cookie

Utilizamos cookies para mejorar tu experiencia de navegación. Al hacer clic en "Aceptar todo", aceptas el uso de cookies.

avatar

TIKVAH-ETHIOPIA

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው። @tikvahuniversity @tikvahethAfaanOromoo @tikvahethmagazine @tikvahethsport @tikvahethiopiatigrigna #ኢትዮጵያ

Mostrar más
Advertising posts
1 316 411Suscriptores
+1 46524 hours
+8 1677 days
+27 77930 days

Carga de datos en curso...

Tasa de crecimiento de suscriptores

Carga de datos en curso...

#ጋና #ፀረግብረሰዶም ባለፈው ወር መጨረሻ #የጋና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) ጠንካራ ይዘት ያለው " የፀረ-ግብረሰዶም " ረቂቅ ህግ አፅድቋል። ረቂቅ ህጉ በክርስቲያኑ ፣ በሙስሊሙ እና በጋና ባሕላዊ መሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ድጋፍ ያለው ነው። ወደ ተግባር እንዲገባና ህግ ሆኖ እንዲወጣ ግን የፕሬዜዳንት ናና አኩፎ-አዶን ፊርማ እየጠበቀ ነው። በጋና አሁንም ቢሆን ግብረሰዶማዊነት እስከ 3 ዓመት ድረስ ወደ እስር ቤት ያስወረውራል። በአዲሱ ረቂቅ ህግ ላይ ቅጣቱ ጠበቅ እንዲል የተደረገ ሲሆን ፦ - በማንኛውም መንገድ ግብረሰዶማውያንና እንቅስቃሴያቸውን ማስተዋወቅ - የግብረሰዶም ስብስብ መፍጠር - ግብረሰዶማውያንን ስፖንሰር ማድረግ - ግብረሰዶማውያንን እና የሚያደርጉትን ማንኛውም እንቅስቃሴ በምንም መልኩ መደገፍ እስከ አምስት (5) ዓመት ወደ እስር ቤት ያስወረውራል። ምዕራባውያኑና በሰብዓዊ መብት ላይ የሚሰሩ ተቋሞቻቸው የጋና ፓርላማ ያፀደቀውን ረቂቅ ህግ ክፉኛ ነው የተቃወሙት። የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት እስካሁን ያልፈረሙበት ሲሆን ረቂቅ ህጉን የሚደግፈው ህዝብ " ምነው ዘገዩ ? " የሚሉ ቅሬታዎች እያነሳ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጋና መገናኛ ብዙሃን ላይ ተመልክቷል። የሀገሬው ሰው ፕሬዜዳንቱ #እንዲፈርሙ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ እርዳታ ሰጪ ምዕራባውን ፣ የሰብዓዊ መብት ተቋማት እንዳይፈርሙበት እያሳሰቡ ናቸው። ጋና ጠንካራ ነው የተባለውን የፀረ-ግብረሰዶም ህግን ወደ ተግባር ምታስገባው ከሆነ በሚቀጥሉት አምስት እና ስድስት ዓመታት ውስጥ ከዓለም ባንክ የምታገኘውን 3.8 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ ልታጣ ትችላለች ተብሏል። @tikvahethiopia
Mostrar todo...
