ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡
Больше📈 Аналитический обзор Telegram-канала ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
Канал ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (@beteafework) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 54 178 подписчиков, занимая 991 место в категории Религия и духовность и 584 место в регионе Эфиопия.
📊 Показатели аудитории и динамика
С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 54 178 подписчиков.
Согласно последним данным от 03 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 724, а за последние 24 часа — 27, при этом общий охват остаётся высоким.
- Статус верификации: Не верифицирован
- Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 21.23%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 8.68% реакций от общего числа подписчиков.
- Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 11 503 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 4 703 просмотров.
- Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 189.
📝 Описание и контентная политика
Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
“በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡”
Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 04 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.
Загрузка данных...
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 04 июля | +13 | |||
| 03 июля | +31 | |||
| 02 июля | +18 | |||
| 01 июля | +31 |
| 2 | ተግሣፅ ዘቅዱስ ኤፍሬም
ሕይወትህን በአግባቡ መምራት ትፈልጋለህን? እንግዲያውስ ትሕትናን ተለማመድ፤ ያለ ትሕትና ተገቢውን ሕይወት መምራት አይቻልም፡፡ ሥራህን ሁሉ በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ጀምር፡፡ ያን ጊዜ ፍሬዎችህ ወደ መንግሥተ ሰማያት ይደርሳሉ።
ሰው ከትሕትና ከራቀ ከትክክለኛው መንገድ ርቋል ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔርን የተወ ሰውን ርኵስ መንፈስ እንደ ሳውል ያስጨንቀዋል። የጠላት ወጥመድ በማር የተቀባ ነው፡፡ በማር ጣዕም የሚማረክ ሰው ሐዘንን ሁሉ በያዘ ወጥመድ ይያዛል። ትሕትናን ውደዱ፤ ያን ጊዜ ከሰይጣን ወጥመድ ውስጥ አትወድቁም፡፡ በትሕትና ክንፍ በበረራችሁ ቁጥር ሁል ጊዜ ከጠላት ወጥመድ በላይ ትሆናላችሁ።
ግልፍተኝነት እንደ በሰበሰ ረጅም ዛፍ ነው፤ ቅርጫፎቹ ሁሉ በቀላሉ የሚሰበሩ ናቸው᎓᎓ አንድ ሰው በወጣባቸው ጊዜ ከወጣበት ከፍታ ወዲያውኑ ይወድቃል፡፡ በመልካም ሐሳብ ልቡናው የበራ ሰው ግን ምስጉን ነው፤ ክብሩም ታላቅና ዘላለማዊ ነው።
እንግዲህ ራሳችንን ለመቆጣጠር እንጣር ያን ጊዜ ኃጢአታችንን እንረዳለን፡፡ ያን ጊዜም ሁል ጊዜ ራሳችንን ዝቅ እናደርጋለን፤ እንደ እባብ በእብሪት መወጠርን እና ራሳችንን ከፍ ከፍ ከማድረግ እንቆጠባለን፡፡ እንግዲህ ራሳችንን ዝቅ ዝቅ ማድረግን እንውደድ፤ በንጹሕ ልቡና ሆነን ምናልባት የተሰጠንን የእግዚአብሔርን ቤተ መቅደስ በኃጢአት ከማቆሸሽ እንታደግ ይሆናል።
