es
Feedback
DW Amharic

DW Amharic

Ir al canal en Telegram

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram DW Amharic

El canal DW Amharic (@dw_amharic) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 54 903 suscriptores, ocupando la posición 4 905 en la categoría Noticias y medios y el puesto 582 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 54 903 suscriptores.

Según los últimos datos del 29 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 123, y en las últimas 24 horas de -7, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: Verificado (confirmado oficialmente por Telegram)
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 7.91%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 5.57% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 340 visualizaciones. En el primer día suele acumular 3 056 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 0.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 30 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Noticias y medios.

54 903
Suscriptores
-724 horas
+417 días
+12330 días
Archivo de publicaciones
አዲስ አበባ-የኢትዮጵያ ፖሊስ «የሰዎች አዘዋዋሪዎች መሪ» ያለዉን ግለሰብ መያዙን አስታወቀ የኢትዮጵያ የፌደራል ፖሊስ ከማላዊ ፖሊስና ከኢንተርፖል ጋር በመተባበር በኢትዮጵያዉን ወጣቶች ላይ «ከባድ
አዲስ አበባ-የኢትዮጵያ ፖሊስ «የሰዎች አዘዋዋሪዎች መሪ» ያለዉን ግለሰብ መያዙን አስታወቀ የኢትዮጵያ የፌደራል ፖሊስ ከማላዊ ፖሊስና ከኢንተርፖል ጋር በመተባበር በኢትዮጵያዉን ወጣቶች ላይ «ከባድ ኢሰብአዊ ድርጊት ሲፈጽም ነበር» ያለዉን ተጠርጣሪ መያዙን አስታወቀ።ፖሊስ ዛሬ በማሕበራዊ መገናኛ ዘዴ ባሰራጨዉ ዘገባ እንዳለዉ አድነዉ ባሻዉ ዉዳሞ የተባለዉ ተጠርጣሪ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከሐድያና ከከንባታ ዞኖች በርካታ ወጣቶችን እያታለለ ወደ ደቡብ አፍሪቃ ሲያሻግር ነበር።ፖሊስ «አደገኛ» ያለዉ አድነዉ ባሻዉ ዉዳሞና ተባባሪዎቹ፣ ወጣቶችን በኬንያ በኩል የተለያዩ የደቡባዊ አፍሪቃ ሐገራትን አቋርጠዉ ደቡብ አፍሪቃ ለማስገባት ከእያንዳዳቸዉ ከ600ሺሕ እስከ 800 ሺሕ ብር ይቀበሉ እንደነበር በመረጃ ማረጋገጡን ፖሊስ አስታዉቋል።በዘገባዉ መሠረት፣ ተጓዦቹ ጋንቦ ከተባለዉ ጫካ ጀምሮ በየደረሱበት በረሐብና ዉሐ ጥም ይሰቃያሉ።ተጠርጣሪዎቹ፣ ወጣቶቹን በሕገ-ወጥ መንገድ ናይሮቢ ከተማ ካስገቡ በኋላ፣« በአንድ ክፍል ውስጥ በማጎር፣ ከቤተሰቦቻቸው ተጨማሪ ገንዘብ እንዲያስልኩ ያስገድዳሉ፤ ገንዘብ ማስላክ ያልቻሉትን በኤሌክትሪክ ንዝረት ጭምር እያሰቃዩ» እስከ 100 ሺሕ ብር የሚደርስ ተጨማሪ ገንዘብ ያስከፍላሉም።የኢትዮጵያ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ለመያዝ ከ2015 ጀምሮ ከኢንተርፖል ጋር በመተባበር ሲከታተል እንደነበረ አስታዉቋል።የማላዊ ፖሊስ ዋነኛዉን ተጠርጣሪ አድነዉ ባሻዉ ዉዳሞን ይዞ ትናንት ለኢትዮጵያ ፖሊስ ማስረከቡን የኢትዮጵያ ፈደራል ፖሊስ አስታዉቋል።

አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ በምታደርገው ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ ወደ “ጸረ-ኢትዮጵያ ጥምረት” እንዳጋደለች የሚጠቁሙ ዘገባዎችን “ሐሰተኛና አሳሳች” በማለት በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የመካከለኛው
አሜሪካ በአፍሪካ ቀንድ በምታደርገው ዲፕሎማሲያዊ እንቅስቃሴ ወደ “ጸረ-ኢትዮጵያ ጥምረት” እንዳጋደለች የሚጠቁሙ ዘገባዎችን “ሐሰተኛና አሳሳች” በማለት በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የመካከለኛው ምሥራቅና አፍሪካ ጉዳዮች ከፍተኛ አማካሪ ማሳድ ቡሎስ አጣጣሉ። ቡሎስ የትኛው መገናኛ ብዙኃን እንዲህ ዐይነት ዘገባ እንዳቀረበ በግልጽ ባይጠቅሱም “የተሳሳተና አላስፈላጊ ውጥረት የሚፈጥር” እንደሆነ ተችተዋል። ቡሎስ “ዩናይትድ ስቴትስ ቅድሚያ የሚሰጣቸውን የጋራ ጉዳዮች ወደፊት ለማራመድ ከኢትዮጵያ እንዲሁም በመላው የአፍሪካ ቀንድ እና ሰፊው የቀይ ባሕር አካባቢ ከሚገኙ ሀገራት ሁሉ ጋር አብራ ትሠራለች” ሲሉ በኤክስ ባሠፈሩት ጽሁፍ ገልጸዋል። የአሜሪካ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አማች የሆኑት ማሳድ ቡሎስ ከአንድ ሣምንት ገደማ በፊት በካይሮ ከግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አብደልላቲ፣ ከኤርትራ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳሌሕ እና ከሶማሊያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አብዲሳላም አብዲ አሊ ጋር ተገናኝተው ነበር። ከሦስቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር ባደረጉት ውይይት አገራቱ ከአሜሪካ ጋር ካላቸው ግንኙነት ባሻገር የአፍሪካ ቀንድን የተመለከቱ ጉዳዮች ትኩረት እንደተሰጣቸው ቡሎስ በኤክስ ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል። በቀጠናው ከፍተኛ ውጥረት በተፈጠረበት ወቅት ከሦስቱ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጋር በካይሮ ያደረጉት ውይይት ከፍተኛ ትኩረት ስቧል። ቡሎስ ግን አገራቸው የምትከተለው ዲፕሎማሲ “ተቀናቃኝ የሃገራት ጎራ የመፍጠርና ክፍፍልን ከማባባስ” ይልቅ ከሁሉም አጋሮች ጋር “ግጭትን በመከላከል ዘላቂ ሰላም እና ጸጥታ ማበረታታት” ላይ ያተኮረ እንደሆነ ተከላክለዋል። የዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ አሜሪካ ከኤርትራ ጋር የነበራትን ግንኙነት ለማረቅ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል።

