cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

DW Amharic

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
42 341
Obunachilar
+3124 soatlar
+3347 kunlar
+1 46330 kunlar
Postlar arxiv
https://p.dw.com/p/4fQzb?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
Hammasini ko'rsatish...
https://p.dw.com/p/4fQns?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
Hammasini ko'rsatish...
https://p.dw.com/p/4fR0y?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
Hammasini ko'rsatish...
https://p.dw.com/p/4fRJK?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
Hammasini ko'rsatish...
https://p.dw.com/p/4fQm1?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
Hammasini ko'rsatish...
https://p.dw.com/p/4fR2d?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
Hammasini ko'rsatish...
ሶማሌላንድ የበርበራ ወደብ የኢትዮጵያን 30 በመቶ ጭነት እንዲያስተናግድ ትፈልጋለች ኤኮኖሚኢትዮጵያ Eshete Bekeleከ የተባበሩት ዓረብ ኤሚሬቶች ንብረት የሆነው ዱባይ ወርልድ ኩባንያ የሚያስተዳድረው የበርበራ ወደብ የኢትዮጵያን 30 በመቶ ጭነት እንዲያስተናግድ የሶማሌላንድ ባለሥልጣናት አቅደዋል። ለዚህም የወደብ አጠቃቀም እና የጉምሩክ ሥርዓቶችን የተመለከተ ሥምምነት በኢትዮጵያ እና በሶማሌላንድ መካከል መፈረም አለበት። ሥምምቱ በሚቀጥሉት 60 ቀናት ሊፈረም እንደሚችል የሶማሌላንድ የወደቦች አስተዳደር ባለሥልጣን ኃላፊ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። https://p.dw.com/p/4fP5U?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
Hammasini ko'rsatish...
ኢትዮጵያውያን ቲክቶከሮች ስለቲክ ቶክ መታገድ ምን ይላሉ? ፀሀይ ጫኔ የአሜሪካ የተወካዮች ምክር ቤት ቲክ ቶክ ከቻይናው ኩባንያ ባይትዳንስ እጅ እስካልወጣ ድረስ በሀገሪቱ ውስጥ እገዳ ለመጣል የሚያስችል ረቂቅ ህግ ያለፈው ቅዳሜ አጽድቋል።ያ ለመሆኑ ቲክ ቶክ ቢታገድ በይዘት ፈጣሪዎች እና በተጠቃሚዎች ላይ ምን ተፅዕኖ ያሳድራል? https://p.dw.com/p/4fM0x?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
Hammasini ko'rsatish...
በአማራ ክልል የእርዳታ ፈላጊዎች ቁጥር ወደ 2.5 ሚሊዮን ማሻቀቡ መንግስት አጠቃላይ በአማራ ክልል በችግር ላይ ለሚገኙ ነዋሪዎች በየወሩ ከ2 .2ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደሚያደርግም የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ፕሮግራም ማስተባበሪያ ኮሚሽን አስታወቀ ፡፡ https://p.dw.com/p/4fOPp?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
Hammasini ko'rsatish...
የባህላዊ እሴቶች ሚና ለሰላም "ሃሳባችንን እንደ ኋላ ቀር የማየት አባዜ ሰፍኗል፡፡ ትውልዱ ጋር አውቃለሁ ባይነት ከፋ፡፡ ይህ ደግሞ አይሆንም፡፡ አሁንም ላለው ችግር እኛ የምንለው ተቀባይነት አጣ እንጂ ከመናገር ሀሳብ ከመስጠት ታቅበን አናውቅም” https://p.dw.com/p/4fNtv?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
Hammasini ko'rsatish...
ባህላዊ እሴቶች ሚና ለሰላም "ሃሳባችንን እንደ ኋላ ቀር የማየት አባዜ ሰፍኗል፡፡ ትውልዱ ጋር አውቃለሁ ባይነት ከፋ፡፡ ይህ ደግሞ አይሆንም፡፡ አሁንም ላለው ችግር እኛ የምንለው ተቀባይነት አጣ እንጂ ከመናገር ሀሳብ ከመስጠት ታቅበን አናውቅም” https://p.dw.com/p/4fNtv?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
Hammasini ko'rsatish...
