DW Amharic
前往频道在 Telegram
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።
显示更多📈 Telegram 频道 DW Amharic 的分析概览
频道 DW Amharic (@dw_amharic) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 54 769 名订阅者,在 新闻与媒体 类别中位列第 4 795,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 575 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 54 769 名订阅者。
根据 08 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -58,过去 24 小时变化为 -6,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 已认证(Telegram 官方确认)
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 7.88%。内容发布后 24 小时内通常能获得 5.49% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 314 次浏览,首日通常累积 3 006 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።”
凭借高频更新(最新数据采集于 09 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 新闻与媒体 类别中的关键影响点。
54 769
订阅者
-624 小时
+47 天
-5830 天
帖子存档
54 770
ኢቦላ፣ ከሞት ያመለጡት ተስፋን ይሰብካሉ፣ የገዳዩ በሽታ ሥርጭት ግን አልተገታም
ምሥራቂዉ ኮንጎ አልፎ አልፎ የሚታይ ተስፋ ብልጭ ብሏል።በኢቦላ ተሕዋሲ ሥርጭት ከፉኛ የተጎዳችዉ ቤኒ ከተማ ከተሕዋሲ መፈወሷ የተረጋገጠ የመጀሪያዋ ሰዉ ተመዝግቦባታል።በሽታዉ ግን አሁንም እየተዛመተ ነዉ።የጤና ባለሙያዎችም ከተሕዋሲዉ ጋር ብቻ ሳይሆን ከፍርሐት፣ከተሳሳተ መረጃና ከጊዜ ጋር እየታገሉ ነዉ።ከኢቦላ የዳነችዉ የቤኒ ነዋሪ ማሕበረሰቡ ተስፋ እንዳይቆርጥ ትመክራለች።እሷ መዳንዋ የተረጋገጠዉ በሽታዉን ለመከላከል ባለሙያዎች በሚረባረቡበት ወቅት ነዉ።(ቪዲዮዉን ይመልከቱ)
54 770
የቀጥታ ስርጭት ማስታወቂያ
የረቡዕ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ስርጭታችን የዓለም ዜና ይቀድማል። ዜናውን በሚከተለው የዜና መጽሔት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለዋጋ ንረት የሰጡት ማብራሪያ ና የሕዝብ አስተያየት፤
ትግራይ ክልል ይካሄዳል የተባለው የወጣቶች የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላና ይህን በመቃወም በቅርቡ ይካሄዳል የተባለው ሰልፍ፤
የኢትዮጵያን ኤኮኖሚ በሚመለከት የባለሙያዎች እይታ፤
ሀገራዊ የምክክር ጉባኤና የሕዝቡ አስተያየት እንዲሁም ባገረሸው የኢራን አሜሪካ ጦርነት ምክንያት የነዳጅ ዘይት ዋጋ ዳግም ማሻቀቡን የሚያስቃኙ ዘገባዎችን ተካተዋል።
ሳምንታዊው የኤኮኖሚው ዓለም ኢትዮጵያ 5.5 ቢሊዮን ዶላር ካገኘችበት የወርቅ ገበያ ብሔራዊ ባንክ እንዲወጣ አይኤምኤፍ የሚገፋው ለምንድነው? በማለት ይጠይቃል። ሳይንስ እና ቴክኒዎሎጂ ደግሞ የሰው ሠራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ በሕግ እንዲመራ መጠየቁን ይዳስሳል።
