ru
Feedback
ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል

ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል

Открыть в Telegram

📈 Аналитический обзор Telegram-канала ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል

Канал ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል (@mkpublicrelation) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 51 504 подписчиков, занимая 1 057 место в категории Религия и духовность и 616 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 51 504 подписчиков.

Согласно последним данным от 18 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 650, а за последние 24 часа — 23, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 13.50%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 7.68% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 6 952 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 3 954 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 54.

📝 Описание и контентная политика

Описание канала не предоставлено.

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 19 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

51 504
Подписчики
+2324 часа
+1457 дней
+65030 день
Архив постов
photo content

የተተኪ መምህራን ሥልጠና ሲወስዱ የቆዩ ሠልጣኞች መመረቃቸውን የአሜሪካ ማእከል ገለጸ ሐምሌ ፱/፳፻፲፰ ዓ.ም በማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማእከል ግቢ ጉባኤያት ማስተባበሪያ ክፍል ከዲሲ ንኡስ ማእከል
+1
የተተኪ መምህራን ሥልጠና ሲወስዱ የቆዩ ሠልጣኞች መመረቃቸውን የአሜሪካ ማእከል ገለጸ ሐምሌ ፱/፳፻፲፰ ዓ.ም በማኅበረ ቅዱሳን የአሜሪካ ማእከል ግቢ ጉባኤያት ማስተባበሪያ ክፍል ከዲሲ ንኡስ ማእከል ጋር በመሆን  ያዘጋጀውና ከተለያዩ የአሜሪካ ግዛቶች የመጡ ተማሪዎች ለሦስት ሳምንታት ሜሪላንድ በሚገኘው የማኅበሩ ጽ/ቤት የተከታተሉትን ሥልጠና አጠናቀው ተመርቀዋል:: ደቀ መዛሙርቱ በቆይታቸው ሃይማኖት እና ክርስቲያናዊ ሥነ ምግባርን ጨምሮ ሌሎች ትምህርቶችንም የወሰዱ ሲሆን በ3 ደረጃዎች ተከፍሎ ሲሰጥ በነበረው ሥልጠና ተማሪዎች በቀጣይ ወደ ኮሌጆቻቸው ሲመለሱ ለሕይወታቸው የሚጠቅማቸውን ስንቅ እንዳገኙ ያነጋገርናቸው ሠልጣኞች ገልጸዋል:: አክለውም በቆይታቸው ያገኙትን ትምህርት  በየሚያገለግሉበት ቤተ ክርስቲያን ሕጻናትን ለማስተማር እንደሚጠቀሙበት የገለጹልን ሲሆን በግቢ ለሚገጥማቸው ተግዳሮት መሻገሪያ እንደሚሆናቸው ተናግረዋል። ሥልጠናውን ከሰጡት መምህራን መካከል የዝግጅት ክፍላችን ያነጋገራቸው ቀሲስ ዶ/ር ቴዎድሮስ በበኩላቸው  ሥልጠናው ለቀጣይ ሕይወታቸው አቅጣጫ የሚሰጥ ነው ያሉ ሲሆን አክለውም ወደየመጡብት አካባቢ ሲመለሱ ጠንክረው ቤተ ክርስቲያንን እንዲያገልግሉ አደራ ሰጥተናቸዋል ብለዋል :: ከነበሩት 24 ሠልጣኖች መካከል አራቱ ሴቶች ሲሆኑ ለመጀመርያ ጊዜ በዚህ ዙር ሥልጠና ሴቶች ተሳታፊ መሆናቸውም ተገልጿል።   በመጨረሻም ሠልጣኞቹ ሥልጠናውን በብቃት ማጠናቀቃቸውን የሚገልጽ የተዘጋጀላቸውን የምስክር ወረቀት ተቀብለዋል::

በመርሐ ግብሩም የአሸናፊ ተማሪዎች ንድፍ ላይ የዳኞች ሙያዊ ግምገማ ምልክታ፣ “የቤተ ክርስቲያን ሕንጻ ግንባታ ተግዳሮቶች እና መፍትሔዎች” በተመለከተ ጥናታዊ ጽሑፎች እና ሌሎችም ይቀርባሉ። ምእመናን ፣ተማሪዎች፣ ቀጣሪ ድርጅቶች፣ ጉዳዩ የሚመለከታችሁ አጋርና ባለድርሻ አካላት፣ አርክቴክቶችና የምሕንድስናው ዘርፍ ሙያተኞች በቦታው ተገኝታችሁ ሙያዊ ምክራችሁን እንድትለግሱ ብሎም የአሸናፊ ተማሪዎችን ሥራ እንድታበረታቱ ጥሪ ቀርቧል።

