko'proq olish uchun, iltimos, boshqa reja tanlang.