DW Amharic
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel DW Amharic
Channel DW Amharic (@dw_amharic) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 55 572 subscribers, ranking 4 723 in the News & Media category and 592 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 55 572 subscribers.
According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 392 over the last 30 days and by -10 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Verified (Officially confirmed by Telegram)
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 9.12%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 6.39% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 5 072 views. Within the first day, a publication typically gains 3 554 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 07 September | +2 | |||
| 06 September | +12 | |||
| 05 September | +11 | |||
| 04 September | +15 | |||
| 03 September | +22 | |||
| 02 September | +27 | |||
| 01 September | +11 |
| 2 | No text... | 949 |
| 3 | የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ለ8 መቶ 40 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ
የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል መንግስት መጪውን አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ ለ8 መቶ 40 የሕግ ታራሚዎች ይቅርታ አደረገ፡፡ የክልሉ ፍትህ ቢሮ ሃላፊ አቶ ሙሉቀን ታደሰ ለዶቼ ቬለ እንደገለጹት ታራሚዎቹ ይቅርታውን ያገኙት በማረሚያ ቤት ቆይታቸው ባሳዩት መልካም ሥነ-ምግባር እና በሕግ የተደነገገውን የይቅርታ መስፈርት አሟልተው በመገኘታቸው ነው ፡፡
በተጨማሪም በጤና ችግር፤ በዕድሜ መግፋትና ከሕጻናት ጋር አብረዉ የታሰሩ እንደነበሩ የጠቀሱት አቶ ሙሉቀን ከተፈረደባቸው ሲሶ እና ከግማሽ በላይ የፍርድ ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ መሆናቸውን ተናግረዋል ፡፡ተራሚዎቹ ይቅርታውን ያገኙት በይቅርታ አሰጣጥ ሥነ-ሥርዓት አዋጅ መሠረት ጉዳያቸው ለክልሉ መንግስት የይቅርታ ቦርድ ቀርቦ ተቀባይነት በማግኘቱ መሆኑን የቢሮው ሃላፊ ገልጸዋል ፡፡
የይቅርታው ተጠቃሚ የሆኑ የሕግ ታራሚዎች የይቅርታን እሴት ተላብሰው ሰላም ወዳድ፣ ለሕግ ተገዥና አምራች ዜጋ በመሆን የበደሉትን ህብረተሰብ በማገልግል በልማት ሊክሱ እንደሚገባ መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላሁን ከበደ “ ህብረተሰቡም ይቅርታ የተደረገላቸው የህግ ታራሚዎች በፈፀሙት ጥፋት የተፀፀቱና በአግባቡ ታርመው የወጡ መሆኑን በመረዳት መልካምና አምራች ዜጋ እንዲሆኑ አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግላቸው ጥሪዬን አቀርባለሁ “ ብለዋል ፡፡
ፎቶ፡ ከደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ፍትህ ቢሮ የተወሰደ | 958 |
| 4 | በምስራቅ ጀርመንዋ ፌደራዊ ግዛት ዛክሰን አንሀልት ትናንት እሁድ በተካሄደው የምክር ቤት ምርጫ በስፋት እንደተገመተው አማራጭ ለጀርመን በጀርመንኛው ምህጻሩ AfD እጅግ የላቀ ድምጽ በማሸነፍ ከፍተኛ ድል ተቀዳጅቷል። በሀገር አቀፍ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ ትኩረት ስቦ በቆየው በዚህ ምርጫ የጀርመን የሕገ መንግሥት ደኅንነት አስከባሪ መስሪያ ቤት ቀኝ ጽንፈኛ ብሎ የፈረጀው AfD በመጀመሪያ ደረጃ ውጤት 43.8 በመቶ ድምጽ ማሸነፉ ተረጋግጧል።
