DW Amharic
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።
نمایش بیشتر📈 تحلیل کانال تلگرام DW Amharic
کانال DW Amharic (@dw_amharic) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 55 605 مشترک است و جایگاه 4 717 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 592 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 55 605 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 02 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 518 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 17 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید شده (به صورت رسمی توسط تلگرام)
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 9.20% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 6.64% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 5 113 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 3 692 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 03 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 03 سپتامبر | +22 | |||
| 02 سپتامبر | +27 | |||
| 01 سپتامبر | +11 |
| 2 | የውጭ ተዋጊዎች እና ድጋፍ ሰጭ ኃያሎች የሱዳኑን ግጭትና በሲቪሎች ላይ የሚፈጸመውን ጥቃት እያባባሱ ነው ሲል አንድ በተባበሩት መንግሥታት የሚደገፍ መርማሪ ቡድን አስታወቀ። ድርጅቱ የሾመው የምርመራ ቡድን በሱዳኑ ጦርነት የውጭ ኃይሎች ተሳትፎ የተዋጊዎቹን ወታደራዊ አቅም በማጠናከር የተራቀቁ ወታደራዊ ዘመቻዎችን እንዲያካሂዱ በማስቻል በሰላማዊ ሰዎች ላይ አስከፊ መዘዞች እያስከተሉ ነው ሲል አስታውቋል።
ቡድኑ ባቀረበው ዘገባ መሠረት የሱዳኑን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ለመደገፍ የውጭ ተቀጣሪዎች ፣ የውጭ ተዋጊዎችን ይመለምላሉ ፣ያሰለጥናሉ፣ ያዘምታሉ። ድንበር ተሻጋሪ ኃይሎችም የጦር መሳሪያዎች ተተኳሾች ወታደራዊ ቴክኖሎጂ እና ልዩ ልዩ ድጋፎችም ጭምር እንደሚያደርጉ በዘገባው ጠቅሷል።
የሱዳን መደበኛ ጦርም በሚያካሂዳቸው ዘመቻዎች ሲቭሎችንና የሲቪል መሠረተ ልማቶችን የሚጎዱ ከውጭ የተሰጡትን ድሮኖችን እንደሚጠቀም የሚያሳምኑ ብዙ ምክንያቶች እንደነበሩም በምርመራው ውጤት አመልክቷል።
