DW Amharic
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel DW Amharic
Channel DW Amharic (@dw_amharic) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 55 591 subscribers, ranking 4 723 in the News & Media category and 592 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 55 591 subscribers.
According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 392 over the last 30 days and by -10 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Verified (Officially confirmed by Telegram)
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 9.12%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 6.39% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 5 072 views. Within the first day, a publication typically gains 3 554 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 06 September | +12 | |||
| 05 September | +11 | |||
| 04 September | +15 | |||
| 03 September | +22 | |||
| 02 September | +27 | |||
| 01 September | +11 |
| 2 | የጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና
በየመን መንግስት ኃይሎችና «በኢራን ይደገፋሉ» የሚባሉት የሑቲ ደፈጣ ተዋጊዎች መካከል ትላንት አገርሽቶ እስከ ዛሬ በተካሄደ ውግያ ከሁለቱም ወገን ከ140 በላይ ወታደሮች መገደላቸውን ተሰማ። ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰላማዊ ሰዎችም ተገድለዋል ነው የተባለው።
በምሥራቅ ጀርመን በምትገኘው የዛክሰን አንሃልት ግዛት የአካባቢ ምርጫ እየተካሄደ ነው። የግዛቲቱ ምክር ቤት አባላት በሚመረጡበት ምርጫ እስካሁን ድምጽ የሰጡ መራጮች ቁጥር ከአምስት ዓመታት በፊት ከነበረው ከፍተኛ ብልጫ ያለው እንደሆነ የጀርመን ዜና አገልግሎት ዘግቧል
። በኔፓልና በቻይናዋ ቲቤት ድንበር በደረሰው የቅፅበታዊ ጎርፍ አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 1,400 ገደማ መድረሱን የየሐገራቱ ባለስልጣናት ዛሬ አስታወቁ። ደብዛቸው ያልታወቀ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በመኖራቸው የሟቾች ቁጥር ከዚህ ሊያሻቅብ እንደሚችልም ተነግሯ
ል። የአሜሪካው ፕረዚደንትዶናልድ ትራምፕ የሰላም መልዕክተኞች ዛሬ ክዬቭ ገብቷል። የልኡካንቡድኑ ወደ ዩክሬይን ያቀኑት ትላንት ከሩስያው ፕረዚደንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ከተነጋገሩ በኋላ ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ ሩስያበጥቁር ባሕር ትቀዝፍ የነበረች አንዲት የዩክሬይን ዕቃ ጫኝ መርከብ መምታቷን አስታውቃለች። መርከቧ ከምዕራባውያን ሐገራት ለዩክሬይን የተላከ የጦር መሳሪ ጭና ነበር ተብሏል።
https://pepurl.com/p/5Lmku?at_medium=Messenger&at_campaign=Telegram&at_channel=DW_Amharic&at_dw_language=am | 2 624 |
| 3 | በኢትዮጵያ ሰላም ለምን እውን መሆን አልቻለም?
