DW Amharic
前往频道在 Telegram
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።
显示更多📈 Telegram 频道 DW Amharic 的分析概览
频道 DW Amharic (@dw_amharic) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 54 844 名订阅者,在 新闻与媒体 类别中位列第 4 817,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 577 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 54 844 名订阅者。
根据 17 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -113,过去 24 小时变化为 -2,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 已认证(Telegram 官方确认)
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 8.37%。内容发布后 24 小时内通常能获得 6.01% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 589 次浏览,首日通常累积 3 297 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።”
凭借高频更新(最新数据采集于 18 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 新闻与媒体 类别中的关键影响点。
54 844
订阅者
-224 小时
+207 天
-11330 天
帖子存档
54 844
...የአፍሪቃ ኅብረትን ጨምሮ በርካታ ዓለም አቀፍ ተቋማትን በምታስተናግደው ታሪካዊት ሀገር ኢትዮጵያ የግለሰቦችና የሀገር ደኅንነት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መሆኑን በመግለጽም፤ ይህ ሁሉ በቂ የመገናኛ ብዙኃን ሽፋንና ትኩረት እንዳላገኘም አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ ውስጥ እየተፈጸመ ነው ላሉት ዘርና ሃይማኖትን መሰረት ላደረገ ጥቃት ተጠያቂነት እንደሌለ በማመልከትም ፍትህ እና ተጠያቂነት እንዲኖር ጥሪ አቅርበዋል።
በዛሬዋ ኢትዮጵያ ውስጥ በመንግሥትም ሆነ በታጣቂ ኃይሎች የሚፈጸሙ የጦር ወንጀሎች፤ በሰብአዊነት ላይ የሚፈጸም ወንጀልና የዘር ፍጅት ተጠያቂነት የሌለበት ነው ሲሉም ተችተዋል። ገለጻውን ካደመጡ የአውሮጳ ፓርላማ አባላት አንዱ፤ «ለምድነው መንግሥት የራሱ ሕዝብ ላይ በሰው አልባ አውሮፕላን (ድሮን)ም ሆነ በሌሎች የጦር መሣሪያዎች ጥቃት የሚያደርሰው?» ሲሉ ጠይቀዋል።
በምላሻቸው «ኢትዮጵያ ውስጥ የክፉ ነገሮች ሁሉ ምንጭ ሕገ መንግሥቱ ነው» ያሉት ዶክተር አስፋወሰን፤ «ከዓለም በጎሳ ላይ የተመሠረተ ፌደራሊዝም ያለባት ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ» እንደሆነችም ጠቁመዋል። በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በሌሎችም በርካታ ጎሳዎች ባሉባቸው የአፍሪቃ ሃገራት የፖለቲካ አካሄድ «አንድነት በልዩነት ፤ ልዩነት በአንድነት» የሚል መሆን እንደሚገባውም ሃሳባቸውን አጋርተዋል።
54 844
የአውሮጳ የሕግና የፍትህ ማዕከል (European Centre for law and Justice ) ባለሥልጣናት ዛሬ ከቀትር በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተፈጸሙ ያሉ ጥቃቶችን የተመለከተ ገለጻ ተደረገ። የአውሮጳ የሕግና የፍትህ ማዕከል ከቀናት በፊት ሽትራስቡርግ ፈረንሳይ በሚገኘው የሕብረቱ ምክር ቤት በጎን በሚካሄድ መድረክ ኢትዮጵያውን ላይ እየተፈጸመ ስላለ ወከባና ጥቃት እንደሚያደምጥ ዐሳውቆ ነበር። በቀጠሮው መሠረትም በዛሬው ዕለት የመድረኩ ዋነኛ ተናጋሪ ልዑል ዶክተር አስፋወሰን አሥራተ፤ በተለይ «በዝምታ የሚፈጸመው የአማራ ስቃይ» በሚል ርዕስ ዝርዝር ገለጻ አድርገዋል።
ልዑል ዶክተር አስፋወን አስራተን በማስተዋወቅ የጀመሩት መድረኩን ከጋበዙት የአውሮጳ ምክር ቤት አባላት አንዱ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፦ «ኢትዮጵያ ውስጥ በአንድ አቅጣጫ ብቻ የእርስ በእርስ ጦርነት ብቻ ያለ ይመስለኝ ነበር» ያሉ ሲሆን፤ ከሚደርሷቸው መረጃዎች ግን ጥቃት ግጭቱ በየቦታው መሰራጨቱን መረዳታቸውን ተናግረዋል።
ዶክተር አስፋወሰን በበኩላቸው በገለጻቸው ኢትዮጵያ ውስጥ በሲቪሎች ላይ እየተፈጸመ ነው ያሉትን ጥቃት እና ግድያ መንግሥት ማስቆም አልቻለም ሲሉ ወቅሰዋል። «ብዙ ጊዜ የመንግሥት ሚና ምንድነው እያልኩ እጠይቃለሁ» ያሉት ልጅ ዶክተር አስፋወሰን አስራተ፤ ቅድሚያ የሕዝቡን ደኅንነት ማስከበር የመንግሥት ኃላፊነት እንደሆነ አጽንኦት ሰጥተዋል። ...