መልካም ጸሎት በሳግ እና በዕንባ የታጀበ ነው፤ በተለይ ደግሞ በምሥጢር የሚፈስ ዕንባ፣ በልቡናው ከፍታ ሆኖ የሚጸልይ ጌታውን በፊቱ ያያል። እኛ የምንኖረውና የምንሔደው በእርሱ ፈቃድ ነውና። ልቡናችሁ ከጠነከረ በጌታችን ፊት አልቅሱ እርሱ የዕውቀትን ብርሃን ይገልጥላችኋል፤ ወደ እርሱ የሚወስዳችሁ አዲስ ልብንም ይሰጣችኋል።
ንስሓ የገቡና ምሕረት የለመኑ ሰዎች ዕዳቸው ተሰረዘላቸው፤ ነገር ግን ለሠራኸው በደል ምሕረት ስትለምን ወንጀልን እና በደልን፤ በወንድምህም ላይ ቂም መያዝን መተው ይገባሃል። ፍቅር ሳይኖርህ ወደ እግዚአብሔር የምታደርገው ልመና ከተዘጋው በር ውጭ ይቀራል፡፡ የጸሎትን በር የሚከፍት ፍቅር ብቻ ነው፡፡
ወንድምህን ብታስቀይም እግዚአብሐርን ታሳዝናለህ፤ ካንተ ጋር ካለው ከወንድምህ ጋር ሰላምን ከፈጠርህ ግን በሰማይ ካለው ከእግዚአብሔር ጋር ትታረቃለህ፡፡ ወንድምህን በፍቅር ብትቀበለው፣ በደሉንም ይቅር ካልከው እግዚአብሔርን ተቀበልክ፡፡
ስለዚህ በተናደዱ ሰዎች በኩል ከእግዚአብሔር ጋር ታረቅ፤ እንግዲህ የተበሳጩትን በማስደሰት እግዚአብሔርን አስደስተው፣ በታሰሩት ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን ጎብኘው፣ በተራቡት ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን አብላው፤ በታረዙ ሰዎች በኩል እግዚአብሔርን አልብሰው፣ መንገደኛን በመቀበል እግዚአብሔርን በአልጋህ ላይ አስተኛው፤ እግሮቹንም እጠበው፣ በማዕድህም አስቀምጠው፣ እንጀራህንም ከእርሱ ጋር ተካፈል፤ ጽዋህንም ስጠው᎓᎓ እርሱ ታላቅ ፍቅሩን አሳይቶሃልና፤ እርሱ ስለ አንተ ብሎ ትበላው ዘንድ ሥጋውን ቆርሶልሃል፣ ትጠጣው ዘንድም ደሙን አፍስሷል።
(ድርሳነ ቅዱስ ኤፍሬም ገጽ 334 - 336 በዲ/ን መዝገቡ ከፍያለው የተተረጎመ) | 3 304 |
| 3 | ሰላም ቤተሰቦች
➛ 1 ተአምረ ማርያም ባለ 366ቱ ተአምር
➛ 1 ተአምረ ኢየሱስ እና
➛ 1 ስንክሳር የዓመቱ
➛ 1 ሃይማኖተ አበው
➛ አጣን
➛ ዘቢብ
➛ የሰም ጧፍ
ለእመቤታችን ቤተክርስቲያን ያስፈልጋል!
ፈቃደኛ የሆናችሁ በውስጥ መስመር @natansolo ኑ።
እስከ አሁን 8850 ብር ደርሶልናል። | 3 504 |
| 4 | ሰላም ቤተሰቦች
➛ 1 ተአምረ ማርያም ባለ 366ቱ ተአምር
➛ 1 ተአምረ ኢየሱስ እና
➛ 1 ስንክሳር የዓመቱ
➛ 1 ሃይማኖተ አበው
➛ አጣን
➛ ዘቢብ
➛ የሰም ጧፍ
ለእመቤታችን ቤተክርስቲያን ያስፈልጋል!
ፈቃደኛ የሆናችሁ በውስጥ መስመር @natansolo ኑ።
እስከ አሁን 8250 ብር ደርሶልናል። | 4 203 |
| 5 | አስቸኳይ የጥንቃቄ መልእክት!
Trust፣ Google TV እና Known የተባሉ ጉዳት አምጪ የአንድሮይድ መተግበሪያዎች በማስፈንጠሪያዎች (links) አማካይነት እንደ Google Chrome፣ Telegram እና WhatsApp ባሉ መድረኮች ላይ በስፋት እየተሰራጩ ነው። በስልክዎ ላይ ከተጫኑ፣ እርስዎ ሳያውቁ ገንዘብ ሊያዘዋውሩብዎ እና ሌሎች የግል መረጃዎ ላይ ሌላም ጉዳት ሊያደርሱብዎ ይችላሉ።
በመሆኑም፣ የተለያዩ መተግበሪያዎችን ወደ ስልክዎ ለማውረድ፣ እንደ Play Store ወይም App Store ያሉ የታመኑ ምንጮችን ይጠቀሙ። ነገር ግን፣ በGoogle Chrome፣ በTelegram ወይም በWhatsApp አማካይነት የሚላኩ መተግበሪያዎችን ወደ ስልክዎ አያውርዱ፤ በእነሱ በኩል የሚላኩ አጠራጣሪ ማስፈንጠሪያዎችንም ሳያረጋግጡ አይክፈቱ።
በተጨማሪም፣ልዩ ልዩ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያዎችን እንደ Play Store ወይም App Store ያሉ የታመኑ ምንጮችን ከማውረድዎ በተጨማሪ የባዮሜትሪክ (Biometrics) እና የፒን (PIN) የደኅንነት ማረጋገጫዎችን አጣምረው ይጠቀሙ። | 5 210 |
| 6 | ሰላም ቤተሰቦች
➛ 1 ተአምረ ማርያም ባለ 366ቱ ተአምር
➛ 1 ተአምረ ኢየሱስ እና
➛ 1 ስንክሳር የዓመቱ
➛ 1 ሃይማኖተ አበው
➛ አጣን
➛ ዘቢብ
➛ የሰም ጧፍ
ለእመቤታችን ቤተክርስቲያን ያስፈልጋል!
