ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል
📈 Telegram kanali ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል analitikasi
ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል (@mkpublicrelation) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 51 360 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 1 066-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 621-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 51 360 obunachiga ega bo‘ldi.
10 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 715 ga, so‘nggi 24 soatda esa 13 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 13.83% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 7.68% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 7 102 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 3 945 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 55 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Kanal uchun tavsif kiritilmagan.
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 11 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 11 Iyul | 0 | |||
| 10 Iyul | +19 | |||
| 09 Iyul | +32 | |||
| 08 Iyul | +18 | |||
| 07 Iyul | +34 | |||
| 06 Iyul | +31 | |||
| 05 Iyul | +21 | |||
| 04 Iyul | +23 | |||
| 03 Iyul | +31 | |||
| 02 Iyul | +24 | |||
| 01 Iyul | +18 |
| 2 | ማኅበረ ቅዱሳን ለደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ ሁለ ገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት እያስገነባ እንደሚገኝ ገለጸ
ሐምሌ ፪/፳፻፲፰ ዓ.ም
ማኅበረ ቅዱሳን በጎ አድራጊ አካላትን በማስተባበር በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ደባርቅ ከተማ የደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ ሁለ ገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት እያስገነባ እንደሚገኝ ገልጿል።
ማኅበረ ቅዱሳን በቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገትና መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች አገልግሎት የፕሮጀክት ዝግጅትና ትግበራ ምክትል ኃላፊ የሆኑት ኢ/ር ማስተዋል አበበ (ወ/ሪት) እንደገለጹት የደብረ ሐዊ የቅዱስ ያሬድ ገዳም በኢኮኖሚ አቅሙን ለማሳደግና አገልግሎቱን ለማስቀጠል የሚረዳ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት በሁለት ዙር እንደሚከናወን ተናግረዋል።
ይህም በመጀመሪያው ዙር B+G+4 ወለል ሕንጻ እየተገነባ እንደሚገኝ የተጠቀሰ ሲሆን ማኅበሩ በዚህ ዙር የሚጠበቅበትን ድርሻ ለማጠናቀቅ በመወጣት ረገድ 75.79% መድረሱን ተገልጿል።
ግንባታው በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚገኙ ድጋፍ አድራጊ አካላትን በማስተባበር የተከናወነ ነው ተብሏል።
በመጨረሻም ቅዱስ ያሬድ ለቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለሀገር ባለውለታ እንደመሆኑና ገዳሙ ጥንታዊ በመሆኑ ለመናንያኑ የዕለት ጉርስ፣ የዓመት ልብስ እንዲሁም ለአገልግሎቱ የሚያስፈልጉ ነገሮችን በማድረግ ገዳሙ ያለበትን ደረጃ ለማቆየት ሁሉም ምእመን በሀሳብ፣ በጉልበትና በገንዘብ የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ ይገባል ሲሉ ኢ/ር ማስተዋል አበበ ጥሪ አቅርበዋል። | 1 |
| 3 | "የአኀት አብያተ ክርክቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ" የፓናል ውይይት ዘገባ
ክፍል ፫
ሐምሌ ፫/፳፻፲፰ ዓ.ም
የአኀት አብያተ ክርክቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት ግንቦት ፳፱/፳፻፲፰ ዓ.ም ተካሄዶ የነበረ ሲሆን በውይይቱም የሚክትሉተ ሦስት ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
፩ኛ - የአኀት አብያተ ክርስቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ - በመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል በመንበረ ፓትርያሪክ ጠ/ቤ/ክ ጥናት፣ ምርምርና መረጃ መምሪያ ኀላፊ እና የቅ/ሲኖዶስ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ኀላፊ እንዲሁም የሊቃውንት ጉባኤ አባል
፪ኛ - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት፣ ትግበራ፣ ክትትልና ግምገማ ከትናንት እስከ ዛሬ - በመ/ር ባሕረ ጥበባት ሙጨ
፫ኛ - የቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት ትግበራና የማኅበረ ቅዱሳን ድርሻ - በዶ/ር በሪሁን ተፈራ የማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ
ጽሑፎችና አጠቃላይ ውይይቱ በሦስት ክፍል የቀረበ ሲሆን የነበረው የማጠቃለያ ውይይት ሦስተኛው ክፍል እንደ ሚከተለው ቀርቧል፡፡ https://youtu.be/x3hRmh2hDPY?si=UpIKdQymapn-yg-I | 3 417 |
| 4 | ዜና ገዳማት | 3 338 |
| 5 | ኑ ! ስደታቸው በሰንበትና በክረምት ለሆነባቸው እንድረስላቸው።
---***---
ለአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር
ወደ መርሐግብሩ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ። https://zoom.us/j/93407133345
