uk
Feedback
DW Amharic

DW Amharic

Відкрити в Telegram

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу DW Amharic

Канал DW Amharic (@dw_amharic) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 54 772 підписників, посідаючи 4 795 місце в категорії Новини і ЗМІ та 575 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 54 772 підписників.

За останніми даними від 08 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на -58, а за останні 24 години на -6, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Верифікований (Офіційно підтверджено Telegram)
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 7.88%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 5.49% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 4 314 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 3 006 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 0.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 09 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Новини і ЗМІ.

54 772
Підписники
-624 години
+47 днів
-5830 день
Архів дописів
ዱባይ-የቀድሞዉ የኢራን ላዕላይ መሪ አያቶላሕ ዓሊ ኻምኔይ ተቀበሩ ዩናይትድ ስቴትስና እስራኤል ባለፈዉ የካቲት ማብቂያ ላይ የገደሏቸዉ የኢራን የፖለቲካና የኃይማኖት መሪ አያቶላሕ ዓሊ ኻምኔይ ዛሬ ተ
ዱባይ-የቀድሞዉ የኢራን ላዕላይ መሪ አያቶላሕ ዓሊ ኻምኔይ ተቀበሩ ዩናይትድ ስቴትስና እስራኤል ባለፈዉ የካቲት ማብቂያ ላይ የገደሏቸዉ የኢራን የፖለቲካና የኃይማኖት መሪ አያቶላሕ ዓሊ ኻምኔይ ዛሬ ተቀበሩ።እስራኤልና ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን ላይ ጦርነት በከፈቱበት ዕለት እግአ የካቲት 28 ቀን 2026 ከኻምኔይ ሌላ ሴት ልጃቸዉን፣ የልጅ ልጃቸዉን፣ አማቻቸዉንና 11 ባለሥልጣኖቻቸዉን ገድለዋል።ባለቤታቸዉም ክፉኛ ቆስለዉ ኋላ ሞተዋል።የኻምኔይን ሥልጣን የያዙት ያሁኑ የኢራን ላዕላይ መሪ ሞጅታባ ኻምኔይም የዚያን ቀን ቆስለዋል።ሞጅታባሕ የላዕላይ መሪነቱን ሥልጣን ቢይዙም እስከ ዛሬ ድረስ ለሕዝብ እይታ አልቀረቡም።ካለፈ,ዉ ሳምንት ጀምሮ ለአባታቸዉ በተደረገዉ የሽኝት ሥርዓትም ሆነ በዛሬዉ የቀብር ሥርዓት ላይ አልተገኙም።ኢራንን ከ30 ዓመታት በላይ የመሩት ዓሊ ኻምኔይ ዛሬ የተቀበሩት በሐገሪቱ ሰሜን-ምሥራቅ ቅዱስ የቀብር ሥፍራ ማሻሐ,ድ ዉስጥ ነዉ።ማሽሐድ የኻሚኔይ የትዉልድ ሥፍራም ናት።የኻምኔይ አስከሬን ወደ ቀብሩ ስፍራ ከመወሰዱ ከሰዓታት በፊት የዩናይትድ ስቴትስ ጦር ርዕሠ-ከተማ ቴሕራንን ከማሻሐድ ከተማ ጋር የሚያገኛኘዉን የባቡር መስመር ጨምሮ የተለያዩ የኢራን ሰላማዊ የመሠረተ-ልማት አዉታሮችን አዉድሟል።ይሁንና በቀብር ሥርዓቱ ላይ ለመገኘት በመቶ ሺሕ የሚቆጠር የኢራን ሕዝብ የማሻሐድ ከተማን አጥለቅልቋት ነዉ የዋለዉ።ሕዝቡ በሺዓ እስልምና እምነት የብቀላ ጥሪ ምልክት የሆነዉን ቀይ አርማ እያዉለበለበ እስከ ቀብሩ ሥፍራ ድረስ ተጉዟል።

