es
Feedback
ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

Ir al canal en Telegram

በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

El canal ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (@beteafework) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 55 943 suscriptores, ocupando la posición 916 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 588 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 55 943 suscriptores.

Según los últimos datos del 19 septiembre, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 686, y en las últimas 24 horas de 43, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 17.17%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 7.98% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 9 602 visualizaciones. En el primer día suele acumular 4 466 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 114.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 20 septiembre, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

55 943
Suscriptores
+4324 horas
+2507 días
+68630 días

Carga de datos en curso...

Nube de Etiquetas
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
septiembre '26
septiembre '26
+530
en 33 canales
agosto '26
+813
en 42 canales
Get PRO
julio '26
+737
en 31 canales
Get PRO
junio '26
+809
en 31 canales
Get PRO
mayo '26
+1 053
en 47 canales
Get PRO
abril '26
+1 078
en 70 canales
Get PRO
marzo '26
+664
en 44 canales
Get PRO
febrero '26
+1 024
en 55 canales
Get PRO
enero '26
+584
en 42 canales
Get PRO
diciembre '25
+850
en 42 canales
Get PRO
noviembre '25
+706
en 59 canales
Get PRO
octubre '25
+669
en 64 canales
Get PRO
septiembre '25
+395
en 61 canales
Get PRO
agosto '25
+676
en 49 canales
Get PRO
julio '25
+724
en 68 canales
Get PRO
junio '25
+433
en 39 canales
Get PRO
mayo '25
+523
en 12 canales
Get PRO
abril '25
+1 215
en 59 canales
Get PRO
marzo '25
+1 654
en 82 canales
Get PRO
febrero '25
+1 022
en 38 canales
Get PRO
enero '25
+2 106
en 70 canales
Get PRO
diciembre '24
+2 118
en 57 canales
Get PRO
