ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል
📈 Análisis del canal de Telegram ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል
El canal ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል (@mkpublicrelation) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 50 677 suscriptores, ocupando la posición 1 100 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 629 en la región Etiopía.
📊 Métricas de audiencia y dinámica
Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 50 677 suscriptores.
Según los últimos datos del 11 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 723, y en las últimas 24 horas de 30, conservando un alto alcance.
- Estado de verificación: No verificado
- Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 15.95%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 10.00% de reacciones respecto al total de suscriptores.
- Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 8 083 visualizaciones. En el primer día suele acumular 5 070 visualizaciones.
- Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 61.
📝 Descripción y política de contenido
No se ha proporcionado la descripción del canal.
Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 12 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.
Carga de datos en curso...
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 12 junio | +23 | |||
| 11 junio | +31 | |||
| 10 junio | +32 | |||
| 09 junio | +15 | |||
| 08 junio | +15 | |||
| 07 junio | +15 | |||
| 06 junio | +33 | |||
| 05 junio | +17 | |||
| 04 junio | +14 | |||
| 03 junio | +21 | |||
| 02 junio | +24 | |||
| 01 junio | +17 |
| 2 | በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት አባታዊ መልእክት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በተከሰተው ችግር ጥልቅ ኃዘን የተሰማት መሆኑን ገልጸው ምእመናን በሃይማኖታቸው እንዲጸኑ፣በፈተና ሁሉ እንዲታገሱ አደራ ካሉ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ ኃዘንተኞችን እንዲያጽናና ከዳግም ኃዘን እንዲሰውርልን ዘወትር እንጸልያለን በማለት ቃለ ምዕዳንና ቃለ ቡራኬ ሰጥተዋል።
በመጨረሻም ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ለተፈናቀሉ ወገኖች የተዘጋጀውን እርዳታ ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ለብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ አስረክበዋል።
በዕለቱ የአቦምሳ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎችና አባ ገዳዎች ተገኝተዋል።
መረጃው የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው። | 4 056 |
| 3 | በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ ልዑክ አርሲ-አቦምሳ ወረዳ ተገኝቶ ምዕመናንን አጽናና።
ሰኔ ፬/፳፻፲፰ ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የተካሄደውን ጥቃት ተከትሎ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተ ክርስቲያናችን ልዑክ በሥፍራው በመገኘት ተጎጂዎችን እንዲያጽናና ጊዜያዊ እርዳታም እንዲያደርግ ያስተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ዛሬ ማለዳ ወደ አርሲ ዞን አቦምሳ ወረዳ በመጓዝ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች አጽናንቷል፤ ጊዜያዊ እርዳታም አበርክቷል።
በአቦምሳ ወረዳ የትንሣኤ ብርሃን ደብረ ገነት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በመገኘት ተጎጂ ኦርቶዶክሳውያንን ያጽናኑት
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት አባታዊ መልእክት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በኦርቶዶክሳውያን ልጆቿ ላይ በደረሰው ጉዳት እጅግ በጣም ማዘኗን ገልጸው እግዚአብሔር አምላክ ለሞቱት ወገኖቻችን መንግስተ ሰማያትን እንዲያወርስልን፣ለቤተሰቦቻቸው መጽናናት እንዲያድልልን የዘወትር ጸሎታችን ነው።በርቱ፣ጠንክሩ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን ብለዋል።
አያይዘውም ቋሚ ሲኖዶስ በአካል ተገኝቶ እናንተን ለማጽናናትና ጊዜያዊ ድጋፍ ለማድረግ በመካከላችሁ ተገኝተናል ያሉት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ችግሩን ከመሰረቱ ለመፍታትና የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን ለመሥራት የሚያስችል ዐቢይ ኮሚቴ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ተሰይሞ ወደ ሥራ ገብቷል ብለዋል። | 3 943 |
| 4 | ✝️የጾም ቁርሳችን፣
ለወገኖቻችን✝️ +++
በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች እያጋጠሙ ባሉ ማኅበራዊ ቀውሶች( ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች፣ መፈናቀልና ጦርነት ) ብዙ ወገኖቻችን ለከፋ ችግር ተጋልጠዋል።
እርስዎም ለእነዚህ ወገኖች የጾም ቁርስዎን በመለገስ ቸርነትን ያድርጉ!
