Addis Maleda - አዲስ ማለዳ
📈 Аналитический обзор Telegram-канала Addis Maleda - አዲስ ማለዳ
Канал Addis Maleda - አዲስ ማለዳ (@addismaleda) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 32 083 подписчиков, занимая 7 712 место в категории Новости и СМИ и 1 054 место в регионе Эфиопия.
📊 Показатели аудитории и динамика
С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 32 083 подписчиков.
Согласно последним данным от 07 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 208, а за последние 24 часа — 13, при этом общий охват остаётся высоким.
- Статус верификации: Не верифицирован
- Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 13.75%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 9.51% реакций от общего числа подписчиков.
- Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 4 412 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 3 051 просмотров.
- Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 8.
📝 Описание и контентная политика
Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
“ዜና ከምንጩ”
Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 08 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Новости и СМИ.
Загрузка данных...
| Дата | Привлечение подписчиков | Упоминания | Каналы | |
| 07 июля | +16 | |||
| 06 июля | +18 | |||
| 05 июля | +7 | |||
| 04 июля | +11 | |||
| 03 июля | +21 | |||
| 02 июля | +29 | |||
| 01 июля | +10 |
| 2 | Нет текста... | 512 |
| 3 | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በበጀት ዓመቱና የስድስተኛው የፓርላማ ዘመን የመጨረሻቸው በሆነው መደበኛ ስብሰባ ጊዜ ወስደው ካብራሯቸው ጉዳዮች መካከል ህወሓትን የተመለከተው አንደኛው ነው።
ዐቢይ፤ በዚህ ገለጻቸው፣ ህወሓት ’ዘመኑን የሚመጥን’ አለመሆኑን፤ ‛ከሻዕቢያም ሆነ ከሱዳን ጋር ቢጣመሩ መንግስታቸውን እንደማይገረስሱ’ ደጋግመው ተናግረዋል።
የእነሱ ማሸነፍ ‛ሞት’ መሆኑን አመልክተዋል።
ሙሉውን ለማየት ማስፈንጠሪያው ላይ ያገኙታል፦
https://youtu.be/mPqY_Ot5kTk?si=Oz6YuhzCzv_lnJyG | 2 941 |
| 4 | ደሳለኝ ጫኔ ቀደም ሲል ለጠቅላይ ሚኒስትሩ በርካታ ጥያቄዎች ያነሱ ሲሆን ዐቢይም የፓርላማ አባሉን ደሳለኝ ጫኔን ስም ከሦስት ጊዜ በላይ በመጥራት፣ ከከዚህ ቀደሙ በተለየ መልኩ ሲያወድሷቸው እና ሲያደንቋቸው ተስተውሏል፡፡
ሙሉውን ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመከተል ያገኙታል፡-
https://youtu.be/bZUdBqzi0XA?si=je0DeKsYMADYVVqV | 3 332 |
