DW Amharic
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።
إظهار المزيد📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام DW Amharic
تُعد قناة DW Amharic (@dw_amharic) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 54 854 مشتركاً، محتلاً المرتبة 4 884 في فئة الأخبار والوسائط والمرتبة 582 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 54 854 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 20 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 35، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -8، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: موثّقة (مؤكدة رسمياً من تيليجرام)
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 7.77%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 5.56% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 264 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 3 048 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 0.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 21 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الأخبار والوسائط.
جاري تحميل البيانات...
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 20 يوليو | +8 | |||
| 19 يوليو | +24 | |||
| 18 يوليو | +24 | |||
| 17 يوليو | +19 | |||
| 16 يوليو | +12 | |||
| 15 يوليو | +22 | |||
| 14 يوليو | +15 | |||
| 13 يوليو | +19 | |||
| 12 يوليو | +22 | |||
| 11 يوليو | +12 | |||
| 10 يوليو | +22 | |||
| 09 يوليو | +9 | |||
| 08 يوليو | +9 | |||
| 07 يوليو | +5 | |||
| 06 يوليو | +18 | |||
| 05 يوليو | +10 | |||
| 04 يوليو | +19 | |||
| 03 يوليو | +12 | |||
| 02 يوليو | +20 | |||
| 01 يوليو | +1 |
| 2 | https://pepurl.com/p/5HQjH?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 1 655 |
| 3 | https://pepurl.com/p/5HS1U?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 1 |
| 4 | https://pepurl.com/p/5HQmG?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 1 388 |
| 5 | https://pepurl.com/p/5HS1U?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 1 345 |
| 6 | https://pepurl.com/p/5HQki?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 1 384 |
| 7 | https://pepurl.com/p/5HQgs?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 1 470 |
| 8 | የዕለተ ሰኞ ሐምሌ 13 ቀን፣ 2018 ዓ.ምየቀጥታ ሥርጭት ማስታወቂያ!
ዜናውን በሚከተለው የዜና መጽሔት፤ የምክክር ጉባኤ ከተጀመረ ወዲህ ወደ ምክክር ሂደቱ የገቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች አሉ ስለመባሉ፣ የኦሮምያ ክልል ምክር ቤት ጨፌ ስለክልሉ የፀጥታው ሁኔታ መምከሩን፣ በደቡብና ሰሜን ወሎ በመሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈጸም ዝርፍያ መባባሱን፣ ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን ግጭት ማገርሸት የአፍሪካ ቀንድን የበለጠ ስጋት ውስጥ መቀጠሉን የሚያስቃኙ ዘገባዎችን አካቷል።ከዕለተ ሰኞ ሳምንታዊ መሰናዶ ቀዳሚው ማህደረ ዜና ዝግጅት ፤አሜሪካ ለአፍሪቃ ህብረት የሶማሊያ ተልዕኮ የምታደርገውን የገንዘብ እና የሎጂስቲክስ ድጋፍ ልታቆም ነው መባሉን ፤ የስፓርት ዝግጅት ደግሞ ትናንት በስፔን አሸናፊነት የተጠናቀቀውን የዓለም ዋንጫን ጨምሮ ሌሎች ስፓርታዊ ዘገባዎችን አካቷል።
አብራችሁን እንትቆዩ ግብዣችን ነው!