የትግራይ ተፈናቃዮች መመለስ በአማራ ክልል በኩል ጥያቄ በሚነሳባቸው አካባቢዎች የተመሰረቱ ሕገወጥ አስተዳደሮቹ ፈርሰው ተፈናቃዮች ወደ ቀዬአቸው የሚመለሱበት ምቹ ሁኔታ ሊፈጠር፣ አዳዲስ ሰፋሪዎች ከያዙት ቦታ ሊወጡ ከፌደራሉ መንግስት ጋር በነበረ ውይይት መግባባት ላይ መደረሱ ጀነራል ታደሰ ወረደ ተናግሯል። https://p.dw.com/p/4fOsk?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
Hammasini ko'rsatish...
"አስቸኳይ መፍትሔ የሚሹ" የመብት ጥሰቶች ከ 52 ደቂቃዎች በፊትከ 52 ደቂቃዎች በፊት በምስራቅ ወለጋ ዞን ሰቡሲሬ ወረዳ ሞቶ ቀበሌ ሚያዚያ 6 እና 7 ቀን 2016 ዓ.ም 14 የአካባቢው ነዋሪዎች በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች መገደላቸውን እንዲሁም በምዕራብ አርሲ ዞን ታጣቂዎች በሰዎች ላይ ግድያ፣ እገታ እና የአካል ጉዳት መፈፀማቸውን ገልጾ፤ 5 ሰዎች በዚሁ ዞን በታጣቂዎች መገደላቸውን ኢሰመጉ አስታውቋል። https://p.dw.com/p/4fOfE?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
Hammasini ko'rsatish...
DW Amharic የሚያዝያ 23 ቀን 2016 የዓለም ዜና የአውሮፓ ኅብረት ለኢትዮጵያውያን የቪዛ አሰጣጥ ሒደት እንዲጠብቅ ያሳለፈውን ውሳኔ እንዲያጤን ኢትዮጵያ ጠየቀች። የአፍሪካ ኅብረት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንቶች 6 ሚሊዮን ዶላር ለማጭበርበር የተደረገ ሙከራ ማክሸፉን አስታወቀ። ከ7 ሚሊዮን በላይ ደቡብ ሱዳናውያን የምግብ ዋስትና እጦት ሊገጥማቸው እንደሚችል ተመድ አስጠነቀቀ። እስራኤል በጋዛ ወደምትገኘው ራፋ ያቀደችውን ወታደራዊ ዘመቻ አሜሪካ አሁንም እንደምትቃወም ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ገለጹ። ሩሲያ በዩክሬን ጦርነት የማረከቻቸውን የምራባውያን የጦር መሣሪያዎች፣ ብረት ለበስ ተሽከርካሪዎች እና ወታደራዊ ሠነዶች በሞስኮ ለዕይታ አቀረበች። https://p.dw.com/p/4fP3o?maca=amh-RED-Telegram-dwcom አስተያየት ለመስጠት ይኽን ቦት ይጠቀሙ 👉🏾 @dwamharicbot
Hammasini ko'rsatish...
01:43
Video unavailableShow in Telegram
የአዲስ አበባ ጎርፍ ያጠፋው ህይወት አዲስ አበባ ዉስጥ ባለፈዉ ዕሁድ ከእኩለ ለሌት ጀምሮ የጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለዉ ጎርፉ በትንሽ ግምት 13 ሰዎች ወሰደ።አንዳድ የዓይን ምስክሮች የሟቾቹ ቁጥር 14 ነዉ ይላሉ።ከጎርፍ አደጋው የተረፉ እንዳሉት ጎርፉ ድንገት የደረሰዉ ጎርፍ የወሰዳቸዉ ሰዎች ሰዎች ጎዳና ላይ የሚያድሩ ችግረኞች ነበሩ።የዓይን ምስክሮቹ እንዳሉት በተኙበት ከአጠገባቸዉ በጎርፍ ከተወሰዱት ሰዎች እስካሁን የተገኘዉ የ8ቱ አስከሬን ብቻ ነዉ።(የቪዲዮ ዘገባ በስዩም ጌቱ)
Hammasini ko'rsatish...