ድጋፍ ለማድረግ :-
#በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
1. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
2. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
3. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
4. በወጋገን ባንክ - 0837331610101
5. በወገን ፈንድ ፡- https://Www.wegenfund.com/mknu መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት | 4 228 |
| 5 | Sin texto... | 4 783 |
| 6 | በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል 29 ለሚሆኑ የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች የዲቁና ማዕረግ ማሰጠቱን ገለጸ
ሰኔ ፬/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ዋና ክፍል የአብነት ትምህርት ሲያስተምራቸው የነበሩ ከ10 ግቢ ጉባኤያት ለተውጣጡ ተማሪዎች ኅዳር 3/2018 ዓ.ም የካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ከብፁዕ አቡነ መቃርዮስ ዲቁና መቀበላቸውን የአዲስ አበባ ማእከል ግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ዋና ክፍል የትምህርት፣ አብነትና አቅም ማጎልበቻ ክፍል ኃላፊ ወ/ሪት አበባ አማረ ገልጸዋል።
ተማሪዎቹ ከዘመናዊ ትምህርት ጎን ለጎን የአብነት ትምህርትን ሲማሩ የቆዩ ሲሆን በክህነት አገልግሎት እንዲሳተፉ ለማድረግ እና ዘመኑን የዋጁ ካህናትን ለማፍራት ተማሪዎችን የዲቁና ማዕረገ ክህነት እንዲቀበሉ አድርጓል፡፡
በዕለቱም ብፁዕ አቡነ መቃርዮስ ዲያቆና የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሥርዓት ጠብቀው፣ ቤተ ክርስቲያን ያለባትን ችግር በመረዳትና ማኅበሩ ያመቻቸላችሁን እድል ልታመሰግኑ ይገባል በማለት የተናገሩ ሲሆን ለወደፊት ቤተ ክርስቲያንን በቅንነት ማገልገል አለባችሁ በማለት የአደራ ቃላቸውን ሰጥተዋል።
የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች የአብነት ት/ት እንዲማሩ እና ክህነት እንዲቀበሉ መደረጉ ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሚማሩ ተማሪዎች ቤተ ክርስቲያንን እና ሀገራቸውን በአርአያነት በማገልገል ክርስቲያናዊ የዜግነት ግዴታቸውን እንዲወጡ ያስችላል ተብሏል፡፡
መረጃው የማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ሚዲያ ነው። | 1 588 |
| 7 | የዲያቆናት ጉባኤ በአትላንታ ጆርጂያ ተካሄደ
ሰኔ ፫/፳፻፲፰ ዓ.ም
በአትላንታ ከተማ አካባቢ ከሚገኙ ስምንት አብያተ ክርስቲያናት ለተውጣጡ ለ43 ዲያቆናት ለሁለት ቀናት የቆየ ሥልጠና በአትላንታ መካነ ሕይወት አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ቤተ ክርስቲያን አዳራሽ ተካሄዷል።
ሥልጠናው በቀሲስ ዶክተር መብራቱ ኪሮስ የተሰጠ ሲሆን ኦርቶዶክሳዊ ቅዳሴ ከሌሎች የሚለይበት፣ ያለውን ክብር እና ዋጋ በስፋት የተዳሰሰበትና እንደ አገልጋይ ዲያቆን በዚህ የቅዳሴ አገልግሎት ውስጥ የሚፈጸሙ ምስጢራትን ከሚዜመው ዜማና ከሚደረጉት ኩነቶች ጋር እያገናዘቡና እያስማሙ መስጠታቸው ተገልጿል።
በሥልጠናው የቅዳሴ ክፍሎችን እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን የልጅነት ጥምቀት ቢፈጸም፣ ሥርዓተ ተክሊል ቢደረግ፣ምሥጢረ ንስሐ ሲፈጸምና ምሥጢረ ክህነት ሲከናወን ማሰርያና መደምደሚያ የሆነው በዚህ የቅዳሴ አገልግሎት የሚፈጸመው ቅዱስ ቁርባን እንደሆነ በሰፊው ያብራሩ ሲሆን ሠልጣኝ ዲያቆናትም ይህንን በመረዳት ለክህነታቸው ከፍተኛ ክብር እንዲሰጡና እንዲጠብቁት በጸሎት፣ እግዚአብሔርን በመፍራት፣ በትሕትና ሆነው አገልግሎቱን እንዲፈጽሙ አስፍተው አስተምረዋል።
በጉባኤው የውይይት፣ የጥያቄና መልስ መርሐ ግብር የተከናወነ ሲሆን በዚህም በሥልጠናው የተሳተፉ ሠልጣኝ ዲያቆናትም በመርሐ ግብሩ ብዙ ቁም ነገሮችን እንደተረዱና የተቀበሉትም ክህነት የከበረ ዋጋ ያለው መሆኑን ከሰጡት አስተያየት ለመረዳት ተችሏል።
ዘገባው የአትላንታ ንኡስ ማእከል ሚድያ ክፍል ነው። | 6 587 |
| 8 | በማኅበረ ቅዱሳን የጅማ ማእከል ዝክረ ቅዱስ ያሬድ መርሐ ግብር አከናወነ
ሰኔ ፫/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን የጅማ ማእከል "ሕያው ዜማከ ወሕያው ድርሳንከ (ዜማህ ሕያው ነው ድርሰትህም ሕያው ነው)" በሚል መሪ ቃል የዝክረ ቅዱስ ያሬድ መርሐ ግብር አከናውኗል።
በመርሐ ግብሩም በቅዱስ ያሬድና አበርክቶው ዙሪያ በመ/ር ጌቱ ምትኩ ትምህርት የተሰጠ ሲሆን፤ ሥነ-ጽሑፍና ዝማሬ በማእከሉ መዘምራን፤ የበገና መዝሙር በተመራቂዎች፤ እንዲሁም በወቅታዊ የኦርቶዶክሳዊ መዝሙር አገልግሎት በጎ እድሎች፣ ተግዳሮቶችና የመፍትሔ ሐሳቦች ዙሪያ ዳሰሳዊ ጥናት ቀርቧል።
በማያያዝ በዕለቱ የበገና ሠልጣኞቹንም ለ5ኛ ዙር አስመርቋል።
ማእከሉ ባለፉት ዓመታት ከ120 በላይ ሠልጣኞችን ያስመረቀ ሲሆን በዘንድሮ በጅማ ከተማ ለ5ኛ ዙር እና በሊሙ ገነት ወረዳ ማእከል ለ1ኛ ዙር አሠልጥኖ ማስመረቁም ተገልጿል። | 6 043 |
| 9 | ✝️የጾም ቁርሳችን፣
ለወገኖቻችን✝️ +++
በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች እያጋጠሙ ባሉ ማኅበራዊ ቀውሶች( ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች፣ መፈናቀልና ጦርነት ) ብዙ ወገኖቻችን ለከፋ ችግር ተጋልጠዋል።
እርስዎም ለእነዚህ ወገኖች የጾም ቁርስዎን በመለገስ ቸርነትን ያድርጉ!
