cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

DW Amharic

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Більше
Рекламні дописи
42 067Підписники
+3924 години
+2807 днів
+1 41930 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

Показати все...
የዓለም ዜና፦ ሚያዚያ 18 ቀን 2016 ዓ.ም.

የሚያዚያ 18 ቀን 2016 ዓ.ም. አርዕሰተ ዜና የአፍሪቃ ሕብረት «የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው» በሚል የተሰራጨው መረጃ «የተሳሳተ» ነው ሲል የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ አስታወቀ። የሶማሊያ መንግሥት ራሽን በመስረቅ የተጠረጠሩ በዩናይትድ ስቴትስ የሰለጠኑ የልዩ ኮማንዶ አባላት ማገዱንና ማሰሩን አስታወቀ። በጋዛ ሰርጥ አስቸኳይ ፣ቅድመ ሁኔታ የሌለውና ዘላቂ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ቻይና ጥሪ አቀረበች። የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ በጋዛ የተኩስ አቁም ላይ እንዲደረስ በጸጥታው ምክር ቤት የሚደረገውን ጥረት ማደናቀፍ እንዲቆምም ጠይቃለች።

የሚያዚያ 18 ቀን 2016 ዓ.ም. አርዕሰተ ዜና የአፍሪቃ ሕብረት «የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው» በሚል የተሰራጨው መረጃ «የተሳሳተ» ነው ሲል የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ አስታወቀ። የሶማሊያ መንግሥት ራሽን በመስረቅ የተጠረጠሩ በዩናይትድ ስቴትስ የሰለጠኑ የልዩ ኮማንዶ አባላት ማገዱንና ማሰሩን አስታወቀ። በጋዛ ሰርጥ አስቸኳይ ፣ቅድመ ሁኔታ የሌለውና ዘላቂ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ቻይና ጥሪ አቀረበች። የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ በጋዛ የተኩስ አቁም ላይ እንዲደረስ በጸጥታው ምክር ቤት የሚደረገውን ጥረት ማደናቀፍ እንዲቆምም ጠይቃለች። https://p.dw.com/p/4fEoL?maca=amh-RED-Telegram-dwcom 👉🏾 @dwamharicbot
Показати все...
የዓለም ዜና፦ ሚያዚያ 18 ቀን 2016 ዓ.ም.

የሚያዚያ 18 ቀን 2016 ዓ.ም. አርዕሰተ ዜና የአፍሪቃ ሕብረት «የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው» በሚል የተሰራጨው መረጃ «የተሳሳተ» ነው ሲል የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ አስታወቀ። የሶማሊያ መንግሥት ራሽን በመስረቅ የተጠረጠሩ በዩናይትድ ስቴትስ የሰለጠኑ የልዩ ኮማንዶ አባላት ማገዱንና ማሰሩን አስታወቀ። በጋዛ ሰርጥ አስቸኳይ ፣ቅድመ ሁኔታ የሌለውና ዘላቂ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ቻይና ጥሪ አቀረበች። የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ በጋዛ የተኩስ አቁም ላይ እንዲደረስ በጸጥታው ምክር ቤት የሚደረገውን ጥረት ማደናቀፍ እንዲቆምም ጠይቃለች።

Показати все...
የሶማሊላንዷ ሀርጌሳና በርበራ ወደብ በጋዜጠኛው ዕይታ

ሶማሊላንድ ከሶማሊያ እራሷን በመነጠል እራስ ገዝ ከሆነች ሦስት አስርት ዓመታት አለፉ። ዛሬም ግን ሶማሊላንድ እንደ ሀገር ዓለም አቀፍ እውቅና አላገኘችም።

Показати все...
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስለ አፍሪቃ ሕብረት ምን አለ?

የአፍሪቃ ሕብረት «የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው» በሚል የተሰራጨው መረጃ «የተሳሳተ» ነው ሲል የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ አስታወቀ።

Показати все...
ምርጫ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስድስተኛው ዙር ቀሪና ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ምርጫ እንደሚካሄድ አስታወቀ። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ አፋር፣ ሶማሌና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ በሚገኙ ምርጫ ክልሎች የምርጫ ማስፈጸሚያ ጊዜ ሴለዳ ቦርዱ ይፋ አድርጓል።

Показати все...
በአፍሪቃ የጸረ- ሺብር ትግል ላይ የመከረ ከፍተኛ ስብሰባ

በአፍሪቃ እየተስፋፋና እየተጠናከረ ነው የተባለውን የአሸባሪዎች ጥቃት ለመክላከል ብሎም ለማጥፋት በሚቻልበት ሁኔታ የመከረ የአፍርቃ የጸረ ሽብርና ደህንነት ከፍተኛ ጉባኤ በዚህ ሳምንት ሰኞና ማክሰኞ በናይጀሪያ ዋና ከተማ አቡጃ ተካሂዷል።