https://p.dw.com/p/4fMSS ?maca=amh-RED-Telegram-dwcom @dwamharicbot
Hammasini ko'rsatish...
ሶማሌላንድ እና ኢትዮጵያ በሁለት ወራት ገደማ የመጨረሻውን ሥምምነት ይፈራረማሉ ተብሎ ይጠበቃል ከ 26 ደቂቃዎች በፊትከ 26 ደቂቃዎች በፊት ለሶማሌላንድ እውቅና ለኢትዮጵያ የባሕር ኃይል የጦር ሠፈር በኪራይ የሚሰጠው ሥምምነት በሁለት ወራት ገደማ ይፈረማል ተብሎ እንደሚጠበቅ የሶማሌላንድ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ትብብር ሚኒስትር ኢሳ ካይድ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል። ኢትዮጵያ ለባሕር ኃይል የጦር ሠፈር ልትከራይ የምትችላቸው ሦስት አማራጭ ቦታዎች መለየታቸውን ሚኒስትሩ ገልጸዋል። https://p.dw.com/p/4fJoS
Hammasini ko'rsatish...
የዓለም ዜና፤ የሚያዝያ 20 ቀን 2016 ዓ.ም ሰኞ አርስተ ዜና --154 የትግራይ ተወላጅ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ከጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ በእሥር ላይ መሆናቸውን ቅድሚያ ለሰብዓዊነት ኢትዮጵያ የተባለ የሲቪክ ድርጅት አስታወቀ። --የአውሮጳ ህብረት ለኢትዮጵያውያን ዜጎች የሚሰጠውን ቪዛ ለመገደብ መወሰኑን ዛሬ አስታወቀ። --በኬንያ ስምጥ ሸለቆ ከተማ አቅራቢያ የሚገኝ አንድ ግድብ ተንዶ በትንሹ 42 ሰዎች ሞቱ። በኬንያ ሰሞኑን የዘነበዉ ከባድ ዝናብ በተለይ መዲና ናይሮቢ ላይ በርካቶችን አፈናቅሏል። --የቡርኪናፋሶ ወታደራዊ ጁንታ የዶቼ ቬሌን ራድዮ ጨምሮ የተለያዩ ዓለም አቀፍ የዜና ማሰራጫዎችን እና ጋዜጦችን ማገዱ አስታወቀ። ወታደራዊዉ ጁንታ ይህን ያደረገዉ ሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅት ሂዉማን ራይትስ ዎች ያወጣዉን መግለጫ ለምን ዘገባችሁ በሚል ነዉ። --የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን የእስራኤል እና የሃማስ ጦርነት ሲያበቃ፤ ከአረብ ሀገራት መሪዎች ጋር በጋዛ ጉዳይ ላይ ለመምከር በሳዑዲ ዋና ከተማ ሪያድ መግባታቸዉ ተዘገበ። ዝርዝሩን ያድምጡ! https://p.dw.com/p/4fJoV
Hammasini ko'rsatish...
https://p.dw.com/p/4fIfq ?maca=amh-RED-Telegram-dwcom 👉🏾 @dwamharicbot
Hammasini ko'rsatish...