ፈቃደኛ የሆናችሁ በውስጥ መስመር @natansolo ኑ።
እስከ አሁን 8250 ብር ደርሶልናል። | 4 692 |
| 7 | "መጥፎ ቀን እና ጥሩ ቀን የሚባል ነገር የለም። ያለው ጸሎት አድርገህ የወጣህበት ቀን እና ጸሎት ሳታደርግ የወጣህበት ቀን ነው። ያልጸለይክባቸው ቀናት በክፉ ምኞትና የሥጋ ፍላጎት የተሞሉ ስለሆኑ ክፉ ቀናት ናቸው።"
ቅዱስ ቄርሎስ ሣድሳዊ | 4 688 |
| 8 | "ሥጋ በዝሙት እንደሚረክስ ኹሉ፥ ነፍስም በሰይጣናዊ አሳቦች፣ በእኩይ ሃይማኖትና በእኩይ ግብር ትረክሳለች፡፡ አንድ ሰው "በሥጋ ድንግል ነኝ" ቢል፥ ነገር ግን በወንድሙ የሚቀና ከኾነ እርሱ ድንግል አይደለም፡፡ ከቅናት ጋር ሩካቤ ስለ ፈጸመ ድንግልናውን አጥቷል፡፡ ውዳሴ ከንቱን የሚወድድም እርሱ ድንግል አይደለም፡፡ የቅናት ስሜት ክብረ ድንግልናውን አሳጥቶታል፡፡ ስሜት ወደ ውሳጤው ዘልቆ ገብቶ የነፍሱን ድንግልና አፍርሶበታልና። ወንድሙን የሚጠላም እርሱ ድንግል ከመኾን በላይ ነፍሰ ገዳይ ነው። በአጠቃላይ እያንዳንዱ ሰው በተገዛለት ክፉ ስሜት ድንግልናውን ያጣል። ስለዚሁ ምክንያትም ቅዱስ ጳውሎስ እነዚህን ኹሉ መቀላቀሎችን አራቀ የነፍሳችን ጸር የኾኑ ማናቸውንም አሳቦች ወደን ፈቅደን ባለመቀበል ደናግል እንድንኾን አዘዘን።
እንግዲህ እነዚህን ነገሮች በተመለከተ ልንናገረው የሚገባን ምንድን ነው? የእግዚአብሔርን ምሕረት ልንቀበል የምንችለው እንዴት ነው? ልንድን የምንችለውስ እንዴት ነው? ጸሎትንና የጸሎት ፍሬዎች የኾኑትን እነርሱም ትሕትናንና የውሃትን ዘወትር ለራሳችን እንያዝ ብዬ እነግራችኋለሁ። እርሱ “ከእኔ ተማሩ፤ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ" ብሎአልና (ማቴ.11፥29)። ክቡር ዳዊትም፦- “የተሰበረን መንፈስ ለእግዚአብሔር ሠዋ፤ የተሰበርውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም” ብሎአል (መዝ.50፥17)። እግዚአብሔር ከተሰበረ፣ ትሑት ከኾነና ከሚያመስግን ልብ በላይ አጥብቆ የሚወድደው የለምና።
ስለዚህ ወንድሜ! አንተም ያላሰብከውና የሚያናውጽ መከራ ቢገጥምህ መጠጊያ ይኾኑህ ዘንድ ሰዎችን እንዳትመለከት፤ ዘላቂና ቋሚ ያይደለ እርዳታን እንዳትፈልግ ተጠንቀቅ። ይልቅ ኹሉንም ናቃቸው፤ በአሳብህም መድኃኒተ ነፍሳት ወደ ኾነው ወደ እግዚአብሔር ተፋጠን። ልባችንን መጠገን (መፈወስ) የሚቻለው ልባችንን ብቻውን የሠራ (የፈጠረ) እና ግብራችንን ኹሉ የሚያውቅ እርሱ ብቻ ነውና (መዝ.32፥15)። ወደ ሕሊናችን ጓዳ መግባት፣ አሳባችንን መመርመር ልባችንንም ማጽናናት ሥልጣን (ኃይል) ያለው አርሱ ብቻ ነውና። እርሱ ልባችንን ካላጽናና ሰዎች ኹሉ የሚያደርጉልን ነገር ትርፍና ረብ የለሽ ነውና። እግዚአብሔር ሲያጽናናንና ሲያረጋጋን ግን እንደ ገና ሰዎች ቍጥር በሌለው መከራ ቢያውኩንም በፍጹም እኛን መጉዳት አይቻላቸውም፤ እርሱ ልባችንን ጽኑዕ ሲያደርግ ማንም እኛን ለማነዋወጽ ኃይል የለውምና።"