ድጋፍ ለማድረግ ፡-
1. Mahibere Kidusan in Europa e.V.
IBAN: DE14 3704 0044 0307 8037 00
BIC: COBADEFFXXX
Reason of payment – 007
2. Mahibere Kidusan in UK
Banking - NatWest
Sort Code - 60 12 51
Acc. No - 364 25 591
Reason of Payment: 007
3. በስዊድን ለምትገኙ፡-
ACCOUNT NUMBER - 9960 3421234653
BIC - NDEASESS
IBAN - SE15 9500 0099 6034 2123 4653
ACCOUNT HOLDER - MAHIBERE KIDUSAN I SVERIGE
NORDEA BANK
Reason of Payment: 007
4. በኢትዮጵያ
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000309803648
በአቢሲኒያ ባንክ 37235458
በአሐዱ ባንክ 0025393810901 | 3 396 |
| 6 | ለበለጠ መረጃ፡-
በአካል 5 ኪሎ ማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ 1ኛ ወለል
ወይም
· በስልክ.ቁ፡- +251 921803238
· በኢሜል፡- yagelgilotber@eotcmk.org
· በቴሌግራም፡- @Zeyklekulu
· WhatsApp:- +251 91 352 8494
· ለመመዝገብና አገልግሎትን ለማግኘት :-
👇 👇 👇
https://forms.gle/CgYYC5gX6oxd3HGS7
ዘመነ ክረምትን በአገልግሎት በር! | 4 300 |
| 7 | ኑ ! ስደታቸው በሰንበትና በክረምት ለሆነባቸው እንድረስላቸው።
---***---
ለአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር
ወደ መርሐግብሩ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ። https://zoom.us/j/93407133345
ድጋፍ ለማድረግ ፡-
1. Mahibere Kidusan in Europa e.V.
IBAN: DE14 3704 0044 0307 8037 00
BIC: COBADEFFXXX
Reason of payment – 007
2. Mahibere Kidusan in UK
Banking - NatWest
Sort Code - 60 12 51
Acc. No - 364 25 591
Reason of Payment: 007
3. በስዊድን ለምትገኙ፡-
ACCOUNT NUMBER - 9960 3421234653
BIC - NDEASESS
IBAN - SE15 9500 0099 6034 2123 4653
ACCOUNT HOLDER - MAHIBERE KIDUSAN I SVERIGE
NORDEA BANK
Reason of Payment: 007
4. በኢትዮጵያ
በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000309803648
በአቢሲኒያ ባንክ 37235458
በአሐዱ ባንክ 0025393810901 | 5 471 |
| 8 | ለበለጠ መረጃ፡-
በአካል 5 ኪሎ ማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ 1ኛ ወለል
ወይም
· በስልክ.ቁ፡- +251 921803238
· በኢሜል፡- yagelgilotber@eotcmk.org
· በቴሌግራም፡- @Zeyklekulu
· WhatsApp:- +251 91 352 8494
· ለመመዘገቢና አገልግሎትን ለማግኝት :-