የተወደዳችሁ የዶቹ ቬለ አድማጮች እና ተከታታዮች የሚያዝያ 21ቀን 2016 ዓ.ም. ስርጭታችን ከጥቂት ጊዜ በኋላ በፌስቡክ በቀጥታ ይደመጣል። ለዕለቱ ከተጠናቀሩ ዘገባዎች መካከል፤ ሶማሌ ላንድ እና ኢትዮጵያ የተፈራረሙት የመግባቢያ ስምምነት በሁለት ወራት ውስጥ ተግባራዊ ሊሆን እንደሚችል የሶማሌ ላንድ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር መግለጹ፤ የአላማጣ ተፈናቃዮች ከሰፈሩበት እንዲለቁ መደረጋቸው ፤ የልጅነት ልምሻ ወይም ፖሊዮ ትግራይ ክልል ውስጥ በወረርሽኝ መልክ መቀስቀሱ ፤ የጎርፍ አደጋ የሚያሰጋቸው የአፋር ፣ የአማራ ፣ የኦሮሚያ ፣ የሶማሌ እና ደቡብ ክልሎች፤ ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ሐይቅ ዓሳ እየተሰገረ ስለመሆኑ፣ ሳምንታዊው ማኅደረ ዜና መፍትሄ ያጣውን የሱዳን ጦርነት ይቃኛል፤ የስፖርት ዝግጅታችንም በሳምንቱ የመጨረሻ ቀናት የተከናወኑ ዋና ዋና ስፖርታዊ ክንውኖችን አሰባስቧል። የዓለም ዜናን ጨምሮ ሁሉንም በሰዓቱ ተገንታችሁ እንድትከታተሉን ከወዲሁ የአክብሮት ግብዣችን ይድረሳችሁ። የዶቼ ቬለን የየዕለቱን የዜና እና የዜና መጽሔት ጥንቅሮች ከዩቲዩብ ቻናላችን ማግኘት እንደምትችሉ እናስታውሳችሁ። ትክክለኛው የዶይቼ ቬለ የዩቲዩብ ቻናል ከታች ያለው ሲሆን እስከዛሬ ሰብስክራብ ያላደረጋችሁ በማድረግ በዩቲዩብም ቤተሰባችን ሁኑ። ለሌሎችም ማጋራት አትርሱ። እናመሰግናለን። https://www.youtube.com/@dwamharic/videos
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
የጀርመን ዐቃቢያነ ህግ በሁለት የዩክሬን ወታደሮች ላይ የቢላዋ ጥቃት ፈጽሟል ባሉት አንድ ሩስያዊ ላይ ምርመራ መጀመራቸውን አስታወቁ ። በጥቃቱ የ36 ዓመቱ ወታደር ወዲያው ህይወቱ ሲያልፍ ሌላኛው የ26 ዓመት ወታደር በጸና ቆስሎ ወደ ሆስፒታል ከተወሰደ በኋላ ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል። ሩስያዊው በዩክሬናውያን ወታደሮች ላይ ጥቃቱን ያደረሰው ትናንት እሁድ ደቡባዊ ጀርመን ውስጥ በምትገኘው ሙርናው ከተማ ከገበያ ማዕከል አጠገብ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል። በጥቃቱ የተጠረጠረው የ57 ዓመቱ ሩሲያዊ በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ በቁጥጥር ሥር በመዋሉን ፖሊስ አስታውቋል። ጥቃት አድራሹ ግለሰብ በቁጥጥር ስር ከዋለ በኋላ ፖለቲካዊ ተልዕኮ ይኑረው አይኑረው ምርመራ መጀመራቸውን ሙኒክ የሚገኘው ዋና ዐቃቢ ህግ አመልክቷል። በደቡብ ጀርመን የዩክሬን ቆንስላ የወታደሮችን መደብ በመለየት ከቤተሰቦቻቸው ጋር ግንኙነት ማድረግ መጀመሩን ገልጧል። የዩክሬን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲሚትሮ ኩሌባ በሙኒክ የሚገኘው ቆንስላ ጉዳዩን በቅርበት እንዲከታተል እና ከጀርመን የህግ አካላት ጋር በትብብር እንዲሰሩ መመሪያ መስጠታቸው ተጠቁሟል። የጀርመን መንግስ ቃል አቃባይ ስለ ጉዳዩ ተጠይቆ ፖሊስ በምርመራ ላይ መሆኑን በመጥቀስ ተጨማሪ መረጃ ከመስጠት ተቆጥቧል። ሩሲያ ዩክሬንን ከወረረች በኋላ ከአንድ ሚሊዮን በላይ የሀገሪቱ ዜጎች በጀርመን ጥገኝነት ጠይቀዋል። በርካታ ሩሲያውያን ስደተኞችም ጀርመን ውስጥ ይኖራሉ።