መልካም ጊዜ ። | 2 384 |
| 9 | የትግራይ ክልል በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም፣ በምርጫም፣ በምክክር ጉባኤ፣ በአገራዊ የፖሊሲ ዉሳኔዎችም አለመካፈሉ ክልሉን በሚመራዉ በሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ (ህወሓት) ና በኢትዮጵያ ፌደራዊ መንግሥት መካከል የተፈጠረዉ ጠብ እየተካረረ መምጣቱን መስካሪ መስሏል https://pepurl.com/p/5HKwL?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 4 223 |
| 10 | የሐምሌ 12 ቀን 2018 የዓለም ዜና
• በሶማሌ ክልል ቀብሪ በያሕ ወረዳ ዛሬ ለሊት በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ12 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ ሦስት ሰዎች ጉዳት ደረሰባቸው።
• የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ለሚቀጥለው ዓመት የ704 ቢሊዮን ብር በጀት አጸደቀ። ጨፌ ኦሮሚያ ዛሬ ባካሔደው 11ኛ መደበኛ ስብስባ ያጸደቀው በጀት ከ2018 ጋር ሲነጻጸር በ75 በመቶ ገደማ ጭማሪ አሳይቷል።
• በመጪዎቹ ሦስት ቀናት በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ምዕራባዊ ክፍሎች፤ በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልልና በጋምቤላ ክልል በተወሰኑ አካባቢዎች በሚጥል ከባድ ዝናብ ምክንያት የጎርፍ መጥለቅለቅ ሊከሰት እንደሚችል የኢትዮጵያ የአደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስጠነቀቀ።
• የታንዛኒያ ሰንደቅ የሚያውለበልብ ነዳጅ ጫኝ መርከብ ከየመን የባሕር ዳርቻ አካባቢ ከሶማሊያ ሳይሆኑ አይቀሩም በተባሉ የባሕር ላይ ወንበዴዎች ታገተ። የታገተው የንግድ መርከብ በሰሜን ምሥራቅ ሶማሊያ ባሪ ግዛት ወደሚገኝ የውኃ ክልል እንዲጓዝ መደረጉን የመረጃ ምንጮች ለአሶሼትድ ፕሬስ ተናግረዋል።
• አሜሪካ ሁለት ወታደሮቿ በዮርዳኖስ ከተገደሉ በኋላ ኢራንን “ለመቅጣት” አዲስ ዙር የለሊት የአየር ላይ ድብደባ ፈጸመች።
• ሩሲያ ለሊቱን በኪየቭ ከተማ በፈጸመችው ኃይለኛ የሚሳይል ጥቃት አንድ ሰዉ ሲገደል 16 መቁሰላቸውን የዩክሬን ፕሬዝደንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ አስታወቁ።
• የእስራኤል የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትር ኢዲት ሲልማን አዞዎች ለጸጥታ ጥበቃ ጥቅም ላይ እንዲውሉ የሚፈቅድ የሕግ ማሻሻያ አደረጉ። https://pepurl.com/p/5HOJu?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 3 880 |
| 11 | የታንዛኒያ ሰንደቅ የሚያውለበልብ ነዳጅ ጫኝ መርከብ ከየመን የባሕር ዳርቻ አካባቢ ከሶማሊያ ሳይሆኑ አይቀሩም በተባሉ የባሕር ላይ ወንበዴዎች ታገተ። የታገተው የንግድ መርከብ በሰሜን ምሥራቅ ሶማሊያ ባሪ ግዛት ወደሚገኝ የውኃ ክልል እንዲጓዝ መደረጉን የመረጃ ምንጮች ለአሶሼትድ ፕሬስ ተናግረዋል።
