cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

Wasu Mohammed(ዋሱ መሀመድ)

እንኳን ደህና መጡ‼ ✔ማስታወቂያ ለማሰራት እና ጥቆማ ለመስጠት በዚህ ይጠቀሙ ☞https://t.me/WasuMohammed ✔ ቻናሉን ለመቀላቀል Join ☞http://t.me/Wasulife ከልብ አመሰግናለሁ♥🙏

Більше
Рекламні дописи
202 545Підписники
-59824 години
-2 6027 днів
-1 68530 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

ቡርኪናፋሶ ቢቢሲ እና ቪኦኤን ጨምሮ ከሰባት በላይ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችን አገደች። ምዕራብ አፍሪካዊቷ ቡርኪናፋሶ ከሰባት በላይ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎችን አግዳለች። ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ሂውማን ራይትስ ዋች የቡርኪና ፋሶ ጦር 50 ህጻናትን ጨምሮ 223 ንጹሀንን ገድሏል ሲል ሪፖርት አውጥቷል። ይህንን ሪፖርት መነሻ በማድረግም በቡርኪና ፋሶ ያሉ ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች ዋቢ አድርገው ዘገባ የሰሩ ሲሆን የሀገሪቱ መንግስትም እገዳ ጥሎባቸዋል፡፡ በቡርኪና ፋሶ መንግስት እገዳ ከተጣለባቸው ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች መካከልም ቪኦኤ፣ ቢቢሲ፣ ለሞንዴ፣ ዘ ጋርዲያን፣ ዶቸቪሌ፣ ቲቭ5 ሞንዴ ኦስት ፍራንስ፣ ኤፒ እና ሌሎችም ተጠቃሽ ናቸው፡፡ በቡርኪና ወታደራዊ መንግስት እገዳ የተጣለባቸው ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች እስካሁን በጉዳዩ ዙሪያ ያወጡት መግለጫ የለም፡፡ ማሊ፣ ኒጀር እና ቡርኪና ፋሶ የአጋርነት ስምምነት ተፈራረሙ የቡርኪና ፋሶ መንግስት በሚዲያዎቹ ላይ እገዳ የጣለው የሀገሪቱን ጦር ስም አጠልሽታችኋል በሚል ሲሆን የሂዩማን ራይትስ ዋች ሪፖርትንም ውድቅ አድርጓል፡፡ በመፈንቅለ ስልጣን ስልጣን የተቆጣጠረው የወቅቱ የቡርኪናፋሶ ወታደራዊ መንግስት ከምዕራባዊን ሀገራት ጋር ያለውን ግንኙነት በየጊዜው በማቋረጥ ላይ ሲሆን እንደ ዓለም ባንክ እና አይኤምኤፍ ያሉ አበዳሪ ተቋማትም ግንኙነታቸውን አቋርጠዋል፡፡ አፍሪካ ህብረት እና የምዕራብ አፍሪካ የኢኮኖሚ ማህበረሰብ ወይም ኢኮዋስ ቡርኪናፋሶን ጨምሮ መፈንቅለ መንግስት ያደረጉት ማሊ እና ኒጀርንም ከአባልነት ሲያግድ ሀገራቱ በምላሹ ከኢኮዋስ አባልነት መውጣታቸውን አስታውቀዋል፡፡via Alain ======================== አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 ማስታወቂያና ጥቆማ 👇መቀበያ https://t.me/wasumohammed
Показати все...
👍 33 3😱 2
የአውሮፓ ህብረት ምክር ቤት ለኢትዮጵያውያን በጊዜያዊነት ወደ አውሮፓ የመግቢያ ቪዛ ፈቃድ መስጠት የሚከልክል ውሳኔ ማሳለፉ ተሰማ። ለክልከላው የሰጠው ምክንያት ከኢትዮጵያ መንግስት በቂ ትብብር እያገኘሁ ባለመሆኑ ነው ብሏል። በተጨማሪም የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን እዚህ ውሳኔ ላይ ያደረሰው በህብረቱ ሀገራት በህገወጥነት በሚቆዩ ኢትዮጵያውያን ዜጎች ዙሪያ ከሀገሪቱ መንግስት በቂ ትብብር እያገኘሁ ባለመሆኑ ነው ብሏል። በዚህም የህብረቱ ለአባል ሃገራት ከዚህ በኋላ ኢትዮጵያውያን ቪዛ አመልካቾች ቪዛ ሲፈልጉ አስፈላጊ ሰነዶችን እንዲያቀርቡ እና በአውሮፓ ህብረት ህግ የተቀመጠውን መደበኛ መስፈርቶች እንዲያሟሉ እንደሚገደዱ ተጠቁሟል። አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 ማስታወቂያና ጥቆማ 👇መቀበያ https://t.me/wasumohammed
Показати все...
