cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል

በማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል የምዕመናን መረጃ መለዋወጫና ትምህርት መስጫ አውታር ነው፡፡

نمایش بیشتر
Advertising posts
34 329مشترکین
+2924 ساعت
+1637 روز
+83130 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

የማኅበረ ቅዱሳን ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ማስተባበሪያ ማየት ለተሳናቸው ምእመናን የጸሎት መጽሐፍትን አዘጋጅቶ አስመረቀ። በስብከተ ወንጌል አገልግሎት ሰፊ ሥራዎችን እየሠራ የሚገኘው የማኅበረ ቅዱሳን ትምህርት እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ማስተባበሪያ የስብከተ ወንጌልና የርቀት ትምህርት አገልግሎት ዋና ክፍል ማየት ለተሳናቸው ምእመናን አገልግሎት የሚውል የብሬል የጸሎት መጽሐፍትን እና የድምጽ ትምህርቶችን በማዘጋጀት አስመርቋል። በመርሐ ግብሩ ላይ በአዲስ አበባ ስድስት ኪሎ ማየት የተሳናቸው ት/ቤት ግቢ ጉባኤ ሥር መንፈሳዊ ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ ለሚገኙ ተማሪዎች የብሬል መጽሐፍቱ በነጻ የተሰጣቸው ሲሆን በቀጣይ ማስተባበሪያው በሌሎች አገራችን ክፍሎች እያስተማራቸው ለሚገኙ ማየት የተሳናቸው ምእመናን ተደራሽ ለማድረግ እንደሚሠራ ተገልጿል። በዕለቱ ማኅበረ ቅዱሳን መሰል ሥራዎችን በትኩረት በማከናወን የስብከተ ወንጌል አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረገ እንደሆነ የተጠቀሰ ሲሆን በተለይ የብሬል መጽሐፍት እና የድምጽ ትምህርቶቹን በሚገባ ለማዳረስ የአጋር አካላት ድጋፍ እንደሚያስፈልገው ተጠቁሟል።
نمایش همه...
የማኅበረ ቅዱሳን ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ማስተባበሪያ ማየት ለተሳናቸው ምእመናን የጸሎት መጽሐፍትን አዘጋጅቶ አስመረቀ። በስብከተ ወንጌል አገልግሎት ሰፊ ሥራዎችን እየሠራ የሚገኘው የማኅበረ ቅዱሳን ትምህርት እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ማስተባበሪያ የስብከተ ወንጌልና የርቀት ትምህርት አገልግሎት ዋና ክፍል ማየት ለተሳናቸው ምእመናን አገልግሎት የሚውል የብሬል የጸሎት መጽሐፍትን እና የድምጽ ትምህርቶችን በማዘጋጀት አስመርቋል። በመርሐ ግብሩ ላይ በአዲስ አበባ ስድስት ኪሎ ማየት የተሳናቸው ት/ቤት ግቢ ጉባኤ ሥር መንፈሳዊ ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ ለሚገኙ ተማሪዎች የብሬል መጽሐፍቱ በነጻ የተሰጣቸው ሲሆን በቀጣይ ማስተባበሪያው በሌሎች አገራችን ክፍሎች እያስተማራቸው ለሚገኙ ማየት የተሳናቸው ምእመናን ተደራሽ ለማድረግ እንደሚሠራ ተገልጿል። በዕለቱ ማኅበረ ቅዱሳን መሰል ሥራዎችን በትኩረት በማከናወን የስብከተ ወንጌል አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረገ እንደሆነ የተጠቀሰ ሲሆን በተለይ የብሬል መጽሐፍት እና የድምጽ ትምህርቶቹን በሚገባ ለማዳረስ የአጋር አካላት ድጋፍ እንደሚያስፈልገው ተጠቁሟል።
نمایش همه...