ማኅበረ ቅዱሳን ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ሲያካሂድ የቆየውን የኪነ ሕንጻ ንድፍ ውድድር አሸናፊዎች ይፋ ማድረጊያ መርሐ ግብር ሊያዘጋጅ መሆኑ ተገለጸ። ሐምሌ ፰/፳፻፲፰ ዓ.ም ማኅበረ ቅዱሳ
ማኅበረ ቅዱሳን ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ሲያካሂድ የቆየውን የኪነ ሕንጻ ንድፍ ውድድር አሸናፊዎች ይፋ ማድረጊያ መርሐ ግብር ሊያዘጋጅ መሆኑ ተገለጸ። ሐምሌ ፰/፳፻፲፰ ዓ.ም ማኅበረ ቅዱሳን ባለፉት 34 ዓመታት ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊና ማኅበራዊ አገልግሎት መሳካት ካበረከታቸው አገልገሎቶች መካከል ኦርቶዶክሳውያን ሙያተኞች በሙያቸው ለቤተ ክርስቲያን ነጻ ሙያዊ አገልግሎት እንዲሰጡ ማድረግ ቀዳሚው ተልእኮ መሆኑ ተገልጿል። በዚሁ መሠረት የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት ኦርቶዶክሳውያን ሙያተኞችን በየሙያቸው በማደራጀት ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስልታዊ አበርክቶ ያላቸው ተግባራትን እየፈጸመ እንደሚገኝም ተጠቅሷል። በምሕንድስናው ዘርፍ የሚገኙ ሙያተኞችም ያላቸውን ሳይንሳዊ ዕውቀት ከቤተ ክርስቲያን ጥንታዊ የኪነ ሕንጻ ዕውቀት ጋር በማዋሐድ፣ በተገቢው ሁኔታ ለአገልግሎት እንዲያውሉት ለማድረግ እንዲቻል፣ በየዓመቱ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት (የግቢ ጉባኤያት) ተማሪዎች መካከል የቤተ ክርስቲያን ንድፍ ሥራ ውድድር ያካሂዳል። በያዝነው የ2018 ዓ.ም አገልግሎት ዘመንም በ10 ማእከላት ውስጥ የሚገኙ 259 የአርክቴክቸራል ተማሪዎች በዚህ ውድድር ለመሳተፍ ተመዝግበው ሥራዎቻቸውን አቅርበው በየማእከላቱ በሚገኙ ዳኞች ሲገመገሙ የቆዩ ሲሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ1-3ኛ በመውጣት አሸናፊ የሚሆኑትን ለመለየት በዋናው ማእከል ደረጃ የ19 ተማሪዎች ሥራ በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ባላቸው ዳኞች ተገምግመዋል። በዚሁ መሠረት ከ1-3ኛ ደረጃ ይዘው ያጠናቀቁ አሸናፊዎች ቅዳሜ ሐምሌ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 7፡00 ጀምሮ በማኅበሩ ሕንጻ 3ኛ ወለል በሚካሄድ የዕውቅና እና የሽልማት መርሐ ግብር ላይ ይፉ ይደረጋሉ ተብሏል።

የሁሉም ማስተባብርያዎችን በአንድ ቦታ የሚያሰባስበው የአሜሪካ ማእከል 28ኛ ጠቅላላ ጉባኤም በአትላንታ ከተማ ከሐምሌ 24 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ/ም እንደሚካሄድ ለማወቅ ተችሏል። ዘገባው የአሜሪካ ማእከል ሚዲያ ክፍል ነው።

በማኅበረ ቅዱሳን አሜሪካ ማእከል ሥር ያሉ ማስተባበሪያ ማእከላት ጠቅላላ ጉባኤያቸውን አካሄዱ ሐምሌ ፰/፳፻፲፰ ዓ.ም የማኅበሩን ተቋማዊ ለውጥ ተከተሎ በአሜሪካ ማእክል ሥር የተቋቋሙት ሦስት ማስተባበ
+3
በማኅበረ ቅዱሳን አሜሪካ ማእከል  ሥር ያሉ ማስተባበሪያ ማእከላት ጠቅላላ ጉባኤያቸውን አካሄዱ ሐምሌ ፰/፳፻፲፰ ዓ.ም የማኅበሩን ተቋማዊ ለውጥ ተከተሎ በአሜሪካ ማእክል ሥር የተቋቋሙት ሦስት ማስተባበሪያዎች የ2018 ዓ.ም ጠቅላላ ጉባኤያቸውን በበየነ መረብ ያካሄዱ ሲሆን ይህም በየሁለት ዓመቱ በአካል እንዲካሄድ የተወሰነውን ውሳኔ መሠረት በማድርግ እንደሆነ ተገልጿል። ከሦስቱ ማስተባበሪያ ማእከላት ውስጥ አንዱ የሆነው የምሥራቅ ማስተባበሪያ በኢንዲያና ግንኙነት ጣቢያ አዘጋጅነት የተካሄደ ሲሆን የኦሃዮ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል በጉባኤው በመገኘት  የሀገረ ስብከታቸውን መልእክት አስተላልፈዋል::   የመካከለኛ ማስተባበርያ ያዘጋጀው የካንሳስ ግንኙነት ጣቢያ ሲሆን የሚንሶታና አካባቢው ሀገረ ስብከት  ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል በጉባኤው ተገኝተው አባታዊ መመሪያና ቡራኬ ሰጥተዋል።   በተመሳሳይ የምዕራብ ማስተባበርያን ያዘጋጀው ደግሞ የአሪዞና ግንኙነት ጣቢያ ሲሆን በጉባኤው ላይ የተገኙት የሰሜን ካሊፎንያ፤ ኔቫዳና አሪዞና  አህጉረ ስብከት   ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ ዶ/ር አቡነ ቴዎፍሎስ መልእክት በማስተላለፍ ተተኪው ትውልድ ላይ ማኅበሩ ትኩረት አድርጎ እንዲሠራ አሳሰበዋል፤ ሀገረ ስብከታቸውም ለሚጠየቀው  ሁሉ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርግም  አሳውቀል። በጉባኤው በሦስቱም ማስተባበሪያዎች የ2018 ዓ/ም ዕቅድ አፈጻጸም  እንዲሁም የ2019 ዓ/ም ዕቅድ ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን ለቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት የሚመሩ የሥራ አስፈጻሚዎች ምርጫ ተካሄዷል። ማስተባበርያዎች ከተመሠረቱ ሦስት ዓመት ያስቆጠሩ ሲሆን በአጭር ጊዜ ውስጥ በርካታ ስኬቶችን ማስመዝገባቻቸው ተነሥቶ የበለጠ ውጤታማ እንዲሆኑ አባላት በንቃት የሚቻላቸውን ሁሉ እንዲያበረክቱም ጥሪ ቀርቧል።

አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በስም በአካል በግብር ሦስት በባሕርይ በሕልውናና በፈቃድ አንድነት ጽኑዓን (የጸኑ) ናቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ተገኙ፣ በዚህ ጊዜ ያልፋሉ አይባሉም መጀመሪያም መጨረሻም እነርሱ ናቸውና፡፡ ቅድስት ሥላሴን የሰው አእምሮ አጥንቶ እና ተመራምሮ ሊደርስበት አይችልም ምክንያቱም ከዕውቀትና ከአእምሮ በላይ ስለሆነ ይህንንም ለማስረዳት  ሊቁ ቅዱስ አትናቴዎስ ዘአንጾኪያ “ወበፈጢረ ኵሉ ፍጥረታት ቅድስት ሥላሴ ኅቡራነ መለኮት እለ ርሑቃን እምኵሉ ዓቅም ወኁልቊ፡፡ ቅዱስ አትንቴዎስ ዘአንጾኪያ በከሀሊነት ፍጥረትን ሁሉ በመፍጠር ከአብ ከወልድ ጋር አንድ ነው፤ በመለኮት አንድ የሚሆኑ፤ ሦስት አካላት ከመወሰን፤ ከቊጥር ሕግ ሁሉ የራቁ ናቸው”፡፡ ሃይ.አበ ፻፰፡፪  እንዲህ ስለተባለ ግን ስለ ሥላሴ ማወቅና መማር አይቻልም ማለት አይደለም ምክንያቱም በመጻሕፍት ተጽፎ እንደምናገኘውና አባቶቻችን እንዳስተማሩን ቅድስት ሥላሴ በባሕርያቸው የማይመረመሩ ቢሆንም ለእኛ ግን በምንችለውና በምንረዳው ልክ እንደ አቅማችን በተለያየ መንገድ ራሳቸውን ገልጸውልናል ሥላሴ እንደ እናት ርኅሩኀን ናቸውና በእናት ሥርዓት ‹‹ቅድስት ሥላሴ›› እንላቸዋለን፡፡ ይህንንም ሊቁ አባታችን ቅዱስ ዮሐንስ ዘአንጾኪያ በሃይማኖተ አበውእንዲህ ሲል ይገልጸዋል ወኢናንቀለቅል ለግሙራ ኀበ ካልእ ሃይማኖት በእንተ ቅድስት ሥላሴ ቅዱስ የሐንስ ዘአንጾኪያ  ስለ ምሥጢረ ሥላሴ ካመንነው እምነት ወደ ሌላ ሃይማኖት አንናወጥም በማለት ሥላሴን ቅድስት ሥላሴ ብሎ በሴት (በእናት) አንቀጽ ሲናገር እናያለን ስለዚህ ሥላሴ እኛ በምንረዳው ልክ በተለያየ አገላለጽ ተገልጸዋል ካልን ከተገለጹበት መንገድ አንዱ በኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ ፲፰፡፩_፲፮ ተጽፎ እንደ ምናገኘው  ለአባታችን ለቅዱስ አብርሃምና ለእናታችን ለቅድስት ሣራ የተገለጸበት መንገድ ነው ከፍጥረታት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የአብርሃምን ያህል በሥላሴ ዘንድ የተወደደ ሰው የለም አባታችን ቅዱስ አብርሃም የደግነት ሁሉ አባት ነውና  ስለዚህ ዛሬ የምናስበውና ምናከብረው  ይህንን ነው ።   ይኸውም ታሪኩን ስንመለከተው ፡- አብርሃም በተመሳቀለ መንገድ  በቀትርም ጊዜ እርሱ በድንኳኑ ደጃፍ ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር በመምሬ የአድባር ዛፍ ተገለጠለት። ዓይኑንም አነሣና እነሆ፥ ሦስት ሰዎች በፊቱ ቆመው አየ ባያቸውም ጊዜ ሊቀበላቸው ከድንኳኑ ደጃፍ ተነሥቶ ሮጠ፥ ወደ ምድርም ሰገደ፥እንዲህም አለ፦   አቤቱ፥ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደ ሆነ ባሪያህን አትለፈኝ ብዬ እለምናለሁ ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ፥ እግራችሁን ታጠቡ፥ ከዚህችም ዛፍ በታች ዕረፉ ቍራሽ እንጀራም ላምጣላችሁ፥ ልባችሁንም ደግፋ ከዚያም በኋላ ትሄዳላችሁ ስለዚህ ወደ ባሪያችሁ መጥታችኋልና። እነርሱም፦ እንዳልህ አድርግ አሉት። አብርሃምም ወደ ድንኳን ወደ ሣራ ዘንድ ፈጥኖ ገባና፦ ሦስት መስፈሪያ የተሰለቀ ዱቄት ፈጥነሽ አዘጋጂ፥ ለውሺውም፥ እንጎቻም አድርጊ አላት።   አብርሃምም ወደ ላሞቹ ሮጠ፥ እጅግ የሰባም ታናሽ ጥጃ ያዘና ለብላቴናው ሰጠው፥ ያዘጋጅም ዘንድ ተቻኰለ። እርጎና ወተትም ያዘጋጀውንም ጥጃ አመጣ፥ በፊታቸውም አቀረበው እርሱም ከዛፉ በታች በፊታቸው ቆሞ ነበር፥ እነርሱም በሉ። እነርሱም፦ ሚስትህ ሣራ ወዴት ናት? አሉት። እርሱም፦ በድንኳኑ ውስጥ ናት አላቸው። እርሱም፦ የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተ በእውነት እመለሳለሁ ሚስትህ ሣራም ልጅን ታገኛለች አለ። ሣራም በድንኳን ደጃፍ በስተ ኋላው ሳለች ይህንን ሰማች።   አብርሃምና ሣራም በዕድሜአቸው ሸምግለው ፈጽመው አርጅተው ነበር በሴቶች የሚሆነውም ልማድ ከሣራ ተቋርጦ ነበር። ሣራም በልብዋ እንዲህ ስትል ሳቀች፦ ካረጀሁ በኋላ በውኑ ፍትወት ይሆንልኛልን? ጌታዬም ፈጽሞ ሸምግሎአል።