ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል
📈 Аналитический обзор Telegram-канала ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል
Канал ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል (@mkpublicrelation) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 50 769 подписчиков, занимая 1 096 место в категории Религия и духовность и 628 место в регионе Эфиопия.
📊 Показатели аудитории и динамика
С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 50 769 подписчиков.
Согласно последним данным от 13 июня, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 747, а за последние 24 часа — 46, при этом общий охват остаётся высоким.
- Статус верификации: Не верифицирован
- Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 15.83%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 9.56% реакций от общего числа подписчиков.
- Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 8 033 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 4 853 просмотров.
- Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 59.
📝 Описание и контентная политика
Описание канала не предоставлено.
Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 14 июня, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.
Загрузка данных...
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 14 июня | +26 | |||
| 13 июня | +47 | |||
| 12 июня | +30 | |||
| 11 июня | +31 | |||
| 10 июня | +32 | |||
| 09 июня | +15 | |||
| 08 июня | +15 | |||
| 07 июня | +15 | |||
| 06 июня | +33 | |||
| 05 июня | +17 | |||
| 04 июня | +14 | |||
| 03 июня | +21 | |||
| 02 июня | +24 | |||
| 01 июня | +17 |
| 2 | Нет текста... | 3 242 |
| 3 | በማኅበረ ቅዱሳን የቡርጂ ወረዳ ማእከል በዳሻቴ ቋንቋ የተተረጎሙ 62 መዝሙራትን አስመረቀ
ሰኔ ፭/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን ዲላ ማእከል የቡርጂ ወረዳ ማእከል ስብከተ ወንጌልና ዜማ አገልግሎት ዋና ክፍል አስተባባሪነት ከአማርኛ ወደ ዳሻቴ ቋንቋ ተተርጉመው የተዘጋጁ 62 መዝሙራት በቡርጂ ዞን በሶያማ ደብረ ሣህል ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አስመርቋል።
በምረቃ መርሐ ግብሩ የወረዳ ቤተ ክህነት የሥራ ኃላፊዎች፣ መምህራንና፣ ዘማሪያን ፣ የደብሩ ካህናት እና ሰበካ ጉባኤ አባላት እንዲሁም የሰ/ት/ቤት አባላትና ምእመናን ተገኝተዋል።
በጉባኤው በዋና ማእከል ደረጃ ተመርጠው ከተሰጡ 120 መዝሙራት መካከል ለ8 ወራት የትርጉምና የዜማ ጥናት ሥራ ተጠናቆ ለኅትመት የበቁትን 62 መዝሙራት በዜማ ወጥበብ ስቱዲዮ ቀረጻና ቅንብር ሥራ በማጠናቀቅ ለምረቃ የተዘጋጁ መሆኑን በቀረበው ሪፖርት የተገለጸ ሲሆን የትርጉም ሥራው ዋና ዓላማ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ምእመናን በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው እያደመጡ እግዚአብሔርን እንዲያመሰግኑበትና የወንጌል አገልግሎት ይበልጥ እንዲስፋፋ ለማድረግ ነው ተብሏል።
