Addis Maleda - አዲስ ማለዳ
📈 Аналитический обзор Telegram-канала Addis Maleda - አዲስ ማለዳ
Канал Addis Maleda - አዲስ ማለዳ (@addismaleda) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 32 099 подписчиков, занимая 7 712 место в категории Новости и СМИ и 1 054 место в регионе Эфиопия.
📊 Показатели аудитории и динамика
С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 32 099 подписчиков.
Согласно последним данным от 07 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 208, а за последние 24 часа — 13, при этом общий охват остаётся высоким.
- Статус верификации: Не верифицирован
- Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 13.75%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 9.51% реакций от общего числа подписчиков.
- Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 412 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 3 051 просмотров.
- Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 8.
📝 Описание и контентная политика
Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
“ዜና ከምንጩ”
Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 08 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Новости и СМИ.
Загрузка данных...
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 08 июля | +18 | |||
| 07 июля | +16 | |||
| 06 июля | +18 | |||
| 05 июля | +7 | |||
| 04 июля | +11 | |||
| 03 июля | +21 | |||
| 02 июля | +29 | |||
| 01 июля | +10 |
| 2 | Нет текста... | 2 336 |
| 3 | Нет текста... | 2 371 |
| 4 | አሜሪካና ኢራን ወታደራዊ ጥቃት ልውውጥ መጀመራቸው በቀጣናው ያለውን ውጥረት እንዲባባስ አድርጎታል ተባለ
ረቡዕ፣ ሀምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
አሜሪካ በሆርሙዝ ሰርጥ ላይ በሶስት የነዳጅ ጫኝ መርከቦች ላይ ለተፈጸመው ጥቃት ምላሽ በመስጠት በኢራን ላይ ከ80 በላይ ወታደራዊ ዒላማዎችን መምታቷን ያስታወቀች ሲሆን ኢራን በብኩሏ በ ቀጠናው በሚገኙ የ አሜሪካ ወታደራዊ ጣቢያ ላይ ጥቃትን ፈፅማለች።
የአሜሪካ ማዕከላዊ የጦር ዕዝ እንደገለጸው ኢራን ላይ ከፈፀማቸው የጥቃት ዒላማዎች መካከል ከ60 በላይ የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ኮር የሆኑ እና አነስተኛ የባህር ጀልባዎች እንደሚገኙበት ቢቢሲ ዘግቧል።
በተጨማሪም በጥቃቱ የተመቱ ሌሎች ወታደራዊ ተቋማትና መሣሪያ ማከማቻዎች እንዳሉ አስታውቋል።
የኢራን መንግስታዊ ሚዲያዎች በበኩላቸው የአሜሪካ ጥቃት በቄሽም ደሴት እና በባንዳር አባስ እንድሁም በሲሪክ አካባቢዎች ላይ ጥቃቱ መፈጸሙን ዘግበዋል። በፍንዳታው የተነሳ በቁርጥራጭ ፍንዳታ የተጎዱ ሰዎች መኖራቸው የተገለፀ ቢሆንም የተጎጂዎችን ቁጥር ግን እስካሁን በይፋ አልተገለፀም።
ኢራን በሆርሙዝ ሰርጥ በሶስቱ የነዳጅ መርከቦች ላይ ለተፈጸመው ጥቃት ኃላፊነቷን በቀጥታ ባትወስድም፣የአሜሪካ ባለሥልጣናት ግን ጥቃቱ ከኢራን ጋር የተያያዘ መሆኑን በመግለጽ ለዚህም አፀፋ ወታደራዊ እርምጃ መውሰዳቸውን ገልፀዋል።