👇 👇 👇
https://forms.gle/CgYYC5gX6oxd3HGS7
ዘመነ ክረምትን በአገልግሎት በር! | 5 938 |
| 9 | https://youtu.be/P_t_2pp8EpY | 5 182 |
| 10 | ይህ በእንዲህ እንዳለ የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት በበኩሉ በየዓመቱ ለካህናት የሚሰጠውን የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ሥልጠና 15 ዲያቆናትን ሲያሠለጥን የቆየ ሲሆን ከሥልጠናው ጎን ለጎን ለማዕረገ ቅስና የሚያበቃቸውን ትምህርት በመስጠት ማዕረገ ቅስና እንዲቀበሉ አድርጓል።
ሥልጠናው በአርባ ምንጭ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ገዳም ጽርሐ ተዋሕዶ የካህናት ማሠልጠኛ ተቋም ሲሰጥ የቆየ ሲሆን ተቋሙ ለ58ኛ ጊዜ ማሠልጠኑ ተነግራል።
ማኅበረ ቅዱሳን በያዘው መርሐ ግብር 11 ሠልጣኞችን በማስተማር ስምንቱ ማዕረገ ቅስና እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን በሀገረ ስብከቱ መርሐ ግብር ከሠለጠኑት 15 ዲያቆናት መካከል ስምንቱ ማዕረገ ቅስና እንዲያገኙ በማድረግ በአጠቃል ከ26 ሠልጣኞች መካከል 16ቱ ከብፁዕ አቡነ ኤልያስ ማዕረገ ቅስና ተቀብለዋል።
ሠልጣኞች ወደየ አካባቢያቸው ሲመለሱ ወንጌልን በማስፋፋት፣ የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን በመክፈትና የክህነት አገልግሎት በመስጠት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናቸውን ያገለግላሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ መረጃው አመላክቷል። | 5 826 |
| 11 | ማኅበረ ቅዱሳን ያስተማራቸውንና ያሠለጠናቸውን ዲያቆናት አስመረቀ።
ሐምሌ ፩/፳፻፲፰ ዓ.ም
የማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል ከአርባ ምንጭ ማእከል ጋር በጋራ በመሆን ከጋሞና አከባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት፣ ከጎፋና ባስኬቶ ዞኖች ሀገረ ስብከት እና ከወላይታ ሀገረ ስብከት ከተለያዩ ወረዳዎች የተወጣጡ 11 ዲያቆናትን ሲያስተምርና ሲያሰለጥን ቆይቶ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ/ም ማዕረገ ቅስና እንዲቀበሉ በማድረግ አስመርቋል።
በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት በአርባ ምንጭ ቅድስት ማርያም ገዳም አዳሪ አብነት ት/ቤት ሥልጠና ሲወስዱ የነበሩ ዲያቆናት ከሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ከብፁዕ አቡነ ኤልያስ ማዕረገ ቅስና ተቀብለው ተመርቀዋል ።
ሠልጣኝ ዲያቆናቱ የአገልጋይ እጥረት ካሉባቸው የሀገረ ስብከቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተወጣጡ ሲሆኑ ማኅበረ ቅዱሳን የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ እና በማስተባበር ዲያቆናቱ ለማዕረገ ቅስና እንዲበቁ አድርጓል።