ቴሕራን-የዩናይትድ ስቴትስና የኢራን አዲስ ግጭት ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን ከትናንት በስቲያ ሌሊት የጀመሩት አዲስ ጥቃትና አፀፋ ጥቃት እስከ ዛሬ ጠዋት ድረስ እንደቀጠለ ነዉ።የዩናይትድ ስቴትስ ጦር
ቴሕራን-የዩናይትድ ስቴትስና የኢራን አዲስ ግጭት ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን ከትናንት በስቲያ ሌሊት የጀመሩት አዲስ ጥቃትና አፀፋ ጥቃት እስከ ዛሬ ጠዋት ድረስ እንደቀጠለ ነዉ።የዩናይትድ ስቴትስ ጦር ትናንት ደቡባዊና ማዕከላዊ ኢራን የሚገኙ የተለያዩ ከተሞችና ደሴቶችን ደብድቧል።የኢራን ባለሥልጣናት ዛሬ እንዳስታወቁት የአሜሪካ ጦር ትናንት ማታ በከፈተዉ ጥቃት 14 ሰዎች ገድሏል።ሌሎች 78 አቁስሏል።አንዳድ ከተሞች የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተቋርጦም ነበር።የዩናይትድ ስቴትስ ማዕከላዊ ዕዝ እንዳስታወቀዉ ጦሩ አዲስ ጥቃት የከፈተዉ ኢራን በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚተላለፉ መርከቦችን የማወክ አቅሟን ለማዳከም ነዉ። እስራኤልና ዩናይትድ ስቴትስ ባለፈዉ የካቲት ማብቂያ ኢራን ላይ ጦርነት ከመክፈታቸዉ በፊት ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን የባሕር መሥመር የሚያዉክ እርምጃ ወስዳ አታዉቅም።የአሜሪካ ጦር ትናንት በኢራን ከተሞች፣ ደሴቶችና ተቋማት ላይ የከፈተዉን ጥቃት ለመበቀል የኢራን ጦር ኃይል ዛሬ ሲነጋጋ በተለያዩ የአረብ ሐገራት የሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሠፈሮችን አጥቅቷል።የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ እንዳስታወቀዉ ጦሩ ባሕሬይንና ኩዌት የሚገኙ የዩናይትድ ስቴትስ የጦር ሠፈሮችን ደብድቧል።ወደ ዮርዳኖስም 10 ቦሊስቲክ ሚሳዮሎች ማወንጨፉን አስታዉቋል። ዮርዳኖስ በበኩሏ ጦር ኃይሏ 8 የኢራን ሚሳዬሎችን «አክሽፏል» ብላለች።የኢራን መንግሥት የሚቆጣጠረዉ አንድ ራዲዮ ጣቢያ ዛሬ ማርጃዉን እንደዘገበዉ የኢራን ጦር ባሕሬይን ባሕር ላይ የሚገኙ የዩናይትድ ስቴትስ ባሕር ሰርጓጅ መርከብንና ሌሎች የጦር መርከቦችን ደብድቧል።ዩናይትድ ስቴትስና ኢራን ከሁለት ሳምንት በፊት የተፈራረሙት የተኩስ አቁም ሥምምነት መፍረሱን የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ትናንት አስታዉቀዉ ነበር።

EANC ኤርትራ ዉስጥ የሐገሪቱ አንድነት ተጠብቆ፤ የአፋርን ጨምሮ የሐገሪቱ ነባር ብሔሮች የባሕል፣ የቋንቋ፣ የማንነት፣ የምጣኔ ሐብትና የፖለቲካ ነፃነት የተከበረባት ፌደራዊ ሥርዓት እንዲመሠረት እን
EANC ኤርትራ ዉስጥ የሐገሪቱ አንድነት ተጠብቆ፤ የአፋርን ጨምሮ የሐገሪቱ ነባር ብሔሮች የባሕል፣ የቋንቋ፣ የማንነት፣ የምጣኔ ሐብትና የፖለቲካ ነፃነት የተከበረባት ፌደራዊ ሥርዓት እንዲመሠረት እንደሚታገል አስታዉቋል።በመግለጫዉ መሠረት በ3ኛዉ የEANC ጉባኤ ላይ ከኢትዮጵያና ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጨምሮ የተለያዩ ማሕበራት፣ ድርጅቶችና የሕብረተሰብ ክፍሎችን የወከሉ ፖለቲከኞች፣ ተንታኖች፣ሙሕራን፣ ባሕላዊ መሪዎችና የሐገር ሽማግሌዎች ተካፍለዋል።