54 844
የሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም.
የስርጭት ማስታወቂያ
ጤና ይስጥልን የተከበራችሁ የዶቼ ቬለ ተከታታዮች ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ የሚቀርበው የሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም. ስርጭታችን፤ በዜና መጽሔት፦
አሳሳቢው የጦርነት ስጋት በሰሜን ኢትዮጵያ ፣የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ «የቁጫ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ»ን አቤቱታ ውድቅ ማድረጉ፣ ዩናይትድ ስቴትሰና ኢራን ደረሱበት የተባለው ስምምነት አፍሪካን እንዳያዘናጋ ተንታኛች ማሳሰባቸው እንዲሁም ትራምፕን ጨምሮ የቡድን ሰባት አባል ሀገራት መሪዎች ዩክሬንን ለመደገፍ መስማማታቸውን የሚያስቃኙ ዘገባዎች ተካተዋል።
ስለቻት ጂፒቲ ምን ይላሉ? ለወጣቶች ክፉ መካሪ ነው የሚሉት አሉ፤ ሳይንስና ቴክኒዎሎጂ ስለ «ክፉ መካሪው ቻት ጂፒቲ» የሚለን ይኖረዋል።
የዕለተ ረቡዕ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም. ስርጭታችንን ለመከታተል በሰዓቱ ወደ ዶቼ ቬለ DW ማኅበራዊ መገናኛ ዘዴ ገጾች ጎራ እንድትሉ ከወዲሁ እንጋብዛለን።
የዶቼ ቬለን ስርጭት በሳተላይት ለመከታተል አድራሻው፣ በኢትዮ ሳት ወይንም (NSS-12) በ10,985.0 ሜጋ ኸርዝ፣ ሆሪዞንታል፣ DW-08 ላይ ፈልጉን። ትራንስፖንደሩ፦ MEH 01 ወይንም EAH 01 ነው።
54 844
የኢኳቶሪያል ጊኒ መንግሥት አላሳካሁም ባላቸው ግቦቹ ምክንያት ሥልጣን መልቀቁ ተነገረ። የሀገሪቱ ፕሬዝደንት ልጅ የሆኑት ምክትል ፕሬዝደንት ቴዎዶሮ ንጉማ ኦቢያንግ ማንጌ ትናንት ይፋ እንዳደረጉት የኢኳቶሪያል ጊኒ ጠቅላይ ሚኒስትር የመንግሥት ባለሥልጣናትን የመልቀቂያ ደብዳቤ አቅርበዋል። ምክንያታቸው የመንግሥት ካቢኔ ከግብ ለማድረስ ካቀዳቸው እስካሁን ያሳካው 10 በመቶ ብቻ ነው የሚል ነው። እንዲያም ሆኖ መንግሥት ሊያሳካ አቅዶ እስካሁን አልሆነለትም የተባለው ምን እንደሆነ ግልጽ አለመደረጉን ሮይተርስ አመልክቷል።
የኢኳቶሪያል ዴሞክራቲክ ገዢ ፓርቲ (ፒዲጄ) መግለጫ እንዳመለከተው መንግሥት በሥልጣን ላይ በነበረበት ወቅት እንደ የመንግ|ሥት አስተዳደር፣ የመሠረተ ልማት፣ የመንግሥት አገልግሎቶች እና የኢኮኖሚ ልማት ባሉ ዘርፎች የተለያዩ ተነሳሽነቶችን ተግባራዊ አድርጓል።
የመንግሥት ባለሥልጣናት የጋራ ሥራቸውን መልቀቅም የመንግሥትን መዋቅርን በማሻሻል ለታሰቡ አዳዲስ ቅድሚያ የሚሰጣቸው በየጊዜው የሚከናወኑ የተቋማዊ መልሶ ማደራጀት ሂደቶች አካል ነው ሲል ፓርቲው በፌስቡክ ገፁ ላይ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
የኢኳቶሪያል ጊኒ ፕሬዝደንት ቴዎዶሮ ኦቢያንግ ንጉማ ምባሶጎ ከጎርጎሪዮሳዊው 1979 ዓ,ም ጀምሮ ሥልጣን እንደያዙ ነው። ይህም በዓለማችን ለረዥም ዓመታት በሥልጣን የሰነበቱ ፕሬዝደንት ያደርጋቸዋል። ልጃቸውም ምክትላቸው ሆኖ ኤኳቶሪያል ጊኒን በቤተሰብ እየመሩ ነው።