(ንስሓ እና ምጽዋት ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እንዳስተማረው ገጽ 73-74 ገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተረጎመው) | 5 757 |
| 9 | ሰላም ቤተሰቦች
➛ 1 ተአምረ ማርያም ባለ 366ቱ ተአምር
➛ 1 ተአምረ ኢየሱስ እና
➛ 1 ስንክሳር የዓመቱ
➛ 1 ሃይማኖተ አበው
➛ አጣን
➛ ዘቢብ
➛ የሰም ጧፍ
ለእመቤታችን ቤተክርስቲያን ያስፈልጋል!
ፈቃደኛ የሆነ በውስጥ መስመር @natansolo ኑ። | 5 209 |
| 10 | "ክርስቶስና ሙሴ"
የዕብራውያን መልእክት ትምህርት በሰንበት ቲዩብ
https://youtu.be/bHgQ1Techd4?si=KTCJ06OifpV6sKqZ | 5 710 |
| 11 | ሰላም ቤተሰቦች
➛ 1 ተአምረ ማርያም ባለ 366ቱ ተአምር
➛ 1 ተአምረ ኢየሱስ እና
➛ 1 ስንክሳር የዓመቱ
➛ 1 ሃይማኖተ አበው
➛ አጣን
➛ ዘቢብ
➛ የሰም ጧፍ
ለእመቤታችን ቤተክርስቲያን ያስፈልጋል!
ፈቃደኛ የሆነ በውስጥ መስመር @natansolo አናግሩን። | 5 860 |
| 12 | በመስቀል ምልክት ሳታማትብ ከቤትህ አትውጣ፡፡ በትር፣ መሳሪያ፣ የማይበገር ምሽግም ይሆንሀል፡፡ ሰውም ሆነ ጋኔን አንተን ለማጥቃት አይደፍሩም፤ እንደዚህ ያለ ኃይለኛ የጦር ትጥቅ ታጥቀሃልና፡፡ ይህም አንተ ልክ እንደ ወታደር እንደሆንክ፣ ከአጋንንት ጋር ለመዋጋት ዝግጁ እንደሆንክ፣ በድልም አክሊልን እንደምታገኝ ምልክት ነው፡።
መስቀሉ ያደረገውን አታውቁምን? ሞትን አሸንፏል፣ ኃጢአትን አጥፍቷል፣ ሲኦልን ባዶ አድርጓል፣ ሰይጣንን ከዙፋን አውርዷል፣ አጽናፈ ዓለሙንም ወደ እግዚአብሔር መልሷል፡፡
ታዲያ ኃይሉን ትጠራጠራለህ? መስቀሉ ይህን ኹሉ ድንቅ ነገር አድርጎልናል፤ መስቀል በአጋንንት ፊት የቆመ የሽንፈታቸው መታሰቢያ ነው፤ ክርስቶስ እባቡን የገደለበት ሰይፍም ነው:: መስቀል የአብ ፈቃድ፣ የአንድያ ልጁ ክብር፣ የመንፈስ ቅዱስ ደስታ፣ የመላእክት ውበት፣ የቤተክርስቲያን ጠባቂ ነው፡፡ ጳውሎስም እንዳለው መስቀል የቅዱሳን መከታ ነው፤ የዓለም ኹሉ ብርሃንም ነው፡፡
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ➛የነፍስ ምግብ ገጽ 78 በፍሉይ ዓለም የተተረጎመ) | 7 081 |
| 13 | ሰላም ቤተሰቦች
➛ 1 ተአምረ ማርያም ባለ 366ቱ ተአምር
➛ 1 ተአምረ ኢየሱስ እና
➛ 1 ስንክሳር የዓመቱ
➛ 1 ሃይማኖተ አበው
➛ አጣን
➛ ዘቢብ
➛ የሰም ጧፍ
ለእመቤታችን ቤተክርስቲያን ያስፈልጋል!