👏 1
#ጋና #ፀረግብረሰዶም ባለፈው ወር መጨረሻ #የጋና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) ጠንካራ ይዘት ያለው " የፀረ-ግብረሰዶም " ረቂቅ ህግ አፅድቋል። ረቂቅ ህጉ በክርስቲያኑ ፣ በሙስሊሙ እና በጋና ባሕላዊ መሪዎች ዘንድ ከፍተኛ ድጋፍ ያለው ነው። ወደ ተግባር እንዲገባና ህግ ሆኖ እንዲወጣ ግን የፕሬዜዳንት ናና አኩፎ-አዶን ፊርማ እየጠበቀ ነው። በጋና አሁንም ቢሆን ግብረሰዶማዊነት እስከ 3 ዓመት ድረስ ወደ እስር ቤት ያስወረውራል። በአዲሱ ረቂቅ ህግ ላይ ቅጣቱ ጠበቅ እንዲል የተደረገ ሲሆን ፦ - በማንኛውም መንገድ ግብረሰዶማውያንና እንቅስቃሴያቸውን ማስተዋወቅ - የግብረሰዶም ስብስብ መፍጠር - ግብረሰዶማውያንን ስፖንሰር ማድረግ - ግብረሰዶማውያንን እና የሚያደርጉትን ማንኛውም እንቅስቃሴ በምንም መልኩ መደገፍ እስከ አምስት (5) ዓመት ወደ እስር ቤት ያስወረውራል። ምዕራባውያኑና በሰብዓዊ መብት ላይ የሚሰሩ ተቋሞቻቸው የጋና ፓርላማ ያፀደቀውን ረቂቅ ህግ ክፉኛ ነው የተቃወሙት። የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት እስካሁን ያልፈረሙበት ሲሆን ረቂቅ ህጉን የሚደግፈው ህዝብ " ምነው ዘገዩ ? " የሚሉ ቅሬታዎች እያነሳ መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጋና መገናኛ ብዙሃን ላይ ተመልክቷል። የሀገሬው ሰው ፕሬዜዳንቱ #እንዲፈርሙ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ እርዳታ ሰጪ ምዕራባውን ፣ የሰብዓዊ መብት ተቋማት እንዳይፈርሙበት እያሳሰቡ ናቸው። ጋና ጠንካራ ነው የተባለውን የፀረ-ግብረሰዶም ህግን ወደ ተግባር ምታስገባው ከሆነ በሚቀጥሉት አምስት እና ስድስት ዓመታት ውስጥ ከዓለም ባንክ የምታገኘውን 3.8 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ከፍተኛ ገንዘብ ልታጣ ትችላለች ተብሏል። @tikvahethiopia
Mostrar todo...
በሀገራችን አንዳንድ መልካም የስራ ስነምግባር የጎደላቸው ፣ ከአሸከርካሪዎች ጉቦ ካልተቀበሉ ቀኑ መሽቶ የማይነጋ የሚመስላቸው ፣ አንዳንዴም ሆን ብለው ምክንያት ፈልገው የቅጣት ወረቀት ለመፃፍ በኃላም #ጉቦ ለመቀበል የማይፈነቅሉት ድንጋይ የሌላቸው ፣ ፀሀዩ በረታብኝ ፥ ዝናቡም አካፍብኝ ብለው የሚጠለሉ የትራፊክ የፖሊስ አባላት እንዳሉት ሁሉ ፦ - ለስራቸው ታማኝ - ህግን አክባሪ - ቅን አገልጋይ - ፀሀይ ፣ ዝናብ ሳይሉ ህዝብን አክብረው የሚሰሩ በርካታ የትራፊክ ፖሊስ አባላት አሉ። ለእነዚህ አይነት ህዝብን አክብረው ምንም አይነት ሁኔታ ሳይገድባቸው ለሚሰሩ የትራፊክ ፖሊስ አባላት #ምስጋና ይገባል። በሀገራችን ካሉ ከተሞች አንዷ በሆነችው የሰላም ተምሳሌቷ #ድሬዳዋ ❤️ የትራፊክ ፖሊስ አባላቶቿ በተለያየ ጊዜ በመልካም ስነምግባራቸው ስማቸው ተደጋግሞ ይነሳል። ትላንትና በከተማው ከባድ ዘናብ ዘንቦ በነበረበት ወቅት የትራፊክ መጨናነቅና አደጋ እንዳይከሰት አንድ የትራፊክ ፖሊስ አባል በዝናብ ውስጥ ሆኖ ስራውን ሲያከናውን የሚያሳይ የተቀረጹ ቪድዮዎች እና ፎቶዎች ብዙዎች በማህበራዊ ሚዲያ ሲያጋሩት ውለዋል። @tikvahethiopia
Mostrar todo...