በዚሁ መሠረት ፓርቲው ከግዛቲቱ ምክር ቤት 83 መቀመጫዎች 39ኙን በማሸነፍ የዛክሰን አንሀልት ጠቅላይ ሚኒስትር የመሆን እድሉን በእጁ ያስገባ መስሎ ነበር። ይሁንና ከግዛቲቱ ምክር ቤት መቀመጫዎች ከ50 በመቶ የሚበልጡትን ባለማግኘቱ ይህ አይሆንለትም። በዚህ ምክንያትም ፓርቲው ተጣማሪ ማግኘት ይኖርበታል።
ሁለቱ ጀርመኖች የዛሬ 36 ዓመት እንደተዋሀዱ ለአራት ዓመታት ፤ከ8 ዓመት በኋላ ደግሞ እንደገና ለተከታታይ 25 ዓመታት ግዛቲቱን የመራው ወግ አጥባቂው የክርስቲያን ዴሞክራት ኅብረት ፓርቲ በጀርመንኛው ምህጻር CDU በምርጫው ከተጠበቀውም እጅግ አሽቆልቁሎ 17 በመቶ ድምጽ ብቻ ማግኘቱ አስደንግጧል።
ከCDU ጋር ተጣምረው ግዛቲቱን ሲያስተዳድሩ ከነበሩት ፓርቲዎች አንዱ አንጋፋው SPD ፣9.3 በመቶ ድምጽ ብቻ ሲያገኝ ሌላው ተጣማሪ የነጻ ዴሞክራቶቹ ፓርቲ ደግሞ 2.6 በመቶ ድምጽ ብቻ በማሸነፍ በግዛቲቱ ፓርላማ ውስጥ እንኳን መቀመጫ ማግኘት የማይችል ፓርቲ ሆኗል።
የጀርመን ነባር ፓርቲዎች ከAfD ጋር ለመስራት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ፓርቲው እስከዛሬ በ16ቱ የጀርመን ፌደራል ግዛቶች በጥምር መንግስት ውስጥ ተሳትፎ የለውም። ከአሁኑ ምርጫ ውጤት በኃላም እስካሁን ከፓርቲው ጋር ተጣምሮ መስራት እንደሚፈልግ የገለጸ ፓርቲ አልተገኘም። | 2 710 |
| 5 | በዛክሰን አንሃልት ግዛት በተካሔደው ምክር ቤታዊ ምርጫ ቀኝ አክራሪው አማራጭ ለጀርመን ከ44% በላይ ድምጽ በማግኘት እንደሚያሸንፍ መራጮች ድምጽ ሰጥተው ሲወጡ የተሰበሰበ አስተያየት አሳይቷል። የመራኄ መንግሥት ፍሬድሪሽ ሜርስ ክርስቲያን ዴሞክራት ኅብረት (CDU) በምርጫው ከተሰጡ ድምጾች 18.5% እንደሚያገኝ ይፋዊ ያልሆነው ውጤት አሳይቷል። https://tinyurl.com/4ttmy3s3 | 3 966 |
| 6 | የጳጉሜ 1 ቀን 2018 ዓ/ም የዓለም ዜና
በየመን መንግስት ኃይሎችና «በኢራን ይደገፋሉ» የሚባሉት የሑቲ ደፈጣ ተዋጊዎች መካከል ትላንት አገርሽቶ እስከ ዛሬ በተካሄደ ውግያ ከሁለቱም ወገን ከ140 በላይ ወታደሮች መገደላቸውን ተሰማ። ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰላማዊ ሰዎችም ተገድለዋል ነው የተባለው።
በምሥራቅ ጀርመን በምትገኘው የዛክሰን አንሃልት ግዛት የአካባቢ ምርጫ እየተካሄደ ነው። የግዛቲቱ ምክር ቤት አባላት በሚመረጡበት ምርጫ እስካሁን ድምጽ የሰጡ መራጮች ቁጥር ከአምስት ዓመታት በፊት ከነበረው ከፍተኛ ብልጫ ያለው እንደሆነ የጀርመን ዜና አገልግሎት ዘግቧል
። በኔፓልና በቻይናዋ ቲቤት ድንበር በደረሰው የቅፅበታዊ ጎርፍ አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር 1,400 ገደማ መድረሱን የየሐገራቱ ባለስልጣናት ዛሬ አስታወቁ። ደብዛቸው ያልታወቀ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በመኖራቸው የሟቾች ቁጥር ከዚህ ሊያሻቅብ እንደሚችልም ተነግሯ
ል። የአሜሪካው ፕረዚደንትዶናልድ ትራምፕ የሰላም መልዕክተኞች ዛሬ ክዬቭ ገብቷል። የልኡካንቡድኑ ወደ ዩክሬይን ያቀኑት ትላንት ከሩስያው ፕረዚደንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር ከተነጋገሩ በኋላ ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ ሩስያበጥቁር ባሕር ትቀዝፍ የነበረች አንዲት የዩክሬይን ዕቃ ጫኝ መርከብ መምታቷን አስታውቃለች። መርከቧ ከምዕራባውያን ሐገራት ለዩክሬይን የተላከ የጦር መሳሪ ጭና ነበር ተብሏል።
https://pepurl.com/p/5Lmku?at_medium=Messenger&at_campaign=Telegram&at_channel=DW_Amharic&at_dw_language=am | 4 141 |
| 7 | በኢትዮጵያ ሰላም ለምን እውን መሆን አልቻለም?
