ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics"
ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ!
Ko'proq ko'rsatish📈 Telegram kanali ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics" analitikasi
ወሒድ የዕቅበተ ኢሥላም መጣጥፍት"Wahid Articles of Islamic Apologetics" (@wahidcom) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 62 463 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 821-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 510-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 62 463 obunachiga ega bo‘ldi.
07 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 817 ga, so‘nggi 24 soatda esa -17 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 24.14% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 8.24% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 15 080 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 5 144 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 0 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“ዳዒ ወሒድ በኢሥላም እና በክርስትና መካከል ያለውን ልዩነት እና አንድነት በንጽጽር የሚያስቀምጥ ወንድም ነው። ለዚህም የቋንቋ፣ የሰዋስው፣ የዐውድ፣ የተዛማች እና የሥነ አመክንዮ ሙግት በማቅረብ የሚታወቅ ተሟጋች እና ጦማሪ ነው። ለሙግቱ ነጥብ በዋነኝነት የሚጠቀምባቸው ቋንቋ ዐማርኛ፣ ግዕዝ፣ እንግሊዝኛ፣ ዐረቢኛ፣ ዕብራይስጥ እና ግሪክ ናቸው። መልካም የንባብ፣ የጥናት፣ የማነጻጸር ጊዜ ይሁንልዎ...”
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 08 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 08 Iyul | +14 | |||
| 07 Iyul | +1 | |||
| 06 Iyul | +10 | |||
| 05 Iyul | +13 | |||
| 04 Iyul | +10 | |||
| 03 Iyul | +22 | |||
| 02 Iyul | +15 | |||
| 01 Iyul | 0 |
| 2 | ቆሞስ አባ ገብረ ማርያም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ የትምህርት ገበታ ንባብ ቤት፣ ዜማ ቤት እና መጽሐፍ ቤት የሚባሉ ክፍሎች አሉ።
፨ ንባብ ቤት ግዕዝ ንባብ፣ ውርድ ንባብ እና ቁም ንባብ ሆነ የሚነበቡ መልዕክተ ዮሐንስ፣ ወንጌለ ዮሐንስ፣ መዝሙረ ዳዊት፣ የዘውትር ጸሎት፣ ውዳሴ ማርያም፣ አንቀጸ ብርሃን፣ ይወድስዋ መላእክት፣ መልክአ ማርያም፣ መልክአ ኢየሱስ ተጠቃች ናቸው።
፨ ዜማ ቤት ውዳሴ ማርያም፣ መስተጋብዕ፣ አርባዕት፣ አርያም፣ ሠልስት እና ቅዳሴ ወሰዐታት ወዘተ ናቸው።
፨ መጽሐፍ ቤት የጉባኤ ቤት ሲሆኑ መጽሐፈ ብሉይ፣ መጽሐፈ ሐዲስ፣ መጽሐፈ መነኮሳት እና መጽሐፈ ሊቃውንት ናቸው።
1.መጽሐፈ ብሉይ 46 የብሉይ መጻሕፍት የሥነ አፈታት ጥናት አንድምታ ነው፣
2. መጽሐፈ ሐዲስ 35 የሐዲስ መጻሕፍት የሥነ አፈታት ጥናት አንድምታ ነው፣
3. መጽሐፈ መነኮሳት የሚባሉት ማር ይስሐቅ፣ ፊልክስዩስ እና አረጋዊ መንፈሳዊ ናቸው።
4. መጽሐፈ ሊቃውንት የሚባሉት ሃይማኖተ አበው፣ ድርሳነ ቄርሎስ፣ ድርሳነ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ተግሣጸ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ፍትሐ ነገሥት፣ 14ቱ መጽሐፈ ቅዳሴ እና አቡሻሕር ናቸው።
ቆሞስ አባ ገብረ ማርያም ጌጡ በጉባኤ ቤት ያለፉ በብሉይ ኪዳን ያስመሰከሩ መጋቤ ብሉይ፣ በሐዲስ ኪዳን ያስመሰከሩ መጋቤ ሐዲስ፣ በመጽሐፈ መነኮሳት ያስመሰከሩ ቆሞስ፣ በመጽሐፈ ሊቃውንት ያስመሰከሩ ሊቀ ሊቃውንት ናቸው፥ በዚህም እርሳቸው አራቱንም ያስመሰከሩ አራት ዓይና ናቸው።
"ፆታ" ማለት "ወገን" "መደብ" "ተቃራኒ የመራቢያ አካል" "ተራ" ማለት ነው፦
ዘጸአት 39፥10 ዕንቍዎቹንም በአራት "ተራ" አደረጉበት።
"ተራ" ለሚለው በግዕዙ የገባው ቃል "ፆታ" ነው፥ ስለዚህ "ፆታ" የሚለው ቃል እንደየ ዐውዱ ይለያያል። "ፆታ" ለሁለት ይከፈላል፥ አንዱ የተፈጥሮ ፆታ ሲሆን ተቃራኒ የመራቢያ አካል ያለው ወንድ እና ሴት ነው፥ ሁለተኛው የሰዋስው ፆታ ሲሆን በወንድ አንቀጽ የሚቀመጥ የተባዕታይ መደብ እና በሴት አንቀጽ የሚቀመጥ የአንስታይ መደብ ነው። ነፍስ፣ መላእክት እና ፈጣሪ "እርሱ" ወይም "እርሷ" እያልን ስንጠቀም የሰዋስው መደብ እንጂ ወንድ ወይም ሴት አይደሉም።
ቆሞስ አባ ገብረ ማርያም ይህ ነገር ጠፍቷቸው ሳይሆን አንድ ሁለት ፉት ብለው እንደሆነ ከራሳቸው አንደበት ተናግረዋል። ይህ ዳህጸ ልሳን ሳይሆን ዳህጸ ምሥጢር ነው።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom | 6 748 |
| 3 | Matn yo'q... | 5 958 |
| 4 | "ለእግዚአብሔር እንደሰው የተወሰነ፣ የተከፋፈለ፣ ቅርጽ ያለው አካል የለውም አልን እንጂ አካል የለውም አላልንም። ያ አካሉ ደግሞ ድንቡልቡል ነው አንልም። ያ በምልአት ያለው አካል ወሰን የሌለበት ዓይን፣ እጅ፣ እግር አለው። ሃይማኖተ አበው የሚገልጽልን ይህንን ነው። ዐይኑ ከሆነ ቦታ፣ እጁ ከሆነ ቦታ፣ እግሩ ከሆነ ቦታ ተከፋፍሎ አለ ማለት ግን ክሕደት ይሆናል። ዐይኑ ካለበት ቦታ ሁሉ እጁ እግሩ አለ። አንዱ ኖሮ ሌላው የሌለበት ቦታ የለም። ይህንን ካልን መከፋፈል፣ ቅርጽ ማውጣት ውስጥ መግባት ነውና። ይህ ደግሞ አእምሯችን የፈጠረው እንጂ ለእግዚአብሔር አይነገርም። ዐይን፣ እጅ፣ እግር፣...ወዘተ እንዳለው እናምናለን። ዐይኑ፣ እጁ፣ እግሩ፣...ግን የተከፋፈለ፣ ቅርጽ ያለው፣ የተወሰነ ነው አንልም"
መምህር በትረ ማርያም አበባው | 9 711 |
| 5 | ምልክቶቹ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
31፥37 ሌሊት እና ቀንም ፀሐይ እና ጨረቃም ከምልክቶቹ ናቸው፡፡ وَمِنْ آيَاتِهِ اللَّيْلُ وَالنَّهَارُ وَالشَّمْسُ وَالْقَمَرُ
አምላካችን አሏህ ከእርሱ በፊት ምንም ነገር ስለሌለ "አል አወል" الْأَوَّل ነው፥ ከእርሱ በኃላ ምንም ነገር ስለሌለ "አል አኺር" الْآخِر ነው። እርሱ በሲፋቱ ግልጽ ስለሆነ "አዝ ዛሂር" الظَّاهِر ነው፥ እርሱ በዛቱ ስውር ስለሆነ "አል ባጢን" الْبَاطِن ነው፦
57፥3 እርሱ ፊትም ያለ እና ኋላም ቀሪ፥ ግልጽ እና ስውር ነው፡፡ እርሱም ነገሩን ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡ هُوَ الْأَوَّلُ وَالْآخِرُ وَالظَّاهِرُ وَالْبَاطِنُ ۖ وَهُوَ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمٌ
የአሏህ ዛት ከፍጡራን ውጪ እና ባሻገር ስላለ "መጅሁል" مَجْهُول ነው፥ "መጅሁል" مَجْهُول ማለት "የማይታወቅ"Unknowable" ማለት ሲሆን ይህ አፖፋቲኮስ ነው። "አፖፋቲኮስ" ἀποφατικός ማለት "አሉታዊ"Negation" ማለት ነው። ይህንን በቀላሉ እንድትረዱ ይህንን ጥቅስ ተመልከቱ፦
ኢዮብ 36፥26 እነሆ አምላክ ታላቅ ነው፥ እኛም አናውቀውም። የዘመኑም ቍጥር አይመረመርም። הֶן־אֵל שַׂגִּיא וְלֹא נֵדָע מִסְפַּר שָׁנָיו וְלֹא־חֵקֶר
"እኛም አናውቀውም" የሚለው ይሰመርበት! የአሏህ ሲፋህ ፍጡራንን ያካበበ ስለሆነ "መዕሉም" مَعْلُوم ነው፥ "መዕሉም" مَعْلُوم ማለት "የሚታወቅ"Knowable" ማለት ሲሆን ይህ ካታፋቲኮስ ነው። "ካታፋቲኮስ" καταφατικός ማለት "አውንታዊ"Affirmation" ማለት ሲሆን የአሏህን ሲፋት ማስበት ነው፥ የአሏህ ሲፋት በግልጠት የሚታወቅ ነው።