#አስቸኳይ “ አጋቾቹ ወደ ታች ዘቅዝቀው እየገረፉት ቪዲዮ ላኩልኝ። ‘1.7 ሚሊዮን ብር ካላስገባሽ ልጅሽን #ገድለን ቪዲዮ እንልክልሻለን’ አሉኝ ” - የታጋች እናት በሊቢያ ደላሎች የታገተው የሀዋሳው ተወላጅ ኢትዮጵያዊ ወጣት ጌድዮ ሳሙኤል፣ በአጋቾቹ ልዩ ልዩ ድብደባዎች እየተፈጸሙበት እንደሚገኝ ፣ አጋቾቹ ወጣቱን ለመልቀቅ 1.7 ሚሊዮን ብር እንደጠየቁ፣ ገንዘቡ በፍጥነት ካልገባ “ እንገድለዋለን ” በማለት የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ እንደሰጡ የታጋች ቤተሰቦች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ። የታጋቹ እናት ወ/ሮ ገነት ጥላሁን ይግለጡ በሰጡት ቃል፣ “ አጋቾቹ ወደ ታች ዘቅዝቀው እየገረፉት ቪዲዮ ላኩልኝ። ‘1.7 ሚሊዮን ብር ካላስገባሽ ልጅሽን ገድለን ቪዲዮ እንልክልሻለን’ አሉኝ። የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ እባካችሁ ልጄን ታደጉኝ ” ሲሉ እያለቀሱ ጠይቀዋል። “ በሄደ በ17 ቀኑ ከሊቢያ ስልክ በጓደኛው አማካኝነት ተደወለልኝ። ስልኩን ሳነሳ ‘ሊቢያ ላይ ተይዟልና 950 ሺሕ ብር ተጠይቋል’ ብሎ ጓደኛው ነገረኝ ” ያሉት የታጋቹ እናት፣ “ ከዚያ ወዲያውኑ ደግሞ ሊቢያዎቹ እየገረፉት ምስል ላኩልኝ። አካውንትም ላኩልኝ ‘ገንዘብ ላኪ’ ብለው ” ሲሉ አስረድተዋል። አክለውም፣ “ እንደገና ለ3ኛ ጊዜ መደኃኒት ሰጥተውት እንደ እብድ እያደረገው ቪዲዮ ላኩልኝ። እንደገና ለ4ኛ ጊዜ ደግሞ ወደ ታች #ዘቅዝቀው #እየገረፉት ቪዲዮ ላኩልኝ። ከዚያ ‘ተሽጧል 1.7 ሚሊዮን ብር አምጭ’ ብለው ደወሉ። ቪዲዮ እያሳዩም ‘1.7 ሚሊዮን ብር ታመጫለሽ አታመጭም?’ አሉኝ ” ብለዋል። በዚህም “ እኔ የለኝም ግን የኢትዮጵያ ሕዝብ ጉልበቴ ስለሆነ ለምኘ፣ እርዳታ አሰባስቤም እከፍላለሁ አልኳቸው። ለ5ኛ ጊዜ እንደገና #ፀጉሩን ላጭተው የሆነ #ውሻ አስመስለው ምስል ላኩልኝ። ከዚያ በኋላ በቃ ‘የጨመረሻ ቀን ብለው’ ደወሉ። ልጄም በጣም #እያለቀሰ ‘አስለቅቂኝ’ አለኝ። እነርሱም ‘ነገ #አርብ 1.7 ሚሊዮን ብር ካላስገባሽ ልጅሽን በፊት ለፊትሽ ገድለን ቪዲዮ እንልክልሻለን ” አሉኝ ሲሉ አንብተዋል። አጋቾቹ ‘ብር ላኪ’ ሲሏቸው ባለማወቅ የመፍትሄ መንገድ መስሏቸው የላኩትን አካውንት በሕግ እንዳሳገዱ፣ በዚህም አጋቾቹ የወጣቱን ስቃይ እንዳበዙት፣ ከታገተ ከአንድ ወር በላይ እንደሆነው፣ ገንዘቡ እስኪሟላ ተጨማሪ ቀን መጠየቃቸውን የገለጹት እናት፤ “ ፌደራልም ሊቢያና ሱዳን ድንበር ላይ የሊቢያ መግቢያ ላይ ነው የታገተው ብለው ነገሩኝ ” ብለዋል። ወ/ሮ ገነት፣ ምርመራውን ይዞታል የተባሉ የፌደራል ፓሊስ አባል የአጋቹን አካል ቢደርሱበትም በሕግ በኩልም መፍትሄ እንዳላገኙ አስረድተዋል። ያላቸው አሁናዊ የምርመራ ሂደትን በተመለከተ ምላሽ እንዲሰጡ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው መርማሪው የፌደራል ፓሊስ ጉዳዩን በጽሞና ከሰሙ በኋላ “ መልስ መሰጠት የሚችለው እንደ ተቋም ስለሆነ በተቋሙ በኩል ኦፊሻል ደብዳቤ ይዘው በአካል መጥተው አመራሮችን ማነጋገር ይችላሉ ” ከማለት ውጪ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም። ሆኖም ስለጉዳዩ በደብዳቤ ጠይቀን ምላሹን በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል። እናት አጋቾቹ ከጠየቁት ውስጥ እስካሁን የተሰበሰበው ወደ 350 ሺሕ ብር ብቻ እንደሆነ አስረድተው “ ሀዘን ላይ ነኝ። በቅርቡ ልጄ ሞቶብኛል። አሁን ደግሞ ይሄ ደረሰልኝ ብዬ፣ አሁን እንደዚህ ሆነብኝ። የኢትዮጵያ ሕዝብ ረድቶኝ ልጄን እንዲያስለቅቅልኝ በትህትና እጠይቃለሁ ” ሲሉ ተማጽነዋል። ድጋፍ ማድረግ የምትፈልጉ የወ/ሮ ገነት ጥላሁን ይግለጡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000523577402 ሲሆን ሌሎችም የሂሳብ ቁጥሮች ከላይ ተያይዟል። በስልክ ልታገኟቸው የምትፈልጉ 0916848184፣ 0911720985 ደውሉላቸው። @tikvahethiopia
Mostrar todo...
#Update ዛሬ ከቀኑ 09:46 ጀምሮ ከባህርዳርና አካባቢው በስተቀር በመላው ኢትዮጵያ ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል መልሶ መገናኘት መጀመሩን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሳውቋል። አብዛኛው የአዲስ አበባ ክፍል እና የተቀሩት የሀገሪቱ ክፍሎች መልሰው ኃይል ማግኘት እንደቻሉ ተገልጿል። የተቀሩትን አካባቢዎች መልሶ ለማገናኘት ጥረቱ መቀጠሉ ተነግሯል። @tikvahwthiopia
Mostrar todo...
ዛሬ ከቀኑ 09:46 ጀምሮ ከባህርዳርና አካባቢው በስተቀር በመላው ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉ መቋረጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታውቋል። በሲስተም ላይ በገጠመ ችግር ኃይል መቋረጡን ያስታወቀው ተቋሙ  ለጊዜው የችግሩን ምክንያት ለማወቅ ጥረት እየተደረገ ነው ብሏል። የተቋረጠውን ኤሌክትሪክ መልሶ የማገናኘት ሥራ የተጀመረ መሆኑን የገለጸው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል፥ ችግሩን በመቅረፍ ዳግም ሲስተሙ ተመልሶ እስኪገናኝ ድረስ በትዕግስት ጠብቁ ሲል አስታውቋል። #NB: ተቋሙ ይህንን መረጃ በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ ከደቂቃዎች በፊት ያወጣው ሲሆን አሁን ላይ በአንዳንድ አከባቢዎች የተቋረጠው የኤሌክትሪክ ኃይል መመለሱን ማረጋገጥ ችለናል። @tikvahethiopia
Mostrar todo...