37🙏 7👍 6
ይሁን እንጅ እስራኤል ሁሉ ለእግዚአብሔር በኵር ሆነው ሊዘልቁ ባለመቻላቸው፣ ለደብተራ ኦሪት ለክህነት አገልግሎት ተመራጭ ባለመሆናቸው እግዚአብሔር ከነገደ ሌዊ አሮንና ልጆቹን ለቤተ መቅደሱ አገልግሎት በመለየቱና በመምረጡ ደቂቀ ቆሬና ሌሎቹ ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ መግባት የክህነትን ሥራም መሥራት ፈልገው በሙሴ ላይ ማመጻቸውን፣ ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ ገብተው ማጠን መፈለጋቸውና ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው ያለጸጋቸው በፈጸሙት ተግባር ደቂቀ ቆሬ ተቀሥፈዋል፤ ዳታንና አቤሮንን መሬት አፏን ከፍታ ውጣቸዋለች እሳትም ከሰማይ ወርዳ ያጥኑ የነበሩትን ሁለት መቶ ኀምሳ ሰዎች በልታቸዋለች፡፡ (ዘፍ.፲፮፥፩-፴፭) የዘመናችንን ደቂቀ ቆሬዎች፣ ዳታንና አቤሮንን ግን እግዚአብሔር ምድር ከፍቶ እንዳያሰምጣቸው እሳት ከሰማይ ወርዶ እንዳያቃጥላቸው ታግሧቸዋል፡፡ ምክንያቱም ዓመቱም ዓመተ ምሕረት ዘመኑም ዘመነ ምሕረት ዘመነ ንስሓ ነውና፡፡ በዚህ ምክንያት ድፍረት ተሞልተው፣ ቤተ ጸሎት የተባለችውን የክርስቶስ ቤት ቤተ ምስያጥ ወፈያት ያደረጉ ደቂቀ ቆሬዎች ዛሬም በቤተ ክርስቲያን ለክብረ ክህነት ዝቅ ማለት ምክንያት ናቸው፡፡ ለ.ሳይማሩ የተሾሙ ካህናት መኖር፡- ክህነት ባለፉት ክፍሎች እንዳየነው ትልቅ ኃላፊነትን የሚጠይቅ ማዕረገ ሹመት ነው፡፡ ምዕራፍ ቁጥር ጠቅሶ ምሥጢር አደላድሎ፣ የራቀውን አቅርቦ፣ የረቀቀውን አጉልቶ፣ የጎደለውን ሞልቶ፣ በምሳሌ አዋዝቶ ማስተማርን፣ አስተምሮ ማሳመንን፣ አሳምኖ ማጥመቅን፣ አጥምቆ ማቁረብን፣ ናዝዞ መፍታትን፣ በአፍኣም በጽሑፍም መናፍቃንን ተከራክሮ መርታትን ምእመናንን መጠበቅን የሚጠይቅ ተግባር ነው፡፡ አንድ ካህን በውስጥ በአፍኣ ለሚያገለግለው አገልግሎት ጥበብ መንፈሳዊ ጥበብ ሥጋዊ ዕውቀትም ያለው መሆን አለበት፡፡ አሁን አሁን ዕውቀት አልባ የክህነት ሰዎች ትልቅ የዘመናችን የቤተ ክርስቲያን ተግዳሮት ሆነዋል፡፡ ‹‹ሕዝቤ ከዕውቀት ማጣት የተነሣ ጠፍቷል›› እንዳለ ነቢዩ ሆሴዕ ከዕውቀት ማጣት የተነሳ ለጠፋው በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ ላለው፣ በምንደኞችና በሐሰተኛ ነቢያት ለተወሰደው ምእመን ሃይማኖታዊ የዕውቀት ብርሃንን ሊያበራ የሚገባው ካህን እየጠፋ በመምጣቱና የዕውቀት ጾመኞች በመብዛታቸው ክብረ ክህነት ተፈትኗል የሚል አረዳድ አለን፡፡ (ሆሴ.