ፈቃደኛ የሆነ በውስጥ መስመር @natansolo አናግሩን። | 6 111 |
| 14 | "የተወደዳችሁ አሁንም ዕድል ስላላችሁ ወደ ክርስቶስ በተሰበረ ልብ በንስሐ ተመለሱ።"
አባ ሙሴ ጸሊም | 6 314 |
| 15 | "አንድ ሰው የራሱን ኃጢአት ሁልጊዜ በፊቱ የሚያይና የሚመረምር ከሆነ፣ በሌላው ሰው ላይ ያለውን ድክመትና ኃጢአት ለማየት አይፈልግም። የገዛ ራሱን ሙት (ኃጢአቱን) ትቶ የሌላውን ሰው ሙት ሊቀብር የሚሄድ ሰው የለምና። አንተም የራስህን በደል እያሰብህ የምታለቅስ ከሆነ፣ በሌላው ወንድምህ ላይ ለመፍረድና እርሱን ለማሳነስ ጊዜ አይኖርህም። በሰዎች ላይ ከመፍረድ ይልቅ ራስን መውቀስ፣ ከጥላቻ ይልቅ ፍቅርን መምረጥ የእውነተኛ ክርስትና መጀመሪያ ነው።"
አባ ሙሴ ጸሊም
#ሰኔ_24
አባ ሙሴ ጸሊም (ጥቁሩ ሙሴ) አስቀድሞ ኃይለኛ፣ ነፍሰ ገዳይ፣ ቀማኛና የጣዖት አምላኪ የነበረ ኋላም የእግዚአብሔርን መንገድ ፍለጋ ወደ አስቄጥስ ገዳም በመሄድ ንስሐ ገብቶ የመነኰሳት አባት (አበ ምኔት) ለመሆን የበቃ የታላቅ አባት ነው።
እርሱም በጸሎቱ ዝናምን ከሰማይ የሚያዘንብ፣ በትሕትናውና በጽኑዕ ገድሉ የከበረና "በሰይፍ የገደለ በሰይፍ ይገደላል" የሚለውን የጌታ ቃል ለመፈጸም የበርበር ሰዎችን ሰይፍ በደስታ በመቀበል ሰኔ 24 ቀን ከሰባት መነኰሳት ጋር በሰማዕትነት አርፏል፣
ቅዱስ ሙሴ ጸሊም የንስሐ ኃይል ምን ያህል ታላቅ እንደሆነና ሰውን ከኃጢአት ጥልቁ አውጥቶ ወደ ቅድስና ማማ እንደሚያደርስ ያየንበት አባት ነው።
በረከቱ ይደርብን! | 8 207 |
| 16 | "ፈተና ሲገጥመን ውስጣችን ሊረበሽ ወይም በቀቢጸ ተስፋ ሊያዝ አይገባውም፡፡ ወርቅን የሚያነጥር ሰው በእሳት ውስጥ የጨመራትን የወርቅ ቅንጣት እዚያ ውስጥ ምን ያህል ጊዜ መቆየት እንዳለባት ያውቃል፤ መቼ ከእሳቱ ሊያወጣት እንደሚገባውም ያውቃል፡፡ እንዲሁ እስከ መጨረሻው በእሳቱ ውስጥ ተጥላ እንድትቀርና በዚያ እንድትቃጠል አይፈቅድም፡፡
እግዚአብሔር ደግሞ ይህን ከወርቅ አንጣሪው በላይ ያውቃል፡፡ መቼ ከርኩሰታችን እንደምንነጻ ያውቃል፡፡ በመኾኑም ራሳችንን በመጣልና ተስፋ በመቁረጥ በክፋት ላይ ክፋት እየጨመርን እንዳንኼድ ሽቶ መቼ ከዚያ ፈተና እንደሚያወጣን ያውቃል፡፡
ስለዚህ ድንገት ያላሰብነው ነገር ቢገጥመን በፍጹም የምናማርር፣ ወይም ተስፋ የምንቆርጥ ልንኾን አይገባንም፡፡ ከዚህ ይልቅ የእነዚህ ነገሮች ምንነትን የሚያውቅ እግዚአብሔርን መጠበቅ፣ እርሱ እስከ ፈቀደው ጊዜ ድረስም ልቡናችንን በእሳት እንዲፈተን ማድረግ ይገባናል። ምክንያቱም ይህ ነገር በእኛ ላይ እንዲኾን (እንዲመጣ) የፈቀደው ለእኛ ጥቅምና በዚያ ውስጥ ኾነን በምናሳየው ጥረት ይበልጥ ሊያከብረን ስለሚወድ ነው፡፡"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ወደ ኦሎምፒያስ ከላከው መልእክት የተቀነጨበ | 7 839 |