መርከቡ ባለፈው አርብ የታገተው ከየመን ሙካላ ወደብ ጉዞ ከጀመረ በኋላ ነው። በአሁኑ ወቅት በፑንትላንድ ባሪ ግዛት ውስጥ ከካሉላ የባሕር ዳርቻ ተይዞ ይገኛል። ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ የመረጃ ምንጮች መርከቡ በሰባት የሶማሊያ የባሕር ላይ ወንበዴዎች እንደታገተ ተናግረዋል።
ባልተለመደ ፍጥነት ወደ ቦሳሶ ይጓዝ የነበረው መርከብ በታገተበት ወቅት የአደጋ መልዕክት አስተላልፎ እንደነበር አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል። በነዳጅ ጫኙ መርከብ ላይ ምን ያክል ሠራተኞች እንደነበሩም ይሁን የደረሰ ጉዳት ስለመኖሩ የሚታወቅ ነገር የለም። የፑንትላንድ ባለሥልጣናት እና የመርከቡ ባለቤቶችም እስካሁን ዝምታን መርጠዋል። | 3 445 |
| 12 | በደቡብ አፍሪካ የኮበርግ ኑክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሰራተኞች ለጨረር መጋለጣቸውን የሀገሪቱ የኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።
በኮበርግ ኑክሌር ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ውስጥ የጥገና ሥራ ሲያከናውኑ የነበሩ በርካታ ሠራተኞች በሦስት የተለያዩ አጋጣሚዎች ለጨረር መጋለጣቸውን የኢነርጂ ሚኒስትሩ ኮሲየንሾ ራሞክጎፓ ዛሬ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።
አደጋዎቹ የተገደቡ እንደነበሩ የገለጹት ሚንስትሩ ምንም ዓይነት የራዲዮአክቲቭ ንጥረ ነገር ወደ አካባቢው እንዳልተለቀቀ ተናግረዋል። በዚህም በአቅራቢያው በሚገኙ ማህበረሰቦች ላይም ምንም ዓይነት አደጋ እንዳልተደቀነ ማረጋገጫ ሰጥተዋል።
ከኬፕ ታውን በስተሰሜን 30 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው በዚህ የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ አደጋዎቹ የተከሰቱት ባለፉት ሰኔ 23፣ 25 እና ሰኔ 30 2018 ዓ/ም ቀናት እንደነበር የጀርመን ዜና አገልግሎት ዲፒኤ ዘግቧል።
ለአደጋው መንስኤ የሆነው የጣቢያውን የአየር ማናፈሻ ሥርዓት ያደናቀፈ« ጊዜያዊ የኃይል መቆራረጥ ነው» ያሉት ሚንስትሩ ሰራተኞቹ የደረሰባቸው የጨረር መጠን ከተለመደው የጥርስ ራጅ (X-ray) ምርመራ ከሚገኘው ጨረር ያነሰ መሆኑንም አመልክተዋል።
የሀገሪቱ የኑክሌር ደህንነት ክፍል ኃላፊ ቬላፊ ንቱሊ በበኩላቸው የተከሰቱት አደጋዎች ሪፖርት ሊደረግላቸው ከሚገቡ ዋና ዋና የኑክሌር ደህንነት ክስተቶች ደረጃ በታች መሆናቸውን ገልጸዋል።
ደቡብ አፍሪካ በቅርብ ዓመታት ውስጥ በከፍተኛ የኤሌክትሪክ እጥረት እና በተደጋጋሚ የኃይል መቆራረጥ ሲያጋጥማት ቆይታለች። የሀገሪቱ መንግስት ይበልጥ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አቅርቦት ለመገንባት የኑክሌር ኃይልን እንደ ትልቅ መፍትሄ ነው የሚመለከተው። | 3 521 |
| 13 | የእስራኤል የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትር ኢዲት ሲልማን አዞዎች ለጸጥታ ጥበቃ ጥቅም ላይ እንዲውሉ የሚፈቅድ የሕግ ማሻሻያ አደረጉ። ሚኒስትሩ የአዞዎች ምደባ ከዱር እንስሳት “በማቆያ የተራቡ የዱር እንስሳት” ወደሚል እንዲቀየር ማድረጋቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል።
