Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Канал Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር) (@ibnumunewor) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 109 882 підписників, посідаючи 311 місце в категорії Релігія і духовність та 282 місце у регіоні Ефіопія.
📊 Показники аудиторії та динаміка
З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 109 882 підписників.
За останніми даними від 05 вересня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 488, а за останні 24 години на 1, загальне охоплення залишається високим.
- Статус верифікації: Не верифікований
- Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 13.69%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 7.50% реакцій від загальної кількості підписників.
- Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 15 038 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 8 238 переглядів.
- Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 0.
📝 Опис та контентна політика
Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
“كناشة ابن منور”
Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 06 вересня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.
Триває завантаження даних...
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 06 вересня | +11 | |||
| 05 вересня | +12 | |||
| 04 вересня | +17 | |||
| 03 вересня | +26 | |||
| 02 вересня | +2 | |||
| 01 вересня | +4 |
| 2 | ደርስ፦
* ኪታቡ ተውሒድ
* ክፍል - 21
* የሚሰጥበት ቦታ፦ ሑዘይፋህ መስጂድ (የሺ ደበሌ ከፍ ብሎ)
* የሚሰጥበት ጊዜ፦ ቅዳሜና እሁድ ከመግሪብ በኋላ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 2 837 |
| 3 | ዛሬ እሁድ ነሐሴ ዐ1/2018 የኪታቡ ተውሒድ ደርስ ይኖራል፣ ኢንሻአላህ።
* ቦታ፦ ሑዘይፋ መስጂድ (ከየሺ ደበሌ ከፍ ብሎ)
* ጊዜ፦ ዘወትር ቅዳሜና እሁድ ከመግሪብ እስከ ዒሻ
* ኪታቡ የሌላችሁ በዚህ ሊንክ pdf ፋይል ታገኛላችሁ:- https://t.me/IbnuMunewor/9564 | 5 990 |
| 4 | የሃይለ ስላሴ መንግስት ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር የነበራትን የፌዴሬሽን ትስስር አፍርሶ ሲያዋህድ የነፍጥ ትግሉን ሀ ብሎ የጀመረው ሓሚድ ኢድሪስ አዋቴ እንደሆነ ይነገራል። ሰላሳ አመት በወሰደው የኤርትራ የነፃነት ትግል ላይ ሙስሊሞቹ ፋና ወጊ ነበሩ። ነገር ግን ገና ከነፃነቱ ጫፍ ሳይደርሱ ነው በሸዕቢያ አከርካሪያቸው የተመታው። ከነፃነት በኋላም ለኤርትራ ሙስሊሞች የኢሳያስ መንግስት ከደርግ የባሰ እንጂ የተሻለ አይደለም።
