Addis Maleda - አዲስ ማለዳ
📈 تحلیل کانال تلگرام Addis Maleda - አዲስ ማለዳ
کانال Addis Maleda - አዲስ ማለዳ (@addismaleda) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 31 885 مشترک است و جایگاه 7 857 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 1 064 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 31 885 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 10 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 141 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 7 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 19.09% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 10.84% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 6 086 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 3 458 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 15 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“ዜና ከምንጩ”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 11 ژوئن, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 11 ژوئن | +3 | |||
| 10 ژوئن | +13 | |||
| 09 ژوئن | +4 | |||
| 08 ژوئن | +17 | |||
| 07 ژوئن | +14 | |||
| 06 ژوئن | +6 | |||
| 05 ژوئن | +5 | |||
| 04 ژوئن | +5 | |||
| 03 ژوئن | +18 | |||
| 02 ژوئن | +17 | |||
| 01 ژوئن | +34 |
| 2 | بدون متن... | 971 |
| 3 | በእነክርስቲያን ታደለ የክስ መዝገብ ፍርድ ቤቱ ለዋናው ብይን መደበኛ ቀጠሮ ባይሰጥም፤ ማረሚያ ቤቱ ግን ለሰኔ 16 ተቀጠረ
ሐሙስ፣ ሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነክርስቲያን ታደለ የክስ መዝገብ ላይ “ክሳቸውን ይከላከሉ ወይስ በነፃ ይሰናበቱ?” የሚለውን ዋና ብይን ለመስጠት መደበኛ ቀጠሮ ለመቁረጥ ፈቃደኛ ሳይሆን መቅረቱን የተከሳሾቹ ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ ለአዲስ ማለዳ ገለጹ።
ፍርድ ቤቱ ለብይኑ መደበኛ ቀን ባይቆርጥም፣ ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት እየተፈጸመብን ነው ስላሉት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ግን የማረሚያ ቤቱ ኃላፊ ማብራሪያ ይዘው እንዲቀርቡ ለሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ጠበቃ ሰለሞን ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ስለነበረው የችሎት ውሎ እንደተናገሩት፣ ተከሳሾቹ “ፍርድ ቤቱ ለብይኑ ለምንድነው ቀጠሮ የማይሰጠን?” ሲሉ ላቀረቡት ጥያቄ፣ ችሎቱ ሲመልስ “ጉዳዩ ሊያልቅ የተወሰነ ነገር ስለሆነ የቀረው ይሄ ነው የሚባል ቀን አልወስንም” ማለቱን ገልጸዋል።
በመሆኑም ጉዳዩ ሊጠናቀቅ የተቃረበ በመሆኑ፣ ፍርድ ቤቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰቱን ለመስማት በሰየመው በዚሁ “በሰኔ 16 ቀን ላይ ዋናው ብይን ሊገለጽ ይችላል፤ ካልሆነ ግን ከዛ በኋላ ባሉት ቀናት ልናሰማ እንችላለን” የሚል ውሳኔ ማስተላለፉን ጠበቃው ጠቅሰዋል።
በዕለቱ ተከሳሾቹ “ጉዳዩን የሚከታተሉ የሚዲያ አካላት እና ቤተሰቦቻችን ቀኑን ቀድመው ማወቅና መስማት ስላለባቸው መደበኛ ቀጠሮ ሊሰጠን ይገባል” የሚል ጠንከር ያለ ጥያቄ ቢያነሱም፣ ችሎቱ ግን ተጨማሪ ቀጠሮ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆን “በሰኔ 16 ወይም ከዚያ በኋላ ብይኑን እናሰማለን” በማለት የዕለቱን ችሎት ማጠናቀቁ ታውቋል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 1 292 |
