cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
77 222
Obunachilar
+3424 soatlar
+2657 kunlar
+1 16130 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

አሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሒ ወበረካቱሁ ይህ ወንድማችን ወሎ ቦረና ከላላ ወረዳ ልጓማ የምትባል አካባቢ ተወልዶ ያደገ ነዉ። ተጨማሪ ስልክ 09 14 36 37 98 ወይንም 09 31 82 91 83 ሼር እያደረጋችሁ።
Hammasini ko'rsatish...
ጠፍቶ የነበረው ወንድም ተገኝቷል አልሐምዱሊላህ። ሰበብ የሆናችሁ አላህ ጀዛኩሙላሁ ኸይረን።
Hammasini ko'rsatish...
السلام عليكم ይህ ወንድማችን ዛሬ ጠዋት 3:00 ላይ ኮካ ማዞርያ አካባቢ ከመኖርያ ቤት እንደወጣ አልተመለሰም።ትንሽ የአይምሮ ችግር ስላለበት ያየው ሰው በተጠቀሱት ስልክ ደውሎ ይጠቁመን። +251991197169 +251911572323
Hammasini ko'rsatish...
አንድ ነጥብ ለአስተውሎት ~ በጣም ከምንሸወድባቸው ነገሮች ውስጥ አንዱ በእውቀት የሚበልጡንን መሻይኾች ልንጠቀምባቸው አለመቻላችን ነው። በሃገራችን የመንሃጅ ግንዛቤ በጣም የሳሳ እንደሆነ ማንም የማይክደው ሐቅ ነው። ይሄ ክፍተት ደግሞ ብዙ መሻይኾች ላይ ይጎላል። ለወቅታዊ ኪታቦችና ለኢንተርኔት የቀረበው ወጣት #አንፃራዊ በሆነ መልኩ ትንሽ ሻል የሚልበት ሁኔታ አለ። በንፅፅር ነው እያወራሁ ያለሁት። ትንሽ እውቀት የራሱ ብዙ ድክመት አለበትና የማንክደው ብዙ ጣጣ እያመጣብን ነው። ሌሎችን ችግሮች ለጊዜው ልተውና በተነሳሁበት ጉዳይ ላይ ያለውን ላንሳ። ድርቅና (ዒናድ) ሳይሆን የግንዛቤ ችግር ያለባቸውን መሻይኾች መቅረብ እንጂ መራቅ ለሁሉም አይበጅም። ይሄ ማግለልና መግፋት ለነሱም፣ ለኛም፣ ለቆምንለት አላማም፣ ለወገናችንም የሚበጅ አይደለም፡፡ እና ተውሒድና ሱናን መውደድ፣ የሱና ዑለማዎችን ማክበር፣ ለደሊል እጅ መስጠት ካሸተትንባቸው ክፍተቶችን ብናይ እንኳ ከመራቅ ይልቅ መቅረባችን ነው የሚያተርፈን። 1ኛ:- ለነሱም ውለታ መዋል ነው። እኛ ችላ ስንላቸው በሌሎች ይጠለፋሉ። ይሄ ከዚህ ቀደም በስፋት ተከስቷል። እኛ ስንርቃቸው የሌሎች ሲሳይ ሆነዋል። በራሳችን ላይ ጠላት አብዝተናል። ካለፈው ልንማር በቃ ልንል ይገባል፡፡ 2ኛ:- ለሰፊው ህዝበ ሙስሊም፦ እነዚህ መሻይኾች ህዝብ ዘንድ የተሻለ ቦታ ስለሚኖራቸው የነሱ መጠንከር ለህዝብ ይተርፋል፡፡ እኛ ባግባቡ ካልቀረብናቸው ግን ሌሎች አካላት የሱናን ደዕዋ በጥላቻና በስጋት እንዲመለከቱ አድርገው ይሞሏቸዋል። ይሄ ደግሞ ዞሮ ዞሮ ዳፋው ለህዝብ ነው የሚተርፈው። 