| 5 | “ከዚህ ቀደም 5 ቢሊዮን ዶላር ወጪ ይደረግባቸው የነበሩ ምርቶችን በሀገር ውስጥ መተካት” መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለጹ
ማክሰኞ፣ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በኢንዱስትሪው ዘርፍ በተከናወኑ ስኬታማ ሥራዎች ሳቢያ ከዚህ ቀደም 5 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ የውጭ ምንዛሬ ይወጣባቸው የነበሩ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ምርት መተካት መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም፣ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የ20.3 በመቶ ዕድገት ማስመዝገቡንና በቀጣዩ ዓመት ከኢንዱስትሪ ወጪ ንግድ (ኤክስፖርት) 1 ቢሊዮን ዶላር ገቢ እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ የኢኮኖሚውንና የኢንዱስትሪውን ዘርፍ አፈጻጸም ያብራሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ በተለይም በኮንስትራክሽንና በግብዓት ምርቶች ላይ ትልቅ ለውጥ መመዝገቡን ገልጸዋል። በቅርቡ አንድ የሴራሚክ ፋብሪካ ተመርቆ ሥራ መጀመሩን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ሌላ ተጨማሪ ትልቅ ፋብሪካም ተገንብቶ (ተመርቆ) በቅርቡ ወደ ሥራ እንደሚገባ ይፋ አድርገዋል።
ከሴራሚክ በተጨማሪ በሲሚንቶ፣ በመስታወት እና በብረት ምርቶች ላይ ሰፋፊ መዋቅራዊ ሥራዎች መከናወናቸውን ጠቁመዋል። የነበሩት የሲሚንቶ ፋብሪካዎች የማምረት አቅም እንዲያድግ ከመደረጉም በላይ፣ አዲሱ የለሚ ሲሚንቶ ፋብሪካ ተገንብቶ ወደ ማምረት በመሸጋገሩ በሀገሪቱ የሲሚንቶ አቅርቦት ላይ በዚህ ዓመት የ16 በመቶ ዕድገት መመዝገቡን አስረድተዋል።
በአጠቃላይ የኢንዱስትሪ ዘርፉን ዕድገት በተመለከተ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ የማኑፋክቸሪንግ ንዑስ ዘርፍ የ20.3 በመቶ ከፍተኛ ዕድገት ማሳየቱን አብራርተዋል። በቀጣዩ ዓመትም ከኢንዱስትሪ ወጪ ንግድ 1 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ እየተሠራ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
ከአጠቃላዩ የኢንዱስትሪ ዘርፍ የ12.7 በመቶ ዕድገት እንደሚጠበቅ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ይህ ውጤት በዘርፉ ላይ የተከናወኑት ስትራቴጂካዊ ሥራዎች ምን ያህል ውጤታማ መሆናቸውን የሚያሳይ ነው ብለወዋል፡፡
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 3 015 |
| 6 | Нет текста... | 2 292 |
| 7 | ዐቢይ ወደስልጣን ከመጡ 8 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ አዲስ ዩኒቨርስቲ እየገነቡ መሆኑን ተናገሩ
ማክሰኞ፣ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
ባለፉት ስምንት ዓመታት አንድም አዲስ ዩኒቨርሲቲ ሳይገነባ የቆየው መንግሥት፣ አሁን ላይ በዓይነቱ ልዩ የሆነ “የመደመር የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ዩኒቨርሲቲ” መገንባት መጀመሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) አስታወቁ። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ግንባታው ከአንድ ዓመት በኋላ እንደሚጠናቀቅ በመጠቆም፣ “በየትኛውም ዓለም የምንጓጓለትን ደረጃ ያሟላ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ውስጥ ማየታችን አይቀርም” ሲሉ ተናግረዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ወደስልጣን ከመጡበት ጊዜ አንስቶ አጽዕኖት ሰጥተው ከተናገሯቸው ጉዳዮች መካከል “አዲስ ዩኒቨርስቲ አንገነባም” የሚለው በዋነኝት ይገኝበታል፡፡ ዐቢይ ይህን ለመጀመሪያ ጊዜ የተናገሩት የወዳጅነት ሁለት ፓርክ ሲመረቅ ለጋዜጠኞች በሰጡት ቃል ሲሆን ከዛ በኋላ ግን በፓርላማውና በሌሎች መድረኮች መንግስታቸው አዲስ ዩኒቨርስቲ እንደማይገነባ ደጋግመው ገልጸዋል፡፡
በዛሬው ፓርላማ ግን አዲስ ዩኒቨርስቲ መንግስታቸው እየገነባ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡ የሀገሪቱን የትምህርት ሥርዓትና አዳዲስ ፕሮጀክቶችን አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ ላለፉት ስምንት ዓመታት አዳዲስ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ከመገንባት ይልቅ ትኩረት የተደረገው መሠረቱ ላይ መሆኑን ገልጸዋል።
“ከታች ያለውን ሳንሠራ እላይ ብንሠራ ዋጋ የለውም” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ በታችኛው እርከን ላይ ባሉ ተማሪዎች ላይ ብዙ መሥራት ስለሚጠበቅ በርካታ ትምህርት ቤቶችና የሕፃናት ማቆያዎችን መገንባታቸውን አስታውሰዋል። በአሁኑ ወቅት በበርካታ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ያሉ ኮንዶሚኒየሞች ባዶ ክፍሎች ሆነው መገኘታቸውን ጠቅሰው፣ ይህም ቀደም ሲል ለትምህርት ጥራት መሠረት ባለመጣሉ የመጣ ችግር መሆኑን አብራርተዋል።
አሁን እየተገነባ ስላለው ልዩ ተቋም ሲያብራሩም፣ ግንባታው ከአንድ ዓመት በኋላ ሙሉ በሙሉ እንደሚያልቅና በጥራት ረገድም በኢትዮጵያም ሆነ በአፍሪካ ደረጃ ወደፊት የሚገነቡ ዩኒቨርሲቲዎች ሊወዳደሩት በማይችሉበት እጅግ ከፍተኛ ጥራት እየተገነባ መሆኑን በልበ ሙሉነት ተናግረዋል።
የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (ኤ.አይ.) የዓለም የወደፊት አቅጣጫ መሆኑን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ መንግሥታቸው ይህንን ቀድሞ በመረዳትና በማቀድ እየሠራ መሆኑንና ውጤቱም ወደፊት በጉልህ የሚታይ ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።
የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ፣ ኩረጃን ለማስቀረት እና ቴክኖሎጂን ለመጠቀም እየተደረገ ያለው ሙከራ ተስፋ ሰጪ መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “ነገር ግን ገና የተሟላ አይደለም፣ ብዙ ሥራ ይጠበቅብናል፤ ገና የምናስብበት ቦታ ላይ አልደረስንም፤ አካሄዳችን ግን ፍጹም የሚያዋጣ ነው” ሲሉ አስረድተዋል።
በመጨረሻም ስለ ቀጣዩ ትውልድ ያላቸውን አዎንታዊ አመለካከት የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አዲሱ ትውልድ በዕውቀትና በቴክኖሎጂ የታገዘ በመሆኑ የሚያሰጋ እንዳልሆነና የሀገሪቱ ፖለቲካም ሆነ ልማት ወደዚህኛው ትውልድ ሲሸጋገር ኢትዮጵያ ፍጹም አትራፊ እንጂ ተጎጂ አትሆንም ሲሉ ንግግራቸውን አጠቃልለዋል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 530 |
| 8 | Нет текста... | 2 332 |
| 9 | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ በዛሬው የፓርላማ ውሏቸው “ህወሓት መጥረቢያ ነው፤ ሻዕቢያ ደግሞ እንጨት” ነው ሲሉ በይነዋቸዋል፤ እንዴት የሚለውን ከታች የሚገኘውን ማስፈንጠሪያ በመጫን ተከታተሉት!!