በዕለቱ በመርሐ ግብሩ የተገኙ የወረዳ ቤተ ክህነቱ የሥራ ኃላፊዎች እንደገለጹት በአካባቢያችን ስብከተ ወንጌልን ምእመናን በሚሰሙት ቋንቋ ተደራሽ ለማድረግ የሚያግዝ በመሆኑ ማኅበሩን ያመሰገኑ ሲሆን ሁሉም ደብራት፣ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት፣ ሰበካ ጉባኤና ሰ/ት/ቤቶች መዝሙሩን በማስጠናትና ተደራሽ በማድረግ ምእመኑ ሃይማኖቱን እንዲያውቅ እንድታደርጉ በማለት አሳስበዋል።
በመጨረሻም በአባቶች ቡራኬ የመዝሙር ምረቃው የተከናወነ ሲሆን በዚህ ሥራ ላይ ከጅምሩ እስከ ፍጻሜ በመሳተፍ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላት ምስጋና በማቅረብ የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል። | 6 027 |
| 4 | በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት አባታዊ መልእክት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በተከሰተው ችግር ጥልቅ ኃዘን የተሰማት መሆኑን ገልጸው ምእመናን በሃይማኖታቸው እንዲጸኑ፣በፈተና ሁሉ እንዲታገሱ አደራ ካሉ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ ኃዘንተኞችን እንዲያጽናና ከዳግም ኃዘን እንዲሰውርልን ዘወትር እንጸልያለን በማለት ቃለ ምዕዳንና ቃለ ቡራኬ ሰጥተዋል።
በመጨረሻም ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ለተፈናቀሉ ወገኖች የተዘጋጀውን እርዳታ ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ለብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ አስረክበዋል።
በዕለቱ የአቦምሳ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎችና አባ ገዳዎች ተገኝተዋል።
መረጃው የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው። | 5 267 |
| 5 | በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ ልዑክ አርሲ-አቦምሳ ወረዳ ተገኝቶ ምዕመናንን አጽናና።
ሰኔ ፬/፳፻፲፰ ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የተካሄደውን ጥቃት ተከትሎ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተ ክርስቲያናችን ልዑክ በሥፍራው በመገኘት ተጎጂዎችን እንዲያጽናና ጊዜያዊ እርዳታም እንዲያደርግ ያስተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ዛሬ ማለዳ ወደ አርሲ ዞን አቦምሳ ወረዳ በመጓዝ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች አጽናንቷል፤ ጊዜያዊ እርዳታም አበርክቷል።
በአቦምሳ ወረዳ የትንሣኤ ብርሃን ደብረ ገነት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በመገኘት ተጎጂ ኦርቶዶክሳውያንን ያጽናኑት
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት አባታዊ መልእክት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በኦርቶዶክሳውያን ልጆቿ ላይ በደረሰው ጉዳት እጅግ በጣም ማዘኗን ገልጸው እግዚአብሔር አምላክ ለሞቱት ወገኖቻችን መንግስተ ሰማያትን እንዲያወርስልን፣ለቤተሰቦቻቸው መጽናናት እንዲያድልልን የዘወትር ጸሎታችን ነው።በርቱ፣ጠንክሩ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን ብለዋል።
አያይዘውም ቋሚ ሲኖዶስ በአካል ተገኝቶ እናንተን ለማጽናናትና ጊዜያዊ ድጋፍ ለማድረግ በመካከላችሁ ተገኝተናል ያሉት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ችግሩን ከመሰረቱ ለመፍታትና የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን ለመሥራት የሚያስችል ዐቢይ ኮሚቴ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ተሰይሞ ወደ ሥራ ገብቷል ብለዋል። | 5 190 |
| 6 | ✝️የጾም ቁርሳችን፣
ለወገኖቻችን✝️ +++
በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች እያጋጠሙ ባሉ ማኅበራዊ ቀውሶች( ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች፣ መፈናቀልና ጦርነት ) ብዙ ወገኖቻችን ለከፋ ችግር ተጋልጠዋል።
እርስዎም ለእነዚህ ወገኖች የጾም ቁርስዎን በመለገስ ቸርነትን ያድርጉ!
