es
Feedback
ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል

ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል

El canal ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል (@mkpublicrelation) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 51 359 suscriptores, ocupando la posición 1 066 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 621 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 51 359 suscriptores.

Según los últimos datos del 11 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 684, y en las últimas 24 horas de -1, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 13.87%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 7.71% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 7 121 visualizaciones. En el primer día suele acumular 3 962 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 53.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 12 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

51 359
Suscriptores
-124 horas
+1377 días
+68430 días
Archivo de publicaciones
ኑ ! ስደታቸው በሰንበትና በክረምት ለሆነባቸው እንድረስላቸው። ---***--- ለአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ወደ መርሐግብሩ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ
ኑ ! ስደታቸው በሰንበትና በክረምት ለሆነባቸው እንድረስላቸው። ---***--- ለአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር   ወደ መርሐግብሩ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ። https://zoom.us/j/93407133345 ድጋፍ ለማድረግ ፡- 1.   Mahibere Kidusan in Europa e.V. IBAN: DE14 3704 0044 0307 8037 00 BIC: COBADEFFXXX Reason of payment – 007   2.   Mahibere Kidusan in UK Banking - NatWest Sort Code - 60 12 51 Acc. No - 364 25 591 Reason of Payment: 007   3.   በስዊድን ለምትገኙ፡- ACCOUNT NUMBER - 9960 3421234653 BIC - NDEASESS IBAN - SE15 9500 0099 6034 2123 4653 ACCOUNT HOLDER - MAHIBERE KIDUSAN I SVERIGE NORDEA BANK Reason of Payment: 007   4.   በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000309803648 በአቢሲኒያ ባንክ 37235458 በአሐዱ ባንክ 0025393810901

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ …›› (ማቴ፲፣፳፰) ከዲ/ን ተስፋዬ ቻይ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ሥጋንም የሚገድሉትን  ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ …›› (ማቴ፲፣፳፰)   ከዲ/ን ተስፋዬ ቻይ  ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያትን የምሥራቹን ወንጌል ሰብከው የጨለመውን የሰው ልጅ ልቡና በወንጌል ብርሃንነት ያበሩ ዘንድ፣ ከጣዖተ አምልኮ አውጥተው የፈጠራቸውን የሚመግባቸውን እግዚአብሔር ያውቁና ያመልኩ ዘንድ፣ በጠላት ዲያቢሎስ አሳሳችነት የመረረ ሕይወታቸውን በወንጌል ጨውነት ያጣፍጡ ዘንድ ወደ ዓለም በላካቸው ጊዜ ጠላት ዲያሎስ በክፉዎች እያደረ መከራ እንደሚያመጣባቸው፣ ይህንንም እንደ እባብ ብልህ ፣እንደ ርግብ የዋህ ሆነው እንዲያልፉ ፣ሳይፈሩና ሳይሰቀቁ እንዲመሰክሩ አዘዛቸው ፤ መከራቸው ስደት ፣መጠማት፣ ግርፋትና ረኀብ ባቻ ሳይሆን ሥጋዊ ሞት( የነፍስ ከሥጋ መለየት) እንደሚገጥማቸውና ይህም አንዳች እንዳያስፈራቸው ነገራቸው፤ ምድራዊ ሩጫቸው በሰማዕትነት ቢገታም ሰማየያዊ መኖሪ ዘለዓለማዊ ሕይወት እንዳለ የታመነውን ተስፋ ሰጣቸው፡፡ ቅዱሳን አበው ሐዋርያት ጌታችን ሞትን ድል አድርጎ በተነሣ በአርባኛው ቀን፣ ካረገ በአሥረኛው ቀን ባናገረው ትንቢት ፣በገባላቸው ቃል መሠረት የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ላከላቸው፣በጾም በጸሎ መንፈሳዊ ተግባራቸውን ጀመሩ ፤እምነታቸው ጸንቶ፣ፍርሃት ርቆላቸው ጥቡዐን ( ደፋሮች) ሆነው የእውቀት ተከፍሎ ሳይኖርባቸው ፤ዓለምን በዕጣ ተከፋፍለው የምሥራቹን ወንጌል ማስተማር ጀመሩ፡፡ https://eotcmk.org/a/በስመ-አብ-ወወልድ-ወመንፈስ-ቅዱስ-አሐዱ-አ-3/