፬፥፮) ካህን በእግዚአብሔርና በሕዝቡ መካል ሆኖ የሚያስታርቅ፣ ለማስተማር የተሾመ ነውና ሕዝቡን የሃይማኖትን ትምህርት ገልጦ በማስተማር በሕገ እግዚአብሔር በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እንዲኖሩ ማጽናት የሚችል የተማረ የተመራመረ መሆን አለበት፡፡ ምክንያቱም ‹‹ካህኑ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር መልክተኛ ነውና ከንፈሮቹ ዕውቀትን ይጠብቁ ዘንድ ይገባዋል፡፡ ሰዎችም ሕግን ከአፉ ይፈልጉ ዘንድ ይገባቸዋል›› ተብሏልና፡፡ (ሚል.፪፥፯) በፍትሐ ነገሥትም ካህን ወንጌልን በማስተማር ምእመናንን የሚረዳ፣ እውነተኛ ትምህርት በማስተማር ሰውን ማጽናናት የሚቻለው፣ ክደው ሊያስክዱት የሚተናኮሉትን የሚከራከራቸው መሆን አለበት የሚል ሥርዓት ተሠርቷል፡፡ (ፍት. መን. አንቀጽ ስድስት ክፍል አንድ) ምንም እንኳን መጻሕፍት ይህን ቢሉም በተጨባጭ አሁን ያለችው ቤተ ክርስቲያን ላይ የተሾሙና እየተሾሙ ያሉ አንዳንድ የክህነት ሰዎች (ከዲያቆን እስከ ኤጲስ ቆጶስ) ሐዋርያዊ ተልዕኳቸውን ለመወጣት የሚያስችል መንፈሳዊና ሥጋዊ ዕውቀት የጎደላቸው መሆን ግልጽ ተግዳሮት ከመሆኑም በላይ ሞኝ ባያፍር የሞኝ ዘመድ ያፍር እንዲሉ ምእመናንንና ቤተ ክርስቲያንን የሚያስነቅፍ ለክብረ ክህነት የማይመጥን ተግባር ያለ ዕውቀት እየፈጸሙ ለክብረ ክህነት መቀነስ ወይም መጓደል ምክንያት ሲሆኑ ይታያል፡፡ ሐ. የሥነ ምግባር ጉድለት መኖር፡- ቤተ ክርስቲያን አቻ የማይገኝላት ትልቋ የሥነ ምግባር ትምህርት ቤት ናት፡፡ የተጣመመ የሚቃናባት፣ የታመመ የሚፈወስባት፣ ቀማኛው መጽዋች፣ ንፉጉ ለጋስ፣ ርኩሱ ቅዱስ፣ ዘማዊው ድንግል ኃጥኡ ጻድቅ የሚሆንባት የሥርዓት፣ የምግባር ማዕከል ናት፡፡ ቤተ ክርስቲያን የሥነ ምግባር ትምህርት ቤት ስትባል መምህራኖቿ ደግሞ ባለክህነቶቹ ዲያቆናቱ፣ ካህናቱና ጳጳሳቱ መሆናቸው ግልጽ ነው፡፡ የሰብእና መገንቢያ፣ የምግባር የትሩፋት ማዕከል፣ የሞራል ከፍታ ማሳያ፣ የሕግና ሥርዓት ምንጭ የነበረች ቤተ ክርስቲያን አሁን ስለምን የሥርዓት አልበኞች፣ የጨካኞችና የመዝባሪዎች