በህወሃት ትግል ላይም የትግራይ ሙስሊሞች አጥንታቸውን ከስክሰው ደማቸውን አፍስሰው ብዙ ዋጋ ከፍለዋል። ይሁን እንጂ አክሱምን እንዳያረክሱ ተብሎ መስገጃና መቃብር ተነፍገዋል። ከዚህ በላይ ጭካኔ የለም። ሴቶች ልጆቻቸውም ሻሽ ለብሰው እንዳይማሩ ተከልክለዋል። ጭፈራና አስካሪ መጠጥ የማያረ^ክሳት አክሱም በመስጂድና በሙስሊም መቃብር እንደምትረክስ የሚታመነው ሙስሊሞች በክልሉ ወሳኝ ሃይሎች ዘንድ ምን ያህል የተናቁ እንደሆኑ በቂ ማሳያ ነው።
ሌሎቹም "የነፃነት ትግሎች" ከዚህ የራቀ እይታና ግብ የላቸውም። ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለመቃወም አሕመድ ዐሊ የሚለውን የአባቱን ስም እንደማታገያ የሚጠቀም ኋላ ቀር ስብስብ ከስም ባለፈ ጠቅላዩ ሙስሊም ቢሆን ኖሮ ዘመቻቸው ዛሬ ከምናየውም የተለየ ይሆን ነበር።
ቀላል የማይባል ሙስሊም ግን በነዚህ አካላት የማይረባ ፕሮፓጋንዳ እየተጠለፈ አብሮ በመሰለፍ ከባድ ዋጋ ሲከፍል ይታያል። መስዋእትነት አልልህም። ዱንያ ኣኺራህን እያጣህ ኪሳራ እንጂ ቅንጣት ታክል መስዋእትነት አታገኝም። ለነዚህ እምነትህን ለሚፀየፉ አካላት ህይወትና ንብረትህን ቀርቶ እንቅልፍህን ልትሰዋላቸው አይገባም። ለራስህም፣ ለቤተሰብህም ብትኖር ነው የሚሻለው። በውጥረትና በትግል ላይ እያለ እምነትህን ያላከበረ አካል በተደላደለ ሁኔታ ላይ ሲሆን መብቴን ያከብራል ብለህ አታስብ።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 6 946 |
| 5 | «አሁን የመጡት መሪያችን (ዶር አብይ አሕመድ ዓሊ) የአባታቸውና የአያታቸው ስም የእኛ እምነት ስለማይመስል ከተመረጡ ጀምሮ እንቅልፍ አልወሰደንም»
የአፓርታይዷ ቄስ የኢትዮጵያን መሪ ስሙ ከሱ ስም ጋር አንድ ዓይነት መሆን አለበት፣ መለየት የለበትም ብሎ ያምናል😎
ለማንኛውም ከእነዚህ ጋር ነው እየኖርን ያለነው። እነዚህ በሙስሊሙ ላይ በአከባቢያቸው እየፈጸሙት ያለ ግፍ መፈጠርን ያስጠላል።
መረጃው ከ ትግራይ ሙስሊም ሚድያ ገፅ የተወሰደ ነው።
ህወሓትም ቢሆን ከዚህ የተሻለ አመለካከት የለውም። በፌዴራል መንግስት ተገፍቻለሁ እያለ ዞሮ የክልሉን ሙስሊሞች በሃይማኖታቸው ሰበብ በያይነቱ የግፍ አይነት ያወርድባቸዋል። አቅሙ በቀለለበት በዚህ ጊዜ በደል ከመፈፀም ያልተመለሰ ድርጅት ያለ ተቀናቃኝ አገር ቢቆጣጠር ክፋቱ ከዚህም የባሰ ነው የሚሆነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 7 539 |
| 6 | السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
ሳምንታዊ የደርስ ፕሮግራም
~
* ቦታ፦ ሑዘይፋ መስጂድ
* ጊዜ፦ ዘወትር እሁድ ከረፋዱ 4:00 ጀምሮ
ኪታቦች
1. منھج السالكين
2. كن سلفيا على الجادة
3. من أصول عقيدة أهل السنة فوزان
ሼር በማድረግ አግዙን ባረከላሁ ፊኩም። | 8 400 |
| 7 | ከሐራም ነገር ከባዱ የመጀመሪያው ነው። ከዚያ ሲደጋገም እየቀለለ ይሄዳል። ከዚያ እንዲሁ ተራ ነገር ይሆናል። ከዚያ ልማድ ይሆናል። ከዚያ ይጣፍጣል። ከዚያ ልብ ይሸፈናል። ከዚያ ልብ ሌላ ሐራም መፈለግ ይጀምራል።
አንድ ሷሊሕ ሰው እንዲህ ይላል፦ "ነፍስህ ወደ ወንጀል ከጋበዘችህ በዚች አንቀፅ አጭር ቃለ መጠይቅ አድርግላት :-
{ أَذَ ٰلِكَ خَیۡرٌ أَمۡ جَنَّةُ ٱلۡخُلۡدِ ٱلَّتِی وُعِدَ ٱلۡمُتَّقُونَۚ }
"ይሄ ነው የሚሻለው ወይስ ጥንቁቆቹ ተስፋ የተሰጧት የዘለዓለሟ ጀነት?" [አልፉርቃን፡ 15]
በዚህ ሐራም ነገሮችን መዳፈር በበዛበት ዘመን ይህቺን አንቀጽ ማስተዋል ምንኛ አንገብጋቢ ነው?!