በአጸፋው የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ ኮር በባህሬንና በኩዌት የሚገኙ የአሜሪካ ወታደራዊ ጣቢያዎችን በሚሳይልና በድሮን ማጥቃቱን አስታውቋል። አክሎም በሁለቱ ሀገራት በሚገኙ ወሳኝ በሆኑ 85 የአሜሪካ ወታደራዊ ተቋማት ላይ ጥቃት መፈፀሙን በመግለፅ ከእነዚህም መካከል በባህሬን የሚገኘው የአሜሪካ ባህር ኃይል ዋና መምሪያ እና በኩዌት ያለው የአየር ኃይል ጣቢያን ጠቅሷል።
ባለፈው ወር በቴህራንና በዋሽንግተን መካከል ግጭቱን ለማስቆምና የተኩስ አቁምን ለማራዘም የመግባቢያ ስምምነት ተፈርሞ እንደነበር የሚታወቅ ቢሆንም ከቅርብ ቀናት ወድህ የሚደረጉ የወታደራዊ ጥቃት ልውውጥ ስምምነቱን ከፍተኛ አደጋ ውስጥ እንደጣሉት የዲፕሎማሲ ታዛቢዎች ይገልጻሉ።
የሆርሙዝ ሰርጥ ከዓለም የነዳጅና የፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ንግድ 20 በመቶ ያህሉ የሚያልፍበት ወሳኝ የባህር መተላለፊያ በመሆኑ የተባባሰው ግጭት በዓለም የኃይል አቅርቦት፣በነዳጅ ዋጋ እና በክልሉ የደህንነት ሁኔታ ላይ ከፍተኛ ስጋት እያሳደረ መሆኑ ተገልጿል።
ምስል_ጌቲ ምስል(Gatty images)
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 964 |
| 5 | Нет текста... | 2 492 |
| 6 | “ፍረጃውን እንደ ሽልማት ነው የምቆጥረው” ጌታቸው ረዳ
የኤርትራ መንግስት እና ህወሓት ስልጣናቸውን ለማስቀጠል የትግራይን ህዝብ ማስያዥያ “ኮላተራል” እያደረጉት ነው በማለት የጠቅላይ ሚኒሰትሩ አማካሪ ጌታቸው ረዳ ወነጀሉ
ረቡዕ፣ ሀምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የጠቅላይ ሚኒስትሩ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ጌታቸው ረዳ፤ የህወሓት አመራር እና የኤርትራ መንግስት የራሳቸውን የፖለቲካ ህልውና ለማራዘም ሲሉ የትግራይን ህዝብ እንደ ማስያዥያ “ኮላተራል”እያደረጉት ይገኛል በማለት ከሰሱ። አማካሪው የህወሓትን ቡድን “የወንጀለኞች ኢንተርፕራይዝ” ብለው የጠሩት ሲሆን በኪም ጆንግ ኡን ከምትመራው ሰሜን ኮሪያ ጋር በማወዳደር፣ ከመሬት በተለቀመ መሳሪያ የሚታኮስ ቡድን ነው ሲሉ በይነውታል።
የቀድሞው የህወሓት ምክትል ሊቀመንበር እና የአሁኑ የስምረት ፓርቲ ፕሬዝዳንት፣ እንዲሁም የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ የሆኑት ጌታቸው ረዳ በትግራይ ክልል ላይ የደረሰውን ታላቅ ጥፋት በስልታዊ መንገድ የፈጸመውና የክልሉን የልማት ተቋማት ያደቀቀው የኤርትራ መንግስት ቢሆንም፣ የህወሓት አመራር ግን ዛሬ ላይ የራሱን ዕድሜ ለማራዘም ሲል ከዚሁ የኤርትራ አገዛዝ ጋር ጭምር አብሮ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል። ጌታቸው ህወሓት እየሄደበት ያለው መንገድ ከሰሜን ኮሪያም የባሳ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
ከብሔራዊው ቴሌቪዥን ጣያ ጋር ቆይታ ያደረጉት ጌታቸው፤ “ከሰሜን ኮሪያ ጋር ማወዳደር ልክ አይደለም፤ ቢያንስ ሥርዓት ያለው መንግስት እኮ ነው፣ ሳይንስ ልማት ምናምን የሚያደርግ፣ አቅሙ በፈቀደው መጠን እኮ ምርምሮችን ውስጥ ይገባል፤ ዓለም ጋር ተወዳዳሪ ሊያደርጉት የሚችሉ ሚሳኤሎችን፣ ባልስቲክ ይሰራል።” ያሉት ጌታቸው መልስ ብለው ደግሞ ህወሓትን “ይሄኛው ከሰፈር በተለቀመ ጥይት ገጥሜ በሰው ማዕበል ዘመቻ መንግስት እቀይራለሁ ብሎ የሚያምን ከስህተቱ በተደጋጋሚ ሳይማር አሁንም ሌላ ስህተት ለመፈጸም የኔ ሞኖፖሊ ነው ብሎ የሚያምን ነው” ብለዋል። ህወሓት፣ “አፋኝ” በሚል የተገለጸ አዋጅ ከጥቂት ሳምንታት በፊት ማውጣቱ የሚታወስ ሲሆን ይህም ከሀገር ውስጥና ዓለምአቀፍ ተቋማት ጭምር ውግዘትን እንዲከተለው ማድረጉ አይዘነጋም፡፡ጌታቸውም፣ ህወሓት ህግ የማውጣት ስልጣን የለውም ባይ ናቸው።
አማካሪው፤ ከገዢው ፓርቲ ጋር በመስራታቸው እንዴ ወንጀለኛ እና የትግራይን ህዝብ እንደከዳ እንደሚቆጠሩ አንስተው “እኔ እንደ በወንጀል መጠየቅ ያለብኝ ይሄን ወንጀለኛ ቡድን በወቅቱ ባለማጋለጤ ነው” ያሉ ሲሆን “የፈለጉትን ታርጋ ቢሰጡኝ እንዴ ሽልማት ነው የምቆጥረው” ብለዋል።
