DW Amharic
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።
Ko'proq ko'rsatish- Kanalning o'sishi
- Post qamrovi
- ER - jalb qilish nisbati
Ma'lumot yuklanmoqda...
Ma'lumot yuklanmoqda...
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የልጃገረዶች ጠለፋ መባባሱ ተገለጠ። በክልሉ ኮሬ ዞን ውስጥ «እየተባባሰ መጥቷል» ባሉት ጠለፋ የተነሳ ሴት ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ መቸገራቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል። ቡርኪና ፋሶ ሦስት የፈረንሳይ ዲፕሎማቶችን ከሀገር አባረረች። ፈረንሳይ ውሳኔውን አሳዛኝ ብላዋለች። የደቡብ ሱዳን ፖለቲከኞች በሀገሪቱ ምርጫ ለማካሄድ አስቸኳይ እርምጃ መውሰድ እንዳለባቸው የተመድ አሳሰበ። ኢራን እስራኤል የኒኩሊየር ተቋሟ ላይ ጥቃት የምትሰነዝር ከሆነ በአጸፋው የእስራኤልን የኒኩሊየር መሰረተ ልማት ኢላማ እንደምታደርግ አስጠነቀቀች።
የወልቃይት፣ ጠገዴ ጠለምትና ራያ ጉዳይ በፖለቲካዊ ውሳኔ እንዲፈታ በአሜሪካ የሚገኙ 8 ኢትዮጵያ ሲቪክ ድርጅቶች ጥሪ አቀረቡ።
በተለይም ከቅርብ ቀናት ወዲህ በትግራይ እና አማራ ክልል አዋሳኝ አካባቢዎች ግጭቶች እያገረሹ ይገኛሉ። በዚህም ሞትና መፈናቀል ተከስቷል። የሁለቱ ክልል አስተዳደሮችም እርስ በራሳቸው እየተወነጃጀሉ ይገኛሉ።
ለጥንታዊቷ ሀረር ከተማ ከወራት በፊት በዓለም አቀፉ የሳይንስ ፣ የትምህርት እና የባህል ድርጅት በእንግሊዝኛ ምኅፃሩ/ UNESCO ሁለተኛ ቅርስ ሆኖ የተመዘገበው የሽዋልኢድ ዓመታዊ በዓል የከተማይቱን የቱሪስት መዳረሻነት እድል ይበልጥ ያሰፋል የሚል እምነት አሳድሯል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን «እየተባባሰ መጥቷል» ባሉት ጠለፋ የተነሳ ሴት ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት ለመላክ መቸገራቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ ። በዞኑ በድርጊቱ ፈጻሚዎች ላይ አስተማሪ የሆነ ቅጣት ስለማይሰጥ አሁን ላይ ሴት ልጆች ወጥተው ለመግባት ሥጋት ውስጥ መውደቃቸውን ነው ነዋሪዎቹ ለዶቼ ቬለ የተናገሩት ።
በኢትዮጵያ ለተከሰተው የከፋ የሰብአዊ ቀውስ ድጋፍ ለማሰባሰብ ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ውስጥ በተደረገው ዓለም አቀፍ ድጋፍ የማሰባሰብ ሥራ ከታቀደው እጅግ ዝቅ ያለ ገንዘብ ቃል መገባቱ ተገለጠ ። 3.24 ቢሊዮን ዶላር ለማሰባሰብ ታቅዶ ቃል የተገባው ግን 630 ሚሊዮን ዶላር መሆኑም ተጠቅሷል ።
ረቡዕ ሚያዝያ 9 ቀን የጀመረው የ27ቱ የአውሮጳ ኅብረት አገሮች የመሪዎች ስብሰባ ዛሬ ከስአት በኋላ ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ተጠናቅቋል ። የጉባኤው አጀንዳ ምን ነበር? ትናንት እና ዛሬ የተከናወነው የኅብረቱ የመሪዎች ጉባኤ ምንስ ውሳኔ አሳልፎ ተጠናቀቀ?
የዓዉደ ርእዩ መጠርያ ንጹሕ ምንጭ ኢትዮጵያ ይሰኛል። ኢትዮጵያ ብዙ ንጹሕ ምንጮች አልዋት። ከነዚህ ንጹሕ ምንጮች መካከል፤ የራስዋን ድርሳናት፤ ሥነ- ነገር የከተበችባቸዉ ፊደላት የሚጠቀሱ ናቸዉ። እግዚቢሽኑን የሚመሰገን ፤ የወጣቶቹ ሥራ ለሃገሪዉ ሃገሩን፤ ነባር ባህሉን እና እዉቀቱን እንዲያዉቅ የሚያደርግ ብዙ ምንጮችንም የሚያሳይ ነዉ።