https://www.youtube.com/watch?v=QqpTjzXa-UE | 2 494 |
| 10 | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ “በአርሲ የተፈጸመውን ጥቃት በሌሎች አካባቢዎችም ለመድገም የታቀደውን ሴራ መንግሥት አክሽፎታል” ሰሲሉ ተናገሩ
ማክሰኞ፣ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በአርሲ ዞን የተፈጸመውን ጥቃት በአዲስ አበባን ጨምሮ በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች ለመድገም እና ግጭቱን ኃይማኖታዊ መልክ ለማስያዝ የታቀዱ በርካታ የቦምብ ጥቃቶችን ጨምሮ የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን መንግሥት ማክሸፉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም፣ በአርሲው ግጭት ሕይወታቸው ከጠፋው 11 ሰዎች መካከል 8ቱ ሕዝብን ለመጠበቅ የተሰዉ ሚሊሻዎችና ፖሊሶች መሆናቸውን በመግለጽ፣ የእነሱን መስዋዕትነት ማርከስ አሳፋሪ ተግባር ነው ሲሉ ወቅሰዋል።
የአርሲውን አለመረጋጋት በተመለከተ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ፤ ድርጊቱ የእምነት ተኮር ሳይሆን ሽፍቶች ሰዎችን በመግደልና በማፈናቀል የነበረውን ሰላማዊ ድባብ ለማጠልሸት የፈጸሙት መሆኑን ገልጸዋል።
ጥቃቱን በሌሎች ቦታዎችም ለመፈጸም በተልዕኮ ይንቀሳቀሱ የነበሩ
ኃይሎችን መንግሥት ማክሸፍ መቻሉን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ በአዲስ አበባ ያሉትን ጨምሮ በኃይማኖታዊ ቦታዎች ላይ ጥቃት ለማድረስ የተዘጋጁ በርካታ ቦምቦች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ይፋ አድርገዋል። ግጭቱን ኃይማኖታዊ ለማስመስል ጥረት ቢደረግም፣ በአርሲው ጥቃት ሕይወታቸው ከጠፋው ዜጎች መካከል ሙስሊሞችም እንደሚገኙበት ጠቁመዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንደተናገሩት፣ በኢትዮጵያ ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ ስለነበረ ያሰቡትን ማድረግ ያቃታቸው ኃይሎች፣ ሕዝቡን ለማጥቃት ወደ አንድ የአርሲ መንደር አምርተዋል። በአርሲ በተፈጠረው ግጭት ሕዝብን በሚከላከልና በሚያጠቃ ኃይል መካከል በተደረገ ውጊያ የ11 ሰዎች ሕይወት ሲቀጠፍ፣ ከእነዚህ ውስጥ 8ቱ ሚሊሻዎችና የፖሊስ አባላት መሆናቸውን አስረድተዋል።
“ሕዝብ እንዳይመታ እየተዋደቀ ያለን ሰው በሃይማኖት ጥላ ሥር ሆኖ መውቀስ ተገቢ ነውን?” ሲሉ የጠየቁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መስዋዕትነት የከፈሉትን የጸጥታ አካላት ማወደስና ማመስገን ሲገባ፣ የእነሱን መስዋዕትነት ማርከስ በብዙ ፖለቲከኞች ዘንድ መታየቱ እጅግ አሳፋሪ ድርጊት መሆኑን ገልጸዋል።
በአርሲ የነበረውን አለመረጋጋት ተከትሎ ተፈናቅለው ከነበሩ ዜጎች መካከል በአሁኑ ወቅት ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት ወደ ቀያቸው መመለሳቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አስታውቀዋል።
ቀሪዎቹን ተፈናቃዮችም በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመመለስና በዘላቂነት ለማቋቋም፣ የመንግሥት የሕግ ማስከበርና የመልሶ ማቋቋም እርምጃዎች ተጠናክረው እየቀጠሉ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 604 |