ጌታቸው አክለውም የትግራይ ወጣቶች በሰላም መኖርና ሌላው የሀገሪቱ ክፍል ላይ እንደሚታየው የልማት ተጠቃሚ መሆን በሚፈልጉበት ወቅት የህወሓት አመራር ግን የራሱን ስልጣን ለማስጠበቅ ሲል ወጣቶችን በኃይል እያሰለፈ ይገኛል ሲሉ ከስሰዋል። ይባስ ብሎም “ስደተኞችን ለመጠበቅ በሚል” ሰበብ ወጣቶቹን እስከ ሱዳን ደማዚንና ኩርሙ ድረስ በመውሰድ በውጊያ ላይ እያስፈጃቸው ይገኛል ብለዋል።
ይህ የጌታቸው የትናንት ምሽት ውንጀላ፣ ከትናንቱ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የረፋድ ተመሳሳይ ውንጀላ ጋር እጅጉን የሚስማማ ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በትናንትናው ዕለት በተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመጨረሻ መደበኛ ስብሰባ፣ “ህወሓት የትግራይ ልጆችን እያፈሰ ለሱዳን እየሸጠ ነው” ሲሉ በተመሳሳይ መወንጀላቸው አይዘነጋም፡፡
የጠቅላዩ አማካሪ አክለውም የኤርትራ መንግስት ሁሉንም ነገር በጦርነት ለመፍታት በሚከተለው መመሪያ ምክንያት የሀገሪቱ ህዝብ ቁጥር በሚለዮን በሚቆጠር አውርዶ አፍሪካ ውስጥ ትልቁ የስደተኛ ምንጭ መሆኗን ጠቅሰው አሁን ላይ ህወሓት እየተከተለው ያለው “አምባገንናዊ” አካሄድም ትግራይን የኤርትራን እጣ ፈንታ እንድትደግም እያደረጋት ነው ሲሉ አስጠንቅቀዋል። ይህም በዚህ ከቀጠለ በቅርቡ ትግራይ በምስራቅ አፍሪካ በስደት ቀዳሚውን ደረጃ ትይዛለች ብለዋል።
በትግራይ ህወሓት “ሕገ አራዊት” የሆነ ህግ አውጥቷል ያሉት ጌታቸው የትግራይን ወጣት ህይወት “ቅንጣት ታህል” አይቆጥሩትም በማለት የግዳጅ ምልመላን የሚቃወሙ ወጣቶች ላይ የተጣለውን የ50 ሺህ ብር ቅጣትና እስራት የያዘ ሰብአዊ መብትን ረገጣን የሚያበረታታ መሆኑን አመልክተዋል፡፡
የህወሓት ቡድን የትግራይን ህዝብ የህልውና አደጋ ላይ የጣለ እና “ከመወገድ ውጭ ሌላ ተስፋ የሌለው የወንጀል ኢንተርፕራይዝ” ነው በማለት የገለጹት አማካሪው ይህንን አጥፊ አካሄድ ለማስቆም የፌደራል መንግስቱ እና የትግራይ ሕዝብ ሚና ወሳኝ ነው ብለዋል።
የፌደራል መንግስቱ የትግራይ ህዝብ የኢትዮጵያና የፌደሬሽኑ አካል መሆኑን በመቀበል ክልሉ ከዚህ ስቃይ የሚላቀቅበትን መንገድ ማፈላለግ አለበት ሲሉም ጥሪ አስተላልፈዋል። መንግስት እስካሁን ያሳየው ትዕግስት እንደተጠበቀ ሆኖ የትግራይ የፖለቲካ ኃይሎች ለውጥ ለማምጣት በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ላይ በቀናነትና በደንብ በማገዝ የደጋፊነት ሚናውን መወጣት ይኖርበታል ሲሉ አሳስበዋል።
ዋናው ለውጥ መምጣት ያለበት በራሱ በትግራይ ህዝብ እና በትግራይ የፖለቲካ ሀይሎች እንቅስቃሴ መሆኑን የገለጹት ጌታቸው የህውሃት ቡድን “አንድ አዳርም ቢሆን በስልጣን መንበር ላይ የሚቀጥልበት እድል” ሊዘጋ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። አክለውም ህወሓት ቢችል “ከፋኖ እና ሸኔ” ጋር በመሆን አዲስ አበባ መጥቶ ስልጣን መያዝ እንደሚፈልግ አንስተዋል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 822 |
| 7 | Нет текста... | 2 721 |
| 8 | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በበጀት ዓመቱና የስድስተኛው የፓርላማ ዘመን የመጨረሻቸው በሆነው መደበኛ ስብሰባ ጊዜ ወስደው ካብራሯቸው ጉዳዮች መካከል ህወሓትን የተመለከተው አንደኛው ነው።
ዐቢይ፤ በዚህ ገለጻቸው፣ ህወሓት ’ዘመኑን የሚመጥን’ አለመሆኑን፤ ‛ከሻዕቢያም ሆነ ከሱዳን ጋር ቢጣመሩ መንግስታቸውን እንደማይገረስሱ’ ደጋግመው ተናግረዋል።
የእነሱ ማሸነፍ ‛ሞት’ መሆኑን አመልክተዋል።
ሙሉውን ለማየት ማስፈንጠሪያው ላይ ያገኙታል፦
https://youtu.be/mPqY_Ot5kTk?si=Oz6YuhzCzv_lnJyG | 3 858 |
| 9 | ደሳለኝ ጫኔ ቀደም ሲል ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በርካታ ጥያቄዎች ያነሱ ሲሆን ዐቢይም የፓርላማ አባሉን ደሳለኝ ጫኔን ስም ከሦስት ጊዜ በላይ በመጥራት፣ ከከዚህ ቀደሙ በተለየ መልኩ ሲያወድሷቸው እና ሲያደንቋቸው ተስተውሏል፡፡
