es
Feedback
DW Amharic

DW Amharic

Ir al canal en Telegram

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram DW Amharic

El canal DW Amharic (@dw_amharic) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 54 769 suscriptores, ocupando la posición 4 795 en la categoría Noticias y medios y el puesto 575 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 54 769 suscriptores.

Según los últimos datos del 08 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -58, y en las últimas 24 horas de -6, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: Verificado (confirmado oficialmente por Telegram)
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 7.88%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 5.49% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 314 visualizaciones. En el primer día suele acumular 3 006 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 0.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 09 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Noticias y medios.

54 769
Suscriptores
-624 horas
+47 días
-5830 días
Archivo de publicaciones
ኢቦላ፣ ከሞት ያመለጡት ተስፋን ይሰብካሉ፣ የገዳዩ በሽታ ሥርጭት ግን አልተገታም ምሥራቂዉ ኮንጎ አልፎ አልፎ የሚታይ ተስፋ ብልጭ ብሏል።በኢቦላ ተሕዋሲ ሥርጭት ከፉኛ የተጎዳችዉ ቤኒ ከተማ ከተሕዋሲ መፈወሷ የተረጋገጠ የመጀሪያዋ ሰዉ ተመዝግቦባታል።በሽታዉ ግን አሁንም እየተዛመተ ነዉ።የጤና ባለሙያዎችም ከተሕዋሲዉ ጋር ብቻ ሳይሆን ከፍርሐት፣ከተሳሳተ መረጃና ከጊዜ ጋር እየታገሉ ነዉ።ከኢቦላ የዳነችዉ የቤኒ ነዋሪ ማሕበረሰቡ ተስፋ እንዳይቆርጥ ትመክራለች።እሷ መዳንዋ የተረጋገጠዉ በሽታዉን ለመከላከል ባለሙያዎች በሚረባረቡበት ወቅት ነዉ።(ቪዲዮዉን ይመልከቱ)

የቀጥታ ስርጭት ማስታወቂያ የረቡዕ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ስርጭታችን የዓለም ዜና ይቀድማል። ዜናውን በሚከተለው የዜና መጽሔት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለዋጋ ንረት የሰጡት ማብራሪያ ና የ
የቀጥታ ስርጭት ማስታወቂያ የረቡዕ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ስርጭታችን የዓለም ዜና ይቀድማል። ዜናውን በሚከተለው የዜና መጽሔት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለዋጋ ንረት የሰጡት ማብራሪያ ና የሕዝብ አስተያየት፤ ትግራይ ክልል ይካሄዳል የተባለው የወጣቶች የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላና ይህን በመቃወም በቅርቡ ይካሄዳል የተባለው ሰልፍ፤ የኢትዮጵያን ኤኮኖሚ በሚመለከት የባለሙያዎች እይታ፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤና የሕዝቡ አስተያየት እንዲሁም ባገረሸው የኢራን አሜሪካ ጦርነት ምክንያት የነዳጅ ዘይት ዋጋ ዳግም ማሻቀቡን የሚያስቃኙ ዘገባዎችን ተካተዋል። ሳምንታዊው የኤኮኖሚው ዓለም ኢትዮጵያ 5.5 ቢሊዮን ዶላር ካገኘችበት የወርቅ ገበያ ብሔራዊ ባንክ እንዲወጣ አይኤምኤፍ የሚገፋው ለምንድነው? በማለት ይጠይቃል። ሳይንስ እና ቴክኒዎሎጂ ደግሞ የሰው ሠራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ በሕግ እንዲመራ መጠየቁን ይዳስሳል። ዝግጅቶቹን ለመከታተል ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ ቀጠሮአችሁ ከዶቼቬለ ጋር ይሁን