ከዚህ ቀደም ፍልስጤማውያን ተይዘው የሚገኙባቸውን እስር ቤቶች በአዞዎች በመክበብ ለመጠበቅ የሚያስችል የሕግ ረቂቅ አቅርበዋል የተባሉት ቀኝ አክራሪው የእስራኤል የብሔራዊ ደሕንነት ሚኒስትር ቤን ጋቪር ውሳኔውን በአዎንታ እንደተቀበሉ የዜና ወኪሉ ዘግቧል።
ቤን ጋቪር ከትላንት በስቲያ በፌስቡክ ገጻቸው ከእስር ቤት “ለማምለጥ መሞከር እያሰባችሁ ነው? መልሳችሁ አስቡበት” የሚል ማስጠንቀቂያ በአርቴፊሺያል ኢንተለጀንስ ከተፈጠረ ምስል ጋር አያይዘው አጋርተው ነበር። በምስሉ የብሔራዊ ደሕንነት ሚኒስትሩ አንገቱ ላይ የቀበቶ መጎተቻ የተደረገለት አዞ ይዘው ይታያሉ። በዚህ የፌስቡክ መልዕክት “ሚኒስትር ቤን ጋቪርና ሲልማን እስር ቤቶችን በአዞዎች ለመክበብ እየተባበሩ ነው” የሚል ጽሁፍ አብሮ እንደሠፈረ የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
የእስራኤል የተፈጥሮና የፓርኮች ባለሥልጣን የቤን ጋቪርን ምክረ-ሐሳብ እንደተቃወመ ቻናል 13 የተባለው የእስራኤል የቴሌቭዥን ጣቢያ ዘግቧል። አሁን የተደረገው የምደባ ለውጥ እንስሳቱን በተመለከተ የሚደረገውን ቁጥጥር ከተፈጥሮና ፓርኮች ባለሥልጣን ወደ “የጸጥታ አካል” ያዘዋውረዋል። ይህ አካል ቤን ጋቪር የሚመሩት የእስራኤል የእስር ቤቶች አገልግሎት ሊሆን እንደሚችል የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
በዘገባው መሠረት ባለፈው ረቡዕ ተፈርሞ ሥራ ላይ የዋለው ሕግ የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትሩ ለጸጥታ ዓላማ አስፈላጊ ናቸው ብለው ከወሰኑ የናይል አዞዎች እንዲራቡ ይፈቅዳል። አዞዎቹ ወደ ዱር እንዳይለቀቁ ለመከላከል የሚያዙበትን ሁኔታ የሚወስኑት የተፈጥሮና ፓርኮች ባለሥልጣን ዳይሬክተር ናቸው።
ሐማስ መስከረም 26 ቀን 2016 ከፈጸመው ጥቃት በኋላ የተያዙ የቡድኑ ታጣቂዎች በሚገኙበት የኬትዚዮት እስር ቤት ዙሪያ ቤን ጋቪር አዞዎች የማስፈር ዕቅድ እንዳላቸው የእስራኤል መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል። እስር ቤቱ የሚገኘው በደቡባዊ እስራኤል ነው። | 3 766 |
| 14 | የእስራኤል የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትር ኢዲት ሲልማን አዞዎች ለጸጥታ ጥበቃ ጥቅም ላይ እንዲውሉ የሚፈቅድ የሕግ ማሻሻያ አደረጉ። ሚኒስትሩ የአዞዎች ምደባ ከዱር እንስሳት “በማቆያ የተራቡ የዱር እንስሳት” ወደሚል እንዲቀየር ማድረጋቸውን አሶሼትድ ፕሬስ ዘግቧል። 👇 | 3 281 |
| 15 | የሐምሌ 11፣ቀን 2018 ዓ/ም የአድማጮች ማኅደር ዝግጅት
ተፈጥሮ ከነ ምናምኗ ውብ፣ ድንቅናማራኪናት።በምደራችን ካሉ ፍጠረታት ሁሉ በራሱ ጊዜ ተፈጥሮን ተክቶ የሚቆም አንድም ፍጡር የለም።ይላሉ የሐረሩ ዉቤ ታሪኩ ። ከመንግስትም ሆነ ከተቀዋሚ ፓርቲዎ እየወጡ ያሉ ጥላቻ አዘል እና ጦርነት ቀስቃሽ መግለጫዎች መርገብ አለባቸው፤ ፋሲል ሲራክ ቸው። እናንተም አስተያየት መላክ ከፈለጋችሁ amharic@dw.com የኢሜል አድራሻችን ነው። 0049-228-429-164995 ደግሞ የድምጽ መልዕክት መቀበያ ስልካችን ነው። በፌስ ቡክ ሜሴንጀር ወይም በቴሌግራምም የጽሑፍም ሆነ የድምጽ መልዕክት መላክ ትችላላችሁ።
https://pepurl.com/p/5HKci?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 4 390 |
| 16 | ዳንጎቴ በምሥራቅ አፍሪቃ ለመጀመሪያው የነዳጅ ዘይት ማጣሪያ ፕሮጀክት ኬንያን ለምን መረጡ?