የሐምሌ 22፣ 2018 ዓ/ም የቀጥታ ስርጭት ማስታወቂያ · ግድያና ጥቃትን የተመለከቱ የምርመራ ውጤቶች ትኩረት አግኝተዋልን? ሲል የሚጠይቀው ቀዳሚ ዘገባ ነው። · ከ90 ሺህ በላይ ተፈናቃዮች በ4 ጣ
የሐምሌ 22፣ 2018 ዓ/ም የቀጥታ ስርጭት ማስታወቂያ ·         ግድያና ጥቃትን የተመለከቱ የምርመራ ውጤቶች ትኩረት አግኝተዋልን? ሲል የሚጠይቀው ቀዳሚ ዘገባ ነው። ·         ከ90 ሺህ በላይ ተፈናቃዮች በ4 ጣቢያዎች ለብርቱ ዝናምና ጎርፍ ተጋልጠዋል መባሉ፤ ·         የኢትዮጵያ አየር መንገድ የዓመቱ ስኬቶች እና ያጋጠሙት ፈተናዎች፤ ·         IOM ምስራቅ አፍሪቃውያን በዓለም አቀፍ ወንጀል እንዲሳተፉ እየተገደዱ ነው ማለቱ ·         እንዲሁም የሰው ሠራሽ አደጋ በማጃንግ ዞን ጥብቅ ደን ላይ አደጋ ደቅኗል የሚሉ ዘገባዎች በቅደም ተከተል ይቀርባሉ።    ሳምንታዊዎቹ ከኤኮኖሚው ዓለም «የኢትዮጵያ ባለሥልጣናት ኩባንያዎች በካፒታል ገበያ እንዲያስመዘግቡ ግፊት እያደረጉ ነው» በሚል ርእስ እንዲሁም ሣይንስና ቴክኖሎጂ፦ «ዓለምን ሥጋት ላይ የጣለው በAI የሚፈፀም ጠለፋ እና ማጭበርበር» በሚል ትንታኔ ቀርቦበታል ። ሥርጭታችን በሳተላይት ለምትከታተሉ፣ በኢትዮ-ሳት ወይንም (NSS-12) በ10985,0 ሜጋ ኸርዝ፣ ሆሪዞንታል፣ DW-08 ላይም ማድመጥ ይቻላል ። ትራንስፖንደሩ፦ MEH01 ወይንም EAH01 ነው ። ፈልጉን ። በኢንተርኔት DW Amharic በተባለው መተግበሪያ በተንቀሳቃሽ ስልክ እና ታብሌትም ልትከታተሉን ትችላላችሁ ። በፌስ ቡክ DW Amharic ዝግጅታችን በቀጥታ ሲሰራጭ ማድመጥ አስተያየት መስጠትም ትችላላችሁ ።

...67 ቡድናትን የሚያስተናብረዉ ንቅናቄ እንዳስታወቀዉ የዩናይትድ ስቴትስና የሳዑዲ አረቢያ ጦር ኃይላት ዛሬ በኢራቅ ሰባት አዉራጃዎች ዉስጥ በከፈቱት ጥቃት 20 ተዋጊዎቹን ገድለዋል።ሌሎች 32 አቁስለዋል።ንቅናቄዉ የሟች ጓዶቹን ደም ለመበቀል የአሜሪካና የሳዑዲ አረቢያን ጥቅሞች ለማጥቃት ዝቷልም።ዘገቦች እንደጠቆሙት ንቅናቄዉ በኢራቅ፣ በኢራንና በአሜሪካኖች ድጋፍ እንደ ግሪጎሪያኑ አቆጣጠር በ2014 እስላማዊ መንግሥትን ለመዉጋት የተመሰረተ ነዉ።

የአሜሪካ እና የኢራን ጦርነት ሳዑዲ አረቢያንም ቀስ በቀስ እያስገባ ነዉ። ባለፈዉ ሳምንት በኢራን ይደገፋሉ ከሚባሉት ከየመን ሁቲዎች ጋር ስትቀጣቀጥ የነበረችዉ ሳዑዲ አረቢያ ዛሬ ደግሞ ከዩናይትድ ስ
የአሜሪካ እና የኢራን ጦርነት ሳዑዲ አረቢያንም ቀስ በቀስ እያስገባ ነዉ። ባለፈዉ ሳምንት በኢራን ይደገፋሉ ከሚባሉት ከየመን ሁቲዎች ጋር ስትቀጣቀጥ የነበረችዉ ሳዑዲ አረቢያ ዛሬ ደግሞ ከዩናይትድ ስቴትስ ጎን ተሰልፋ ኢራቅን ደብድባለች።የሪያድ ገዢዎች ጦራቸዉ አሜሪካኖችን ተከትሎ ኢራቅን ለመደብደቡ የሰጡት ምክንያት ከኢራን ጋር ግንኙነት አለዉ የሚባለዉ የኢራቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ኃይላት የተባለዉ ንቅናቄ ሳዑዲ አረቢያን በድሮን መትቷል የሚል ነዉ።67 ቡድናትን የሚያስተናብረዉ ንቅናቄ እንዳስታወቀዉ የዩናይትድ ስቴትስና የሳዑዲ አረቢያ ጦር ኃይላት ዛሬ በኢራቅ ሰባት አዉራጃዎች ዉስጥ በከፈቱት ጥቃት 20 ተዋጊዎቹን ገድለዋል።ሌሎች 32 አቁስለዋል።ንቅናቄዉ የሟች ጓዶቹን ደም ለመበቀል የአሜሪካና የሳዑዲ አረቢያን ጥቅሞች ለማጥቃት ዝቷል።ባግዳድ-የአሜሪካና የኢራን ዉጊያ አድማሱን እያሰፋ ነዉ ዩናይትድ ስቴትስ ከኢራን ጋር በገጠመችዉ ጦርነት ሳዑዲ አረቢያም ቀስ በቀስ እየገባችበት ነዉ።ባለፈዉ ሳምንት በኢራን ይደገፋሉ ከሚባሉት ከየመን ሁቲዎች ጋር ስትቀጣቀጥ የነበረችዉ ሳዑዲ አረቢያ ዛሬ ደግሞ ከዩናይትድ ስቴትስ ጎን ተሰልፋ ኢራቅን ደብድባለች።የሪያድ ገዢዎች ጦራቸዉ አሜሪካኖችን ተከትሎ ኢራቅን ለመደብደቡ የሰጡት ምክንያት ከኢራን ጋር ግንኙነት አለዉ የሚባለዉ የኢራቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ኃይላት የተባለዉ ንቅናቄ ሳዑዲ አረቢያን በድሮን መትቷል የሚል ነዉ።...