የትግራዩ ክልሉ ጦርነት በውጪ ኃይሎች ፖለቲካዊ ተፅዕኖና በአፍሪቃ ሕብረት ሽምገላ በፕሪቶሪያ ውል ቢቋጭም ግጭት ጦርነቱ ግን በአማራ ክልል በሌላ መልኩ ቀጠለ:: ኦሮሚያም ሰላም ከራቃቸው ክልሎች ቀዳሚው ነው። በርከት ባሉ መደበኛና ኢመደበኛ ታጣቂና አማጻያን ፍልሚያ የሲቪሉ ማኀበረሰብ ኑሮ ለሰቀቀን ከተዳረገ ከርሟል።
https://pepurl.com/p/5LdKy?at_medium=Messenger&at_campaign=Telegram&at_channel=DW_Amharic&at_dw_language=am | 3 619 |
| 8 | ከፍተኛ ጫና ውስጥ የሚገኙት የፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ዓለም አቀፉን የእግር ኳስ አስተዳዳሪ ለመምራት በሚቀጥለው ዓመት በሚካሔደው ምርጫ ዳግም እንደሚወዳደሩ የተቋሙ ቃል አቀባይ አስታወቁ።
ፕሬዝዳንቱ በጎርጎሮሳዊው 2027 በሚካሔደው ምርጫ በድጋሚ እንደሚወዳደሩ በሚያዝያ ወር ማስታወቃቸውን ያስታወሱት የፊፋ ቃል አቀባይ “ምንም የተቀየረ ነገር የለም። ኢንፋኒቲኖ በድጋሚ ለመመረጥ ይቀርባሉ” ብለዋል።
ፊፋ የ56 ዓመቱ ስዊትዘርላንዳዊ በድጋሚ ለፕሬዝደንትነት እንደሚወዳደሩ ያረጋገጠው ከፍተኛ ተቃውሞ የቀሰቀሰ ዕቅድ ካቀረቡ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።
ኢንፋንቲኖ በፊፋ መርሐ-ግብሮች የግል ኢንቨስትመንት ለማካተት “ፊፋ ፎርዋርድ ኢንተርፕራይዝ” የተባለ ተቋም ለማቋቋም የጀመሩት ውጥን ከፍተኛ ተቃውሞ አስነስቶባቸው ነበር። ተሳክቶላቸው በድጋሚ ከተመረጡ እስከ ጎርጎሮሳዊው 2031 ፊፋን በፕሬዝደንትነት ይመራሉ። | 3 585 |
| 9 | በየመን መንግስት ኃይሎችና «በኢራን ይደገፋሉ» የሚባሉት የሑቲ ደፈጣ ተዋጊዎች መካከል ትላንት አገርሽቶ እስከ ዛሬ በተካሄደ ውግያ ከሁለቱም ወገን ከ140 በላይ ወታደሮች መገደላቸውን ተሰማ። ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰላማዊ ሰዎችም ተገድለዋል ነው የተባለው።
ትላንት ከሰዓት በኋላ በደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍል የሑቲ አማፅያን የባብ አል መንደብን ለመቆጣጠር የሚያስችሏቸውን ስልታዊ ቦታዎች መቆጣጠራቸውን ታውቋል። የሑቲ አማፅያኑን ግስጋሴን ለመግታት ሳውዲ ዓረብያ የየመን መንግስት ወታደሮችን በመደገፍ በሑቲዎች ላይ ከባድ የተባለለት የአየር ድብደባ ማካሄዷን መረጃዎች ያመላክታሉ።
እስከዛሬ በዘለቀው ውግያ ከመንግስት ወታደሮች 84፤ ከሑቲ አማፅያን ደግሞ 57ወታደሮች መገደላቸውን የሁለቱም ወገኖች የሚመለከታቸው ባለስልጣናት እንዳረጋገጡለት የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። | 3 601 |
