ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል
📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል
Канал ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል (@mkpublicrelation) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 51 201 підписників, посідаючи 1 071 місце в категорії Релігія і духовність та 620 місце у регіоні Ефіопія.
📊 Показники аудиторії та динаміка
З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 51 201 підписників.
За останніми даними від 03 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 633, а за останні 24 години на 29, загальне охоплення залишається високим.
- Статус верифікації: Не верифікований
- Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 16.60%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 7.88% реакцій від загальної кількості підписників.
- Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 8 497 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 4 033 переглядів.
- Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 48.
📝 Опис та контентна політика
Опис каналу не надано.
Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 04 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.
Триває завантаження даних...
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 04 липня | +1 | |||
| 03 липня | +31 | |||
| 02 липня | +24 | |||
| 01 липня | +18 |
| 2 | Немає тексту... | 3 468 |
| 3 | "የአኃት አብያተ ክርክቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ" የፓናል ውይይት ዘገባ ፤ ፤ ክፍል ፩
ሰኔ ፳፮/፳፻፲፰ ዓ.ም
የአኃት አብያተ ክርክቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት ግንቦት ፳፱/፳፻፲፰ ዓ.ም ተካሄዶ የነበረ ሲሆን በውይይቱም የሚክትሉተ ሦስት ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
፩ኛ - የአኃት አብያተ ክርስቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ - በመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል በመንበረ ፓትርያሪክ ጥናት፣ ምርምርና መረጃ መምሪያ ኃላፊ እና የቅ/ሲኖዶስ ኮምዪኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ እንዲሁም የሊቃውንት ጉባኤ አባል
፪ኛ - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት፣ ትግበራ፣ ክትትልና ግምገማ ከትናንት እስከ ዛሬ - በመ/ር ባሕረ ጥበባት ሙጨ
፫ኛ - የቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት ትግበራና የማኅበረ ቅዱሳን ድርሻ - በዶ/ር በሪሁን ተፈራ የማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ
ጽሑፎችና አጠቃላይ ውይይት በሦስት ክፍል የቀረበ ሲሆን በመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል ስለ አኃት አብያተ ክርስቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ የቀረበው የመጀመሪያው ክፍል እንደ ሚከተለው ቀርቧል፡፡https://youtu.be/1QC70jI2QDU?si=tlpK_B2CaR-K5mQJ | 3 960 |
| 4 | https://youtu.be/gR5sk-DMId8?si=8KqsZhOyFXoaFYdp | 3 719 |
| 5 | “መሠረተ ሃይማኖት” የተባለ የልጆች መጽሐፍ የፊታችን እሑድ እንደሚመረቅ የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ገለጸ
ሰኔ ፳፭ /፳፻፲፰ ዓ.ም
የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎትን በስፋት ተደራሽ ለማድረግ የሚውል “መሠረተ ሃይማኖት” በሚል ርእስ የተዘጋጀ የልጆች መጽሐፍ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በማኅበሩ ሕንጻ 3ኛ ወለል ንቡረ ዕድ ድሜጥሮስ አዳራሽ እንደሚመረቅ በማኅበረ ቅዱሳን የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ አገልግሎት ዳይሬክተር ዲ/ን ሙሉጌታ ነጋ ገልጸዋል።
መጽሐፉ በዲ/ን ማርኤል ሽመልስ የተዘጋጀ ሲሆን የክርስትና መሠረተ እምነት የሆኑትን አምስቱን አዕማደ ምሥጢራት ለልጆች በሚገባ መልኩ የተጻፈ መሆኑን ዲ/ን ሙሉጌታ ነጋ ተናግረዋል።
በመርሐ ግብሩ ትምህርተ ወንጌል፣ የስብከተ ወንጌል ዘጋቢ ፊልምና የመጽሐፍ ምርቃቱ ይከናወናል ተብሏል። | 5 410 |
| 6 | የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎትም በ2018 ዓ.ም ያለፉት 9 የአገልግሎት ወራት ብቻ በመላ ሀገራችን 15 የሚደርሱ አስቸኳይ ማኅበራዊ ድጋፍ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ አድርጓል። በያዝነው ጾመ ሐዋርያትም “የጾም ቁርሳችን ለወገኖቻችን” በሚል መሪ ቃል ሰፊ የማኅበራዊ ድጋፍ ማሰባሰብ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል። አርሲን ጨምሮ፣ በልዩ ልዩ ማኅበራዊ ቀውሶች የተጎዱ ወገኖችን ሕይወት ለመታደግ፣ የምእመናን ተሳትፎ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ ቀርቧል።
ድጋፍ ለማድረግ፡-
#በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
በአሐዱ ባንክ 0025393810901
በአቢሲንያ ባንክ 37235458
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000309803648
በወጋገን ባንክ 0837331610101
በአዋሽ ባንክ -01329817420400 እንዲሁም
በወገን ፈንድ፡- https://Www.wegenfund.com/mknu መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። | 5 906 |
| 7 | ማኅበረ ቅዱሳን በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ ወረዳ ጠለታ ለሚገኙ ተፈናቃዮች ከ1.2 ሚሊዮን ብር ወጭ የሆነበት አስቸኳይ የምግብ ግብዓቶች ድጋፍ አደረገ።
ሰኔ ፳፬/፳፻፲፰ ዓ.ም
በአርሲ ሀገረ ስብከት በተለያዩ ወረዳዎች በሚገኙ ምእመናን ላይ እየደረሰ ባለው ተከታታይ ጥቃት የተጎዱ ወገኖችን ለመርዳት ከሀገረ ስብከቱ ጋር በቅርበት እየሠራ የሚገኘው ማኅበረ ቅዱሳን፣ በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ መሪነት ድጋፍ ለማድረስ ሲሠራ ቆይቷል::
በዚህም በአርሲ ሀገረ ስብከት አሰኮ ወረዳ ቤተ ክህነት ሥር በምትገኘዋ ጠለታ ጨፋ ቢዮ ቀበሌ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያንን እና በካራ ኩፍቴና መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ላይ በደረሰው ጥቃት ተፈናቅለው በእሬቻ ሚካኤል ለሚገኙ ተፈናቃዮች አስቸኳይ ድጋፍ አድርጓል።