"ወሕይ" وَحْى የሚለው ቃል "አውሓ" أَوْحَىٰ ማለትም "ገለጠ" ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ግልጠት"Revelation" ማለት ነው፥ "ወሕይ" وَحْى እራሱ "ወሕይ ዓም" وَحْى عَامّ እና "ወሕይ ኻሥ" وَحْى خَاصّ ተብሎ ለሁለት ይከፈላል።
፨ "ዓም" عَامّ ማለት "ጥቅል"General" ማለት ሲሆን "ወሕይ ዓም" وَحْى عَامّ ማለት "ጥቅላዊ ግልጠት"General Revelation" ማለት ነው፦
99፥5 ጌታህ ለእርሷ "በማሳወቁ" ምክንያት፡፡ بِأَنَّ رَبَّكَ أَوْحَىٰ لَهَا
16፥68 ጌታህም ወደ ንብ እንዲህ ሲል "አስታወቀ"፦ «ከተራራዎች፣ ከዛፍም፣ ሰዎች ከሚሠሩትም ቀፎ ቤቶችን ያዢ፡፡ وَأَوْحَىٰ رَبُّكَ إِلَى النَّحْلِ أَنِ اتَّخِذِي مِنَ الْجِبَالِ بُيُوتًا وَمِنَ الشَّجَرِ وَمِمَّا يَعْرِشُونَ
ሁለቱም አናቅጽ ላይ "አሳወቀ" ለሚለው የገባው ቃል "አውሓ" أَوْحَىٰ ሲሆን አምላካችን አሏህ በፍጥረቱ እራሱ የገለጠበት ግልጠት ጥቅላዊ ግልጠት ነው፥ "አያቱል ከውኒያህ" آيَات الكَوْنِيَّة ማለት "ተፈጥሬአዊ ምልክት" ማለት ሲሆን አሏህ እራሱን የገለጠበት በተፈጥሮ ውስጥ ምልክቶች ነው፦
31፥37 ሌሊት እና ቀንም ፀሐይ እና ጨረቃም ከምልክቶቹ ናቸው፡፡ وَمِنْ آيَاتِهِ اللَّيْلُ وَالنَّهَارُ وَالشَّمْسُ وَالْقَمَرُ
"ምልክቶቹ" ለሚለው የገባው ቃል "አያቲ-ሂ" آيَاتِهِ ሲሆን ይህ "አያቱል ከውኒያህ" آيَات الكَوْنِيَّة ነው፦
45፥3 በሰማያት እና በምድር ውስጥ ለምእምናን ሁሉ እርግጠኛ "ምልክቶች" አሉ፡፡ إِنَّ فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ لَآيَاتٍ لِّلْمُؤْمِنِينَ
52፥36 ወይስ ሰማያትን እና ምድርን ፈጠሩን? አይደለም አያረጋግጡም፡፡ أَمْ خَلَقُوا السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضَ ۚ بَل لَّا يُوقِنُونَ
፨ "ኻስ" خَاصّ ማለት "ተናጥል"Specifical" ማለት ሲሆን "ወሕይ ኻስ" وَحْى خَاصّ ማለት "ተናጥሎአዊ ግልጠት"Specifical Revelation" ማለት ነው፦
4፥163 እኛ ወደ ኑሕ እና ከርሱ በኋላ ወደ ነበሩት ነቢያት እንዳወረድን ወደ አንተም አወረድን፡፡ إِنَّا أَوْحَيْنَا إِلَيْكَ كَمَا أَوْحَيْنَا إِلَىٰ نُوحٍ وَالنَّبِيِّينَ مِن بَعْدِهِ
"አወረድን" ለሚለው የገባው ቃል "አውሐይና" أَوْحَيْنَا ሲሆን አምላካችን አሏህ በነቢያቱ እራሱ የገለጠበት ግልጠት ተናጥሎአዊ ግልጠት ነው፥ "አያቱ አሽ ሸርዒያህ" آيَات الشَرْعِيَّة ማለት "ሸሪዓዊ ምልክት" ማለት ሲሆን አሏህ እራሱን የገለጠበት በአንቀጾቹ ነው፦
7፥35 የአዳም ልጆች ሆይ! ከእናንተ ውስጥ በእናንተ ላይ "አንቀጾቼን" የሚያነቡ መልእክተኞች ቢመጧችሁ ከእናንተ ክሕደትን የተጠነቀቁ እና መልካምንም የሠሩ በእነርሱ ላይ ፍርሃት የለባቸውም፡፡ እነሱም አያዝኑም፡፡ يَا بَنِي آدَمَ إِمَّا يَأْتِيَنَّكُمْ رُسُلٌ مِّنكُمْ يَقُصُّونَ عَلَيْكُمْ آيَاتِي ۙ فَمَنِ اتَّقَىٰ وَأَصْلَحَ فَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ
"አንቀጾቼ" ለሚለው የገባው ቃል "አያቲ" آيَاتِي ሲሆን ወደ መልእክተኞቹ የሚያወርደው ወሕይ የእርሱ ምልክቶቹ ሲሆን "አያቱ አሽ ሸርዒያህ" آيَات الشَرْعِيَّة ነው፦
18፥106 ነገሩ ይህ ነው፡፡ በክህደታቸው "አንቀጾቼን" እና መልእክተኞቼን መሳለቂያ አድርገው በመያዛቸው ፍዳቸው ገሀነም ነው፡፡ ذَٰلِكَ جَزَاؤُهُمْ جَهَنَّمُ بِمَا كَفَرُوا وَاتَّخَذُوا آيَاتِي وَرُسُلِي هُزُوًا
አምላካችን አሏህ በምልክቶቹ ያመኑ ባሮቹ ያድርገን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 9 537 |
| 6 | Matn yo'q... | 10 022 |
| 7 | የምሥራቅ ሥነ መለኮት የኦርቶዶክስ ሥነ መለኮት ሲሆን ከ 1296 ድኅረ ልደት እስከ 1359 ድኅረ ልደት ይኖር የነበረው ጎርጎርዮስ ፓላማስ"Gregory Palamas" ያፋፋው ፓላማዊ ሥነ መለኮት"Palamite Theology" የኦርቶዶክስ አንቀጸ እምነት ሆኗል፥ ፓላማዊ ሥነ መለኮት "በኡሲያህ እና በኢኔርጌያ መካከል የእውነት ልዩነት"Real distinction" አለ" የሚል ነው።
በኦርቶዶክስ ሥነ መለኮት ውስጥ ያለው በኡሲያህ እና በኢኔርጌያ መካከል የእውነት ልዩነት በፓላማዊነት"Palamism" ይፋፋ እና ይዳብር እንጂ ከጥንትም በአበው ነበረ፥ ሦስቱ የቀጰዶቅያን አበው"Cappadocian Fathers" የሚባሉት ባስልዮስ ዘቂሳሪያ፣ የባስሊዮስ ወንድም ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ እና ጓደኛው ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ ናቸው። ባስልዮስ ዘቂሳሪያ "ታላቁ ባስልዮስ" በሚል የሚታወቅ ሲሆን ስለ ምንነት እና ስለ የምንነት ባሕሪዮት እንዲህ ይለናል፦
"እርሱ(ኢይኖመስ) እንዳለው አምላክ ነጠላ ነው፥ እናም የእርሱን ባሕሪ"Attribute" ማወቅ የምትችሉትን ማንኛውንም ባሕሪ ከምንነቱ"Essence" ነው"።
Letters (St. Basil of Caesarea) Letter 234 Number 1
"የአምላክ ታላቅነት፣ ኃይሉን፣ ጥበቡን፣ መልካምነቱን፣ በእኛ ላይ ያለውን ሲሳዩን እና የፍርዱን ፍትሓዊነትነት እናውቃለን" እንላለን፥ ነገር ግን የእሱን እውነተኛ ምንነት"Essence" አይደለም"።
Letters (St. Basil of Caesarea) Letter 234 Number 1
"በምንነቱ እና በእያንዳንዱ በተዘረዘሩት ባሕሪያት መካከል ልዩነት እንዳለ እራሳቸውን አምነዋልና፥ ባሕሪያት የተለያዩ ሲሆኑ ምንነቱ ነጠላ ነው። "አምላካችንን ከባሕሪያቱ እናውቀዋለን፥ ነገር ግን ወደ እርሱ ምንነት ለመቅረብ አንዳፈርም" እንላለን፥ የእሱ ባሕሪያት ወደ እኛ ሲወርዱ ነገር ግን የእርሱ ምንነት ከአጸዳችን ባሻገር ይቀራል"።
Letters (St. Basil of Caesarea) Letter 234 Number 1
ባስልዮስ ዘቂሳሪያ በግልጽ በኡሲያ እና በኢኔርጌያ መካከል ያለውን ልዩነት ፍትንው እንዲህ ከላይ አርጎ ገልጿል። የባስሊዮስ ወንድም ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ በኡሲያ እና በኢኔርጌያ መካከል ያለውን ልዩነት ቁልጭ አርጎ አስቀምጧል፦
"የምትጠቀሙበት እያንዳንዱ ስም የኑባሬ ባሕሪ ነው፥ ነገር ግን የኑባሬ አይደለም"።
Against Eunomius (Gregory of Nyssa) Book VII(7) Number 5
"ምክንያቱም በተፈጥሮው ከዓይናችን በላይ የሆነው አምላክ በባሕሪያቱ ይገለጻል፥ ኑባሬው በአጸዱ ባሉት ባሕሪዮት ይገለጻል"።
On the Beatitudes (Gregory of Nyssa) Homily 6
ከጥንትም ጀምሮ በነበሩት አበው ሆነ በኦርቶዶክስ ሥነ መለኮት "አምላክ በኢኔርጌያ እንጂ በኡሲያ አልተገለጸም አይገለጽም" ብለው ያምናሉ። ዮሐንስ ዘደማስቆ"John of Damascus" በኡሲያ እና በኢኔርጌያ መካከል ያለውን ልዩነት እንዲህ ሲል አስቀምጦአል፦
"አምላክ የአምላክን ምንነት እንደማያሳይ እና ነገር ግን የምንነቱን ባሕሪያት ብቻ እንደሚያሳይ ማረጋገጥ እንችላለን፥ ምክንያቱም ስለ እርሱ ቸር፣ ጻድቅ፣ ጥበበኛ እና የመሳሰሉትን ስትናገር የምትናገረው የአምላክን ምንነት ሳይሆን የምንነቱን ባሕርያት ብቻ ነው"።
An Exposition of the Orthodox Faith (John of Damascus) Book I(1) Chapter 4
በነገራችን ላይ በኦርቶዶክስ ሥነ መለኮት ኢኔርጌያ ያልተፈጠረ፣ ዘላለማዊ እና ኡሲያ ያልሆነ ነው፥ ኢኔርጌያ የተባሉት ችሎታ፣ ኃይል፣ ንግሥና፣ ፍርድ፣ ቸርነት፣ ምሕረት፣ ጥበብ፣ ዕውቀት የአምላክ ናቸው እንጂ እያንዳቸው አምላክ አይደሉም። "አምላክ እነዚህ ባሕርዮት አሉት" እንጂ "አምላክ ናቸው" አይባልም፥ ለምሳሌ፦ የእኔ ማየት፣ መስማት፣ መናገር፣ ማወቅ የእኔ ባሕሪዮት እንጂ እኔ አይደለሁም። የእኔ ማየት፣ መስማት፣ መናገር፣ ማወቅ ወሒድ ሳይሆኑ የወሒድ ናቸው፥ ከወሒድ ውጪም አይደሉም።