| 11 | Нет текста... | 2 466 |
| 12 | በትግራይ ከ60 ሺህ በላይ ታጣቂዎችን በክፍያ አሰናብተናል፤ ቤተሰቦቻቸው አዲስ አበባ ያሉትንም ያልነካነው በአንድ ሰው ምክንያት ሙሉ ቤተሰብ መታመስ ስለሌለበት ነው” ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር)
ማክሰኞ፣ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ
የፕሪቶሪያው ስምምነት በርካታ ውጤቶችን ማስገኘቱን የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፤ መንግሥት ለሰላም ካለው ቁርጠኝነት የተነሳ ከ60 ሺህ ያላነሱ ታጣቂዎችን አስፈላጊውን ክፍያ ፈጽሞ ማሰናበቱንና ምርኮኞችን መፍታቱን አስታውቀዋል።
አሁን ላይ በክልሉ ሰላም የሚያውኩ አካላት ቤተሰቦች አዲስ አበባና ውጭ ሀገር እንደሚኖሩ ጠቁመው፣ “የቤተሰቦቻቸውን ሰላም ያልነካንበት ምክንያት በአንድ ሰው ጥፋት ቤተሰብ መታመስ ስለሌለበት ነው” ሲሉ ተናግረዋል።
የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ስምምነቱ እንደ ተራ ድርድር ብቻ የሚታይ ሳይሆን በርካታ ተጨባጭ ውጤቶችን ያስገኘ መሆኑን ገልጸዋል።
ስምምነቱን “አሸናፊ እና ተሸናፊ እኩል ተቀምጠው የተወያዩበት ታላቅ ክስተት” ሲሉ የገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንግሥት ካሸነፈ በኋላ የተሸነፈውን ኃይል ቁጭ አድርጎ መደራደር ብቻ ሳይሆን፣ በችግር ውስጥ የነበሩ የታጠቁ ኃይሎችን “ቀልቦ” እና ብዙ ድጋፍ ሰጥቶ ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት ማሳየቱን አብራርተዋል።
በስምምነቱ የተገኙ ስኬቶችን የዘረዘሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ማቋቋም መቻሉን፣ ከ60 ሺህ ያላነሱ የታጠቁ ኃይሎች አስፈላጊው ክፍያ ተፈጽሞላቸው ከሰራዊቱ እንዲሰናበቱ መደረጉን፣ እንዲሁም በርካታ እስረኞችና ምርኮኞች መፈታታቸውን ጠቅሰዋል።
በመንግሥት የተለቀቁ አንዳንድ ምርኮኞች አሁን ላይ “ለትግራይ ተቆርቋሪ ነን” በማለት ላይ እንደሚገኙም አክለዋል። በተጨማሪም በክልሉ የተለያዩ መሠረታዊ አገልግሎቶችን ለማስጀመር መቻሉንና እነዚህ ኃይሎች “ሀብትና ንብረታችን ነው” የሚሉትን ጠብቆ በማቆየት ለራሳቸው ማስረከቡን ገልጸዋል።
አሁን ላይ በክልሉ ሰላምን የሚያውኩ አካላትን ጠንከር ባለ መልኩ የኮነኑት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ “በክልሉ ሰላምን የሚያውኩ ኃይሎች ሚስቶቻቸውና ልጆቻቸው አዲስ አበባ እና ውጭ ሀገር እንደተቀመጡ እናውቃለን፤ አዲስ አበባ ያሉ ቤተሰቦቻቸውን ያልነካንበት ምክንያት በአንድ ሰው ምክንያት ሙሉ ቤተሰብ መታመስ ስለሌለበት ነው” ብለዋል።
የፕሪቶሪያውን ስምምነት ተከትሎ “በርካታ አኩራፊዎች ተፈጥረዋል፣ ከእኛም ገሸሽ ያሉ አሉ” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ስምምነቱ እንዲህ ዓይነት በርካታ ውስብስብ ነገሮችን በውስጡ የያዘ መሆኑን አስረድተዋል።