54 844
... ማዕከሉ የኢትዮጵያ መንግሥት ምርጫ በሚካሄድበት ዕለት በሸርካ ወረዳ ሁለት ዘመዳማቾች በጌዶ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን መቀበራቸውን የግለሰቦቹን ስም በመጥቀስ ገልጿል። በዋዜማው ታጣቂዎች ወደ ቤታቸው መጥተው ንብረቶቻቸውንና ከብቶቻቸውን ሰርቀዋል፤ የሰዎቹም አስከሬን ከቤታቸውን ዐሥር ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ሚታና ጋዶ በተባለ ስፍራ መገኘቱንም አመልክቷል። ግንቦት 22 እና 23 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ታጣቂዎች በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን ውስጥ ተዘዋውረው የኦርቶዶክስ ክርስቲያን ሲቪሎችን በቤታቸው፤ በመንገድ ላይ እና ሲሸሹ መግደላቸውን፤ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ የቆየውን የቅዱስ ገብርኤልን ቤተክርስቲያን ማቃጠላቸውን፤ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያንን ዘርፈው ማቃጠላቸውን ዘርዝሯል። የኦርቶዶክስ ክርስቲያን ቤተሰቦችን በመለየትም ቤቶቻቸውን በእሳት ማቃጠላቸውን ንብረቶችንም መዝረፋቸውንም ገልጿል። የአውሮጳ የሕግና የፍትህ ማዕከል መግለጫ በተለያዩ ጊዜያት ጥቃት የተፈጸመባቸው ቦታቸው በዝርዝር በመጥቀስ የተፈጸሙ ድርጊቶችን ማስረጃ በማጣቀስ አቅርቧል። የአውሮጳ የሕግና የፍትህ ማዕከል፦ «በሲቪል ክርስቲያኖች እና አማራዎች ላይ ተከታታይነት ያለው» ሲል የገለጠው «ጥቃት» በተመድ የዘር ፍጅት መከላከል ድንጋጌ እና በሮም ደንቦች (የዓለም አቀፍ የጦር ወንጀሎች መዳኛ ፍርድ ቤት) አኳያ ብርቱ የሕግ ጥያቄዎችን ያስነሳል ብሏል።
54 844
የአውሮጳ የሕግና የፍትህ ማዕከል ኢትዮጵያ ውስጥ እየተባባሰ ነው ያለውን ግድያ አስመልክቶ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የዘር ፍጅት መከላከል ቢሮ ጥሪ አቀረበ። ማዕከሉ በቅርቡ አርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ በትንሹ 37 ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች መገደላቸውን አብያተ ክርስቲያንም መቃጠላቸውን አመልክቷል። ማዕከሉ ትናንት ባወጣው ማሳሰቢያው ኢትዮጵያ ውስጥ አጠቃላይ ምርጫ በሚካሄድበት ወቅት በአንድ ወገን ክርስቲያኖች ሟች ወገኖቻቸውን ይቀብሩ፤ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሲቪሎችም ከመኖሪያ ቀያቸው ይሳደዱ ይፈናቀሉ እንደነበር ገልጿል። ግድያው «ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ክርስቲያኖች ላይ በተደጋጋሚ ከተፈጸመው ጥቃቶች