ሙሉውን ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመከተል ያገኙታል፡-
https://youtu.be/bZUdBqzi0XA?si=je0DeKsYMADYVVqV | 3 951 |
| 10 | “ከዚህ ቀደም 5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ይደረግባቸው የነበሩ ምርቶችን በሀገር ውስጥ መተካት” መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ
ማክሰኞ፣ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተከናወኑ ስኬታማ ሥራዎች ሳቢያ ከዚህ ቀደም 5 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሬ ይወጣባቸው የነበሩ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም፣ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የ20.3 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡንና በቀጣዩ ዓመት ከኢንዱስትሪ ወጪ ንግድ (ኤክስፖርት) 1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ የኢኮኖሚውንና የኢንዱስትሪውን ዘርፍ አፈጻጸም ያብራሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ በተለይም በኮንስትራክሽንና በግብዓት ምርቶች ላይ ትልቅ ለውጥ መመዝገቡን ገልጸዋል። በቅርቡ አንድ የሴራሚክ ፋብሪካ ተመርቆ ሥራ መጀመሩን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ሌላ ተጨማሪ ትልቅ ፋብሪካም ተገንብቶ (ተመርቆ) በቅርቡ ወደ ሥራ እንደሚገባ ይፋ አድርገዋል።
ከሴራሚክ በተጨማሪ በሲሚንቶ፣ በመስታወት እና በብረት ምርቶች ላይ ሰፋፊ መዋቅራዊ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። የነበሩት የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የማምረት አቅም እንዲያድግ ከመደረጉም በላይ፣ አዲሱ የለሚ ሲሚንቶ ፋብሪካ ተገንብቶ ወደ ማምረት በመሸጋገሩ በሀገሪቱ የሲሚንቶ አቅርቦት ላይ በዚህ ዓመት የ16 በመቶ ዕድገት መመዝገቡን አስረድተዋል።
በአጠቃላይ የኢንዱስትሪ ዘርፉን ዕድገት በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ የማኑፋክቸሪንግ ንዑስ ዘርፍ የ20.3 በመቶ ከፍተኛ ዕድገት ማሳየቱን አብራርተዋል። በቀጣዩ ዓመትም ከኢንዱስትሪ ወጪ ንግድ 1 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ እየተሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
ከአጠቃላዩ የኢንዱስትሪ ዘርፍ የ12.7 በመቶ ዕድገት እንደሚጠበቅ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ይህ ውጤት በዘርፉ ላይ የተከናወኑት ስትራቴጂካዊ ሥራዎች ምን ያህል ውጤታማ መሆናቸውን የሚያሳይ ነው ብለወዋል፡፡
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 3 705 |
| 11 | Нет текста... | 3 130 |
| 12 | ዐቢይ ወደስልጣን ከመጡ 8 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ አዲስ ዩኒቨርስቲ እየገነቡ መሆኑን ተናገሩ
ማክሰኞ፣ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