ማኅበረ ቅዱሳን አዳዲስ ተጠማቂያንና የአገልጋይ ካህናት እጥረት ካሉባቸው አካባቢዎች የተወጣጡ 11 ዲያቆናትን በመመልመል አሠልጥኖ ወደ አገልግሎት ማሠማራት በያዘው ስልታዊ ዕቅዱ መሠረት ሙሉ ወጫቸውን በመሸፈን ሲያሰለጥን ቆይቷል።
ዲያቆናቱ ለማዕረገ ቅስና የሚያበቃቸውን ኪዳን፣ ሊጦን ፣ መስተብቁዕ እና ዋና ዋና የቅዳሴ ዜማዎችን ያካተተ ትምህርት ሲማሩ የቆዩ ሲሆን ከመሠረታዊው የክህነት ትምህርት ጎን ለጎን የትምህርተ ሃይማኖት ሥልጠናዎች ማለትም ትምህርተ ሃይማኖት መግቢያ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ፣የቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን፣ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን፣ ነገረ ቅዱሳንና ነገረ ማርያም፣ ክርስቲያናዊ ሥነ-ምግባር፣ ሐዋርያዊ ተልእኮ፣ የስብከት ዘዴዎች እንዲሁም ተግባቦት ተሰጥተዋል። | 5 792 |
| 12 | በመጨረሻም የየካ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት ዘካሪያስ ሐዲስ ከማእከሉ እና ከሰንበት ት/ቤት አንድነት ጋር ለመሥራት ያላቸው ፍላጎት እና ሁልጊዜም ለሚያደርጉት ቀና ትብብር ምስጋና ቀርቦ ሌሎች ክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ይህን አብሮ የማገልገል ተሞክሮ ልምድ ቢወስዱ ለቤተ ክርስቲያን ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑ ተገልጾ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል።
መረጃው የማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ሚዲያ ነው። | 5 062 |
| 13 | ለዲያቆናት ፣ ካህናት እና ሰባክያነ ወንጌል ሥልጠና መሰጠቱ ተገለጸ።
ሐምሌ ፩/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል የምሥራቅ ማስተባበሪያ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የካ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት እና ከሰ/ት /ቤት አንድነት ጋር በመተባበር ከ23 አድባራት ለተውጣጡ 291 ዲያቆናት፣ካህናት ፣ሰባክያነ ወንጌል በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ሥልጠና መሰጠቱን ማስተባበሪያው ገልጿል።
የሥልጠናው ዓላማ ካህናት የንስሓ ልጆቻቸውን አያያዝ በተመለከተ፣ በቤተ ክርስቲያን የውስጥ ሥርዓት ላይ ማለትም ማሕሌት፣ ሰዓታት ፣ ኪዳን፣ ቅዳሴ ፣የዐውደ ምሕረት መርሐ ግብርና ሌሎች አገልግሎቶችም የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓት በጠበቀ መልኩ እንዲከወኑ ማስቻል ዋና ዓላማ ተደርጎ እንደተዘጋጀ ተገልጿል።
ሰባክያነ ወንጌል የአገልግሎት ድርሻቸው በዐውደ ምሕረት ላይ በተመደቡበት ዕለት በማስተማር ብቻ ተገድቦ እንዳይቀር ከካህናቱ ጋር በመመካከር የንስሓ ልጆቻቸውን ማስተማር ፣ ምእመናንን ማስተማር ፣ማነጽ እና ያላመኑትን አስተምሮ መመለስ እንደሚያስፈልግ እና ኀላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ለማድረግ ዓላማ ያደረገ መሆኑ በሥልጠናው ላይ ተጠቁሟል።