ስለዚህ እኛ ሙሥሊሞች በዛት እና በሲፋት መካከል ያለውን ልዩነት ስናስቀምጥ እና የአሏህ ማየት፣ መስማት፣ መናገር፣ ማወቅ ወዘተ "አሏህ ሳይሆኑ የአሏህ ባሕሪያት ናቸው" ስንል በቀላሉ መረዳት ትችላላችሁ። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይወፍቃችሁ! ለእኛም ኢሥቲቃማህ ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 15 155 |
| 8 | ዛት እና ሲፋት
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
21፥22 የዐርሹ ጌታ አሏህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡ فَسُبْحَانَ اللَّهِ رَبِّ الْعَرْشِ عَمَّا يَصِفُونَ
"ዛት" ذَات ማለት "ምንነት"Essence" ወይም "ኑባሬ"Being" ማለት ሲሆን ምንነት የማንነት መሠረት እና የባሕርዮት ባለቤት ነው፥ "ሲፋህ" صِفَة የሚለው ቃል "ወሶፈ" وَصَفَ ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ባሕሪ"Attribute" ማለት ነው፦
21፥22 የዐርሹ ጌታ አሏህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡ فَسُبْحَانَ اللَّهِ رَبِّ الْعَرْشِ عَمَّا يَصِفُونَ
37፥180 የማሸነፍ ጌታ የሆነው ጌታህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡ سُبْحَانَ رَبِّكَ رَبِّ الْعِزَّةِ عَمَّا يَصِفُونَ
43፥82 የሰማያት እና የምድር ጌታ የዙፋኑ ጌታ ከሚሉት ነገር ሁሉ ጠራ፡፡ سُبْحَانَ رَبِّ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ رَبِّ الْعَرْشِ عَمَّا يَصِفُونَ
ሦስቱም አናቅጽ ላይ "ከሚሉት"They Attribute" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "የሲፉነ" يَصِفُونَ ሲሆን ሥርወ ቃሉ "ወሶፈ" وَصَفَ ነው፥ "ሠልቢያህ" سَلْبِيَّة ማለት "አሉታዊ"Negative" ማለት ሲሆን ሰዎች አሏህን የሚወስፉበት ይህ ለአሏህ ያልተገባ ባሕሪ "ሲፋህ ሠልቢያህ" صِفَة سَلْبِيَّة ነው።
"ሲፋት" صِفَات ደግሞ "ሲፋህ" صِفَة ለሚለው ብዙ ቁጥር ሲሆን "ባሕሪዮት" ወይም "ባሕሪያት"Attributes" ማለት ነው፥ "ኢሥሙ አዝ ዛት" اِسْمُ الذَات ማለት "የምንነት ስም"Concrete Name" ማለት ሲሆን "አሏህ" اللَّه የሚለው ስም የዛቱ ስም ነው። "መውሱፍ" مَوْصُوف ማለት የባሕሪ "ባለቤት" ማለት ሲሆን አሏህ መውሱፍ እንጂ ሲፋህ አይደለም፥ "ወስፍ" وَصْف ማለት "ገላጭ"Description" ማለት ሲሆን እያንዳንዱ የአሏህ ባሕሪያት ዛቱን የሚገልጡ ናቸው።
በቁርኣን አሏህ እራሱን የወሶፈበት ወስፍ ከፍጥረት መፈጠር በፊት የእርሱ ባሕርያት የሆኑትን "ቁድራህ" قُدْرَة "ቁዋህ" قُوَّة "ሙልክ" مُلْك "ሑክም" حُكْم "ከረም" كَرَم "ረሕማህ" رَحْمَة "መሐባህ" مَحَبَّة "ሒክማህ" حِكْمَة "ዒልም" عِلْم "ከላም" كَلَام "ሠምዕ" سَمْع "በሲራህ" بَصِيرَة ወዘተ ሲሆኑ ያልተፈጠሩ ቀዲም ናቸው፥ "ቀዲም" قَدِيم ማለት መነሻ እና ጅማሮ የሌለው "ዘላለማዊ"Eternal" ማለት ነው።
"ሱቡቲያህ" ثُبُوتِيَّة ማለት "አውንታዊ"Positive" ማለት ሲሆን አሏህ በቁራኑ እራሱን የወሶፈበት ወስፍ "ሲፋህ ሠልቢያህ" صِفَة سَلْبِيَّة ነው፥ የአሏህን ሲፋህ በማስበት ከይፊያውን ወደ አሏህ ተፍዊድ በማድረግ መቀበል የንዑዳን እና የኅሩያን ሙሥሊሞች መታወቂያ ነው።
"ተዕጢል" تَعْطِيل ማለት "ማራቆት" ማለት ሲሆን ከ 696 እስከ 745 ድኅረ ልደት ይኖር በነበረው በጀህም ኢብኑ ሶፍዋን የተጀመረ ዐቂዳህ "ጀህሚያ" جَهْمِيَّة እና ከ 699 እስከ 748 ድኅረ ልደት ይኖር በነበረው በዋሲል ኢብኑ ዐጣእ የተጀመረ ዐቂዳህ "ሙዕተዚላህ" مُعْتَزِلَة ከላይ የተዘረዘሩትን የአሏህን ባሕሪዮት ያራቁታሉ፥ ከ 874 እስከ 936 ድኅረ ልደት ይኖር በነበረው በአቡ አል ሐሠን አል አሽዐሪይ የተጀመረ ዐቂዳህ "አሽዐሪያህ" أَشْعَرِيّة ከፊል የአሏህን ባሕሪያት በማራቆት በታሪክ ይታወቃሉ።
የአርስጣጣሊስ"Aristotle" ፍልስፍና የተጸናወታቸው እነዚህ ሰዎች በቶማስ አኳይነስ"Thomas Aquinas" ላይ ተጽዕኖ አሳድረውበታል፥ ቶማስ አኳይነስ በአሽዐሪይ አል ገዛሊ፣ በአርስጣጣሊስ ግርፍ ኢብኑ ሢና፣ በአርስጣጣሊስ ቅጥቅጥ አል ፋራቢይ፣ በአርስጣጣሊስ ጀሌ ኢብኑ ሩሽድ ተጽዕኖ ሥር ወድቋል።
የምዕራብ ሥነ መለኮት የካቶሊክ ሥነ መለኮት ሲሆን ከ 1225 ድኅረ ልደት እስከ 1274 ድኅረት ይኖር የነበረው ቶማስ አኳይነስ ያፋፋው ቶማሳዉ ሥነ መለኮት"Thomite Theology" የካቶሊክ አንቀጸ እምነት ሆኗል፥ ቶማሳዉ ሥነ መለኮት "አምላክ ነው እንጂ አለው" የሚባል ባሕሪዮት አያስቀምጥም።
"መለኮት ሁሉን ቻይ፣ ኃያል፣ ንጉሥ፣ ፈራጅ፣ ቸር፣ አፍቃሪ፣ ጥበበኛ፣ ዐዋቂ፣ መሐሪ፣ ተናጋሪ፣ ሰሚ፣ ተመልካች ነው" እንጂ ከፍጥረት በፊት "አለው" የሚባሉትን ችሎታ፣ ኃይል፣ ንግሥና፣ ፍርድ፣ ቸርነት፣ ምሕረት፣ ጥበብ፣ ዕውቀት፣ ንግግር፣ ማየት፣ መስማት ባሕሪዮት አይቀበሉም፥ ይህ በካቶሊክ ሥነ መለኮት "ፍጹም መለኮታዊ ነጠላዊነት"Absolute Divine Simplicity" ሲሆን ከጀህሚያ" እና ከሙዕተዚላህ እሳቤ ጋር ተመሳሳይ ነው።
በካቶሊክ ሥነ መለኮት ውስጥ ያለው ፍጹም መለኮታዊ ነጠላዊነት በቶማሳዉ ሥነ መለኮት ቶማሳዊነት"Thomism" ይፋፋ እና ይዳብር እንጂ በ 1054 ድኅረ ልደት "ታልቁ ክፍልል"Great Schism" ከአስባላቸው ልዩነት አንዱ በኡሲያህ እና በኢኔርጌያ መካከል ያለውን ልዩነት ላይ አለመስማማት ነው።
"ኡሲያ" οὐσία ማለት "ምንነት"Essence" ማለት ሲሆን "ኢኔርጌያ" ἐνέργειᾰ "ባሕሪ"Attribute" ማለት ነው፥ ቶማስ አኳይነስ፦ "ምንነት እና ባሕሪ የአሳብ ልዩነት"Virtual distinction" እንጂ የእውነት ልዩነት የላቸውም" የሚል እምነት አለው።
የምሥራቅ ሥነ መለኮት የኦርቶዶክስ ሥነ መለኮት ሲሆን ከ 1296 ድኅረ ልደት እስከ 1359 ድኅረ ልደት ይኖር የነበረው ጎርጎርዮስ ፓላማስ"Gregory Palamas" ያፋፋው ፓላማዊ ሥነ መለኮት"Palamite Theology" የኦርቶዶክስ አንቀጸ እምነት ሆኗል፥ ፓላማዊ ሥነ መለኮት "በኡሲያህ እና በኢኔርጌያ መካከል የእውነት ልዩነት"Real distinction" አለ" የሚል ነው። | 11 451 |
| 9 | መለኮታዊ ነጠላነት
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
112፥1 በል «እርሱ አሏህ አንድ ነው»። قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ
"ሙፍረድ" مُفْرَد ማለት የማይከፈል "ነጠላ"Simple" ማለት ሲሆን አሏህ እርሱ የማይከፋፈል አንድ ነጠላ ምንነት እና ማንነት ነው፦
112፥1 በል «እርሱ አሏህ አንድ ነው»። قُلْ هُوَ اللَّهُ أَحَدٌ
"አሐድ" أَحَد ማለት "ፍጹም አንድ" ማለት ሲሆን አሏህ በማንነቱ ሆነ በምንነቱ አንድ ነው፥ "ኢፍራድ" إِفْرَاد ማለት "ነጠላነት"Simplicity" ማለት ሲሆን በኢሥላም ሥነ መለኮት "ኢፍራድ" إِفْرَاد ማለት "መለኮታዊ ነጠላነት"Divine Simplicity" ማለት ነው።
"ሙረከብ" مُرَكَّب ማለት "ውቅር" "ክፍልፍ"Complex" ማለት ሲሆን አሏህ ልክ እንደ ሥላሴ ከሦስት ማንነቶች የተዋቀረ አሊያም የባሕሪያቱ ድምር ውጤት አይደለም፥ "ተርኪብ" تَرْكِيب ማለት "ክፍልፍልነት"Complexity" ማለት ሲሆን በኢሥላም ሥነ መለኮት "ተርኪብ" تَرْكِيب ማለት "መለኮታዊ ክፍልፍልነት"Divine Complexity" ማለት ነው።
ተርኪብ በኢሥላም ኢንካር የተደረገ እሳቤ ነው፥ ኢንካር ማለት "ውግዝ"Anathema" ማለት ሲሆን አሏህን የአካል ውቅር፣ ክፍልፍል እና ድምር አርጎ መውሰድ "ተርኪብ" تَرْكِيب ነው።
