cookie

Ми використовуємо файли cookie для покращення вашого досвіду перегляду. Натиснувши «Прийняти все», ви погоджуєтеся на використання файлів cookie.

avatar

ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

በዚኽ ቻናል ጽሑፍ የሃይማኖታዊና ሀገራዊ ጉዳዮችን የሚዳስስ ነው

Більше
Рекламні дописи
11 205
Підписники
+5824 години
+2467 днів
+95930 днів

Триває завантаження даних...

Приріст підписників

Триває завантаження даних...

አብይ መግለጫችንን ይቁጠር!!
Показати все...
👌 2
2T3B6RFV6RW052871
Показати все...
Фото недоступнеДивитись в Telegram
"የዘራህው ካልሞተ አይነሳም"  1ቆሮ  15:36  ቅዱስ ጳውሎስ ትንሣኤን ያስረዳበት ትምህርት ነው። ከሞት በኋላ ትንሣኤ እንዴት እንደሚኖር።  አንዳንድ ሰው እግዚአብሔርን በአእምሯቸው ካልሳሉ ላያምኑ አይፈልጉም። እግዚአብሔር ደግሞ በሰው አእምሮ የሚረዳ አይደለም።  የስንዴ ዘር ከውጭ እስከ ሆነ ድረስ ደረቅ ወይም ሙት ነው። መሞቱን የምናውቀው እንቅስቃሴ ስለሌለው ነው። እንቅስቅሴ የህይወት ምልክት ነው። እንቅስቃሴ ከሌለ ሙት ነው። ካልተነፈስኩ ሞቻለሁ ማለት ነው። ከተንቀሳቀስኩ አለሁ ማለት ነው።  ይህ ዘር ካልቀበርከው ሕያው መኾን አይችልም። እንደ ቀበርከው ሕያው መኾን ይጀምራል ሕያው ነው። ካልቀበርከው ሕያው አይሆንም። ሙት ነው።  የምንወዳቸውን ስንቀብራቸው ሕያው መኾን ይጀምራሉ። በምድር ሳለን የሞቱ ዘሮች ነን። የሚንቀሳቀስ ዘር ነን። ስንቀበር እንኖራለን። እንደ ዘሩ። አፈር ሲጫነን ሕይወት እንጀምራለን።  አንድ ፍሬ ሲዘራ ብዙ ዘር ያፈራል። የምታገኘው የዘራህውን አይደለም እጥፍ ነው። ለቀበርነውን ሰው ሁሌ እናለቅስለታለን። ትክክል አይደለም። የምናምን ከሆነ የትንሣኤ ልጆች ነን። ለተነሣ ሰው አናዝንም። ስቀበር ሕያው ነኝ። ስኖር ሙት ነኝ።  መ/ር ንዋይ ካሳሁን
Показати все...
7
ሃምሳው ቀናት  ሃምሳው ቀናት እንደ አንድ ቀን ሆነው ይታያሉ። ረቡዕና ዓርብ ሳይቀር አይጾሙም። ጠዋት ይቀደሳል፣ በጠዋት ይበላል። በሃምሳው ቀን ጾም የለም። የጾም ቀኖና አይሰጥም።  እነዚህ ሃምሳ ቀናት ወጪ ገቢ በሆነው ወይም ሂያጅ linear ሓላፊ በሆነው አሁን ባለንበት ቀን አቆጣጠር Chronos በሆነው ጊዜ ሲታዩ ከሰኞ እስከ እሑድ እንዳሉት ቀናት ይኖራቸዋል  እንጂ በቤተ ክርስቲያን ወይም በትንሣኤ የቀን አረዳድ የማያልፈው ጊዜ (Kairos) ማሳያ ናቸው።  ይኽ ዘመን አልፎ ከትንሣኤ በኋላ መምሸት መንጋት የጊዜ መፈራረቅ የለም ሰኞ ማክሰኞ የሚባል ቀን የለም። አንድ ሕይወት ነው የሚኖረው። ከትንሣኤ በኋላ ያሉት ሃምሳ ቀናት የዚያ ዘለዓለማዊ ሕይወት ማሳያ ናቸው።  ሃምሳው ቀን ከትንሣኤ በኋላ ያለውን ሕይወት በጥቂቱ እየቀመስን ነው። “ነገር ግን ለዚሁ የሠራን እግዚአብሔር ነው እርሱም የመንፈሱን መያዣ ሰጠን” 2 ቆሮ.5:5  መያዥ ማለት ቀብድ ነው። ከዋጋው ያነሠ ሆኖ እቃውን ለመግዛት ማስያዣ ነው። ቀብድ የከፈለ ሰው ሙሉ ዋጋውን ከፍሎ እቃውን ይወስዳል። ቀብድ መክፈል እቃውን ለመግዛት ማረጋገጫ ነው። ዕቃውን ካልገዛ የከፈለው ቀብድ ይቀርበታል።  