ማኅበረ ቅዱሳን ለደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ ሁለ ገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት እያስገነባ እንደሚገኝ ገለጸ ሐምሌ ፫ /፳፻፲፰ ዓ.ም ማኅበረ ቅዱሳን በጎ አድራጊ አካላትን በማስተባበር በሰሜን ጎንደር ሀገ
ማኅበረ ቅዱሳን ለደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ ሁለ ገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት እያስገነባ እንደሚገኝ ገለጸ   ሐምሌ ፫ /፳፻፲፰ ዓ.ም  ማኅበረ ቅዱሳን በጎ አድራጊ አካላትን በማስተባበር በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ደባርቅ ከተማ የደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ ሁለ ገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት እያስገነባ እንደሚገኝ ገልጿል።   ማኅበረ ቅዱሳን በቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገትና መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች አገልግሎት የፕሮጀክት ዝግጅትና ትግበራ ምክትል ኃላፊ የሆኑት ኢ/ር ማስተዋል አበበ (ወ/ሪት) እንደገለጹት የደብረ ሐዊ የቅዱስ ያሬድ ገዳም በኢኮኖሚ ዐቅሙን ለማሳደግና አገልግሎቱን ለማስቀጠል የሚረዳ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት በሁለት ዙር  እንደሚከናወን ተናግረዋል።  ይህም በመጀመሪያው ዙር B+G+4 ወለል ሕንጻ እየተገነባ እንደሚገኝ የተጠቀሰ ሲሆን ማኅበሩ በዚህ ዙር  የሚጠበቅበትን ድርሻ ለማጠናቀቅ በመወጣት ረገድ 75.79% መድረሱን ተገልጿል።   ግንባታው በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚገኙ ድጋፍ አድራጊ አካላትን በማስተባበር የተከናወነ ነው ተብሏል።  በመጨረሻም ቅዱስ ያሬድ ለቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለሀገር  ባለውለታ  እንደመሆኑና ገዳሙ ጥንታዊ በመሆኑ ለመናንያኑ የዕለት ጉርስ፣ የዓመት ልብስ እንዲሁም ለአገልግሎቱ የሚያስፈልጉ ነገሮችን በማድረግ ገዳሙ ያለበትን ደረጃ ለማቆየት ሁሉም ምእመን በሐሳብ፣ በጉልበትና በገንዘብ የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ ይገባል ሲሉ ኢ/ር ማስተዋል አበበ  ጥሪ አቅርበዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን ለደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ ሁለ ገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት እያስገነባ እንደሚገኝ ገለጸ   ሐምሌ ፪/፳፻፲፰ ዓ.ም  ማኅበረ ቅዱሳን በጎ አድራጊ አካላትን በማስተባበር በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ደባርቅ ከተማ የደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ ሁለ ገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት እያስገነባ እንደሚገኝ ገልጿል።   ማኅበረ ቅዱሳን በቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገትና መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች አገልግሎት የፕሮጀክት ዝግጅትና ትግበራ ምክትል ኃላፊ የሆኑት ኢ/ር ማስተዋል አበበ (ወ/ሪት) እንደገለጹት የደብረ ሐዊ የቅዱስ ያሬድ ገዳም በኢኮኖሚ አቅሙን ለማሳደግና አገልግሎቱን ለማስቀጠል የሚረዳ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት በሁለት ዙር  እንደሚከናወን ተናግረዋል።  ይህም በመጀመሪያው ዙር B+G+4 ወለል ሕንጻ እየተገነባ እንደሚገኝ የተጠቀሰ ሲሆን ማኅበሩ በዚህ ዙር  የሚጠበቅበትን ድርሻ ለማጠናቀቅ በመወጣት ረገድ 75.79% መድረሱን ተገልጿል።   ግንባታው በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚገኙ ድጋፍ አድራጊ አካላትን በማስተባበር የተከናወነ ነው ተብሏል።  በመጨረሻም ቅዱስ ያሬድ ለቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለሀገር  ባለውለታ  እንደመሆኑና ገዳሙ ጥንታዊ በመሆኑ ለመናንያኑ የዕለት ጉርስ፣ የዓመት ልብስ እንዲሁም ለአገልግሎቱ የሚያስፈልጉ ነገሮችን በማድረግ ገዳሙ ያለበትን ደረጃ ለማቆየት ሁሉም ምእመን በሀሳብ፣ በጉልበትና በገንዘብ የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ ይገባል ሲሉ ኢ/ር ማስተዋል አበበ  ጥሪ አቅርበዋል።

