en
Feedback
DW Amharic

DW Amharic

Open in Telegram

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel DW Amharic

Channel DW Amharic (@dw_amharic) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 54 821 subscribers, ranking 4 819 in the News & Media category and 577 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 54 821 subscribers.

According to the latest data from 18 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -105 over the last 30 days and by -7 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Verified (Officially confirmed by Telegram)
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 8.39%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 6.09% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 602 views. Within the first day, a publication typically gains 3 338 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 19 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

54 821
Subscribers
-724 hours
+37 days
-10530 days
Posts Archive
የሥርጭት ማስታወቂያ ሥርጭታችን እንደወwሮው በዓለም ዜና ይጀምራል። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ትላንት ሐሙስ “አክራሪ” ባላቸው የህወሓት አመራሮች እና በቤተሰቦቻቸው ላይ የቪዛ ማዕቀብ ጥሏል።
የሥርጭት ማስታወቂያ ሥርጭታችን እንደወwሮው በዓለም ዜና ይጀምራል። የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ትላንት ሐሙስ “አክራሪ” ባላቸው የህወሓት አመራሮች እና በቤተሰቦቻቸው ላይ የቪዛ ማዕቀብ ጥሏል። የውጭ ጉዳይ ሚስትር ማርኮ ሩቢዮ እርምጃውን የወሰዱት በህወሓት እና በፌድራል መንግሥት በተካረሩበት ወቅት ነው። ማዕቀቡን የተመለከቱ ዘገባዎች በዛሬው የዜና መፅሔት ይቀርባሉ። በተጨማሪም የዎላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ እና የኢዜማ ዕጩዎች ባለፈው ግንቦት 24 ቀን 2018 በተካሔደው ምርጫ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና በክልል ምክር ቤቶች መቀመጫ ማሸነፋቸውን ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አውጇል። ምክር ቤቶቹን የሚቀላቀሉትን የተቃዋሚ ፖለቲከኞች ስለምርጫው ውጤት የዶቸ ቨለ ዘጋቢ አነጋግሯቸዋል። እነዚህን ጨምሮ በዛሬው የዜና መጽሔት በአምስት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ ዘገባዎች ይቀርባሉ። ሣምንታዊው የከወጣቶች ዓለም ዝግጅት አሜሪካ፣ ካናዳና ሜክሲኮ በጋራ ያዘጋጁትን የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች የሚመለከት ነው። እንድትከታተሉን በአክብሮት እንጋብዛለን።

ዶይቼ ቬለ የጦማረ-ዜና (Newsletter )አገልግሎት ተጠቃሚ ይሁኑ! የተወደዳችሁ የዝግጅታችን ታዳሚያን ከስርጭታችን ውስጥ በየሳምንቱ አንዴ ተመርጦ እንዲላክላችሁ የምትፈልጓቸው የጦማረ ዜና (New
ዶይቼ ቬለ የጦማረ-ዜና (Newsletter )አገልግሎት ተጠቃሚ ይሁኑ! የተወደዳችሁ የዝግጅታችን ታዳሚያን ከስርጭታችን ውስጥ በየሳምንቱ አንዴ ተመርጦ እንዲላክላችሁ የምትፈልጓቸው የጦማረ ዜና (Newsletter ) ስብስቦችን በቀጥታ በኢሜል አድራሻዎ እንዲላክልዎ ከፈለጉ ከስር ባለው ማገናኛ ውስጥ ባለው ባዶ ቦታ የኢሜል አድራሻዎን በማስገባት የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ትችላላችሁ። ከስር ቀጥሎ በሰፈረ ክፍት ቦታ ላይ እስማማለሁ የአጠቃቀም ደንብ.* የሚለውን በመጫን «ያስገቡ» የሚለውን ሲነኩ በቀላሉ ተመዘገቡ ማለት ነው ። የዚሁ አገልግሎታችን ተጠቃሚ እንድትሆኑ ተጋብዛችኋል። የዶይቼ ቬለ የጦ ማረ-ዜና (Newsletter)አገልግሎት https://syst em.promio-connect.com/register/16401/default/am/single-registration/83494