👍 17 5😱 2🎉 2
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ። የ2016 የትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆኗል። የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሐምሌ 3 እስከ ሐምሌ 5 ለማህበራዊ ሳይንስ ፤ ከሐምሌ  9 እስከ ሐምሌ 11/2016 ዓ/ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች በበይነ መረብ (Online) እና በዩኒቨርሲቲ ውስጥ በወረቀት ይሰጣል። በወረቀት ላይ የሚፈተኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ከሰኔ 30 እስከ ሐምሌ 01/2016 ዓ/ም እንዲሁም የተፈጥሮ ሳይንስ ከሐምሌ 6 እስከ 7/2016 ዓ/ም ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡ ይሆናል።  መረጃው የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ነው።
Показати все...
👍 30 5😢 3😱 2
ADVERTISMENT መልካም ዜና ለፓስፖርት አመልካቾች ሰሞኑን በተደረገ የዳሰሳ ጥናት መሰረት ኢሚግሬሽን ፓስፖርት አልደረሰንም ብለው ቅሬታ ከሚያቀርቡት 50 በመቶ የሚሆኑት ፓስፖርታቸው የደረሰ ግን ስልክ በትክክል ሳይሞሉ ቴክስት ያልገባላቸው ወይም ከወጡት ዝርዝር ውስጥ ስማቸውን ባግቡ ያላዩ ናቸው። በርግጥ በ￶ዚ አመት ብቻ ከ 700ሺ በላይ እንደመታተሙ የኢሚግሬሽን ቻናል እራሱ ከ 120 በላይ ዝርዝር እንደመኖሩ ከዛ ሁሉ ዝርዝር ፈልጎ ማግኘት ከባድ ሊሆን ይችላል. . . ወጣቶች ሰብሰብ ብለው ዛሬ አንድ መፍትሄ ይሰጣል ያሉትን መተግበሪያ ይፋ አድርገዋል። መተግበሪያው ስም ወይም request number በመጠቀም ብቻ በዚ አመት ከታተሙት ውስጥ መኖሩን አለመኖሩን እና የታተመበትን ቀን ይነግራል። መተግበሪያውን ለራስ አገልግሎት ለመጠቀም ነፃ ሲሆን የብዙ ሰዉ ቼክ ለማድረግ እና ለረጅም ጊዜ ለመጠቀም ግን ክፍያ ይኖረዋል።
Показати все...
👍 33👏 3 2
በሚዛን ቴፒ ሆስፒታል በስድስት ወራት በደም እጦት 20 እናቶች ህይወታቸውን አጥተዋል ተባለ። በሚዛን ቴፒ #ሆስፒታል በስድስት ወራት ውስጥ በደም እጦት ምክንያት 20 እናቶች በሆስፒታል እያሉ ህይወታቸውን ማጣታቸው ተገለጸ። ሆስፒታሉ የደም፣ የመድሃኒት፣ ኦክስጅንና ለምርመራ የሚያግዙ ኬሚካሎች እጥረት እንዳለበትም ተገልጿል። በሚዛን ከተማ በሆስፒታል በደም እጥረት ከሚሞቱ እናቶች በተጨማሪ ሆስፒታል ሳይመጡ የሚሞቱም