የቡድኑ ሊቀ መንበር ሞሀመድ ቻንዴ ኦትማን እንዳሉት ከውጭ የሚገኘው ድጋፍ ለሲቪሎች ሊደረግ የሚገባ ሰፊ ጥበቃ አላመጣም ። ከዚያ ይልቅ ኦትማን ሰላማዊ ሰዎች ቤቶቻቸው፣ ሆስፒታሎች ትምሕርት ቤቶች ገበያዎች እና የስደተኞች መጠለያዎች ላይ በሚደርስ ጥቃት ከፍተኛ ዋጋ እየከፈሉ ነው ብለዋል። የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ምርመራውን ካስጀመረ የፊታችን ጥቅምት ወር ሦስት ዓመት ይደፍናል። ከተጀመረ ሦስት ዓመት ተኩል ገደማ ያስቆጠረው በሱዳን ጦርና በፈጥኖ ደራሹ ኃይል መካከል የሚካሄደው ውጊያ በአስር ሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ገድሏል ፤ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩትን ደግሞ ከቀያቸው አፈናቅሏል። | 889 |
| 3 | https://p.dw.com/p/5L1lS?maca=amh-RED-Telegram-dwcom@dwamharicbot | 856 |
| 4 | ኔፓል እና ቲቤት ውስጥ በደረሰው የጎርፍ አደጋ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ከአንድ ሺህ 200 መብለጡን ባለሥልጣናት አስታወቁ። አደጋው በደረሰ በስምንተኛው ቀን ዛሬም 4875 ሰዎች ይሙቱ ይኑሩ አልታወቀም።
ዛሬ በወጡ መግለጫዎች መሠረት ያሉበት ካልታወቀው መካከል ፣601 የውጭ ዜጎች ይገኙበታል። የጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት በሁለቱም ሀገራት ደብዛቸው የጠፋ ዜጎቹ ቁጥር ከፍተኛ ነው ብሎ እንደሚገምት አስታውቋል። በርካታ የብሪታንያ ዜጎችም የደረሱበት አይታወቅም።
ከተገኙት በአደጋውከሞቱ ሰዎች አስከሬኖች መካከል የአብዛኛዎቹ ማንነት ገና አልተለየም። በአንዳንድ ሁኔታዎችም የሰዎች አጥንቶች ብቻ እንደተገኙም የእርዳታ ሠራተኞች ተናግረዋል።
የበረዶ ክምርና የድንጋይ ናዳም የተቀላቀለበት ጎርፍ አንዳንድ መንደሮችን ሙሉ በሙሉ ጠራርጎ በመውሰዱ በቢሊዮንች ዶላር የሚቆጠር ንብረትም እንዳልነበር ሆኗል። የተመድ እንደሚለው በአደጋው ወደተጎዳው አካባቢ እርዳታ ማቀበሉ ፣መንገዶች በመዘጋጋታቸው ምክንያት እጅግ አስቸጋሪ ሆኗል። | 1 641 |
| 5 | ኢራን ዛሬ ኩዌት በሚገኙ የዩናይትድ ስቴትስ ወታደራዊ ጦር ሰፈሮች ላይ የሚሳይልና የድሮን ጥቃት ፈጸመች። የኢራን ጦር እንዳስታወቀው ኩዌት የሚገኘውን የአህመድ አል ጃበር የአየር ኃይል ጦር ሰፈር ዛሬ በሚሳይሎችና በድሮኖች መቷል።
የኩዌት ጦር ሠራዊት በበኩሉ ከኢራን የተተኮሰ አንድ ሚሳይልና አንድ ድሮን አክሽፌያለሁ ብሏል። ኢራን ከዚህ ሌላ በተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች የሚገኘውን የአል ሚንሀድ የአየር ኃይል ጦር ሰፈርንም እንደመታች አስታውቃለች። የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ግን በበጦር ሰፈሩ ደረሰ ስለተባለው ጥቃት ምንም አላለችም።
ጥቃቱን በዜጎቿ እንዲሁም በሀገሪቱ ነዋሪዎች ደኅንነት እና መረጋጋት ላይ ቀጥተኛ ስጋት ያስከተለ ያለችው ኩዌት ሎሎች ዓለም አቀፍ ሕግጋትንም የሚጥስ ስትል ኮንናለች። ቴህራን እንዳለችው የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች ኩዌት ባህሬን ዮርዳኖስ ኢራቅ እና ኩርዲስታን ግዛቶች የሚገኙ የአሜሪካን የጦር ሰፈሮችና ኃይሎች የጥቃት ዒላማዎቿ ናቸው።
የዛሬው የኢራን ጥቃት በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን ላይ ለጣለችው ጥቃት የተወሰደ የአጸፋ እርምጃ ነው። | 2 334 |