ድጋፍ ለማድረግ :-
#በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
1. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
2. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
3. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
4. በወጋገን ባንክ - 0837331610101
5. በወገን ፈንድ ፡- https://Www.wegenfund.com/mknu መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት | 5 166 |
| 7 | Нет текста... | 5 711 |
| 8 | በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል 29 ለሚሆኑ የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች የዲቁና ማዕረግ ማሰጠቱን ገለጸ
ሰኔ ፬/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ዋና ክፍል የአብነት ትምህርት ሲያስተምራቸው የነበሩ ከ10 ግቢ ጉባኤያት ለተውጣጡ ተማሪዎች ኅዳር 3/2018 ዓ.ም የካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ከብፁዕ አቡነ መቃርዮስ ዲቁና መቀበላቸውን የአዲስ አበባ ማእከል ግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ዋና ክፍል የትምህርት፣ አብነትና አቅም ማጎልበቻ ክፍል ኃላፊ ወ/ሪት አበባ አማረ ገልጸዋል።
ተማሪዎቹ ከዘመናዊ ትምህርት ጎን ለጎን የአብነት ትምህርትን ሲማሩ የቆዩ ሲሆን በክህነት አገልግሎት እንዲሳተፉ ለማድረግ እና ዘመኑን የዋጁ ካህናትን ለማፍራት ተማሪዎችን የዲቁና ማዕረገ ክህነት እንዲቀበሉ አድርጓል፡፡
በዕለቱም ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ ዲያቆና የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሥርዓት ጠብቀው፣ ቤተ ክርስቲያን ያለባትን ችግር በመረዳትና ማኅበሩ ያመቻቸላችሁን እድል ልታመሰግኑ ይገባል በማለት የተናገሩ ሲሆን ለወደፊት ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ማገልገል አለባችሁ በማለት የአደራ ቃላቸውን ሰጥተዋል።
የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች የአብነት ት/ት እንዲማሩ እና ክህነት እንዲቀበሉ መደረጉ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚማሩ ተማሪዎች ቤተ ክርስቲያንን እና ሀገራቸውን በአርአያነት በማገልገል ክርስቲያናዊ የዜግነት ግዴታቸውን እንዲወጡ ያስችላል ተብሏል፡፡
መረጃው የማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ሚዲያ ነው። | 1 588 |
| 9 | የዲያቆናት ጉባኤ በአትላንታ ጆርጂያ ተካሄደ
ሰኔ ፫/፳፻፲፰ ዓ.ም
በአትላንታ ከተማ አካባቢ ከሚገኙ ስምንት አብያተ ክርስቲያናት ለተውጣጡ ለ43 ዲያቆናት ለሁለት ቀናት የቆየ ሥልጠና በአትላንታ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን አዳራሽ ተካሄዷል።
ሥልጠናው በቀሲስ ዶክተር መብራቱ ኪሮስ የተሰጠ ሲሆን ኦርቶዶክሳዊ ቅዳሴ ከሌሎች የሚለይበት፣ ያለውን ክብር እና ዋጋ በስፋት የተዳሰሰበትና እንደ አገልጋይ ዲያቆን በዚህ የቅዳሴ አገልግሎት ውስጥ የሚፈጸሙ ምስጢራትን ከሚዜመው ዜማና ከሚደረጉት ኩነቶች ጋር እያገናዘቡና እያስማሙ መስጠታቸው ተገልጿል።
በሥልጠናው የቅዳሴ ክፍሎችን እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን የልጅነት ጥምቀት ቢፈጸም፣ ሥርዓተ ተክሊል ቢደረግ፣ምሥጢረ ንስሐ ሲፈጸምና ምሥጢረ ክህነት ሲከናወን ማሰርያና መደምደሚያ የሆነው በዚህ የቅዳሴ አገልግሎት የሚፈጸመው ቅዱስ ቁርባን እንደሆነ በሰፊው ያብራሩ ሲሆን ሠልጣኝ ዲያቆናትም ይህንን በመረዳት ለክህነታቸው ከፍተኛ ክብር እንዲሰጡና እንዲጠብቁት በጸሎት፣ እግዚአብሔርን በመፍራት፣ በትሕትና ሆነው አገልግሎቱን እንዲፈጽሙ አስፍተው አስተምረዋል።