| 4 | بدون متن... | 1 226 |
| 5 | የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ለነዳጅ ተሽከሪካሪዎች የሚሰጠው ሰሌዳ ዋጋ እስከ 56 ሺህ ብር እንደሚያስከፍል አስታወቀ
ሐሙስ፣ ሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ መስጠት የጀመረ ሲሆን፣ ለነዳጅ ተሽከርካሪዎች የሚሰጠው ሰሌዳ ዋጋ እስከ 56 ሺህ ብር መሆኑን ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል።
ባለሥልጣኑ እንደገለጸው፣ ይህ የወጣው ዋጋ አዲሱ የቴክኖሎጂ ሰሌዳ የሚሰጠውን የረዥም ጊዜ አስተማማኝ ጥቅም ከግምት ውስጥ ያስገባ ነው።
አዲሱ የሰሌዳ አሰጣጥ አገልግሎት በዛሬው ዕለት በባለሥልጣኑ 11 ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች በይፋ የተጀመረ ሲሆን፣ በቅድሚያ ሰሌዳ ለማውጣት ተመዝግበው በመጠባበቅ ላይ ለሚገኙ ከአንድ ሺህ በላይ ደንበኞች እየተሰጠ ይገኛል።
በቀጣይም የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር በሚያወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ሌሎች ተሽከርካሪዎችም ደረጃ በደረጃ አዲሱን ሰሌዳ እንዲወስዱ ይደረጋል።
ይህ አዲስ ሰሌዳ ከተሽከርካሪዎች ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ የደኅንነትና የሥርቆት ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት እንዲያስችል ተደርጎ ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር የተሳሰረ መሆኑ ተገልጿል።
አሁን ላይ በሥራ ላይ የዋለው ሰሌዳ ከቻይና ተመርቶ የገባ ቢሆንም፣ ለአመራረት ቀላል በመሆኑ በቀጣይ በአገር ውስጥ ተመርቶ ተደራሽ ለማድረግ መታቀዱም ተመልክቷል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 1 717 |
| 6 | بدون متن... | 1 628 |
| 7 | የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ለነዳጅ ተሽከሪካሪዎች የሚሰጠው ሰሌዳ ዋጋ እስከ 56 ሺህ ብር እንደሚያስከፍል አስታወቀ
ሐሙስ፣ ሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ መስጠት የጀመረ ሲሆን፣ ለነዳጅ ተሽከርካሪዎች የሚሰጠው ሰሌዳ ዋጋ እስከ 56 ሺህ ብር መሆኑን ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል።
ባለሥልጣኑ እንደገለጸው፣ ይህ የወጣው ዋጋ አዲሱ የቴክኖሎጂ ሰሌዳ የሚሰጠውን የረዥም ጊዜ አስተማማኝ ጥቅም ከግምት ውስጥ ያስገባ ነው።
አዲሱ የሰሌዳ አሰጣጥ አገልግሎት በዛሬው ዕለት በባለሥልጣኑ 11 ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች በይፋ የተጀመረ ሲሆን፣ በቅድሚያ ሰሌዳ ለማውጣት ተመዝግበው በመጠባበቅ ላይ ለሚገኙ ከአንድ ሺህ በላይ ደንበኞች እየተሰጠ ይገኛል።
በቀጣይም የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር በሚያወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ሌሎች ተሽከርካሪዎችም ደረጃ በደረጃ አዲሱን ሰሌዳ እንዲወስዱ ይደረጋል።
ይህ አዲስ ሰሌዳ ከተሽከርካሪዎች ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ የደኅንነትና የሥርቆት ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት እንዲያስችል ተደርጎ ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር የተሳሰረ መሆኑ ተገልጿል።
አሁን ላይ በሥራ ላይ የዋለው ሰሌዳ ከቻይና ተመርቶ የገባ ቢሆንም፣ ለአመራረት ቀላል በመሆኑ በቀጣይ በአገር ውስጥ ተመርቶ ተደራሽ ለማድረግ መታቀዱም ተመልክቷል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 1 |