3ኛው:- ጥቅም ለራሳችን ነው፡፡ እኛ ትንሽዬ የመንሃጅ ግንዛቤ አለችን ማለት (ያውም ከኖረ) ከነሱ በእውቀት በለጥን ማለት አይደለም፡፡ እንዲያውም ከነጭራሹ እውቀት አለን ማለትም አይደለም። እነሱ ዘንድ መንሃጅ ላይ የግንዛቤ ክፍተት መታየቱ እውቀት የላቸውም ማለት አይደለም፡፡ ለሁለቱም ወገን የሚበጀው መቀራረቡ ነው። እነሱ ዘንድ ያለውን ክፍተት ከቻልን ኪታብ እየገዛንላቸው ፣ ካልሆነ እያዋስናቸው፣ የታላላቅ ዑለማዎችን ንግግር እያሰማናቸው፣ በአደብ እየተከራከርናቸው ለመሙላት መጣር አለብን። በተለይ ኪታብ መስጠት ያለው ዋጋ ቀላል አይደለምና በዚህ ላይ ልንረባረብ ይገባል። የኛን ጅህልና ደግሞ ቁጭ ብሎ በመማር መግፈፍ አለብን። ይህን ስናደርግ ለራሳችንም፣ ለመሻይኾቹም፣ ለወገናችንም ትልቅ ውለታ እንውላለን። ለደዕዋችን መፋፋትም ጉልህ ሚና ይኖረዋል፡፡ የማወራው ከላይ እንደገለፅኩት ተውሒድና ሱናን መውደድ፣ የሱና ዑለማዎችን ማክበር፣ ለደሊል ራስን ዝቅ ማድረግ፣ ቅንነት ስለሚታይባቸው መሻይኾች ነው። መቼም በርካታ መሻይኾችና ዱዓቶች ተሰውፍ እና ሌሎችም የተሳሳተ መስመር ውስጥ ከቆዩ በኋላ እንደተመለሱ ይታወቃል። ከአላህ በኋላ ለዚህ መመለሳቸው የተለያዩ ሰበቦች ይኖራሉ። ዛሬም እነዚህን ሰበቦች ችላ ልንላቸው አይገባም። ዛሬም ክፍተት ያለባቸው ሰዎች ሲገጥሙን በመወያየት፣ መረጃ በመለዋወጥ፣ በችግራቸው ከጎናቸው በመቆም ልናቀርባቸው ይገባል። አንተ ትላንት በተለያዩ መስመሮች ላይ አልፈህ መጥተህ ሌሎች ወደሱና እንዳይገቡ በር ለመከርቸም አትታገል። ያለፍክባቸውን አባጣ ጎባጣ መንገዶች መለስ ብለህ አስተውላቸው። = ግንቦት 28/2013 https://t.me/IbnuMunewor
Hammasini ko'rsatish...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

ቻናሌ ላይ በተደጋጋሚ ማስታወቂያ እየተለቀቀ እንደሆነ አሁን አንድ ወንድም አሳወቀኝ። እኔ እያሰራጨሁት እንዳልሆነ እንድታውቁልኝ እፈልጋለሁ። ቀደም ብዬ ያልጠቆምኩት ማስታወቂያው ለኔ ስለማይታየኝ ነው። = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
Hammasini ko'rsatish...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