...የፊፋ ፕሬዝዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ ለ211 አባል ፌዴሬሽኖች በጻፉት እስከ የፊታችን መስከረም 9 ቀን 2019 ዓ/ም ድረስ የፊፋን እቅድ የሚደግፉ ከሆነ እያንዳንዳቸው 40 ሚሊዮን ዶላር እንደሚደርሳቸውን እና ከዚህ ውስጥ "የመጀመሪያ ክፍያውን 20 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያገኙ "ጠቅሰዋል፤ ተብሏል። ፈርመው የማይቀበሉት ግን አሁን ባለው ዓለም አቀፍ የክፍፍል ስርዓት መሠረት 2.7 ሚሊዮን ዶላር ብቻ ያገኛሉ።

የጀርመን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ኃላፊዎች ፊፋ (FIFA) የዓለም ዋንጫን ጨምሮ የውድድሮች ድርሻን ለግል ባለሀብቶች ለመሸጥ ያቀረበውን እቅድ ዛሬ (ረቡዕ) በጽኑ ኮነኑ። ሲናገሩ፦ "በአውሮፓ እግር ኳስ
የጀርመን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ኃላፊዎች ፊፋ (FIFA) የዓለም ዋንጫን ጨምሮ የውድድሮች ድርሻን ለግል ባለሀብቶች ለመሸጥ ያቀረበውን እቅድ ዛሬ (ረቡዕ) በጽኑ ኮነኑ። ሲናገሩ፦ "በአውሮፓ እግር ኳስ ውስጥ የሚገኙ በርካታ አካላት የፊፋን እቅድ በእግር ኳስ ላይ እንደተሰነዘረ ቀጥተኛ ጥቃት አድርገው እንደሚመለከቱት የጀርመን እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምክትል ፕሬዝዳንት እና የአውሮጳ እግር ኳስ ማሕበር ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ምክትል ፕሬዝዳንት ሀንስ ዮአኪም ኪከር ለተሰኘ የስፖርት መጽሔት ተናግረዋል። በአባል ማህበራት መካከል "ድንበር የመጣሱ" ሰፊ ስምምነት እንዳለ ከአህጉሪቱ የእግር ኳስ ማህበር ፕሬዚዳንትን ጨምሮ ከሌሎች ባለስልጣናት ጋር ከተነጋገሩ በኋላ መረዳታቸውን ዮአኪም ተናግረዋል። በዓለም ዋንጫው ስድስት የአውሮጳ ቡድኖች ሩብ ፍፃሜ ሲደርሱ ሦስቱ ደግሞ ግማሽ ፍፃሜ ገብተዋል። የአውሮጳ እግር ኳስ ማህበር እነዚህን የፊፋን ዕቅዶች በመቃወም አንድ ሆኖ ከተቆመ ትልቅ ተፅዕኖ ሊኖረው እንደሚችልም አመልክተዋል። ዓለማቀፉ የእግር ኳስ ማሕበር ፊፋ ትናንት ማክሰኞ እንዳለው ለፊፋ ከፍተኛ ገቢ የሚያስገኘውን የዓለም ዋንጫ ጨምሮ የውድድሮቹን የንግድ መብቶች ሽያጭ ከውድድሮች አደረጃጀት ጋር ለማጣመር (FFE) የተሰኘ ኢንተርፕራይዝ ለማቋቋም አልሟል። ኢንተርፕራይዙን ለግል ባለሀብቶች አነስተኛ የባለቤትነት ድርሻ ለመሸጥ ክፍት እንደሚሆን የጠቆመው ፊፋ የድራሻውም ዋጋ 20 ቢሊዮን ዶላር እንደሆነ ገልጿል።...