ሩስያ በዩክሬንዋ የኻርካይቭ ከተማ ዛሬ ፈጸመችው በተባለ የአየር ጥቃት ቢያንስ 9 ሰላማዊ ሰዎች መቁሰላቸውን የሐገሪቱ ባለስልጣናት አሳወቁ። ከተጎዱት ውስጥ አራቱ ሕጻናት ናቸው ተብሏል። የኻርካይቭ
ሩስያ በዩክሬንዋ የኻርካይቭ ከተማ ዛሬ ፈጸመችው በተባለ የአየር ጥቃት ቢያንስ 9 ሰላማዊ ሰዎች መቁሰላቸውን የሐገሪቱ ባለስልጣናት አሳወቁ። ከተጎዱት ውስጥ አራቱ ሕጻናት ናቸው ተብሏል። የኻርካይቭ ከተማ ከንቲባ ኢሆር ትራኮቭ በቴሌልራም ገጻቸው ያጋሩትን ጠቅሶ የጀርመን ዜና አገልግሎት እንደዘገበው በጥቃቱ ከ40 በላይ የመኖሪያ ቤቶች ላይ ጉዳት ደርሷል። ከሩስያ ድንበር 40 ኪሎሜትሮች ርቃ የምትገኘው ኻርካይቭ ከጦርነቱ በፊት 1.4 ሚልዮን ሕዝብ ይኖርባት እንደነበር መረጃዎች ያመላክታሉ። በዩክሬይንና ሩስያ ጦርነት ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ከተማዋ ተደጋጋሚ የሩስያ የሚሳይልና የአየር ድብደባዎችን ማስተናገዷን ዜናው አክሏል።

የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ «እስራኤል በቀጣናው ቋሚ ጦርነት እንዲኖር ትፈልጋለች» ሲሉ ነቀፉ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ይህን ነቀፌታ የሰነዘሩት በእስራኤል አጣማሪ መንግስት የብሔራዊ
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ «እስራኤል በቀጣናው ቋሚ ጦርነት እንዲኖር ትፈልጋለች» ሲሉ ነቀፉ። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ይህን ነቀፌታ የሰነዘሩት በእስራኤል አጣማሪ መንግስት የብሔራዊ ደህንነት ሚኒስትር ኢታማር ቤን ጋቪር 4 የእስራኤል ወታደሮች በኢራን ይደገፋል በሚባለው ሒዝቦላህ ዛሬ መገደላቸውን ተከትሎ በማሕበራዊ መገናኛ ዘዴአቸው «ኢራን መቃጠል አለባት» የሚል መልእክት ካጋሩ በኋላ ነው። አራግቺ አክለውም «ይህ የዘፈቀደ የዘር ማፅዳት ዕብደት አይደለም፤ በአንድ የእስራኤል የደህንነት ሚኒስትር የተለጠፈ እንጂ» ብለዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አክለውም «እስራኤል በቀጠናው ቋሚ ጦርነት እንዲኖር ትፈልጋለች» በማለት ከስሷል።

የምርጫ ውጤቶች እና ፓርቲዎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ እስከ አሁን የ723 የምርጫ ክልል ውጤቶችን ማፅደቁንና የቀሪ ምርጫ ክልሎች ውጤት ደግሞ በኦዲት ሥራ ላይ እንደሚገኝ አሳውቋል ፡፡ ቅሬታ ከቀረበባቸው 129 የምርጫ ክልሎች ውስጥ 75ቱን ማስረጃ ያልቀረበባቸው ናቸው በመባሉ ውድቅ ሲደረጉ፤ 10ሩ በንግግር ቅሬታቸውን ማንሳታቸውና የተቀሩት ግን በማጣራት ሂደት ላይ እንደሚገኙ ቦርዱ መግለጹ ይታወቃል ፡፡ ከአሸናፊ ፓርቲዎች መካከል ደግሞ አንዳንዶች በቀጣይ ምን እንደሚሠሩ ለዶይቸ ቬለ ተናግረዋል ። በደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የዎላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያ ግንባርን በመወከል ለፌዴራል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ካሸነፉት መካከል አቶ ጎበዜ ጎኣ «አሁን በሕዝባችን የተሰጠንን አደራ ተቀብለን እያንዳንዱን የመንግሥት ክፍተቶች በማሳየትና ችግሮች በወቅቱ እንዲታረሙ በማድረግ ለዜጎች የሚመች አገር ለመፍጠር እንሠራለን “ ብለዋል ፡፡ በዚሁ የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የተወካዮች እና የክልል ምክር ቤት መቀመጫዎችን ካገኙት ፓርቲዎች መካከል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ ኢዜማን በመወከል የክልል ምክር ቤት መቀመጫ አሸናፊ የሆኑት አቶ ዳያሞ ዳሌ ፓርቲያቸው «በሁለቱም ምክር ቤቶች በቅድሚያ ለሰላም እና የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ በሚያስችሉ አጀንዳዎች ላይ ትኩረተ ሰጥቶ እንደሚሠራ ገልጸዋል።#ምርጫ2018 #EthiopiaElection2026 https://pepurl.com/p/5FiyT?maca=amh-RED-Telegram-dwcom