"የአኀት አብያተ ክርክቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ" የፓናል ውይይት ዘገባ ክፍል ፫ ሐምሌ ፫/፳፻፲፰ ዓ.ም የአኀት አብያተ ክርክቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት ግንቦት ፳፱/፳፻፲፰ ዓ.ም ተካሄዶ የነበረ ሲሆን በውይይቱም የሚክትሉተ ሦስት ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። ፩ኛ - የአኀት አብያተ ክርስቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ - በመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል በመንበረ ፓትርያሪክ ጠ/ቤ/ክ ጥናት፣ ምርምርና መረጃ መምሪያ ኀላፊ እና የቅ/ሲኖዶስ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ኀላፊ እንዲሁም የሊቃውንት ጉባኤ አባል ፪ኛ - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት፣ ትግበራ፣ ክትትልና ግምገማ ከትናንት እስከ ዛሬ - በመ/ር ባሕረ ጥበባት ሙጨ ፫ኛ - የቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት ትግበራና የማኅበረ ቅዱሳን ድርሻ - በዶ/ር በሪሁን ተፈራ የማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ ጽሑፎችና አጠቃላይ ውይይቱ በሦስት ክፍል የቀረበ ሲሆን የነበረው የማጠቃለያ ውይይት ሦስተኛው ክፍል እንደ ሚከተለው ቀርቧል፡፡ https://youtu.be/x3hRmh2hDPY?si=UpIKdQymapn-yg-I

ዜና ገዳማት

ኑ ! ስደታቸው በሰንበትና በክረምት ለሆነባቸው እንድረስላቸው። ---***--- ለአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ወደ መርሐግብሩ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ
ኑ ! ስደታቸው በሰንበትና በክረምት ለሆነባቸው እንድረስላቸው። ---***--- ለአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር   ወደ መርሐግብሩ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ። https://zoom.us/j/93407133345 ድጋፍ ለማድረግ ፡- 1.   Mahibere Kidusan in Europa e.V. IBAN: DE14 3704 0044 0307 8037 00 BIC: COBADEFFXXX Reason of payment – 007   2.   Mahibere Kidusan in UK Banking - NatWest Sort Code - 60 12 51 Acc. No - 364 25 591 Reason of Payment: 007   3.   በስዊድን ለምትገኙ፡- ACCOUNT NUMBER - 9960 3421234653 BIC - NDEASESS IBAN - SE15 9500 0099 6034 2123 4653 ACCOUNT HOLDER - MAHIBERE KIDUSAN I SVERIGE NORDEA BANK Reason of Payment: 007   4.   በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000309803648 በአቢሲኒያ ባንክ 37235458 በአሐዱ ባንክ 0025393810901

ለበለጠ መረጃ፡- በአካል 5 ኪሎ ማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ 1ኛ ወለል         ወይም ·  በስልክ.ቁ፡- +251 921803238 ·  በኢሜል፡- yagelgilotber@eotcmk.org ·  በቴሌግራም፡- @Zeyklekulu   ·  WhatsApp:- +251 91 352 8494       · ለመመዝገብና አገልግሎትን ለማግኘት :- 👇 👇 👇 https://forms.gle/CgYYC5gX6oxd3HGS7                          ዘመነ ክረምትን በአገልግሎት በር!