ባለፉት ስምንት ዓመታት አንድም አዲስ ዩኒቨርሲቲ ሳይገነባ የቆየው መንግሥት፣ አሁን ላይ በዓይነቱ ልዩ የሆነ “የመደመር የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ” መገንባት መጀመሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) አስታወቁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንባታው ከአንድ ዓመት በኋላ እንደሚጠናቀቅ በመጠቆም፣ “በየትኛውም ዓለም የምንጓጓለትን ደረጃ ያሟላ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ውስጥ ማየታችን አይቀርም” ሲሉ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ወደስልጣን ከመጡበት ጊዜ አንስቶ አጽዕኖት ሰጥተው ከተናገሯቸው ጉዳዮች መካከል “አዲስ ዩኒቨርስቲ አንገነባም” የሚለው በዋነኝት ይገኝበታል፡፡ ዐቢይ ይህን ለመጀመሪያ ጊዜ የተናገሩት የወዳጅነት ሁለት ፓርክ ሲመረቅ ለጋዜጠኞች በሰጡት ቃል ሲሆን ከዛ በኋላ ግን በፓርላማውና በሌሎች መድረኮች መንግስታቸው አዲስ ዩኒቨርስቲ እንደማይገነባ ደጋግመው ገልጸዋል፡፡
በዛሬው ፓርላማ ግን አዲስ ዩኒቨርስቲ መንግስታቸው እየገነባ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ የሀገሪቱን የትምህርት ሥርዓትና አዳዲስ ፕሮጀክቶችን አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ ላለፉት ስምንት ዓመታት አዳዲስ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ከመገንባት ይልቅ ትኩረት የተደረገው መሠረቱ ላይ መሆኑን ገልጸዋል።
“ከታች ያለውን ሳንሠራ እላይ ብንሠራ ዋጋ የለውም” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በታችኛው እርከን ላይ ባሉ ተማሪዎች ላይ ብዙ መሥራት ስለሚጠበቅ በርካታ ትምህርት ቤቶችና የሕፃናት ማቆያዎችን መገንባታቸውን አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅት በበርካታ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ያሉ ኮንዶሚኒየሞች ባዶ ክፍሎች ሆነው መገኘታቸውን ጠቅሰው፣ ይህም ቀደም ሲል ለትምህርት ጥራት መሠረት ባለመጣሉ የመጣ ችግር መሆኑን አብራርተዋል።
አሁን እየተገነባ ስላለው ልዩ ተቋም ሲያብራሩም፣ ግንባታው ከአንድ ዓመት በኋላ ሙሉ በሙሉ እንደሚያልቅና በጥራት ረገድም በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ደረጃ ወደፊት የሚገነቡ ዩኒቨርሲቲዎች ሊወዳደሩት በማይችሉበት እጅግ ከፍተኛ ጥራት እየተገነባ መሆኑን በልበ ሙሉነት ተናግረዋል።
የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (ኤ.አይ.) የዓለም የወደፊት አቅጣጫ መሆኑን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ መንግሥታቸው ይህንን ቀድሞ በመረዳትና በማቀድ እየሠራ መሆኑንና ውጤቱም ወደፊት በጉልህ የሚታይ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።
የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ፣ ኩረጃን ለማስቀረት እና ቴክኖሎጂን ለመጠቀም እየተደረገ ያለው ሙከራ ተስፋ ሰጪ መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “ነገር ግን ገና የተሟላ አይደለም፣ ብዙ ሥራ ይጠበቅብናል፤ ገና የምናስብበት ቦታ ላይ አልደረስንም፤ አካሄዳችን ግን ፍጹም የሚያዋጣ ነው” ሲሉ አስረድተዋል።
በመጨረሻም ስለ ቀጣዩ ትውልድ ያላቸውን አዎንታዊ አመለካከት የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አዲሱ ትውልድ በዕውቀትና በቴክኖሎጂ የታገዘ በመሆኑ የሚያሰጋ እንዳልሆነና የሀገሪቱ ፖለቲካም ሆነ ልማት ወደዚህኛው ትውልድ ሲሸጋገር ኢትዮጵያ ፍጹም አትራፊ እንጂ ተጎጂ አትሆንም ሲሉ ንግግራቸውን አጠቃልለዋል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 3 266 |
| 13 | Нет текста... | 2 707 |
| 14 | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ በዛሬው የፓርላማ ውሏቸው “ህወሓት መጥረቢያ ነው፤ ሻዕቢያ ደግሞ እንጨት” ነው ሲሉ በይነዋቸዋል፤ እንዴት የሚለውን ከታች የሚገኘውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ተከታተሉት!!