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የእርሻ ትራክተር ተገልብጦ የሦስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ አሥራ አራት ሰዎች ቆሰሉ ፡፡ አደጋው ትናንት የደረሰው በክልሉ ቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ በበቃ ቀበሌ
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል የእርሻ ትራክተር ተገልብጦ የሦስት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ አሥራ አራት ሰዎች ቆሰሉ ፡፡ አደጋው ትናንት የደረሰው በክልሉ ቤንች ሸኮ ዞን ደቡብ ቤንች ወረዳ በበቃ ቀበሌ አብይ 01 በተባለ መንደር ውስጥ ነው ፡፡ ትራክተሩ የተገለበጠው በተጎታች ጋሪ ላይ ሰዎችን ጭኖ በእርሻ ማሳ ውስጥ በመጓዝ ላይ ባለበት ወቅት መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኢንስፔክተር ደጀኔ አሰፋ ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል ፡፡ በክልሉ ከተለመደው ውጪ በትራክተር አደጋ ሲደርስ የመጀመሪያው መሆኑን የተናገሩት ኢንስፔክተሩ፡ ሐምሌ 21 ቀን 2018 ዓ.ም ከአርሻ ማሳ ወደየቤታቸው በመጓዝ ላይ እያሉ ምክንያቱ ባልታወቀ ትራክተሩ ተገልብጦ የሦስት ሰዎች ህይወት አልፏል ፡፡ በስምንት ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል ። በአደጋው ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች በሚዛን ቴፒ ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው እንደሚገኝ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል ፡፡ የአደጋው መንስኤ በትራፊክ ቴክኒክ መርማሪዎች በመጣራት ላይ እንደሚገኝም ጨምረው ገልጸዋል ፡፡

... የአይ ኦ ኤም ዋና ዳይሬክተር ኤሚ ፖፕ ትናንት ማክሰኞ ጄኔቫ ውስጥ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ "አሁን በርካታ መሰል ጉዳዮች በስፋት ሲከሰቱ እያየን ነው" ብለዋል። ዳይሬክተሩ አክለውም "ከ80 በላይ ከሚሆኑ ልዩ ልዩ ሀገራት የመጡ ተጎጂዎች ወደነዚህ የማጭበርበር ድርጊቶች በሕገ-ወጥ መንገድ እየተነዱ " ይገኛሉ። "ብዙ ጊዜ እንግሊዝኛ በጣም በጥሩ ሁኔታ የሚናገሩ፣ የከፍተኛ ትምህርት ዲግሪ ያላቸውና የተወሰነ የትምህርት ደረጃ ያላቸውን ሰዎች እየመለመሉ ነው" ያሉት ዳይሬክተሩ ጉዳዩ "በተለይም በእስያ አህጉር ውስጥ በስፋት እየተካሄደ " እንደሚገኝ አጽንዖት ሰጥተዋል። የተባበሩት መንግሥታት የዕፅ እና የወንጀል መከላከል ጽሕፈት ቤት (UNODC) ግምት ጠቅሶ ዓለማቀፉ የፍልስተኞች ጉዳይ እንደሚለው ፣ ባለፈው ዓመት በምስራቅ እስያ፣ አውስትራሊያ እና ኒውዚላንድ ብቻ የደረሰው የገንዘብ ኪሳራ እስከ 114 ቢሊዮን ዶላር ደርሷል። እንዲሁም በቀጣናው የሚገኙ "የማጭበርበሪያ ግቢዎች" በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ በሕገ-ወጥ መንገድ የተወሰዱ ሠራተኞችን አፍነው ይዘው ሊሆኑ እንደሚችሉም ገልጿል። እንደ አይ ኦ ኤም ከሆነ በጎርጎርሳዉያኑ 2022 እና 2025 መካከል ከ40 ሀገራት የመጡና በእንደዚህ ዓይነት አስገዳጅ ወንጀሎች ውስጥ የወደቁ ከ3,500 በላይ ተጎጂዎችን ረድቷል። ከእነዚህም መካከል ከኢንዶኔዢያ፣ ሕንድ፣ ስሪላንካ፣ ኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ባንግላዴሽ የመጡ ፍልሰተኞች በቅደም ተከተል ከፍተኛውን ጉዳት ያስተናገዱ ናቸው ብሏል።

