en
Feedback
DW Amharic

DW Amharic

Open in Telegram

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel DW Amharic

Channel DW Amharic (@dw_amharic) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 54 772 subscribers, ranking 4 795 in the News & Media category and 575 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 54 772 subscribers.

According to the latest data from 08 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -58 over the last 30 days and by -6 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Verified (Officially confirmed by Telegram)
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 7.88%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 5.49% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 314 views. Within the first day, a publication typically gains 3 006 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 09 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

54 772
Subscribers
-624 hours
+47 days
-5830 days
Posts Archive
https://pepurl.com/p/5GpvG ?maca=amh-RED-Telegram-dwcom

ዱባይ-የቀድሞዉ የኢራን ላዕላይ መሪ አያቶላሕ ዓሊ ኻምኔይ ተቀበሩ ዩናይትድ ስቴትስና እስራኤል ባለፈዉ የካቲት ማብቂያ ላይ የገደሏቸዉ የኢራን የፖለቲካና የኃይማኖት መሪ አያቶላሕ ዓሊ ኻምኔይ ዛሬ ተ
ዱባይ-የቀድሞዉ የኢራን ላዕላይ መሪ አያቶላሕ ዓሊ ኻምኔይ ተቀበሩ ዩናይትድ ስቴትስና እስራኤል ባለፈዉ የካቲት ማብቂያ ላይ የገደሏቸዉ የኢራን የፖለቲካና የኃይማኖት መሪ አያቶላሕ ዓሊ ኻምኔይ ዛሬ ተቀበሩ።እስራኤልና ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን ላይ ጦርነት በከፈቱበት ዕለት እግአ የካቲት 28 ቀን 2026 ከኻምኔይ ሌላ ሴት ልጃቸዉን፣ የልጅ ልጃቸዉን፣ አማቻቸዉንና 11 ባለሥልጣኖቻቸዉን ገድለዋል።ባለቤታቸዉም ክፉኛ ቆስለዉ ኋላ ሞተዋል።የኻምኔይን ሥልጣን የያዙት ያሁኑ የኢራን ላዕላይ መሪ ሞጅታባ ኻምኔይም የዚያን ቀን ቆስለዋል።ሞጅታባሕ የላዕላይ መሪነቱን ሥልጣን ቢይዙም እስከ ዛሬ ድረስ ለሕዝብ እይታ አልቀረቡም።ካለፈ,ዉ ሳምንት ጀምሮ ለአባታቸዉ በተደረገዉ የሽኝት ሥርዓትም ሆነ በዛሬዉ የቀብር ሥርዓት ላይ አልተገኙም።ኢራንን ከ30 ዓመታት በላይ የመሩት ዓሊ ኻምኔይ ዛሬ የተቀበሩት በሐገሪቱ ሰሜን-ምሥራቅ ቅዱስ የቀብር ሥፍራ ማሻሐ,ድ ዉስጥ ነዉ።ማሽሐድ የኻሚኔይ የትዉልድ ሥፍራም ናት።የኻምኔይ አስከሬን ወደ ቀብሩ ስፍራ ከመወሰዱ ከሰዓታት በፊት የዩናይትድ ስቴትስ ጦር ርዕሠ-ከተማ ቴሕራንን ከማሻሐድ ከተማ ጋር የሚያገኛኘዉን የባቡር መስመር ጨምሮ የተለያዩ የኢራን ሰላማዊ የመሠረተ-ልማት አዉታሮችን አዉድሟል።ይሁንና በቀብር ሥርዓቱ ላይ ለመገኘት በመቶ ሺሕ የሚቆጠር የኢራን ሕዝብ የማሻሐድ ከተማን አጥለቅልቋት ነዉ የዋለዉ።ሕዝቡ በሺዓ እስልምና እምነት የብቀላ ጥሪ ምልክት የሆነዉን ቀይ አርማ እያዉለበለበ እስከ ቀብሩ ሥፍራ ድረስ ተጉዟል።

