DW Amharic
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።
Show more- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Data loading in progress...
በቤጂንግ የግማሽ ማራቶን ውድድር ቻይናዊ ሯጭን ሆን ብለው አሸናፊ አድርገውታል የተባሉት ኢትዮጵያዊ እና ኬንያዊ አትሌቶች እንዲሁም ቻይናዊዉ አትሌት የወሰዱትን ሜዳሊያና ሽልማት ተነጠቁ። ኬንያ የመከላከያ ኢታማዦር ሹሙን ጨምሮ ሌሎች ዘጠኝ ከፍተኛ መኮንኖች በሄሊኮፕተር አደጋ ከሞቱ። ዛሬ በሃገሪቱ የሦስት ቀናት ሃዘን ታወጇል። በ1 ሚሊየን የምርጫ ጣቢያዎች ድምጻቸውን የሚሰጡ ህንዳውያን ለስድስት ሳምንታት የሚዘልቀዉን ምርጫ ዛሬ ጀመሩ። አሜሪካ በተመድ የፀጥታ ም/ቤት ውስጥ ሙሉ አባል ለመሆን ፍልስጤም ያቀረበችዉን ማመልከቻ ድምጽን በድምጽ የመሻር መብቷን ተጠቅማ ዉድቅ አደረገች።
oይነሥውር መሆኑ የስፖርት ዘገባ ከመሥራት እንዳላገደው ይናገራል።ጋዜጠኛ መረጃዎችን አሰባስቦ እና ተንትኖ ለአድማጮቹ የሚያደርስ መሆኑን የጠቀሰው ሙሉቀን “ እኔ ይህንኑ የዘገባ ሥራ ለዛውም በስፖርት ዘርፍ እየሠራሁ እገኛለሁ, እይታን ከሚፈልጉ ከኮሜንታተርነት እና ከዳኝነት ሥራዎች በስተቀር አንድ አይነ ሥውር ስፖርትን መዘገብ ይችላል» ብሏል ፡፡
በምዕራብ ወለጋ ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ የወባ በሽታ መስፋፋቱና ከ200 በላይ ሰዎች በወባ መታመማቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ። በዚህ ቶሌ በተባለው አካባቢ የሚገኙ ዜጎች የዛሬ ሁለት ዓመት ገደማ ተፈናቅለው ወሎ እና ደብረብርሃን ቆይቶ በየካቲት ወር 2016 መጀመሪያ ላይ ወደቤታቸው የተመለሱ ናቸው።
ባለፈው ሳምንት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ኦፊሰር በተገደሉበት ምሥራቅ ሸዋ ዞን መቂ ከተማ ከሰሞኑ በኅቡዕ ታወጀ ከተባለው የመጓጓዣ አገልግሎት እቀባ ጋር በተያያዘ ተሽከርካሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱ እየተነገረ ነው።
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ኦፊሰር የነበሩት ፖለቲከኛ በቴ ዑርጌሳ በአሰቃቂ ሁኔታ በትውልድ አካባቢያቸው መቂ ከተማ ተገድለው ከተገኙ 11 ቀናት አልፈዋል። በዚህ ጊዜ ውስጥም በርካቶችን ያስቆጣው የፖለቲከኛው ግድያ በርካታ ሁነቶችን አስተናግዷል።
የአማራና የትግራይ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች ግጭት መከሰቱ ለምን? ጠ/ሚ አቢይ አሕመድ ከመገናኛ ብዙኃን ተቋማትና ጋዜጠኞች ጋር እንዲወያዩ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ምክር ቤት መጠየቁ፤ በኢትዮጵያ ለሚታየዉው የከፋ የሰብዓዊ ቀውስ ምላሽ ለመስጠት በመንግሥትና ዓለምአቀፍ አጋሮች በተጠራው የገንዘብ ማሰባሰብ 610 ሚሊዮን ዶላር መሰብሰቡ።
በትግራይና አማራ አዋሳኝ አካባቢዎች የተከሰቱ ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ ብቻ መፈታት እንዳለባቸው ምሁራን አመለከቱ።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የልጃገረዶች ጠለፋ መባባሱ ተገለጠ። በክልሉ ኮሬ ዞን ውስጥ «እየተባባሰ መጥቷል» ባሉት ጠለፋ የተነሳ ሴት ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ መቸገራቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል። ቡርኪና ፋሶ ሦስት የፈረንሳይ ዲፕሎማቶችን ከሀገር አባረረች። ፈረንሳይ ውሳኔውን አሳዛኝ ብላዋለች። የደቡብ ሱዳን ፖለቲከኞች በሀገሪቱ ምርጫ ለማካሄድ አስቸኳይ እርምጃ መውሰድ እንዳለባቸው የተመድ አሳሰበ። ኢራን እስራኤል የኒኩሊየር ተቋሟ ላይ ጥቃት የምትሰነዝር ከሆነ በአጸፋው የእስራኤልን የኒኩሊየር መሰረተ ልማት ኢላማ እንደምታደርግ አስጠነቀቀች።
የወልቃይት፣ ጠገዴ ጠለምትና ራያ ጉዳይ በፖለቲካዊ ውሳኔ እንዲፈታ በአሜሪካ የሚገኙ 8 ኢትዮጵያ ሲቪክ ድርጅቶች ጥሪ አቀረቡ።