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
ከታላቁ ህዳሴ ግድብ በቀን እስከ 250 ኪሎ ግራም የሚደርስ የዓሳ ምርት እንደሚገኝ ተገለጸ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ሐይቅ ለበርካታ ወጣቶች የስራ ዕድል መፍጠሩ ተገልጿል። ግድቡ ውሀ መያዝ ከጀመረ ወዲህ በተለይም ለዓሳ ማስገር ምቹ መሆኑን በአካባቢው በዓሣ ማስገር ስራ ላይ የተሰማሩ ወጣቶች ይናገራሉ፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከአንድ መቶ በላይ ወጣቶች በዚሁ ስራ መስክ እንዲሰማሩ በማህበር ማደራጀቱን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ አስታውቋል፡፡ የቢሮው ኃላፊ አቶ ባበክር ሀሊፋ በ8 ወራት ውስጥ 1729 ቶን ዓሳ ምርት ከህዳሴ ግድብ መገኘቱን ገልጸዋል፡፡ የሰላም ተመላሾች የተባሉ ከዚህ ቀደም ታጥቆ ይንቀሳቀሱ የነበሩ ሰዎች ጨምሮ ወጣቶች በሁለት ማህበራት ተደራጅተው ወደ ስራ መግባታቸውን ጽ/ቤቱ አመልክቷል። በአሳ ማስገር ስራ ከተሰማሩ መካከል ወጣት ብርሀኑ እና ወጣት ኢትማን መሐመድ በአሁኑ ወቅት በህዳሴ ግድብ በተፈጠረው ሐይቅ ላይ ዓሳ በማስገር ስራ ተሰማርተው እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ በግደቡ ዳርቻ በሚሰሩት የዓሳ ማስገር ስራ በቀን ከ2 እስከ 3 ኮንታል ዓሳ እንደሚያገኙም ጠቁመዋል። ግድቡ ውሀ መያዝ ከጀመረ ወዲህ በአነስተኛ የሰው ሐይል ዓሳ በማስገር ለአካባቢው ገበያ ሲያቆርቡ ቆይተዋል፡፡ በአካባቢው የዓሳ ማስገር ስራውን ማህበሰረብ ዓቀም ለማድረግና ለማሻሻል ዘመናዊ ጅልባዎች እንደሚያስልጉም ወጣቶቹ ለአሶሳው ወኪላችን ነጋሳ ደሳለኝ ነግረዉታል። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የግብርና ቢሮ በበኩሉ በግድቡ ላይ በተገነባው ግዙፍ የዓሳ ምርት ላይ ለማሰማራት ከ2 መቶ በላይ ወጣቶችን ማደራጀቱን አመልክቷል፡፡ የምሽቱ የዜና መጽሄታችን ዝርዝር ዘገባ ይዟል
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
በሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ ከተማ ወጣ ባለ የመንገድ ዳር የተጠመደ ቦምብ ፈንድቶ ስድስት የሆርሙርድ ቴሌኮም ኩባንያ ሰራተኞች ተገደሉ። ጋራስባሌይ በተሰኘት ግዛት በተፈጸመው ጥቃት ሰራተኞቹ መገደላቸውን ኩባንያው አረጋግጧል። ለጥቃቱ እስካሁን በይፋ ኃላፊነት የወሰደ ወገን የለም። ነገር ግን ከአልቃኢዳ ጋር ግንኙነት እንዳለው የሚነገርለት የሽብር ቡድን አልሸባብ በተደጋጋሚ ሲደርሱ ለነበሩ ጥቃቶች ኃላፊነት ሲወስድ ቆይቷል። በአሁኑ ጥቃት የተገደሉት የቴሌኮም ሰራተኞች ጥቃቱ ሲደርስ በጉዞ ላይ አልያም በስራ ላይ ይሁኑ ተለይቶ የተባለ ነገር የለም። የሶማሊያ መንግስት ባለስልጣናትም ስለጥቃቱ ያሉት ነገር ስለመኖሩ ዘገባው ያለው ነገር የለም። ሃርሙድ የቴሌኮም ኩባንያ በሶማልያ ግዙፉ የግል ኩባንያ ሲሆን በርካታ ሰራተኞችን ከሚያስተዳድሩ የግል ኩባንያዎች ከቀዳሚዎቹ ይጠቀሳል።