እግዚአብሔርም አብርሃምን አለው። ካረጀሁ በኋላ በውኑ እወልዳለሁን? ስትል ሣራ ለምን ሳቀች? በውኑ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር አለን? የዛሬ ዓመት እንደ ዛሬው ጊዜ ወደ አንተ እመለሳለሁ ሣራም ልጅን ታገኛለች። ሣራም ስለ ፈራች፦ አልሳቅሁም ስትል ካደች። እርሱም፦ አይደለም፥ ሳቅሽ እንጂ አላት ። ከታሪኩ እንደምረዳው በብሉይ ኪዳን ከሚገርሙ የሥላሴ ምሳሌዎች አንዱ በአብርሃም ቤት የተፈጸመው ነው ። ምክንያቱም የሠላሴ አንድነትና ሦስትነት የተገለጸበት ነውና  ይህ የአብርሃም መስተንግዶ ታላቅ ትምህርት አለው፤ 1.   አብርሃም እንግዳን አክብሮ በመቀበሉ ሥሉስ ቅዱስን ለመቀበል በቃ እኛም  እንደ አብርሃም እንግዳ ተቀባይ ብንሆን እንደ አብርሃም በጸጋ የእግዚአብሔር ማደሪያ እንሆናለን 2.   አብርሃም እንግዳን አክብሮ በመቀበሉ ከሥሉስ ቅዱስ ተስፋው ተነገረው  እኛም እንደ አብርሃም እንግዳ ተቀባይ ብንሆን እንደ በዚህ ዓለም የጨለመብን ተስፋ በሥላሴ ይበራልናል ። 3.   አብርሃም እንግዳን አክብሮ በፍቅር በመቀበሉ የፍቅር ባለቤት የሆኑ ሥሉስ ቅዱስ ፍቅራቸውን ገለጹበት እኛም እንደ አብርሃም እንግዳን በፍቅር ተቀባይ ብንሆን እንደ አብርሃም ፍቅር ባለቤት ሥሉስ ቅዱስ ፍቅርን በጸጋ ያጎናጽፉናል 4.   አብርሃም እንግዳን አክብሮ በእምነት በመቀበሉ ከሥሉስ ቅዱስ የእምነቱን ዋጋ ተቀብሏል እኛም እንደ አብርሃም እንግዳን በእምነት ተቀባይ ብንሆን እንደ አብርሃም ሥሉስ ቅዱስ የእምነታችንን ዋጋ በመንግሥተ ሰማያት ይሰጡናል ። በአጠቃላይ በዚህ በዓል የሥላሴ ፍቅር የአብርሃም እምነት የሣራ ትዕግሥት በአንድነት የታየበት ብዙ ትምህርት የምንማርበት በዓል ነው  በፍቅር መኖር በእምነት መጽናት ትዕግስትን ገንዘብ ማድረግ ይገባናል ።   በምግባር በሃይማኖት ጸንተን እንደ አእምሮአችን ስፋት በምንችለው መጠን ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያልን በምስጋና ጸንተን የሥላሴን መንግሥት እንወርስ ዘንድ ሥሉስ ቅዱስ ጥበብ ምሥጢርን ይግለጹልን  የቅዱሳኑ ጸሎት ይርዳን አሜን።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩ አምላክ አሜን! አብርሃም ርእየ ፫ተ እደወ፤ በዛቲ ዕለት ምሥጢረ ሥላሴ ዜነወ። "አብርሃም ሦስት ሰዎችን አየ፤ በዚያችም ቀን የቅድስት ሥላሴ ምሥጢር ተገለጠ።"
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ፩  አምላክ አሜን! አብርሃም ርእየ ፫ተ እደወ፤ በዛቲ ዕለት ምሥጢረ ሥላሴ ዜነወ። "አብርሃም ሦስት ሰዎችን አየ፤ በዚያችም ቀን የቅድስት ሥላሴ ምሥጢር ተገለጠ።" የቅድስት ሥላሴ በዓልን ስናከብር የምናስበው ታላቁን የእምነታችንን ምሥጢር ነው። አብ፣ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በመለኮት አንድ በአካል በግብር ሦስት ናቸው ። አምላክ ውእቱ አብ፤ ወአምላክ ውእቱ ወልድ፤ ወአምላክ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ወኢይትበሀሉ ፫ተ አማልክተ፡፡ አላ ፩ዱ አምላክ፡፡ አብ አምላክ ነው፤ወልድም አምላክ ነው፤ መንፈስ ቅዱስም አምላክ ነው፡፡ ግን ሦስት አማልክት አይባሉም አንድ አምላክ እንጂ፡፡ “ወከመዝ ውእቱ እምነትነ በቅድስት ሥላሴ ዘይሴብሑ እምነ ኵሉ ዘውእቶሙ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ወኢንትአመን በካልእ አምላክ እምእሉ ፫ቱ አካላት እለ ፍሉጣን በገጻት ወኢሂ ፍሉጣን በህላዌ መለኮት በከመ ይቤ ዐቢይ መምህር ባስልዮስ በድርሳኑ በእንተ ሃይማኖት ዘቅድስት ሥላሴ ዘውእቶሙ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ህላዌ ዘኢተገብረ ወሥልጣን ከሀሊ ለፈጽሞ ኵሉ ፍጥረታት፡፡ ቅዱስ አትናቴዎስ ዘአንጾኪያ በሁሉ ዘንድ የሚመሰገኑ በቅድስት ሥላሴ የምናምነው እምነት እንዲህ ነው፤ እነዚህም አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ናቸው፤ በገጽ ልዩ በባሕርየ መለኮት የማይለዩ ከሚሆኑ ከእነዚህ ከሦስቱ አካላት በቀር፤ በሌላ አምላክ አናምንም፤ በቅድስት ሥላሴ ስለማመን በተናገረበት ድርሳኑ፤ ደገኛው መምህር ባስልዮስ እንደተናገረ፤ እነዚህም ያልተፈጠረ ባሕርይ ፍጥረትንም ሁሉ ለመፍጠር፤ ለማሳለፍ የሚቻለው ሥልጣን (አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ) ናቸው” ።