ዝግጅቶቹን ለመከታተል ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ ቀጠሮአችሁ ከዶቼቬለ ጋር ይሁን
54 770
የትራምፕ ወቀሳና ዛቻ በኔቶ ጉባኤ
የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት በምህጻሩ ኔቶ ጉባኤ ዛሬ በአንካራ ቱርክ ተጀምሯል። በጉባኤ ላይ የተገኙት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንደቀደሙት ጊዜያት ሁሉ የኔቶ አባል ሀገራትን ሲወቅሱ፣ በስፔይን ላይ ሲዝቱ፤ ግሪንላንድንም ሲያስፈራሩ ተሰምተዋል።
ጉባኤው ከመጀመሩ አስቀድሞ ትራምፕ ከኔቶ ዋና ጸሀፊ ማርክ ሩተ ጋር በተነጋገሩበት ወቅት በኔቶ ደስተኛ አለመሆናቸውን ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። በግሪንላንድ ጉዳይ እንዲሁም ቁጥር አንድ የሽብር ደጋፊ ባሏት በኢራን ጉዳይ ሊረዱን ባለመፈለጋቸው በኔቶ ደስተኛ አይደለንም ብለዋል። ስፔይንን አስፈሪ የኔቶ አባል ሲሉ የተቹት ትራምፕ ከአሁን በኋላ ከስፔን ጋር ምንም ዓይነት የንግድ ግንኙነት አይኖረንምም ብለዋል። ትራምፕ ዛሬ ከስፔን ጋር አገራቸው የነበራትን የንግድ ግንኙነት እንደምታቋረጥ ዝተዋል።
ትራምፕ አሁንም ቢሆን የኔቶ አባል የሆነችውን የዴንማርክን ግዛት ግሪንላንድ የመጠቅለል ፍላጎታቸውን ከመናገር አልተቆጠቡም። ግሪንላንድ ለኛ በጣም አስፈላጊ ስትሆን ለዴንማርክ ግን አስፈላጊ አይደለችም ያሉት ትራምፕ አሁንም እንደሚፈልጓት አጽንኦት ሰጥተዋል።
«እኛ የምንፈልጋት ለዩናይትድ ስቴትስ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ጥበቃ ለማድረግ ነው» በማለት ትራምፕ «ግሪንላንድን መያዝ እኛን ይረዳናል ለዴንማርክ ግን የሚፈይደው አይኖርም» ሲሉም ሞግተዋል።
የኔቶ ዋና ፀሀፊ ማርክ ሩተ እየጨመረ በመጣው የዩናይትድ ስቴትስ ግሪንላንድን የመጠቅለል ፍላጎት ላይ ለመነጋገር ሁለቱ ሀገራት ስምምነት ላይ እንዲደርሱ አሳስበዋል። ይሁንና የዴንማርክ ጠቅላይ ሚኒስትር ሜተ ፍሬድሪክሰን በበኩላቸው ግሪንላንድ «ለሽያጭ እንደማትቀርብ» ኮፕንሀገን ግልጽ አድርጋለች ብለዋል።
54 770
የ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግስት በጀት 2.34 ትሪሊየን ብር በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፀደቀ
የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በትናንቱ 30ኛው መደበኛ ጉባኤው ለፌደራል መንግስት የ2019 በጀት 2.34 ትሪሊየን ብር አጽድቋል። በሙሉ ድምጽ ከጸደቀው በጀት 1.49 ትሪሊዮን ብሩ ከታክስ ገቢ የሚሰበሰብ ፣ ቀሪው 93.7 ቢሊዮን ብር ከልማት አጋሮች በሚገኝ ብድርና ድጋፍ እንዲሁም 320 ቢሊዮን ብር ከሀገር ውስጥ በሚገኝ ብድር የሚሸፈን መሆኑ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢን ጠቅሶ ምክር ቤቱ በድረ ገጽ ላይ አስታውቋል። እንደ ሰብሳቢው በበጀት ድልድሉ 30 በመቶው ለትምህርት፣ ለመንገድ፣ ለጤና፣ ለግብርና፣ ለኃይል አቅርቦት ማስፋፊያ እና ለከተማ ልማት የተመደበ ነው። ለክልሎች የበጀት ድጋፍ ደግሞ 187.3 ቢሊዮን ብር ወይም 15.1 በመቶ ተመድቧል። ይህም በምክር ቤቱ ድረ ገጽ ላይ እንደተጠቀሰው ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ28.4 ቢሊዮን ብር ወይም 17.8 በመቶ ጭማሪ ያሳያል።