| 6 | ሩስያ የሚገኙ የጀርመን የጎቴ ተቋም ቅርንጫፎችን እንደምትዘጋ ሞስኮ አስታወቀች
የጀርመን እና የሩስያ ውዝግብ ዛሬም እንደቀጠለ ነው። በዛሬው እለት ሩስያ በሀገርዋ የሚገኙ የተለያዩ የጀርመን የጎቴ ተቋም ቅርንጫፎችን እንደምትዘጋ አስታውቃለች። ሩስያ ይህን ያለችው በርሊን ቦን የሚገኘውን የሩስያ የባህል ማዕከል ለመዝጋት ትዕዛዝ ባስተላለፈች በማግስቱ ነው።
በጀርመን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የገንዘብ ድጋፍ የሚንቀሳቀሰው የጎቴ ተቋም ጀርመንኛ ቋንቋን የማስፋፋት ዓላማ ያለው መንግሥታዊ ያልሆነ ተቋም ነው።ጀርመን ከዚህ ሌላ ቦን የሚገኘው የሩስያ ቆንስላ ጽህፈት ቤትም እንዲዘጋ ወስናለች።
የሩስያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ዛሬ ለሩስያ ዜና አገልግሎት ታስ እንደተናገሩት ሩስያ የሚገኙት የጎቴ ቅርንጫፎች የሚዘጉት ጀርመን ያሚገኘው የሩስያ የባህል ማዕከል ሲዘጋ ነው ።
በጀርመን እና በሩስያ መካከል ውጥረቱ የተባባሰው ባለፈው ወር ላይፕሲሽ ሀለ አውሮፕላን ማረፊያ የተገኘው ፈንጂዎች የታጨቁበት ድሮን የሩስያ ነው ስትል በርሊን ትናንት በይፋ ካሳወቀች በኋላ ነው።
ጀርመን ላቀረበችባት ክስ ተጨባጭ ማስረጃ አላቀረበችም ስትል የተቃወመችው ሩስያ በትናንትናው እለት በሩስያ የጀርመን አምባሳደርን ጠርታ አነጋግራለች። | 2 848 |
| 7 | https://p.dw.com/p/5Kd3i?maca=amh-RED-Telegram-dwcom@dwamharicbot | 4 024 |
| 8 | https://p.dw.com/p/5KZQS?maca=amh-RED-Telegram-dwcom@dwamharicbot | 3 746 |
| 9 | https://p.dw.com/p/5KWKe?maca=amh-RED-Telegram-dwcom@dwamharicbot | 2 982 |
| 10 | https://p.dw.com/p/5KM3h?maca=amh-Facebook-dw | 2 857 |
| 11 | https://p.dw.com/p/5KbDo?maca=amh-RED-Telegram-dwcom@dwamharicbot | 2 608 |
| 12 | የረቡዕ፤ ነሐሴ 27 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የቀጥታ ሥርጭት ማስታወቂያ
ዜናዉን የሚለጥቀዉ የዜና መጽሔት ጥንቅራችን፦
*የምስራቅ ወለጋ ዞን አንጌር ጉቴ አከባቢ ግጭትና ግጭቱ ያፈናቀላቸው ሰዎች ብሶት
*በጃናሞራ ወረዳ በተከሰተው ድርቅ ከ85 ሺህ በላይ ሰዎች ለከፍተኛ ረሀብ መዳረጋቸው መነገሩ
*በጋምቤላ ክልል የምርት መቀነስን ለማካካስ መስኖ እንደማራጭ መያዙ
*እንዲሁም ጀርመን በሀገርዋ የሚገኙ የተለያዩ የሩስያ ተቋማት እንዲዘጉ መወሰኗ ላይ ያተኮሩ ቅንብሮች ይቀርባሉ ።
ሳምንታዊው ከኤኮኖሚው ዓለም በባለሙያዎች ትንተና በሰጡበት የሐምሌ ወር የዋጋ ግሽበት ላይ ያተኩራል ። ሳይንስና ቴክኖሎጂ ደግሞ ኢንተርኔት በሌለበት ሰዎች ሊጠቀሙባቸው የሚችሏቸው ዲጅታል አማራጮች የትኞቹ እንደሆኑ ይጠቁመናል፤ በድጋሚ የሚቀርብ ነው ።
አብራችሁን ቆዩ ከወዲሁ ግብዣችን ነው ። | 3 537 |
| 13 | ዶይቼ ቬለ ጦማረ-ዜና (Newsletter) አገልግሎት እየሰጠ ነው፥
አሁኑኑ ተጠቃሚ ይሁኑ!