የትግራዩ ክልሉ ጦርነት በውጪ ኃይሎች ፖለቲካዊ ተፅዕኖና በአፍሪቃ ሕብረት ሽምገላ በፕሪቶሪያ ውል ቢቋጭም ግጭት ጦርነቱ ግን በአማራ ክልል በሌላ መልኩ ቀጠለ:: ኦሮሚያም ሰላም ከራቃቸው ክልሎች ቀዳሚው ነው። በርከት ባሉ መደበኛና ኢመደበኛ ታጣቂና አማጻያን ፍልሚያ የሲቪሉ ማኀበረሰብ ኑሮ ለሰቀቀን ከተዳረገ ከርሟል።
https://pepurl.com/p/5LdKy?at_medium=Messenger&at_campaign=Telegram&at_channel=DW_Amharic&at_dw_language=am | 2 328 |
| 4 | ከፍተኛ ጫና ውስጥ የሚገኙት የፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ዓለም አቀፉን የእግር ኳስ አስተዳዳሪ ለመምራት በሚቀጥለው ዓመት በሚካሔደው ምርጫ ዳግም እንደሚወዳደሩ የተቋሙ ቃል አቀባይ አስታወቁ።
ፕሬዝዳንቱ በጎርጎሮሳዊው 2027 በሚካሔደው ምርጫ በድጋሚ እንደሚወዳደሩ በሚያዝያ ወር ማስታወቃቸውን ያስታወሱት የፊፋ ቃል አቀባይ “ምንም የተቀየረ ነገር የለም። ኢንፋኒቲኖ በድጋሚ ለመመረጥ ይቀርባሉ” ብለዋል።
ፊፋ የ56 ዓመቱ ስዊትዘርላንዳዊ በድጋሚ ለፕሬዝደንትነት እንደሚወዳደሩ ያረጋገጠው ከፍተኛ ተቃውሞ የቀሰቀሰ ዕቅድ ካቀረቡ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።
ኢንፋንቲኖ በፊፋ መርሐ-ግብሮች የግል ኢንቨስትመንት ለማካተት “ፊፋ ፎርዋርድ ኢንተርፕራይዝ” የተባለ ተቋም ለማቋቋም የጀመሩት ውጥን ከፍተኛ ተቃውሞ አስነስቶባቸው ነበር። ተሳክቶላቸው በድጋሚ ከተመረጡ እስከ ጎርጎሮሳዊው 2031 ፊፋን በፕሬዝደንትነት ይመራሉ። | 2 774 |
| 5 | በየመን መንግስት ኃይሎችና «በኢራን ይደገፋሉ» የሚባሉት የሑቲ ደፈጣ ተዋጊዎች መካከል ትላንት አገርሽቶ እስከ ዛሬ በተካሄደ ውግያ ከሁለቱም ወገን ከ140 በላይ ወታደሮች መገደላቸውን ተሰማ። ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰላማዊ ሰዎችም ተገድለዋል ነው የተባለው።
ትላንት ከሰዓት በኋላ በደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍል የሑቲ አማፅያን የባብ አል መንደብን ለመቆጣጠር የሚያስችሏቸውን ስልታዊ ቦታዎች መቆጣጠራቸውን ታውቋል። የሑቲ አማፅያኑን ግስጋሴን ለመግታት ሳውዲ ዓረብያ የየመን መንግስት ወታደሮችን በመደገፍ በሑቲዎች ላይ ከባድ የተባለለት የአየር ድብደባ ማካሄዷን መረጃዎች ያመላክታሉ።
እስከዛሬ በዘለቀው ውግያ ከመንግስት ወታደሮች 84፤ ከሑቲ አማፅያን ደግሞ 57ወታደሮች መገደላቸውን የሁለቱም ወገኖች የሚመለከታቸው ባለስልጣናት እንዳረጋገጡለት የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። | 2 700 |
| 6 | በዛክሰን አንሃልት ግዛት እየተካሔደ በሚገኘው ምክር ቤታዊ ምርጫ 1.7 ሚሊዮን ገደማ ዜጎች ድምጽ የሚሰጡ ሲሆን መላው ጀርመንና የተቀረው ዓለም በዐይነ ቁራኛ የሚከታተሉት ነው። ምርጫውን ቀኝ አክራሪው አማራጭ ለጀርመን (AFD) ፓርቲ ሊያሸንፍ እንደሚችል ይጠበቃል። https://tinyurl.com/mtpp3e7 | 2 769 |
| 7 | ትኩረት በአፍሪካ፤ የኒጀር ወቅታዊ ሁኔታ፤ የዛምቢያ የዴሞክራሲ እሴቶች መሸርሸር
« ፕሬዝደንቱ ወደፊት መራመድ አለባቸው። ወደፊት በሚጓዙበት ጊዜ በምርጫው ወቅት የገቡትን ቃል ኪዳን መተግበር አለባቸው። ይህ ማለት ድምፁን ለሳቸው የሰጣቸውም ያልሰጣቸውም ሁላችንም እኩል ነን። የሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ድምፅችን የሚደመጥበት በተለይ ወጣቶች ደግሞ ልዩ ትኩረት የሚያገኙበት እንዲሆን እፈልጋለሁ።»