noviembre '24
+2 209
en 74 canales
Get PRO
octubre '24
+1 841
en 92 canales
Get PRO
septiembre '24
+1 381
en 89 canales
Get PRO
agosto '24
+1 550
en 51 canales
Get PRO
julio '24
+475
en 15 canales
Get PRO
junio '24
+517
en 18 canales
Get PRO
mayo '24
+989
en 26 canales
Get PRO
abril '24
+875
en 26 canales
Get PRO
marzo '24
+998
en 20 canales
Get PRO
febrero '24
+335
en 14 canales
Get PRO
enero '24
+422
en 12 canales
Get PRO
diciembre '23
+326
en 19 canales
Get PRO
noviembre '23
+282
en 11 canales
Get PRO
octubre '23
+148
en 5 canales
Get PRO
septiembre '23
+172
en 0 canales
Get PRO
agosto '23
+174
en 0 canales
Get PRO
julio '23
+498
en 0 canales
Get PRO
junio '23
+525
en 0 canales
Get PRO
mayo '23
+546
en 0 canales
Get PRO
abril '23
+617
en 0 canales
Get PRO
marzo '23
+367
en 0 canales
Get PRO
febrero '23
+500
en 0 canales
Get PRO
enero '23
+504
en 0 canales
Get PRO
diciembre '22
+307
en 0 canales
Get PRO
noviembre '22
+286
en 0 canales
Get PRO
octubre '22
+296
en 0 canales
Get PRO
septiembre '22
+440
en 0 canales
Get PRO
agosto '22
+380
en 0 canales
Get PRO
julio '22
+680
en 0 canales
Get PRO
junio '22
+378
en 0 canales
Get PRO
mayo '22
+443
en 0 canales
Get PRO
abril '22
+514
en 0 canales
Get PRO
marzo '22
+395
en 0 canales
Get PRO
febrero '22
+245
en 0 canales
Get PRO
enero '22
+222
en 0 canales
Get PRO
diciembre '21
+203
en 0 canales
Get PRO
noviembre '21
+254
en 0 canales
Get PRO
octubre '21
+390
en 0 canales
Get PRO
septiembre '21
+409
en 0 canales
Get PRO
agosto '21
+461
en 0 canales
Get PRO
julio '21
+594
en 0 canales
Get PRO
junio '21
+684
en 0 canales
Get PRO
mayo '21
+622
en 0 canales
Get PRO
abril '21
+789
en 0 canales
Get PRO
marzo '21
+719
en 0 canales
Get PRO
febrero '21
+539
en 0 canales
Get PRO
enero '21
+505
en 0 canales
Get PRO
diciembre '20
+19 882
en 0 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
20 septiembre+11
19 septiembre+43
18 septiembre+25
17 septiembre+28
16 septiembre+24
15 septiembre+102
14 septiembre+14
13 septiembre+34
12 septiembre+16
11 septiembre+32