የወንጀለኛ መረቦች በሐሰት የሥራ ማስታወቂያ እየሸነገሉ ከየሐገሩ አስኮብልለዉ በአምደ-መረብ (Online) እንዲያጭበረብሩ የሚያስገድዷቸዉ ሰዎች ብዛት በመቶ ሺሕ እንደሚቆጠር የተባበሩት መንግሥታት ድ
የወንጀለኛ መረቦች በሐሰት የሥራ ማስታወቂያ እየሸነገሉ ከየሐገሩ አስኮብልለዉ በአምደ-መረብ (Online) እንዲያጭበረብሩ የሚያስገድዷቸዉ ሰዎች ብዛት በመቶ ሺሕ እንደሚቆጠር የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታወቀ።የዓለም የፍልሰተኞች ድርጅት IOM እንደሚለዉ ከአጭበርባሪዎቹ ወጥመድ የሚገቡት አብዛኞቹ የተማሩ፣እንግሊዝኛ የሚናገሩና ወጣቶች ናቸዉ። ዓለማቀፉ ድርጅት እንዳለው ተጎጂዎች ብዙውን ጊዜ በውጭ ሀገርራት "የሥራ ዕድል አለ " በሚል የሚወጡ የሐሰት ማስታወቂያዎች በዋናነት የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የሚወጡ ናቸው። በተጠቀሰው የስራ ቦታ ሲደርሱ እስራት እንደሚጠብቃቸው ያመለከተው ድርጅቱ ፍልሰተኞቹ መታወቂያዎቻቸውና የጉዞ ሰነዶቻቸው እንደሚወሰድባቸው እና በኃይል፣ በዛቻ እና "በዕዳ እገታ" አማካኝነት በኦንላይን ማጭበርበር ወንጀሎች ላይ እንዲሳተፉ ይገደዳሉ፤ ብሏል።...

...በተጨማሪም በዚህ ዓመት በጥር እና ሐምሌ ወራት መካከል በርካታ ቦይንግ 727 እና ኢሊዩሺን አውሮፕላኖች በምሽት በኒያላ አውሮፕላን ማረፊያ ማረፋቸውን ሪፖርቱ ያመላክታል። የሮይተርስ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ከእነዚህ አውሮፕላኖች መካከል አንዱ ቦይንግ 737 ባለፈው ዓመት ግንቦት ወር ሲወድም የቡድኑን ተዋጊዎችን አሳፍሮ የነበረ ቢሆንም፣ ስቲቨን ሻውሊስ ወይም ኩባንያዎቹ በምንም ዓይነት ወንጀል ወይም ማዕቀብ መከሰሳቸውን የሚያሳይ ማስረጃ አልተገኘም። የቻድ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን አውሮፕላኖቹ ከሀገሪቱ የመብረር ፈቃድ እንዳልነበራቸው አስታውቋል። እንደዚያም ሆኖ የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አብዱላይ ሳብሬ ፋዱል ጉዳዩ ከሀገር መከላከያ ምስጢር ጋር የተያያዘ መሆኑን ግን አልሸሸጉም ።