ru
Feedback
DW Amharic

DW Amharic

Открыть в Telegram

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала DW Amharic

Канал DW Amharic (@dw_amharic) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 54 903 подписчиков, занимая 4 905 место в категории Новости и СМИ и 582 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 54 903 подписчиков.

Согласно последним данным от 29 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 123, а за последние 24 часа — -7, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Верифицирован (официально подтверждён Telegram)
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 7.91%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 5.57% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 340 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 3 056 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 0.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 30 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Новости и СМИ.

54 903
Подписчики
-724 часа
+417 дней
+12330 день
Архив постов
ሪያድ-ሳዑዲ አረቢያ ቀይ ባሕርን የሚጠብቅ ወታደራዊ ትብብር ልትመሰርት ነዉ። ሳዑዲ አረቢያ የቀይ ባሕር መስመርን ከሁቲዎች ጥቃት የሚከላከል ዓለም አቀፍ የጦር ኃይል ትብብር ልትመሠርት ነዉ።የሳዑዲ
ሪያድ-ሳዑዲ አረቢያ ቀይ ባሕርን የሚጠብቅ ወታደራዊ ትብብር ልትመሰርት ነዉ። ሳዑዲ አረቢያ የቀይ ባሕር መስመርን ከሁቲዎች ጥቃት የሚከላከል ዓለም አቀፍ የጦር ኃይል ትብብር ልትመሠርት ነዉ።የሳዑዲ አረቢያ ባለሥልጣናት «የመቅዘፍን ነፃነት» የሚያስከብር ያሉት የተሻራኪ ሐገራት ጦር ኃይል በቀይ ባሕር ላይ የሚቀዝፉ መርከቦችን ከጥቃት ይከላከላል።በኢራን ይደገፋሉ የሚባሉት የየመን ሁቲዎች ካለፈዉ ሳምንት ጀምሮ የሳዑዲ አረቢያ መርከቦች በቀይ ባህሩ የባብ ኤል መደብ ወሽመጥ በኩል እንዳይልፉ አግደዋል።ሁቲዎች ምናልባትም ወሽመጡን ማቋረጥ የሚፈልጉ መርከቦችን ግብር ሳያስከፍሉ አይቀርም እየተባለ ነዉም።ሳዑዲ አረቢያ አሁን የምታስተባብረዉ ዓለም አቀፍ የባሕር ኃይል፣ የሁቲዎችን እርምጃ የሚያመክን ነዉ።አል ሞኒተር የተባለዉ የአምደ መረብ የዜና ምንጭ እንዳስታወቀዉ እስካሁን ድረስ ግብፅ፣ጅቡቲና ሱዳን ጦር ለማዋጣት ፈቃደኛ ናቸዉ።ፓኪስታን፣ ቱርክ፣ ጀርመን፣ ፈረንሳይና ኢጣሊያን ጨምሮ የተለያዩ የአዉሮጳ ሐገራት ትብብሩን ይቀየጣሉ ተብሎ ይጠበቃል።የራስዋን ሰላም በአፍሪቃ ሕብረት ጦር ድጋፍም ማስከበር ያቃታት ሶማሊያም ጦር ያዋጣሉ ከሚባሉት ሐገራት አንዷ ናት። የሳዑዲ አረቢያ የመከላከያ ሚንስትር ልዑል ኻሊድ ቢን ሠልማን የዩናይትድ ስቴትስን ፈ,ቃድ ለማግኘት ትናንት ዋሽንግተን ዉስጥ ከፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕና ከምክትላቸዉ ጄዲ ቫንስ ጋር ተነጋግረዋል።ዩናይትድ ስቴትስ የትብብሩ አባል እንደምትሆን የዋሽግተን ባለሥልጣናት ፍንጭ ሰጥተዋል።ኢራንን ለመዉጋት 38 ቢሊዮን  ዶላር ያወጣዉ የትራምፕ አስተዳደር ሶማሊያ ለሰፈረዉ የአፍሪቃ ሕብረት ሠራዊት (AUSSOM) የሚያደርገዉን የገንዘብ ድጋፍ ከመጪዉ ጥር ጀምሮ ለማቋረጥ ወስኗል።