በትግራይ ወጣቶች ላይ እየተፈጸመ ስላለው “አፈሳ” ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፤ የትግራይ ወጣቶች ተሽጠው በሱዳን ጦርነት በማያውቁት ጉዳይ ሕይወታቸውን እያጡ መሆኑን ጠቁመዋል። በዚህ ሁሉ ሂደት ውስጥ የትግራይ ሕዝብ ዋነኛ ተጎጂና የችግሩ ገፈት ቀማሽ እየሆነ መምጣቱን በመግለጽ አሰስረድተዋል፡፡
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 524 |
| 13 | Нет текста... | 2 187 |
| 14 | የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉ ደሳለኝ ጫኔ(ዶ/ር) በመጨረሻ የፓርላማ ዘመናቸው ተከታዮቹን ጥያቄዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) አቅርበዋል፡፡
ሙሉ ጥያቄያቸውን ከታች ባለው ማስፈንጠሪያ ያገኙታል።
https://www.youtube.com/watch?v=MyvVTVI0UFo | 2 379 |
| 15 | “ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ቆመን እናጨብጭብላቸው፤ በኢትዮጵያ የፈነጠቀው ብርሃን፤ ይበልጥ እየፈካ ነው” የፓርላማ አባል መሐመድ አህመድ
ማክሰኞ፣ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ቀደም ሲል ከተነሱት የሰላምና የሰብዓዊ ቀውሶች ስጋቶች በተቃራኒ፣ የለውጡ ፍሬዎችና የብልጽግና ጉዞዎች በተግባር እየታዩ መሆናቸውን የጠቀሱት የፓርላማ አባል መሐመድ አህመድ፤ ሀገሪቱ በጥበብና በዕውቀት በሚመራ ብልህ አመራር ውስጥ እያለፈች በመሆኑ “ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ቆመን ልናጨበጭብላቸው ይገባል” ሲሉ ለአመራራቸው ያላቸውን ከፍተኛ አድናቆት ገለጹ።
በምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ ላይ ቀደም ሲል ከተነሱት የተለያዩ የልማት፣ የሰላምና የሰብዓዊ ጉዳዮች አስተያየቶች ቀጥለው ንግግር ያደረጉት የምክር ቤት አባሉ መሐመድ አህመድ፤ በሀገሪቱ የመጣው ለውጥ በተጨባጭ ውጤት የታጀበ መሆናቸውን በስፋት አብራርተዋል።
መሐመድ በንግግራቸው፤ “በሀገራችን የፈነጠቀው የለውጥ ብርሃን ይበልጥ እየፈካ፣ ፍሬው እየጎመራና የጋራ ተስፋችን ይበልጥ እያበበ መጥቷል” ካሉ በኋላ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ በየመስኩ እያሸተ ያለው የብልጽግና ፍሬ ሕይወቱን ከመሠረቱ እንደሚለውጠው ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
ሕዝቡ የጠቅላይ ሚኒስትሩን በጥበብና ዕውቀት የታገዘ ብልህ አመራር ተከትሎ፣ ተደምሮና ተባብሮ በጀመረው አቅጣጫ ለውጡን አፋጥኖ ቢጓዝ የዘመናት ምኞትና ተስፋው እውን እንደሚሆንለትም አክለዋል።
በመንግሥት ላይ የሚሰነዘሩ የተለዩ ትችቶችንና ቅሬታዎችን በብርቱ የሞገቱት የምክር ቤት አባሉ፤ ይህ ስኬት ለአሮጌ የጥላቻ ፖለቲካ አራማጆች እንደማይታይ ጠቁመዋል። “ሕሊናቸው በጥላቻ ሞራ ታውሯልና፤ ዓይናቸው ጥሩ ነገር ማየት አይችልም፤ አንደበታቸውም ከማጣጣልና ከማጠልሸት በስተቀር ምስጋናና ማበረታታትን አያውቅም” ሲሉ ተቃዋሚ ወገኖችን ወቅሰዋል።
ሀቅን ማየትና እውነታን መቀበል የሚችል ንጹህ ሕሊና የታደሉ ሁሉ ጉዳዩን በግልጽ እንደሚገነዘቡት የገለጹት መሐመድ፤ በጠቅላይ ሚኒስትሩ አመራር የዲሞክራሲ ባህል እንዲጎለበት፣ መብቶችና ነጻነቶች እንዲከበሩ እንዲሁም የፖለቲካ ምህዳሩ እንዲሰፋ መደረጉን አንስተዋል። ሁሉም ተዋናይ በሀገሩ ጉዳይ እኩል ተሳትፎ ኖሮት በነጻነት እንዲቀሳቀስ የሚያስችል የፖለቲካ ዐውድ በመፍጠር ረገድ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የአመራር ሚና እጅግ ከፍተኛ መሆኑን አድንቀዋል።