ድጋፍ ለማድረግ :-
#በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
1. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
2. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
3. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
4. በወጋገን ባንክ - 0837331610101
5. በአዋሽ ባንክ 01329817420400
6. በወገን ፈንድ ፡- https://Www.wegenfund.com/mknu መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ለበለጠ መረጃ
09 43 00 04 03
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት | 6 547 |
| 10 | ብሔራዊ ፈተና ለሚወስዱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሥነ ልቡና ሥልጠና ተሰጠ
ሰኔ ፪/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል የደቡብ ማስተባበሪያ ሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ አገልግሎት ክፍል ከአምስት ግንኙነት ማእከላት ጋር በመተባበር የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለሚወስዱ ተፈታኝ ተማሪዎች ሥልጠና መሰጠቱን ማስተባበሪያው አስታውቋል።
በዕለቱም በቀሲስ ኃይለ መስቀል አማካኝነት የሥነ-ልቡና ሥልጠና የተሰጠ ሲሆን በሥልጠናው ተማሪዎች ከፈተና በፊት፣ በፈተና ጊዜ እንዲሁም ከፈተና በኋላ ማድረግ ስላለባቸው ዝግጅት ሰፊ ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን ተማሪዎች ለፈተና ሲቀርቡ በተረጋጋ መንፈስ፣ በልበ ሙሉነት መሆን እንዳለበት ተመላክቷል ።
በመጨረሻም ተማሪዎች የቤተ ክርስቲያን ተረካቢ እና ተስፋዎች መሆናቸውን አውቀው በትምህርታቸው ውጤታማ እንዲሆኑ በማሳሰብ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል ።
መረጃው ፦በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ሚዲያ ነው | 6 037 |
| 11 | ብሔራዊ ፈተና ለሚወስዱ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የሥነ ልቡና ሥልጠና ተሰጠ
ሰኔ ፪/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል የደቡብ ማስተባበሪያ ሕዝብ ግንኙነትና ሚዲያ አገልግሎት ክፍል ከአምስት ግንኙነት ማእከላት ጋር በመተባበር የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለሚወስዱ ተፈታኝ ተማሪዎች ሥልጠና መሰጠቱን ማስተባበሪያው አስታውቋል።
በዕለቱም በቀሲስ ኃይለ መስቀል አማካኝነት የሥነ-ልቡና ሥልጠና የተሰጠ ሲሆን በሥልጠናው ተማሪዎች ከፈተና በፊት፣ በፈተና ጊዜ እንዲሁም ከፈተና በኋላ ማድረግ ስላለባቸው ዝግጅት ሰፊ ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን ተማሪዎች ለፈተና ሲቀርቡ በተረጋጋ መንፈስ፣ በልበ ሙሉነት መሆን እንዳለበት ተመላክቷል ።
በመጨረሻም ተማሪዎች የቤተ ክርስቲያን ተረካቢ እና ተስፋዎች መሆናቸውን አውቀው በትምህርታቸው ውጤታማ እንዲሆኑ በማሳሰብ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል ።
መረጃው ፦በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ሚዲያ ነው | 1 |
| 12 | ✝️የጾም ቁርሳችን፣
ለወገኖቻችን✝️ +++
በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች እያጋጠሙ ባሉ ማኅበራዊ ቀውሶች( ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች፣ መፈናቀልና ጦርነት ) ብዙ ወገኖቻችን ለከፋ ችግር ተጋልጠዋል።
እርስዎም ለእነዚህ ወገኖች የጾም ቁርስዎን በመለገስ ቸርነትን ያድርጉ!