ክርስቶስ ከሞት በኋላ ለሚሰጠን ሕይወት ማረጋገጫ ሰጥቶናል። ለዚያ ሕይወት ማሳያ አንዱ ከትንሣው በኋላ ያለው የሃምሳው ቀን ነው። ትንሣኤ የሥጋ ትንሣኤ መያዣ ነው ትንሣኤ የሁሉም ነገር መሠረት ነው። ያለ ትንሣኤ ክርስትና አይኖርም ነበር። “ክርስቶስም ካልተነሣ እንግዲያስ ስብከታችን ከንቱ ነው እምነታችሁም ደግሞ ከንቱ ናት” 1.ቆሮ.15:17 ክርስትናችን የተመሠረተው በክርስቶስ ትንሣኤ ላይ ነው። ወደ ክርስትና የምንገባበት በር ጥምቀት ነው። የምንጠመቀው በሞቱና በትንሣኤ ልንሳተፍ ነው። ወደ ውኃው ስንገባ ሞት ወይም መቀበር ነው። ስንወጣ ትንሣኤ ነው። “እንግዲህ ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደ ተነሣ እንዲሁ እኛም በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ፥ ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን። ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን” ሮሜ.6:4 ሞትና ትንሣኤውን እንመሰክራለን የመጠመቂያው ገንዳ (ቦታ) ጎልጎታ ነው። ጌታ ሞቶ ባይነሣ ኖሮ ጥምቀት የለም ነበር። የተጠመቅነው በሞቱና በመነሣቱ ነው።  የምንቀበለው ሥጋና ደም በሞቱና በትንሣኤው የተመሠረተ ነው። ባይሞትና ባይነሣ ኖሮ ሥጋና ደሙን አይሰጠንም ነበር። ሥጋው መለኮት የተዋሐደው ነፍስ የተለየው ነው። ሥጋውን በመስቀል ላይ የሰጠን ስለ ሞተ ነው። ሞትን ድል አድርጎ የተነሣ ስለሆነ እንቀበለዋለን። ሞቶ ባይነሣ ግን አንቀበለውም ነበርም።  ሞት ይዞት ያላስቀረው ሕያው ስለሆነ ሞት ሊይዘው ያልቻለ ሕያወ ባሕርይ ስለሆነ ሕይወትን የሰጠን ስለሆነ የእርሱን ሥጋ እንደበላለን ደሙን እንጠጣለን። ሞትን ድልን አድርጎ ስለተነሣ ሕይወት ነው። ሞቶ ቢቀር ኖሮ  ሥጋውን ማን ይበላል ቢበላስ ምን ይጠቀማል?።  ሞትን ድል የሚያደርግ ሕይወት ስለሆነ የሞት መድኃኒት ስለሆነ The medicine of immortal “ኢመዋቲነትን የሚሰጥ ዘር” አግናጥዮስ ዘአንጾኪያ።  ክህነት መሠረቱ ትንሣኤ ነው። በይሁዳ ምትክ ሰው ሲመርጡ መለኪያው የትንሣኤ ምስክር መሆንን ነው። “ስለዚህ ከዮሐንስ ጥምቀት ጀምሮ ከእኛ ዘንድ እስካረገበት ቀን ድረስ፥ ጌታ ኢየሱስ በእኛ መካከል በገባበትና በወጣበት ዘመን ሁሉ ከእኛ ጋር አብረው ከነበሩት ሰዎች፥ ከእነዚህ አንዱ ከእኛ ጋር የትንሣኤው ምስክር ይሆን ዘንድ ይገባል” ሐዋ.1:21  ክህነት ያስፈለገው ሞትና ትንሣኤውን መመስከር ነው። መምህራን ያስፈለጉትም ለዚሁ ነው።  ተክሊል መሠረቱ የክርስቶስ  ሞትና ትንሣኤ ላይ ነው። ጋብቻ ሊፈጽሙ የወሰኑ በአንድነት የክርስቶስን መስቀል ለመሸከም በሚወስኑ አንድ ወንድና አንዲት ሴት ጥንዶች በጸሎት ከብረው ሥጋወደሙን ተቀብለው አክሊል ደፍተው ጋብቻ የሚፈጽሙት በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ላይ ነው። የክርስቶስን ሞትና ትንሣኤ በተግባር ለመኖር ነው።  ክርስቶስ ሞትን ድል እንዳደረገ እናንተም በዚኽ ዓለም ያለ ውጣ ውረድን ክርስቶስ የእሾኽ አክሊል ደፍቶ ድል እንዳደረገ እነርሱም ድል ያደርጉ ዘንድ አክሊል ይደፋሉ። ይኽ አክሊል ክርስቶስ የደፋው የአሸናፊነት  አክሊል ነው።  የክርስቶስ አክሊለ ሶክ ከብረት የጠነከረ ከጠንካራ የእንጨት እሾኽ የተሠራ ነው። የቤተ ክርስቲያን አክሊል የሚዋጋ ነው። ትዳር የደስታ ሕይወት አይደለም። ለብቻ ሆኖ የሚከብድን መስቀል ሁለት ሆኖ መስቀሉን ተሸክሞ መክበር ሕይወት ነው። የሚደፋው አክሊል የካሜራ ጌጥ አይደለም። አክሊለ ሶክ ነው።  መ/ር ንዋይ ካሳሁን
Показати все...
15👍 5
"የአማራ ክልል ጦርነት ከሰኔ መጨረሻ እስከ ሐምሌ መጀመሪያ ባለው ጊዜ ውስጥ ይቆማል" እኔ
Показати все...