የምክር ቤት አባሉ መሐመድ አህመድ ንግግራቸውን ሲያጠቃልሉም ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያላቸውን ክብር በመግለጽ “ረዥም ዕድሜና ጤና እመኝልዎታለሁ” ብለዋል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 450 |
| 16 | Нет текста... | 2 318 |
| 17 | “ፖለቲካዊ ቁጥር ማሳመር እንጂ ከእውነት የራቀ ነው” ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር)
ማክሰኞ፣ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
መንግሥት በጦርነትና በድርቅ ምክንያት የዕለት ደራሽ እርዳታ ያጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች እያሉ፣ የሰብዓዊ ድጋፍ ፈላጊዎችን ቁጥር ከ20 ሚሊዮን በላይ ወደ 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዝቅ አድርጎ ማቅረቡ “ፖለቲካዊ ቁጥር ማሳመር እንጂ ከእውነት የራቀ ነው” ሲሉ የምክር ቤት አባል ደሳለኝ ጫኔ(ዶ/ር) ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ባቀረቡት ጥያቄ ተናገሩ።
በምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ ላይ ጥያቄ ያነሱት ደሳለኝ ጫኔ፤ መንግሥት የመረጃ ማጥራት ሥራ ሠርቻለሁ በሚል ሰብዓዊ ድጋፍ የሚፈልጉ ዜጎችን ቁጥር እጅግ አሳንሶ ማቅረቡን ተቃውመዋል።
በተለያዩ አካባቢዎች ለቤተሰቦቻቸው የሚሆን በቂ ምርት የማያመርቱና ለከፋ ችግር የተጋለጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች መኖራቸውን በመጠቆም፣ “ይህንን ቁጥር ወደ 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዝቅ አድርጎ ማቅረብ ፖለቲካዊ ቁጥር ማሳመር እንጂ የዜጎችን ሕይወት በተጨባጭ የሚያሳይ አይደለም” ሲሉ ወቅሰዋል።
ከተለያዩ ዓለም አቀፍ የእርዳታ ተቋማት የሚወጡ መረጃዎችን የጠቀሱት የምክር ቤት አባሉ፤ ተቋማቱ የሚያስቀምጡት ዝቅተኛ ግምት እንኳ ኢትዮጵያ ውስጥ ከ15 ነጥብ 8 እስከ 21 ነጥብ 4 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች በከፍተኛ የምግብ እጥረት ውስጥ እንደሚገኙ የሚያሳይ መሆኑን አብራርተዋል።
ዶ/ር ደሳለኝ አክለውም መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የእርዳታ እህል እንዳያከፋፍሉ በመንግሥት መከልከላቸውንና ድጋፋቸውን ወደ ጥሬ ገንዘብ እንዲቀይሩ መገደዳቸውን ገልጸዋል። ይህ አሠራር አሁን ካለው የገበያ የዋጋ ግሽበት አንጻር “በርካታ ቤተሰቦችን ለከፋ የምግብ ዋስትና እጥረት የሚዳርግ ነው” ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።
በማክሮ ኢኮኖሚው ረገድ ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅት እና ከዓለም ባንክ የሚገኘውን የገንዘብ ድጋፍ ያነሱት ደሳለኝ፤ “በርካታ ገንዘብ ወደ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚ እያስገቡ መሆኑና በማክሮ ኢኮኖሚው ላይ መረጋጋት መታየቱ ይበል የሚያሰኝ ቢሆንም፣ የተገኘው ለውጥ የኢትዮጵያውያንን ሕይወት በተግባር ካልቀየረ ዘላቂ ትርጉም አይኖረውም” ብለዋል።