10 septiembre+19
09 septiembre+18
08 septiembre+16
07 septiembre+27
06 septiembre+21
05 septiembre+14
04 septiembre+30
03 septiembre+24
02 septiembre+18
01 septiembre+14
Publicaciones del Canal
ወንድሞቼ ሆይ! ቃሉን ስታነቡ ዝም ብላችሁ ቃላትን ለመቁጠር ብቻ አይሁን። ነገር ግን በቃሉ ውስጥ ያለውን መንፈሳዊ ጣዕም ለማግኘት ጸልዩ። የምታነቡትን በተግባር ለመተርጎም ትጉ። 'ቃሉን የሚሰሙ ብቻ ሳይሆኑ የሚያደርጉት ይጸድቃሉ' ተብሏልና። አንድ ምዕራፍ እንኳ ብታነቡ ያቺ ለአንድ ቀን ስንቅ ትሆናችኋለች። ንስሐ የገባ ሰው ልቡ በቃለ እግዚአብሔር ካልታጠበ ዳግመኛ ወደ ኃጢአት ጭቃ መመለሱ አይቀርም። ቃሉ ግን ልባችሁን ይጠብቃል፤ አእምሮአችሁንም ያበራል። ሰዎች ሆይ! መጻሕፍትን አትናቁ። እነርሱ ከሰማይ ወደ እኛ የተላኩ ደብዳቤዎች ናቸው። የሰማዩ ንጉሥ የላከልህን ደብዳቤ ችላ ብለህ እንዴት ሰላምን ታገኛለህ? በመጻሕፍት ውስጥ የታመሙት ፈውስን፣ ያዘኑት መጽናናትን፣ የወደቁት መነሳትን፣ ንስሐ የገቡት ደግሞ የተስፋን ብርሃን ያገኛሉ። በቃለ እግዚአብሔር የምትታጠብ ነፍስ ዘወትር ለምለም ትሆናለች። ስለዚህ በቤታችሁ መጻሕፍትን ለማንበብ ጊዜ መድቡ። ልጆቻችሁንም በቃለ እግዚአብሔር ኮትኩቱ። ዓለማዊ እውቀት ለሥጋዊ ሕይወት ይጠቅም ይሆናል፤ መንፈሳዊ እውቀት ግን ለዘላለም ሕይወት ያበቃል። ንስሐችሁ ፍጹም ይሆን ዘንድ፣ ሕሊናችሁም ከክፉ ሐሳብ ይነጻ ዘንድ ዘወትር በመለኮታዊ መጻሕፍት ንባብ ተጉ። እግዚአብሔር ቃሉን በልባችን ይጻፍልን።" (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ንስሐ ባስተማረበት ድርሳኑ)

2
“በአውሎ ነፋስ መካከል ብትሆን እንኳ አትፍራ፤ መርከቧን የሚመራት ክርስቶስ እስካለ ድረስ ማዕበሉ አያሰምጥህም፤ እግዚአብሔር ፈተናውን ባያርቀው እንኳ ፈተናውን የምትችልበትን ኃይል ይሰጥሃል።’’ ሊቁ አውግስጢኖስ
4 546
3
#የሐዲስ_ኪዳን_መምህሩን_ሕይወት_እንታደግ በሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ትርጓሜ በርካታ ደቀ መዛሙርትን እያነፁ የሚገኙት መምህር ቀለመወርቅ አመሃ ዛሬ የእኛን የደግነት እጅ መዘርጋት የሚሻ ከባድ የልብ ሕመም ገጥሟቸዋል። በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ጉባላፍቶ ወረዳ በድጎ ደብረ ኢየሱስ አዳሪ ትምህርት ቤት ለ5 ዓመታት ተምረው ከተመረቁ በኋላ፣ በጉባላፍቶ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜን ወንበር  ዘርግተው በማስተማር ላይ ይገኛሉ። አሁን ላይ መምህሩ በገጠማቸው የልብ ሕመም ምክንያት በወልድያ ሆስፒታል ቢታከሙም ከአቅም በላይ በመሆኑ ወደ አዲስ አበባ ለከፍተኛ የልብ ሕክምና ተልከዋል። ሕይወታቸውንም ለማዳን ለሚደረገውን አስቸኳይ የልብ ቀዶ ጥገና ከ300,000 (ሦስት መቶ ሺህ) ብር በላይ ያስፈልጋቸዋል። ሰውን ለማዳን ሰው መሆን በቂ ነውና መምህሩ እንደገና ወደ ወንበራቸው ተመልሰው ደቀመዛሙርትን ማፍራት እንዲችሉ፣ በሀገር ውስጥና በውጭ የምትገኙ ኦርቶዶክሳውያንና ደግ አሳቢዎች በሙሉ የቻላችሁትን በሚከተለው አካውንት ድጋፍ ታደርጉ ዘንድ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም እንጠይቃለን።              #በኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ      ለመምህር ቀለመወርቅ አመሃ በላይ               1000513559821 #ለበለጠ_መረጃ፦ ➛ መምህር ቀለመወርቅ - +251920120104 ሼር በማድርግ ይተባበሩ