የተወደዳችሁ የዝግጅታችን ታዳሚያን ከሥርጭታችን ውስጥ በየሳምንቱ አንዴ ተመርጦ እንዲላክላችሁ የምትፈልጓቸው ጦማረ ዜና (Newsletter) ስብስቦችን በኢሜል ለተመዘገባችሁ በቀጥታ በኢሜል አድራሻ መላክ ጀምረናል ። በመሆኑም ከታች ባለው ማገናኛ ውስጥ ባለው ባዶ ቦታ የኢሜል አድራሻዎን በማስገባት እናንተም የአገልግሎቱ ተጠቃሚ መሆን ትችላላችሁ ።
https://system.promio-connect.com/register/16401/default/am/single-registration/83494
ከታች ማገናኛው ውስጥ «የኢሜል አድራሻ» የሚለው ጋር በሰፈረው ክፍት ቦታ የኢሜል አድራሻዎን አስገብተው ከስር «እስማማለሁ የአጠቃቀምደንብ.*» የሚለውን በመጫን «ያስገቡ» የሚለውን ጽሑፍ ሲነኩ በቀላሉ ተመዘገቡ ማለት ነው ። ከዚያም፦ ጦማረ-ዜና (Newsletter) በየሳምንቱ ይደርሶታል ። የአዲሱ አገልግሎታችን ተጠቃሚ እንድትሆኑ ተጋብዛችኋል ።
የዶይቼ ቬለ የጦማረ-ዜና (Newsletter) አገልግሎት!
https://system.promio-connect.com/register/16401/default/am/single-registration/83494 | 2 775 |
| 14 | ትክክለኛውን የዶይቸ ቬለ ቲክቶክ ገጻችን ይከተሉ!
ውድ አድማጮቻችን፦ የትክክለኛው የዶይቸ ቬለ ቲክቶክ ገጽ አባል በመሆን ዝግጅታችንን ተከታተሉ ። በትክክለኛው በዚህ የቲክቶክ አድራሻችን፦
https://www.tiktok.com/@dw_amharic አባል ይሁኑ ። ለወዳጆቻችሁም ያጋሩ ።
የተለያዩ የቪዲዮ እና የድምፅ ዘገባዎችን ትክክለኛው የቲክቶክ ገጻችን በመጎብኘት መመልከት አለያም ማድመጥ ትችላላችሁ ።
በዚህ፦ https://www.tiktok.com/@dw_amharic አዲሱ የቲክቶክ ገጻችን የተለያዩ ዝግጅቶችን ወደፊት እንደምናቀርብ ስንገልጥ በደስታ ነው ።
የዶይቼ ቬለን ሥርጭት በኢትዮሳት ሳተላይት እንዲሁም በፌስቡክ እና ቴሌግራም በቀጥታ ማድመጥ ይቻላል ። | 2 587 |
| 15 | ኮንጎ ውስጥ የኢቦላ «ቀይ ዞን» በተባሉ ቦታዎች በርቀት ይሰጥ የነበረው ትምሕርት ዕቅድ ተተወ
* በገዳዩ ወረርሺኝ እስካሁን ከ3000 በላይ ሰዎች ሞተዋል
* ቀይ ዞኖች ውስጥ ትምህርት በርቀት እንዲሰጥ ታዝዞ ነበር
* መሰል ርምጃዎች ወረርሺኙን እንዳያባብሱ አስግቷል
ኮንጎ ውስጥ በተቀሰቀሰው ገዳዩ የኢቦላ ወረርሺኝ እስካሁን ከሦስት ሺህ በላይ ሰዎች መሞታቸውን የገሪቱ መንግሥት ዐሳወቀ ። ዛሬ ይፋ የኾነው የዴሞክራሲያዊ ኮንጎ ሪፐብሊክ መንግሥት ሠነድ ወረርሺኙ በአገሪቱ ስድስት አውራጃዎች ውስጥ መዳረሱን እንደሚያሳይ ሮይተርስ የዜና ምንጭ ዘግቧል ። በዚህም የተነሳ ኢቱሪ አውራጃ ውስጥ የሚገኙ አንድ ሺህ ትምህርት ቤቶች ወረርሺኙን በከፍተኛ ደረጃ ሊያሰራጩ ይችላሉ በሚል «ቀይ ዞን» ተብለው ተሰይመዋል ።
ከሁለት ሳምንት በፊት የወጣው የአገሪቱ የትምህርት ሚንሥትር መመሪያ፦ ቀይ ዞን በሚል የተሰየሙ ትምህርት ቤቶች በአካል በመገኘት የሚሰጠውን ትምህርት ለጊዜው በርቀት እንዲቀይሩ ያዝዛል ። የትምህርት መርሐ ግብሮች በሬዲዮ እና በቴሌቪዥን እንዲሰጡ እና የቤት ሥራ እና ሌሎች የሚሠሩ ልምምዶችን ያካተቱ ወረቀቶች ደግሞ በየሁለት ሳምንታት ይታደላሉ ይላል ። ኾኖም ኢቱሪ አውራጃ ውስጥ በዚህ ሣምንት ትምህርት ቤቶች እንደተለመደው መከፈታቸውን አንድ የትምህርት ሚንሥትር ለዜና ምንጩ ተናግረዋል ። | 2 675 |
| 16 | ትክክለኛውን የዶይቸ ቬለ የዩቲዩብ ገጻችን ይከተሉ!