የሀገሪቱን ዘላቂ ሰላምና ዕድገት ለማረጋገጥ መዋቅራዊ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባ የገለጹት የምክር ቤት አባሉ፣ “የችግሮቻችንን ሥር መሠረት ችላ በማለት በጊዜያዊ ማስታገሻዎች ሀገርን ረጅም መንገድ መውሰድ አይቻልም” ሲሉ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 485 |
| 18 | Нет текста... | 2 290 |
| 19 | በቀጣዩ የመንግሥት የሥራ ዘመን ዘላቂ ሰላም፣ ብሔራዊ መግባባት እና የሕግ የበላይነትን ማስፈን ላይ ትኩረት እንዲደረግ የምክር ቤት አባል ጠየቁ
ማክሰኞ፣ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
ይህ የተባለው በምክር ቤቱ የ5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 30ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሪፖርታቸው ያነሷቸው የኢኮኖሚ እና የልማት ስኬቶች የሚበረታቱ ቢሆኑም፣ የልማት ውጤቶች መሠረት ግን ዘላቂ ሰላም መሆኑን መብራቱ ዓለሙ (ዶ/ር) ገልጸዋል።
በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች የሚኖሩ ዜጎች በመረጋጋት መኖርን፣ በነፃነት መንቀሳቀስን፣ ሀብታቸውን ማልማትንና ልጆቻቸውን በሰላም ማስተማርን አጥብቀው የሚፈልጉት ጉዳይ መሆኑንም አክለዋል።
በመሆኑም በቀጣዩ የሥራ ዘመን መንግሥት ዘላቂ ሰላም ለማስፈን፣ የብሔራዊ መግባባት ሂደትን ለማፋጠን፣ የሕግ የበላይነትን በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች በእኩል ለማረጋገጥ እና የዜጎችን ደህንነት ለመጠበቅ ምን ዓይነት አዳዲስ የተጠናከሩ ፖሊሲዎችና ተቋማዊ እርምጃዎችን ለመተግበር አቅዷል? ሲሉ ጥያቄያቸውን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ሰንዝረዋል።
በተጨማሪም የኑሮ ውድነትን፣ የሥራ ዕድል ፈጠራንና አካታች ኢኮኖሚን በተመለከተ ማብራሪያ የጠየቁት የምክር ቤት አባሉ፤ የመሠረታዊ ሸቀጦች ዋጋ መናር እና የሥራ ዕድል እጥረት የወጣቶችን ተስፋ እየፈተነ መሆኑን ጠቁመዋል።
በመሆኑም በቀጣዩ የበጀት ዓመት አዲሱ መንግሥት ሲዋቀር የዋጋ ንረትን በዘላቂነት ለመቀነስ፣ ለወጣቶችና ለሴቶች የሥራ ዕድልን በመፍጠርና በማስፋፋት የግሉን ዘርፍ ለማጠናከር፣ እንዲሁም የኢኮኖሚ ዕድገት ፍሬን ለሁሉም ዜጎችና ክልሎች በፍትሐዊነት ለማዳረስ መንግሥት ምን ዓይነት እርምጃዎችን ለመውሰድ እንዳቀደ ጠይቀዋል።
በመሠረተ ልማት በኩልም ሁሉም ክልሎች በእኩል ተጠቃሚ እየሆኑ እንዳልሆነ ያነሱት ዶ/ር መብራቱ፤ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የአስፋልት መንገድ አለመኖር፣ የቴሌኮም አገልግሎት መቆራረጥ እና የኤሌክትሪክ አገልግሎት አለመዳረስ እንደ ትልቅ ችግር የሚታዩ ቢሆንም እስካሁን እልባት አላገኙም ብለዋል።
በመሆኑም በቀጣዩ ዓመት በመሠረተ ልማት ግንባታ ረገድ ለነዚህ ጉዳዮች ልዩ ዕቅድ ሊያዝ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 533 |
| 20 | Нет текста... | 2 338 |
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