"ጂሥም" جِسْم ማለት "አካል"Body" ማለት ሲሆን "ፈጣሪ አካል ነው" ብሎ የሚያስተምር ሰው "ሙጀሠም" مُجَسَّم ሲባል "ፈጣሪ አካል ነው" የሚል አስተምሮቱ "ተጅሢም" تَجْسِيم ይባላል። 9ኛው ክፍለ ዘመን ላይ አቡ ዐብደሏህ ኢብኑ ከራም "ፈጣሪ አካል ነው" ብሎ ያስተምር ነበር፥ የእርሱ ትምህርት "ከራሚያህ" كَرَّامِيَّة ሲባል ኢንካር የተደረገ ትምህርት ነው።
በግሪክ "ሶማ" σώμα ማለት "አካል"Body" ማለት ሲሆን "አምላክ አካል ነው" የሚል ዕይታ "አካላዊ ዕይታ"The Physical View" ይባላል፥ ይህ ዕይታ ካላቸው መካከል ከ 160 እስከ 240 ድኅረት ልደት ይኖር የነበረው ጠርጡሊያኖስ ዘካርቴጅ"Tertullian of Carthage" ነው፦
"በእግጠኝነት "እርሱ በአምላክ መልክ ሲኖር ሳለ ከአምላክ ጋር መተካከልን መቀማት እንደሚገባ ነገር አልቈጠረውም" ፊልጵስዩስ 2፥6 በምን ዓይነት የአምላክ መልክ? በእርግጥ እርሱ ማለት በሆነ መልክ እንጂ በምንም አይደለም። አምላክ መንፈስ ቢሆንም አምላክ አካል መሆኑን ማን ይክዳል? ዮሐንስ 4፥24 መንፈሱ በራሱ መልክ የራሱ የሆነ ተክለ አካል አለውና"።
Against Praxeas (Tertullian) Chapter 7
እዚህ ዐውድ ላይ "አካል" ሲባል "ማንነት"Person" ሳይሆን "ተክለ አካል"Body" ማለት ነው፥ ይህ ዕይታ በዲኑል ኢሥላም መቅቡል ሳይሆን መርዱድ ነው።
በአገራችን ኦርቶዶክስ በስህተት ይሁን ሆን ተብሎ "ለአብ ፍጹም ገጽ፣ ፍጹም መልክ፣ ፍጹም አካል አለው፣ ለወልድም ፍጹም ገጽ፣ ፍጹም መልክ፣ ፍጹም አካል አለው፣ ለመንፈስ ቅዱስ ፍጹም ገጽ፣ ፍጹም መልክ፣ ፍጹም አካል አለው" የሚል ትምህርት አላቸው፥ የአገራችን ሊቅ ደብተራው አማን ነጸረ "ተኀሦሥ" በሚል መጽሐፋቸው እንዲህ ሲሉ ከትበዋል፦
"በብዙኃን ኢትዮጵያውያን የሚደገፈው ትርጓሜ "እግዚአብሔር መልክ አካል አለው፥ ነገር ግን አይመረመርም" የሚል ነው"።
ተኀሦሥ ገጽ 65
ወደ ነጥቡ ስንመለስ 189 ድኅረ ልደት ላይ ኢራኒየስ ዘሊዮን"Irenaeus of Lyon" ስለ ፈጣሪ ሲናገር፦ "እርሱ ነጠላ አንድ ነው እንጂ ከነገሮች የተገጣጠመ ኑባሬ አይደለም" ብሎአል፦
"እርሱ ነጠላ አንድ ነው እንጂ ከነገሮች የተገጣጠመ ኑባሬ አይደለም"።
Against Heresies (St. Irenaeus) Book II(2) Chapter 13 Number 3
በካቶሊክ ሥነ መለኮት "ፍጹም መለኮታዊ ነጠላዊነት"Absolute Divine Simplicity" ሲሆን ይህ እሳቤ የአምላክን ባሕሪዮት በማራቆት ከጀህሚያ" እና ከሙዕተዚላህ እሳቤ ጋር ተመሳሳይ ነው፥ በተቃራኒው የኦርቶዶክስ ሥነ መለኮት "መለኮታዊ ነጠላዊነት" እሳቤ የቀጰዶቅያን አበው እሳቤ ሲሆን በምንነት እና በባሕሪዮት መካከል ልዩነት"Essence-Energy Distinction" የሚያስቀምጠው "EED" የሚባለው እሳቤ ከጥንት እና ከጠዋት ጀምሮ ከሠለፎች ሲወርድ እና ሲወራረድ ከመጣው ከአል አሲሪያህ እሳቤ ጋር ተመሳሳይ ነው።
የእኛ የሙሥሊሞች የጥንቱ ዐቂዳችን "አል አሲሪያህ" الأَثِيرِيّة ነው፥ "አሰር" أَثَر የሚለው ቃል "አሰረ" أَثَرَ ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ትውፊት" "ቅብብሎሽ" "ቅሪት" ማለት ነው። " "አል አሲሪያህ" الأَثِيرِيّة ማለት "ትውፊታዊነት" ማለት ሲሆን የአሏህን ንግግር ቁርኣን እና የተወዳጁ ነቢያችንን"ﷺ" ሡናህ በሐቂቃው ተቀብሎ መከተል እና የአሏህን ሲፋህ በማስበት ከይፊያውን ወደ አሏህ ተፍዊድ ማድረግ አል አሲሪያህ ነው፥ የሠለፎችን ዐቂዳህ ሳይሸራርፍ እና ሳይጨምር ሙጭጭ ብሎ የያዘ የሙሥሊም ዐቂዳህ " "አል አሲሪያህ" الأَثِيرِيّة ይባላል።
በነገራችን ላይ አሏህ ባሕሪያት አሉት እንጂ አሏህ ባሕርያቱን ነው ወይም ባሕሪያቱ አሏህ ነው" ብለን አናምንም፥ በኦርቶዶክስ ሥነ መለኮት "ባሕሪ"Energy" የአምላክ እንጂ አምላክ ነው" ተብሎ አይታመንም። "አሜቴክቶስ" ἀμέθεκτος ማለት "የማይገናኝ" ማለት ሲሆን ፈጣሪ በምንነቱ ከፍጥረት ውጪ ስለሆነ የማይገናኝ ነው፥ "ሜቴክቶስ" μεθεκτός "ማለት "የሚገናኝ" ማለት ሲሆን ፈጣሪ በባሕሪያቱ ከፍጥረቱ ጋር የሚገናኝ ነው። በኢሥላም ሥነ መለኮት አሏህ ከፍጥረት ውጪ በምንነቱ "ምጡቅ"Transcendence" መሆኑ "ተንዚህ" تَنْزِيه ሲባል አሏህ በባሕሪያቱ ከፍጡራን ጋር ያለው ባለው ግኑኝነት እና "ቅርበት"Immanence" ደግሞ "ተቅሪብ" تَقْرِيب ይባላል።
ይልቁንስ በአጽንዖት እና በአንክሮት ካጠናንን ከመኮታዊ ነጠላነት ጋር የሚጋጨው እሳቤ የሥላሴ እሳቤ ነው፥ እያንዳንዱ አምልኮን የሚቀበሉ እና አምላክነትን የሚጋሩ ሦስት ማንነቶች ካሉ ይህ መለኮታዊ ክፍልፍልነት"Divine Complexity" ነው። ኢንሻ አሏህ በቀጣይ ጊዜ ስለ ዛት እና ሲፋት ከክርስትና እና ከኢሥላም አንጻር እንመለከታለን። አምላካችን አሏህ በዐቂዳችን ያጽናን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 11 302 |
| 10 | እርግማን
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
11፥18 ንቁ! የአሏህ እርግማን በበዳዮች ላይ ይሁን፡፡ أَلَا لَعْنَةُ اللَّهِ عَلَى الظَّالِمِينَ
“ዛሊም” ﻇَﺎﻟِﻢ ማለት “በዳይ” ማለት ሲሆን "ዛሊሚን" ظَّالِمِين ደግሞ "በዳዮች" ማለት ነው፥ አሏህ የአምልኮ ሐቅ ገንዘቡ ሆኖ ሳለ በማሻረክ የዞለሙትን በደለኞችንም ናቸው። "ዙልም" ظُلْم ማለት "በደል" ማለት ሲሆን በአሏህ ላይ ምንም ነገር ማጋራት ታላቅ በደል ነው፦
31፥13 ሉቅማንም ለልጁ እርሱ የሚገስጸው ሲሆን፦ «ልጄ ሆይ! በአሏህ አታጋራ! ማጋራት ታላቅ በደል ነውና» ያለውን አስታውስ። وَإِذْ قَالَ لُقْمَانُ لِابْنِهِ وَهُوَ يَعِظُهُ يَا بُنَيَّ لَا تُشْرِكْ بِاللَّهِ ۖ إِنَّ الشِّرْكَ لَظُلْمٌ عَظِيمٌ
"ለዕናህ" لَعْنَة ማለት "እርግማን" "መርገም" "ውግዘት" "ቁጣ" ማለት ነው፥ ከእምነታቸው እና መልእክተኛውም እውነት መኾኑን ከመሰከሩ፣ የተብራሩ አንቀጾችም ከመጡላቸው በኋላ የካዱን ሕዝቦች በዳዮችን ናቸው፦
3፥86 ከእምነታቸው እና መልእክተኛውም እውነት መኾኑን ከመሰከሩ፣ የተብራሩ አንቀጾችም ከመጡላቸው በኋላ የካዱን ሕዝቦች አሏህ እንዴት ያቀናል! አሏህ በዳዮችንም ሕዝቦች አያቀናም፡፡ كَيْفَ يَهْدِي اللَّهُ قَوْمًا كَفَرُوا بَعْدَ إِيمَانِهِمْ وَشَهِدُوا أَنَّ الرَّسُولَ حَقٌّ وَجَاءَهُمُ الْبَيِّنَاتُ ۚ وَاللَّهُ لَا يَهْدِي الْقَوْمَ الظَّالِمِينَ
የአሏህ እርግማን በከሓዲዎች እና በበዳዮች ላይ ይሁን! እነዚያ የካዱት በደለኞች ቅጣታቸው የአሏህ፣ የመላእክት እና የሰዎች ሁሉ እርግማን በእነርሱ ላይ መኾን ነው። እነዚያ የካዱ እነርሱ ከሐዲዎች ኾነውም የሞቱ እነዚያ በእነርሱ ላይ የአሏህ፣ የመላእክት እና የሰዎች ሁሉ እርግማን አለባቸው፦
2፥89 የአሏህ ርግማን በከሓዲዎች ላይ ይኹን፡፡ فَلَعْنَةُ اللَّهِ عَلَى الْكَافِرِينَ
11፥18 ንቁ! የአሏህ እርግማን በበዳዮች ላይ ይኹን፡፡ أَلَا لَعْنَةُ اللَّهِ عَلَى الظَّالِمِينَ
3፥87 እነዚያ ቅጣታቸው የአሏህ፣ የመላእክት እና የሰዎች ሁሉ እርግማን በእነርሱ ላይ መኾን ነው፡፡ أُولَـٰئِكَ جَزَاؤُهُمْ أَنَّ عَلَيْهِمْ لَعْنَةَ اللَّهِ وَالْمَلَائِكَةِ وَالنَّاسِ أَجْمَعِينَ
2፥161 እነዚያ የካዱ እነርሱ ከሐዲዎች ኾነውም የሞቱ እነዚያ በእነርሱ ላይ የአሏህ፣ የመላእክት እና የሰዎች ሁሉ እርግማን አለባቸው፡፡ إِنَّ الَّذِينَ كَفَرُوا وَمَاتُوا وَهُمْ كُفَّارٌ أُولَـٰئِكَ عَلَيْهِمْ لَعْنَةُ اللَّهِ وَالْمَلَائِكَةِ وَالنَّاسِ أَجْمَعِينَ
ደረታቸውን ሞልተው አፋቸውን ከፍተው እንደ አህያ የሚያናፉት ዘለሰኛ ሚሽነሪዎች ለመጽሐፋቸው ባዕዳ እና እንግዳ መሆናቸው የሚያሳብቅባቸው ባይብል ላይ ስለ እርግማን የተጻፈውን በቅጡ እና በአግባብ አለማንበባቸው ነው፦
ምሳሌ 3፥33 የአሏህ መርገም በኃጥእ ቤት ነው፥ የጻድቃን ቤት ግን ይባረካል። لَعْنَةُ اللهِ عَلَى بَيْتِ الشِّرِّيرِ، وَيُبَارِكُ بَيْتَ الأبْرَارِ.