https://www.youtube.com/watch?v=QqpTjzXa-UE | 3 066 |
| 15 | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ “በአርሲ የተፈጸመውን ጥቃት በሌሎች አካባቢዎችም ለመድገም የታቀደውን ሴራ መንግሥት አክሽፎታል” ሰሲሉ ተናገሩ
ማክሰኞ፣ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በአርሲ ዞን የተፈጸመውን ጥቃት በአዲስ አበባን ጨምሮ በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች ለመድገም እና ግጭቱን ኃይማኖታዊ መልክ ለማስያዝ የታቀዱ በርካታ የቦምብ ጥቃቶችን ጨምሮ የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን መንግሥት ማክሸፉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም፣ በአርሲው ግጭት ሕይወታቸው ከጠፋው 11 ሰዎች መካከል 8ቱ ሕዝብን ለመጠበቅ የተሰዉ ሚሊሻዎችና ፖሊሶች መሆናቸውን በመግለጽ፣ የእነሱን መስዋዕትነት ማርከስ አሳፋሪ ተግባር ነው ሲሉ ወቅሰዋል።
የአርሲውን አለመረጋጋት በተመለከተ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፤ ድርጊቱ የእምነት ተኮር ሳይሆን ሽፍቶች ሰዎችን በመግደልና በማፈናቀል የነበረውን ሰላማዊ ድባብ ለማጠልሸት የፈጸሙት መሆኑን ገልጸዋል።
ጥቃቱን በሌሎች ቦታዎችም ለመፈጸም በተልዕኮ ይንቀሳቀሱ የነበሩ
ኃይሎችን መንግሥት ማክሸፍ መቻሉን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በአዲስ አበባ ያሉትን ጨምሮ በኃይማኖታዊ ቦታዎች ላይ ጥቃት ለማድረስ የተዘጋጁ በርካታ ቦምቦች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ይፋ አድርገዋል። ግጭቱን ኃይማኖታዊ ለማስመስል ጥረት ቢደረግም፣ በአርሲው ጥቃት ሕይወታቸው ከጠፋው ዜጎች መካከል ሙስሊሞችም እንደሚገኙበት ጠቁመዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደተናገሩት፣ በኢትዮጵያ ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ ስለነበረ ያሰቡትን ማድረግ ያቃታቸው ኃይሎች፣ ሕዝቡን ለማጥቃት ወደ አንድ የአርሲ መንደር አምርተዋል። በአርሲ በተፈጠረው ግጭት ሕዝብን በሚከላከልና በሚያጠቃ ኃይል መካከል በተደረገ ውጊያ የ11 ሰዎች ሕይወት ሲቀጠፍ፣ ከእነዚህ ውስጥ 8ቱ ሚሊሻዎችና የፖሊስ አባላት መሆናቸውን አስረድተዋል።
“ሕዝብ እንዳይመታ እየተዋደቀ ያለን ሰው በሃይማኖት ጥላ ሥር ሆኖ መውቀስ ተገቢ ነውን?” ሲሉ የጠየቁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መስዋዕትነት የከፈሉትን የጸጥታ አካላት ማወደስና ማመስገን ሲገባ፣ የእነሱን መስዋዕትነት ማርከስ በብዙ ፖለቲከኞች ዘንድ መታየቱ እጅግ አሳፋሪ ድርጊት መሆኑን ገልጸዋል።
በአርሲ የነበረውን አለመረጋጋት ተከትሎ ተፈናቅለው ከነበሩ ዜጎች መካከል በአሁኑ ወቅት ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት ወደ ቀያቸው መመለሳቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አስታውቀዋል።
ቀሪዎቹን ተፈናቃዮችም በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመመለስና በዘላቂነት ለማቋቋም፣ የመንግሥት የሕግ ማስከበርና የመልሶ ማቋቋም እርምጃዎች ተጠናክረው እየቀጠሉ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 3 153 |
| 16 | Нет текста... | 2 813 |