ቴሕራን-የዩናይትድ ስቴትስና የኢራን አዲስ ግጭት ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን ከትናንት በስቲያ ሌሊት የጀመሩት አዲስ ጥቃትና አፀፋ ጥቃት እስከ ዛሬ ጠዋት ድረስ እንደቀጠለ ነዉ።የዩናይትድ ስቴትስ ጦር
ቴሕራን-የዩናይትድ ስቴትስና የኢራን አዲስ ግጭት ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን ከትናንት በስቲያ ሌሊት የጀመሩት አዲስ ጥቃትና አፀፋ ጥቃት እስከ ዛሬ ጠዋት ድረስ እንደቀጠለ ነዉ።የዩናይትድ ስቴትስ ጦር ትናንት ደቡባዊና ማዕከላዊ ኢራን የሚገኙ የተለያዩ ከተሞችና ደሴቶችን ደብድቧል።የኢራን ባለሥልጣናት ዛሬ እንዳስታወቁት የአሜሪካ ጦር ትናንት ማታ በከፈተዉ ጥቃት 14 ሰዎች ገድሏል።ሌሎች 78 አቁስሏል።አንዳድ ከተሞች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋርጦም ነበር።የዩናይትድ ስቴትስ ማዕከላዊ ዕዝ እንዳስታወቀዉ ጦሩ አዲስ ጥቃት የከፈተዉ ኢራን በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚተላለፉ መርከቦችን የማወክ አቅሟን ለማዳከም ነዉ። እስራኤልና ዩናይትድ ስቴትስ ባለፈዉ የካቲት ማብቂያ ኢራን ላይ ጦርነት ከመክፈታቸዉ በፊት ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን የባሕር መሥመር የሚያዉክ እርምጃ ወስዳ አታዉቅም።የአሜሪካ ጦር ትናንት በኢራን ከተሞች፣ ደሴቶችና ተቋማት ላይ የከፈተዉን ጥቃት ለመበቀል የኢራን ጦር ኃይል ዛሬ ሲነጋጋ በተለያዩ የአረብ ሐገራት የሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሠፈሮችን አጥቅቷል።የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ እንዳስታወቀዉ ጦሩ ባሕሬይንና ኩዌት የሚገኙ የዩናይትድ ስቴትስ የጦር ሠፈሮችን ደብድቧል።ወደ ዮርዳኖስም 10 ቦሊስቲክ ሚሳዮሎች ማወንጨፉን አስታዉቋል። ዮርዳኖስ በበኩሏ ጦር ኃይሏ 8 የኢራን ሚሳዬሎችን «አክሽፏል» ብላለች።የኢራን መንግሥት የሚቆጣጠረዉ አንድ ራዲዮ ጣቢያ ዛሬ ማርጃዉን እንደዘገበዉ የኢራን ጦር ባሕሬይን ባሕር ላይ የሚገኙ የዩናይትድ ስቴትስ ባሕር ሰርጓጅ መርከብንና ሌሎች የጦር መርከቦችን ደብድቧል።ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን ከሁለት ሳምንት በፊት የተፈራረሙት የተኩስ አቁም ሥምምነት መፍረሱን የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ትናንት አስታዉቀዉ ነበር።

EANC ኤርትራ ዉስጥ የሐገሪቱ አንድነት ተጠብቆ፤ የአፋርን ጨምሮ የሐገሪቱ ነባር ብሔሮች የባሕል፣ የቋንቋ፣ የማንነት፣ የምጣኔ ሐብትና የፖለቲካ ነፃነት የተከበረባት ፌደራዊ ሥርዓት እንዲመሠረት እን
EANC ኤርትራ ዉስጥ የሐገሪቱ አንድነት ተጠብቆ፤ የአፋርን ጨምሮ የሐገሪቱ ነባር ብሔሮች የባሕል፣ የቋንቋ፣ የማንነት፣ የምጣኔ ሐብትና የፖለቲካ ነፃነት የተከበረባት ፌደራዊ ሥርዓት እንዲመሠረት እንደሚታገል አስታዉቋል።በመግለጫዉ መሠረት በ3ኛዉ የEANC ጉባኤ ላይ ከኢትዮጵያና ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጨምሮ የተለያዩ ማሕበራት፣ ድርጅቶችና የሕብረተሰብ ክፍሎችን የወከሉ ፖለቲከኞች፣ ተንታኖች፣ሙሕራን፣ ባሕላዊ መሪዎችና የሐገር ሽማግሌዎች ተካፍለዋል።