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
በኬንያ ስምጥ ሸለቆ ውስጥ በምትገኝ አንዲት ከተማ አቅራቢያ የሚገኝ ግድብ ተንዶ በትንሹ ለ42 ሰዎች ህልፈት ምክንያት ሆነ። ኃይለኛ ዝናብ ያስከተለው ጎርፍ ለግድቡ መናድ ምክንያት ሲሆን በርካታ ቤቶችን ጠራርጎ መውሰዱን የአካባቢው ባለስልጣናት ዐስታውቀዋል። በአደጋው በርካታ መንገዶች ተቆራርጠዋል፤ በህይወት የተረፉ ሰዎች ከተገኙ በሚልም የህይወት አድን ሰራተኞች በአካባቢው መሰማራታቸውን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዘግቧል። የኑኩሩ ግዛት አስተዳዳሪ ሱዛን ኪሂካ እንዳሉት 42 ሰዎች መሞታቸው ተረጋግጧል። ነገር ግን አሁንም ድረስ በደለል ተውጠው ገና ያልተገኙ በርካታ ሰዎች በመኖራቸው የሟቾች ቁጥር በእጅጉ ሊያሻቅብ ይችላል። ኤል ኒኖ ያስከተለው የአየር ንብረት ለውጥ በኬንያ በዚህ ዓመት በመጋቢት እና ሚያዝያ ወራት ከተለመደው የዝናብ መጠን በላይ እንዲዘንብ አስገድዷል። ኃይለኛ ዝናብ ባስተናገዱ አካባቢዎች በተከሰቱ የጎርፍ መጥለቅለቅ አደጋዎች የሟቾችን ቁጥር ከ140 በላይ አድርሷል፤ ከ130 ሺ በላይ ሰዎችን ከቤት ንብረታቸው አፈናቅሏል። የጎርፍ መጥለቅለቁ በበርካታ አካባቢዎች መንገዶችን ጨምሮ በመሰረተ ልማቶች ላይም ብርቱ ጉዳት ማድረሱን ነው ዘገባው ያመለከተው። ይህንኑ ተከትሎ በእረፍት ላይ የነበሩ ትምህርት ቤቶች መከፈት ከሚገባቸው ቀን እንዲያስተላልፉ የሀገሪቱ የትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል።
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
የአውሮጳ ህብረት ለኢትዮጵያውያን ዜጎች የሚሰጠውን ቪዛ ለመገደብ መወሰኑን አስታወቀ። የኢትዮጵያ መንግስት ህገ ወጥ ስደተኞችን ለመቀበል ከህብረቱ ጋር መተባበር ባለመቻሉ የቪዛ ገደብ እንዲጥል ምክንያት እንደሆነው የአውሮጳ ህብረት ምክር ቤት ዛሬ ሰኞ ባወጣው መግለጫ አመልክቷል። የህብረቱ እርምጃ የተሰማው በጦርነት ከተመሰቃቀሉ የአፍሪቃ ሃገራት በህገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች አማካኝነት የሜድትራንያን ባህርን አቋርጠው የሚመጡትን ስደተኞች ለማስቆም ብርቱ ጥረት እያደረገ ባለበት ወቅት ነው። በህገ ወጥ መንገድ ወደ ህብረቱ አባል ሃገራት የገቡ እና መመለስ ያለባቸውን ዜጎቿን እንድትቀበል በትብብር ለመስራት ሲደረግ የነበረውን ግምገማ ማጠናቀቁን የገለጸው የአውሮፓ ህብረት በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ ትብብር «በቂ አይደለም » ብሏል። የአውሮጳ ህግ አውጪዎች የተሻሻለውን የፍልሰት ስርዓት ባለፈው ወር መጨረሻ ነበር ያጸደቁት ። የአውሮፓ ህብረት የፖለቲካ ማእከል እንዳለው የፍልሰት ስርዓት ማሻሻያው ያለ ህጋዊ ሰነድ ወደ ህብረቱ የሚገቡ የስደተኞችን ቁጥር ይቀንሳል።
Hammasini ko'rsatish...