ሥልጠናው በጠቅላይ ቤተ ክህነት የመሪ ዕቅድ መምሪያ ዐቢይ ኮሚቴ አባል በሆኑት ቀሲስ ብሩህ ተስፋ ሥዩም የተሰጠ ሲሆን ከመርሐ ግብሩ ታዳሚዎች አስተያየትና ጥያቄ ተነሥቶ ምላሽ ተሰጥቷል።
ከዚህ ሥልጠና በኋላ በቀጣይ ከየአድባራቱ አስተዳዳሪዎችእና ጸሓፊዎች ጋር ውይይት ለማድረግ የታቀደ መሆኑን እና በየአጥቢያው የሚገኙ ካህናት፣ መሪጌቶች ፣ዲያቆናት፣ ሰባክያነ ወንጌል አገልግሎቱን በሚጠበቀው ልክ ለማድረግ እንደሚሠራ የክፍለ ከተማው ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት ዘካሪያስ ሐዲስ ገልጸዋል። | 5 730 |
| 14 | ሁሉም አደነቁ ያን ጊዜም አንደበቱ ከድዳነት ተፈትቶለት ተናገረ፣ እግዚአብሔርንም ፈጽሞ አመሰገነው። ስለ ልጁና ስለ መድኃኒታችን መምጣት ልጁ ዮሐንስም የልዑል ነቢይ እንደሚባልና በእግዚአብሔርም ፊት እንደሚሄድ ትንቢት ተናገረ።http://www.eotcmk.org | 5 886 |
| 15 | ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ
ሰኔ ፴ በዚች ዕለት ነቢይ ሰማዕትና ሐዋርያ የሆነ መጥምቁ ዮሐንስ ተወለደ።
ዮሐንስ ማለት እግዚአብሔር ጸጋ ነው ማለት ነው፡፡ትርጓሜ ወንጌልም መጥምቀ መለኮት ዮሐንስን ፍሥሐ ወሐሴት (ተድላናደስታ) ይለዋል ፤ወላጆቹ በእርሱ መወለድ ተደስተዋልና /ሉቃ.፩፥፲፬/፡፡በቅዱስ ወንጌል እንደ ተጻፈ ሄሮድስ የመድኀኒታችን የክርስቶስን መወለድ ከሰብአ ሰገል ሲሰማ መንግሥቴን ይወስድብኛል ብሎ ስለሠጋ ጌታችንን ያገኘሁ መስሎት የቤተልሔም ሕፃናትን መግደል ጀመረ/ማቴ.፪፥፩-፲፮/፡፡
በዚህ ጊዜ ቅድስት ኤልሳቤጥ ልጇን ከሞት ለማዳን ስትል ሕፃኑ ዮሐንስን ይዛ ወደ በረሃ ተሰደደች።
በበረሃም ድንጋይ ቤት ሆኖላቸው፣እግዚአብሔርም ከብርድ፣ከፀሐይና ከአራዊቱ አፍ እየጠበቃቸው መኖር ጀመሩ፡፡ ወደ በረሃ ሲገቡ ቅዱስ ዮሐንስ የሁለት ዓመት ከመንፈቅ ሕፃን ነበር፡፡ ሕፃኑም አደገ ፤በመንፈስም ጠነከረ፤ ለእስራኤል እስከታየበት ቀን ድረስ በምድረ በዳ ኖረ /ሉቃ.፩፥፹/ተብሎ እንደተጻፈ፡፡
ይህም በእናቱ ማኅፀን ውስጥ ሳለ ለእግዚአብሔር ልጅ የሰገደው ነው፣ በመድኅነ ዓለም ክርስቶስ ራስ ላይ እጁን ጭኖ በውኃ ያጠምቀው ዘንድ የተገባው ነው። በቅዱስ ወንጌል እንደ ተነገረ ወንድ ልጅን ትወልድ ዘንድ የኤልሳቤጥ የፅንሷ ወራት በተፈጸመ ጊዜ ወንድ ልጅን ወለደች፤ ዘመዶቿና ጐረቤቶቿ እግዚአብሔር ቸርነቱን እንዳበዛላት በሰሙ ጊዜ ስለእርስዋ ደስ አላቸው።
በስምንተኛውም ቀን ሊገዝሩት መጡ፣ በአባቱም ስም ዘካርያስ ብለው ጠሩት እናቱ ግን አይሆንም ዮሐንስ ይባል አለች። ”ከዘመዶችሽ ስሙ እንዲህ የሚባል የለም” አሏት። አባቱንም ጠቅሰው ”ማን ሊባል ትወዳለህ?”አሉት፤ እርሱም ብራና ለምኖ ስሙ ዮሐንስ ይባል ብሎ ጻፈ ። | 6 150 |
| 16 | ✝️የጾም ቁርሳችን፣
ለወገኖቻችን✝️ +++
በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች እያጋጠሙ ባሉ ማኅበራዊ ቀውሶች( ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች፣ መፈናቀልና ጦርነት ) ብዙ ወገኖቻችን ለከፋ ችግር ተጋልጠዋል።
እርስዎም ለእነዚህ ወገኖች የጾም ቁርስዎን በመለገስ ቸርነትን ያድርጉ!