ሐምሌ 23 ቀን 2018።ጤና ይስጥልኝ እንደምን ዋላችሁ። የዛሬዉ ሥርጭታችን ሁሌም እንደሚሆነዉ የዓለም ዜናን ያስቀድማል።ዜናዉን የሚለጥቀዉ የዜና መጽሔት ጥንቅራችን የሚከተሉትን ርዕሶች ያስተነትናል።
ሐምሌ 23 ቀን 2018።ጤና ይስጥልኝ እንደምን ዋላችሁ። የዛሬዉ ሥርጭታችን ሁሌም እንደሚሆነዉ የዓለም ዜናን ያስቀድማል።ዜናዉን የሚለጥቀዉ የዜና መጽሔት ጥንቅራችን የሚከተሉትን ርዕሶች ያስተነትናል።-- -የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ የመረጃ ተደራሽነት ላይ የተሰጡ አስተያየቶች። -የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ጉባኤና የሌሎች ሀገሮች ተሞክሮ። -የአፍሪካ ኀብረት በሶማሊያ ያለው ሚና ወደ ፖለቲከዊ ተልዕኮ እንዲሸጋገር መጠየቁ። -በድሬደዋ በ2.2 ቢሊየን ብር አዳሪ ትምህርት ቤትን ጨምሮ የተለያዩ የትምህርት ተቋማት ግንባታ በመካሄድ ላይ መሆኑ። -የጣና ሀይቅን በከፊል የሸፈነዉ የእንቦጭ አረም፣ የአካባቢውን አሳ አጥማጆችና የውሃ ትራንስፖርት አገልጋዮችን ኑሮ ማወኩን ነዋሪዎች አስታወቁ። -አዉሮጳ የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያንና ትዉልደ ኢትዮጵያዉያን አመታዊ የስፖርትና የባሕል ትርዒት--ናቸዉ። ሳምንታዊዉ የባሕል መድረክ ከጀርመን ዩንቨርስቲ በዶክትሪት ድግሪ የተመረቀዉን ኢትዮጵያዊ የገበሬ ልጅ ማንነተንና ሥራዉን ያስተዋዉቀናል።ከሥርጭታችን ጋር መልካም ቆይታ።

የተለያዩ-የዩናይትድ ስቴትስና የኢራን ዉጊያ እንደቀጠለ ነዉ የዩናይትድ ስቴትስ ጦር ሌሊቱን የተለያዩ የኢራን ግዛቶች፣ የጦር ሠፈሮችና ተቋማትን መደብደቡን አስታወቀ። የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENT
የተለያዩ-የዩናይትድ ስቴትስና የኢራን ዉጊያ እንደቀጠለ ነዉ የዩናይትድ ስቴትስ ጦር ሌሊቱን የተለያዩ የኢራን ግዛቶች፣ የጦር ሠፈሮችና ተቋማትን መደብደቡን አስታወቀ። የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ (CENTCOM) እንዳስታወቀዉ ጦሩ ለሁለት ተከታታይ ሰዓታት በሰነዘረዉ ጥቃት የኢራን እስላማዊ አብታዊ ዘብ ጦር ሠፈርን፣ የሚሳዬል ማምረቻና ማወንጨፊያ ሥፍራዎችን ደብድቧል።የዜና ምንጮች እንደዘገቡት ግን የአሜሪካ ጦር በተለይ ቀሼም ደሴት የሚገኝ የመኖሪያ ሕንፃን ደብድቦ ባልና ሚስትን ከ2 ዓመት ሕጻን ልጃቸዉ ጋር ገድሏል።የኢራን ባለሥልጣናት በበኩላቸዉ የአሜሪካ ጦር ዛንጅን ግዛት በከፈተዉ ጥቃት ሶስት የእስላማዊ አብታዊ ዘብ ባልደረቦችን ገድሏል።የዩናይትድ ስቴትስ ጦር ከሁለቱ አካባቢዎች በተጨማሪ ኪሽ ደሴትን፣ ቡሸርና የኢራን የነዳጅ ማዕከል የምትባለዉ የኹዜስታን ግዛትን ድብድቧል።ኢራን ኩዌት ላይ በከፈተችዉ አፀፋ ጥቃት ቢያንስ አንድ ሰዉ ገድላለች።የኢራን ጦር ዛሬ ሲነጋጋ በርካታ ሚሳዬሎችን ወደ ዮርዳኖስ ማወንጨፉን የዮርዳኖስ ባለሥልጣናት አስታዉቀዋል።ሚሳዬሎቹ ያደረሱት ጉዳት ሥለመኖር አለሞሩ ግን የአማን ባለሥልጣናት ያሉት ነገር የለም።