በቀን 700ሺህ በርሜል የተጣራ ነዳጅ ዘይት እንደሚያቀርብ የተነገረው ተቋሙ ኬንያን ብቻ ሳይሆን መላውን የምሥራቅ አፍሪቃ አካባቢ ይለውጣል የሚል ተስፋ ተጥሎበታል። ተቋሙ በአፍሪካ ሁለተኛው ትልቁ የነዳጅ ማጣሪያ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። በምስራቅ አፍሪቃ የነዳጅ አቅርቦትን፣ ንግድን እና የኢኮኖሚ እድገትን እንደገና ሊቀርጽ ይችላልም ተብሏል።
https://p.dw.com/p/5HLGl?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 4 030 |
| 17 | አፍሪካ የእንስሳት ሐብቷን በሚገባ መጠቀም እንዳልቻለች ተገለፀ
ዩጋንዳ ወደ ኢትዮጵያ እየላከች ነው የሚባለውን የስጋ ምርት በተመለከተም፣ ያን ያህል የጎላ እንዳልሆና ምርቱን እያስገባ ያለውም አንድ ሆቴል መኾኑን ጠቅዋል። ምርቱ የተቀነባበረ ስለኾነም፣ እንደ ምግብነት በምግብና መድሃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን በኩል የገባ መኾኑን አስረድተዋል።
https://pepurl.com/p/5HMFV?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 3 467 |
| 18 | «የምግብ ዕርዳታ ድጋፍ አልተደረገልንም»
"ርሀብ አለ በጣም፣ ሰው በጣም ተጎድቶ ነው ያለው። ህፃኖቹም ምንም ምንም ያገኙት ነገር የለም። ትልልቆቹም እየለመኑ ነው የሚበሉት፤ እኛም ዝም ብለን ነው ያለነው። "
https://pepurl.com/p/5HMNN?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 3 003 |
| 19 | ህወሓትን የሚያወግዝ ሰላማዊ ሰልፍ አዲስ አበባ
ከሰላምና ለውጥ ፈላጊዎች እንቅስቃሴ አስተባባሪዎች አንዱ የሆኑት አቶ ከበደ አሰፋ ህወሓት ላይ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጫና እንዲያደርግ ይህንን ሰልፍ መጥራታቸውን ገልፀዋል።
https://pepurl.com/p/5HMDh?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 2 776 |
| 20 | የሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ-ም የዓለም ዜና
የዛሬው የዓለም ዜና ፤በአዲስ አበባ ከተማ ህወሓትን የሚቃወም ሰልፍ መካሄዱን፤ኢራን 'የአሜሪካ ጥቃቶች ከቀጠሉ ምንም አይነት የፖለቲካ ድንበር ደህንነቱ የተጠበቀ አይሆንም' ስትል ማስጠንቀቋን፣የሊባኖስ ፕሬዝዳንት ትራምፕን ለማግኘት ወደ ዋሽንግተን ማቅናታቸውን፤በጀርመን ከፍተኛ የሽብር ስጋት መኖሩን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር መግለፁን፣ዩክሬይን በሁለት የሩስያ ግዛቶች ሌሊቱን ለዛሬ አጥቢያ ፈጸመችው በተባለ የድሮን ጥቃቶች 8 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸውን የሩስያ ባለስላጣናት ማስታወቃቸውን እንዲሁም ህንድ የመጀመሪያውን የግል ሮኬት ወደ ህዋ ማምጠቋን አካቷል።
https://pepurl.com/p/5HMj2?maca=amh-RED-Telegram-dwcom | 3 443 |