• #ክርስትና በማኀበራዊ ዐምድ ሥር ደግሞ "#በጋብቻ ውስጥ የሚታዩ ችግሮችና መፍትሔዎቻቸው " ክፍል ፪ በሚል ርእስ ዐቢይ ርእስ በመልአከ ሰላም ቀሲስ ደጀኔ ሺፈራው በትዳር ውስጥ ለሚፈጠሩ ችግሮች መፍትሔዎች በሚል ሰፊት ትምህርት ታሰተምራለች። • #በእናስተዋውቃችሁ ዐምድ ሥር “# የጥንቷ «አናቶሊያ» የክርስትና መልክና የዘመናት ማዕበል ክፍል ሁለት " በሚል ርእስ ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናት እና የጉባኤያቱ ስፍራዎች በስፋት ታስቃኛለች ። • #በነገዋ ቤተ ክርስቲያን #ዐምድ ሥር “ በውጭ ሀገር ያለችው ቤተ ክርስቲያን ዕድገት፣ አሁናዊ ዕድሎችና ተግዳሮቶች ክፍል ሁለት " በውጭ ያለችው ቤተ ክርስቲያን መልካም አጋጣሚዎችና ዕድሎች ፤መፍትሔዎች በስፋት ይዛለች ። #በኪነ ጥበብ ዐምድ "#የታቦት ትከሻዎች ክፍል_፪ "በሚል ርእስ ታስነብባለች ። • #የጥያቄዎቻችሁ መልስ ዐምድ “የክርስትና ጉዞ በቱርክ ጥንታዊና አሁናዊ ሁኔታ # ክፍል _፪" በሚል ርእስ #በቱርክ የነበሩት ታሪካዊና ኦርቶዶክሳዊ ቅርሶች በምን ሁኔታ እንደሚገኙ ፣በአሁኑ ወቅት በቱርክ የክርስትና ሕይወት ምን እንደሚመስል፤በቱርክ የደረረው የክርትና መውደቅ ለእኛ ለኦርቶዶክሳውያን ምን ያስተምረናል? መምህራን ተጉዘው ነበር፡፡ በዚህም መሠረት ባደረጉት ጉብኝት የተመለከቱትንና የተረዱትን ያካፍሉን ዘንድ የመጻሕፍተ ሐዲሳት መምህር የሆኑትን መምህር ኀይለ ማርያም ዘውዱን ጋብዘናል፡፡ ያካፍሉን ዘንድ የመጻሕፍተ ሐዲሳት መምህር የሆኑትን መምህር ኀይለ ማርያም ዘውዱን ጋብዘናል፡፡ ሐመር መጽሔት ፴፫ኛ ዓመት ቍጥር ፯ በማሰራጨት ፡በማንበብና በማስነበብ የድርሻችን እንወጣ ! Magazine @eotcmk.org #ሐመር #መጽሔትበ ዝግጅት ክፍል