ኤርትራዉያን ዴሞክራሲያዊ ሽግግር ለማድረግ እንዲተባበሩ EANC ጠየቀ የኤርትራ አፋር ብሔራዊ ኮንግረስ (EANC) ኤርትራ ዉስጥ «በሠላማዊ መንገድ» ዴሞክራሲያዊ ለዉጥ ለማምጣት የሐገሪቱ «ዴሞክራሲያ
ኤርትራዉያን ዴሞክራሲያዊ ሽግግር ለማድረግ እንዲተባበሩ EANC ጠየቀ የኤርትራ አፋር ብሔራዊ ኮንግረስ (EANC) ኤርትራ ዉስጥ «በሠላማዊ መንገድ» ዴሞክራሲያዊ ለዉጥ ለማምጣት የሐገሪቱ «ዴሞክራሲያዊ» የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶችና የተለያዩ የሕብረተሰብ አካላት እንዲተባበሩ ጠየቀ።ኮንግረሱ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ፣ ድርጅቶችና የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ዉይይት፣ ድርድርና መግባባታቸዉን አጠናክረዉ እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርቧልም። EANC ባለፈዉ ሳምንት አርብና ቅዳሜ ባደረገዉ 3ኛ ጉባኤዉ ማጠቃላያ ላይ ባወጣዉ መግለጫ እንዳለዉ የወደፊቷ ኤርትራ «በአምባገነን» ሥርዓት፣ «በአግላይነት» ወይም አንዱ ሌላዉን «በመጫን» ላይ ልትመሠረት አትችልም።በ8 ገፆች የተጠናቀረዉ መግለጫ ኢትርትራ ዉስጥ ሰብአዊ መብቶች፣ የተለያዩ ብሔሮች መብቶች፣ እንዲከበሩና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲሰፍን የሚደረገዉን ጥረት የተለያዩ ዓለም አቀፍ፣ አሐጉራዊና አካባቢያዊ ማሕበራትና መንግሥታት እንዲረዱ ጠይቋል። ጉባኤዉ በተለይ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኤርትራ ዉስጥ ይደርሳል የሚባለዉን የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን መከታተሉን እንዲቀጥል ጠይቆ፣ ኤርትራ በቅርቡ የተባበሩት መንግሥታት የምጣኔ ሐብትና የማሕበራዊ ጉዳይ ምክር ቤት (ECOSOC) አባል ሆና በመመረጥዋ ያደረበትን ቅሬታ ገልጿል።ኤርትራ ዉስጥ የሚፈፀመዉን ግፍና በደል በመሸሽ ከ200 ሺሕ በላይ የኤርትራ አፋሮች መፈናቀላቸዉን ወይም መሰደዳቸዉን መግለጫዉ «አሳዛኝ» ብሎታል።

ታንዛኒያ ውስጥ ሥልጡን የውይይት መድረክ ሲጠፋ ወጣቶች እጃቸውን አጣጥፈው አልqt,ቀመጡም፥ ይልቁንስ የፖለቲካ ውይይቱን ወደ ማኅበራዊ መገናኛ መድረክ ወስደው አነቃቅተውታል ። ታንዛኒያዊው ሙዚቀኛ እና አራማጁ አርቲስት ዋካዚ ስለ ዲሞክራሲ እየተጠናከረ የመጣውን የዲጄታል ንቅናቄ እየመራ ነው #africaexplained https://pepurl.com/p/5Gmi2?maca=amh-RED-Telegram-dwcom