በቅርቡ የተፈጸመ መሆኑን» በማመልከትም ድርጊቱ «በመላው ኢትዮጵያ በአማራ ሕዝብ ላይ እየተደረገ ነው» ያለውን «ግፍና ጭካኔ የጨመረ ስጋት ነው» ብሏል። የሁኔታውን መባባስ ምክንያት በማድረግም የአማራ ሕዝብ እና በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የክርስቲያን ማኅበረሰቦች እያጋጠሟቸው ያሉ አደጋዎችን በተመለከተ የአውሮጳ የሕግና የፍትህ ማዕከል አስቸኳይ አቤቱታውን ለተመድ የዘር ፍጅት መከላከል ቢሮ አቅርቧል።....
54 844
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቁጫ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በቁጫ ምርጫ ክልል የተካሄደው ምርጫ እንዲሰረዝ ሲል ያቀረበውን አቤቱታ ውድቅ አደረገ። ቦርዱ የፓርቲውን ጥያቄ ሳይቀበለው የቀረው ቅሬታው በበቂ ማስረጃ ባለመደገፉ ነው ብሏል። ፓርቲው በበኩሉ የተፈጸመው የምርጫ ሕግ ጥሰት የጣት አሻራን ጨምሮ በፎረንሲክ ምርመራ እንዲጣራ ያቀረብኩትን ጥያቄ ቦርዱ ተፈጻሚ አላደረግም ሲል ወቅሷል።
የቅሬታው መነሻ «በቁጫ ምርጫ ክልል የምርጫ ሕግን የተላለፉ፣ የመራጮችን ነጻነት እና ምስጢራዊነት የጣሱ ድርጊቶች ተፈጽመዋል የሚል ነው። በዚህም ምክንያት «በቁጫ ምርጫ ክልል የተካሄደው ምርጫ እንዲሰረዝ » ሲል ነበር ፓርቲው ጥያቄውን ለቦርዱ ያቀረበው።
የቁጫ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እጩዎቹን አቅርቦ የተወዳደረው በጋሞ ዞን ቁጫ ምርጫ ክልል ነው።
ፓርቲው በምርጫው ላይ ታይተዋል ያላቸውን የምርጫ ሕግ ጥሰቶች ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቅሬታውን ያቀረበው ባለፈው ግንቦት 24 የተካሄደው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ተከትሎ ነበር። ምርጫ ቦርድ ያሳለፈውን ውሳኔ እንዳልተቀበለው የጠቀሰው ፓርቲው ጉዳዩን ወደ መደበኛ ፍርድ ቤት እንደሚወስድ አስታውቋል። ሙሉ ዘገባው በስርጭት ሰዓታችን ይቀርባል። ተከታተሉ። #ምርጫ2018 #EthiopiaElection2026
54 844
የባቫሪያ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የፌደራል ግዛቱ የስለላ ተቋም የቀኝ ጽንፈኛው ፓርቲ አማራጭ ለጀርመን (AFD)ን ክትትል ማድረግ ይችላል ሲል ወሰነ። የባቫሪያ ፍርድ ቤትን እርምጃ ሌሎች በርካታ ፌደራል ግዛቶችም ተግባራዊ ለማድረግ እየሞከሩ ነው። ሙኒክ የሚገኘው የጀርመን ባቫሪያ ፌደራል ግዛት ከፍተኛ የፍርድ ቤት አስተዳደርይህን ውሳኔ ያሳለፈው ዛሬ ረቡዕ ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም. ነው።