Показати все...
የመንግሥት መግለጫ፣የቀጠለው የቤቶች ፈረሳ ፣የህንጻዎች መደርመስ

«የሽግግር ፍትህ ብቸኛ መፍትሄ አይሆንም ሌሎች አማራጮች ይፈተሹ መፈናቀል ለወረኞች በር ይከፍታል የተባለው ለመፈናቀል ምክንያት የሆኑ ችግሮች በጊዜ መፍትሄ ስላልተሰጣቸው ነው መንግስት ሀገር መምራት ከጀመረባት ቀን አንስቶ የተፈጠሩ አለመግባባቶች በጊዜው በሽግግር ፍትህ መታከም ነበረባቸው አሁን ከመጨረሻ መጀመሩ ይከብዳል።»

የሚያዝያ 17 ቀን 2016 ዓ.ም. ዋና ዋናዎች፤ የሰላም ሚኒስትር ደኤታ የነበሩት አቶ ታዬ ደንደአ በዛሬ ዕለት የፀረሰላም ኃይሎችን በመደገፍና ጦር መሣሪያ ይዞ በመገኘት ወንጀል ክስ ተመሰረተባቸው። ታንዛኒያ ውስጥ በደረሰ የጎርፍ አደጋ የ155 ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር አስታወቁ። እስያ ውስጥ ደግሞ በሙቀት ማዕበል ሰዎች እየሞቱ ነው። ቱርክና ግሪክ ከሰሃራ በመጣ አቧራ አየራቸው ታፍኗል። ማዕከላዊ ናይጀሪያ ውስጥ ከባድ ዝናብ በአንድ እስር ቤት ላይ ጉዳት ማድረሱን ተከትሎ 120 የሚሆኑ እስረኞች ማምለጣቸው ተሰማ። ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኢትዮጵያም ሆነ በመላው ዓለም የወባ በሽታ ስርጭት በእጅጉ መስፋፋቱ እና የሚያደርሰው ጉዳትም እየከፋ መምጣቱ ተገለጸ። ዝርዝሩን ያድምጡ ያንብቡ https://p.dw.com/p/4fC8H?maca=amh-RED-Telegram-dwcom 👉🏾 @dwamharicbot
Показати все...
የሚያዝያ 17 ቀን 2016 ዓ.ም. የዓለም ዜና

የሰላም ሚኒስትር ደኤታ የነበሩት አቶ ታዬ ደንደአ በዛሬ ዕለት የፀረሰላም ኃይሎችን በመደገፍና ጦር መሣሪያ ይዞ በመገኘት ወንጀል ክስ ተመሰረተባቸው። ታንዛኒያ ውስጥ በደረሰ የጎርፍ አደጋ የ155 ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር አስታወቁ። እስያ ውስጥ ደግሞ በሙቀት ማዕበል ሰዎች እየሞቱ ነው። ቱርክና ግሪክ ከሰሃራ በመጣ አቧራ አየራቸው ታፍኗል። በማዕከላዊ ናይጀሪያ ከባድ ዝናብ በእስር ቤት ላይ ጉዳት ማድረሱን ተከትሎ 120 የሚሆኑ እስረኞች ማምለጣቸው ተሰማ። ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኢትዮጵያም ሆነ በመላው ዓለም የወባ በሽታ ስርጭት በእጅጉ መስፋፋቱ እና የሚያደርሰው ጉዳትም እየከፋ መምጣቱ ተገለጸ።

Показати все...
የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለታጣቂዎች ያቀረበዉ ጥሪና ተግዳሮቱ

አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ፍልስፍና ረዳት ፕሮፈሰር ሲሳይ አሰምሬ የኮሚሽኑን ገለጻ ለመረዳት መቸገራቸውን ይናገራሉ፡፡ “ኮሚሽኑ የታጠቁ አካላት መንግስት ያስረናል ይጮቅነናል በሚል ነው ትጥቅ አንግበው በራሳቸው መንገድ የሚታገሉት

Показати все...
በአሸባሪነት የተከሰሱ ተጠርጣሪዎች የችሎት ውሎ

በዛሬው ችሎት ዐቃቤ ሕግ ክስ ማሻሻል ምስክሮችን ለጉዳት የሚዳርግ ነው በሚል ያንን ማድረግ እንደማይችል በጽሑፍ አቤቱታ አቅርቧል። የተከሳሽ ጠበቆችም በበኩላቸው በቃል ክርክር በማድረግ ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ የተከሳሾችን ጥያቄ እንዲመልስ ተከራክረዋል።