የምርጫ ውጤቶች እና ፓርቲዎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ እስከ አሁን የ723 የምርጫ ክልል ውጤቶችን ማፅደቁንና የቀሪ ምርጫ ክልሎች ውጤት ደግሞ በኦዲት ሥራ ላይ እንደሚገኝ አሳውቋል ፡፡ ቅሬታ ከቀረበባቸው 129 የምርጫ ክልሎች ውስጥ 75ቱን ማስረጃ ያልቀረበባቸው ናቸው በመባሉ ውድቅ ሲደረጉ፤ 10ሩ በንግግር ቅሬታቸውን ማንሳታቸውና የተቀሩት ግን በማጣራት ሂደት ላይ እንደሚገኙ ቦርዱ መግለጹ ይታወቃል ፡፡ ከአሸናፊ ፓርቲዎች መካከል ደግሞ አንዳንዶች በቀጣይ ምን እንደሚሠሩ ለዶይቸ ቬለ ተናግረዋል ። በደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የዎላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያ ግንባርን በመወከል ለፌዴራል የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ካሸነፉት መካከል አቶ ጎበዜ ጎኣ «አሁን በሕዝባችን የተሰጠንን አደራ ተቀብለን እያንዳንዱን የመንግሥት ክፍተቶች በማሳየትና ችግሮች በወቅቱ እንዲታረሙ በማድረግ ለዜጎች የሚመች አገር ለመፍጠር እንሠራለን “ ብለዋል ፡፡ በዚሁ የደቡብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የተወካዮች እና የክልል ምክር ቤት መቀመጫዎችን ካገኙት ፓርቲዎች መካከል የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ ኢዜማን በመወከል የክልል ምክር ቤት መቀመጫ አሸናፊ የሆኑት አቶ ዳያሞ ዳሌ ፓርቲያቸው «በሁለቱም ምክር ቤቶች በቅድሚያ ለሰላም እና የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ በሚያስችሉ አጀንዳዎች ላይ ትኩረተ ሰጥቶ እንደሚሠራ ገልጸዋል።#ምርጫ2018 #EthiopiaElection2026 https://pepurl.com/p/5FiyT?maca=amh-RED-Telegram-dwcom

አብዛኛው የጀርመን ሕዝብ የጀርመን ጦር በሆርሙዝ ሰርጥ የፀጥታ ማስከበር ሥራ የድርሻውን እንደሚወጣ መግለጹን በአዎንታ እንደሚደግፉት አንድ ጥናት አረጋገጠ። ZDF የተባለ የዜና ማሰራጫ ጣቢያ ጥናቱን
አብዛኛው የጀርመን ሕዝብ የጀርመን ጦር በሆርሙዝ ሰርጥ የፀጥታ ማስከበር ሥራ የድርሻውን እንደሚወጣ መግለጹን በአዎንታ እንደሚደግፉት አንድ ጥናት አረጋገጠ። ZDF የተባለ የዜና ማሰራጫ ጣቢያ ጥናቱን ያካሄደው 1,190 ሰዎችን በመጠየቅ ሲሆን አመራረጡም በድንገተኛ ሆኖ በስልክና በኢንተርኔት መካሄዱን አሳውቋል። እ.አ.አ. ከሰኔ 16 እስከ 18 2026 ዓ.ም በተካሄደ ጥናት 57% የጥናቱ ተሳታፊዎች የጀርመን ተሳትፎን ሲደግፉ 38% ደግሞ እንደማይደግፉ መግለጻቸውን የጀርመን ዜና አገልግሎት ዘግቧል።