ኤርትራዉያን ዴሞክራሲያዊ ሽግግር ለማድረግ እንዲተባበሩ EANC ጠየቀ የኤርትራ አፋር ብሔራዊ ኮንግረስ (EANC) ኤርትራ ዉስጥ «በሠላማዊ መንገድ» ዴሞክራሲያዊ ለዉጥ ለማምጣት የሐገሪቱ «ዴሞክራሲያ
ኤርትራዉያን ዴሞክራሲያዊ ሽግግር ለማድረግ እንዲተባበሩ EANC ጠየቀ የኤርትራ አፋር ብሔራዊ ኮንግረስ (EANC) ኤርትራ ዉስጥ «በሠላማዊ መንገድ» ዴሞክራሲያዊ ለዉጥ ለማምጣት የሐገሪቱ «ዴሞክራሲያዊ» የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶችና የተለያዩ የሕብረተሰብ አካላት እንዲተባበሩ ጠየቀ።ኮንግረሱ የፖለቲካ ፓርቲዎቹ፣ ድርጅቶችና የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ዉይይት፣ ድርድርና መግባባታቸዉን አጠናክረዉ እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርቧልም። EANC ባለፈዉ ሳምንት አርብና ቅዳሜ ባደረገዉ 3ኛ ጉባኤዉ ማጠቃላያ ላይ ባወጣዉ መግለጫ እንዳለዉ የወደፊቷ ኤርትራ «በአምባገነን» ሥርዓት፣ «በአግላይነት» ወይም አንዱ ሌላዉን «በመጫን» ላይ ልትመሠረት አትችልም።በ8 ገፆች የተጠናቀረዉ መግለጫ ኢትርትራ ዉስጥ ሰብአዊ መብቶች፣ የተለያዩ ብሔሮች መብቶች፣ እንዲከበሩና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲሰፍን የሚደረገዉን ጥረት የተለያዩ ዓለም አቀፍ፣ አሐጉራዊና አካባቢያዊ ማሕበራትና መንግሥታት እንዲረዱ ጠይቋል። ጉባኤዉ በተለይ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ኤርትራ ዉስጥ ይደርሳል የሚባለዉን የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን መከታተሉን እንዲቀጥል ጠይቆ፣ ኤርትራ በቅርቡ የተባበሩት መንግሥታት የምጣኔ ሐብትና የማሕበራዊ ጉዳይ ምክር ቤት (ECOSOC) አባል ሆና በመመረጥዋ ያደረበትን ቅሬታ ገልጿል።ኤርትራ ዉስጥ የሚፈፀመዉን ግፍና በደል በመሸሽ ከ200 ሺሕ በላይ የኤርትራ አፋሮች መፈናቀላቸዉን ወይም መሰደዳቸዉን መግለጫዉ «አሳዛኝ» ብሎታል።

ታንዛኒያ ውስጥ ሥልጡን የውይይት መድረክ ሲጠፋ ወጣቶች እጃቸውን አጣጥፈው አልqt,ቀመጡም፥ ይልቁንስ የፖለቲካ ውይይቱን ወደ ማኅበራዊ መገናኛ መድረክ ወስደው አነቃቅተውታል ። ታንዛኒያዊው ሙዚቀኛ እና አራማጁ አርቲስት ዋካዚ ስለ ዲሞክራሲ እየተጠናከረ የመጣውን የዲጄታል ንቅናቄ እየመራ ነው #africaexplained https://pepurl.com/p/5Gmi2?maca=amh-RED-Telegram-dwcom

ኢቦላ፣ ከሞት ያመለጡት ተስፋን ይሰብካሉ፣ የገዳዩ በሽታ ሥርጭት ግን አልተገታም ምሥራቂዉ ኮንጎ አልፎ አልፎ የሚታይ ተስፋ ብልጭ ብሏል።በኢቦላ ተሕዋሲ ሥርጭት ከፉኛ የተጎዳችዉ ቤኒ ከተማ ከተሕዋሲ መፈወሷ የተረጋገጠ የመጀሪያዋ ሰዉ ተመዝግቦባታል።በሽታዉ ግን አሁንም እየተዛመተ ነዉ።የጤና ባለሙያዎችም ከተሕዋሲዉ ጋር ብቻ ሳይሆን ከፍርሐት፣ከተሳሳተ መረጃና ከጊዜ ጋር እየታገሉ ነዉ።ከኢቦላ የዳነችዉ የቤኒ ነዋሪ ማሕበረሰቡ ተስፋ እንዳይቆርጥ ትመክራለች።እሷ መዳንዋ የተረጋገጠዉ በሽታዉን ለመከላከል ባለሙያዎች በሚረባረቡበት ወቅት ነዉ።(ቪዲዮዉን ይመልከቱ)