Photo unavailableShow in Telegram
በጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ አነሳሽነት«ጎዳናዎችን ጽዱ ለማድረግ» ገንዘብ የማሰባሰብ መርኃ ግብር በይፋ ተጀምሯል። በማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች እየተሰራጩ ያሉ መረጃዎች እንደሚያሳዩት የመንግስት ባለስልጣናትን ጨምሮ በርካቶች የገንዘብ ድጋፍ ያደረጉባቸውን የባንክ ማስረጃ እያጋሩ ነው። መዲናዪቱ አዲስ አበባን ጨምሮ ዋና ዋና የክልል ከተሞችም ይሁኑ ሌሎች የጎዳናም ይሁን የውስጥ ለውስጥ መንገዶች በተለያየ መጠን የሚገለጽ የንጽህና ችግር እንዳለባቸው ሲነገር ይሰማል። አንዳንድ አካባቢዎች ለጤና ጠንቅ በሚሆን ደረጃ የከፋ መጥፎ ጠረን ወይም ሽታ የሚወጣባቸው አካባቢዎች ጥቂት አይደሉም ። በየመንገዱ ቆሻሻ መጣልም ያን ያህልም ነውር ያልሆነባቸው አካባቢዎች በርካቶች ናቸው። ከዚህ ሁሉ የከፋው ግን በከተሞች የመጸዳጃ ቤቶች አለመኖር ሰው በየመንገድ ዳር እስከመጸዳዳት የደረሰባቸው እና ከዘመኑ ጋር የማይሄዱ ሰብአዊ ድርጊቶች ሲታይ ችግሩ ምን ያህል አሳሳቢ እንደሆነ በግልጽ ያሳያል። የጎዳናም ይሆን የየአካባቢ ንጽህናን ለማስጠበቅ ጠቅላይ ሚንስትሩ ከሰሞኑ ያስጀመሩትን መርሃ ግብር ካለው ችግር አንጻር በበጎ ተመልክተው ድጋፋቸውን የሰጡ በርካቶች የመሆናቸውን ያህል ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የንጽህና ችግር እንዲህ በዘመቻ ብቻ መፍትሄ ያስገኛል ወይ የሚለው ጥያቄም መነሳቱ አይቀርም። እንደሁ ከሰሞኑ ጠቅላይ ሚንስትሩ ያስጀመሩትን «የጽዱ ጎዳና» መርሃ ግብር እንዴት አገኛችሁት ? በእርግጥ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው በተለይ የጎዳና ጽዳት ችግር እንዲህ በዘመቻ ብቻ ይፈታል ብላችሁ ታስባላችሁ? ካልሆነስ ሌላ ምን አማራጭ ሃሳብ ታቀርባላችሁ ? ሃሳባችሁን አጋሩን ተወያዩበትም። ምስል ጠቅላይ ሚንስትር ጽ/ቤት
Hammasini ko'rsatish...