4 526
4
ንስሐና ምጽዋት የነፍስ ሁለት ዓይኖች ናቸው። አንዱ ቢጠፋ ሌላኛው ብቻውን ሙሉ እይታ አይሰጠውም። ኃጢአትህ እንዲፋቅልህ ትፈልጋለህን? እንኪያስ የምሕረት በርን በምጽዋት አንኳኳ። 'የሚምሩ ብፁዓን ናቸው፤ ምሕረትን ያገኛሉና' ተብሏል። አንተ ለባልንጀራህ ካልራራህ እግዚአብሔር እንዲራራልህ እንዴት ትጠይቃለህ? ምጽዋት ሰጪውን ከኃጢአት እስራት ትፈታዋለች፤ ተቀባዩንም ከችግር ታሳርፈዋለች። ወንድሞቼ ሆይ! አትሳሳቱ፤ ገንዘባችሁ እዚህ ምድር ላይ ይቀራል። ይዛችሁት የምትሄዱት ምጽዋታችሁን ብቻ ነው። በሕይወት እያላችሁ ለነፍሳችሁ ስንቅ አዘጋጁ። ድሆች የእግዚአብሔር መሠዊያዎች ናቸው። በቤተክርስቲያን ያለውን መሠዊያ እንደምታከብሩ ሁሉ፣ እነዚህን ሕያው መሠዊያዎች (ድሆችን) አክብሩ። በድሃው እጅ ላይ የምታስቀምጠው ስጦታ በቀጥታ ወደ እግዚአብሔር እጅ ይደርሳል። ስለዚህ ንስሐችሁ ፍሬ እንዲያፈራ፣ ጸሎታችሁም እንዲሰማ ዘወትር በምጽዋት ትጉ።" ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ንስሐ ባስተማረበት ድርሳኑ)
6 068
5
"ኃጢአት ሲሠራ ባየኸው ወንድምህ ላይ አትፍረድ፥ አንተ ግልጽ የወጣ ኃጢአቱን እንጅ በስውር ለካህን የሚነግረውን ንስሐ አታውቅምና። ስለዚህ የራስህን ድካም ተመልከት።" ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ
6 236
6
#የሐዲስ_ኪዳን_መምህሩን_ሕይወት_እንታደግ በሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ትርጓሜ በርካታ ደቀ መዛሙርትን እያነፁ የሚገኙት መምህር ቀለመወርቅ አመሃ ዛሬ የእኛን የደግነት እጅ መዘርጋት የሚሻ ከባድ የልብ ሕ+2
#የሐዲስ_ኪዳን_መምህሩን_ሕይወት_እንታደግ በሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት ትርጓሜ በርካታ ደቀ መዛሙርትን እያነፁ የሚገኙት መምህር ቀለመወርቅ አመሃ ዛሬ የእኛን የደግነት እጅ መዘርጋት የሚሻ ከባድ የልብ ሕመም ገጥሟቸዋል። በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ጉባላፍቶ ወረዳ በድጎ ደብረ ኢየሱስ አዳሪ ትምህርት ቤት ለ5 ዓመታት ተምረው ከተመረቁ በኋላ፣ በጉባላፍቶ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን የሐዲስ ኪዳን ትርጓሜን ወንበር ዘርግተው በማስተማር ላይ ይገኛሉ። አሁን ላይ መምህሩ በገጠማቸው የልብ ሕመም ምክንያት በወልድያ ሆስፒታል ቢታከሙም ከአቅም በላይ በመሆኑ ወደ አዲስ አበባ ለከፍተኛ የልብ ሕክምና ተልከዋል። ሕይወታቸውንም ለማዳን ለሚደረገውን አስቸኳይ የልብ ቀዶ ጥገና ከ300,000 (ሦስት መቶ ሺህ) ብር በላይ ያስፈልጋቸዋል። ሰውን ለማዳን ሰው መሆን በቂ ነውና መምህሩ እንደገና ወደ ወንበራቸው ተመልሰው ደቀመዛሙርትን ማፍራት እንዲችሉ፣ በሀገር ውስጥና በውጭ የምትገኙ ኦርቶዶክሳውያንና ደግ አሳቢዎች በሙሉ የቻላችሁትን በሚከተለው አካውንት ድጋፍ ታደርጉ ዘንድ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስም እንጠይቃለን። #በኢትዮጵያ_ንግድ_ባንክ ለመምህር ቀለመወርቅ አመሃ በላይ 1000513559821 #ለበለጠ_መረጃ፦ ➛ መምህር ቀለመወርቅ - +251920120104 ሼር በማድርግ ይተባበሩ
7 253
7
ከእራት በኋላ  ያለው ጊዜ የምስጋና ጊዜ ነው፡፡ ምስጋናን የሚያቀርብ ደግሞ ንቁና የተረጋጋ ይሆናል፡፡ ከእራት በኋላ ወደ ጸሎት እንጂ ወደ መኝታ አንሂድ፡፡ ያለበለዚያ ግን በደመ ነፍስ ከሚመሩት አውሬዎች የበለጠ በደመ ነፍስ የምንመራ እንሆናለን፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