በድምሩ 1.2 ሚሊዮን ብር ወጭ የሆነበት 114 ኩንታል የጤፍ ዱቄት ለተጎጅዎች የደረሰ ሲሆን ይህ ድጋፍ የተደረገው በሀገር ውስጥና በመላው ዓለም ከሚገኙ በጎ አድራጊ ምእመናንና ተቋማት በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ነው።
በድጋፍ ርክክብ ወቅትም የአሰኮ ወረዳ ቤተ ክህነት ተወካዮች፣ የማኅበረ ቅዱሳን አሰኮ ወረዳ ማእከል አመራር አባላት፣ የአካባቢው የመንግሥት መዋቅር መሪዎችና በጎ አድራጊ ተቋማት ተገኝተው ድጋፉን ለተጎጅዎች አከፋፍለዋል።
ሀገረ ስብከቱና የሚመለከተቻው የመንግሥት ተወካዮችም፣ ማኅበረ ቅዱሳንም ለተጎጅዎች ባደረገው ድጋፍም ምስጋና አቅርበዋል። | 5 946 |
| 8 | አንድ ፊኒሺንግ_ዕቃ_ትውልድ ለሚታነጽበት የማኅበረ ቅዱሳን የልህቀት ማእከል ድጋፍ እናድርግ✝️✝️
ድጋፍ ለማድረግ
1.በንግድ ባንክ 1000003780717
2.በአሐዱ ባንክ 0003488710901
3.በአቢሲኒያ ባንክ 4753388
4.በአዋሽ ባንክ 01320021428400
5.በወጋገን ባንክ 0057130830101
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://forms.gle/E87npdh8XnWWN3vV7 | 6 309 |
| 9 | አሶሳ፣ እንጅባራ፣ መቱ፣ ግልገል በለስ፣ ሎጊያ፣ ሩቅ ምሥራቅና ዲላ ማእከላት ጠቅላላ ጉባኤያቸውን አከናወኑ
ሰኔ ፳፫/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የአሶሳ ማእከል 28ኛ ዓመት፣ የእንጅባራ ማእከል 20ኛ ዓመት፣ የመቱ ማእከል 28ኛ ዓመት፣ የዲላ ማእከል 6ኛ ዓመት፣ ግልገል በለስ፣ ሎጊያና ሩቅ ምሥራቅ ማእከላት ጠቅላላ ጉባኤያቸውን አከናውነዋል።
በጠቅላላ ጉባኤው አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የየሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ እና የሀገረ ስብከቱ የየመምሪያ ክፍል ኀላፊዎች ፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ የሰንበት ትምህርት ቤትና የማኅበራት ተወካዮች፣ የዋናው ማእከል ተወካዮች፣ የማእከላቱ የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላት፣ የወረዳ ማእከላት ተወካዮች እንዲሁም የማኅበሩ አባላት ተሳትፈዋል።
በመርሐ ግብሩ ትምህርተ ወንጌል፣ መዝሙር፣ የ2018 ዓ. ም ዕቅድ ክንውን፣ የኦዲት ሪፖርት ቀርቦ በዕቅድ አፈጻጸሙ ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጎ ጸድቋል። | 6 018 |
| 10 | አሶሳ፣ እንጅባራ፣ መቱ፣ ግልገል በለስ፣ ሎጊያ፣ ሩቅ ምሥራቅና ዲላ ማእከላት ጠቅላላ ጉባኤያቸውን አከናወኑ
ሰኔ ፳፫/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የአሶሳ ማእከል 28ኛ ዓመት፣ የእንጅባራ ማእከል 20ኛ ዓመት፣ የመቱ ማእከል 28ኛ ዓመት፣ የዲላ ማእከል 6ኛ ዓመት፣ ግልገል በለስ፣ ሎጊያና ሩቅ ምሥራቅ ማእከላት ጠቅላላ ጉባኤያቸውን አከናውነዋል።
በጠቅላላ ጉባኤው አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ የየሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ እና የሀገረ ስብከቱ የየመምሪያ ክፍል ኀላፊዎች ፣ የአድባራት አስተዳዳሪዎች፣ የሰንበት ትምህርት ቤትና የማኅበራት ተወካዮች፣ የዋናው ማእከል ተወካዮች፣ የማእከላቱ የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላት፣ የወረዳ ማእከላት ተወካዮች እንዲሁም የማኅበሩ አባላት ተሳትፈዋል።
በመርሐ ግብሩ ትምህርተ ወንጌል፣ መዝሙር፣ የ2018 ዓ. ም ዕቅድ ክንውን፣ የኦዲት ሪፖርት ቀርቦ በዕቅድ አፈጻጸሙ ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጎ ጸድቋል። | 1 |