ድጋፍ ለማድረግ :-
#በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
1. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
2. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
3. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
4. በወጋገን ባንክ - 0837331610101
5. በወገን ፈንድ ፡- https://Www.wegenfund.com/mknu መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን። | 11 005 |
| 17 | የአዲስ አበባ ማእከል 109 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች በደረጃ አንድ ተተኪ መምህራን መመረቃቸውን ገለጸ።
ሰኔ ፳፱/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ዋና ክፍል የግቢ ጉባኤያት ተቋማዊ ልማት ክፍል በደረጃ አንድ ሲያሠለጥናቸው የቆዩ የግቢ ጉባኤ ተማሪዎችን ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓም ማስመረቁን በዋና ክፍሉ የግቢ ጉባኤያት ተቋማዊ ልማት ምክትል ኀላፊ መምህር መስፍን ግርማ ገልጸዋል።
የሥልጠናው ዓላማ የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች ከቀለም ትምህርታቸው ጎን ለጎን የማስተማር ዐቅም ያላቸውን ተማሪዎች ሥልጠና በመስጠት በግቢ ጉባኤ የሚያገለግሉ ተተኪ መምህራንን ማፍራትና ማሰማራት ላይ ያለመ ነው።
በዕለቱም ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶክተር ሙሉጌታ ሥዩም የማኅበረ ቅዱሳን ሥራ አመራር አባል ምክርና የአገልግሎት ልምዳቸውን ያካፈሉ ሲሆን በሥልጠናው ጥሩ አርአያ ላሳዩ ሁለት መምህራን የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል ።
በመጨረሻም የአዲስ አበባ ማእከል ሰብሳቢ ዲያቆን ኃይለ ማርያም መድኅን ለተመራቂዎች "ዛሬ የተመረቃችሁት የመጨረሻ ሳይሆን የመጀመሪያ መሆኑን አውቃችሁ ተጠያቂ መምህር ለመሆን እያነበባችሁና ከሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እየጠየቃችሁ እራሳችሁን አሳድጉ፣ በተሰጣችሁ መክሊት በማገልገል እንድታተርፉ፣ አገልግሎታችሁ በፍቅርና በትሕትና ይሁን" በማለት መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በሥልጠናው ጥሩ ውጤት ላመጡ 3 ተማሪዎች የመጽሐፍት ሽልማትና ለተመራቂዎች የአደራ መስቀል በቀሲስ ገዛኸኝ በቀለ ተሰጥቷቸው መርሐ ግብሩ ተጠናቋል።
መረጃው ፦ በማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ሚዲያ ነው | 5 543 |
| 18 | ከዚህ ባሻገር ብፁዕነታቸው የብፁዕ አቡነ አብርሃምን መልእክት በሚያጠናክር መልኩ "ሊቃውንቱ ለቅድስት ቤተክርስቲያን አንድነት ፣ ከቀድሞው በበለጠ በጋራ ሊቆሙ ፣ አንድ ድምፅ ሁነውም ሊመክሩ ፣ ምክረ ሐሳባቸውንም ለቅዱስ ሲኖዶስ በትጋት ሊያቀርቡ" እንደሚገባ ጠቁመዋል።
የተመራቂ ደቀመዛሙርት መምህር የሆኑት ሊቀ ሊቃውንት ስምዓ ኮነ መልአክ ተማሪዎቻቸው ለዚህ ደረጃ በመብቃታቸው መደስታቸውን ገልጸው በቀጣይም በምስክር ጉባኤ ቤቱ በነበራቸው ቆይታ የቀሰሙትን ጥንታዊ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ዕውቀት ተግባር ላይ በማዋል ለቤተ ክርስቲያንና ለሀገር የሚጠቅም አገልግሎት እንዲሰጡ አሳስበዋል።
የምስክር ጉባኤ ቤቱ ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን እያከናወነ ስለመሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን በምርቃት በዓል ላይ ለመምህራን ማረፊያ እንዲሁም ወደ ምስክር ጉባኤ ቤቱ ለሚመጡ እንግዶች መቀበያ የሚሆን ሕንጻ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
ይህ አዲስ ሕንጻ የጉባኤ ቤቱን የትምህርት ሥርዓት ለማጠናከር፣ ለተማሪዎችም የተሻለ የአስተዳደርና አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያግዝ ተጠቁሟል።