6 848
8
Sin texto...
46
9
ሰይጣን ኃጢአት እንድትሠራ ሲገፋፋህ 'ድፍረትን' ይሰጥሃል። 'እግዚአብሔር መሐሪ ነው፣ አንድ ጊዜ ብትሠራው ምን ይልሃል? ቆይተህ ንስሐ ትገባለህ' እያለ በኃጢአት ላይ እንድትደፋፈር ያደርግሃል። አንተ ተሸንፈህ ኃጢአቱን ከፈጸምክ በኋላ ግን ሰይጣን ስልቱን ይቀይራል። ያን ጊዜ ደግሞ 'እፍረትንና ተስፋ መቁረጥን' ያመጣብሃል። 'እንዲህ ያለ ኃጢአት ሠርተህ እንዴት እግዚአብሔር ፊት ትቆማለህ? አንተ ረክሰሃል፣ ንስሐህ ተቀባይነት የለውም፣ ሞትህም ለገሃነም ነው' እያለ በልብህ ይጮኻል። አንተ ግን የሰይጣንን ተንኮል አሸንፈው። ኃጢአት ልትሠራ ስትል 'እፈር'፤ ንስሐ ልትገባ ስትል ግን 'ደፋር ሁን'። ሰይጣን ግን ኃጢአት ስትሠራ እንድትደፍር፣ ንስሐ ስትገባ ደግሞ እንድታፍር ያደርግሃል። ይህ ትልቅ ስህተት ነው። ኃጢአት ቍስል ነው፣ ንስሐ ግን መድኃኒት ነው። ቍስል ያለው ሰው ቍስሉን ለሐኪም ለማሳየት አያፍርም፤ ካሳየው ይፈወሳል፣ ከሸሸገው ግን ይበሰብሳል። አንተም ኃጢአትህን ለእግዚአብሔር ንገረው፤ እርሱም ይፈውስሃል። (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ንስሐ ባስተማረበት ድርሳኑ)
8 420
10
"የቤተ ክርስቲያን ካህን ለአንተ እንደ መንፈሳዊ አባት ይኹንልህ፡፡ አንድ ሕመምተኛ ስውር በሽታዎቹን በግልፅ ለሐኪም እንደሚያሳይና ከዚያም እንደሚድን ኹሉ፥ አንተም ምሥጢሮችህን ለካህን በግልፅ ንገር፤ [ትድንማለህ]፡፡” (ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ)
8 025
11
"የአባቶቻችን የሐዋርያት ትዕዛዝ ነው፡፡ ሰው በልቦናው ቂምንና በቀልን ቅንዓትንና ጠብን በባልንጀራው ላይ በማንም ላይ ቢሆን አይያዝ፡፡" (ሥርዓተ ቅዳሴ)
8 863
12
አንተ ሰው እስኪ ንገረኝ! በዓይንህ ውስጥ ጉድፍ እንዲገባ የማትፈቅድ ኾነህ ሳለ በነፍስህ ላይ እልፍ ወትእልፊት የጉድፍ ክምሮች እንዲገቡ ቸለል ትላለህን? ታዲያ ዕለት ዕለት በነፍሳችን ብሌን ላይ እያከማቸነው ያለነውን ቆሻሻ የምናጸዳው መቼ ይኾን? እሾኾቹን የምንቆርጣቸው መቼ ይኾን? አረሞችን የምንነቅላቸው መቼ ይኾን? እንግዲህ ወዲህ መከሩ እንደ ቀረበ አታውቅምን? እኛ ግን እርሻችንን እንኳን ገና አላረስንም፣ አላለሰለስንም፡፡ እንግዲህ ገበሬው (የወይኑ ባለቤት) በመጣ ጊዜ ስሕተት ቢያገኝ ምንድን ነው የምንለው? እኮ የምንመልሰው ምን ይኾን? ዘር የሚሰጠንን ሰው አጥተን ነው ብለን ነው የምንለው? በፍጹም! ዘሩ'ማ ዕለት ዕለት እየተዘራ ነው፡፡ እሾኾቹን የሚቆርጥ ሰው አጥተን ነው የምንለው? ኧረ በጭራሽ! ዕለት ዕለት ማጭዱን እንደ ሳልን ነው፡፡ የዚህ ዓለም ሕይወት ውጣ ውረድ ይዞህ ነውን? ለምን ታዲያ ይህ ዓለም በአንተ ዘንድ ስቁል አልኾነም? የተበደረውን ዕጥፍ ሳያደርግ ያንኑ ብቻ መልሶ የሚከፍል እርሱ ክፉ አገልጋይ ከኾነ ይህቺውን ብትኾን የሚያጠፋስ ምን ብለን ነው ልንጠራው የምንችለው? ያ ሰው እጁና እግሩ ታስሮ ጥርስ ማፋጨት ወዳለበት ከተጣለ፥ ሠናያትን ገንዘብ እናደርግ ዘንድ የሚያነሣሡን እልፍ ምክንያቶች እያሉ ወደ ኋላ የምንልና የማንፈቅድ እኛ ታዲያ እንደ ምን ያለ መከራ ይገባን ይኾን? እንዲህ እንዳታደርግ አንተን ለማሳመን የማይበቃው እስኪ የትኛው ነው? የዓለሙን ርኵሰት አላየህምን? የዚህን ዓለም ሕይወት ርግጠኛ ያለመኾን አልተመለከትክምን? የዚህን ዓለም ድካም፣ በዚህ ዓለም ለሚቀር ደመወዝ የሚወጣውን ላብ አላየህምን? እኮ እስኪ ንገረኝ! ምግባር ሲሠራ ላብ ጠብ ርግፍ የሚያደርግ ክፋት ሲሠራ ግን ምንም ምን ድካምና መከራ የሌለው ነውን? በፍጹም! ታዲያ በኹለቱም ዘንድ ውጣ ውረድ ካለው ይህን ያህል ትርፍ ያለውን ለምን አትመርጥም? እንዲያውም አንዳንድ ሠናያት ድካምን የሚጠይቁ አይደሉም፡፡ እስኪ ንገረኝ! የስድብ ቃልን ላለመናገር፣ በባልንጀራህ ላይ ላለመቈጣት፤ ላለመዋሸት፤ ላለመማል የሚፈልግብህ ድካም እንደ ምን ያለ ድካም ነው? ምንም ድካምን አይጠይቅም! ይልቅስ እጅጉን ድካም ያለውና ብዙ የሚያስጨንቀው እነዚህን ለማድረግ ነው፡፡ እንግዲህ እነዚህን እንኳን ላለማድረጋችን ልናቀርበው የምንችል ሰበብ እንደ ምን ያለ ሰበብ እንደ ምን ያለ ምክንያት ይኾን? ከስንፍናችንና ከልል ዘሊልነታችን የተነሣ ድካም የሚጠይቁትንም እንደማንሠራቸው በዚህ ግልፅ ነውና፡፡ ስለዚህ ከዘለዓለም እስከ ዘለዓለም ድረስ ክብርና ኃይል የባሕርይገንዘቡ በሚኾን በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቸርነቱና ሰውን መውደዱ በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ለዚህ የበቃን እንኾን ዘንድ ይህን ኹሉ ልብ ብለን አስተውለን፥ ከክፉ እንሽሽ፤ ሠናያትንም እንምረጥ፡፡ አሜን! (የማቴዎስ ወንጌል ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንደተረጎመው ቅጽ 2 ድርሳን 42 ገጽ 368-370 ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው)
9 829
13
https://youtu.be/r-KCP5LG7dY?si=_6CbOkHlM07uX-xP
7 573
14
ሁለቱን ሐሳቦች ተረዷቸውና ተጠንቀቋቸው አንደኛው "አንተ ቅዱስ ነህ" የሚለው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ "መቼም ቢሆን ልትድን አትችልም" የሚለው ነው፡፡ ሁለቱም ሐሳቦች ከጠላት ናቸው፤ በትዕቢትና ተስፋ በመቁረጥ የተሞሉ እውነት የሌላቸው ናቸው፡፡ አንተ ግን ለራስህ ይህን በለው "እኔ ታላቅ ኃጢአተኛ ነኝ ሥራዬ በፊቴ ነው ግን አምላክ መሐሪ ነው! ሰዎችንም በጣም ይወዳል፤ ስለዚህ ኃጢአቴን ይቅር ይለኛል፡፡" አባ ስልዋኖስ ዘአምድ
8 932
15
#ከንስሐ_ርቀን_ይቅርታን_አናገኝም ንስሐ ለተጠመቁ ሰዎች ከጥምቀት በኋላ የተሰጠች ሀብት ናት፡፡ ይህንንም የሚያስረዳ ነገር በጥምቀት ከእግዚአብሔር ከምትገኝ ልጅነት ሁለተኛ ማዕረግ ናት፡፡ በሃይማኖት ገንዘብ ያደረግነው  የመንግስተ ሰማይ መያዣ ከናት፡፡ በንስሐ ምክንያት የእግዚአብሔርን ቸርነት እናገኛለን፡፡ ንስሐ ለሚሿት ሰዎች የተከፈተች የይቅርታ በር ናት፡፡ በንስሐ በርነት ከፈጣሪ ወደሚገኝ ቸርነት እንቀርባለን፡፡ መከላከያ ከሚሆን ከንስሐ ርቀን ይቅርታን አናገኝም፡፡ አምላክ የጻፈው መጽሐፍ እንደተናገረ ሁላችን በድለናልና ያለ ዋጋ በይቅርታው ከኃጢአት እንነጻለን፡፡ ንስሐ እግዚአብሔርን በመፍራት፣ በሃይማኖትና በልቡና የምትገኝ ሁለተኛ ጸጋ ናት፡፡ ሀብታተ ምስጢራት ከሚገኙበት ከመንፈሳዊ ፍቅር እስክንደርስ ድረስ የሚጠብቀን መንፈሳዊ ዕውቀት ነው፡፡ (ምክር ወተግሣጽ ዘማር ይስሐቅ)
9 301
16