ኑ ! ስደታቸው በሰንበትና በክረምት ለሆነባቸው እንድረስላቸው። ---***--- ለአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ወደ መርሐግብሩ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ
ኑ ! ስደታቸው በሰንበትና በክረምት ለሆነባቸው እንድረስላቸው። ---***--- ለአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር   ወደ መርሐግብሩ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ። https://zoom.us/j/93407133345 ድጋፍ ለማድረግ ፡- 1.   Mahibere Kidusan in Europa e.V. IBAN: DE14 3704 0044 0307 8037 00 BIC: COBADEFFXXX Reason of payment – 007   2.   Mahibere Kidusan in UK Banking - NatWest Sort Code - 60 12 51 Acc. No - 364 25 591 Reason of Payment: 007   3.   በስዊድን ለምትገኙ፡- ACCOUNT NUMBER - 9960 3421234653 BIC - NDEASESS IBAN - SE15 9500 0099 6034 2123 4653 ACCOUNT HOLDER - MAHIBERE KIDUSAN I SVERIGE NORDEA BANK Reason of Payment: 007   4.   በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000309803648 በአቢሲኒያ ባንክ 37235458 በአሐዱ ባንክ 0025393810901

ለበለጠ መረጃ፡- በአካል 5 ኪሎ ማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ 1ኛ ወለል ወይም · በስልክ.ቁ፡- +251 921803238 · በኢሜል፡- yagelgilotber@eotcmk.org · በቴሌግራም፡- @Zeyklek
ለበለጠ መረጃ፡- በአካል 5 ኪሎ ማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ 1ኛ ወለል         ወይም ·  በስልክ.ቁ፡- +251 921803238 ·  በኢሜል፡- yagelgilotber@eotcmk.org ·  በቴሌግራም፡- @Zeyklekulu   ·  WhatsApp:- +251 91 352 8494       · ለመመዘገቢና አገልግሎትን ለማግኝት :- 👇 👇 👇 https://forms.gle/CgYYC5gX6oxd3HGS7                          ዘመነ ክረምትን በአገልግሎት በር!

ይህ በእንዲህ እንዳለ የጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት በበኩሉ በየዓመቱ ለካህናት የሚሰጠውን የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ሥልጠና 15 ዲያቆናትን ሲያሠለጥን የቆየ ሲሆን ከሥልጠናው ጎን ለጎን ለማዕረገ ቅስና የሚያበቃቸውን ትምህርት በመስጠት ማዕረገ ቅስና እንዲቀበሉ አድርጓል።   ሥልጠናው በአርባ ምንጭ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ገዳም ጽርሐ ተዋሕዶ የካህናት ማሠልጠኛ ተቋም ሲሰጥ የቆየ ሲሆን ተቋሙ ለ58ኛ ጊዜ ማሠልጠኑ ተነግራል። ማኅበረ ቅዱሳን በያዘው መርሐ ግብር 11 ሠልጣኞችን በማስተማር ስምንቱ ማዕረገ ቅስና እንዲያገኙ የተደረገ ሲሆን በሀገረ ስብከቱ መርሐ ግብር ከሠለጠኑት 15 ዲያቆናት መካከል ስምንቱ ማዕረገ ቅስና እንዲያገኙ በማድረግ በአጠቃል ከ26 ሠልጣኞች መካከል 16ቱ ከብፁዕ አቡነ ኤልያስ ማዕረገ ቅስና ተቀብለዋል።   ሠልጣኞች ወደየ አካባቢያቸው ሲመለሱ ወንጌልን በማስፋፋት፣ የተዘጉ አብያተ ክርስቲያናትን በመክፈትና የክህነት አገልግሎት በመስጠት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናቸውን ያገለግላሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ መረጃው አመላክቷል።