የቀጥታ ስርጭት ማስታወቂያ የረቡዕ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ስርጭታችን የዓለም ዜና ይቀድማል። ዜናውን በሚከተለው የዜና መጽሔት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለዋጋ ንረት የሰጡት ማብራሪያ ና የ
የቀጥታ ስርጭት ማስታወቂያ የረቡዕ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ስርጭታችን የዓለም ዜና ይቀድማል። ዜናውን በሚከተለው የዜና መጽሔት የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለዋጋ ንረት የሰጡት ማብራሪያ ና የሕዝብ አስተያየት፤ ትግራይ ክልል ይካሄዳል የተባለው የወጣቶች የግዳጅ ወታደራዊ ምልመላና ይህን በመቃወም በቅርቡ ይካሄዳል የተባለው ሰልፍ፤ የኢትዮጵያን ኤኮኖሚ በሚመለከት የባለሙያዎች እይታ፤ ሀገራዊ የምክክር ጉባኤና የሕዝቡ አስተያየት እንዲሁም ባገረሸው የኢራን አሜሪካ ጦርነት ምክንያት የነዳጅ ዘይት ዋጋ ዳግም ማሻቀቡን የሚያስቃኙ ዘገባዎችን ተካተዋል። ሳምንታዊው የኤኮኖሚው ዓለም ኢትዮጵያ 5.5 ቢሊዮን ዶላር ካገኘችበት የወርቅ ገበያ ብሔራዊ ባንክ እንዲወጣ አይኤምኤፍ የሚገፋው ለምንድነው? በማለት ይጠይቃል። ሳይንስ እና ቴክኒዎሎጂ ደግሞ የሰው ሠራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ በሕግ እንዲመራ መጠየቁን ይዳስሳል። ዝግጅቶቹን ለመከታተል ከምሽቱ አንድ ሰዓት ላይ ቀጠሮአችሁ ከዶቼቬለ ጋር ይሁን

የትራምፕ ወቀሳና ዛቻ በኔቶ ጉባኤ የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት በምህጻሩ ኔቶ ጉባኤ ዛሬ በአንካራ ቱርክ ተጀምሯል። በጉባኤ ላይ የተገኙት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ
የትራምፕ ወቀሳና ዛቻ በኔቶ ጉባኤ የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል ኪዳን ድርጅት በምህጻሩ ኔቶ ጉባኤ ዛሬ በአንካራ ቱርክ ተጀምሯል። በጉባኤ ላይ የተገኙት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንደቀደሙት ጊዜያት ሁሉ የኔቶ አባል ሀገራትን ሲወቅሱ፣ በስፔይን ላይ ሲዝቱ፤ ግሪንላንድንም ሲያስፈራሩ ተሰምተዋል። ጉባኤው ከመጀመሩ አስቀድሞ ትራምፕ ከኔቶ ዋና ጸሀፊ ማርክ ሩተ ጋር በተነጋገሩበት ወቅት በኔቶ ደስተኛ አለመሆናቸውን ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። በግሪንላንድ ጉዳይ እንዲሁም ቁጥር አንድ የሽብር ደጋፊ ባሏት በኢራን ጉዳይ ሊረዱን ባለመፈለጋቸው በኔቶ ደስተኛ አይደለንም ብለዋል። ስፔይንን አስፈሪ የኔቶ አባል ሲሉ የተቹት ትራምፕ ከአሁን በኋላ ከስፔን ጋር ምንም ዓይነት የንግድ ግንኙነት አይኖረንምም ብለዋል። ትራምፕ ዛሬ ከስፔን ጋር አገራቸው የነበራትን የንግድ ግንኙነት እንደምታቋረጥ ዝተዋል። ትራምፕ አሁንም ቢሆን የኔቶ አባል የሆነችውን የዴንማርክን ግዛት ግሪንላንድ የመጠቅለል ፍላጎታቸውን ከመናገር አልተቆጠቡም። ግሪንላንድ ለኛ በጣም አስፈላጊ ስትሆን ለዴንማርክ ግን አስፈላጊ አይደለችም ያሉት ትራምፕ አሁንም እንደሚፈልጓት አጽንኦት ሰጥተዋል። «እኛ የምንፈልጋት ለዩናይትድ ስቴትስ ብቻ ሳይሆን ለዓለም ጥበቃ ለማድረግ ነው» በማለት ትራምፕ «ግሪንላንድን መያዝ እኛን ይረዳናል ለዴንማርክ ግን የሚፈይደው አይኖርም» ሲሉም ሞግተዋል። የኔቶ ዋና ፀሀፊ ማርክ ሩተ እየጨመረ በመጣው የዩናይትድ ስቴትስ ግሪንላንድን የመጠቅለል ፍላጎት ላይ ለመነጋገር ሁለቱ ሀገራት ስምምነት ላይ እንዲደርሱ አሳስበዋል። ይሁንና የዴንማርክ ጠቅላይ ሚኒስትር ሜተ ፍሬድሪክሰን በበኩላቸው ግሪንላንድ «ለሽያጭ እንደማትቀርብ» ኮፕንሀገን ግልጽ አድርጋለች ብለዋል።

DW Amharic - Статистика та аналітика Telegram каналу @dw_amharic