በጉባኤው የውይይት፣ የጥያቄና መልስ መርሐ ግብር የተከናወነ ሲሆን በዚህም በሥልጠናው የተሳተፉ ሠልጣኝ ዲያቆናትም በመርሐ ግብሩ ብዙ ቁም ነገሮችን እንደተረዱና የተቀበሉትም ክህነት የከበረ ዋጋ ያለው መሆኑን ከሰጡት አስተያየት ለመረዳት ተችሏል።
ዘገባው የአትላንታ ንኡስ ማእከል ሚድያ ክፍል ነው። | 7 058 |
| 10 | በማኅበረ ቅዱሳን የጅማ ማእከል ዝክረ ቅዱስ ያሬድ መርሐ ግብር አከናወነ
ሰኔ ፫/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የጅማ ማእከል "ሕያው ዜማከ ወሕያው ድርሳንከ (ዜማህ ሕያው ነው ድርሰትህም ሕያው ነው)" በሚል መሪ ቃል የዝክረ ቅዱስ ያሬድ መርሐ ግብር አከናውኗል።
በመርሐ ግብሩም በቅዱስ ያሬድና አበርክቶው ዙሪያ በመ/ር ጌቱ ምትኩ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን፤ ሥነ-ጽሑፍና ዝማሬ በማእከሉ መዘምራን፤ የበገና መዝሙር በተመራቂዎች፤ እንዲሁም በወቅታዊ የኦርቶዶክሳዊ መዝሙር አገልግሎት በጎ እድሎች፣ ተግዳሮቶችና የመፍትሔ ሐሳቦች ዙሪያ ዳሰሳዊ ጥናት ቀርቧል።
በማያያዝ በዕለቱ የበገና ሠልጣኞቹንም ለ5ኛ ዙር አስመርቋል።
ማእከሉ ባለፉት ዓመታት ከ120 በላይ ሠልጣኞችን ያስመረቀ ሲሆን በዘንድሮ በጅማ ከተማ ለ5ኛ ዙር እና በሊሙ ገነት ወረዳ ማእከል ለ1ኛ ዙር አሠልጥኖ ማስመረቁም ተገልጿል። | 6 428 |
| 11 | ✝️የጾም ቁርሳችን፣
ለወገኖቻችን✝️ +++
በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች እያጋጠሙ ባሉ ማኅበራዊ ቀውሶች( ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች፣ መፈናቀልና ጦርነት ) ብዙ ወገኖቻችን ለከፋ ችግር ተጋልጠዋል።
እርስዎም ለእነዚህ ወገኖች የጾም ቁርስዎን በመለገስ ቸርነትን ያድርጉ!
ድጋፍ ለማድረግ :-
#በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
1. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
2. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
3. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
4. በወጋገን ባንክ - 0837331610101
5. በአዋሽ ባንክ 01329817420400
6. በወገን ፈንድ ፡- https://Www.wegenfund.com/mknu መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ለበለጠ መረጃ
09 43 00 04 03
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት | 6 968 |
| 12 | ብሔራዊ ፈተና ለሚወስዱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሥነ ልቡና ሥልጠና ተሰጠ
ሰኔ ፪/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል የደቡብ ማስተባበሪያ ሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ አገልግሎት ክፍል ከአምስት ግንኙነት ማእከላት ጋር በመተባበር የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለሚወስዱ ተፈታኝ ተማሪዎች ሥልጠና መሰጠቱን ማስተባበሪያው አስታውቋል።
በዕለቱም በቀሲስ ኃይለ መስቀል አማካኝነት የሥነ-ልቡና ሥልጠና የተሰጠ ሲሆን በሥልጠናው ተማሪዎች ከፈተና በፊት፣ በፈተና ጊዜ እንዲሁም ከፈተና በኋላ ማድረግ ስላለባቸው ዝግጅት ሰፊ ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን ተማሪዎች ለፈተና ሲቀርቡ በተረጋጋ መንፈስ፣ በልበ ሙሉነት መሆን እንዳለበት ተመላክቷል ።
በመጨረሻም ተማሪዎች የቤተ ክርስቲያን ተረካቢ እና ተስፋዎች መሆናቸውን አውቀው በትምህርታቸው ውጤታማ እንዲሆኑ በማሳሰብ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል ።
መረጃው ፦በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ሚዲያ ነው | 6 426 |