ዐረቢኛው ባይብል ላይ "ለዕነቱል ሏህ" لَعْنَةُ الله በማለት ፍንትው እና ቁልጭ አርጎ አስቀምጦታል፥ "ኃጥእ" ማለት "ኃጢአተኛ" ማለት ሲሆን መርገም የሚያመጣው የአምላክን ትእዛዝ አለመስማት፣ ከትእዛዙ መንገድ ፈቀቅ ማለት፣ ሌሎችንም አማልክት መከተል ነው፦
ዘዳግም 11፥26 እነሆ እኔ ዛሬ በፊታችሁ በረከትንና መርገምን አኖራለሁ፤
ዘዳግም 11፥27 በረከትም እኔ ዛሬ ለእናንተ የማዝዘውን የአምላካችሁን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ብትሰሙ፤
ዘዳግም 11፥28 መርገምም የአምላካችሁን የያህዌህን ትእዛዝ ባትሰሙ፥ ዛሬም ካዘዝኋችሁ መንገድ ፈቀቅ ብትሉ፥ ሌሎችንም የማታውቋቸውን አማልክት ብትከተሉ ነው።
ዘለሰኛ ሚሽነሪዎች ለመጽሐፋቸው ምን ያህል ዳተኛ እና ልግመኛ እንደሆኑ ተመለከታችሁን? ዘለሰኛ ሚሽነሪዎች ድሮም እና ዘንድሮም ሲያዘጠዝጡ እና ሲያውደለድሉ እንጂ ሲሻሻሉ አይታዩም። መፈናጀሉን እና መጀናፈሉን ትተው በትህትና ቢያነቡ አይሻልምን? በአዲስ ኪዳንም እኮ እርማን አለ፦
1ኛ ቆሮንቶስ 16፥22 ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን የማይወድ ቢኖር "የተረገመ ይሁን"።
"የተረገመ ይሁን" አሚን። ከኢየሱስ አብ እንደሚመልጥ አንድ ሰው ካላመነ አሁንም ቢሆን የተረገመ ነው፦
ዮሐንስ 14፥28 የምትወዱኝስ ብትሆኑ ከእኔ አብ ይበልጣልና።
ለመጽሐፋቸው ባይተዋሮች እንደ ውኃ ፈሳሽ እንደ እንግዳ ደራሽ ዱብ ያለውን ይህንን ጥቅስ ሲያዩ ምን ይውጣቸው ይሆን? ስለዚህ "ቁርኣን የእርግማን መጽሐፍ ነው" ብሎ በዕውር ድንብር ሙግት ማዋቀር እና ማደራጀት ከንቱ ተምኔት ነው። አምላካችን አሏህ ሂዳያውን ይወፍቃቸው! ለእኛም ኢሥቲቃማውን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 16 480 |
| 11 | አራተኛው አካል
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
21፥22 በሁለቱ ውስጥ ከአሏህ ሌላ አማልክት በነበሩ ኖሮ በተበላሹ ነበር፡፡ የዐርሹ ጌታ አሏህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡ لَوْ كَانَ فِيهِمَا آلِهَةٌ إِلَّا اللَّهُ لَفَسَدَتَا ۚ فَسُبْحَانَ اللَّهِ رَبِّ الْعَرْشِ عَمَّا يَصِفُونَ
በሥላሴ እሳቤ አብ፣ ወልድ እና መንፈስ ቅዱስ በአካል ሦስት ስለሆኑ "ሦስቱ አማልክት" ይባላሉ፦
ሰይፈ ሥላሴ ዘሐሙስ ምዕራፍ 5 ቁጥር 22
"ሠለስቱ አማልክት ልዑላን አሐዱ ሥልጣነ ምልክናሆሙ"
ትክክለኛ ትርጉሙ "የአምላክነታቸው ሥልጣን አንድ የሆነ ሦስቱ አማልክት ልዑላን ናቸው" የሚል ነው፥ ዐማርኛው ላይ "የገዥነታቸው ሥልጣን አንድ ሲሆን ሦስቱ ልዑላን ገዥዎች ናቸው" ብሎ ቢያስቀምጥም "ሠለስቱ አማልክት" ማለት "ሦስቱ አማልክት" ማለት ነው።
በሁለቱ ማለትም በሰማይ እና በምድር ውስጥ ከአሏህ ሌላ አማልክት በነበሩ ኖሮ በተበላሹ ነበር፡፡ የዐርሹ ጌታ አሏህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፦
21፥22 በሁለቱ ውስጥ ከአሏህ ሌላ አማልክት በነበሩ ኖሮ በተበላሹ ነበር፡፡ የዐርሹ ጌታ አሏህ ከሚሉት ሁሉ ጠራ፡፡ لَوْ كَانَ فِيهِمَا آلِهَةٌ إِلَّا اللَّهُ لَفَسَدَتَا ۚ فَسُبْحَانَ اللَّهِ رَبِّ الْعَرْشِ عَمَّا يَصِفُونَ
እንደ ዐበይት ክርስትና መንፈስ ቅዱስ ሦስተኛው አካል እና የግጻዌ መለኮት አባል ነው፥ እንደ ባይብሉ ግን መንፈስ ቅዱስ ከአምላክ አፍ እና አፍንጫ የሚወጣ እስትንፋስ ነው፦
መዝሙር 33፥6 ሠራዊታቸውም ሁሉ "በ-"አፉ እስትንፋስ" ጸኑ። וּבְר֥וּחַ פִּ֝֗יו כָּל־צְבָאָֽם׃
ዘጸአት 15፥8 "በ-"አፍንጫህ እስትንፋስ" ውኆች ተከመሩ። וּבְר֤וּחַ אַפֶּ֙יךָ֙ נֶ֣עֶרְמוּ מַ֔יִם
እነዚህ ሁለት አናቅጽ ላይ "እስትንፋስ" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "ሩሓህ" רוּחַ ሲሆን "መንፈስ" ማለት ነው፥ እንደ ባይብሉ አምላክ መንፈስ ሲሆን ከእርሱ መንፈሱ የሚፈስ ነው፦
ዮሐንስ 4፥24 አምላክ መንፈስ ነው። Πνεῦμα ὁ Θεός,
ኢዮኤል 2፥28 መንፈሴን በሥጋ ሁሉ ላይ አፈስሳለሁ። אֶשְׁפּ֤וֹךְ אֶת־ רוּחִי֙ עַל־ כָּל־ בָּשָׂ֔ר
በተመሳሳይ ፍቅር ከአምላክ ነው፥ አምላክ ፍቅር ነው። የአምላክ ፍቅር ልክ እንደ መንፈሱ ይፈሳል፦
1ኛ ዮሐንስ 4፥7 ፍቅር ከአምላክ ነው። ἡ ἀγάπη ἐκ τοῦ Θεοῦ ἐστιν,
1ኛ ዮሐንስ 4፥8 አምላክ ፍቅር ነው። ὁ Θεὸς ἀγάπη ἐστίν.
ሮሜ 5፥5 በተሰጠንም በመንፈስ ቅዱስ "የአምላክ ፍቅር በልባችን ስለ ፈሰሰ" ተስፋ አያሳፍርም። ἡ δὲ ἐλπὶς οὐ καταισχύνει, ὅτι ἡ ἀγάπη τοῦ Θεοῦ ἐκκέχυται ἐν ταῖς καρδίαις ἡμῶν διὰ Πνεύματος Ἁγίου τοῦ δοθέντος ἡμῖν.
"የአምላክ ፍቅር በልባችን ስለ ፈሰሰ" የሚለው ይሰመርበት! ከአምላክ የሆነው ፍቅር ከአምላክ የሚፈስ ከሆነ እራሱን የቻለ ማንነት ነውን? ከአምላክ የሚፈሰው ፍቅር ይታገሣል፣ ቸርነትን ያደርጋል፣ ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ ዓመፃ ደስ አይለውም፣ ሁሉን ይታገሣል፣ ሁሉን ያምናል፣ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፣ በሁሉ ይጸናል፦
1ኛ ቆሮንቶስ 13፥4-7 ፍቅር ይታገሣል፣ ቸርነትን ያደርጋል፣ ፍቅር አይቀናም፣ ፍቅር አይመካም፣ አይታበይም፣ የማይገባውን አያደርግም፣ የራሱንም አይፈልግም፣ አይበሳጭም፣ በደልን አይቆጥርም፣ ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ ዓመፃ ደስ አይለውም፣ ሁሉን ይታገሣል፣ ሁሉን ያምናል፣ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፣ በሁሉ ይጸናል።
እና ፍቅር እራሱን የቻለ አራተኛ አካል ነውን? "የራሱን አይፈልግም" ሲል "ራሱ" የሚለው ድርብ ተውላጠ ስም እራሱን የቻለ አካል መሆኑን ያስረዳልን? የሥላሴ አማንያን"Trinitarian" ሆይ! የረሳችሁትን አራተኛ አካል ላስታውሳችሁ ብዬ ነው። አምላካችን አሏህ ውስብስብ ከሆነው ከሥላሴ ትምህርት ያውጣችሁ! እኛንም በተውሒድ ትምህርት ያጽናን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 16 856 |
| 12 | እንኳን አደረሳችሁ!