መነኻሪያ ተደርጋ እስክትታይ ወረደች? ብሎ መጠየቅ ይገባል፡፡ አሁንም መልሱ ከክብረ ክህነት መጓደል ያደርሰናል፡፡ ድፍረት፣ ትዕቢት፣ ፍቅረ ዝሙት፣ ፍቅረ ንዋይ፣ ፍቅረ ሥልጣን፣ ዘረኝነት፣ ጎሰኝነት ፖለቲካ የተሸከሙ፣ ለእግዚአብሔርም ለክፉ ሥጋዊ ፍላጎታቸውም ባሪያ ለመሆን የሚሞክሩ፣ በጥቅሉ የመንፈስ ፍሬዎች የማይታይባቸው ክፉ ሠራተኞች በክህነትና በካህናት ስም መዋቅሯ ውስጥ ስለተሰገሰጉ ነው፡፡ (ገላ.፭፥፳፪) ንጹሓን የሚሸማቀቁባት፣ ፍትህ ርትዕ የጠፋባት፣ መገፋፋትና መነቃቀር መገለጫዋ እስኪመስል፣ በፖለቲካ የሤራ አስተሳሰብ የሚመሩ ብዙ ሥርዓት አልበኞች መዋቅሯን ተብትበው በመያዛቸው ነው ብለን እናምናለን፡፡ በዚህ ምክንያት ክብረ ክህነት እየተናቀ፣ አላፊ አግዳሚው ባልሰላ ምላሱ፣ ባልተሞረደ ጥርሱ የሚያላምጣት ቤተ ክርስቲያን፣ የጸኑት ልጆቿ አንገት የሚደፉበት፣ ያልጸኑት ተስፋ ቆርጠው ወደ ሌላ እምነት ቤት የሚሄዱበት፣ ቤተ ክርስቲያን በዘርፈ ብዙ የመልካም አስተዳደር ችግር ውስጥ እንድትወድቅ ያደረገ የሥነ ምግባር ችግር አለ፡፡ ምንም እንኳን መጽሐፍ ‹‹ያለ ሥርዓት የሚሔዱትን ገሥጿቸው›› ቢልም ታላላቆቹ፣ አዋቂዎቹ በአርአያ ክህነት በግርማ ሽበት፣ በምግባር በትሩፋት የሚታወቁት ዝምታን በመምረጣቸው ቤተ ክርስቲያን በፈተና እንድትሞላ ክብረ ክህነት እንዲቃለል፣ ሥርዓት እንዲጠፋ ምክንያት ሆኗል ብለን እናምናለን፡፡ በጥቅሉ ክህነት በዘመናችን በብዙ ተግዳሮቶች ውስጥ ያለ፣ ልዩ ትኩረትን የሚሻ ዐቢይ ጉዳይ ነው፡፡ ያልተማሩ ከድንቁርናቸው፣ ሥርዓት አልበኞቹም ከክፉ መንገዳቸው እንዲላቀቁ፣ በቆሬ መንገድ የቆሙ ከመንገዳቸው እንዲመለሱ የሚያደርግም ኃይል ነው፡፡ ሆኖም ግን ለቤተ ክርስቲያን ክህነት ጸጋቸው፣ አገልግሎት መለያቸው፣ ሥርዓት መገለጫቸው ሆነው በአርአያ ክህነት የሚመላለሱ፣ በክብረ ክህነት የሚገለጹ የክህነት ሰዎችን ለማፍራት የሠራነው ሥራ የለም፡፡ በምድር ያለች ሰማያዊት የሆነች ቤተ ክርስቲያናችን የምትከፈትበት ቁልፍ ክህነት እንዲከበር ምን እናድርግ? ክብረ ክህነት ነገ ምን መልክ ይኑረው? ክብረ ክህነት እንዲመለስ፣ የቤተ ክርስቲያን የስሟ መጠሪያ የመልኳ መታያ ሆኖ እስከ ምጽአት እንዲዘልቅ ከማን ምን ይጠበቃል? የሚሉ ጉዳዮችን ‹‹ክብረ ክህነት ነገ›› በሚል ክፍል አምስትን እናቀርብላችኋለን፤ ቸር እንሰንብት!
نمایش همه...