| 17 | በትግራይ ከ60 ሺህ በላይ ታጣቂዎችን በክፍያ አሰናብተናል፤ ቤተሰቦቻቸው አዲስ አበባ ያሉትንም ያልነካነው በአንድ ሰው ምክንያት ሙሉ ቤተሰብ መታመስ ስለሌለበት ነው” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር)
ማክሰኞ፣ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ
የፕሪቶሪያው ስምምነት በርካታ ውጤቶችን ማስገኘቱን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ መንግሥት ለሰላም ካለው ቁርጠኝነት የተነሳ ከ60 ሺህ ያላነሱ ታጣቂዎችን አስፈላጊውን ክፍያ ፈጽሞ ማሰናበቱንና ምርኮኞችን መፍታቱን አስታውቀዋል።
አሁን ላይ በክልሉ ሰላም የሚያውኩ አካላት ቤተሰቦች አዲስ አበባና ውጭ ሀገር እንደሚኖሩ ጠቁመው፣ “የቤተሰቦቻቸውን ሰላም ያልነካንበት ምክንያት በአንድ ሰው ጥፋት ቤተሰብ መታመስ ስለሌለበት ነው” ሲሉ ተናግረዋል።
የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ስምምነቱ እንደ ተራ ድርድር ብቻ የሚታይ ሳይሆን በርካታ ተጨባጭ ውጤቶችን ያስገኘ መሆኑን ገልጸዋል።
ስምምነቱን “አሸናፊ እና ተሸናፊ እኩል ተቀምጠው የተወያዩበት ታላቅ ክስተት” ሲሉ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንግሥት ካሸነፈ በኋላ የተሸነፈውን ኃይል ቁጭ አድርጎ መደራደር ብቻ ሳይሆን፣ በችግር ውስጥ የነበሩ የታጠቁ ኃይሎችን “ቀልቦ” እና ብዙ ድጋፍ ሰጥቶ ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት ማሳየቱን አብራርተዋል።
በስምምነቱ የተገኙ ስኬቶችን የዘረዘሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ማቋቋም መቻሉን፣ ከ60 ሺህ ያላነሱ የታጠቁ ኃይሎች አስፈላጊው ክፍያ ተፈጽሞላቸው ከሰራዊቱ እንዲሰናበቱ መደረጉን፣ እንዲሁም በርካታ እስረኞችና ምርኮኞች መፈታታቸውን ጠቅሰዋል።
በመንግሥት የተለቀቁ አንዳንድ ምርኮኞች አሁን ላይ “ለትግራይ ተቆርቋሪ ነን” በማለት ላይ እንደሚገኙም አክለዋል። በተጨማሪም በክልሉ የተለያዩ መሠረታዊ አገልግሎቶችን ለማስጀመር መቻሉንና እነዚህ ኃይሎች “ሀብትና ንብረታችን ነው” የሚሉትን ጠብቆ በማቆየት ለራሳቸው ማስረከቡን ገልጸዋል።
አሁን ላይ በክልሉ ሰላምን የሚያውኩ አካላትን ጠንከር ባለ መልኩ የኮነኑት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “በክልሉ ሰላምን የሚያውኩ ኃይሎች ሚስቶቻቸውና ልጆቻቸው አዲስ አበባ እና ውጭ ሀገር እንደተቀመጡ እናውቃለን፤ አዲስ አበባ ያሉ ቤተሰቦቻቸውን ያልነካንበት ምክንያት በአንድ ሰው ምክንያት ሙሉ ቤተሰብ መታመስ ስለሌለበት ነው” ብለዋል።
የፕሪቶሪያውን ስምምነት ተከትሎ “በርካታ አኩራፊዎች ተፈጥረዋል፣ ከእኛም ገሸሽ ያሉ አሉ” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ስምምነቱ እንዲህ ዓይነት በርካታ ውስብስብ ነገሮችን በውስጡ የያዘ መሆኑን አስረድተዋል።
በትግራይ ወጣቶች ላይ እየተፈጸመ ስላለው “አፈሳ” ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ የትግራይ ወጣቶች ተሽጠው በሱዳን ጦርነት በማያውቁት ጉዳይ ሕይወታቸውን እያጡ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህ ሁሉ ሂደት ውስጥ የትግራይ ሕዝብ ዋነኛ ተጎጂና የችግሩ ገፈት ቀማሽ እየሆነ መምጣቱን በመግለጽ አሰስረድተዋል፡፡
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 998 |
| 18 | Нет текста... | 2 507 |