| 11 | በመርሐ ግብሩ የአሶሳ ማእከል የጽ/ቤት ኀላፊ ዲ/ን አበራ እሸቱ ማኅበረ ቅዱሳን ከ1984 ዓ.ም. ጀምሮ በዩኒቨርሲቲዎችና ኮሌጆች የሚማሩ ኦርቶዶክሳውያን ወጣቶችን በማደራጀትና በማስተማር በርካታ ተማሪዎችን ማስመረቁን ገልጸው ተመራቂዎቹም ቤተ ክርስቲያናቸውን፣ ሀገራቸውንና ማኅበረሰባቸውን በትጋትና በታማኝነት እንዲያገለግሉ አሳስበዋል።
በመጨረሻም ለሁሉም ተመራቂዎች የአደራ መስቀል ተሰጥቶ ጉባኤው በአባቶች ቡራኬና ጸሎት ተጠናቅቋል።
ምንጭ፦ በማኅበረ ቅዱሳን የአሶሳ ማእከል ነው። | 4 485 |
| 12 | የአሶሳ ማእከል ለ5 ዓመታት ያስተማራቸውን የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች አስመረቀ
ሰኔ ፳፫/፳፻፲፰ ዓ.ም.
በማኅበረ ቅዱሳን የአሶሳ ማእከል የግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ዋና ክፍል ለአምስት ተከታታይ ዓመታት በምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ አረጋዊ ቤተ ክርስቲያን በመደበኛ መርሐ ግብር ሲያስተምራቸው የቆዩ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባኤ ተማሪዎችን አስመርቋል።
የግቢ ጉባኤ አገልግሎት ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ የሚያገኙትን አካዳሚ ዕውቀት ከመንፈሳዊ ትምህርት፣ ከሥነ ምግባር ሥልጠናና ከአገልግሎት ልምድ ጋር በማጣመር ለቤተ ክርስቲያን፣ ለሀገርና ለማኅበረሰብ ጠቃሚ የሆነ ትውልድ ለማፍራት በተከታታይ የሚሠራ አገልግሎት መሆኑን ተጠቅሷል።
በምረቃ ሥነ ሥርዐቱ የፋርማሲ ትምህርት ክፍል ተማሪ ዲ/ን ኪዳነ ማርያም ውለታው 3.98 GPA በማስመዝገብ የዩኒቨርሲቲውን ዋንጫና የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሲሆን በግቢ ጉባኤ የአብነት ትምህርትን በመከታተል የዲቁና ማዕረግ በመቀበል አካዳሚያዊ ስኬትና መንፈሳዊ እድገት አብረው ሊያድጉ እንደሚችሉ አስመስክሯል።
ተሸላሚው ዲ/ን ኪዳነ ማርያም ውለታው እንደገለጸው በግቢ ጉባኤ ያገኘው መንፈሳዊ ትምህርት፣ የጊዜ አጠቃቀም ሥልጠናና የአገልግሎት ልምድ በአካዳሚያዊ ውጤቱ ላይ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳደረገለት ገልጿል።
በተመሳሳይ የሕግ ትምህርት ተመራቂው ዲ/ን ጥበቡ አለኽኝ በግቢ ጉባኤ ያገኘው ዕውቀትና የአገልግሎት ልምድ ለመንፈሳዊ ሕይወቱ፣ ለትምህርቱና ለወደፊት ሕይወቱ ጠቃሚ መሆኑን ተናግሯል። | 4 306 |
| 13 | ከተመራቂ የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች መካከል ከቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ተማሪ ነጋሽ አሰፋ 39A⁺ በማስመዝገብ አጠቃላይ 3.98 ውጤት በማምጣት 1ኛ ደረጃን እና ተማሪ ቤተልሔም ጥላሁን 3.92 እንዲሁም 30A⁺ በማምጣት በዩኒቨርሲቲ ደረጃ የተዘጋጀውን ዋንጫ በሁለቱም ጾታ በማሸነፍ በድምሩ ስድስት ሜዳሊያዎችን በመውሰድ በሁለት በኩል የተሳሉ ሰይፎች የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች መሆናቸውን በአደባባይ አስመስክረዋል።
ዘገባ በማኅበረ ቅዱሳን የደብረ ማርቆስ ማእከል ሚዲያ አገልግሎት ነው። | 4 447 |
| 14 | ደብረ ማርቆስ ማእከል 252 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎችን አስመረቀ።
ሰኔ ፳፫/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የደብረ ማርቆስ ማእከል ግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ዋና ክፍል ለ4 ዓመታት
በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ እንድማጣ ገነተ ኢየሱስ ዋናው ግቢ 150 እና ጤና ካምፓስ የመቃ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን 102 በድምሩ 252 ተማሪዎችን ካህናት አባቶች፣ የማእከሉ የሥራ አስፈጻሚ አባላትና የተመራቂ ቤተሰቦች በተገኙበት ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም አስመረቋል።