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
59፥7 መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት፡፡ ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ። አሏህንም ፍሩ፡፡ አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና وَمَآ ءَاتَىٰكُمُ ٱلرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَىٰكُمْ عَنْهُ فَٱنتَهُوا۟ ۚ وَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ ۖ إِنَّ ٱللَّهَ شَدِيدُ ٱلْعِقَابِ ፡፡
“ዒድ” عِيد የሚለው ቃል “ዓደ” عَادَ ማለትም “ተመላለሰ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “ምልሰት” ማለት ነው፥ ይህ “መደሰቻ” ወይም “በዓል” በየዓመቱ ስለሚመላለስ ይህንን ስያሜ አግኝቷል። ነቢያችን”ﷺ” የነገሩን ዓመታዊ በዓል ሁለት ብቻና ብቻ ናቸው፥ እነርሱም፦ ዒዱል ፊጥር እና ዒዱል አድሓ ናቸው። ከታች ያለውን ደሊል ተመልከት፦
ሡነን አቢ ዳዉድ መጽሐፍ 2, ሐዲስ 745
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 121
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 91
ማንኛውም መመሪያ ቁርአን እና የነቢያችን”ﷺ” ሐዲስ ላይ ይገኛል። አላህም፦ “መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት! ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ” ብሎናል፦
59፥7 *መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት፡፡ ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ*፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና وَمَآ ءَاتَىٰكُمُ ٱلرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَىٰكُمْ عَنْهُ فَٱنتَهُوا۟ ۚ وَٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ ۖ إِنَّ ٱللَّهَ شَدِيدُ ٱلْعِقَابِ ፡፡
ኢማም ቡኻርይ : መጽሐፍ 53, ሐዲስ 7
ዓኢሻህ”ረ.ዐ.” እንደተረከችው የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ *"“ማንኛውም ሰው ከትእዛዛችን ያልሆነ አንድ ነገር ቢፈጥር ተቀባይነት የለውም"*። عَنْ عَائِشَةَ ـ رضى الله عنها ـ قَالَتْ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم “ مَنْ أَحْدَثَ فِي أَمْرِنَا هَذَا مَا لَيْسَ فِيهِ فَهُوَ رَدٌّ ”.
በፀሐይ አቆጣጠር መስከረም እንዲሁ በጨረቃ አቆጣጠር ሙሐረም አዲስ ዓመት እና የወር መጀመሪያ ነው፥ ነገር ግን እነዚህን ዘመን መለወጫ በዓል አርጎ በመያዝ "እንኳን አደረሳችሁ" መባባል ሸሪዓዊ መሠረት የሌለው፣ ቀደምት ሠለፎች ያላደረጉት እና ቢድዓህ ነው። የሚገርመው "ከዒዱል ፊጥር እና ከዒዱል አድሓ ውጪ በዓል የለም፥ እንኳን አደረሳችሁ አይባልም" ብለው መውሊድን የሚቃወሙ ጥቂት ሰዎች ሙሐረምን ጠብቀው "እንኳን አደረሳችሁ" ማለታቸው አልሸሹም ዞር አሉ ነው። ሊወገዙስ አይገባምን? በኢሥላም አሕካም በአምስት ዋና ዋና ክፍል ሲከፈሉ፥ ከአምስቱ አንዱ "ሐላል" ነው። "ሐላል" حَلاَل ማለት "የተፈቀደ" ማለት ነው፦
16፥116 *"በአላህም ላይ ውሸትን ልትቀጣጥፉ ምላሶቻችሁ በሚመጥኑት ውሸት «ይህ የተፈቀደ ነው፥ ይህም እርም ነው» አትበሉ"*፡፡ وَلَا تَقُولُوا لِمَا تَصِفُ أَلْسِنَتُكُمُ الْكَذِبَ هَـٰذَا حَلَالٌ وَهَـٰذَا حَرَامٌ لِّتَفْتَرُوا عَلَى اللَّهِ الْكَذِبَ
እዚህ አንቀጽ ላይ “የተፈቀደ” ለሚለው የገባው ቃል “ሐላል” حَلاَل መሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። ቅሉ እና ጥቅሉ ግን ከዚያ በተቃራኒ ሸሪዓህ በመቃረን ከሃይማኖት አላህ በእርሱ ያልፈቀደውን ለእነርሱ የደነገጉ በአሏህ ላይ አሻርከዋል፦
42፥21 *"ከሃይማኖት አላህ በእርሱ ያልፈቀደውን ለእነርሱ “የደነገጉ” ተጋሪዎች ለእነርሱ አሏቸውን?"* أَمْ لَهُمْ شُرَكَاءُ شَرَعُوا لَهُم مِّنَ الدِّينِ مَا لَمْ يَأْذَن بِهِ اللَّهُ
እዚህ አንቀጽ ላይ “የደነገጉ” ለሚለው የገባው ቃል “ሸረዑ” شَرَعُوا ሲሆን መለኮታዊ ያልሆነ ከዝንባሌአቸው ሸሪዓህ መደንገጋቸው የሚያሳይ ቃል ነው። “ሸሪክ” شَرِيك ማለት “ተጋሪ” ማለት ነው፥ የሸሪክ ብዙ ቁጥር ደግሞ “ሹረካእ” شُرَكَاء ሲሆን “ተጋሪዎች” ማለት ነው፥ አሏህ በእርሱ ያልፈቀደውን ነገር ሐላል ማድረግ ለእነርሱ የደነገጉ በአላህ ሐቅ ላይ ተጋሪዎች አሏቸው። እነዚህ የአሏህን ሐቅ የሚጋሩ ሰዎች እራሳቸው ተሕሊል እና ተሕሪም በማድረጋቸው ጣዖታት ናቸው፦
4፥60 ወደ እነዚያ እነርሱ በአንተ ላይ በተወረደው እና ከአንተ በፊትም በተወረደው አምነናል ወደሚሉት አላየህምን? “በእርሱ እንዲክዱ በእርግጥ የታዘዙ ሲኾኑ ወደ ጣዖት መፋረድን ይፈልጋሉ”፡፡ أَلَمْ تَرَ إِلَى الَّذِينَ يَزْعُمُونَ أَنَّهُمْ آمَنُوا بِمَا أُنزِلَ إِلَيْكَ وَمَا أُنزِلَ مِن قَبْلِكَ يُرِيدُونَ أَن يَتَحَاكَمُوا إِلَى الطَّاغُوتِ وَقَدْ أُمِرُوا أَن يَكْفُرُوا بِهِ
አንድ ሰው አሏህ ካወረደው ውጪ፦ "ይህ ነገር ሐራም ነው፥ ይህ ነገር ሐላል ነው" ካለ እርሱ ጣዖት ነው። “ጧጉት” طَّٰغُوت የሚለው ቃል “ጦጋ” طَغَىٰ ማለትም “ወሰን አለፈ” ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “በአላህ ሐቅ ላይ ወሰን ማለፍ” ማለት ነው። አምላካችን አሏህ ሸሪዓችን፦ "ሐላል ያለውን ሐላል፥ ሐራም ያለውን ሐራም" የምንለን ያድርገን! ዝንባሌአችንን ከመከተል ይጠብቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 20 593 |
| 13 | https://t.me/Wahidcom/4197 | 17 303 |
| 14 | “ደጃል” دَّجَّال የሚለው ቃል “ደጀለ” دَجَلَ ማለትም “አጭበረበረ” ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን “አጭበርባሪ” ወይም “ሐሳዌ” ማለት ነው፥ ቀደምት ሠለፎች ይህንን አሰር ለእኛ አስተላልፈውልናል። "አሰር" أَثَر የሚለው ቃል "አሰረ" أَثَرَ ከሚል ሥርወ ቃል የመጣ ሲሆን "ትውፊት" "ቅብብሎሽ" "ቅሪት" ማለት ነው፥ "ሠለፍ" سَلَف የሚለው ቃል "ሠለፈ" سَلَفَ ማለትም "ቀደመ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ቀደምት" ማለት ነው፦
9፥100 ከስደተኞቹ እና ከረዳቶቹም ሲኾኑ "የመጀመሪያዎቹ ቀዳሚዎች" እነዚያም በበጎ ሥራ የተከተሏቸው አሏህ ከእነርሱ ወዷል እነርሱም ወደዋል፡፡ በሥሮቻቸውም ወንዞች የሚፈሱባቸውን ገነቶች በውስጣቸው ዘለዓለም ነዋሪዎች ሲኾኑ ለእነርሱ አዘጋጅቶላቸዋል፡፡ ይህ ታላቅ ዕድል ነው፡፡ وَالسَّابِقُونَ الْأَوَّلُونَ مِنَ الْمُهَاجِرِينَ وَالْأَنصَارِ وَالَّذِينَ اتَّبَعُوهُم بِإِحْسَانٍ رَّضِيَ اللَّهُ عَنْهُمْ وَرَضُوا عَنْهُ وَأَعَدَّ لَهُمْ جَنَّاتٍ تَجْرِي تَحْتَهَا الْأَنْهَارُ خَالِدِينَ فِيهَا أَبَدًا ۚ ذَٰلِكَ الْفَوْزُ الْعَظِيمُ
"የመጀመሪያዎቹ ቀዳሚዎች" የሚለው ኃይለ ቃል ይሰመርበት! እነዚህም "ሰሓቢይ" صَحَابِيّ ሲባሉ የነቢያችን”ﷺ” ውድ “ባልደረባ”companion” ናቸው፥ "የተከተሏቸው" የተባሉት ሁለተኛው ትውልድ "ታቢዒይ" تَابِعِيّ እና ሦስተኛው ትውልድ "ታቢዑ አት-ታቢዒን" تَابِع التَابِعِين ናቸው። እነዚህ ሦስት ትውልድ ሠለፍዩን ናቸው፦