42👍 26🙏 13
‹‹ነገን ዛሬ እንሥራ›› ክፍል አራት ክብረ ክህነት ዛሬ ክህነት የቤተ ክርስቲያን መመሥረቻና የመንግሥተ እግዚአብሔር መግቢያ ቁልፍ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን የተመሠረተችው ዐለት በተባለ ቅዱስ ጴጥሮስ ክህነት ላይ ነው፡፡ (ማቴ.፲፮፥፲፰) አንድ ቤት በአሸዋ እና በድቡሽት ላይ ቢሠራ ነፋስ ይገለብጠዋል፤ ጎርፍ ይጠራርገዋልና በማይናወጥ ጽኑ ዐለት ላይ ማነጽ የብልህ እና አዋቂ ግንበኛ ግብሩ በመሆኑ የቤተ ክርስቲያን ባለቤት ቤቱን በጴጥሮስ ዐለት ላይ መሥርቷት ዘመናትን ተሻግራ ለትውልድ ክብር ሆና ዘልቃለች፡፡ ለቤተ ክርስቲያን የውስጥ ጌጥ የውጭ ፈርጥ፣ የታች መሠረት የላይ ጉልላት ክህነት መሆኑን መረዳት አይከብድም፡፡ ’’ኢኀደጋ ለምድር እንበለ ካህናት ወዲያቆናት፣ እምቅድመ ዓለም ወእስከ ለዓለም፤ ቸሩ አምላካችን እግዚብአሔር ለዘለዓለም እስከ ለዓለም ምድርን ያለ ካህናትና ዲያቆናት አልተዋትም’’ እንዲል፤ (የኅዳር ጽዮን ዋዜማ) ቤተ ክርስቲያናችንን ያለ ክህነትና ካህናት ፈጽሞ ያልተዋት ቢሆንም አሁን ግን ክብረ ክህነት በዘመናችን በርካታ ተግዳሮቶች ተጋርጠውበታል፡፡ ሀ. ያልተካኑ ሰዎች በክህነት ቦታ መሰየማቸው፡- ቤተ ክርስቲያን ውስጥ አንዳንዶቹ ሳይጠሩ ተጠርተናል፣ ሳይመረጡ ተመርጠናል፣ ሳይካኑ ተክህነናል በማለት እንደ ደቂቀ ቆሬ፣ እንደ ደቂቀ ኤልያብ እንዲሁም የፋሌት ልጅ በድፍረት የተነሡ፣ መቅደሱን የሚያረክሱ፣ ከዕውቀትም ከሃይማኖትም ያነሱ ደፋሮች ቤተ ክርስቲያንን እግር ከወርች አስረው የያዙበት ዘመን በመሆኑ ክብረ ክህነት ችግር ላይ ወድቋል፡፡ (ዘኍ.፲፮፥፩-እስከ ፍጻሜ) በኦሪት ዘፍጥረት አንድ ታሪክ አለ፡፡ ሙሴ ሕዝበ እስራኤልን ባሕር ከፍሎ ጠላት አስጥሞ በኵረ ግብጽን አጥፍቶ በኵረ እስራኤልን ሁሉ ለራሱ በኩር ማድረጉ የተመዘገበ ታሪክ ነው፡፡(ዘፀ. ፲፪፥፩-፲፪)
نمایش همه...
👍 15 4
The opulent man is the resemblance of our Lord. The ardour are various grace we are endowed from God. The faithful servant who served in faithfulness are all the righteous, saints and holy people who lived on earth in service of the Lord by the ardour they are given with diligence. The lazy and wicked servant represents those sinners who did not profit by the ardour given to them. The Lord approaching in control of them is the truth about the Lord’s second coming for judgment in giving each of us the value of work. The Lord telling each servant to “Enter into the joy of your Lord” is the affirmation of righteous entrance to the Kingdom of Heaven. The order of punishment on the wicked and lazy servant to be “cast the unprofitable servant into the outer” is the indication of sinners to be thrown to hell. Dear Brethren, we then shall ask ourselves if we are like the faithful servants. We ought to understand the vitality of faithfulness and generosity in good service. Being faithful is the submission to God, obedience and living by His law without any qualm but with absolute faith which safeguards us from being falsifiers, thieves, adultery and heresies. It also enables us to serve with our skill, talents and bequest. He has taught us to praise Him with our words, sing in harp and mesenko for Him, prostrate by our knees and love Him with all our heart. He has shown us to generously, in goodness and kindness share our possession to others. If we have one bread, to give the half to others; share our cloth or shoe if we have extra; to feed and water the hunger and thirsted from our buffet; sympathize those in tribulation and misery as well as to take care the sick people. Then brethren, as a good children of God, we shall become faithful and generous servant! May God’s mercy and benevolence be with us, Amen!
نمایش همه...