“እግዚአብሔር የሚወዳችሁ አንድም እግዚአብሔርን የምትወዱት ወንድም እኅቶቼ ሆይ! እግዚአብሔር በሥጋ ከባረከን በላይ በነፍስ የባረከን ይበልጣልና ስለዚሁ ልናመሰግነው ይገባናል፤ ምድራዊ መጠጥን አንድም ምድራዊ መብልን ከመስጠት መንፈሳዊ መጠጥንና መብልን መስጠት ይበልጣልና፡፡ እግዚአብሔር አስቀድሞ ለእሥራኤላውያን መናውን የሰጣቸው በኋላም እስራኤል ዘነፍስ ለምንባል ለእኛ ቅዱስ ሥጋዉንና ክቡር ደሙን የሰጠንም ስለዚሁ ነውና በሥጋ ከሰጠን ይልቅ በነፍስ የሰጠን ስለሚበልጥ እግዚአብሔርን እጅግ ልናመሰግነው ይገባናል፡፡ እግዚአብሔር በሥጋ ሲባርከን በዚያው (በሥጋዊው ነገር ላይ ብቻ) እንድንቀር አይደለም፤ የበለጠ ወደርሱ እንድንቀርብ ነው እንጂ፡፡ ሥጋዊውን ስጦታ ይዘን የምንቀር ከሆነ ግን ዓላማውን ስተናልና ልናስተካክል ይገባናል፡፡ ተወዳጆች ሆይ! በአፍአ ከተባረክነው ይልቅ በነፍስ የተባረክነው ይበልጣልና ስለዚያ እግዚአብሔርን ልናመሰግነው ይገባናል ብዬ እማልዳችኋለሁ፡፡ ለምን? መንፈሳዊው ነገር ከእኛ ዘንድ ካለ፥ ሥጋዊ ነገር ቢቀርም ምንም አናጣምና፡፡ መንፈሳዊውን ካጣን ግን ከእኛ ዘንድ ምን ተስፋ፥ ምንስ መጽናናት ይቀርልናል? አስቀድመን መንግሥቱንና ጽድቁን እንድንሻ የተፈለገውም ስለዚሁ ነው፡፡ የምወዳችሁ ልጆቼ! አስቀድመን እውነተኛውን ሀብት ይኸውም ሰማያዊውን ሀብት እንለምን፤ ርሱንም ለማግኘት እንጣጣር ብዬ እማልዳችኋለሁ፡፡ ሌላው ከዚያ በኋላ ይቀጥላል፡፡ እኛ ስለለመንን ሳይሆን ልቡናችን ዋናውን ስለፈለገ፡፡ ጸሎታችንን የምናገላብጠው ከሆነ ግን በነፍስ በሥጋ የተጐዳን እንኾናለን፡፡” (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ- የክርስቲያን መከራ እና ሌሎች ገጽ 27)
10 202
17
እግዚአብሔር የሚወዳችሁ እናንተም የምትወዱት ልጆቼ! አዲሱ ዓመት የእውነት አዲስ ዓመት እንዲኾንላችሁ ካሻችሁ ነፍሳችሁን ከኀጢአት ቀንበር አላቋት እንጂ ድጋሜ በኀጢአት ሸክም አትጫኗት፡፡ አሮጌው ዓመት እንዳለቀ ስታዩ እግዚአብሔርን አመስግኑት፡፡ ወደሌላ ዘመን አሸጋግሯቸዋልና እግዚአብሔርን አመስግኑት፡፡ ልቡናችሁንም ውቀሱት፡፡ በዕሜአችሁ ስንት ጊዜ እያለፈ እንደ ኾነ እያሰባችሁም ራሳችሁን እንዲህ ብላችሁ ጠይቁት፡- “ቀናት እየሮጡ ነው፡፡ ዓመታቱም እየነጐዱ ነው፡፡ የዕድሜዬ መንገድም እየተጋመሰ ነው፡፡ ታዲያ ምን በጐ ምግባር ያዝኩ? ከዚህ ምድር የማልፍበት ቀን እየቀረበ ነው፡፡ ታዲያ ምን የጽድቅ ሥራ ሠራሁ? በዚህ ዕድሜዬ መሥራት የነበረብኝ ምግባር ትሩፋት ዕድሜዬ ሲገፋ ማድረግ አልችልም፡፡ ታዲያ ዕድሜዬ ሲገፋ ማድረግ የማልችላቸውም የጽድቅ ሥራዎች (ፆም፣ ጸሎት፣ ስግደት፣ አገልግሎት፣… ዕድሜ ሲገፋ ይከብዳሉና) እንዳቅሜ እያደረግኩ ነውን?” ተወዳጆች ሆይ! አዲስ ዓመት ሲመጣ እነዚህን ነገሮች በጥንቃቄ ልናስብባቸው ይገባናል፡፡ ይህን እያደረግንም ስለ ቀጣዩ ዓመት እናስብ፡፡ ይህን የምናደርግ ከኾነ “ቀኖቻቸውም በከንቱ አለቁ፤ ዓመቶቻቸውም በችኰላ” አይባልብንም (መዝ.78፡3)፡፡ ዕለት ዕለት በዓልን እናድርግ ብዬ የገለጥኩላችሁም ይኸው ነው፡፡ የእኛ በዓል ዘወትር መኾን ይገባዋል፡፡ የክርስቲያኖች በዓል በዓመታትና በቀናት ብቻ መወሰን የለበትም፡፡ ቤተ ክርስቲያንም በሳምንት፣ በወር፣ በዓመት የሚከበሩ በዓላት እንዲኖሩ ማድረጓ ዘወትር ከዚሁ ልንርቅ እንደማይገባ ማሳሰቧ እንጂ ሌላ አይደለምና፡፡ ይህን በዓል በየዕለቱ ማድረግም ለኹሉም ይቻላል፤ ለድኻውም ለባለጸጋውም ይቻላል፡፡ በዓልን ለማድረግ (የጽድቅ ሥራን ሠርቶ ሐሴት ለማድረግ) የሚያስፈልገው ቅን ልቡና እንጂ ገንዘብ አይደለምና፡፡ (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ  ሰማዕትነት አያምለጣችሁ ገጽ 13-19 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመው)
10 172
18
“ፊተኛ ኑሮአችሁን እያሰባችሁ እንደሚያታልል ምኞት የሚጠፋውን አሮጌውን ሰው አስወግዱ፥ በአእምሮአችሁም መንፈስ ታደሱ፥ ለእውነትም በሚሆኑ ጽድቅና ቅድስና እንደ እግዚአብሔር ምሳሌ የተፈጠረውን አዲሱን ሰው ልበሱ።” ኤፌ 4፥22
9 386
19
Sin texto...