ድጋፍ ለማድረግ :-
#በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡-
1. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901
2. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458
3. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648
4. በወጋገን ባንክ - 0837331610101
5. በአዋሽ ባንክ 01329817420400
6. በወገን ፈንድ ፡- https://Www.wegenfund.com/mknu መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ለበለጠ መረጃ
09 43 00 04 03
የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት | 9 798 |
| 13 | የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለሚወስዱ ተማሪዎች የሥነ ልቡና ዝግጅት ሥልጠና መሰጠቱ ተገለጸ
ሰኔ ፩/፳፻፲፰ ዓ.ም
በማኅበረ ቅዱሳን ሥር የሚገኙ ማእከላትና ወረዳ ማእከላት ከሰንበት ትምህርት ቤቶች ጋር በመተባበር የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ለሚወስዱ ተማሪዎች የሥነ ልቡና ዝግጅት ሥልጠና መሰጠቱ ተገልጿል።
ሥልጠናው ተማሪዎች የሚፈተኑትን ብሔራዊ ፈተና በልበ ሙሉነት፣ በተረጋጋ መንፈስ፣ በሥነ-ልቡና ዝግጁነት መወጣት እንዲችሉ እና መንፈሳዊ ጥንካሬን እንዲሰንቁ እንዲሁም ተማሪዎች በፈተና ወቅት የሚመጣን ጭንቀት ተቋቁመው ማለፍ እንዲችሉና በአግባቡ ጊዜያቸውን መጠቀም እንዲችሉ ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑ ተጠቁሟል።
በዚህም በጅማ፣ በአርባ ምንጭ፣ በሐረማያ፣ በዱራሜ፣ በሑመራ፣ በሰቆጣ፣ በደሴ፣ በቦንጋና በሌሎች ማእከላት እንዲሁም በወረዳ ማእከላት ሥልጠናው ተሰጥቷል። | 7 555 |
| 14 | Sin texto... | 7 037 |
| 15 | Sin texto... | 7 229 |
| 16 | የምሥራቅ አርሲ ጥቃትና የፍትሕ ጥያቄ | እውነታውና የንጹሐን ድምፅ!
የቪዲዮውን ሊንክ በመጫን ሙሉ ታሪኩን አሁኑኑ ይመልከቱ፦
https://youtu.be/BChuKE7nWSg
ላይክ (Like) በማድረግ ይደግፉን፣
ለሌሎችም እንዲደርስና ግንዛቤ እንዲፈጠር ሼር (Share) ያድርጉት፣
ያላችሁን ማንኛውንም አስተያየት በኮሜንት (Comment) ያጋሩን።
አብራችሁን ስላላችሁ ከልብ እናመሰግናለን! | 11 701 |
| 17 | "የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሐዋርየዊ ተልእኮና ዓላማ ለማሳካት አገልግሎትን በዕቅድ መፈጸም ይገባል" ሲሉ መምህር ዋሲሁን በላይ ገለጹ
ግንቦት ፴/፳፻፲፰ ዓ.ም
የአኃት አብያተ ክርክቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት ተካሄዷል።
በጉባኤው የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ሥራ አስፈጻሚ መ/ር ዋሲሁን በላይ የእንኳን ደኅና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በንግግራቸው በየትኛውም የቤተ ክርስቲያን መዋቅርና ማኅበራችንን ጨምሮ አገልግሎትን በዕቅድ መፈጸም የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዓላማን ለማሳካት ወሳኝ ገዳዮች መካከል አኔዱ ነው ብለዋል፡፡
በተለይም ከዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ ከአኃት አብያተ ክርስቲያናት የምንማራቸው ትምህርቶች አሉ ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው አክለውም የቤተ ክርስቲያናችን መሪ ዕቅድ ተግባራዊ እንዲሆን የሁሉ አካላት ጥረት እጅግ አስፈላጊ ነው ብለዋል።