ከዐረብኛ የተመለሰ
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 8 938 |
| 8 | ደርስ፦
* ኪታቡ ተውሒድ
* ክፍል - 20
* የሚሰጥበት ቦታ፦ ሑዘይፋህ መስጂድ (የሺ ደበሌ ከፍ ብሎ)
* የሚሰጥበት ጊዜ፦ ቅዳሜና እሁድ ከመግሪብ በኋላ
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 9 144 |
| 9 | ዛሬ እሁድ ነሐሴ 30/2018 የኪታቡ ተውሒድ ደርስ ይኖራል፣ ኢንሻአላህ።
* ቦታ፦ ሑዘይፋ መስጂድ (ከየሺ ደበሌ ከፍ ብሎ)
* ጊዜ፦ ዘወትር ቅዳሜና እሁድ ከመግሪብ እስከ ዒሻ
* ኪታቡ የሌላችሁ በዚህ ሊንክ pdf ፋይል ታገኛላችሁ:- https://t.me/IbnuMunewor/9564 | 9 727 |
| 10 | ~ ሃኪም እና ታማኝነት ~
~
አንድ ሃኪም / ሃኪም ቤት ሊታከም ለመጣ ሰው ታማኝ መሆን አለበት።
* የታካሚውን ሚስጥር ሊያወጣ አይፈቀድም። የታካሚውን ምስል ያለ ፈቃዱ ለሚዲያ ሊያቀርብ አይገባም።
* ከአቅሙ በላይ የሆነ ነገር ከገጠመው ወደተሻለ ቦታ መጠቆም እንጂ የሰውን ልጅ መለማመጃ ሊያደርግ አይፈቀድም። ከባድ ወንጀል ነው።
* ገንዘቡን ያላግባብ ሊያስወጣው አይፈቀድም። የሰው ገንዘብ ሐራም የሚሆነው በስርቆትና በዝርፊያ ብቻ አይደለም። ምርመራና መድሃኒት በማዘዝ፣ አስተኝቶ በማከም፣ በቀዶ ህክምና፣ በየትኛውም መንገድ ባልተገባ መልኩ የታካሚውን ገንዘብ ያስወጣ ሰው የሰው ገንዘብ እየዘረፈ ነው። ይህን ያደረገ ሰው እያንዳንዱ ሰው ገንዘቡን እንዴት እንዳመጣው እና በምን እንዳወጣው በሚጠየቅበት አስፈሪው የቂያማ ቀን ወዮለት። ዛሬ ያላግባብ ለተወሰደ ገንዘብ ሁሉ ነገ ጥብቅ ሂሳብ አለ። ብር በብር አይመለስም። ከመልካም ስራህ ነው ተላልፎ የሚሰጠው። እሱ ካልበቃ የተበዳይ ወንጀል ነው ባንተ ላይ የሚጣለው። ለማይረባ አላፊ ዱንያ ዘላለማዊ ህይወትን ከማጨለም መጠንቀቅ ይገባል።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ነሐሴ 30/2014)
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 9 350 |
| 11 | https://t.me/merkezabumussa1?videochat=ef8edee7a2de72bdbb | 2 148 |
| 12 | ደርስ፦
~
* ሉምዐቱል ኢዕቲቃድ
* ክፍል፦ 09
* የኪታቡን pdf በዚህ ሊንክ ታገኛላችሁ:- https://t.me/IbnuMunewor/9934
* የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 21 | 9 857 |
| 13 | ኢኽወቲ ወአኸዋቲ ፊ'ላህ!