| 17 | "በማዕበል መሀል እንዳለች ታንኳ ልብህ በጭንቀት ስትናወጥ፣ ማዕበሉን ጸጥ ማድረግ ወደሚችለው ወደ ክርስቶስ ፊት ቅረብ። ጭንቀትህ የቱንም ያህል ከባድ ቢሆን፣ የእግዚአብሔር ቸርነት ግን ከዚያ ይበልጣል። እርሱ ስለ አንተ የሚያስብ አባት ነውና ነገ ምን እሆናለሁ ብለህ አትጨነቅ፤ የዛሬን ቀን የሰጠህ አምላክ የነገውንም ማዕበል በጥበቡ ያሳልፈዋል። ብዙ ጊዜ የምንጨነቀው ሁሉንም ነገር በራሳችን አቅም ለመወጣት ስንሞክር ነው፤ ነገር ግን ሸክምህን በጸሎት ወደ እርሱ ስትጥለው፣ እርሱ በልብህ ውስጥ ሰላምን ያሳድራል። ቅዱሳን ሐዋርያት በዓለም ሳሉ ብዙ መከራና ጭንቀት ገጥሟቸዋል፤ ነገር ግን ልባቸው አልፈራም፤ ምክንያቱም ከእነርሱ ጋር ያለው ጌታ ከዓለም ሁሉ እንደሚበልጥ ያውቁ ነበርና። አንተም ዛሬ ሸክምህን ለእርሱ ስጥ፤ እርሱ ደግሞ ዕረፍትን ይሰጥሃል።"
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ) | 8 943 |
| 18 | የድጋፍ ጥሪ
"ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።"
ላለፉት ዓመታት በፈለገ ሰላም ሰንበት ትምህርት ቤት በልዩ ልዩ የአገልግሎት ክፍሎች በትጋት ሲያገለግል የቆየው ወንድማችን ዲ/ን እሸቱ ኤፍሬም (ሀብተ ወልድ)፤ አሁን ላይ ለበለጠና ለተሻለ አገልግሎት ለማዘጋጀት አስቧል።
በመሆኑም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በታላቁ የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለመማር ተመዝግቧል።
የወንድማችን አጠቃላይ የትምህርት ክፍያ (Tuition Fee) በስፖንሰር የተሸፈነ ሲሆን፣ ትምህርቱን በጉባኤ ቤት ሆኖ ለመከታተል ግን የዓመት ቀለብ (የምግብ ወጪ) ድጋፍ ያስፈልገዋል።
ይህንን በጎ አገልግሎት በመረዳት ወንድማችንን በዕውቀት ተኮትኩቶ ለቤተ ክርስቲያን እንዲተርፍ ማገዝ የምትፈልጉ ወንድሞችና እህቶች በሚከተለው አካውንት እንድታግዙት ከታላቅ አክብሮት ጋር በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ➛ ለእሸቱ ኤፍሬም
1000327329492
ስልክ ➛ 0985650289
"እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፥ እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና።" (፪ኛ ቆሮ ፱፥፯) | 7 661 |
| 19 | እንደ ኃጢአት አዋራጅ የለም
እንደ ኃጢአት አዋራጅ የለም፡፡ ኃጢአትን የሚያደርግ ሰው በሐፍረት ካባ ብቻ የሚከናነብ አይደለም፤ አስቀድሞ ከነበረው ማስተዋልና ማገናዘብም ይዋረዳል እንጂ፡፡ ይህንንም ለመረዳት የአዳም የቀድሞ ክብሩን ማሰብ እንቸችላለን፡፡
