DW Amharic
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።
نمایش بیشتر- مشترکین
- پوشش پست
- ER - نسبت تعامل
در حال بارگیری داده...
در حال بارگیری داده...
የሚያዚያ 18 ቀን 2016 ዓ.ም. አርዕሰተ ዜና የአፍሪቃ ሕብረት «የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው» በሚል የተሰራጨው መረጃ «የተሳሳተ» ነው ሲል የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ አስታወቀ። የሶማሊያ መንግሥት ራሽን በመስረቅ የተጠረጠሩ በዩናይትድ ስቴትስ የሰለጠኑ የልዩ ኮማንዶ አባላት ማገዱንና ማሰሩን አስታወቀ። በጋዛ ሰርጥ አስቸኳይ ፣ቅድመ ሁኔታ የሌለውና ዘላቂ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ቻይና ጥሪ አቀረበች። የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ በጋዛ የተኩስ አቁም ላይ እንዲደረስ በጸጥታው ምክር ቤት የሚደረገውን ጥረት ማደናቀፍ እንዲቆምም ጠይቃለች።
የሚያዚያ 18 ቀን 2016 ዓ.ም. አርዕሰተ ዜና የአፍሪቃ ሕብረት «የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው» በሚል የተሰራጨው መረጃ «የተሳሳተ» ነው ሲል የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ አስታወቀ። የሶማሊያ መንግሥት ራሽን በመስረቅ የተጠረጠሩ በዩናይትድ ስቴትስ የሰለጠኑ የልዩ ኮማንዶ አባላት ማገዱንና ማሰሩን አስታወቀ። በጋዛ ሰርጥ አስቸኳይ ፣ቅድመ ሁኔታ የሌለውና ዘላቂ የተኩስ አቁም እንዲደረግ ቻይና ጥሪ አቀረበች። የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ በጋዛ የተኩስ አቁም ላይ እንዲደረስ በጸጥታው ምክር ቤት የሚደረገውን ጥረት ማደናቀፍ እንዲቆምም ጠይቃለች።
ሶማሊላንድ ከሶማሊያ እራሷን በመነጠል እራስ ገዝ ከሆነች ሦስት አስርት ዓመታት አለፉ። ዛሬም ግን ሶማሊላንድ እንደ ሀገር ዓለም አቀፍ እውቅና አላገኘችም።
የአፍሪቃ ሕብረት «የውጭ ምንዛሪ ሒሳቡን ወደ ሌላ ሀገር ሊያዘዋውር ነው» በሚል የተሰራጨው መረጃ «የተሳሳተ» ነው ሲል የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስድስተኛው ዙር ቀሪና ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸው የሀገሪቱ አካባቢዎች ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም ምርጫ እንደሚካሄድ አስታወቀ። በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ አፋር፣ ሶማሌና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ በሚገኙ ምርጫ ክልሎች የምርጫ ማስፈጸሚያ ጊዜ ሴለዳ ቦርዱ ይፋ አድርጓል።
በአፍሪቃ እየተስፋፋና እየተጠናከረ ነው የተባለውን የአሸባሪዎች ጥቃት ለመክላከል ብሎም ለማጥፋት በሚቻልበት ሁኔታ የመከረ የአፍርቃ የጸረ ሽብርና ደህንነት ከፍተኛ ጉባኤ በዚህ ሳምንት ሰኞና ማክሰኞ በናይጀሪያ ዋና ከተማ አቡጃ ተካሂዷል።
«የሽግግር ፍትህ ብቸኛ መፍትሄ አይሆንም ሌሎች አማራጮች ይፈተሹ መፈናቀል ለወረኞች በር ይከፍታል የተባለው ለመፈናቀል ምክንያት የሆኑ ችግሮች በጊዜ መፍትሄ ስላልተሰጣቸው ነው መንግስት ሀገር መምራት ከጀመረባት ቀን አንስቶ የተፈጠሩ አለመግባባቶች በጊዜው በሽግግር ፍትህ መታከም ነበረባቸው አሁን ከመጨረሻ መጀመሩ ይከብዳል።»
የሰላም ሚኒስትር ደኤታ የነበሩት አቶ ታዬ ደንደአ በዛሬ ዕለት የፀረሰላም ኃይሎችን በመደገፍና ጦር መሣሪያ ይዞ በመገኘት ወንጀል ክስ ተመሰረተባቸው። ታንዛኒያ ውስጥ በደረሰ የጎርፍ አደጋ የ155 ሰዎች ሕይወት መጥፋቱን የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር አስታወቁ። እስያ ውስጥ ደግሞ በሙቀት ማዕበል ሰዎች እየሞቱ ነው። ቱርክና ግሪክ ከሰሃራ በመጣ አቧራ አየራቸው ታፍኗል። በማዕከላዊ ናይጀሪያ ከባድ ዝናብ በእስር ቤት ላይ ጉዳት ማድረሱን ተከትሎ 120 የሚሆኑ እስረኞች ማምለጣቸው ተሰማ። ባለፉት ጥቂት ዓመታት በኢትዮጵያም ሆነ በመላው ዓለም የወባ በሽታ ስርጭት በእጅጉ መስፋፋቱ እና የሚያደርሰው ጉዳትም እየከፋ መምጣቱ ተገለጸ።
አስተያየታቸውን ለዶይቼ ቬለ የሰጡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ፍልስፍና ረዳት ፕሮፈሰር ሲሳይ አሰምሬ የኮሚሽኑን ገለጻ ለመረዳት መቸገራቸውን ይናገራሉ፡፡ “ኮሚሽኑ የታጠቁ አካላት መንግስት ያስረናል ይጮቅነናል በሚል ነው ትጥቅ አንግበው በራሳቸው መንገድ የሚታገሉት
በዛሬው ችሎት ዐቃቤ ሕግ ክስ ማሻሻል ምስክሮችን ለጉዳት የሚዳርግ ነው በሚል ያንን ማድረግ እንደማይችል በጽሑፍ አቤቱታ አቅርቧል። የተከሳሽ ጠበቆችም በበኩላቸው በቃል ክርክር በማድረግ ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ የተከሳሾችን ጥያቄ እንዲመልስ ተከራክረዋል።