ማኅበረ ቅዱሳን ያስተማራቸውንና ያሠለጠናቸውን ዲያቆናት አስመረቀ። ሐምሌ ፩/፳፻፲፰ ዓ.ም የማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል ከአርባ ምንጭ ማእከል ጋር በጋራ በመሆን ከጋሞና አከባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከ
+3
ማኅበረ ቅዱሳን ያስተማራቸውንና  ያሠለጠናቸውን ዲያቆናት አስመረቀ። ሐምሌ ፩/፳፻፲፰ ዓ.ም የማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል ከአርባ ምንጭ ማእከል ጋር በጋራ በመሆን ከጋሞና አከባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት፣ ከጎፋና ባስኬቶ ዞኖች ሀገረ ስብከት እና ከወላይታ ሀገረ ስብከት ከተለያዩ ወረዳዎች የተወጣጡ 11 ዲያቆናትን ሲያስተምርና ሲያሰለጥን ቆይቶ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ/ም ማዕረገ ቅስና እንዲቀበሉ በማድረግ አስመርቋል። በጋሞና አካባቢው ዞኖች ሀገረ ስብከት በአርባ ምንጭ ቅድስት ማርያም ገዳም አዳሪ አብነት ት/ቤት ሥልጠና ሲወስዱ የነበሩ ዲያቆናት ከሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ከብፁዕ አቡነ ኤልያስ ማዕረገ ቅስና ተቀብለው ተመርቀዋል ።   ሠልጣኝ ዲያቆናቱ የአገልጋይ እጥረት ካሉባቸው የሀገረ ስብከቱ የተለያዩ አካባቢዎች የተወጣጡ ሲሆኑ ማኅበረ ቅዱሳን የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ እና በማስተባበር ዲያቆናቱ ለማዕረገ ቅስና እንዲበቁ አድርጓል።   ማኅበረ ቅዱሳን አዳዲስ ተጠማቂያንና የአገልጋይ ካህናት እጥረት ካሉባቸው አካባቢዎች የተወጣጡ 11 ዲያቆናትን በመመልመል አሠልጥኖ ወደ አገልግሎት ማሠማራት በያዘው ስልታዊ ዕቅዱ መሠረት ሙሉ ወጫቸውን በመሸፈን ሲያሰለጥን ቆይቷል። ዲያቆናቱ ለማዕረገ ቅስና የሚያበቃቸውን ኪዳን፣ ሊጦን ፣ መስተብቁዕ እና ዋና ዋና የቅዳሴ ዜማዎችን ያካተተ ትምህርት ሲማሩ የቆዩ ሲሆን ከመሠረታዊው የክህነት ትምህርት ጎን ለጎን የትምህርተ ሃይማኖት ሥልጠናዎች ማለትም ትምህርተ ሃይማኖት መግቢያ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ፣የቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን፣ ምስጢራተ ቤተ ክርስቲያን፣ ነገረ ቅዱሳንና ነገረ ማርያም፣ ክርስቲያናዊ ሥነ-ምግባር፣ ሐዋርያዊ ተልእኮ፣ የስብከት ዘዴዎች እንዲሁም ተግባቦት ተሰጥተዋል።

በመጨረሻም  የየካ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት ዘካሪያስ ሐዲስ ከማእከሉ  እና ከሰንበት ት/ቤት አንድነት  ጋር ለመሥራት ያላቸው ፍላጎት እና ሁልጊዜም ለሚያደርጉት ቀና ትብብር ምስጋና ቀርቦ ሌሎች ክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ይህን አብሮ የማገልገል ተሞክሮ ልምድ ቢወስዱ ለቤተ ክርስቲያን ያለው አስተዋፅኦ ከፍተኛ መሆኑ ተገልጾ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል። መረጃው የማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ሚዲያ ነው።