| 19 | የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉ ደሳለኝ ጫኔ(ዶ/ር) በመጨረሻ የፓርላማ ዘመናቸው ተከታዮቹን ጥያቄዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) አቅርበዋል፡፡
ሙሉ ጥያቄያቸውን ከታች ባለው ማስፈንጠሪያ ያገኙታል።
https://www.youtube.com/watch?v=MyvVTVI0UFo | 2 883 |
| 20 | “ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ቆመን እናጨብጭብላቸው፤ በኢትዮጵያ የፈነጠቀው ብርሃን፤ ይበልጥ እየፈካ ነው” የፓርላማ አባል መሐመድ አህመድ
ማክሰኞ፣ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ቀደም ሲል ከተነሱት የሰላምና የሰብዓዊ ቀውሶች ስጋቶች በተቃራኒ፣ የለውጡ ፍሬዎችና የብልጽግና ጉዞዎች በተግባር እየታዩ መሆናቸውን የጠቀሱት የፓርላማ አባል መሐመድ አህመድ፤ ሀገሪቱ በጥበብና በዕውቀት በሚመራ ብልህ አመራር ውስጥ እያለፈች በመሆኑ “ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ቆመን ልናጨበጭብላቸው ይገባል” ሲሉ ለአመራራቸው ያላቸውን ከፍተኛ አድናቆት ገለጹ።
በምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ ላይ ቀደም ሲል ከተነሱት የተለያዩ የልማት፣ የሰላምና የሰብዓዊ ጉዳዮች አስተያየቶች ቀጥለው ንግግር ያደረጉት የምክር ቤት አባሉ መሐመድ አህመድ፤ በሀገሪቱ የመጣው ለውጥ በተጨባጭ ውጤት የታጀበ መሆናቸውን በስፋት አብራርተዋል።
መሐመድ በንግግራቸው፤ “በሀገራችን የፈነጠቀው የለውጥ ብርሃን ይበልጥ እየፈካ፣ ፍሬው እየጎመራና የጋራ ተስፋችን ይበልጥ እያበበ መጥቷል” ካሉ በኋላ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ በየመስኩ እያሸተ ያለው የብልጽግና ፍሬ ሕይወቱን ከመሠረቱ እንደሚለውጠው ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
ሕዝቡ የጠቅላይ ሚኒስትሩን በጥበብና ዕውቀት የታገዘ ብልህ አመራር ተከትሎ፣ ተደምሮና ተባብሮ በጀመረው አቅጣጫ ለውጡን አፋጥኖ ቢጓዝ የዘመናት ምኞትና ተስፋው እውን እንደሚሆንለትም አክለዋል።
በመንግሥት ላይ የሚሰነዘሩ የተለዩ ትችቶችንና ቅሬታዎችን በብርቱ የሞገቱት የምክር ቤት አባሉ፤ ይህ ስኬት ለአሮጌ የጥላቻ ፖለቲካ አራማጆች እንደማይታይ ጠቁመዋል። “ሕሊናቸው በጥላቻ ሞራ ታውሯልና፤ ዓይናቸው ጥሩ ነገር ማየት አይችልም፤ አንደበታቸውም ከማጣጣልና ከማጠልሸት በስተቀር ምስጋናና ማበረታታትን አያውቅም” ሲሉ ተቃዋሚ ወገኖችን ወቅሰዋል።
ሀቅን ማየትና እውነታን መቀበል የሚችል ንጹህ ሕሊና የታደሉ ሁሉ ጉዳዩን በግልጽ እንደሚገነዘቡት የገለጹት መሐመድ፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አመራር የዲሞክራሲ ባህል እንዲጎለበት፣ መብቶችና ነጻነቶች እንዲከበሩ እንዲሁም የፖለቲካ ምህዳሩ እንዲሰፋ መደረጉን አንስተዋል። ሁሉም ተዋናይ በሀገሩ ጉዳይ እኩል ተሳትፎ ኖሮት በነጻነት እንዲቀሳቀስ የሚያስችል የፖለቲካ ዐውድ በመፍጠር ረገድ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የአመራር ሚና እጅግ ከፍተኛ መሆኑን አድንቀዋል።
የምክር ቤት አባሉ መሐመድ አህመድ ንግግራቸውን ሲያጠቃልሉም ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያላቸውን ክብር በመግለጽ “ረዥም ዕድሜና ጤና እመኝልዎታለሁ” ብለዋል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 680 |