በመርሐ ግብሩ ለተመራቂ ተማሪዎች የእንኳን ደስ አላችሁና የማኅበሩን መልእክት ያስተላለፉት የማእከሉ ሰብሳቢ ድረስ እንዳላማው ጌታ በወንጌሉ
“ነገር ግን ሽሽታችሁ በክረምት እንዳይሆን ጸልዩ” (ማቴ.24 ÷20) በማለት የክረምትን ዝናብ ውርጭ፣ ጭቃ የተሰቀቀ /የሰነፈ/ ገበሬ በበጋው ወራት ረሃብ፣ ችጋር፣ ሰቆቃ እንደሚያጋጥመው የታወቀ ነው። እናንተ ይህንን ተገንዝባችሁ እንደ ታታሪ ገበሬ በበጋ መሬቱን አርሶ እና አለስልሶ፣ ዘሩን አዘጋጅቶ፣ በክረምት ዘርቶ፣ አርሞ ኮትኩቶ በመኸር ወቅት መልካሙን የስንዴ፣ የጤፍ፣ የገብስ ምርቱን በብዙ ትዕግሥት ጠብቆ እንደሚሰበስበው ሁሉ እናንተም ለዚህ ፍሬ ለመብቃት ወጥታችሁ፣ ወርዳችሁ፣ ረጅም ሰዓታትን አንብባችሁ፣ ብዙ መጻሕፍት በማገላበጥ፣ ለትምህርቱ የተመደበውን ሰዓት በክፍል ተቀምጣችሁ ተምራችሁ እና የሚሰጡ የቤት ሥራዎችን እና ፕሮጀክቶችን በተገቢው ሁኔታ ሠርታችሁ፣ የቀረቡላችሁን የተለያዩ ፈተናዎችን በማለፍ፣ የመምህሮቻችሁን ቃል ተቀብላችሁ፣ የቤተሰቦቻችሁን እና የጓደኞቻችሁን በጎ ምክር ሰምታችሁ ለዚህች ፍሬ የበቃችሁ ያለመታከት በብዙ ትዕግሥት ነውና እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል። | 4 397 |
| 15 | በአዲስ አበባ ማእከል 477 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች መመረቃቸው ገለጸ።
ሰኔ ፳፫/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ዋና ክፍል የቅድስት ልደታ ማስተባበሪያ 9 ግቢ ጉባኤ እና የቅዱስ እስጢፋኖስ ማስተባባሪያ 2 ግቢ ጉባኤ ሰኔ 21ቀን 2018 ዓ.ም በማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያምና ደብረ መድኀኒት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን 477 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎችን አስመርቋል።
በዕለቱም ትምህርተ ወንጌል በመምህር ዮሐንስ ጌታቸው ፣መዝሙር በምዕራብ ማስተባበሪያ መዘምራን ፣ወረብ በተመራቂ ተማሪዎች የቀረበ ሲሆን የማኅበረ ቅዱሳን ሥራ አመራር ጉባኤ ጸሓፊ ዲ/ን ብንያም አያሌው፣ የአዲስ አበባ ማእከል ሰብሳቢ ዲ/ን ኀይለ ማርያም ፣የማእከሉ የጽ/ቤት ኀላፊ አቶ ካሳሁን ኀይሌ፣ የማእከሉ ግቢ ጉባኤ አገልግሎት ዋና ክፍል ኀላፊ ሚካኤል ብርሃኔ፣ የደብሩ አገልጋዮች ፣ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የተመራቂ ተማሪ ወላጆች ተገኝተዋል።
የማኅበረ ቅዱሳን ሥራ አመራር ጉባኤ ጸሓፊ ዲ/ን ብንያም አያሌው ለተመራቂ ተማሪዎች የእንኳን አደረሳችሁ መልእክትና የማኅበሩን መልእክት "ያለ ዋጋ የተቀበላችሁትን ያለ ዋጋ እንድትሰጡ የአደራ ምክራችን ነው፣ብዙ ዋጋ ለከፈሉ ወላጆቻችሁና ቤተሰቦቻችሁ የምትችሉትን ሁሉ በማድረግ ማገዝ ይጠበቅባችኋል፣በተማራችሁት ትምህርት በሙያችሁ ሀገርንና ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በታማኝነት በማገልገል እስከመጨረሻው ድረስ እንድትጸኑ" በማለት መልእክት አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች የዕውቅናና የምስክር ወረቀት እንዲሁም ለሁሉም የግቢ ጉባኤ ተመራቂ ተማሪዎች በአባቶች ቡራኬ የአደራ መስቀል ተሰጥቶ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል።
መረጃው በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ሚዲያ ነው። | 6 053 |
| 16 | በዘንድሮው ዓመት ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ካዘጋጃቸው 18 ሜዳሊያ ዋንጫውን ጨምሮ 14ቱ በግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች የተወሰዱ መሆኑን በማኅበረ ቅዱሳን የባሕር ዳር ማእከል የግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ዋና ክፍል ኀላፊ ቀሲስ ምሕረት እንዳለው ገልጸዋል።