ኢማም ቡኻርይ መጽሐፍ 83, ሐዲስ 72
ዒምራን ኢብኑ ሑሰይን እንደተረከው፦ “ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ ከእናንተ ምርጡ የእኔ ትውልድ ነው፥ ቀጥሎ ያሉት እነርሱን የሚከተሉት ነው፥ ለጥቆ ያሉት የሚከተሉትን የሚከተሉ ናቸው”*። قَالَ سَمِعْتُ عِمْرَانَ بْنَ حُصَيْنٍ، يُحَدِّثُ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ خَيْرُكُمْ قَرْنِي، ثُمَّ الَّذِينَ يَلُونَهُمْ، ثُمَّ الَّذِينَ يَلُونَهُم
ዐሊሞች ከተወዳጁ ነቢያችንን"ﷺ" ሐዲስ እና ከሠለፎችን አሰር በደሊል ሲያንቆራጥጡት ረሻድ ኸሊፋህ፦ "የሙሐመድ"ﷺ" ሐዲስ ሆነ የሠለፎችን አሰር የሚባለውን ነገር አልቀበልም፥ ቁርኣን በቁርኣን ብቻ ይፈሠራል" ብሎ አረፈው። የእርሱ ፈለግ የሚከተሉ ዛሬ ላይ በመላው ዓለም ሲኖሩ አሥራ አራት ትውልድ በቅብብሎሽ የመጣውን የቁርኣን አረዳድ ሙሉ ለሙሉ አይቀበሉም።
ቁርኣኒይ የሚባሉት ሙናፊቁን "ቁርኣን በቁርኣን እንጂ አይብራራም፥ ቁርኣንን የሚያብራራ መጽሐፍ ሆነ ሰው የለም" ብለው የተወዳጁ ነቢያችንን"ﷺ" ንግግር ሆነ የሠለፎችን አረዳድ አይቀበሉም፥ የሚያጅበው ግን እራሳቸው በራሳቸው መንገድ ቁርኣን ፈሣሪዎች እና የተፍሢር መጽሐፍ ማዘጋጀታቸው ነው። ይህ አባባላቸው የሰፈር ጉልቤዎች ትዝ አሉኝ፥ የሰፈር ጉልቤዎች "እቃውን ማንም ማውረድ አይችልም" ይለሉና እራሳቸው በወሰኑት ሒሣብ ያወርዳሉ። በተመሳሳይ ቁርኣኒይ የሚባሉት ሙፍሠዲን "ቁርኣን የተብራራ ነው፥ ማንም ማብራራት አይገባውም" ይሉክና እራሳቸው አብራሪ ሆነው ታገኛቸዋለህ።
ቁርኣኒያዎች አቋማቸው "ተውራት ለሙሣ አልተወረደም፥ ለማን እንደወረደ ቁርኣን አይገልጽም። እስራኤል ያዕቆብ አይደለም፥ ያዕቆብ ማን እንደሆነ ቁርኣን አይገልጽም" ይላሉ፥ ከዚያ የሐዲስ እና የሠለፎችን ተፍሢር ስታስቀምጥ አይቀበሉም። እነዚህ ሰዎች በመላው ዓለም ላይ ኢኽቲላጥን አስፋፊዎች ናቸው፥ "ኢኽቲላጥ" اِخْتِلَاط ማለት "መደባለቅ" ማለት ሲሆን ወንድ እና ሴትን በትምህርት፣ በጉባኤ፣ በአምልኮ ቦታ ደባልቀው የሚያስተምሩ እና ትውልድን የሚያበላሹ ናችው።
ይህ ፈሣድ አገራችን ላይ እንደ ሰደድ እሳት በድብቅ እየተስፋፋ የነበረ ሲሆን አሁን ላይ ግን ጭንብሉን ገልጦ በግልጽ በማኅበራዊ መገናኛ ብዙኃን እየተስፋፋ ይገኛል፥ ይህንን ጉዳይ ስናስጠነቅቅ ትውልዱን በፈሣድ እንዳይበከል እና የእሳት እራት እንዳይሆን እንጂ የሰዎችን ግላዊ ስብዕና ለመንካት በፍጹም እና በጭራሽ አይደለም። አውቀው ይሁን ሳያውቁ የቁርኣንያን እሳቤ የሚያራምዱትን አምላካችን አሏህ ሂዳያውን ይወፍቃቸው! እኛንም ከቁርኣኒያህ ፈሣድ እና ኒፋቅ ይጠብቀን! አሚን።
✍ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 19 387 |
| 15 | ቁርኣኒያህ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
33፥40 ሙሐመድ ከወንዶቻችሁ የአንድንም ሰው አባት አይደለም፥ ነገር ግን የአሏህ መልእክተኛ እና "የነቢያት መደምደሚያ" ነው። مَا كَانَ مُحَمَّدٌ أَبَا أَحَدٍ مِنْ رِجَالِكُمْ وَلَٰكِنْ رَسُولَ اللَّهِ وَخَاتَمَ النَّبِيِّينَ
"ቁርኣኒያህ" قُرْآنِيَّة ማለት "ቁርኣን ብቻ" የሚል እና የተወዳጁ ነቢያችንን"ﷺ" ሐዲስ ሆነ የሠለፎችን አሰር የማይቀበል እሳቤ ሲሆን ይህንን እሳቤ የሚያራምዱ ሰዎች "ቁርኣኒይ" قُرْآنِيّ ይባላሉ፥ ቁርኣኒያን የጀመረው እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር ከ 1933 ድኅረ ልደት እስከ 1990 ድኅረ ልደት ይኖር የነበረው ግብፃዊ እና አሜሪካዊ ረሻድ ኸሊፋህ ነው። ረሻድ ኸሊፋህ፦ "እኔ የአሏህ መልእክተኛ ነኝ" ብሎ ሲያውጅ በወቅቱ የነበሩት ዐሊሞችን የአሏህን ንግግር ጠቀሱበት፦
33፥40 ሙሐመድ ከወንዶቻችሁ የአንድንም ሰው አባት አይደለም፥ ነገር ግን የአሏህ መልእክተኛ እና "የነቢያት መደምደሚያ" ነው። አሏህም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው። مَا كَانَ مُحَمَّدٌ أَبَا أَحَدٍ مِنْ رِجَالِكُمْ وَلَٰكِنْ رَسُولَ اللَّهِ وَخَاتَمَ النَّبِيِّينَ وَكَانَ اللَّهُ بِكُلِّ شَيْءٍ عَلِيمًا
እርሱም፦ "የነቢያት መደምደሚያ" እንጂ "የመልእክተኞች መደምደሚያ" አይልም" በማለት እርሱ ነቢይ እንዳልሆነ እና መልእክተኛ እንደሆነ ተናገረ፥ ዐሊሞችንም፦ "መልእክተኛ እራሱ ነቢይ ሳይሆን መልእክተኛ መሆን አይችልም" ሲሉት "መስፈርቱን አልቀበልም" አለ። ይህንን የተረዱት ዐሊሞችን የተወዳጁ ነቢያችንን"ﷺ" ሐዲስ ጠቀሱለት፦
ጃምዒ አት-ቲርሚዚይ መጽሐፍ 8, ሐዲስ 2272
አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ ”በእርግጥም መልእክተኛነት እና ነቢይነት ተዘግቷል። ከእኔ በኃላ መልእክተኛም ነቢይም የለም"። حَدَّثَنَا أَنَسُ بْنُ مَالِكٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم ” إِنَّ الرِّسَالَةَ وَالنُّبُوَّةَ قَدِ انْقَطَعَتْ فَلاَ رَسُولَ بَعْدِي وَلاَ نَبِيَّ
ነቢያችን"ﷺ" በሡናህ መልእክተኛ እና ነቢይ እንደማይመጣ እንቅጩን ፍርጥ አርገው እንዲህ ነግረውናል፥ ነገር ግን የመጨረሻይቱ ሰዓት አትቆምም ሠላሳ የሚቃረቡ ደጃሎች ቀጣፊዎች ተነስተውስ፦ “እኔ የአሏህ መልእክተኛ ነኝ” ብለው ቢናገሩ ቢሆን እንጂ፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 54, ሐዲስ 108
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው ነብዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ “የመጨረሻይቱ ሰዓት አትቆምም ሠላሳ የሚቃረቡ ደጃሎች ቀጣፊዎች ተነስተውስ፦ “እኔ የአሏህ መልእክተኛ ነኝ” ብለው ቢናገሩ ቢሆን እንጂ”። عَنْ أَبِي، هُرَيْرَةَ عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ ” لاَ تَقُومُ السَّاعَةُ حَتَّى يُبْعَثَ دَجَّالُونَ كَذَّابُونَ قَرِيبٌ مِنْ ثَلاَثِينَ كُلُّهُمْ يَزْعُمُ أَنَّهُ رَسُولُ اللَّهِ | 15 812 |
| 16 | Matn yo'q... | 13 889 |
| 17 | Matn yo'q... | 13 505 |
| 18 | Ovozli xabar | 16 945 |
| 19 | ካቶሊክ፣ የምሥራቅ ኦርቶዶክስ፣ የጽብሓውያን ኦርቶዶክስ እና ጥቂት የፕሮቴስታንት ጎጥ እና አንጃ ይህንን ጥቅስ ተንተርሰው "ዝርግ ሳሕን ጠረጴዛ አለን" ቢሉም ዝርግ ሳሕን ጠረጴዛውን "ታቦት ነው" አይሉም፥ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ውጪ ያሉት ባለ ጠረጴዛ አብያተ ክርስቲያናት ባለ ሳጥኑ ታቦት "በአዲስ ኪዳን ቀርቷል" የሚል አቋም አላቸው። ከዚያ ይልቅ ዝርግ ሳሕን ጠረጴዛውን "መሠዊያ" ይሉታል፦
ዕብራውያን 13፥10 መሠዊያ አለን፥ ከእርሱም ሊበሉ ድንኳኒቱን የሚያገለግሉ መብት የላቸውም።
እዚህ አንቀጽ ላይ "መሠዊያ" እያለ ያለው ሙሴ እያየ ሢሠራ የነበረው ሰማያዊ መሠዊያ ነው፥ በሰማይ ካለው መሠዊያ ከሱራፌልም አንዱ በእጁ በጕጠት የወሰደው ፍም ነበረ፦
ኢሳይያስ 6፥6 ከሱራፌልም አንዱ እየበረረ ወደ እኔ መጣ፥ በእጁም ከመሠዊያው በጕጠት የወሰደው ፍም ነበረ።
"ፍሙ" "ጉጠቱ" "መሠዊያው" ቁሳዊ እንዳልሆነ እሙን እና ቅቡል ነው፥ ሰማይ ላይ መሠዊያ እንዳለ ብዙ ጥቅስ አለ፦ ራእይ 9፥13 ራእይ 6፥9 ራእይ 14፥18 ተመልከት! ድንኳኒቱን የሚያገለግሉ የብሉይ ኪዳን ሌዋውያን ከሰማያዊ መሠዊያ ሊበሉ መብት የላቸውም፦
ራእይ 19፥9 ወደ በጉ ሰርግ እራት የተጠሩ ብፁዓን ናቸው።
ራእይ 3፥20 ከእርሱም ጋር እራት እበላለሁ እርሱም ከእኔ ጋር ይበላል።