| 13 | ብሔራዊ ፈተና ለሚወስዱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሥነ ልቡና ሥልጠና ተሰጠ
ሰኔ ፪/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል የደቡብ ማስተባበሪያ ሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ አገልግሎት ክፍል ከአምስት ግንኙነት ማእከላት ጋር በመተባበር የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለሚወስዱ ተፈታኝ ተማሪዎች ሥልጠና መሰጠቱን ማስተባበሪያው አስታውቋል።
በዕለቱም በቀሲስ ኃይለ መስቀል አማካኝነት የሥነ-ልቡና ሥልጠና የተሰጠ ሲሆን በሥልጠናው ተማሪዎች ከፈተና በፊት፣ በፈተና ጊዜ እንዲሁም ከፈተና በኋላ ማድረግ ስላለባቸው ዝግጅት ሰፊ ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን ተማሪዎች ለፈተና ሲቀርቡ በተረጋጋ መንፈስ፣ በልበ ሙሉነት መሆን እንዳለበት ተመላክቷል ።
በመጨረሻም ተማሪዎች የቤተ ክርስቲያን ተረካቢ እና ተስፋዎች መሆናቸውን አውቀው በትምህርታቸው ውጤታማ እንዲሆኑ በማሳሰብ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል ።
መረጃው ፦በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ሚዲያ ነው | 1 |
| 14 | ✝️የጾም ቁርሳችን፣
ለወገኖቻችን✝️ +++
በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች እያጋጠሙ ባሉ ማኅበራዊ ቀውሶች( ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች፣ መፈናቀልና ጦርነት ) ብዙ ወገኖቻችን ለከፋ ችግር ተጋልጠዋል።
እርስዎም ለእነዚህ ወገኖች የጾም ቁርስዎን በመለገስ ቸርነትን ያድርጉ!
ድጋፍ ለማድረግ :-
#በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
1. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
2. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
3. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
4. በወጋገን ባንክ - 0837331610101
5. በአዋሽ ባንክ 01329817420400
6. በወገን ፈንድ ፡- https://Www.wegenfund.com/mknu መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ለበለጠ መረጃ
09 43 00 04 03
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት | 11 951 |
| 15 | የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለሚወስዱ ተማሪዎች የሥነ ልቡና ዝግጅት ሥልጠና መሰጠቱ ተገለጸ
ሰኔ ፩/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን ሥር የሚገኙ ማእከላትና ወረዳ ማእከላት ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ጋር በመተባበር የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለሚወስዱ ተማሪዎች የሥነ ልቡና ዝግጅት ሥልጠና መሰጠቱ ተገልጿል።
ሥልጠናው ተማሪዎች የሚፈተኑትን ብሔራዊ ፈተና በልበ ሙሉነት፣ በተረጋጋ መንፈስ፣ በሥነ-ልቡና ዝግጁነት መወጣት እንዲችሉ እና መንፈሳዊ ጥንካሬን እንዲሰንቁ እንዲሁም ተማሪዎች በፈተና ወቅት የሚመጣን ጭንቀት ተቋቁመው ማለፍ እንዲችሉና በአግባቡ ጊዜያቸውን መጠቀም እንዲችሉ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተጠቁሟል።
በዚህም በጅማ፣ በአርባ ምንጭ፣ በሐረማያ፣ በዱራሜ፣ በሑመራ፣ በሰቆጣ፣ በደሴ፣ በቦንጋና በሌሎች ማእከላት እንዲሁም በወረዳ ማእከላት ሥልጠናው ተሰጥቷል። | 8 875 |
| 16 | Нет текста... | 7 336 |
| 17 | Нет текста... | 7 599 |
| 18 | የምሥራቅ አርሲ ጥቃትና የፍትሕ ጥያቄ | እውነታውና የንጹሐን ድምፅ!