©ፈለገ ገነት ሚዲያ | 4 863 |
| 19 | የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት የ፬ቱ ጉባኤያት የምስክር ጉባኤ ቤት 19 ደቀ መዛሙርትን ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት አስመረቀ።
ሰኔ ፳፱/፳፻፲፰ ዓ.ም
በምርቃት መርሐ ግብሩ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የባሕር ዳር እና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የስካንዲቪያንስ እና የግሪክ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ የምስክር ጉባኤ ቤቱ መምህር ሊቀ ሊቃውንት ስምዓ ኮነ መልአክ ፣ የጠቅላይ ቤተክህነት የሥራ ኀላፊዎች ፣ የምስክር ጉባኤ ቤቶች መምህራን ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ፣ ተመራቂዎችና የተመራቂ ደቀመዛሙርት ወዳጅ ዘመዶች እንዲሁም ጥሪ የተረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ብፁዕ አቡነ አብርሃም በመርሐ ግብሩ ላይ ለተመራቂ ደቀ መዛሙርት እና ለቤተ ክርስቲያን የእንኳን ደስ ያላችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈው "የዛሬ ተመራቂ ደቀ መዛሙርት የነገ መምህራን የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሉዓላዊነትነት ተከብሮ እንዲዘልቅ ፣ ከአጥቢያ ጀምሮ እስከ የቅዱስ ሲኖዶስ የተዘረጋው የቤተ ክርስቲያን ሰንሰለት ይበልጥ ጠንካራ እንዲሆን ለሐዋርያዊ አገልግሎት በምትጓዙበት ሁሉ በርትታችሁ ልትሠሩ ይገባል" ብለዋል።
ብፁዕነታቸው አክለውም "በማያስፈልገው መልኩ የጥንቱን እውቀታችሁን አታዘምኑት" የአባቶቻችን ትርጓሜም ወደ ቀጣይ ትውልድ ተጠብቆ እንዲተላለፍ ተግታችሁ ሥሩ ፣ ከእውቀት ባሻገር ለመንፈሳዊነትም ልዩ ትኩረት እንድትሰጡ ደግሞም የምታስተምሩትን በተግባር መኖር ከተመራቂ ደቀመዛሙርት እንደሚጠበቅ አመላክተዋል።
ብፁዕ አቡነ ኤልያስ በበኩላቸው ተመራቂ ደቀመዛሙርት ለፍሬ እንዲበቁ ምኞታቸውን በመግለፅ ሊቃውንት በዚህ መልኩ መመረቃቸው ጥንት ያልነበረ አሁን ግን የተለመደ ታላቅ ተግባር ነውና "ትልቅ ዕድል" ነው ብለዋል። | 6 257 |
| 20 | የዲላ ማእከል ለ7ኛ ዙር ያሠለጠናቸውን 63 የበገና ሠልጣኞች አስመረቀ።
ሰኔ ፳፱/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የዲላ ማእከል ለ7ኛ ዙር ያሠለጠናቸውን 63 የበገና ሠልጣኞች ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም አባቶች ካህናት፣የተመራቂ ቤተሰቦች እና የዲላ ማእከል አባላት በተገኙበት አስመርቋል ።
በዕለቱ መዝሙርና ትምህርተ ወንጌል የቀረበ ሲሆን መ/ር ታሪኩ ወንድማገኝ በማኅበረ ቅዱሳነን የዲላ ማእከል ሰብሳቢ ላለፉት ስድስት ወራት የበገና ሥልጠና ሲወስዱ ለነበሩ ተመራቂዎች እና የተመራቂ ቤተሰቦች የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈው ተመራቂዎች እግዚአብሔርን በበገና ከማመስገን ባሻገር በሕይወታቸው መልካም ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባር ሊኖራቸው ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
በመርሐ ግብሩ የተገኙት የቅ/ኡራኤል ቤተ ክርስቲያን አገልጋይና የማእከሉ አባል ቀሲስ ተቋም
የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈው ተማሪዎች አልባሌ ቦታ ከመዋል ይልቅ እግዚአብሔርን ለማመስገን በተመረጠ ቦታ መገኘታቸው መልካም ነው ብለዋል።
በተጨማሪ ይህ ዝማሪ መንፈሳዊ በረከት ያለው በመሆኑ ለሌሎች አርአያ በመሆን በመንፈሳዊ ሥነ ምግባር ልትኖሩ ይገባል በማለት ገልጸዋል።
በተመሳሳይ በደሴ ማእከል ለ4ኛ ዙር ያሠለጠናቸውን 38 በገና ደርዳሪዎችን በበደሌ ደ/ሣህል መድኃኔዓለም ካቴድራል አስመርቋል። | 5 804 |