# ሥርዐተ ምንኵስናን መታደግ የሚቻለው ወቅታዊ መግለጫዎችን በማውጣት ወይም ጊዜያዊ ውይይቶች ን በማካሄድ ብቻ አይደለም ።" ሐምሌ ዕትም በ፳፻፲፰ ዓ.ም ዐቢይ ጉዳይ ዐምድ ✍️ ༺ ༻ #የኅትመት ዘመ
# ሥርዐተ ምንኵስናን መታደግ የሚቻለው ወቅታዊ መግለጫዎችን በማውጣት ወይም ጊዜያዊ ውይይቶች ን በማካሄድ ብቻ አይደለም ።" ሐምሌ ዕትም በ፳፻፲፰ ዓ.ም ዐቢይ ጉዳይ ዐምድ ✍️ ༺ ༻ #የኅትመት ዘመን ፦#ሐምሌ ፳፻፲፰ ዓ.ም #አዘጋጅ ፦በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ማኅበረ ቅዱሳን በሚዲያ አገልግሎት ተቋም በመጽሔት ዝግጅት ክፍል የሚዘጋጅ ትምህርታዊ መጽሔት • ገጽ ብዛት፦፳፰ ዋጋ ፦፶ ብር •ሐመር መጽሔት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትምህርተ ሃይማኖት ሥርዓትና ትወፊት ጠብቃ በሚዲያ አገልግሎት ተቋም በመጽሔት ዝግጅት ክፍል የሚዘጋጅ ትምህርታዊ መጽሔት በየወሩ የምትወጣ መንፈሳዊ መጽሔት ናት፡፡ •ሐመር መጽሔት ፴፫ኛ ዓመት ቍጥር ፮ ሰኔ ፳፻፲፰ ዓ.ም. ዓ.ም መልእክት ዘማኅበረ ቅዱሳን " እነሆ እንደ በጎች በተኵላዎች መካከል እልካችኋለሁ ›› በሚል ታስነብባለች ። .#ዐውደ ስብከት ሥር” # ‹‹ጫማህን ከእግርህ አውጣ ›› ” በሚል ርእስ ታስነብባለች። #በትምህርተ ሃይማኖት ዐምድ ሥር “# ሐዋርያው ቅዱስ " በሚል ዐቢይ ርእስ በመልአከ ሰላም ቀሲስ ደጀኔ ሺፈራው ስለ ቅዱሰ ጳውሎስ ትምህርትና ሰፊ ትምህርት ይሰጣል ። #ዐቢይ ጉዳይ ዐምድ ሥር ደግሞ “# የሥርዓተ ምንኵስና ቀኖናዊ መሠረቶች፣ ተግዳሮቶችና ተቋማዊ መፍትሔ ዎቹ " ክፍል ሁለት " በሚል ርእስ የምንኵስና ተቋማዊ አደረጃጀት ና ቀኖናዊ ትግበራ፤ መፍትሔ በተመለከተ በዝርዝር ያሳያል ።