ትናንት በኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስለጸደቀው 2.34 ትሪሊየን ብር የፌዴራል መንግስት የ2019 ዓም በጀት ምን አስተያየት አላችሁ ? ጻፉልን
ፎቶ፦ ከኢፌዲሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት
54 770
ዳንጎቴኬንያ ላሙ ወደብ ነዳጅ ዘይት ማጣሪያ ሊገነቡ ነው
ናይጀሪያዊው ቱጃር አሊኮ ዳንጎቴ በኬንያው የላሙ ወደብ በቀን 700 ሺህ በርሜል የሚያመርት የነዳጅ ማጣሪያ ለመገንባት ማቀዳቸው ተረጋገጠ ። አንድ የዳንጎቴ ኩባንያ ከፍተኛ ባለሥልጣንን ጠቅሶ የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዛሬ እንደዘገበው እስካሁን በፕሮጀክቱ ላይ የነበረው ጥርጣሪ እልባት አግኝቷል። የድርጅቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ኤድዊን ዴቫኩማር እንደተናገሩት ከምሥራቅ አፍሪቃ ሀገራት ትልቅ ኤኮኖሚ በምታንቀሳቅሰው በኬንያ የሚገነባው የነዳጅ ማጣሪያ ወደ 30 ወራት የሚጠጋ ጊዜ ይወስዳል።
የፕሮጀክቱን ቦታ በተመለከተ ከታንዛንያ እና ከኬንያዋ የሞምባሳ ወደብ ጋር በተያያዘ ሚስጥራዊና አወዛጋቢ ጉዳዮች እንደነበሩ ዴቫኩማር አስታውሰዋል። የዳንጎቴ ቢሮ ባወጣው መግለጫ ፕሮጀክቱ ወደ ላሙ ስለተዛወረበት ምክንያት ዳንጎቴ ከታንዛንያዋ ፕሬዝዳንት ሳምያ ሱሁሉ ሀሰን ጋር ተነጋግረው ነበር። ታንዛንያም በላሙ ውረታ እንድትሳተፍም ጋብዘውም ነበር።
54 770
የማክሰኞ ሰኔ 30 ቀን፣ 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና
አርዕስተ ዜና
*የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥትን በተመለከተ የሚሻሻል እንጂ «ያለውን የሚያጎድል» ነገር ይፈጠራል ብለው እንደማያስቡ ተናገሩ ። «በሕገ መንግሥቱ ውስጥ ለኢትዮጵያ ጠቃሚ ሐሳቦች ካሉ እንዳሉ ይቀጥላሉ ብዬ አስባለሁ» ሲሉም አክለዋል ።
*የኬንያ ፖሊስ በመዲናይቱ ናይሮቢ ሊካሄድ ታቅዶ የነበረውን «ሳባ ሳባ ዴይ» የተሰኘ የመታሰቢያ ሰልፍ ከለከለ ። የመታሰቢያ ሰልፉ እንዳይከናወን ለማከላከል በዋና ከተማዪቱ ፖሊስ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው በከባዱ የታጠቁ የፀጥታ አካላትን ማሰማራቱን የፈረንሣይ ዜና አገልግሎት (AFP) ዘግቧል ። በጎረቤት ታንዛኒያም ዛሬ ሰልፉ እንዳይካሄድ በርካታ ፖሊሶች ተሰማርተው እንደነበር ተገልጧል ።
*የፈረንሣይ ፕሬዚደንት ኤማኑዌል ማክሮ ሶሪያን በሚጎበኙበት ወቅት በተከሰቱ ሁለት ተከታታይ ፍንዳታዎች 18 ሰዎች ቆሰሉ ። ከቆሰሉት መካከል አራቱ ፖሊሶች መኾናቸውን አሶሺየትድ ፕሬስ የዜና ምንጭ ዘግቧል ።
ሙሉ ዜናውን በድምጽ እና በጽሑፍ በማገናኛው በኩል መከታተል ይቻላል https://pepurl.com/p/5Gj3f?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