"መሠዊያ" መሥዋዕት ማቅረቢያ ከሆነ የምስጋና መሥዋዕት በክርስቶስ ለእግዚአብሔር አብ እንደሚቀርብ የሚናገረው ጥቅስ ተንተርሰው "መሠዊያ" እራሱ ክርስቶስ ነው" የሚሉ እንደ "Clarke's Commentary" ያሉ አብራሪዎች አሉ፦
ቆላስይስ 3፥17 እግዚአብሔር አብን በእርሱ(በክርስቶስ) እያመሰገናችሁ፥ በቃል ቢሆን ወይም በሥራ የምታደርጉትን ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ስም አድርጉት።
ዕብራውያን 13፥15 እንግዲህ ዘወትር ለእግዚአብሔር የምስጋናን መሥዋዕት፥ ማለት ለስሙ የሚመሰክሩ የከንፈሮችን ፍሬ፥ በእርሱ(በክርስቶስ) እናቅርብለት።
"ከእርሱም ሊበሉ" ሲል "ከክርስቶስም ሊበሉ" ማለት ነውና ከእርሱ እራት ሊበሉ ድንኳኒቱን የሚያገለግሉ የብሉይ ኪዳን ሌዋውያን መብት የላቸውም በሚል ይረዱታል። ሆነም ቀረ ሰርግ፣ እራት፣ ምግብ፣ መሠዊያ ፍካሬአዊ እንጂ እማሬአዊ ትርጉም ከሌለው "መሠዊያ አለን" ያለውም ዝርግ ሳሕን ጠረጴዛውን በጭራሽ አይደለም፥ "መሠዊያ አለን" ያለውም "ዝርግ ሳሕን ጠረጴዛውን ነው" ቢባል እንኳን "መሠዊያው ታቦት ነው" የሚል አሳብ በአዲስ ኪዳን ላይ አናገኝም።
ዋና መነሻችን "አክሱም ውስጥ የብሉይ ኪዳን ታቦት የለም" "በአዲስ ኪዳንም ታቦት የሰው አካል እንጂ ዝርግ ሳሕን ጠረጴዛ ወይም መሠዊያ ታቦት ነው" የሚል የለም" የሚል ነው። ሕዝቡን አትዋሹት! አታጭበርብሩት! ሰው የማያነብ ይመስላችኃል? ቅጥፈታችሁ ሰው እያወቀ ሲመጣ ጥሏችሁ ወደ ዲኑል ኢሥላም ይመጣል። አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይወፍቃችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይወፍቀን! አሚን።
✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ
https://t.me/Wahidcom
ወሠላሙ ዐለይኩም | 17 082 |
| 20 | የአዲስ ኪዳን ታቦት
ክፍል ሁለት
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
5፥115 አሏህ፡- «እኔ ማዕድዋን በእናንተ ላይ አውራጅዋ ነኝ፡፡ በኋላም ከእናንተ የሚክድ ሰው እኔ ከዓለማት አንድንም የማልቀጣውን ቅጣት እቀጣዋለሁ» አለ፡፡ قَالَ اللَّهُ إِنِّي مُنَزِّلُهَا عَلَيْكُمْ ۖ فَمَن يَكْفُرْ بَعْدُ مِنكُمْ فَإِنِّي أُعَذِّبُهُ عَذَابًا لَّا أُعَذِّبُهُ أَحَدًا مِّنَ الْعَالَمِينَ
"ማኢዳህ" مَائِدَة ማለት "ማዕድ" ማለት ሲሆን ኢየሱስ ወደ አሏህ «ጌታችን አሏህ ሆይ! ለእኛ ለመጀመሪያዎቻችንና ለመጨረሻዎቻችን በዓል የምትኾንን ከአንተም ተአምር የኾነችን ማዕድ ከሰማይ በእኛ ላይ አውርድ፡፡ ስጠንም፡፡ አንተ ከሰጪዎች ሁሉ በላጭ ነህና» አለ፦
5፥114 የመርየም ልጅ ዒሣ አለ፡- «ጌታችን አሏህ ሆይ! ለእኛ ለመጀመሪያዎቻችንና ለመጨረሻዎቻችን በዓል የምትኾንን ከአንተም ተአምር የኾነችን ማዕድ ከሰማይ በእኛ ላይ አውርድ፡፡ ስጠንም፡፡ አንተ ከሰጪዎች ሁሉ በላጭ ነህና» አለ። قَالَ عِيسَى ابْنُ مَرْيَمَ اللَّهُمَّ رَبَّنَا أَنزِلْ عَلَيْنَا مَائِدَةً مِّنَ السَّمَاءِ تَكُونُ لَنَا عِيدًا لِّأَوَّلِنَا وَآخِرِنَا وَآيَةً مِّنكَ ۖ وَارْزُقْنَا وَأَنتَ خَيْرُ الرَّازِقِينَ
"ዒድ" عِيد ማለት "በዓል" ማለት ሲሆን ይህም በዓል ፋሲካ ነው፥ በዚህ በዓል ከሰማይ የወረደው ማዕድ ኢየሱስ ሳይሆን በተአምር ከሰማይ የመጣ ማዕድ ነው፦
5፥115 አሏህ፡- «እኔ ማዕድዋን በእናንተ ላይ አውራጅዋ ነኝ፡፡ በኋላም ከእናንተ የሚክድ ሰው እኔ ከዓለማት አንድንም የማልቀጣውን ቅጣት እቀጣዋለሁ» አለ፡፡ قَالَ اللَّهُ إِنِّي مُنَزِّلُهَا عَلَيْكُمْ ۖ فَمَن يَكْفُرْ بَعْدُ مِنكُمْ فَإِنِّي أُعَذِّبُهُ عَذَابًا لَّا أُعَذِّبُهُ أَحَدًا مِّنَ الْعَالَمِينَ
ስለዚህ ከሰማይ የወረደው ማዕድ ኢየሱስ ሳይሆን ለኢየሱስ እና ለሐዋርያት ለበዓሉ እንዲበሉት የተሰጠ ማዕድ ነው፥ ቁርኣን ባይብል ላይ የገባውን የተሳሳተ "የጌታ ማዕድ" በዚህ መልኩ አስተካክሎታል።
"ፋሲካ" በሚባል "በዓል" ላይ በመሸም ጊዜ ኢየሱስ ከአሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ ጋር በማዕድ እንደተቀመጠ ይናገራል፦
ማቴዎስ 26፥20 በመሸም ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ደቀ መዛሙርቱ ጋር በማዕድ ተቀመጠ። Ὀψίας δὲ γενομένης ἀνέκειτο μετὰ τῶν δώδεκα μαθητῶν
"ጠረጴዛ" የሚለው የግዕዙ ቃል እራሱ "ማዕድ" ወይም "ገበታ" ማለት እንጂ ባለ አራት እግር ያለው "ጻሕል(ሳሕን) ወይም "ወጭት" ማለት አይደለም፥ "ጠረጴዛ" የሚለው የግዕዙ ቃል እራሱ "ትራፔዛ" τράπεζα ከሚል ግሪክ ኮይኔ የመጣ ሲሆን "ማዕድ" ማለት ነው። ለምሳሌ፦
የሐዋርያት ሥራ 16፥34 ወደ ቤቱም አውጥቶ ማዕድ አቀረበላቸው። ἀναγαγών τε αὐτοὺς εἰς τὸν οἶκον παρέθηκεν τράπεζαν,
እዚህ አንቀጽ ላይ "ማዕድ" ለሚለው የገባው ቃል "ትራፔዛን" τράπεζα እንደሆነ ልብ አድርግ! "ትራፔዛን" τράπεζα የተባለው ምግቡ እንጂ ምግቡ የሚቀመጥበት ወጭት አይደለም፦
መዝሙር 77(78)፥19 አምላክን እንዲህ ብለው አሙት፦ "አምላክ በምድረ በዳ ማዕድን ያሰናዳ ዘንድ ይችላልን? καὶ κατελάλησαν τοῦ Θεοῦ καὶ εἶπαν· μὴ δυνήσεται ὁ Θεὸς ἑτοιμάσαι τράπεζαν ἐν ἐρήμῳ;
እዚህ አንቀጽ ላይ "ማዕድ" ለሚለው የገባው ቃል "ትራፔዛ" τράπεζα ሲሆን በዐረቢኛ ባይብል ላይ "ማኢዳህ" مَائِدَة ነው፥ "ማዕድ" የተባለው የተሰናዳው ምግብ እንጂ ከእንጨት ወይም ከድንጋይ የተዘጋጀ ዝርግ ነገር በፍጹም አይደለም። ይህንን ከተረዳን ዘንዳ ይህንን ጥቅስ እንመልከት፦
1ኛ ቆሮንቶስ 10፥20 ነገር ግን አሕዛብ የሚሠዉት ለአማልክት እንዲሆን እንጂ ለአምላክ እንዳይሠዉ እላለሁ፤ ከአማልክትም ጋር ማኅበረተኞች እንድትሆኑ አልወድም። ἀλλ’ ὅτι ἃ θύουσιν, δαιμονίοις καὶ οὐ Θεῷ θύουσιν· οὐ θέλω δὲ ὑμᾶς κοινωνοὺς τῶν δαιμονίων γίνεσθαι.
"ዳይሞን" δαίμων ማለት በግሪክ ኮይኔ "አምላክ" ማለት ነው፥ የዳይሞን ብዙ ቁጥር ደግሞ "ዳይሞንዮን" δαιμονίων ሲሆን "አማልክት" ማለት ነው፦
የሐዋርያት ሥራ 17፥18 "አዲሶችን አማልክት የሚያወራ ይመስላል" Ξένων δαιμονίων δοκεῖ καταγγελεὺς εἶναι·
ኢስጦኢኮች ከተባሉት ፈላስፎች "አማልክት" ለሚለው የተጠቀሙበት ቃል "ዳይሞንዮን" δαιμονίων እንደሆነ ልብ አድርግ! "አሕዛብ" የተባሉት ግሪካውያን እና ሮማውያን የሚሠዉት ለአማልክቶቻቸው ነው፥ አሕዛብ የሚያቀርቡት ምግብ "ማዕድ" ተብሎአል፦
1ኛ ቆሮንቶስ 10፥21 የጌታን ጽዋ እና የአማልክትን ጽዋ ልትጠጡ አትችሉም፥ ከጌታ ማዕድ እና ከአማልክት ማዕድ ልትካፈሉ አትችሉም። οὐ δύνασθε ποτήριον Κυρίου πίνειν καὶ ποτήριον δαιμονίων· οὐ δύνασθε τραπέζης Κυρίου μετέχειν καὶ τραπέζης δαιμονίων.
"የጌታ ማዕድ" የተባለው በባዶ ጥቅስ "ታቦት" ካላችሁት አሕዛብ ለአማልክት የሚያቀርቡት የአማልክትን ማዕድ "ትራፔዛ" τράπεζα ተብሎአልና ለምን "ታቦት" አትሉትም? "የጌታ ማዕድ" ሆነ "የአማልክት ማዕድ" የተባሉት የሚበሉ ምግብ እንጂ የሚቀርብበት እና የሚሰናዳበት ዝርግ ሳሕን በፍጹም አይደለም። "የጌታን ጽዋ" እና "የአማልክትን ጽዋ" የሚጠጡ እንጂ የሚጠጣበት ዕቃ እንዳልሆነ ሁሉ "የጌታ ማዕድ" ሆነ "የአማልክት ማዕድ" የሚካፈሉት ምግብ እንጂ ጣውላ ሳሕን አይደለም። የጥቅሱ ዐውድ "ማዕድ" የሚለው "ጣውላ ነው" ብልን እንኳን ጣውላውን "ታቦት ነው" የሚል ንግግር ዐውዱ ላይ የት አለ? "የጌታን ታቦት" እና "የአማልክትን ታቦት" ወደሚል ውስብስ እረመጥ ውስጥ ያስገባችኃል። | 12 023 |