https://p.dw.com/p/5LfK5?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 4 213 |
| 8 | https://tinyurl.com/2tzn722c | 3 747 |
| 9 | https://tinyurl.com/3fcpamdf | 486 |
| 10 | https://tinyurl.com/3fcpamdf | 3 169 |
| 11 | https://p.dw.com/p/5LfmX | 1 |
| 12 | https://tinyurl.com/2ja8cdkc | 1 |
| 13 | https://tinyurl.com/2ja8cdkc | 2 984 |
| 14 | https://tinyurl.com/4z7f7kzd | 3 047 |
| 15 | https://p.dw.com/p/5LgIn?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 3 196 |
| 16 | አሜሪካ በፋርስ ባሕረ ሰላጤ ሲቀዝፉ የነበሩ 3 የኢራን ነዳጅ ጫኝ መርከቦችን መትታ ማውደሟን የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ አስታወቀ። ዕዙ እንዳለው ጥቃቱ ኢራን በአካባቢው ባሉ የአሜሪካ የጦር መርከቦች ላይ ለፈጸመችው ጥቃት አጸፋ ነው።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ በመግለጫው ኢራን በአሜሪካ የአውሮፕላን ተሸካሚና «ዲስትሮየር» የተባሉ የጦር መርከቦች ላይ ተደጋጋሚ የሚሳይሎች ጥቃት ብትፈፅምም በሰው ሕይወት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም። በመርከቦቹ ላይ ጉዳት ስለመድረስ አለመድረሱ ግን ዜናው ያለው ነገር የለም።
መርከቦቹ የጫኑት ነዳጅ ለኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ የገቢ ምንጭ ሊሆን ታስቦ እንደነበረ ዕዙ ማከሉን አሶሽየትድ ፕረስ ዘግቧል። | 3 704 |
| 17 | የጀርመን መራሔ መንግስትፍሬደሪሽ ሜርስ «ለሩስያ ግልፅ መልዕክት አስተላልፈናል» አሉ
የጀርመን መራሄ መንግስት ፍሬደሪሽ ሜርስ መንግስታቸው ለድርጊቱ ሩስያን ተጠያቂ ማድረጉ፤ ሩስያ ከአሁን በኋላ በእንዲህ አይነት ተግባራት እንዳትቀጥል ግልጽ መልዕክት ያስተላለፈ ነው ብለዋል።
https://tinyurl.com/y5yj483n | 3 701 |
| 18 | የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ የአፍሪካን አህጉር ትክክለኛ ስፋት የሚያሳይ አዲስ የዓለም ካርታ ጥቅም ላይ እንዲውል የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ አፀደቀ።
በቶጎ አቅራቢነት እና በአፍሪካ ህብረት ደጋፊነት የቀረበውን ይህንን የውሳኔ ሀሳብ በ164 ሀገራት ድጋፍ ሲጸድቅ ፣አሜሪካ ብቸኛ ተቃዋሚ ሀገር ሆና ተመዝግባለች። 6 ሀገራት ደግሞ በዉሳኔው ላይ ድምፅ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
እስካሁን ጥቅም ላይ ሲውል የነበረው የመርኬተር ካርታ ከምድር ወገብ ርቀው የሚገኙ ሀገራትን አጉልቶ የሚያሳይ በመሆኑ የአህጉራትን እውነተኛ መጠን ያዛባ ነበር።
በነባሩ ካርታ ላይ ግሪንላንድ እና አፍሪካ እኩል ተደርገው ቢሳሉም፣ በእውነታው ግን አፍሪካ ከግሪንላንድ በ14 እጥፍ ያህል መብለጧ በጉባኤው ላይ በማሳያነት ቀርቧል።
ጉዳዩን በማነሳሳት ለጉባኤው እንዲቀርብ ያደረገችው የቶጎ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሮበርት ዱሴ ውሳኔውን "ታሪካዊ" ሲሉ አወድሰዉታል። ጉዳዩ «የካርታ ስራ ብቻ ሳይሆን የፍትህ፣ የክብር እና የእኩልነት» ጉዳይ መሆኑን ገልፀዋል።