ኪቭ/ዎርሶ-ሩሲያ ዩክሬንን መደብደቧን እንደቀጠለች ነዉ የሩሲያ ጦር የዩክሬን ርዕሠ-ከተማ ኪቭን ጨምሮ የተለያዩ የሐገሪቱን ከተሞችና ግዛቶች በቦለስቲክ ሚሳዬልና በሰዉ አልባ አዉሮፕላኖች ሲደበድብ አ
ኪቭ/ዎርሶ-ሩሲያ ዩክሬንን መደብደቧን እንደቀጠለች ነዉ የሩሲያ ጦር የዩክሬን ርዕሠ-ከተማ ኪቭን ጨምሮ የተለያዩ የሐገሪቱን ከተሞችና ግዛቶች በቦለስቲክ ሚሳዬልና በሰዉ አልባ አዉሮፕላኖች ሲደበድብ አደረ።ሩሲያ ለሌቱን ያዘነበችዉ የሚሳዬልና የሰዉ አልባ አዉሮፕላን ወዠቦ ዩክሬንን ከፖላንድ ጋር የሚያዋስኑ ከተሞችና መንደሮችን ጭምር አጋይቷል።ጥቃቱን በመፍራት በአስር ሺሕ የሚቆጠሩ የርዕሠ ከተማ ኪቭ ነዋሪዎች ቤታቸዉን ጥለዉ ምድር ዉስጥ በሚገኙ የባቡር ጣቢያዎች ለማደር ተገድደዋል።በጥቃቱ 8 ሰዎች ሲገደሉ፣ ሌሎች ሐምሳ ሰዎች ቆስለዋል።የሩሲያ ጦር የተኮሰዉ ሚሳዬል የዩክሬን ድንበርን አልፎ አንድ የፖላንድ መንደር አጠገብ ማረፉ የዎርሶ ባለሥልጣናት አስታዉቀዋል።ሚሳዬሉ ገላጣ ሥፍራ በማረፉ በሰዉ ላይ ያደረሰዉ ጉዳት የለም።ሩሲያ የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (NATO) አባል የሆነችዉ የፖላንድ አየር ክልልን መጣስዋን የራስዋ የፖላንድ፣የጦር ተሻራኪዉ ድርጅትና የአዉሮጳ ሕብረት አዉግዘዉታል።

ካይሮ-ግብፅ ወደብ ላይ የነበሩ መርከቦች የተመቱት በድሮን መሆኑ ተነገረ ሜድትራኒያን ባሕር ጠረፍ በሚገኘዉ ዳሚታ በተባለዉ የግብፅ ወደብ የቆሙ መርከቦች ትናንት በሰዉ አልባ አዉሮፕላን (ድሮን) መመ
ካይሮ-ግብፅ ወደብ ላይ የነበሩ መርከቦች የተመቱት በድሮን መሆኑ ተነገረ ሜድትራኒያን ባሕር ጠረፍ በሚገኘዉ ዳሚታ በተባለዉ የግብፅ ወደብ የቆሙ መርከቦች ትናንት በሰዉ አልባ አዉሮፕላን (ድሮን) መመታታቸዉን የሐገሪቱ ካቢኔ አስታወቀ።ሁለቱ የጋስ ማጠራቀሚያ መርከቦች ትንናት በእሳት መቃጠላቸዉን የግብፅ ባለሥልጣናት አስታዉቀዉ ነበረ።«ተንሳፋፊ የጋስ ማጠረቀሚያ» የሚባሉት ሁለቱም መርከቦች የዩናይትድ ስቴትስ ናቸዉ። የግብፅ ካቢኔ ዛሬ እንዳስታወቀዉ የቃጠሎዉ መንስኤ ከሁለቱ መርከቦች አንዱ በሰዉ አልባ አዉሮፕላን በመመታቱ እንደሆነ «የመጀመሪያ» ባለዉ ምርመራ አረጋግጧል።ጥቃቱን ሥላደረሰዉ ወገን ማንነት ካቢኔዉ በግልፅ አላስታወቀም፣ እስካሁን ሐላፊነቱን የወሰደ ወገንም የለም።የጦር፣ የፖለቲካ ጉዳይ ተንታኞችና የዜና ምንጮች ግን ጥቃቱን ያደረሱት በዩናይትድ ስቴትስና በተባባሪዎችዋ ሐገራት ጦር የሚጠቁት ኢራን ወይም ተባባሪዎችዋ ሊሆኑ ይችላሉ።እስራኤልና ዩናይትድ ስቴትስ በኢራን ላይ ጦርነት ከከፈቱ ካለፈዉ የካቲት ወዲሕ ከየመን እስከ ሊባኖስ፣ ከፋርስ ባሕረ-ሠላጤ አካባቢ ሐገራት እስከ ዮርዳኖስና ኢራቅ የሚገኙ የአረብ ሐገራት የተፋላሚ ወገኞች የጥቃት ኢላማ ሲሆኑ ግብፅ ግን የደረሰባት ጥቃት አልነበረም።ያሁኑ ጥቃት ግን ብዙዎች ከጦርነቱ በፊት በተደጋጋሚ እንዳስጠነቀቁት ጦርነቱ እድማሱን የማስፋቱ ምልክት ተደርጓል።ጥቃቱ የግብፁን የስዊስ ቦይን እንደ ሆርሙዝና እንደ ባብ ኤል መንደብ ወሽመጦች ሊያዘጋዉ ይችላል የሚል ሥጋትም አሳድሯል።