ለዲያቆናት ፣ ካህናት እና ሰባክያነ ወንጌል ሥልጠና መሰጠቱ ተገለጸ። ሐምሌ ፩/፳፻፲፰ ዓ.ም በማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል የምሥራቅ ማስተባበሪያ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የካ ክፍለ ከተማ
+4
ለዲያቆናት ፣ ካህናት እና ሰባክያነ ወንጌል  ሥልጠና መሰጠቱ ተገለጸ። ሐምሌ ፩/፳፻፲፰ ዓ.ም በማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል የምሥራቅ ማስተባበሪያ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የካ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት እና ከሰ/ት /ቤት አንድነት ጋር በመተባበር ከ23 አድባራት ለተውጣጡ 291 ዲያቆናት፣ካህናት ፣ሰባክያነ ወንጌል በየካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ሥልጠና መሰጠቱን ማስተባበሪያው ገልጿል። የሥልጠናው ዓላማ ካህናት የንስሓ ልጆቻቸውን አያያዝ በተመለከተ፣ በቤተ ክርስቲያን የውስጥ ሥርዓት ላይ ማለትም ማሕሌት፣ ሰዓታት ፣ ኪዳን፣ ቅዳሴ ፣የዐውደ ምሕረት መርሐ ግብርና ሌሎች አገልግሎቶችም የቤተ ክርስቲያንን ሥርዓት በጠበቀ መልኩ እንዲከወኑ ማስቻል ዋና ዓላማ ተደርጎ እንደተዘጋጀ  ተገልጿል።  ሰባክያነ ወንጌል የአገልግሎት ድርሻቸው በዐውደ ምሕረት ላይ በተመደቡበት ዕለት በማስተማር ብቻ ተገድቦ እንዳይቀር ከካህናቱ ጋር በመመካከር የንስሓ ልጆቻቸውን ማስተማር ፣ ምእመናንን ማስተማር ፣ማነጽ እና ያላመኑትን አስተምሮ መመለስ እንደሚያስፈልግ እና ኀላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ለማድረግ ዓላማ ያደረገ መሆኑ በሥልጠናው ላይ ተጠቁሟል።  ሥልጠናው በጠቅላይ ቤተ ክህነት የመሪ ዕቅድ መምሪያ ዐቢይ ኮሚቴ አባል በሆኑት ቀሲስ ብሩህ ተስፋ ሥዩም የተሰጠ ሲሆን ከመርሐ ግብሩ ታዳሚዎች አስተያየትና ጥያቄ ተነሥቶ ምላሽ ተሰጥቷል። ከዚህ ሥልጠና በኋላ በቀጣይ ከየአድባራቱ አስተዳዳሪዎችእና ጸሓፊዎች  ጋር ውይይት ለማድረግ የታቀደ መሆኑን እና በየአጥቢያው የሚገኙ ካህናት፣ መሪጌቶች ፣ዲያቆናት፣ ሰባክያነ ወንጌል  አገልግሎቱን  በሚጠበቀው ልክ ለማድረግ እንደሚሠራ የክፍለ ከተማው ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ምሕረት ዘካሪያስ ሐዲስ ገልጸዋል።

ሁሉም አደነቁ ያን ጊዜም አንደበቱ ከድዳነት ተፈትቶለት ተናገረ፣ እግዚአብሔርንም ፈጽሞ አመሰገነው። ስለ ልጁና ስለ መድኃኒታችን መምጣት ልጁ ዮሐንስም የልዑል ነቢይ እንደሚባልና በእግዚአብሔርም ፊት እንደሚሄድ ትንቢት ተናገረ።http://www.eotcmk.org

ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ሰኔ ፴ በዚች ዕለት ነቢይ ሰማዕትና ሐዋርያ የሆነ መጥምቁ ዮሐንስ ተወለደ። ዮሐንስ ማለት እግዚአብሔር ጸጋ ነው ማለት ነው፡፡ትርጓሜ ወንጌልም መጥምቀ መለኮት ዮሐንስን ፍሥሐ ወ
ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ          ሰኔ ፴ በዚች ዕለት ነቢይ ሰማዕትና ሐዋርያ የሆነ መጥምቁ ዮሐንስ ተወለደ። ዮሐንስ ማለት እግዚአብሔር ጸጋ ነው ማለት ነው፡፡ትርጓሜ ወንጌልም መጥምቀ መለኮት ዮሐንስን ፍሥሐ ወሐሴት (ተድላናደስታ) ይለዋል ፤ወላጆቹ በእርሱ መወለድ ተደስተዋልና /ሉቃ.፩፥፲፬/፡፡በቅዱስ ወንጌል እንደ ተጻፈ ሄሮድስ የመድኀኒታችን የክርስቶስን መወለድ ከሰብአ ሰገል ሲሰማ መንግሥቴን ይወስድብኛል ብሎ ስለሠጋ ጌታችንን ያገኘሁ መስሎት የቤተልሔም ሕፃናትን መግደል ጀመረ/ማቴ.፪፥፩-፲፮/፡፡  በዚህ ጊዜ ቅድስት ኤልሳቤጥ ልጇን ከሞት ለማዳን ስትል ሕፃኑ ዮሐንስን ይዛ ወደ በረሃ ተሰደደች። በበረሃም ድንጋይ ቤት ሆኖላቸው፣እግዚአብሔርም ከብርድ፣ከፀሐይና ከአራዊቱ አፍ እየጠበቃቸው መኖር ጀመሩ፡፡ ወደ በረሃ ሲገቡ ቅዱስ ዮሐንስ የሁለት ዓመት ከመንፈቅ ሕፃን ነበር፡፡ ሕፃኑም አደገ ፤በመንፈስም ጠነከረ፤ ለእስራኤል እስከታየበት ቀን ድረስ በምድረ በዳ ኖረ /ሉቃ.፩፥፹/ተብሎ እንደተጻፈ፡፡ ይህም በእናቱ ማኅፀን ውስጥ ሳለ ለእግዚአብሔር ልጅ የሰገደው ነው፣  በመድኅነ ዓለም ክርስቶስ ራስ ላይ እጁን ጭኖ በውኃ ያጠምቀው ዘንድ የተገባው ነው። በቅዱስ ወንጌል እንደ ተነገረ ወንድ ልጅን ትወልድ ዘንድ የኤልሳቤጥ የፅንሷ ወራት በተፈጸመ ጊዜ ወንድ ልጅን ወለደች፤ ዘመዶቿና ጐረቤቶቿ እግዚአብሔር ቸርነቱን እንዳበዛላት በሰሙ ጊዜ ስለእርስዋ ደስ አላቸው። በስምንተኛውም ቀን ሊገዝሩት መጡ፣ በአባቱም ስም ዘካርያስ ብለው ጠሩት እናቱ ግን አይሆንም ዮሐንስ ይባል አለች። ”ከዘመዶችሽ ስሙ እንዲህ የሚባል የለም” አሏት። አባቱንም ጠቅሰው ”ማን ሊባል ትወዳለህ?”አሉት፤ እርሱም ብራና ለምኖ ስሙ ዮሐንስ ይባል ብሎ ጻፈ ።

✝️የጾም ቁርሳችን፣ ለወገኖቻችን✝️ +++ በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች እያጋጠሙ ባሉ ማኅበራዊ ቀውሶች( ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች፣ መፈናቀልና ጦርነት ) ብዙ ወገኖቻችን ለከፋ ችግር ተጋልጠዋል። እርስዎም ለእነዚህ ወገኖች የጾም ቁርስዎን በመለገስ ቸርነትን ያድርጉ! ድጋፍ ለማድረግ :- #በማኅበረ ቅዱሳን የማኅበራዊ ድጋፍና መልሶ ማቋቋም ሒሳብ ቁጥሮች፡- 1. በአሐዱ ባንክ - 0025393810901 2. በአቢሲንያ ባንክ - 37235458 3. በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - 1000309803648 4. በወጋገን ባንክ - 0837331610101 5. በወገን ፈንድ ፡- https://Www.wegenfund.com/mknu መጠቀም የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