~
አመለካከታችንም፣ ግንዛቤያችንም ስለሚለያይ የምፅፈው ሁሉ ለሁሉ ሰው ይስማማል ተብሎ አይታሰብም። የማንም የግል ፀሐፊ አይደለሁምና የማምንበትን እንጂ ሰው እንዳይከፋ እያልኩ እንደማልፅፍ ማሳወቅ አይጠበቅብኝም። ከዚህ በተቃራኒ፣ ሰው እንደመሆኔ ራሴን ማጥራራት ባልፈልግም፣ ማንንም ለማብሸቅና ለእልህ ከመፃፍም እጠነቀቃለሁ ብዬ አስባለሁ። መነገር አለበት ብዬ የማምንበትን ሃሳብ ሰዎችን እንደሚያስከፋ እያወቅኩም ለመናገር እሞክራለሁ። ይሄ አካሄዴ ለአንዳንዶቻችሁ እልህ፣ ለሌሎች የሒክማ ማጠር፣ ለሌሎች ደግሞ ከፋፋይነት ሊሆን ይችላል። የውስጤን አላህ ያውቃል። በኔ ቤት ለወገኔ ይበጃል የምለውን ማካፈሌ ነው።
የሆነ ሆኖ ሃሳቤ በቀጥታ በፅሁፌ የማሰፍረው ነው። የምደብቀውም የለኝም፣ የምደብቅበትም ምክንያት የለኝም። ይህን የምለው "በዚህ ንግግሩኮ ይህንን ነው የፈለገበት" አይነት ትንታኔ ስለሚገጥመኝ ነው። ተወገዘም፣ ተወደሰም የምፈልገው የፃፍኩትን ነው፣ አለቀ። ሌላ ትርጉም የምትሰጡ ሁሉ! ሆነ ብላችሁ አጣማችሁ ሳይሆን መስሏችሁ ብትሳሳቱብኝ ከየትኛውም ቡድን ብትሆኑ ዐፍው ብያለሁ። ሆነ ብሎ ንግግሬን አጣሞ በመተርጎም ለሚከሰኝ ደግሞ ሂሳባችን ከአላህ ዘንድ ነው።
እኔንም እናንተንም ልባችንን አላህ ለሐቅ ክፍት ያድርግልን። በሐቅ ላይም ይሰብስበን። ኣሚን።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 10 631 |
| 14 | ጥሪ ለሙስሊሙ ኡማ!
(የሃይማኖቱ ጉዳይ ለሚያሳስበው ሃላፊነት ለሚሰማው ሙስሊም ሁሉ!)
~
በአዲስ አበባ እና በአንዳንድ የክልል ከተሞች አሕ^ባሾች ድምፃቸውን አጥፍተው በተጠናከረ መልኩ እየተንቀሳቀሱ ነው፡፡ አካሄዳቸውም ህፃናትን ከተለያዩ አካባቢዎች በመሰብሰብ ረዘም ላለ ጊዜ በማሰልጠን ስለሆነ አደጋውን ይበልጥ የከፋ ያደርገዋል፡፡ በቁርኣን ሒፍዝ ስም በሚሰበስቧቸው ልጆች ልቦና ውስጥ አደገኛ የሆነ መርዝ በመትከል ዐቂዳቸውን እየበከሉ ስለሆነ ወገናችንን ለመታደግ ከወላጆች ዘንድ አስፈላጊውን ግንዛቤ ልንፈጥር፣ የምንችለውን ሁሉ ልናደርግ ይገባናል፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በህዝብ እንደተተፉ የገባቸው አሕ^ባሾች መልካቸውን ቀይረው በአንዳንድ አካባቢዎች በተብሊጎች ስም እየተንቀሳቀሱ ነው፡፡ ሰዎችን በኹሩጅ ከሰበሰቡ በኋላ ቀስ በቀስ የራሳቸውን ብልሹ ዐቂዳ ለማስረግ እየተጉ ነው፡፡
ስለሆነም ነገ አላህ ፊት ከመጠየቃችን በፊት ዛሬ ፈጥነን ነገሮችን በሚገባ ማጤን እና ዙሪያ ገባችንን ማስተዋል የግድ ይለናል፡፡ በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች በሚገኙ የተለያዩ የቁርኣን የሒፍዝ ማእከላት ልጆቻችሁን ያስገባችሁ ወላጆች ሁሉ፡ ነገ አላህ ፊት ከመጠየቃችሁ በፊት፣ የልጆቻችሁንም ዘላለማዊ ህይወት ከማበላሸታችሁ በፊት ከወዲሁ አስፈላጊውን እርምጃ ውሰዱ። ያስገባችሁበትን መርከዝ ምንነት በሚገባ አስረግጡ፡፡ ያለበለዚያ ነገ ብዙ መስዋእትነት ያስከፍለናል፡፡ ከዚያ በላይ ግን ለዘላለማዊ ፀፀት ይጥለናል፡፡ ከዐርሹ በላይ ያለው ጌታችን እንዲህ ይለናል፡-
يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا قُوا أَنْفُسَكُمْ وَأَهْلِيكُمْ نَارًا وَقُودُهَا النَّاسُ وَالْحِجَارَةُ عَلَيْهَا مَلَائِكَةٌ غِلَاظٌ شِدَادٌ لَا يَعْصُونَ اللَّهَ مَا أَمَرَهُمْ وَيَفْعَلُونَ مَا يُؤْمَرُونَ
“እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ነፍሶቻችሁንና ቤተሰቦቻችሁን መቀጣጠያዋ ሰዎችና ደንጋዮች ከሆነችዋ (የጀሀነም) እሳት ጠብቁ፡፡ በርሷ ላይ ጨካኞች፣ ሃይለኞች የሆኑ መላእክት አልሉ፡፡ አላህን ያዘዛቸውን ነገር (በመጣስ) አያምፁትም፡፡ የሚታዘዙትንም ሁሉ ይሰራሉ፡፡” [አት-ተሕሪም፡ 6]
ነብዩም ﷺ እንዲህ ይላሉ፡-
(كُلُّكُمْ رَاعٍ وَكُلُّكُمْ مَسْؤول عَنْ رَعِيَّتِهِ، الإِمَامُ رَاعٍ وَمَسْؤولٌ عَنْ رَعِيَّتِهِ، وَالرَّجُلُ رَاعٍ فِي أَهْلِهِ وَهُوَ مَسْؤولٌ عَنْ رَعِيَّتِهِ، وَالْمَرْأَةُ رَاعِيَةٌ فِي بَيْتِ زَوْجِهَا وَمَسْؤولَةٌ عَنْ رَعِيَّتِهَا، وَالْخَادِمُ رَاعٍ فِي مَالِ سَيِّدِهِ ومَسْؤولٌ عَنْ رَعِيَّتِهِ، قَالَ: وَحَسِبْتُ أَنْ قَدْ قَالَ: وَالرَّجُلُ رَاعٍ فِي مَالِ أَبِيهِ وَمَسْؤولٌ عَنْ رَعِيَّتِهِ- وَكُلُّكُمْ رَاعٍ وَمَسْؤولٌ عَنْ رَعِيَّتِهِ)
“ሁላችሁም እረኞች ናችሁ፡፡ ሁላችሁም ስለ እረኝነታችሁ (ስለ ሃላፊነታችሁ) ተጠያቂ ናችሁ፡፡ መሪ እረኛ ነው፤ ስለ እረኝነቱም ተጠያቂ ነው፡፡ ወንዱ (ባል) በቤተሰቡ ላይ እረኛ ነው፤ ስለ እረኝነቱም ተጠያቂ ነው፡፡ ሴቷም በባሏ ቤት ውስጥ እረኛ ነች፤ ስለ እረኝነቷም ተጠያቂ ነች፡፡ አገልጋይም በአለቃው ንብረት ላይ ተጠያቂ ነው፤ ስለ እረኝነቱም ተጠያቂ ነው፡፡ ‘አንድ ሰው በአባቱ ንብረት ላይ ተጠያቂ ነው፤ ስለ እረኝነቱም ተጠያቂ ነው’ ያሉም ይመስለኛል ይላል ዘጋቢው፡፡ ሁላችሁም እረኞች ናችሁ፡፡ ሁላችሁም ስለ እረኝነታችሁ ተጠያቂ ናችሁ፡፡” [ቡኻሪና ሙስሊም]