መረጃው በማኅበረ ቅዱሳን የባሕር ዳር ማአሰከል ሚዲያ አገልግሎት ክፍል ነው። | 7 447 |
| 17 | በዘንድሮው ዓመት ባሕር ዳር ዩኒቨርስቲ ካዘጋጃቸው 18 ሜዳሊያ ዋንጫውን ጨምሮ 14ቱ በግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች የተወሰዱ መሆናቸው ተገለጸ
ሰኔ ፳፪/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የባሕር ዳር ማእከል በ7 የተለያዩ ግቢ ጉባኤያት ያስተማራቸውን 1,073 የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎችን ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም የአድባራት እና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የተመራቂ ቤተሰቦች በተገኙበት በፔዳ ግቢ ጉባኤ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ አስመርቋል።
አቶ ብርሃኑ አሳሳ በማኅበረ ቅዱሳን የባሕር ዳር ማእከል ምክትል ሰብሳቢ በምረቃ መርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተው የማእከሉን የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት ለተመራቂዎች እና ለተመራቂ ቤተሰቦቻቸው ያስተላለፉ ሲሆን በመልእክታቸው
“በዚህ ዘመን በዘረኝነት፣ በሥርዓት አልበኝነትና በልዩ ልዩ ፈተናዎች ሀገር እየተፈተነች ቢሆንም በግቢ ጉባኤ ሕይወት ማለፋችሁ እንድትተርፉ አድርጓችኋል” ብለዋል።
በዕለቱ በመልአከ ምሕረት ግሩም አለነ የሰሜን ጎጃም ሀገረ ስብከት ሐዋርያዊ አገልግሎት እና ስብከተ ወንጌል መምሪያ ኀላፊ ትምህርተ ወንጌል የሰጡ ሲሆን
ዛሬ ቤተ ክርስቲያን ተሠርታ የተመረቀችበት ቀን በመሆኑ በዚህ ዕለት በመመረቃችሁ ደስታችሁን እጥፍ ድርብ ያደርገዋል“ በማለት የዛሬ ተመራቂዎች በቀጣይ ሕይወታቸው ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል የበረቱ እንዲሆኑ እና ሁሌም ለማወቅና ለመማር መትጋት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
በመርሐ ግብሩ ተሞክሯቸውን ያቀረቡ የከፍተኛ ማእረግ ተመራቂ ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት የማምጣታቸው ምሥጢር በግቢ ጉባኤ ውስጥ መሳተፋቸውና ጊዜያቸውን በአግባቡ መጠቀም በመቻላቸው መሆኑን ገልጸዋል። | 7 883 |
| 18 | በማኅበረ ቅዱሳን ጎባ ወረዳ ማእከል የግቢ ጉባኤ ክፍል ተጠሪ መምህር ፍቃዱ “አዲሱን የሕይወት ጉዞ በምትጀምሩበት ጊዜ ከቤተ ክርስቲያን አትለዩ። የቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ የማስፈጸም ተስፋ እናንተ ናችሁ። የገባችሁትን ቃል ኪዳን አትርሱ። በመጪው ዘመን በሁሉም መልካም ሥራ እንድትበረቱ እንመኛለን። እናንተም እዚህ የምትቀሩ ደግሞ ከወንድሞቻችሁ መልካም አርአያ ውሰዱ።" ሲሉ የዕለቱን መልእክት አስተላልፈዋል።
በዕለቱም የደብሩ አስተዳዳሪ መልአከ ሳህል ቀሲስ ዳኛቸው የተገኙ ሲሆን የስብከተ ወንጌል፣ የመዝሙር መርሐ ግብር ቀርቦ የአደራ መስቀል ለተመራቂዎች በመስጠት እና ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች ከመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የጎባ ሪፈራል ሆስፒታል ግቢ ጉባኤ ሥጦታ ተበርክቶ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል።
ዘገባው በማኅበረ ቅዱሳን የባሌ ሮቤ ማእከል ሚዲያ ነው። | 6 045 |
| 19 | የግቢ ጉባኤ አባል (CGPA) 4.00 ነጥብ በማምጣት የዓመቱ የዋንጫ እና የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆነ።