ውድ አድማጮቻችን ፦ ትክክለኛው የዶይቸ ቬለ ዩቲዩብ ገጽ አባል በመሆን ዝግጅታችንን ተከታተሉ ። በትክክለኛው በዚህ የዩቲዩብ አድራሻችን፦ https://www.youtube.com/channel/UC3-RNH75BEZslJLEoIAxa2A አባል ይሁኑ፥ ለወዳጆቻችሁም ያጋሩ ።
ዶይቸ ቬለ በዓበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪቃ፣ የአውሮጳ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ የዜና ዘገባዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ትንታኔዎችን ያቀርባል ። ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙ የዶይቼ ቬለ ዘጋቢዎች የሚያጠናቅሩት ዜና መጽሄት እና የዓለም ዜና ከሰኞ እስከ ዓርብ በዶይቸ ቬለ ዩቲዩብ ገጻችንም https://www.youtube.com/channel/UC3-RNH75BEZslJLEoIAxa2A ላይ ይቀርባሉ ።
የዶይቼ ቬለን ሥርጭት በሳተላይት እንዲሁም በፌስቡክ በቀጥታ ማድመጥ ይቻላል።
አሁኑኑ የዶይቸቬለ የዩቲዩብ ገፅ ደምበኛ ይሁኑ!
https://www.youtube.com/channel/UC3-RNH75BEZslJLEoIAxa2A
ዶይቸ ቬለን በዩቲዩብም ይከተሉ! | 2 705 |
| 17 | ...ጀርመን ከጥቃቱ ጋር በተገናኘ የሩስያ ቆንስላ ጽ/ቤት እንዲዘጋ መወሰኗን፣ ቤርሊን ከተማ ውስጥ የሚገኝ የባሕል ማእከል ግንባታን ማቋረጧንም ትናንት ዐሳውቃለች ። የሩስያ ፕሬዚደንት ቭላድሚር ፑቲን በቴሌቪዥን በሰጡት አስተያየት የጀርመን ርምጃን፦ «ሌላ ስህተት፤ እጅግ የከፋው» ሲሉ አጣጥለዋል ። ድርጊቱንም «የጀርመን ሕዝብ ፍላጎትን በግልጽ የሚጻረር» ብለዋል ።
ጀርመን ከሩሲያ ጋር አዲስ በገጠመችዉ ዉዝግብ የአዉሮጳ ሕብረት፣ ፈረንሳይና ሌሎች የሕብረቱ አባል ሐገራት ከጀርመን ጎን እንደሚቆሙ አሳውቀዋል ። የአውሮጳ ኅብረት ከዚሁ ከከሸፈው የላይፕትሲሽ ጥቃት ጋር በተገናኘ የሩስያ ከፍተኛ ዲፕሎማትን ጠርቶ ማነጋገሩን ዛሬ ይፋ አድርጓል ። ኅብረቱ የላይፕትሲሹ የድሮን ጥቃት ሙከራ የአውሮጳ ኅብረት እና የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) ሩስያ የዩክሬን አጋዦችን የማተራመስ ሙከራዋ ነው ሲል ከስሷል ።
ይህ ዓይነቱ መካሰስ ከዩክሬን ጋር ለረዥም ጊዜ ጦርነት ውስጥ በገባችው ሩስያ እና ዩክሬንን በማስታጠቅ ጭምር በሚደግፉ እንደ ጀርመን ያሉ የአውሮጳ አገራት መካከል ምን ይፈጥር ይኾን? https://www.facebook.com/dw.amharic/posts/pfbid02neY2mpzdJcKLcSfy8sXzBv74RDAfUW1RS9kp7f9YNZcMxVdqPh8c15nP9segTJxml | 2 511 |