ዳግመኛም ኃጢአትን ከሠራ በኋላ ያገኘውን ውርደት እንመልከተው፡፡ “በሰርክ ጊዜ ጌታ በገነት ውስጥ ድምፀ ሰናኮ ብእሲ እያሰማ ወደነርሱ ሲመጣ በሰሙ ጊዜ አዳምና ሔዋን ከእግዚአብሔር ፊት በገነት ዕንጨት መካከል ተሰወሩ” (ዘፍ.3፥8)፡፡ በዚህስ አዳም እንደ ምን ባለ ውርደት እንደ ተያዘ ታስተውላላችሁን? ምሉእ በኩለሄ ከኾነው፣ ፍጥረታትን ካለ መኖር ወደ መኖር ካመጣው፤ የተሰወረውን ኹሉ ከሚያውቀው፤ የሰውን ልቡና የፈጠረና በኀልዮ የሠሩትን ዐውቆ ከሚፈርደው (መዝ.33፥15)፤ ልብ ያሰበውን ኩላሊት ያጤሰውን መርምሮ ከሚያውቀው (መዝ.7፥9)፤ ልቡናችን ያሰበውን ከሚያውቀው (መዝ.44፥21) ከእግዚአብሔር ሊሸሸግ መውደዱ ከማወቅ ወደ ድንቁርና ከክብር ወደ ኃሣር እንደ ኼደ ያመለክታል፡፡
እኛም ኃጢአት ስንሠራ እንደዚህ ነው፡፡ መሸሸግ ባንችል እንኳን መሰወርን እንሻለን፡፡ ይህን ማድረጋችንም በኃጢአታችን ምክንያት ክብራችን እንደ ምን እንዳጣን፤ ሐፍረታችንን መሸፈንም እንደ ምን እንዳቃተን ያስረዳል፡፡ ነገር ግን ኃጢአትን የሠራ ሰው እንኳንስ በረኻ በኾነች በዚህች ምድር በገነት መካከልም መደበቅ አይችልም፡፡
("የክርስቲያን መከራ እና ሌሎች" በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ገጽ 81 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ) | 7 753 |
| 20 | ማስታወቂያ
ፈጣን፣ አስተማማኝ እና ህጋዊ የዕቃ ማድረስ አገልግሎት!
በልዩ ባስ ክፍለሀገር ተሳፋሪ መኪና ላይ የምሰራ አስተናጋጅ ነኝ። ህጋዊ ደረሰኝ ያላቸውን የእርስዎን ውድ ዕቃዎች፣ መልዕክቶች እና ፖስታዎች ካሉበት ቦታ ተቀብለን በታማኝነት እና በፍጥነት ወደ መዳረሻቸው እናደርሳለን!
የምንሰጣቸው አገልግሎቶች
➛ ማናቸውንም መልዕክቶች እና ፖስታዎች ማድረስ
➛ ማንኛውንም ዓይነት ዕቃዎች በታማኝነት ማጓጓዝ
የምንደርስባቸው ዋና ዋና መስመሮች እና ከተሞች
1ኛ መስመር (ወደ መቀሌ)፦ ቆቦ ➔ አላማጣ ➔ መሆኒ ➔ አቢኣዲ ➔ አድዋ ➔ ሽሬ ... እና መቀሌ
2ኛ መስመር (ወደ ሞያሌ)፦ ሀዋሳ ➔ ዲላ ➔ ሀገረ ማርያም ➔ ቡሌሆራ ➔ ያቤሎ ➔ ሜጋ ... እና ሞያሌ
3ኛ መስመር፦ ነቀምቴ ➔ ደምቢዶሎ ...
4ኛ መስመር፦ ድሬዳዋ
5ኛ መስመር፦ ወላይታ ➔ አርባ ምንጭ
6ኛ መስመር፦ ጅማ እና ሚዛን
7ኛ መስመር፦ ደብረ ብርሃን ➛ ደሴ ➛ ወልድያ
8ኛ መስመር፦ ደብረ ማርቆስ ➛ ባህር ዳር➛ ጎንደር➛ ደብረ ታቦር
"ታማኝነት መለያችን ነው፤ ዕቃዎትን ካሰቡበት እናደርሳለን!"
አሁኑኑ ስልክ ቁጥሮች ይደውሉልን!
0921799534
0907851185
0786799534 | 7 445 |
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