በውይይቱ ሦስት ጥናታዊ ጽሑፎች የቀረቡ ሲሆን የአኃት አብያተ ክርስቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ በመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል በመንበረ ፓትርያሪክ ጥናት፣ ምርምርና መረጃ መምሪያ ኃላፊ እና የቅ/ሲኖዶስ ኮምዪኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ እንዲሁም የሊቃውንት ጉባኤ አባል የቀረበ ሲሆን በ መ/ር ባሕረ ጥበባት ሙጨ የኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት፣ ትግበራ፣ ክትትልና ግምገማ ከትናንት እስከ ዛሬ እንዲሁም በማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር በሪሁን ተፈራ የቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት ትግበራና የማኅበረ ቅዱሳን ድርሻ ላይ ያተኮረ ጥናት ቀርቦ በቀረቡት ጽሑፎች ላይ ውይይት ተደርጓል። | 8 684 |
| 18 | "የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሐዋርየዊ ተልእኮና ዓላማ ለማሳካት አገልግሎትን በዕቅድ መፈጸም ይገባል" ሲሉ መምህር ዋሲሁን በላይ ገለጹ
ግንቦት ፴/፳፻፲፰ ዓ.ም
የአኃት አብያተ ክርክቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት ተካሄዷል።
በጉባኤው የማኅበረ ቅዱሳን ዋና ሥራ አስፈጻሚ መ/ር ዋሲሁን በላይ የእንኳን ደኅና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በንግግራቸው በየትኛውም የቤተ ክርስቲያን መዋቅርና ማኅበራችንን ጨምሮ አገልግሎትን በዕቅድ መፈጸም የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዓላማን ለማሳካት ወሳኝ ገዳዮች መካከል አኔዱ ነው ብለዋል፡፡
በተለይም ከዕቅድ አፈጻጸም ዙሪያ ከአኃት አብያተ ክርስቲያናት የምንማራቸው ትምህርቶች አሉ ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው አክለውም የቤተ ክርስቲያናችን መሪ ዕቅድ ተግባራዊ እንዲሆን የሁሉ አካላት ጥረት እጅግ አስፈላጊ ነው ብለዋል።
በውይይቱ ሦስት ጥናታዊ ጽሑፎች የቀረቡ ሲሆን የአኃት አብያተ ክርስቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ በመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል በመንበረ ፓትርያሪክ ጥናት፣ ምርምርና መረጃ መምሪያ ኃላፊ እና የቅ/ሲኖዶስ ኮምዪኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊ እንዲሁም የሊቃውንት ጉባኤ አባል የቀረበ ሲሆን በ መ/ር ባሕረ ጥበባት ሙጨ የኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት፣ ትግበራ፣ ክትትልና ግምገማ ከትናንት እስከ ዛሬ እንዲሁም በማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር በሪሁን ተፈራ የቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት ትግበራና የማኅበረ ቅዱሳን ድርሻ ላይ ያተኮረ ጥናት ቀርቦ በቀረቡት ጽሑፎች ላይ ውይይት ተደርጓል። | 1 |
| 19 | የልህቀት ማእከሉ የስትራክቸር ሥራ መገባደዱን አስመልክቶ የተከናወነው የምስጋና መርሐ ግብር ተጠናቀቀ
ግንቦት ፳፱/፳፻፲፰ ዓ.ም
በጉባኤው የሥራ አስፈጻሚ ጉባኤ አባላት፣ የማኅበሩ አባላትና ምእመናን ተሳትፈዋል።
በምስጋና መርሐ ግብሩ የማኅበረ ቅዱሳን የልህቀት ማእከልን የተመለከተ ዶክመንተሪ የቀረበ ሲሆን ልህቀት ማእከሉን ግንባታ አስመልክቶ አጠቃላይ ሪፖርት በዲ/ን ኢ/ር ፍሬ ሰንበት አስቻለኝ ቀርቧል።
በተጨማሪም ከተሳታፊዎች ሀሳብ ቀርቦ ለግንባታው መገባደድ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረከቱ አካላት የምስጋና ሰርተፍኬት ተበርክቷል። | 10 298 |
| 20 | በመጨረሻም ዋና ሥራ አስፈጻሚው የመጀመሪያ ዙር የውጭ ፊኒሺንግ ሥራዎች በቅርቡ እንደሚጀመር ገልጸው የዓይነትና የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ ከምንጊዜውም በላይ ከጎናችን እንድትቆሙ በማለት የአደራ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
በጉባኤው መዝሙር የቀረበ ሲሆን ትምህርተ ወንጌል እየተሰጠ ይገኛል። | 7 943 |
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