አዲሱ የውሳኔ ሀሳብ ነባሩን ካርታ ሙሉ በሙሉ የሚያግድ ባይሆንም፣ ትምህርት ቤቶች፣ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች እና ዓለም አቀፍ ድርጅቶች በ2018 የተሰራውን እና ለችግሩ ምላሽ ይሰጣል የተባለውን የ"ኢኳል ኤርዝ" ካርታ እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርቧል።
የአፍሪካ ህብረት በበኩሉ ነባሩ የተዛባ ካርታ በትምህርት፣ በሚዲያ እና በፖለቲካ አስተሳሰብ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ ሲያሳድር መቆየቱን በመግለፅ አዲሱን ውሳኔ ደግፎታል። | 3 893 |
| 19 | በደቡብ ሱዳን ሰሜናዊ ምስራቅ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት 20 ሰዎች ተገደሉ ። አስራ ስድስቱ ወታደሮች እና ፖሊሶች ናቸው ። ጥቃቱ በድርቅ ምክንያት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለማወጅ የተገደ,ደችውን ሀገር ከፊት ለፊት በሚጠብቃት ምርጫ ላይ ብርቱ ፈተና ሳይደቅንባት አይቀርም ተብሏል።
የትናንት አርብ ጥቃት በጎሳዎች መካከል የሚደረግ የከብቶች ዘረፋን ተከትሎ የበቀል እርምጃ ሳይሆን እንዳልቀረ የሀገሪቱ የኢንፎርሜሽን ሚንስትር ዊልያም ዴንግ ቮል ተናግረዋል። እንደዚያም ሆኖ ግን ታጣቂዎቹ ጥቃቱን በአካባቢው በሚገኘው ወታደራዊ የጦር ሰፈር ላይ ለምን እንደፈጸሙ የታወቀ ነገር እንደሌለ ነው ሚንስትሩ የገለጹት።
የጎርጎርሳውያኑ አቆጣጠር በ 2018 በፕሬዚደንት ሳልቫኪር እና ሪክ ማቻር መካከል የተደረገው የስልጣን ክፍፍል ስምምነት በሀገሪቱ ሰላምን አምጥቶ የነበረ ቢሆንም ዘላቂ ሊሆን አልቻለም። በሀገር ክህደት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት ሪክ ማቻር በእስራት ላይ ይገኛሉ ። በዚህም የሁለቱን ወገን ደጋፊ ኃይሎች በተደጋጋሚ ደም አፋሳሽ ግጭቶች ውስጥ እንዲገቡ ምክንያት ሆኗቸዋል።
ባለፈው ወር በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የተሾመው የደቡብ ሱዳን የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ለረጅም ጊዜ ሲጠበቅ የነበረው ምርጫ አዲስ ግጭትን ሊቀሰቅስ እና በጭካኔ የተሞሉ ድርጊቶች የመፈጸም እድል ሊያባብስ ይችላል ብሏል። ኮሚሽኑ በዚህ ሳምንት ሌላ ተጨማሪ የመረጃ ማሰባሰብ ተልዕኮ ያካሂዳል ተብሎ ይጠበቃል። | 3 991 |
| 20 | የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዩክሬን ያለውን ጦርነት ለማስቆም ልዩ መልዕክተኞቻቸውን ወደ ሞስኮ እና ኪዬቭ ሊልኩ ነው። የትራምፕ ልዑካን ጃሬድ ኩሽነር እና ስቲቭ ዊትኮፍ ጉዞ ከተሳካ ወደ ኪዬቭ ሲጓዙ የመጀመሪያው ይሆናል።
ዶናልድ ትራምፕ ልዑካናቸው ወደ ሃገራቱ ይዘውት ስለሚሄዱት የሰላም ዕቅድ ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ቢቆጠቡም፣ "ለሰላም የሚሆን ጥሩ ሀሳብ አለን" ብለዋል።
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘሌንስኪ ልዑካኑ በሞስኮ ከሚያደርጉት ውይይት በኋላ ነገ እሁድ ወደ ኪየቭ እንደሚመጡ አረጋግጠዋል።
ዘሌንስኪ ድርድሩ በሰላም እንዲካሄድ ሲባል ዩክሬን በእነዚህ ቀናት የምታደርገውን የአየር ጥቃት እንደምታቆም ገልጸው፣ ሩሲያም ተመሳሳይ እርምጃ እንድትወስድ ጠይቀዋል።
በሌላ በኩል የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፓስኮቭ የአሜሪካ መልዕክተኞች ወደ ሞስኮ ስለመጣታቸው እስካሁን ማረጋገጫ አልሰጡም።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቪላድሚር ፑቲን በቅርቡ በሰጡት አስተያየት ከዩክሬን ጋር የሚደረገው የሰላም ውይይት መቆሙን ተናግረው ነበር ። | 3 810 |