#እናት እናት ፓርቲ ፥ " መንግሥት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት አባቶችንና ምእመናንን አሰቃቂ ግድያ በማስቆም ከደሙ ነጻ መሆኑን በአስቸኳይ ሊያረጋግጥ ይገባል " ብሏል። ይህን ያለው ከሰሞነኛው የዶዶላው ግድያ በኃላ ባወጣው መግለጫ ነው። " የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶችና ምዕመናን ባለፋት ሶስት አስርት ዓመታት እጅግ በጣም አሰቃቂ ጥቃት ደርሶባቸዋል " ያለው ፓርቲው " በተለይም ባለፉት 5 ዓመታት በቤተክርስቲያኗ እና ምእመናኗ ላይ እየተፈጸመ የሚገኘው ግፍ እና አሰቃቂ ግድያዎች ክፉኛ ተጠናክረው ቀጥለዋል " ሲል ገልጿል። ፓርቲው ፥ በዶዶላ ከተማ ባለፈው ሰኞ በታጣቂ ኃይሎች በተፈጸመ ጥቃት የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ  ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አገልጋይ መርጌታ፣ 2 ልጆቻቸው እና ባለቤታቸውን ጨምሮ ከ2 ወራት በፊት ሥርዓተ ጋብቻቸውን የፈጸሙ ሙሽሮች (አንድ ዲያቆን ከባለቤቱ እና ታላቅ እህቱ ጋር) በአጠቃላይ 7 ንጹሐን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ካህናትና ምዕመናን በአሰቃቂ ሁኔታ በታጣቂዎች መገደላቸውን አመልክቷል። በተጨማሪም በቀን ሥራ ይተዳደሩ የነበሩ 4 ንጹሐን ዜጎችም በታጣቂ ኃይሎች መገደላቸውን ገልጿል። ሌሎች ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው 7 ሰዎችም በዶዶላ አጠቃላይ ሆስፒታል ሕክምና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑን ጠቁሟል። ፓርቲው ፤ " ከዚህ ማብቂያ ካጣው አሰቃቂ ግድያ ጋር በተያያዘ መንግሥት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት አባቶችና ምእመናንን አሰቃቂ ግድያ በማስቆምና መንግሥታዊ ኃላፊነቱን በመወጣት ከእነዚህ ንጹሐን ደም  ነጻ መሆኑን በአስቸኳይ ሊያረጋግጥ ይገባል " ብሏል። @tikvahethiopia
Mostrar todo...
" 11 ንፁሃን ነው የተገደሉት " - የዶዶላ ከተማ አስተዳደር በዶዶላ ባለፈው ሰኞ ዕለት ምሽት 3 ሰዓት ገደማ በተፈፀመ ጥቃት 11 ንፁሃን ሰዎች መገደላቸውን የከተማው አስተዳደር ኮሚኒኬሽን ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ በሰጠው ቃል አረጋግጧል። የከተማው አስተዳደር ለሬድው ጣቢያው " በዕለቱ በድንገት በተፈፀመ ጥቃት 11 ሰዎች ሞተዋል። በጥይት ተመተው የተጎዱም አሉ። ከጥቃቱ ጀርባ በገደብ አሳሳ ፣ አዳባ፣ በክልል ደረጃም ታጥቆ የሚንቀሳቀሰው የሸኔ ቡድን አለ የሚል መላምት አለ ግን ምርመራ እየተካሄደ ነው " ብሏል። ይህ ሁሉ ሰው #ሲገደል የፀጥታ ኃይሉ ለምን በስፍራው አልደረሰም ? ለሚለው ጥያቄ የከተማ አስተዳደሩ ፤ " ጥቃቱ የተፈፀመው በደነባ ክ/ከተማ ደብረ ቅዱሳን ጻድቁ አቡነ ገብረ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አቅራቢያ ነው። ይህ ሆን ብሎ የሃይማኖት አባትን እና ልጆቻቸውን የገደለው እርስ በእርስ ግጭት እንዲነሳ ለማድረግ ነው ብለን እንገምታለን። በጣም ታስቦበት የተፈፀመ ግድያ ነው " የሚል ምላሽ ሰጥቷል። ንፁሃኑ ግድያው የተፈፀመባቸው በቤታቸው እያሉ #በጥይት ተተኩሶባቸው እንደሆነና መንግሥት ግድያውን እንደሚያወግዝ የከተማ አስተዳደሩ ገልጿል። ለመሆኑ የጥቃቱ ፈፃሚዎች ተይዘዋል ? ለሚለው ጥያቄ ፥ የዶዶላ ከተማ አስተዳደር " ክትትል እየተደረገ ነው " የሚል ምላሽ ለሬድዮ ጣቢያው ሰጥቷል። ይህ የአስተዳደሩ ምላሽም አንድም የተያዘ ሰው እንደሌለ የሚጠቁም ነው። በዶዶላ የደብረ ቅዱሳን ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ 2 የቤተክርስቲያን አገልጋዮች ከነሙሉ ቤተሰቦቻቸው በጥይት ተደብድበው መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪና የዓይን እማኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው ይታወሳል። ነዋሪው ፤ አንድ መሪጌታ ከእነባለቤቱ እና ከሁለቱ ልጆቹ ጋ፣ አንድ ዲያቆን ከእነባለቤቱና እህቱ ጋር መገደላቸውን ፤ የመርጌታው ሁለቱ ልጆቹ ሲገደሉ የ1 ዓመት ከ5 ወር ህፃን ብቻ መቅረቱን ገልጸው ነበር። @tikvahethiopia
Mostrar todo...
ኮንሰርት፣ ባዛር ሲያዘጋጁ ፊልም/ቲያትር ሲያቀርቡ የሚታይ የሚጎበኝ ሲኖርዎት የመግቢያውን ትኬት እኛ እንሽጥልዎት! https://www.facebook.com/combanketh https://t.me/combankethofficial ********** በሲቢኢ ብር መተግበሪያ የትኬት ሽያጭ አገልግሎት በቀላሉ ሚሊዮኖች ጋር ይደርሳሉ! #CBE #cbebirr #apps #digitalbanking ************* የሲቢኢ ብር መተግበሪያ ማስፈንጠሪያ፡ • ለአንድሮይድ ስልኮች፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr • ለአፕል ስልኮች፡ https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787
Mostrar todo...
2
🔥ደማቁ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ወደ ሜዳ ሊመለስ ነው🔥 አንድ ቡድን መርተው ቢያውቁም ፔፕ ጋርዲዮላ እና ሚካኤል አርቴታ ባላንጣ ሆነው ሊሰለፉ ግድ ሆኗል 🏆አስተማሪው ከ ተማሪው ጋርለዓመቱ የመጨረሻ ጊዜ ይገናኛሉ! 🎉ዛሬውኑ ፓኬጅዎን ያሳድጉ ጨዋታዎችን ከትንታኔ ፣ ከተጫዋች ብቃትእስከ ቡድን ወኔ በሱፐርስፖርት ይከታተሉ! 🎉ከጥር 6 እስከ መጋቢት 22 ደንበኝነትዎን ሲያሳድጉ... እኛም ቀጣዩን ፓኬጅ ለአንድ ወር እንጋብዝዎታለን! የዲኤስቲቪ አገልግሎቶችን ለማግኘት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ! https://mydstv.onelink.me/vGln/eth2 #PremierLeagueAllonDStv #ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia #DStvSelfServiceET #StepUp
Mostrar todo...
Inicia sesión y accede a información detallada

Te revelaremos estos tesoros después de la autorización. ¡Prometemos que será rápido!