የትራምፕ ወቀሳና ዛቻ በኔቶ ጉባኤ የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት በምህጻሩ ኔቶ ጉባኤ ዛሬ በአንካራ ቱርክ ተጀምሯል። በጉባኤ ላይ የተገኙት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ
የትራምፕ ወቀሳና ዛቻ በኔቶ ጉባኤ የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት በምህጻሩ ኔቶ ጉባኤ ዛሬ በአንካራ ቱርክ ተጀምሯል። በጉባኤ ላይ የተገኙት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንደቀደሙት ጊዜያት ሁሉ የኔቶ አባል ሀገራትን ሲወቅሱ፣ በስፔይን ላይ ሲዝቱ፤ ግሪንላንድንም ሲያስፈራሩ ተሰምተዋል። ጉባኤው ከመጀመሩ አስቀድሞ ትራምፕ ከኔቶ ዋና ጸሀፊ ማርክ ሩተ ጋር በተነጋገሩበት ወቅት በኔቶ ደስተኛ አለመሆናቸውን ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። በግሪንላንድ ጉዳይ እንዲሁም ቁጥር አንድ የሽብር ደጋፊ ባሏት በኢራን ጉዳይ ሊረዱን ባለመፈለጋቸው በኔቶ ደስተኛ አይደለንም ብለዋል። ስፔይንን አስፈሪ የኔቶ አባል ሲሉ የተቹት ትራምፕ ከአሁን በኋላ ከስፔን ጋር ምንም ዓይነት የንግድ ግንኙነት አይኖረንምም ብለዋል። ትራምፕ ዛሬ ከስፔን ጋር አገራቸው የነበራትን የንግድ ግንኙነት እንደምታቋረጥ ዝተዋል። ትራምፕ አሁንም ቢሆን የኔቶ አባል የሆነችውን የዴንማርክን ግዛት ግሪንላንድ የመጠቅለል ፍላጎታቸውን ከመናገር አልተቆጠቡም። ግሪንላንድ ለኛ በጣም አስፈላጊ ስትሆን ለዴንማርክ ግን አስፈላጊ አይደለችም ያሉት ትራምፕ አሁንም እንደሚፈልጓት አጽንኦት ሰጥተዋል። «እኛ የምንፈልጋት ለዩናይትድ ስቴትስ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ጥበቃ ለማድረግ ነው» በማለት ትራምፕ «ግሪንላንድን መያዝ እኛን ይረዳናል ለዴንማርክ ግን የሚፈይደው አይኖርም» ሲሉም ሞግተዋል። የኔቶ ዋና ፀሀፊ ማርክ ሩተ እየጨመረ በመጣው የዩናይትድ ስቴትስ ግሪንላንድን የመጠቅለል ፍላጎት ላይ ለመነጋገር ሁለቱ ሀገራት ስምምነት ላይ እንዲደርሱ አሳስበዋል። ይሁንና የዴንማርክ ጠቅላይ ሚኒስትር ሜተ ፍሬድሪክሰን በበኩላቸው ግሪንላንድ «ለሽያጭ እንደማትቀርብ» ኮፕንሀገን ግልጽ አድርጋለች ብለዋል።

የ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግስት በጀት 2.34 ትሪሊየን ብር በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀደቀ የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በትናንቱ 30ኛው መደበኛ ጉባኤው ለፌደራል መንግስት የ
የ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግስት በጀት 2.34 ትሪሊየን ብር በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀደቀ የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በትናንቱ 30ኛው መደበኛ ጉባኤው ለፌደራል መንግስት የ2019 በጀት 2.34 ትሪሊየን ብር አጽድቋል። በሙሉ ድምጽ ከጸደቀው በጀት 1.49 ትሪሊዮን ብሩ ከታክስ ገቢ የሚሰበሰብ ፣ ቀሪው 93.7 ቢሊዮን ብር ከልማት አጋሮች በሚገኝ ብድርና ድጋፍ እንዲሁም 320 ቢሊዮን ብር ከሀገር ውስጥ በሚገኝ ብድር የሚሸፈን መሆኑ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢን ጠቅሶ ምክር ቤቱ በድረ ገጽ ላይ አስታውቋል። እንደ ሰብሳቢው በበጀት ድልድሉ 30 በመቶው ለትምህርት፣ ለመንገድ፣ ለጤና፣ ለግብርና፣ ለኃይል አቅርቦት ማስፋፊያ እና ለከተማ ልማት የተመደበ ነው። ለክልሎች የበጀት ድጋፍ ደግሞ 187.3 ቢሊዮን ብር ወይም 15.1 በመቶ ተመድቧል። ይህም በምክር ቤቱ ድረ ገጽ ላይ እንደተጠቀሰው ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ28.4 ቢሊዮን ብር ወይም 17.8 በመቶ ጭማሪ ያሳያል። ትናንት በኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስለጸደቀው 2.34 ትሪሊየን ብር የፌዴራል መንግስት የ2019 ዓም በጀት ምን አስተያየት አላችሁ ? ጻፉልን ፎቶ፦ ከኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት

ዳንጎቴኬንያ ላሙ ወደብ ነዳጅ ዘይት ማጣሪያ ሊገነቡ ነው ናይጀሪያዊው ቱጃር አሊኮ ዳንጎቴ በኬንያው የላሙ ወደብ በቀን 700 ሺህ በርሜል የሚያመርት የነዳጅ ማጣሪያ ለመገንባት ማቀዳቸው ተረጋገጠ ።
ዳንጎቴኬንያ ላሙ ወደብ ነዳጅ ዘይት ማጣሪያ ሊገነቡ ነው ናይጀሪያዊው ቱጃር አሊኮ ዳንጎቴ በኬንያው የላሙ ወደብ በቀን 700 ሺህ በርሜል የሚያመርት የነዳጅ ማጣሪያ ለመገንባት ማቀዳቸው ተረጋገጠ ። አንድ የዳንጎቴ ኩባንያ ከፍተኛ ባለሥልጣንን ጠቅሶ የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዛሬ እንደዘገበው እስካሁን በፕሮጀክቱ ላይ የነበረው ጥርጣሪ እልባት አግኝቷል። የድርጅቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ኤድዊን ዴቫኩማር እንደተናገሩት ከምሥራቅ አፍሪቃ ሀገራት ትልቅ ኤኮኖሚ በምታንቀሳቅሰው በኬንያ የሚገነባው የነዳጅ ማጣሪያ ወደ 30 ወራት የሚጠጋ ጊዜ ይወስዳል። የፕሮጀክቱን ቦታ በተመለከተ ከታንዛንያ እና ከኬንያዋ የሞምባሳ ወደብ ጋር በተያያዘ ሚስጥራዊና አወዛጋቢ ጉዳዮች እንደነበሩ ዴቫኩማር አስታውሰዋል። የዳንጎቴ ቢሮ ባወጣው መግለጫ ፕሮጀክቱ ወደ ላሙ ስለተዛወረበት ምክንያት ዳንጎቴ ከታንዛንያዋ ፕሬዝዳንት ሳምያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር ተነጋግረው ነበር። ታንዛንያም በላሙ ውረታ እንድትሳተፍም ጋብዘውም ነበር።

የማክሰኞ ሰኔ 30 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና አርዕስተ ዜና *የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥትን በተመለከተ የሚሻሻል እንጂ «ያለውን የሚያጎድል» ነገር ይፈጠራል ብለው እንደማያስቡ ተናገሩ ። «በሕገ መንግሥቱ ውስጥ ለኢትዮጵያ ጠቃሚ ሐሳቦች ካሉ እንዳሉ ይቀጥላሉ ብዬ አስባለሁ» ሲሉም አክለዋል ። *የኬንያ ፖሊስ በመዲናይቱ ናይሮቢ ሊካሄድ ታቅዶ የነበረውን «ሳባ ሳባ ዴይ» የተሰኘ የመታሰቢያ ሰልፍ ከለከለ ። የመታሰቢያ ሰልፉ እንዳይከናወን ለማከላከል በዋና ከተማዪቱ ፖሊስ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው በከባዱ የታጠቁ የፀጥታ አካላትን ማሰማራቱን የፈረንሣይ ዜና አገልግሎት (AFP) ዘግቧል ። በጎረቤት ታንዛኒያም ዛሬ ሰልፉ እንዳይካሄድ በርካታ ፖሊሶች ተሰማርተው እንደነበር ተገልጧል ። *የፈረንሣይ ፕሬዚደንት ኤማኑዌል ማክሮ ሶሪያን በሚጎበኙበት ወቅት በተከሰቱ ሁለት ተከታታይ ፍንዳታዎች 18 ሰዎች ቆሰሉ ። ከቆሰሉት መካከል አራቱ ፖሊሶች መኾናቸውን አሶሺየትድ ፕሬስ የዜና ምንጭ ዘግቧል ። ሙሉ ዜናውን በድምጽ እና በጽሑፍ በማገናኛው በኩል መከታተል ይቻላል https://pepurl.com/p/5Gj3f?maca=amh-RED-Telegram-dwcom