ስለዚህ ከተጠያቂነት ለመዳን፣ እራሳችንን እና ወገናችንን ለማትረፍ ሃላፊነታችንን እንወጣ፡፡ ወገን ለወገኑ ደራሽ ነው፡፡ አላህ በዲናችን የመጣውን ፈተና ያንሳልን፡፡ የተሻለውንም ይምረጥልን፡፡ ኣሚን፡፡ ይህን መልእክት በሰፊው በማሰራጨት የምንችላትን እናድርግ፡፡ የአላህ ፈቃዱ ከሆነ የሚጠቀምበት ሰው ይኖራል፡፡
=
(ኢብኑ ሙነወር፣ ነሐሴ 29/2007)
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 15 290 |
| 15 | Немає тексту... | 9 337 |
| 16 | ዛሬ ጁሙዐ ረቢዑል አወል 22/1448 (ነሐሴ 29/2018) የሉምዐቱል ኢዕቲቃድ ኪታብ ደርስ ይኖራል፣ ኢንሻአላህ።
* የሚሰጥበት ቦታ: - አሸዋ ሜዳ፣ መስጂዱል ዋሊደይን
* ቀን:- ዘወትር ረቡዕ፣ ሐሙስ እና ጁሙዐ
* ሰዓት፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
* የኪታቡን pdf በዚህ ሊንክ ታገኛላችሁ:- https://t.me/IbnuMunewor/9934
* የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 21
* በቦታው ተገኝታችሁ መከታተል ለማትችሉ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል:- https://t.me/IbnuMunewor | 8 999 |
| 17 | መድ'ኸሊይ እንዳትሆን!
~
ሸይኽ ረቢዕ አልመድ'ኸሊይ - ረሒመሁላህ - እንደማንኛውም ዓሊም ናቸው። ይሄ ደረጃቸውን ዝቅ ማድረግ አይደለም። ከሳቸው የሚበልጡ ታላላቅ ዑለማኦችን በጭፍን መከተል አይፈቀድም ስንል ደረጃቸውን ዝቅ ማድረግ እንደማይሆነው ማለት ነው። ረቢዕ ልክ እንደሌሎቹ ዓሊሞች በየትኛውም ርእስ ላይ ቢሆን ፍፁም አይደሉም። በትንሽ በትልቁ በሸይኽ ረቢዕ ንግግር የሚያስፈራራ ቢኖር ራሱን ነው የሚሸውደው። ሱናን እከተላለሁ የሚል አካል በየትኛውም ዓሊም ላይ ያለው ምልከታ ለከት ሊኖረው ይገባል። አንድን ዓሊም መለኪያም፣ መስፈሪያም፣ መቁረጫም ማድረግ አይገባም። ሸይኽ ዐብዱልዐዚዝ አራጂሒይ - ሐፊዞሁላህ - የሌሎች ዓሊሞችን ንግግር ገሸሽ በማድረግ የሸይኽ ረቢዕን ንግግር በተለዬ የሚይዙ ስለሆኑ ሰዎች ሲጠየቁ እንዲህ ነበር ያሉት፦
يعني جعلوه رسولا، جعلوا ربيع رسولا، جعلوه رسولا، وهذا باطل، هذا باطل، ربيع ... يخطيء و يصيب و لا هو المييزان، الميزان: كلام الله و كلام الرسول، فمن قال: الميزان ربيع، هذا باطل.