| 10 | በዛክሰን አንሃልት ግዛት እየተካሔደ በሚገኘው ምክር ቤታዊ ምርጫ 1.7 ሚሊዮን ገደማ ዜጎች ድምጽ የሚሰጡ ሲሆን መላው ጀርመንና የተቀረው ዓለም በዐይነ ቁራኛ የሚከታተሉት ነው። ምርጫውን ቀኝ አክራሪው አማራጭ ለጀርመን (AFD) ፓርቲ ሊያሸንፍ እንደሚችል ይጠበቃል። https://tinyurl.com/mtpp3e7 | 3 513 |
| 11 | ትኩረት በአፍሪካ፤ የኒጀር ወቅታዊ ሁኔታ፤ የዛምቢያ የዴሞክራሲ እሴቶች መሸርሸር
« ፕሬዝደንቱ ወደፊት መራመድ አለባቸው። ወደፊት በሚጓዙበት ጊዜ በምርጫው ወቅት የገቡትን ቃል ኪዳን መተግበር አለባቸው። ይህ ማለት ድምፁን ለሳቸው የሰጣቸውም ያልሰጣቸውም ሁላችንም እኩል ነን። የሚቀጥሉት አምስት ዓመታት ድምፅችን የሚደመጥበት በተለይ ወጣቶች ደግሞ ልዩ ትኩረት የሚያገኙበት እንዲሆን እፈልጋለሁ።»
https://p.dw.com/p/5LfK5?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 4 644 |
| 12 | https://tinyurl.com/2tzn722c | 4 091 |
| 13 | https://tinyurl.com/3fcpamdf | 486 |
| 14 | https://tinyurl.com/3fcpamdf | 3 541 |
| 15 | https://p.dw.com/p/5LfmX | 1 |
| 16 | https://tinyurl.com/2ja8cdkc | 1 |
| 17 | https://tinyurl.com/2ja8cdkc | 3 356 |
| 18 | https://tinyurl.com/4z7f7kzd | 3 411 |
| 19 | https://p.dw.com/p/5LgIn?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 3 611 |
| 20 | አሜሪካ በፋርስ ባሕረ ሰላጤ ሲቀዝፉ የነበሩ 3 የኢራን ነዳጅ ጫኝ መርከቦችን መትታ ማውደሟን የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ አስታወቀ። ዕዙ እንዳለው ጥቃቱ ኢራን በአካባቢው ባሉ የአሜሪካ የጦር መርከቦች ላይ ለፈጸመችው ጥቃት አጸፋ ነው።
የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ በመግለጫው ኢራን በአሜሪካ የአውሮፕላን ተሸካሚና «ዲስትሮየር» የተባሉ የጦር መርከቦች ላይ ተደጋጋሚ የሚሳይሎች ጥቃት ብትፈፅምም በሰው ሕይወት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም። በመርከቦቹ ላይ ጉዳት ስለመድረስ አለመድረሱ ግን ዜናው ያለው ነገር የለም።
መርከቦቹ የጫኑት ነዳጅ ለኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ የገቢ ምንጭ ሊሆን ታስቦ እንደነበረ ዕዙ ማከሉን አሶሽየትድ ፕረስ ዘግቧል። | 4 131 |