የአዲስ አበባ ማእከል 109 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች በደረጃ አንድ ተተኪ መምህራን መመረቃቸውን ገለጸ። ሰኔ ፳፱/፳፻፲፰ ዓ.ም በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ዋና ክፍ
+3
የአዲስ አበባ ማእከል 109 የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች በደረጃ አንድ ተተኪ መምህራን መመረቃቸውን ገለጸ።   ሰኔ ፳፱/፳፻፲፰ ዓ.ም በማኅበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ማእከል ግቢ ጉባኤያት አገልግሎት ዋና ክፍል የግቢ ጉባኤያት ተቋማዊ ልማት ክፍል  በደረጃ አንድ ሲያሠለጥናቸው የቆዩ የግቢ ጉባኤ ተማሪዎችን ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓም ማስመረቁን በዋና ክፍሉ የግቢ ጉባኤያት ተቋማዊ ልማት ምክትል ኀላፊ መምህር መስፍን ግርማ ገልጸዋል። የሥልጠናው ዓላማ የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች ከቀለም ትምህርታቸው ጎን ለጎን የማስተማር ዐቅም ያላቸውን ተማሪዎች ሥልጠና በመስጠት በግቢ ጉባኤ የሚያገለግሉ ተተኪ መምህራንን ማፍራትና ማሰማራት ላይ ያለመ ነው። በዕለቱም ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ዶክተር ሙሉጌታ ሥዩም የማኅበረ ቅዱሳን ሥራ አመራር አባል ምክርና የአገልግሎት ልምዳቸውን ያካፈሉ ሲሆን በሥልጠናው ጥሩ አርአያ ላሳዩ ሁለት መምህራን የምስክር ወረቀት ተሰጥቷል ። በመጨረሻም የአዲስ አበባ ማእከል ሰብሳቢ ዲያቆን ኃይለ ማርያም መድኅን ለተመራቂዎች "ዛሬ የተመረቃችሁት የመጨረሻ ሳይሆን የመጀመሪያ መሆኑን አውቃችሁ ተጠያቂ መምህር ለመሆን እያነበባችሁና ከሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እየጠየቃችሁ እራሳችሁን አሳድጉ፣ በተሰጣችሁ መክሊት በማገልገል እንድታተርፉ፣ አገልግሎታችሁ በፍቅርና በትሕትና ይሁን" በማለት መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በሥልጠናው ጥሩ ውጤት ላመጡ 3 ተማሪዎች የመጽሐፍት ሽልማትና ለተመራቂዎች የአደራ መስቀል በቀሲስ ገዛኸኝ በቀለ ተሰጥቷቸው መርሐ ግብሩ ተጠናቋል። መረጃው ፦ በማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ሚዲያ ነው

ከዚህ ባሻገር ብፁዕነታቸው የብፁዕ አቡነ አብርሃምን መልእክት በሚያጠናክር መልኩ "ሊቃውንቱ ለቅድስት ቤተክርስቲያን አንድነት ፣ ከቀድሞው በበለጠ በጋራ ሊቆሙ ፣ አንድ ድምፅ ሁነውም ሊመክሩ ፣ ምክረ ሐሳባቸውንም ለቅዱስ ሲኖዶስ በትጋት ሊያቀርቡ" እንደሚገባ ጠቁመዋል። የተመራቂ ደቀመዛሙርት መምህር የሆኑት ሊቀ ሊቃውንት ስምዓ ኮነ መልአክ ተማሪዎቻቸው ለዚህ ደረጃ በመብቃታቸው መደስታቸውን ገልጸው በቀጣይም በምስክር ጉባኤ ቤቱ በነበራቸው ቆይታ የቀሰሙትን ጥንታዊ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ዕውቀት ተግባር ላይ በማዋል ለቤተ ክርስቲያንና ለሀገር የሚጠቅም አገልግሎት እንዲሰጡ አሳስበዋል። የምስክር ጉባኤ ቤቱ ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችን እያከናወነ ስለመሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን  በምርቃት በዓል ላይ ለመምህራን ማረፊያ እንዲሁም  ወደ ምስክር ጉባኤ ቤቱ ለሚመጡ እንግዶች መቀበያ የሚሆን ሕንጻ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል። ይህ አዲስ ሕንጻ  የጉባኤ ቤቱን የትምህርት ሥርዓት ለማጠናከር፣ ለተማሪዎችም የተሻለ የአስተዳደርና አገልግሎት ለመስጠት እንደሚያግዝ ተጠቁሟል። ©ፈለገ ገነት ሚዲያ

ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል - Estadísticas y analítica del canal de Telegram @mkpublicrelation