"መልእክተኛ አደረጉት ማለት ነው?! ረቢዕን መልእክተኛ አደረጉት?! ይሄ ውድቅ ነው። ይሄ ውድቅ ነው። ረቢዕ ... ይስታል፣ ያገኛል። ሚዛን አይደለም። ሚዛኑ የአላህ ንግግር እና የመልእክተኛው ንግግር ነው። ሚዛኑ ረቢዕ ነው የሚል ይሄ ውድቅ ንግግር ነው።" [ከድምፅ ቅጅ የተወሰደ ነው።]
ስለዚህ የአልባኒይ፣ የኢብኑ ባዝ፣ የኢብኑ ዑሠይሚን፣ ወዘተ ንግግር በጭፍን እንደማይወሰደው የረቢዕ ንግግርም በጭፍን አይወሰድም። ረቢዕ በሌሎች መሻይኾች ላይ የሚናገሩትም በማስረጃ የተደገፈ ሲሆን ይወሰዳል፣ ካልሆነ ይጣላል። እንጂ ተናጋሪው ረቢዕ በመሆናቸው ብቻ ይወሰዳል ማለት አይደለም። አልባኒያ፣ ባዚያ፣ ዑሠይሚኒያ፣ ፈውዛኒያ፣ ... የሚባል መዝሀብ እንደሌለው መድ'ኸሊያ የሚባል መዝሀብም የለም። ስለዚህ አኢማዎችን በጭፍን የሚከተል ሐነፊይ፣ ማሊኪይ፣ ሻፊዒይ፣ ሐንበሊይ፣ ... መሆን እንደሌለብህ ሁሉ ረቢዕን በጭፍን የሚከተል መድ'ኸሊይ ልትሆንም አይገባም። እዚህ ላይ በቃል ደረጃ ችግር የለም። በተግባር ግን በተለያዩ መሻይኾች ላይ ድንበር ማለፍ ስላለ ጥንቃቄ እንዲኖረን ማስታወስ ነው የፈለግኩት። (ለጥጠው ሌላ ትርጉም ከሰጡ በኋላ በራሳቸው ምናብ ላይ ነብር ሆነው ለረድ የሚነሱ እንደሚኖሩ እጠብቃለሁ።)
በተረፈ የኢኽ'ዋን ጀሌዎች እዚህ እንዳትመጡ። የዚህ ፅሑፍ ጭብጥ በቅርብም በሩቅም ከናንተ ጋር የሚገናኝ አይደለም። የኢኽ'ዋን ቡድን ዘንድ የአንጃቸውን ጥመት ከተናገርክ፣ የነ ሐሰን አልበና፣ ሰይድ ቁጥብ፣ ቀርዷዊይ፣ ... ጥፉ አካሄዶች ካስጠነቀቅክ፣ ... በኢኽ'ዋን ቫይረስ በተጠቁ አካላት ዘንድ አንተ መድ'ኸሊይ ወይም ጃ'ሚይ ነህ። ልክ የሙታን አምልኮን፣ በአላህ ሲፋት ላይ ማራቆትን ስታወግዝ "ወሃ'ቢይ" እንደምትባለው ማለት ነው። ለነዚህ ሸይኽ ዒምራን ዐሊይ ሪድዋን አልፋሪሲይ - ረሒመሁላህ - እንዳሉት እንላለን፦
قُـلْ لِلَّذِي اتَّـخَـذَ الـتَّـجَـهُّـمَ مَـرْكَـبًـا
وَ رَآهُ دِيـنًـا و ارْتَــضَـاهُ مَـذْهَــــبًـا
وَ لِـمَـذهَبِ الأَبـــرَارِ صَارَ مُـكَـذِّبـًـا
إنْ كَانَ تَـابِـعُ أَحـمَــــدٍ مُـتَـوَهِّــبًـا *** فَـأَنـا الـمُــــقِـرُّ بِـأَ نَّـنِـي وَهَّـــابِي
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥር 17/2016)
=
* የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor | 10 340 |
| 18 | Немає тексту... | 9 447 |
| 19 | الـرد على أبي مُحمـدٍ ابن حـزمٍ(ت456)
في (إنكاره معاني أسمـاء الله)، و(إنكاره أن يُقال: صفةُ الله)
وفي الـخـاتـمـة: خُلاصـةُ البحث في (ثلاثين) نُقطـةً مُـهـمـةً جـدا
قناة الشيخ أبو العباس الشحري
https://t.me/aleabaas | 10 187 |
| 20 | ደርስ፦
~
* ሉምዐቱል ኢዕቲቃድ
* ክፍል፦ 08
* የኪታቡን pdf በዚህ ሊንክ ታገኛላችሁ:- https://t.me/IbnuMunewor/9934
* የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 16 | 10 873 |