ቀኝ ጽንፈኛው ተቃዋሚ ፓርቲ አማራጭ ለጀርመን ግን ይህን ውሳኔ አጥብቆ ተቃውሟል። ጉዳዩንም በፌደራል ደረጃ ይግባኝ እንደሚል አመልክቷል። ሆኖም የሙኒኩ ፍርድ ቤት ይግባኝ የማይጠየቅበት ውሳኔ እንደሆነ አስታውቋል። ፍርድ ቤቱ አክሎም በAFD የቀረበው አቤቱታ ቀደም ብሎ በሌሎች ችሎቶች መታየቱን እና ውድቅ እንደተደረገም ገልጿል። ፓርቲውን በስለላ ተቋማት የመከታተል እቅድ በቅድሚያ የተነገረው በጎርጎሪዮሳዊው 2022 ዓ.ም. ሲሆን በሕግ ለማስቆም የተደረገው የመጀመሪያው ሙከራ በተመሳሳይ የዘመን ቀመር በ2024 ተቀባይነት ሳያገኝ ቀርቷል።
በርካታ ፌደራል ግዛቶችም የጀርመንን ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ለማዳከም እየሞከሩ ነው በሚል ጥርጣሬ ፓርቲው ወይም አንዳንድ አባላቱን ለመከታተል ተመሳሳይ ሙከራ ማድረጋቸው ተገልጿል። በጀርመን ታሪክ እንዲህ ያለው እርምጃ የመጀመሪያ አይደለም። ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ ለቀድሞው የናዚ መንግሥት ምላሽ ለመስጠት የቀኝ ፖለቲካ አራማጆች ላይ ተመሳሳይ አጋጅ ውሳኔዎች ተደንግገው ነበር።
54 844
ተደጋጋሚ ማዛጋት(ማፋሸክ) ለምን ይከሰታል?
ማዛጋት እንደማስነጠስ ሁሉ ልንቆጣጠራቸው ከማንችላቸው የተፈጥሮ ክስተቶች አንዱ ነው። የህክምና ባለሙያዎች ማዛጋት ሰውነት ሲደክምና አዕምሮ ሲከብደው በተፈጥሮ ስርዓት እራሱን የሚያነቃቃበት ስልት ነው ይሉታል።
https://pepurl.com/p/5FWLG?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
54 844
በሥራ ላይ መዋል የጀመረው አዲሱ የአውሮጳ የፈላስያንና ስደተኞች ሕግ
የመንግሥታቱ ድርጅት የስድተኞች መርጃ ድርጅት መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ዛሬ በዓለማችን ክ136 ሚሊዮን በላይ ሕዝቦች ተስድደው መንግሥት አልባ መኾናቸውን ይጠቁማሉ። ጦርንት፤ ድህነት፤ የተፈጥሮ አደጋዎችና የአገዛዝ ሥራቶች ዋናዎቹ ሰዎች ቤት ንብረታቸውን ጥለው እንዲፈናቀሉና እንዲስደዱ የሚያደርጉ ምክንያቶች መሆናቸው ይታመናል።
https://pepurl.com/p/5FWGp?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
54 844
የዋጋ ንረት እና የደመወዝ ጭማሪ ፍላጎት
በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በመካከለኛው ምስራቅ የተከሰተውን ጦርነት ተከትሎ በኢትዮጵያ ተፈጥሮ የነበረው የነዳጅ አቅርቦት ቀውስ የምርቶችን ዋጋ እጅግ ከፍተኛ በሆነ መጠን ማስናሩን በርካቶች ይናገራሉ
https://pepurl.com/p/5FWOw?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
54 844
ተደጋጋሚ ማዛጋት(ማፋሸክ) ለምን ይከሰታል?
ማዛጋት እንደማስነጠስ ሁሉ ልንቆጣጠራቸው ከማንችላቸው የተፈጥሮ ክስተቶች አንዱ ነው። የህክምና ባለሙያዎች ማዛጋት ሰውነት ሲደክምና አዕምሮ ሲከብደው በተፈጥሮ ስርዓት እራሱን የሚያነቃቃበት ስልት ነው ይሉታል።
https://pepurl.com/p/5FWLG?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