እስራኤል ሌሊቱን ለዛሬ አጥቢያ በደቡብ ሊባኖስ በፈጸመችው የአየር ጥቃት 18 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን የሊባኖስ ባለስልጣናት አሳወቁ። እስራኤል በበኩሏ 4 ወታደሮቿ በሂዝቦላህ ጥቃት መገደላቸውን ገ
እስራኤል ሌሊቱን ለዛሬ አጥቢያ በደቡብ ሊባኖስ በፈጸመችው የአየር ጥቃት 18 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን የሊባኖስ ባለስልጣናት አሳወቁ። እስራኤል በበኩሏ 4 ወታደሮቿ በሂዝቦላህ ጥቃት መገደላቸውን ገልጻለች። የሊባኖስ የጤና ሚኒስቴር ዛሬ እንዳሳወቀው በ10 ገጠራማ መንደሮችና ከተሞች ከእኩለ ሌሊት እስከ ንጋት በተካሄደ መጠነ ሰፊ የአየር ድብደባ 18 ሰዎች ሞተው 33 ቆስለዋል። የእስራኤል የመከላከያ ሰራዊት በበኩሉ በደቡብ ሊባኖስ የሒዝቦላህ ይዞታዎች ናቸው ባላቸው የጦር ሰፈሮቻ ላይ ጥቃት ማድረሱን ገልጿል። የመከላከያ ሰራዊቱ አክሎም በኢራን ይደገፋል የሚባለው ሒዝቦላህ በፈጸመው የሮኬትና የከባድ መሣሪያዎች ጥቃት አንድ ኮለኔል የሚገኝባቸው 4 ወታደሮቹ መገደላቸውን አሳውቋል።

በአለፈው የጎርጎሮሳውያኑ 2025 ዓ.ም ጦርነት ባለባቸው ቀጣናዎች ወደ 25,000 በሚጠጉ ሕጻናት ላይ ግድያን ጨምሮ የተለያዩ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እንደተፈጸመባቸው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት
በአለፈው የጎርጎሮሳውያኑ 2025 ዓ.ም ጦርነት ባለባቸው ቀጣናዎች ወደ 25,000 በሚጠጉ ሕጻናት ላይ ግድያን ጨምሮ የተለያዩ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እንደተፈጸመባቸው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባወጣው ሪፖርት ይፋ አደረገ። ለጥሰቱ ታጣቂዎችን ሳይሆን የመንግስት የጸጥታ ኃይሎችን ዋና ተጠያቂ አድርጓል። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶንዮ ጉተረዥ ዓመታዊ ሪፖርት፤ በህጻናቱ ላይ ይደርሳሉ ብሎ ከዘረዘራቸው የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ግድያ፣ አስገድዶ መድፈር፣ አስገዳጅ ወታደራዊ ምልመላ፣ ትምህርት ቤቶችና ሆስፒታሎች ላይ ጥቃት ማድረስ ይገኙባቸዋል። በጥቃት መዘርዝሩ የእስራኤል ጦር 12,445 ጥሰቶችን በማስመዝገብ የመጀመሪያውን ረድፍ ይዟል። ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ 4,114 የሕጻናት ጥቃቶችን በማስመዝገብ ትከተላለች። በሚያንማር፣ ሶማሊያ፣ ናይጄሪያ ከ2,000 በላይ ጥሰቶች መመዝገባቸውን ሪፖርቱ አመላክቷል። የዜናው ምንጭ አሶሽየትድ ፕረስ ነው።

በአሜሪካና ኢራን መካከል ዛሬ በስዊዘርላንድ ታቅዶ የነበረው የሰላም ስምምነት የፊርማ ሥነሥርአት መሰረዙን የስዊትዘርላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ጠቅሶ የፈረንሳይ ዜ
በአሜሪካና ኢራን መካከል ዛሬ በስዊዘርላንድ ታቅዶ የነበረው የሰላም ስምምነት የፊርማ ሥነሥርአት መሰረዙን የስዊትዘርላንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱን ጠቅሶ የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት እንደዘገበው ለዛሬ የታቀደው የስምምነት ፊርማ የማኖር ሥነ ሥርአት መሰረዙን ቢገልፅም ለመሰረዙ የሰጠው ምክንያት የለም። ሚኒስቴር መስሪያቤቱ የመፈረራረም ስነ ስርአቱን ተግባራዊ ለማድረግ እየጣረ መሆኑን ቢገልጽም ቀጣይ የተያዘ ቀነ ቀጠሮ ስለመኖሩም ያለው ነገር የለም። ለሥነስርአቱ መሰረዝ እስራኤል ሌሊቱን ለዛሬ አጥቢያ በደቡብ ሊባኖስ ፈጸመችው የተባለው የአየር ጥቃት ሳይሆን እንዳልቀረ የፖለቲካ ተንታኞች ግምታቸውን ሰጥተዋል።