🙏 5 3
Who is faithful servant? Foremost, service is bestowed for the Almighty Lord; God, Who is the creator of all. Primarily who served Him by praising “Holy Holy Holy” were Angles in the heavens. Then followed the first man kind Adam, where he lived in praising and prayer in heaven. After his defying the Lord’s command though, Adam has lived in misery and chaos tortured and lured by the devil’s scam. Onwards, enemy Satan has been tempting humans into his trap, dragging us out of the true and righteous path for failure. (Genesis 1:8, Book of Aximaros the sixth day) This is certainly tragic and sorrowful to acknowledge, but our Lord and Savior Jesus Christ has told Saint Apostles “In the world you will have tribulation; but be of good cheer, I have overcome the world.” Even if our enemy brings tribulations, misery and anguish upon human race in failing us, if we are to endure all the suffering and pass all the tribulations in good service, we will enter in God’s Kingdom. (John 16:33) A good service is what we serve by our personhood, goodness, sincerity, humility, knowledge and energy in prayer, fasting, alms giving, deeds of benevolence and love. Humans in addition to praising the Lord, needs to live daily in trepidation of God to serve Him. A human with trepidation of God, afar from harm and sin and become good person. He/she will also have a social life filled with sincerity and humility; Does not also desists from doing righteous for others. Moreover, with the spiritual and carnal knowledge as well as the energy, serve the Lord. This is known as a faithful and generous servant. Let us mention one story in scripted in the Holy Bible, in Matthew’s gospel (25:14-30) “For the kingdom of heaven is like a man traveling to a far country, who called his own servants and delivered his goods to them. And to one he gave five talents, to another two, and to another one, to each according to his own ability; and immediately he went on a journey. Then he who had received the five talents went and traded with them, and made another five talents. And likewise he who had received two gained two more also. But he who had received one went and dug in the ground, and hid his lord’s money. After a long time, the lord of those servants came and settled accounts with them. “So he who had received five talents came and brought five other talents, saying, ‘Lord, you delivered to me five talents; look, I have gained five more talents besides them.’ His lord said to him, ‘Well done, good and faithful servant; you were faithful over a few things, I will make you ruler over many things. Enter into the joy of your lord.’ He also who had received two talents came and said, ‘Lord, you delivered to me two talents; look, I have gained two more talents besides them.’ His lord said to him, ‘Well done, good and faithful servant; you have been faithful over a few things, I will make you ruler over many things. Enter into the joy of your lord.’ “Then he who had received the one talent came and said, ‘Lord, I knew you to be a hard man, reaping where you have not sown, and gathering where you have not scattered seed. And I was afraid, and went and hid your talent in the ground. Look, there you have what is yours.’ “But his lord answered and said to him, ‘You wicked and lazy servant, you knew that I reap where I have not sown, and gather where I have not scattered seed. So you ought to have deposited my money with the bankers, and at my coming I would have received back my own with interest. So take the talent from him, and give it to him who has ten talents. ‘For to everyone who has, more will be given, and he will have abundance; but from him who does not have, even what he has will be taken away. And cast the unprofitable servant into the outer.”
نمایش همه...
👍 4 2
  ይህ በእርግጥ አስከፊና አሳዛኝ ቢሆንም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱሳን ሐዋርያት  ‹‹በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ›› በማለት እንደ ነገራቸው ምንም እንኳን ጠላታችን መከራ አጽንቶና ተስፋ አስቆርጦ ብኩንና ከንቱ ሊያደርገን ቢጥርም መከራውን አልፈን፣ ሥቃያችንን ተቋቁመንና ችግራችን ተወጥተን በመልካም አገልግሎት ወደ አምላካችን መንግሥት መግባት ይቻለናል፡፡ (ዮሐ.፲፮፥፴፫)   መልካም አገልግሎት ለእግዚአብሔር አምላክ በሰውነታችን በበጎነታችን፣ በቅንነታችን፣ በትሕትናችን፣ በዕውቀታችንና በጉልበታችን የምናቅርበው የጸሎት፣ የጾም፣ የምጽዋት፣ የትሩፋትና የፍቅር አገልግሎት ነው፡፡ አምላካችንን ከማመስገን በተጨማሪ ዘወትር እርሱን በመፍራት በዕለት ኑሮአችን ልናስበውና ልናገለግለው ይገባል፡፡ ፈሪሃ እግዚአብሔር ያለው ሰው በምንም ዓይነት ሁኔታ ውስት ቢሆን ክፋትና ኃጢአት ከመሥራት ርቆ ይኖራልና፡፡ በቅንነትና በትሕትና የተሞላ የማኅበራዊ ሕይወትም ይኖረዋልና፡፡ ለሌሎች ሰዎችም መልካም ከማድረግ አይቦዝንም፡፡ ከዚህም አልፎ ተርፎ ባካበተው የመንፈሳዊ እና ዓለማዊ ዕውቀት እንዲሁም ባለው ጉልበት አምላኩን ዘወትር ያገለግላል፤ ይህም ተግባሩ ለጌታው የታመነ ታማኝና ቸር አገልጋይ ያሰኘዋል፡፡     በመጽሐፍ ቅዱስ የሐዲስ ኪዳን ክፍል ወንጌል ላይ ቅዱስ ማቴዎስ የጻፈውን አንድ ታሪክ እናንሣ፤ ‹‹አንድ ወደ ሌላ አገር የሚሄድ ባለጸጋ ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንደ ሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና፤  ለእያንዳንዱ እንደ ዓቅሙ ለአንዱ አምስት መክሊት፣ ለአንዱ ሁለት፣ ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ አገር ወዲያው ሄደ። አምስት መክሊትም የተቀበለው ሄዶ ነገደበት ሌላም አምስት አተረፈ፤ እንዲሁም ሁለት የተቀበለው ሌላ ሁለት አተረፈ። አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድር ቈፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ።››   ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው። አምስት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምስት መክሊት አስረክቦ “ጌታ ሆይ፥ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ አምስት መክሊት አተረፍሁበት” አለ። ጌታውም “መልካም፥ አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” አለው።   ሁለት መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ “ጌታ ሆይ፥ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍሁበት” አለ። ጌታውም “መልካም፥ አንተ በጎ፥ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፥ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” አለው።   አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ “ጌታ ሆይ፥ ካልዘራህበት የምታጭድ፣ ካልበተንህበትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤ ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ እነሆ፥ መክሊትህ አለህ” አለ። ጌታውም መልሶ እንዲህ አለው፦ “አንተ ክፉና ሃኬተኛ ባሪያ፥ ካልዘራሁበት እንዳጭድ ካልበተንሁበትም እንድሰበስብ ታውቃለህን? ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር፤ እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር። ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት፤ ዐሥር መክሊትም ላለው ስጡት፤ ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል፤ ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳን ይወሰድበታል። የማይጠቅመውንም ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።›› (ማቴ.፳፭፥፲፬-፴)   ባለ ጸጋ የተባለው ጌታችን ነው፡፡ መክሊት የተባለው ደግሞ ከአምላካችን የተጠን የተለያዩ የአገልግሎት ጸጋዎች ናቸው፡፡ በታማኝነት ያገለገሉት ሰዎች ምሳሌ በምድራዊ ሕይወታቸው በተሰጣቸው ጸጋ በትጋት አምላካቸውን አገልግለው በመልካም ዕረፍት ገነት የገቡት ቅዱሳን ሰዎች ናቸው፤ መክሊቱን የቀበረው ሰነፍ አገልጋይ ደግሞ በተሰጣቸው ጸጋ በታማኝነት ማገልገል  ሲገባቸው ያላገለገሉ ሰዎች ምሳሌ ነው፡፡   ጌታቸው ሊቆጣጠራቸው የመምጣቱ ነገር ጌታችን በዕለተ ምጽአት ለፍርድ ሲመጣ ለሁሉም በሠራው ሥራ መጠን ዋጋ ለመስጠት እንደሚመጣ የሚያመለክት ነው፡፡ ያገለገሉትን ታማኝ አገልጋየችም ለእያንዳንዱ  ‹‹ወደ ጌታህ ደስታ ግባ!››  ማለቱ ታማኝ አገልጋዮች መንግሥተ ሰማያትን እንደሚወርሱ የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ሰነፉ አገልጋይ ወደ ጨለማና ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት ቦታ መወርወሩም ኀጥአን ወደ ገሃነመ እሳት መጣላቸውን የሚያሳይ ነው፡፡   ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ‹‹ጌታውን ያስደሰተው አገልጋይ ታማኝና ቸር አገልጋይ ነው›› በማለት የተናገረው ይህን የወንጌል እውነት የሚገልጽ ነው፡፡ ታማኝነትና ቸርነት ለአገልግሎታችን እጅጉን አስፈላጊዎች ናቸው፡፡ ታማኝ መሆን ያለ ጥርጥርና በፍጹም እውነት ለአምላካችን መገዛት፣ መታዘዝና መኖር እንዲሁም በሕጉ መኖር ነው፡፡ ይህም ለእርሱ ታምነን ያለ ሐሰት፣ ያለ ስርቆት፣ ያለ አመንዝራነት እና ያለ ክህደት ወዘተ. እንድንኖር ይረዳናል፡፡ በተሰጠንም ክሂሎት፣ ተሰጥኦና ትሩፋት ማገልገል ያስችለናል፡፡ በአንደበታችን እንድናመሰግናው፣ በእጆቻችን አጨብጭበን፣ በጣቶቻችን በገና ደርድረንና መሰንቆ መትተን እንድንዘምርለት፣ በጉልበታችን እንድንሰግድለት በልባችን እንድናፈቅረው አስተምሮናል፡፡      ቸር በመሆን ለሌሎች በለጋስነት ካለን ነገር በመስጠትና በማካፈል መኖርን አሳይቶናል፡፡ አንድ ዳቦ ያለው ግማሹን ለሌላው እንዲያካፈል፣ ሁለት ልብስ ወይም ጫማ ያለው ለሌለው እንዲሰጥ፣ ከማዕዳችን ለተራቡ እንድናበላ፣ ከማድጋችን ለተጠሙ እንድናጠጣ፣ ለተቸገሩትና ላዘኑት ቸርነት በማድረግ እንድናስተዛዝን፣ የታመሙትን እንድናስታምም የአምላካችን ቅዱስ ቃል ያዘናል፡፡ እኛም እንደ መልካም ልጆቹ ለእርሱ በመታዘዝ ታማኝና ቸር አገልጋይ እንሁን!   የአምላካችን እግዚአብሔር ቸርነትና ረድኤት አይለየን፤ አሜን!            
نمایش همه...
👍 58 25🙏 16
‹‹ጌታውን ያስደሰተው አገልጋይ ታማኝና ቸር አገልጋይ ነው››  ቅዱስ  ያሬድ          ሚያዚያ ፬፤፳፻፲፮ ዓመተ ምሕረት   ከማንም አስቀድሞ አገልግሎት ለአምላካችን እግዚአብሔር ይገባል፤ በጥንተ ተፈጥሮ በመጀመሪያው ቀን የተፈጠሩት መላእክት ፈጣሪያቸውን ዘወትር ያለማቋረጥ ‹‹ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ›› እያሉ እንደሚያመሰግኑት ሊቁ ቅዱስ ኤጲፋንዮስ በመጽሐፈ አክሲማሮስ ገልጾልናል፡፡ (አክሲማሮስ ዘእሑድ) በዕለተ ዓርብ ሰው ሲፈጠር እንደ መላእክቱ የፈጠረውን ጌታውን እንዲያመሰግን፣ እንዲያገለግል እንዲሁም ስሙን እንዲቀድስና ክቡርን እንዲወርስ በመሆኑም የቀደመ ሰው አዳምም አምላኩን እያመሰገነና በገነትም በጸሎት እየተጋ ኖሯል፡፡         በመጽሐፍ ቅዱስና በሌሎች ቅዱሳት መጻሕፍት ተመዝግቦ እንደምናገኘው ጥንተ ጠላት ዲያብሎስ አምላኩን ለማመስገን ባለመፍቀዱ ተረግሞ ወደ ምድር ከተጣለ በኋላ የሰውን ዘር በተለያዩ መንገዶች በማሳት፣ ከቀናው መንገድና ከጽድቁ ጎዳና በማስወጣት ፈጣሪያቸውን እንዳያገለግሉ ያደርጋል፡፡ (ዘፍ.፩-፰፣ አክሲማሮስ ዘዓርብ)   
نمایش همه...
👍 22🙏 2
👍 32🥰 13 8🤔 3