ዜና ገዳማት

ኑ ! ስደታቸው በሰንበትና በክረምት ለሆነባቸው እንድረስላቸው። ---***--- ለአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ወደ መርሐግብሩ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ
ኑ ! ስደታቸው በሰንበትና በክረምት ለሆነባቸው እንድረስላቸው። ---***--- ለአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር   ወደ መርሐግብሩ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ። https://zoom.us/j/93407133345 ድጋፍ ለማድረግ ፡- 1.   Mahibere Kidusan in Europa e.V. IBAN: DE14 3704 0044 0307 8037 00 BIC: COBADEFFXXX Reason of payment – 007   2.   Mahibere Kidusan in UK Banking - NatWest Sort Code - 60 12 51 Acc. No - 364 25 591 Reason of Payment: 007   3.   በስዊድን ለምትገኙ፡- ACCOUNT NUMBER - 9960 3421234653 BIC - NDEASESS IBAN - SE15 9500 0099 6034 2123 4653 ACCOUNT HOLDER - MAHIBERE KIDUSAN I SVERIGE NORDEA BANK Reason of Payment: 007   4.   በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000309803648 በአቢሲኒያ ባንክ 37235458 በአሐዱ ባንክ 0025393810901

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ …›› (ማቴ፲፣፳፰) ከዲ/ን ተስፋዬ ቻይ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! ሥጋንም የሚገድሉትን  ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ …›› (ማቴ፲፣፳፰)   ከዲ/ን ተስፋዬ ቻይ  ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳን ሐዋርያትን የምሥራቹን ወንጌል ሰብከው የጨለመውን የሰው ልጅ ልቡና በወንጌል ብርሃንነት ያበሩ ዘንድ፣ ከጣዖተ አምልኮ አውጥተው የፈጠራቸውን የሚመግባቸውን እግዚአብሔር ያውቁና ያመልኩ ዘንድ፣ በጠላት ዲያቢሎስ አሳሳችነት የመረረ ሕይወታቸውን በወንጌል ጨውነት ያጣፍጡ ዘንድ ወደ ዓለም በላካቸው ጊዜ ጠላት ዲያሎስ በክፉዎች እያደረ መከራ እንደሚያመጣባቸው፣ ይህንንም እንደ እባብ ብልህ ፣እንደ ርግብ የዋህ ሆነው እንዲያልፉ ፣ሳይፈሩና ሳይሰቀቁ እንዲመሰክሩ አዘዛቸው ፤ መከራቸው ስደት ፣መጠማት፣ ግርፋትና ረኀብ ባቻ ሳይሆን ሥጋዊ ሞት( የነፍስ ከሥጋ መለየት) እንደሚገጥማቸውና ይህም አንዳች እንዳያስፈራቸው ነገራቸው፤ ምድራዊ ሩጫቸው በሰማዕትነት ቢገታም ሰማየያዊ መኖሪ ዘለዓለማዊ ሕይወት እንዳለ የታመነውን ተስፋ ሰጣቸው፡፡ ቅዱሳን አበው ሐዋርያት ጌታችን ሞትን ድል አድርጎ በተነሣ በአርባኛው ቀን፣ ካረገ በአሥረኛው ቀን ባናገረው ትንቢት ፣በገባላቸው ቃል መሠረት የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ላከላቸው፣በጾም በጸሎ መንፈሳዊ ተግባራቸውን ጀመሩ ፤እምነታቸው ጸንቶ፣ፍርሃት ርቆላቸው ጥቡዐን ( ደፋሮች) ሆነው የእውቀት ተከፍሎ ሳይኖርባቸው ፤ዓለምን በዕጣ ተከፋፍለው የምሥራቹን ወንጌል ማስተማር ጀመሩ፡፡ https://eotcmk.org/a/በስመ-አብ-ወወልድ-ወመንፈስ-ቅዱስ-አሐዱ-አ-3/

ማኅበረ ቅዱሳን ለደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ ሁለ ገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት እያስገነባ እንደሚገኝ ገለጸ ሐምሌ ፫ /፳፻፲፰ ዓ.ም ማኅበረ ቅዱሳን በጎ አድራጊ አካላትን በማስተባበር በሰሜን ጎንደር ሀገ
ማኅበረ ቅዱሳን ለደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ ሁለ ገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት እያስገነባ እንደሚገኝ ገለጸ   ሐምሌ ፫ /፳፻፲፰ ዓ.ም  ማኅበረ ቅዱሳን በጎ አድራጊ አካላትን በማስተባበር በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ደባርቅ ከተማ የደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ ሁለ ገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት እያስገነባ እንደሚገኝ ገልጿል።   ማኅበረ ቅዱሳን በቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገትና መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች አገልግሎት የፕሮጀክት ዝግጅትና ትግበራ ምክትል ኃላፊ የሆኑት ኢ/ር ማስተዋል አበበ (ወ/ሪት) እንደገለጹት የደብረ ሐዊ የቅዱስ ያሬድ ገዳም በኢኮኖሚ ዐቅሙን ለማሳደግና አገልግሎቱን ለማስቀጠል የሚረዳ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት በሁለት ዙር  እንደሚከናወን ተናግረዋል።  ይህም በመጀመሪያው ዙር B+G+4 ወለል ሕንጻ እየተገነባ እንደሚገኝ የተጠቀሰ ሲሆን ማኅበሩ በዚህ ዙር  የሚጠበቅበትን ድርሻ ለማጠናቀቅ በመወጣት ረገድ 75.79% መድረሱን ተገልጿል።   ግንባታው በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚገኙ ድጋፍ አድራጊ አካላትን በማስተባበር የተከናወነ ነው ተብሏል።  በመጨረሻም ቅዱስ ያሬድ ለቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለሀገር  ባለውለታ  እንደመሆኑና ገዳሙ ጥንታዊ በመሆኑ ለመናንያኑ የዕለት ጉርስ፣ የዓመት ልብስ እንዲሁም ለአገልግሎቱ የሚያስፈልጉ ነገሮችን በማድረግ ገዳሙ ያለበትን ደረጃ ለማቆየት ሁሉም ምእመን በሐሳብ፣ በጉልበትና በገንዘብ የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ ይገባል ሲሉ ኢ/ር ማስተዋል አበበ  ጥሪ አቅርበዋል።