በርካቶች ናቸው ሲሉ የዞኑ ዋና አስተዳደሪ አቶ ሀብታሙ ካፍተን መናገራቸውን ከኢፕድ ያገኘነው መረጃ ያሳያል። በዞኑ የህዝቡን ጤንነት ለመጠበቅ የሆስፒታል እጥረት ከፍተኛ ችግር መሆኑን አስተዳዳሪው ገልጸዋል ያለው ዘገባው ህዝቡ ባለፉት ሶስት አመታት በወባ ወረርሽኝ ውስጥ በመሆኑ ሆስፒታሉ በታካሚዎች እየተጨናነቀ የሚገኝ በመሆኑ የሚመለከተው አካል ችግሩን ሊቀርፍ ይገባል ሲሉ ማሳሰባቸውን አስታውቋል። ደም ከለጋሾች ቢሰበሰብም የደም ባንክ ባለመኖሩ በደም እጥረት ምክንያት የበርካቶች ህይወት እየጠፋ ይገኛልሲሉ በሚዛን ቴፒ ዩኒቨርስቲ የሚዛን ቴፒ ማስተማሪያ ሆስፒታል ድንገተኛ ህክምና መስጫ ዶክተር ሲሳይ መንግስቱ መናገራቸውንም አመላክቷል። የሚመለከተው አካል ችግሩን ግምት ውስጥ በማስገባት ሆስፒታሉ ድጋፍ ሊደረግለት እንደሚገባ ሜዲካል ዳይሬክተሩ ጥሪ አቅርበዋል። ሆስፐታሉ በአዋቂዎች ድንገተኛ ህክምና ብቻ በቀን ማስተናገድ ከሚችለው ከ60 እስከ 70 በላይ ታካሚዎችን እያስተናገደ ነው። ሆስፒታሉ በ1978 አ.ም ሲገነባ ለ60 ሺ ህዝብ አገልግሎት እንዲስጥ ታስቦ ሲሆን አሁን ላይ ከሁለት ነጥብ አምስት ሚሊዮን ህዝብ በላይ አገልግሎት እየሰጠ ነው ብለዋል። በዚህም በአንድ አልጋ ከሁለት እስከ ሶስት ህጻናት በአንድ ላይ ተኝተው እየታከሙ ነው። የጽኑ ህሙማን ህክምና መስጫ እጥረት በመኖሩም ጽኑ ህክምና ሊገቡ የሚገባቸው ገብተው መታከም አልቻሉም ነው ያሉት። በሆስፒታሉ ከሚገኙ ማሽኖች ውስጥ አብዛኛዎቹ በግብአት እጥረት ምክንያት አገልግሎት አይሰጡም ነው ያሉት።
Показати все...
👍 28😢 8😱 5 4👏 3
ADVERTISMENT አፖርትመንት ላይ በአራቱም አቅጣጫ ግድግዳ share የማያደርግ ቤት አይተው ያውቃሉ ?🤔 👉DMC Real Estate ለሽያጭ ካወጣቸው ቤቶች መካከል 148 ካሬ ላይ ያረፈው ባለ ሁለት መኝታ ቤት ምንም አይነት ግድግዳ share አያደርግም። በተጨማሪ ቤቱ service quarter በሚባል የግንባታ መርህ የተሰራ ስለሆነ ከውጭ ከሚመጡ አላስፈላጊ ድምፅ ይከላከላል ከprivacy አንፃርም ተመራጭ ነው። 65,000 ካሬ ላይ ባረፈዉ ሰፊ መንደር ከstudio እስከ 4 መኝታ ድረስ በፈለጉት የካሬ አማራጭ ከምቹ አከፋፈል ጋር እንዲሁም 50/50 የባንክ አማራጮችን አዘጋጅተናል Tip:- ፈጥነው ከመጡ 2ኛ እና 3ኛ floor ላይ ማግኘት ይችላሉ! ታድያ ምን ይጠብቃሉ ቀድሞ የመጣ ቀድሞ ይስተናገዳል  እንዲሉ ዛሬ ነገ ሳይሉ አሁንኑ👇         ☎️ 0977019814                     ☎️ 0961396467 በመደወል ይመዝገቡ
Показати все...