ሰኔ ፳፪/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን ባሌ ሮቤ ማእከል የጎባ ወረዳ ማእከል በመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ የጎባ ሪፈራል ሆስፒታል ግቢ ጉባኤ 82 ተማሪዎች በጎባ ደብረ ሰላም ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ሰኔ 21 ቀን 2018 ዓ.ም በአባቶች ቡራኬ አሰመርቋል።
ከተመረቁት ተማሪዎች መካከል በግቢ ጉባኤው በሥራ አሰፈጻሚነት ሲያገለግል የነበረው ተማሪ ቶልቻ ከበደ በነርሲንግ የትምህርት መስክ ከ39 ኮርሶች 25ቱን ‘A+’ እና ቀሪውን 'A' በማስመዝገብ አጠቃላይ (CGPA) 4.00 ነጥብ በማምጣት የዓመቱ የዋንጫ እና የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል።
በተጨማሪም ተማሪ ሚኪያስ ገዛኸኝ (CGPA) 3.88 በክሊኒካል ፋርማሲ ከስኩል ኦፍሜዲሲን ከፍተኛውን ውጤት በማምጣት የሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል።
ለዚህ ውጤት ያብቃኝ በግቢ ጉባኤ ውስጥ በጸሎት የእግዚአብሔርን እርዳታ፣ የቅድስት ድንጌል ማርያም ምልጃ እና እገዛ ነው ያለው የዋንጫ እና የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚው ተማሪ ቶልቻ ከበደ ሲሆን በግቢ ጉባኤ ቆየታችን በዓለም እንዳንጠፋ እያስተማሩን ለዚህ ክብር ያበቁኝ የግቢ ጉባኤውን አመራሮች አመሰግናለው ብሏል።
ተማሪ ቶልቻ አክሎ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚገኙ ተማሪዎች ወደ ግቢ ጉባኤ ገብተው በመማር ወደ እግዚአብሔር መቅረብ አለባቸው በማለት ምክሩን የለገሰ ሲሆን ተማሪው ከፍተኛ ውጤት በማምጣቱም የማስተርስ ዲግሪ የትምህርት ዕድል ከመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ አግኝቷል። | 6 537 |
| 20 | በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን።
" ሰኔ ጎልጎታ "
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህች ቀን (ሰኔ 21) ልጇን ወዳጇን ጐልጐታ በሚባል ቦታ ላይ እንባዋ እንደ ጅረት እስኪፈስ ድረስ ለኃጥአን ምሕረትን ለምናዋለች:: ጌታችንም ‹‹ስምሽን የጠራውን፤ በቃል ኪዳንሽ ያመነውን ሁሉ እምርልሻለሁ፡፡›› ብሎ ቃል ኪዳን ሰጥቷታል፡፡
ክፍል ፪
…የቀጠለ
ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም ተአምኆ ቅዱሳን በሚባለው ታላቅ መጽሐፉ ፡-
“ሰላም ለቤተ ክርስቲያን ቅድስት ማኅደረ ስብሐት ምዕዋደ መላእክት እመ ኵሉ ሕዝብ”
(የሕዝብ ሁሉ እናት የመላእክት መዘዋወሪያ (ቦታ) የምስጋና ማደሪያ ለሆነችው ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሰላምታ ይገባል) ብሏታል፡፡
ይኸው ሊቅ አባ ጊዮርጊስ በተመሳሳይ መልኩ እናትነቷን በሰባቱ ጊዜያት የሕማማት ሰላምታው ላይ፡-
“ሰላም ለኪ ቤተ ክርስቲያን እምየ ዘትጼንዊ መጽርየ
ብኪ ጸናዕኩ እምከርሠ እምየ
ቤተ ክርስቲያን አክሊለ ርእስየ ሰላም ለኪ”
(እንደ ቀጋ መዓዛሽ ያማረ ቤተ ክርስቲያን እናቴ ሰላምታ ለአንቺ ይገባል፤ ከእናቴ ማሕፀን ጀምሮ በአንቺ ጸናሁ፤ የራሴ አክሊል የምትሆኝ ቤተ ክርስቲያን ሰላምታ ለአንቺ ይገባሻል)
“በሐኪ በሐኪ ቤተ ክርስቲያን እምነ
ግበሪ ሰላመ ማእከሌነ
እምኀይለ ፀላኢ ወፀር ዕቀቢ ኪያነ
ትንብልናኪ የሀሉ ምስሌነ፤ ሰላም ለኪ”በማለት ሊቃውንት ስለ ቤተክርስቲያን ክብር በሰፊው ጽፈዋል።
ሐዋርያትም የሠሩት ሦስት ክፍል አድርገው ሲሆን፣ ይህም የመጀመሪያው የታቦተ አዳም፤ ሁለተኛው የታቦተ ሙሴ፤ ሦስተኛው የታቦተ ኢየሱስ ክርስቶስ ምሳሌ ነው፡፡ ዳግመኛም የሦስቱ ዓለማት ማለትም የመጀመሪያው የጽርሐ አርያም፣ ሁለተኛው የኢዮር፣ ሦስተኛው የጠፈር ምሳሌ ነው፡፡