አዲስ አበባ-የኢትዮጵያ ፖሊስ «የሰዎች አዘዋዋሪዎች መሪ» ያለዉን ግለሰብ መያዙን አስታወቀ የኢትዮጵያ የፌደራል ፖሊስ ከማላዊ ፖሊስና ከኢንተርፖል ጋር በመተባበር በኢትዮጵያዉን ወጣቶች ላይ «ከባድ
አዲስ አበባ-የኢትዮጵያ ፖሊስ «የሰዎች አዘዋዋሪዎች መሪ» ያለዉን ግለሰብ መያዙን አስታወቀ የኢትዮጵያ የፌደራል ፖሊስ ከማላዊ ፖሊስና ከኢንተርፖል ጋር በመተባበር በኢትዮጵያዉን ወጣቶች ላይ «ከባድ ኢሰብአዊ ድርጊት ሲፈጽም ነበር» ያለዉን ተጠርጣሪ መያዙን አስታወቀ።ፖሊስ ዛሬ በማሕበራዊ መገናኛ ዘዴ ባሰራጨዉ ዘገባ እንዳለዉ አድነዉ ባሻዉ ዉዳሞ የተባለዉ ተጠርጣሪ ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ከሐድያና ከከንባታ ዞኖች በርካታ ወጣቶችን እያታለለ ወደ ደቡብ አፍሪቃ ሲያሻግር ነበር።ፖሊስ «አደገኛ» ያለዉ አድነዉ ባሻዉ ዉዳሞና ተባባሪዎቹ፣ ወጣቶችን በኬንያ በኩል የተለያዩ የደቡባዊ አፍሪቃ ሐገራትን አቋርጠዉ ደቡብ አፍሪቃ ለማስገባት ከእያንዳዳቸዉ ከ600ሺሕ እስከ 800 ሺሕ ብር ይቀበሉ እንደነበር በመረጃ ማረጋገጡን ፖሊስ አስታዉቋል።በዘገባዉ መሠረት፣ ተጓዦቹ ጋንቦ ከተባለዉ ጫካ ጀምሮ በየደረሱበት በረሐብና ዉሐ ጥም ይሰቃያሉ።ተጠርጣሪዎቹ፣ ወጣቶቹን በሕገ-ወጥ መንገድ ናይሮቢ ከተማ ካስገቡ በኋላ፣« በአንድ ክፍል ውስጥ በማጎር፣ ከቤተሰቦቻቸው ተጨማሪ ገንዘብ እንዲያስልኩ ያስገድዳሉ፤ ገንዘብ ማስላክ ያልቻሉትን በኤሌክትሪክ ንዝረት ጭምር እያሰቃዩ» እስከ 100 ሺሕ ብር የሚደርስ ተጨማሪ ገንዘብ ያስከፍላሉም።የኢትዮጵያ ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ለመያዝ ከ2015 ጀምሮ ከኢንተርፖል ጋር በመተባበር ሲከታተል እንደነበረ አስታዉቋል።የማላዊ ፖሊስ ዋነኛዉን ተጠርጣሪ አድነዉ ባሻዉ ዉዳሞን ይዞ ትናንት ለኢትዮጵያ ፖሊስ ማስረከቡን የኢትዮጵያ ፈደራል ፖሊስ አስታዉቋል።