👍 6🥰 2👏 2 1
በአዲስ አበባ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ የ4 ሰዎች ሕይወት አለፈ በአዲስ አበባ ከተማ ዛሬ ንጋት ላይ በጣለው ዝናብ ሳቢያ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 11 ወረገኑ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የ4 ሰዎች ሕይወት አልፏል። የከተማ አስተዳደሩ ማስተር ፕላናቸውን ያልተከተሉ የወንዝ ዳርቻ ግንባታዎች ሕብረተሰቡን ለጎርፍ አደጋ እንደሚያጋልጡ በጥናት መለየቱ ተገልጿል፡፡ ይህንን የአደጋ ስጋትና ተጋላጭነት በመሠረታዊነት የሚፈቱ ፕላኑን የጠበቁ ዘላቂ የመፍትሄ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም ተጠቁሟል፡፡ በመሆኑም ተመሳሳይ አደጋዎች እንዳያጋጥሙ ከከተማ አስተዳደሩ እና ከእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የሚተላለፉ የጥንቃቄ መልዕክቶች ተግባራዊ እንዲደረጉ ጥሪ መቅረቡን የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡ ኤፍ ቢ ሲበመዲናዋ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ የ4 ሰዎች ሕይወት አለፈ በአዲስ አበባ ከተማ ዛሬ ንጋት ላይ በጣለው ዝናብ ሳቢያ በተከሰተ የጎርፍ አደጋ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 11 ወረገኑ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የ4 ሰዎች ሕይወት አልፏል። የከተማ አስተዳደሩ ማስተር ፕላናቸውን ያልተከተሉ የወንዝ ዳርቻ ግንባታዎች ሕብረተሰቡን ለጎርፍ አደጋ እንደሚያጋልጡ በጥናት መለየቱ ተገልጿል፡፡ ይህንን የአደጋ ስጋትና ተጋላጭነት በመሠረታዊነት የሚፈቱ ፕላኑን የጠበቁ ዘላቂ የመፍትሄ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝም ተጠቁሟል፡፡ በመሆኑም ተመሳሳይ አደጋዎች እንዳያጋጥሙ ከከተማ አስተዳደሩ እና ከእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የሚተላለፉ የጥንቃቄ መልዕክቶች ተግባራዊ እንዲደረጉ ጥሪ መቅረቡን የኮሚሽኑ መረጃ ያመላክታል፡፡ ኤፍ ቢ ሲ
Показати все...
👍 1😢 1💔 1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ልዑካን ቡድናቸው በዓለም አቀፉ የልማት ማኅበር (አይ ዲ ኤ) 21ኛ የማሟያ ጉባኤ ላይ ለመገኘት ናይሮቢ ኬንያ ገብተዋል። ጉባኤው ማኅበሩ ደጋፊዎች እና ተባባሪ አካላት በአፍሪካ የልማት የገንዘብ ድጋፍ ቀዳሚ የትኩረት መስኮችን ለማመላከት እና አፅንዖት ለመስጠት ያለመ ነው ተብሏል። የገንዘብ ድጋፍ አቅራቢዎች በ21ኛው የማኅበሩ ዘመን ድጋፋቸውን ለመጨመር በፅኑ እንዲያጤኑ የማሳሰብ አላማ ያነገበም መሆኑ ተገልጿል። ይህ ድጋፍ የአፍሪካን የልማት ተግዳሮቶች እና መልካም ዕድሎች በተገቢው መንገድ ለማስተናገድ እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
Показати все...
👍 24😁 6 5🤣 3😱 2
ADVERTISMENT አፊያ ሙሀመድ ከፍተኛ የባህል ሕክምና እና ዘመናዊ የዋግምት አገልግሎት   የምንሰጣቸው የባህል ህክምናዎች ➢ ለውጭና ለውስጥ ኪንታሮት ➢ ለማድያት ➢ ለሱኳር በሽታ ➢ለጉበት(ለወፍ በሽታ) ➢ለጨጎራ ህመም ➢ለስፈተወሲብ ➢ለደም ግፊት ➢ለአስም ወይም ሳይነስ ➢ለሚጥል በሺታ ➢ ለእሪህና ቁርጥማት ➢ለራስ ህመም (ማይግሪን) ➢ለቺፌ ና ለጭርት ➢ለቋቁቻና ፎረፎር ➢ለእጢና ለእባጭ ➢ለወገብ ህመም ➢ለመካንነት ለወድም ለሴትም ➢ለጆሮና ለአይን ህመም ➢ለሆድ ህመም ➢ዘመናዊ የዋግምት አገልግሎት በተቋማችን እንሰጣለን። 👉ከኢትዮጵያ ባህላዊ ህክምና አዋቂዎች ማህበር በዘርፉ ህጋዊ የባህል ህክምና ፍቃድ ያለን ነን። አድራሻ:አዲስ አበባ አየር ጤና    ስልክ ቁጥር   📲0927506650                          📲0987133734                          📲0956522222 ቴሌግራም ቻናላችን https://t.me/+08vmUP_ntvE5NmM0
Показати все...