እንዲሁም መጀመሪያው የኤረር፣ ሁለተኛው የራማ፣ ሦስተኛው የኢዮር አምሳል ነው፡፡ በኤረር፡- መላእክት፣ መኳንንት፣ ሊቃናት፤ በራማ፡- ሥልጣናት፣ መናብርት፣ አርባብ፤ በኢዮር፡- ኃይላት፣ ኪሩቤል፣ ሱራፌል ይኖራሉ፡፡ እነዚህ ዘጠኙ ነገደ መላእክት የዘጠኙ መዓርጋተ ቤተ ክርስቲያን (መዓርጋተ ክህነት) አምሳል ሲኾኑ፣ ይኸውም መላእክት – የመዘምራን፤ መኳንንት – የአናጕንስጢሳውያን፤ ሊቃናት – የንፍቀ ዲያቆናት፤ ሥልጣናት – የዲያቆናት፤ መናብርት – የቀሳውስት፤ አርባብ – የቆሞሳት፤ ኃይላት – የኤጲስ ቆጶሳት፤ ሱራፌል – የጳጳሳት፤ ኪሩቤል – የሊቃነ ጳጳሳት አምሳሎች ናቸው፡፡
ይህም በታች (በምድር) የሚኖሩ ደቂቀ አዳም ከቅዱሳን በቀር ወደ ላይ (ወደ ሰማይ) መውጣት እንደማይቻላቸው፣ ከመዘምራን እስከ ጳጳሳት ድረስ ያሉ ካህናትም ከእነርሱ በላይ ያሉትን መዓርግ መሥራት (መፈጸም) እንደማይቻላቸው ያጠይቃል፡፡ እንደዚሁም በላይ የሚኖሩ መላእክት ወደ ታች መውረድ እንደሚቻላቸው ሊቃነ ጳጳሳትም ከእነርሱ በታች ያሉ ካህናትን ተልእኮ መፈጸም (መሥራት) እንደሚቻላቸው ያስረዳል፡፡
በጽርሐ አርያም መንበረ ብርሃን (የብርሃን መንበር)፤ ታቦተ ብርሃን (የብርሃን ታቦት)፤ መንጦላዕተ ብርሃን (የብርሃን መጋረጃ)፤ እንደዚሁም ፬ ጸወርተ መንበር (መንበሩን የሚሸከሙ)፤ ፳፬ አጠንተ መንበር (መንበሩን የሚያጥኑ) መላእክት አሉ፡፡ ጽርሐ አርያም – የመቅደስ፤ መንበረ ብርሃን – የመንበር፤ መንጦላዕተ ብርሃን – የቤተ መቅደሱ መጋረጃ፤ ፬ቱ ጸወርተ መንበር – የ፬ቱ ሊቃነ ጳጳሳት ወይም የመንበሩ እግሮች፤ ፳፬ቱ አጠንተ መንበር – የጳጳሳት (የኤጲስ ቆጶሳት) አምሳሎች ናቸው፡፡
ሊቀ ጳጳስ ባስልዮስም በዘመኑ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም በታነጸው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሥዕል ለማሳል በመሻቱ ሠሌዳ ፈለገ፤ ከአንድ ባለጠጋ ዘንድ እንዳለም ሰምቶ እንዲሰጠው ቢያስልክበትም ባለጠጋው ግን ለልጆቹ እንደሆነና ከዚያም አልፎ በመድፈር በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ላይ የስድብ ቃል ተናገረ፤ በቅጽበትም ወድቆ ሞተ፤ በዚህን ጊዜ ልጆቹ በመፍራታቸው ሠሌዳውን ከብዙ ወርቅና ዕንቊ ጋር ወደ ቅዱስ ባስልዮስ ወሰዱለት፤ እርሱም ሠሌዳውን ወደ ሠዓሊው ወስዶ እንዲሥልበት ሰጠው፤ ሆኖም ግን እመቤታችን ድንግል ማርያም በራእይ ተገልጻ ሥዕሏን በሠሌዳው እንዳይሥል ከለከለችው፤ ከዐመፀኛ እጅ የተገኘ ነበርና፡፡ የአንዱ በቀኝ የአንዱ በግራ የተሣለ የእመቤታችን ሥዕል ቀይ ሠሌዳ ያለበትንም ሥፍራ ነገረችው፡፡
ቅዱስ ባስልዮስም እመቤታችን ወደ አመለከተችው ቦታ በመሄድ ሠሌዳውን አግኝቶ ወደ ቤተ ክርስቲያኗ አምጥቶ ሁለት ምሰሶዎች ከቤተ መቅደሱ ፊት ለፊት ካቆመ በኋላ ሥዕሏን በዚያ አስቀመጠ፡፡ እግዚአብሔር አምላክም በምሰሶዎቹ በታች የውኃ ምንጭ አፈለቀ፤ ድውያንም በእርሷ ይፈወሱ ነበር፡፡ ከእመቤታችንም ሥዕል በሽተኞች የሚፈውስ የዘይት ቅባት መፍሰስም ጀመረ፡፡
ነገር ግን አንዲት ሴት በፈለቀው ምንጭ ውኃ ስትታጠብ መላ ሰውነቷ በለምጽ ተሸፈነ፤ በዚህን ጊዜም ቅዱስ ባስልዮስ አስጠርቶ ምን እንደሆነች ጠየቃት፤ እርሷም የእኅቷን ባል እንደወደደችና እኅቷን በመርዝ ገድላ እንዳገባችው ነገረችው፤ ቅዱስ ባስልዮስም ታላላቅ ሦስት ኃጢአት በመሥራቷ ምንአልባት እግዚአብሔር ይቅር ይላት እንደሆነ ንስሓ እንድትገባ አዘዛት፤ ነገር ግን በዚያች ሰዓት ምድር ተሰንጥቃ ዋጠቻት፤ እርሷ ቤተ ክርስቲያንን ተዳፍራለችና፡፡
እኛም የቤተ ክርስቲያን ልጆች ቤተ ክርስቲያንን በማክበርና ሥርዓቱን በመጠበቅ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ክብረ በዓል እናከብር ዘንድ ይገባል፡፡
ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በረከት ያሳትፈን፤ አሜን።
ምንጭ፤ መጽሐፈ ስንክሳር ዘወርኃ ሰኔ ፳ እና ፳፩ | 7 183 |
Вже доступно! Дослідження Telegram за 2025 — головні інсайти року 