የቪዲዮውን ሊንክ በመጫን ሙሉ ታሪኩን አሁኑኑ ይመልከቱ፦
https://youtu.be/BChuKE7nWSg
ላይክ (Like) በማድረግ ይደግፉን፣
ለሌሎችም እንዲደርስና ግንዛቤ እንዲፈጠር ሼር (Share) ያድርጉት፣
ያላችሁን ማንኛውንም አስተያየት በኮሜንት (Comment) ያጋሩን።
አብራችሁን ስላላችሁ ከልብ እናመሰግናለን! | 12 555 |
| 19 | "የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሐዋርየዊ ተልእኮና ዓላማ ለማሳካት አገልግሎትን በዕቅድ መፈጸም ይገባል" ሲሉ መምህር ዋሲሁን በላይ ገለጹ
ግንቦት ፴/፳፻፲፰ ዓ.ም
የአኃት አብያተ ክርክቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት ተካሄዷል።
በጉባኤው የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ሥራ አስፈጻሚ መ/ር ዋሲሁን በላይ የእንኳን ደኅና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በንግግራቸው በየትኛውም የቤተ ክርስቲያን መዋቅርና ማኅበራችንን ጨምሮ አገልግሎትን በዕቅድ መፈጸም የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዓላማን ለማሳካት ወሳኝ ገዳዮች መካከል አኔዱ ነው ብለዋል፡፡
በተለይም ከዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ ከአኃት አብያተ ክርስቲያናት የምንማራቸው ትምህርቶች አሉ ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው አክለውም የቤተ ክርስቲያናችን መሪ ዕቅድ ተግባራዊ እንዲሆን የሁሉ አካላት ጥረት እጅግ አስፈላጊ ነው ብለዋል።
በውይይቱ ሦስት ጥናታዊ ጽሑፎች የቀረቡ ሲሆን የአኃት አብያተ ክርስቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ በመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል በመንበረ ፓትርያሪክ ጥናት፣ ምርምርና መረጃ መምሪያ ኃላፊ እና የቅ/ሲኖዶስ ኮምዪኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ እንዲሁም የሊቃውንት ጉባኤ አባል የቀረበ ሲሆን በ መ/ር ባሕረ ጥበባት ሙጨ የኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት፣ ትግበራ፣ ክትትልና ግምገማ ከትናንት እስከ ዛሬ እንዲሁም በማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር በሪሁን ተፈራ የቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት ትግበራና የማኅበረ ቅዱሳን ድርሻ ላይ ያተኮረ ጥናት ቀርቦ በቀረቡት ጽሑፎች ላይ ውይይት ተደርጓል። | 8 996 |
| 20 | "የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሐዋርየዊ ተልእኮና ዓላማ ለማሳካት አገልግሎትን በዕቅድ መፈጸም ይገባል" ሲሉ መምህር ዋሲሁን በላይ ገለጹ
ግንቦት ፴/፳፻፲፰ ዓ.ም
የአኃት አብያተ ክርክቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት ተካሄዷል።
በጉባኤው የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ሥራ አስፈጻሚ መ/ር ዋሲሁን በላይ የእንኳን ደኅና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በንግግራቸው በየትኛውም የቤተ ክርስቲያን መዋቅርና ማኅበራችንን ጨምሮ አገልግሎትን በዕቅድ መፈጸም የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዓላማን ለማሳካት ወሳኝ ገዳዮች መካከል አኔዱ ነው ብለዋል፡፡
በተለይም ከዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ ከአኃት አብያተ ክርስቲያናት የምንማራቸው ትምህርቶች አሉ ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው አክለውም የቤተ ክርስቲያናችን መሪ ዕቅድ ተግባራዊ እንዲሆን የሁሉ አካላት ጥረት እጅግ አስፈላጊ ነው ብለዋል።
በውይይቱ ሦስት ጥናታዊ ጽሑፎች የቀረቡ ሲሆን የአኃት አብያተ ክርስቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ በመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል በመንበረ ፓትርያሪክ ጥናት፣ ምርምርና መረጃ መምሪያ ኃላፊ እና የቅ/ሲኖዶስ ኮምዪኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ እንዲሁም የሊቃውንት ጉባኤ አባል የቀረበ ሲሆን በ መ/ር ባሕረ ጥበባት ሙጨ የኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት፣ ትግበራ፣ ክትትልና ግምገማ ከትናንት እስከ ዛሬ እንዲሁም በማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር በሪሁን ተፈራ የቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት ትግበራና የማኅበረ ቅዱሳን ድርሻ ላይ ያተኮረ ጥናት ቀርቦ በቀረቡት ጽሑፎች ላይ ውይይት ተደርጓል። | 1 |
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