10 921
20
#የአዲስ_ዓመት_ጸሎት_በአቡነ_ሺኖዳ አቤቱ ጌታ ሆይ፦ ዓመቱን የተባረከ አድርገው። አንተን ደስ የሚያሰኝ ንጹሕ ዓመት ይሁን። መንፈስ የሚገለጥበት ዘመን ይሁን፣ ከእኛ ጋራም ይሥራ፤ እጆቻችንን ያዝና አሳቦቻችንን ከዓመቱ መጀመሪያ እስከ ማብቂያው ድረስ አንተ ምራቸው። አንተ ደስ ያሰኝህ ዘንድ ይህ ዓመት የአንተ ይሁን፡፡ ይህ አመት አዲስ ዓመት ስለሆነ በኃጢአታችንና በበደላችን አናርክሰው። እግዚአብሔር ሆይ፦ በዚህ ዓመት ልንሠራው ባቀድነው በማንኛውም ሥራ ውስጥ አንተ ከእኛ ጋር ሁን፤ እኛ ዝም እንላለን አንተ ሁሉንም ነገር ታደርጋለህ፡፡ አቤቱ ጌታ ሆይ፦ ይህ ዓመት መልካም ይሁን። በእያንዳንዳችን ላይ ፈገግታን ግለጥ፤ የሁላችንንም ልብ አስደስት፤ በችግራችን ውስጥ ጸጋህ ይገለጥ፤ የተፈተኑትንም አንተ እርዳቸው፤ የአሳብ ሰላምንና ጸጥታን አድለን፡፡ ለተቸገሩት ስጣቸው፤ የታመሙትን ፈውሳቸው፣ ያዘኑትን አጽናናቸው፡፡ ጌታችን ሆይ፦ ለራሳችን ብቻ አንጠይቅህም ያንተ ስለሆኑት ስለሁሉም እንጠይቃለን የፈጠርኻቸው ባንተ ደስ እንዲሰኙ ነው ይህ ከሆነ በአንተ ደስ እንዲሰኙ አድርጋቸው ቃልህ ለሁሉም ልብ ይደርስ ዘንድ ስለ ወንጌል አገልግሎትና ስለ ቤተ-ክርስቲያናችን እንጠይቅሃለን፤ ስለሃገራችንም እንጠይቅሃለን፡፡ መንግሥትህ በሁሉ ስፍራ እንድትመጣም ስለ ዓለም ሰላም እንጠይቅሃለን፡፡ ዓመቱ ፍሬያማና በመልካም ነገሮች የተሞላ ይሁን፡፡ እያንዳንዱ ቀንና ሰዓት የራሱ የሆነ ስራ አለው አንተ የሚባክን ጊዜ ይኖርህ ዘንድ አትፍቀድ፡፡ ሕይወታችንን በእንቅስቃሴ በሥራና በምርት የተሞላ አድርግ፤ ለምርታማና ለተቀደሰ ልፋታችን በረከትህን አድለን፡፡ በተግባራችን ውስጥ ሁሉ የመንፈስ ቅዱስ ኅብረት ከእኛ ጋር ይሁን። አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ እስከዚች ሰዓት ድረስ ጠብቀህ ስላቆየኸንና ይህንን ዓመት ስላደልከን እናመሰግንሃለን፣ እንባርክህማለን፡፡
11 004