| 18 | ...ጀርመን ከጥቃቱ ጋር በተገናኘ የሩስያ ቆንስላ ጽ/ቤት እንዲዘጋ መወሰኗን፣ ቤርሊን ከተማ ውስጥ የሚገኝ የባሕል ማእከል ግንባታን ማቋረጧንም ትናንት ዐሳውቃለች ። የሩስያ ፕሬዚደንት ቭላድሚር ፑቲን በቴሌቪዥን በሰጡት አስተያየት የጀርመን ርምጃን፦ «ሌላ ስህተት፤ እጅግ የከፋው» ሲሉ አጣጥለዋል ። ድርጊቱንም «የጀርመን ሕዝብ ፍላጎትን በግልጽ የሚጻረር» ብለዋል ።
ጀርመን ከሩሲያ ጋር አዲስ በገጠመችዉ ዉዝግብ የአዉሮጳ ሕብረት፣ ፈረንሳይና ሌሎች የሕብረቱ አባል ሐገራት ከጀርመን ጎን እንደሚቆሙ አሳውቀዋል ። የአውሮጳ ኅብረት ከዚሁ ከከሸፈው የላይፕትሲሽ ጥቃት ጋር በተገናኘ የሩስያ ከፍተኛ ዲፕሎማትን ጠርቶ ማነጋገሩን ዛሬ ይፋ አድርጓል ። ኅብረቱ የላይፕትሲሹ የድሮን ጥቃት ሙከራ የአውሮጳ ኅብረት እና የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) ሩስያ የዩክሬን አጋዦችን የማተራመስ ሙከራዋ ነው ሲል ከስሷል ።
ይህ ዓይነቱ መካሰስ ከዩክሬን ጋር ለረዥም ጊዜ ጦርነት ውስጥ በገባችው ሩስያ እና ዩክሬንን በማስታጠቅ ጭምር በሚደግፉ እንደ ጀርመን ያሉ የአውሮጳ አገራት መካከል ምን ይፈጥር ይኾን? https://www.facebook.com/dw.amharic/posts/pfbid02neY2mpzdJcKLcSfy8sXzBv74RDAfUW1RS9kp7f9YNZcMxVdqPh8c15nP9segTJxml | 2 867 |
| 19 | ጀርመን በላይፕትሲሽ ከተማ የአየር ማረፊያ ለከሸፈው ጥቃት ሩስያን ተጠያቂ አደረገች
ላይፕትሲሽ አየር ማረፊያ ሐምሌ 28 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ለከሸፈው የሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን) ጥቃት የጀርመን መንግሥት ሩስያን ተጠያቂ አደረገ ። «የፌዴራል መንግሥቱ ላይፕትሲሽ ውስጥ ለተቀናበረው ጥቃት ኃላፊነቱ የሩስያ ስለመኾኑ ደምድሟል» ሲሉ የጀርመን የአገር ውስጥ ሚንሥትር አሌክሳንደር ዶብሪንድት ትናንት ማክሰኞ ቤርሊን ውስጥ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ተናግረዋል ።
የጀርመን ውጭ ጉዳይ ሚንሥትር ዮሐን ቫደፑል በበኩላቸው፦ የጥቃቱ ዓይነት «ሩስያ ከዩክሬን ጋር በምታደርገው ጦርነት የምትጠቀምበት» መኾኑን ጠቅሰዋል ። መሰል የሩስያ ጥቃቶችም አውሮጳን የማወክ፦ «የረዥም ጊዜ ተከታታይ ተልእኮ ነው» ብለዋል ። ባለፈው ሳምንት የጀርመን መገናኛ አውታሮች፦ ፈንጂ የጫነ ሌላ ሦስተኛ ድሮን አየር ማረፊያው ውስጥ ተገኝቶ ነበር ሲሉ መዘገባቸው ይታወሳል ... | 2 942 |
| 20 | https://p.dw.com/p/5K1qZ?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 3 314 |