👍 10🥰 3 2
ተመራማሪዎች በቀን ውስጥ ለተወሰነ ጊዜ የእግር ጉዞ ማድረግ የአዕምሯችንን አቅም ለማሳገድ እንደሚረዳ አስታወቁ። አዲስ የተሰራ የኒውሮሳይንስ ጥናት እንዳመለከተው ከሆነ ለ20 ደቂቃ የእግር ጉዞ ማድረግ የአዕምሯችን አዲስ መረጃ ለመውሰድና ለመያዝ እንዲዘጋጅ ያደርገዋል። በተለይም ውሳኔ ለመስጠት፣ ጭንቀትን ለመቆጣጠርና፣ በባህሪያችን ዙሪያ የሚያቅደው የአእምሯችን ክፍል ላይ አዎንታዊ ተጽእኖ እንዳለው ነው ተመራማሪዎች ያስታወቁት። ሌሎች አይነት የአካል ብቃት እንቅስቃሴዎች የአዕምሮ ጤናን ለመጠበቅ እንዲመረዱ የሚታወቅ ቢሆንም፤ ይህኛው ጥናት ግን የግር ጉዞ እና የየእምሮ አቅም ላይ ትኩረትን ያድረገ እንደሆነም አስታውቀዋል። በዚህም በቀን ለ20 ደቂቃ እና ከዚያ በላይ የእግር ጉዞ ማድረግ የአእምሮን አቅም እንደሚያሳድግ እና ምንም እንቅስቃሴ ካለማድረግ የተወሰነ የእግር ጉዞ ማድረግ እንደሚሻልም ጥናቱ አመላክቷል። የሳንፎርድ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ጥናቱን ባከናወኑበት ወቅት ተሳታፊዎች የእግር ጉዞ የሚያደርጉ እና የማያደርጉን በመለየት ክትትል ያደረጉ ሲሆን፤ በዚህም ለ20 ደቂቃ የእግር ጉዞ የሚያደርጉ ሰዎች ተቀምጠው ከሚውሉት የተሻለ ሆነው ተገኝተዋል። ተመራማሪዎች የአእምሮ እንቅስቃሴን በኤሌክትሮኤንሴፋሎግራፊ (ኢኢጂ) መለካት ምን እየተፈጠረ እንዳለ የተመለከቱ ሲሆን፤ በዚህም የእግር ጉዞ የሚያደርጉ ሰዎች ላይ ተጨባጭ እና አወንታዊ ተፅእኖዎችን አይተዋል። የትላልቅ የቴክኖሎጂ ኩባንያ መስራችና ባለቤቶች ከመቀመጥ ይልቅ እየተራመዱ ስብሰባ ማድረግን እንደሚመርጡም ጥናቱ ለአብነት አስቀምጧል። ከእነዚህም ውስጥ የፌስቡክ መስረችና ባለቤት ማርክ ዙከርበርግ እና የአፕል ኩባያው ስቲቭ ጆብስ ስብሰባን ቁጭ ብሎ ከማድረግ ይልቅ እየተራመዱ ማካሄድን በማበረታታት ይታወቃሉ ተብሏል። የዘመናዊ መድሃኒት አባት ተብሎ የሚታወቀው ሂፖክራትስም የእግር ጉዞ “የሰው ልጆች ምርጡ መድሃኒት” ብሎ እንደሚገልጸውም ነው ተመራማሪዎቹ ያስታወቁት። እንቅስቃሴ ማድረግ የአእምሮ አቅምን እና ጤናን ከማጠናከር በተጨማሪም የልብ እና ሳንባ ጤናን ለመጠበቅ እና አጥንቶችን ለማጠንከር እንዲሁም የምግብ መፈጨትን እና የደም ስኳርን ለማስተካልም ይረዳል።via Alain አዳዲስ መረጃዎች እንዲደርስዎ Join አድርገው👇በዚህ ይከታተሉ https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 https://t.me/+WNLm9dbzuIlp9DF4 ማስታወቂያና ጥቆማ 👇መቀበያ https://t.me/wasumohammed
Показати все...
👍 44 4🔥 1🥰 1👏 1🙏 1