ማኅበረ ቅዱሳን ለደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ ሁለ ገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት እያስገነባ እንደሚገኝ ገለጸ   ሐምሌ ፪/፳፻፲፰ ዓ.ም  ማኅበረ ቅዱሳን በጎ አድራጊ አካላትን በማስተባበር በሰሜን ጎንደር ሀገረ ስብከት ደባርቅ ከተማ የደብረ ሐዊ ቅዱስ ያሬድ ሁለ ገብ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት እያስገነባ እንደሚገኝ ገልጿል።   ማኅበረ ቅዱሳን በቤተ ክርስቲያን ሁለንተናዊ እድገትና መንፈሳዊ ትምህርት ቤቶች አገልግሎት የፕሮጀክት ዝግጅትና ትግበራ ምክትል ኃላፊ የሆኑት ኢ/ር ማስተዋል አበበ (ወ/ሪት) እንደገለጹት የደብረ ሐዊ የቅዱስ ያሬድ ገዳም በኢኮኖሚ አቅሙን ለማሳደግና አገልግሎቱን ለማስቀጠል የሚረዳ የገቢ ማስገኛ ፕሮጀክት በሁለት ዙር  እንደሚከናወን ተናግረዋል።  ይህም በመጀመሪያው ዙር B+G+4 ወለል ሕንጻ እየተገነባ እንደሚገኝ የተጠቀሰ ሲሆን ማኅበሩ በዚህ ዙር  የሚጠበቅበትን ድርሻ ለማጠናቀቅ በመወጣት ረገድ 75.79% መድረሱን ተገልጿል።   ግንባታው በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚገኙ ድጋፍ አድራጊ አካላትን በማስተባበር የተከናወነ ነው ተብሏል።  በመጨረሻም ቅዱስ ያሬድ ለቤተ ክርስቲያንም ሆነ ለሀገር  ባለውለታ  እንደመሆኑና ገዳሙ ጥንታዊ በመሆኑ ለመናንያኑ የዕለት ጉርስ፣ የዓመት ልብስ እንዲሁም ለአገልግሎቱ የሚያስፈልጉ ነገሮችን በማድረግ ገዳሙ ያለበትን ደረጃ ለማቆየት ሁሉም ምእመን በሀሳብ፣ በጉልበትና በገንዘብ የበኩሉን ድርሻ ሊወጣ ይገባል ሲሉ ኢ/ር ማስተዋል አበበ  ጥሪ አቅርበዋል።

"የአኀት አብያተ ክርክቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ" የፓናል ውይይት ዘገባ ክፍል ፫ ሐምሌ ፫/፳፻፲፰ ዓ.ም የአኀት አብያተ ክርክቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ በሚል መሪ ቃል የፓናል ውይይት ግንቦት ፳፱/፳፻፲፰ ዓ.ም ተካሄዶ የነበረ ሲሆን በውይይቱም የሚክትሉተ ሦስት ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል። ፩ኛ - የአኀት አብያተ ክርስቲያናት የአገልግሎት ዕቅድ ዝግጅትና ትግበራ ተሞክሮ - በመ/ር ዳንኤል ሰይፈ ሚካኤል በመንበረ ፓትርያሪክ ጠ/ቤ/ክ ጥናት፣ ምርምርና መረጃ መምሪያ ኀላፊ እና የቅ/ሲኖዶስ ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ኀላፊ እንዲሁም የሊቃውንት ጉባኤ አባል ፪ኛ - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት፣ ትግበራ፣ ክትትልና ግምገማ ከትናንት እስከ ዛሬ - በመ/ር ባሕረ ጥበባት ሙጨ ፫ኛ - የቤተ ክርስቲያን የዕቅድ ዝግጅት ትግበራና የማኅበረ ቅዱሳን ድርሻ - በዶ/ር በሪሁን ተፈራ የማኅበረ ቅዱሳን የሕዝብ ግንኙነትና ትብብር አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ ጽሑፎችና አጠቃላይ ውይይቱ በሦስት ክፍል የቀረበ ሲሆን የነበረው የማጠቃለያ ውይይት ሦስተኛው ክፍል እንደ ሚከተለው ቀርቧል፡፡ https://youtu.be/x3hRmh2hDPY?si=UpIKdQymapn-yg-I

ዜና ገዳማት

ኑ ! ስደታቸው በሰንበትና በክረምት ለሆነባቸው እንድረስላቸው። ---***--- ለአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ወደ መርሐግብሩ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ
ኑ ! ስደታቸው በሰንበትና በክረምት ለሆነባቸው እንድረስላቸው። ---***--- ለአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን አስቸኳይ ሰብአዊ ድጋፍ የማሰባሰቢያ መርሐ ግብር   ወደ መርሐግብሩ ለመግባት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ። https://zoom.us/j/93407133345 ድጋፍ ለማድረግ ፡- 1.   Mahibere Kidusan in Europa e.V. IBAN: DE14 3704 0044 0307 8037 00 BIC: COBADEFFXXX Reason of payment – 007   2.   Mahibere Kidusan in UK Banking - NatWest Sort Code - 60 12 51 Acc. No - 364 25 591 Reason of Payment: 007   3.   በስዊድን ለምትገኙ፡- ACCOUNT NUMBER - 9960 3421234653 BIC - NDEASESS IBAN - SE15 9500 0099 6034 2123 4653 ACCOUNT HOLDER - MAHIBERE KIDUSAN I SVERIGE NORDEA BANK Reason of Payment: 007   4.   በኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000309803648 በአቢሲኒያ ባንክ 37235458 በአሐዱ ባንክ 0025393810901

ለበለጠ መረጃ፡- በአካል 5 ኪሎ ማኅበረ ቅዱሳን ሕንጻ 1ኛ ወለል         ወይም ·  በስልክ.ቁ፡- +251 921803238 ·  በኢሜል፡- yagelgilotber@eotcmk.org ·  በቴሌግራም፡- @Zeyklekulu   ·  WhatsApp:- +251 91 352 8494       · ለመመዝገብና አገልግሎትን ለማግኘት :- 👇 👇 👇 https://forms.gle/CgYYC5gX6oxd3HGS7                          ዘመነ ክረምትን በአገልግሎት በር!