* ሰበብ እየፈለገ ሌሎችን ከሱና የሚያስወጣ አካል መጨረሻ ላይ ሌሎችን ባስወጣበት በር ራሱ ይወጣል። * እወቅ! ሌሎች ላይ የመዘዝከው የኢልዛም ሰይፍ ወዳንተም ይዞራል። እቆርጥበታለሁ ያልከው ይቆርጥሃል። * ሰለፊያ የወደድከውን የምታስገባበት፣ የጠላሀውን የምታስወጣበት ያ'ባትህ ግቢ አይደለም። ሰለፊያ ኢስላም ማለት እንጂ ሌላ ቡድን አይደለም። ይህንን ከቃላት ባሻገር በተግባር አስረግጥ። * በዚህ ዘመን በመንሀጅ ስም ተጠቅልሎ ያለው አብዛኛው ጩኸት የአመል ችግር ነው። ያለበለዚያ ሰው እንዴት እስ'ካፍንጫው በተነከረበት ጥፋት ሌሎችን ሊከስ ይደፍራል? * በሺርክና በቢድዐ መፈረጅ ከሺርክና ከቢድዐ የማስጠንቀቅ ያህል ቀላል አይደለም። ሁለተኛው ላይ ካለህ ትጋት ይልቅ የመጀመሪያውን መድፈርህ መታመምህን ነው የሚያሳየው። ሳይጠናብህ ታከመው። = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
Hammasini ko'rsatish...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

ጭፍራው ቅርቃር ውስጥ ገብቷል ~ ቅልጥ እንደ ቅቤ - ፍርስ እንደ ሸክላ ሁሉ ነገር እርቃን - እነ ሳይሞቅ ፈላ! ይሄ ሰካራም ጭፍራ ብዙ እንደማይራመድ በጣም እርግጠኛ ነበርኩ። በዚህ ፍጥነት ድንብርብሩ ሲወጣ፣ ጉዱ ሲዘከዘክ ማየት ግን የጠበቅኩት አልነበረም። ከሁለት ዓመት በፊት መሰለኝ ወራቤ ላይ አንድ ወንድም ዐብዱልሐሚድ ለተሞ አንድ መንሀጅ ላይ ሁለት አመት ሶብሮ መቆየት አይችልም ጠብቁ ሲል ሰምቼው ነበር። ምናልባት የሆነ ያክል ተጋኖ ይሆን? አላውቅም። ንግግሩ ግን በውስጡ የሆነ እውነት አዝሏል። አሁን ላይ አንዳንድ ነገሮች ጫፋቸው እየዘለቀ ነው። እውነትና ንጋት እያደር ይጠራል እንዲሉ ይሄው እየጠራ መጣ። በየጊዜው እየወጡ ካሉ በርካታ የቪዲዮ እና የፎቶ ማስረጃዎች ውስጥ ለጊዜው አንድ ማሳያ ልጥቀስ፦ ጠሃ ኸዲር የዚህ የተንቀዠቀዠ ጭፍራ አጫፋሪ መሆኑ ፀሐይ የሞቀው ጉዳይ ነው። ሶሻል ሚዲያ ላይ እየዘለቀ ሁለት ሶስት መስመር ስድብ መፃፍን ቁም ነገር ያደረገ በተግባር ግን በተለያየ ቦታ የተለያየ ፊት የሚጠቀም ሰው ነው። * ሳዑዲ ውስጥ ጤነኛ ያልሆኑ ሰዎች ዘንድ ቁጭ ብሎ ለአመታት ይማራል። እዚህ ደግሞ እነ እከሌ ከእነ እከሌ ጋር ተቀመጡ እያለ ፎቶ ይለጥፋል። የሳዑዲ ኤምባሲ ሲጋብዛቸው ራሱም ጭፍራዎቹም ከነዚያው ከሚያወግዛቸው አካላት ጋር አንድ ላይ ይጣዳል። በተለያዩ ቦታ የተለያየ ፊት በማሳየት ላይ ተክኖበታል። * መሻይኾች ዘንድ ሌላ ሰው ነው። ማህበራዊ ሚዲያ ላይ ደግሞ ሌላ። * ሳዑዲ ውስጥ ሌላ ሰው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ሌላ። * እንደ ባህሩና ሑሴን ያሉ ተናካሽ ጓዶቹ ጋር ሲሆን ሌላ ነው። አቃቂር እያወጡ፣ ቅጥፈት እየለጠፉ የሚናከሱ አውሬዎች ናቸው። እያደናነቀ የሚያስተዋውቃቸው የሀረር አካባቢ ጭፍራዎቹ ደግሞ እሱ በሚስላቸው 'ሙስተዋ' ላይ እንዳልሆኑ በሚገባ ያውቃል። ያያያዝኩት ቪዲዮ ለዚህ አንድ ምስክር ነው። በቪዲዮው ላይ የጠሀ ጭፍራ የሆኑት (የነበሩት ብለው ይሻል ይሆን?) እነ ኢልያስ ዐባስ እና አሕመድ ሙሐመድ (ጭሮ?) ከነ ዶክተር ጀይላን ጋር ተቀማምጠው የአንድነት መግለጫ ያወጡበት ጉባዔ ነው። ቪዲዮው ላይ ከሰፈረው ቃል ቀንጨብ ላድርግ፦ 1- የዶክተር ጀይላን ንግግር፦ "በሀረር ዑለማኦች መካከል ልዩነት እንደሌለ እንዲሁም በዑለማኦቹ መካከል ልዩነት ለመፍጠር የሚጥሩ አካላት በዑለማእ ስም የሚነግዱ እንደሆኑ፤ እኛ ሁላችንም አንድ እና የተሰማማን እንደሆንን፤ በመካከላችን ልዩነት እንደሌለ የሀረር እና የኢትዮጵያ መሻይኽ ጉባኤ ገልጿል።" 2- የኢልያስ ዐባስ ንግግር፦ "እኛ እንደ አሕመድ ሱኣላ እና እንደ ዶክተር ጀይላን ካሉ ታላላቅ ዑለማኦች ጋር ነን። ድሮም፣ አሁንም በመካከላችን ልዩነት የለም። እስከ ዘላለም ከነሱ አንለይም።" 3- የሸይኽ አሕመድ ሙሐመድ ንግግር:- "እኛ አሁን ከዑለማኦቻችን ጋር ነን። እነሱን ከሚሳደቡ አካላት ድሮም አሁንም የጠራን ነን። ፈፅሞ ከነሱ (እነሱን ከሚሳደቡት) ጋር አንሆንም።" ልብ በሉ! ጠሀ ኸዲር እነዚህን ሁለቱ ሰዎች (ማለትም ኢልያስ ዐባስ እና አሕመድ ሙሐመድ) ሞቅ አድርጎ ያወድሳል። ያሰራጭላቸዋልም፡፡ ለምሳሌ ያክል በቅርቡ እንዲህ ሲል ፅፏል:- أشد على أيديكم يا أبطال شرق هرر فضيلة الشيخ Sheek Iliyaas Abbaas وفضيلة الشيخ Shekh Ahmade Muhammed زادكم الله قوة إلى قوتكم فقد أقضت جهودكم المضاجع وألهبت المشاعر وأسهرت وهزت ولن يهنأ منهم أحد مهما كان بعدما التهبت الأحشاء واضطرمت! = እነዚህ የጠሀ ጀግኖች ግን፡ 1ኛ፦ ከነ ዶክተር ጀይላን ጋር እንደሆኑ ድሮም፣ አሁንም በመካከላችን ልዩነት እንደ ሌለ ገልፀዋል። እስከ ዘላለም ከነሱ እንደማይለዩም አስረግጠው ገልፀዋል። 2ኛ:- እነሱን (እነ ዶክተር ጀይላንን) ከሚሳደቡ አካላት ድሮም አሁንም የጠራን ነን። ፈፅሞ እነሱን ከሚሳደቡ ጋር አንሆንም ማለታቸውን ያዙ። እዚህ ላይ ቁጥር አንድ ተጠቃሹ ጠሀ ኸዲር ነው። አሞሌው አልሰራም። ከዚህ በኋላ ያለው ምርጫ ሁለት ነው። 1ኛው ምርጫ፦ ወይ እንደ ግለቱ እያዩ ሲያሻቸው "እኛ ድሮም ጀምሮ መንሀጅ ገብቶናል፣ ለ 20፣ ለ30 አመታት ሰለፊያን (የነሱን ቨርዥን) ስናስተምር ነው የኖርነው፣ ከኢኽዋን የጠራን ነን፣ ..." እያሉ መሞገት፤ ሲላቸው ደግሞ እነዚያኑ ኢኽዋን የሚሏቸውን ሰዎች "ድሮም አሁንም አንድ ነን፣ ዘላለም አንለያይም" እያሉ የጋራ መግለጫ እያወጡ መቀጠል። የተለያየ መመዘኛ፣ የተለያየ ፊት እያሳዩ መሄድ ለጠሀ ከባድ አይመስለኝም። ይሄ ግን የሰለፊ መገለጫ አይደለም። ሸይኽ ሙቅቢል እንዲህ ይላሉ፦ فالحزبي مستعد أن يكون له خمسة أوجه والنبي صلى الله عليه وسلم يقول : إن من شر الناس ذا الوجهين الذي يأتي هـولاء بوجه وهؤلاء بوجه . أما السني فإنه متمسك بدينه سواء رضي فلان أو لم يرضَ بخلاف الحزبيين . "ቡድንተኛ ሰው አምስት ፊት ሊኖረው ዝግጁ ነው። ነብዩ ﷺ 'ከክፉ ሰዎች ውስጥ የሆነው ባለ ሁለት ፊት ነው። ያ እነዚያ ዘንድ በአንድ ፊት፣ ሌሎቹን ደግሞ በሌላ ፊት የሚቀርበው።' ሱኒይ የሆነ ሰው ግን እከሌ ቢወድም ሆነ ቢጠላ ዲኑን አጥብቆ የሚይዝ ነው። ከቡድንተኞች በተለየ።" [ቱሕፈቱል ሙጂብ፡ 290] 2ኛው ምርጫ፦ ከነዚህ ሲያወድሳቸው ከነበሩ አካላት መለያየቱን ማወጅ ነው። ሰውየው ተቃራኒ ነገሮችን የማስተናገድ ልምድ ቢኖረውም ይሄኛው ግን ለመሸፈንም የሚመች አይደለም። "ግመል ሰርቆ አጎንብሶ" አይሆንም። ስለዚህ መለያየትን ከማወጅ ውጭ ምርጫ አይኖርም። ካህያ ቆዳ የተሰራ ቤት ይበታተናል ጅብ የጮኸ ለት! - የነዚህ ሰዎች ጉድ ይሄ ብቻ አይደለም። አለ ገና! ستُبْدي لكَ الأيّامُ ما كنتَ جاهلاً - ويأتِيكَ بالأخبارِ مَن لم تُزَوِّدِ = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
Hammasini ko'rsatish...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

ኢብኑ ቁዳማ አልመቅዲሲይ - ረሒመሁላህ - እንዲህ ይላሉ፦ "አብዛኞቹ ሰዎች የጠፉት የሰዎችን ውግዘት በመፍራት እና ሙገሳቸውን በመሻት ነው። በዚህ የተነሳ እንቅስቃሴያቸው እንዳለ ሰዎችን ከማስደሰት ጋር በሚገጥም መልኩ ይሆናል። ይህም ሙገሳን በመሻትና ውግዘትን በመፍራት ነው። ይሄ አጥፊ ስለሆነ ሊታከም ግድ ይላል።" "ሙኽተሶሩ መንሃጂል ቃሲዲን፡ 212] = የቴሌግራም ቻናል፡- https://t.me/IbnuMunewor
Hammasini ko'rsatish...
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)

كناشة ابن منور

Hammasini ko'rsatish...
ሩፈይዳ online market Official

ሩፈይዳ On line market የተለያዩ ሺቲዎች ፣ሻርብ፣ ጎጎራ ፈር ካልሲዎች፣ስትረች ሂጃቦች ፣አንደር ሂጃብ፣ጅልባቦች በፈለጉት ጨርቅ በፈለጉት ዲዛይን፣ጓንት፣ስቶክ ና ሳንዲ ካልሲዎች ጀለቢያ (ቶብ) አንደር ዌሮች ......እኛጋ ያገኛሉ ይዘዘዙን ያሉበት እናደርሳለን ለበለጠ መረጃ @Upda_ting ወይም @HNAAIM +251945253245 +251962187613 አድራሻ ፦ አዲስ አበባ