| 8 | ለቀጣዩ በጀት ዓመት የማዳበሪያ ድጎማ 100 ቢሊዮን ብር መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ
ሐሙስ፣ ሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የገንዘብ ሚኒስቴር ለ2019 ዓ.ም ለማዳበሪያ ድጎማ እንዲውል የታሰበው በጀት 100 ቢሊዮን ብር አድርጎ ለህዝብ እንደራሴዎች አቅረበ። ሚኒስቴሩ ለ2019 በጀት ዓመት 2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ አድርጎ ረቂቁን ያቀረበ ሲሆን በበጀት ዓመቱ የፌደራል መንግስት ከሀገር ውስጥ ገቢ ምንጮች እና ከውጭ ሀገር እርዳታ 1.8 ትሪሊዮን ገቢ ለመሰበስብ እቅድ መያዙን ተናግሯል።
የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ በዛሬው ዕለት በቀጣዩ የሐምሌ ወር ላይ የሚጀምረውን የበጀት ዓመት ዝርዝር እና መጠን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 5ተኛ ዓመት የሥራ ዘመን 25ተኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ቀርበው አብራርተዋል፡፡
ከማዳበሪያ በተጨማሪ ለነዳጅ ድጎማ እንዲውል የታሰበው በጀት 20 ቢሊዮን ብር እንደሆነ የገለጹት ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ካፒታልን ለማሳደግ 116.4 ቢሊዮን ብር ከመንግስት ግምጃ ቤት የተመደበ መሆኑን ለፓርላማው አስረድተዋል ።
ከዚሁ በተጨማሪም ለልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ማስፋፊያ የሚያስፈልገውን በጀት ከግምት ውስጥ በማስገባት የካፒታል ወጪዎች በዋናነት የነባር ፕሮጀክቶችን ለማስፈፀም የሚያስፈልገውን ወጪ እንዲያካትት መደረጉን ተገልጿል።
የክልሎችን የበጀት ድጋፍ በተመለከተ በ2018 የተደረገውን የክልል ሰራተኞች እና ተሿሚዎች የደመወዝ ጭማሪ ማስተካከያ ዓመታዊ ወጪን በ2018 ከጸደቀው የክልሎች የጥቅል በጀት ድጋፍ ጋር በመደመር ለ2019 በጀት ዓመት እስከ አምስት በመቶ ጭማሪ እንዲኖረው ተደርጓል ብለዋል። ሚኒስትሩ አክለውም በአጠቃላይ የ2019 የመንግስት ወጪ ፖሊሲ የፊስካል ቁመናን ማጠናከር እና የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባትን በሚያስተካክል መልኩ የተዘጋጀ ነው ብለዋል ።
የ2019 የፌደራል መንግስት ረቂቅ በጀት የተመጠነ የበጀት ጉድለት እንዲኖረው ተደርጎ የተዘጋጀ በጀት ነው ያሉ ሲሆን ይህም ከ ሀገር ውስጥ እና ዉጭ በሚገኝ ገንዘብ እንደሚሸፈን አንስተዋል።
የ2019 የፌደራል መንግስት ረቂቅ በጀት የተመጠነ የበጀት ጉድለት እንዲኖረው ተደርጎ የተዘጋጀ በጀት ነው ያሉ ሲሆን ይህም ከ ሀገር ውስጥ እና ዉጭ በሚገኝ ገንዘብ እንደሚሸፈን አንስተዋል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 389 |
| 9 | بدون متن... | 2 130 |
| 10 | አሜሪካ በኢራን ላይ በከባድ ቦንቦች የታገዘ ድብደባ ማድረሷን ተከትሎ ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥ ሙሉ ለሙሉ መዝጋቷን አስታወቀች
ሐሙስ፣ሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ ማለዳ)
በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ወታደራዊ ግጭት በከፍተኛ ሁኔታ ማገርሸቱን ተከትሎ፣ የኢራን ወታደራዊ ዕዝ የዓለም የነዳጅ አቅርቦት ቁልፍ መተላለፊያ በሆነው የሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የነዳጅ ጫኝ መርከቦችንና የንግድ ትራፊክን ሙሉ በሙሉ መዝጋቱን አስታወቀ።
ኢራን ይህን አስቸኳይ እርምጃ የወሰደችው የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግዝ አሜሪካ በኢራን ቁልፍ ተቋማት ላይ ጠንካራ የአየር ድብደባ ማድረሷን በይፋ ከገለጹ በኋላ ሲሆን አሁን ላይ ምንም ዓይነት መርከብ ቦታው ማለፍ አይችልም ብላለች። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኢራን ስምምነቱን የማትቀበል ከሆነ በነገው ዕለት አይታው የማታውቀው ጥቃት እንፈፅማለን ሲሉ ዝተዋል።
የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግዝ በፍሎሪዳ ከሚገኘው የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ዋና መሥሪያ ቤት በሰጡት መግለጫ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ያስተላለፉትን ትዕዛዝ መሠረት በማድረግ የአሜሪካ ጦር በኢራን ውስጥ በሚገኙ ቁልፍ ወታደራዊ እና የስትራቴጂክ ተቋማት ላይ የቦምብ ድብደባ አካሂደናል ሲሉ አስታውቀዋል። ሚኒስትሩ ይህንን እርምጃ “ኢራን በቀጣናው በምታሳየው መተናኮስ እና በሰላም ድርድሩ ላይ በወሰደችው ግትር አቋም” ምክንያት የመጣ መሆኑን በመግለፅ ጥቃቱ በተሳካ ሁኔታ መከናወኑንና የኢራንን ወታደራዊ አቅም ለማዳከም የታለመ ነው ሲሉ ተናግረዋል።
ይህንን የአሜሪካን ድብደባ ተከትሎ የኢራን ኻታም አል-አንቢያ የተሰኘው ከፍተኛ ጥምር ጦር እዝ አስቸኳይ መግለጫ ያወጣ ሲሆን የሆርሙዝ ወሽመጥ ለማንኛውም ዓይነት የባህር ላይ ትራፊክ በተለይም ለነዳጅ ጫኝ እና ለንግድ መርከቦች ሙሉ በሙሉ ዝግ መሆኑን አስታውቋል።
እዙ አክሎም ትዕዛዙን ጥሶ ለመሻገር በሚሞክር በማንኛውም መርከብ ላይ ጦሩ ወታደራዊ እርምጃ ይወስዳል ሲል አስጠንቅቋል። የኢራን መንግስታዊ ሚዲያዎች በሆርሙዝ አቅራቢያ በነበሩ የአሜሪካ የጦር መርከቦች ላይ የ ሚሳኤልና የድሮን ጥቃት መሰንዘሩን የዘገቡ ቢሆንም የአሜሪካ ወታደራዊ ባለሥልጣናት ግን የተመታ መርከብ የለም በማለት አስተባብለዋል።
አሁን ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለፍጆታ የሚውለው የድንጋይ ከሰልና የነዳጅ አቅርቦት አንድ አምስተኛው የሚሻገርበት የሆርሙዝ ወሽመጥ መዘጋት በዓለም የነዳጅ ገበያ ላይ ወዲያውኑ ከፍተኛ ጭማሪ አስከትሏል ሲል ለሮይተርስ ዘግቧል።
እንደ አዲስ የተከሰተው ይህ ወታደራዊ ግጭት ባለፈው ሚያዝያ ወር ላይ በሁለቱ ወገኖች መካከል ተደርሶ የነበረውን ደካማ የተኩስ አቁም ስምምነት ሙሉ በሙሉ ያፈረሰ ሲሆን የመካከለኛው ምስራቅ ቀጣና በሙሉ ወደ ከፋ የጦርነት ቀውስ ሊከተው እንደሚችል ዓለም አቀፍ ተንታኞች ስጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 326 |
| 11 | بدون متن... | 2 009 |
| 12 | በአፋር ክልል በራህሌ ወረዳ የተከሰተውን ሰደድ እሳት መቆጣጠር አስቸጋሪ ሁኖብኛል አለ
ሐሙስ፣ሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ ማለዳ)
በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት፣በኪልበቲ ረሱ ዞን ራህሌ ወረዳ በሚገኝ ጥብቅ ደን ውስጥ ድንገተኛ የሰደድ እሳት መከሰቱን አሰታውቆ መቆጣጠር አስቻጋሪ ሁኖብኛል ሲል አስታወቀ።
እሳቱ የተከሰተው ትላንት በትላንትናው ዕለት ዕኩለ ቀን ላይ ሲሆን በወረዳው ሃሌጉቢ ቀበሌ፣ ልዩ ስሙ አፋዓዶና ዔሊ ገረብ በተባለ ስፍራ መሆኑን የክልሉ መረጃ ያመላክታል። አደጋው እንደተከሰተ የአካባቢው ማህበረሰብ እና የወረዳው አመራሮች በጋራ በመሆን እሳቱን ለመቆጣጠር ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ መሆኑን አንስቷል።
ክልሉ አክሎም እስካሁን ባለው ሂደት በሰው ሕይወት፣ በእንስሳትና በንብረት ላይ የደረሰ ጉዳት የሌም ያለ ቢሆንም እሳቱን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ማዋል ግን አዳጋች ነው ብሏል። ለእሳቱ መባባስና በቁጥጥር ስር አለመዋል እንደ ምክንያት ያነሳው የአካባቢው ጥቅጥቅ ያለና ጥብቅ የደን ሽፋን በመሆኑ፤ ከፍተኛ የሙቀት እና ደረቅ የአየር ሁኔታበመኖሩ መሆኑን አንስቷል።
ክልሉ በተጨማሪም መልክዓ ምድሩ ተራራማና አስቸጋሪ በመሆኑ የእሳት አደጋ መከላከያ ተሽከርካሪዎች ወደ ስፍራው መድረስ አለመቻላቸው ለመቆጣጠር አዳጋች መሆኑን ባወጣው መግለጫ አንስቷል።
እነዚህ ተግዳሮቶች እሳቱ ወደ ሌሎች አጎራባች አካባቢዎች እንዳይዛመት ለመከላከል እየተደረገ ያለውን ጥረት በእጅጉ ፈታኝ አድርገውታል ያለ ሲሆን ለመቆጣጠር የሚደረገው ጥረት በቂም አለመሆኑን አንስቷል።
የሰደድ እሳቱን ለመቆጣጠር በራህሌ ወረዳ ብቻ የሚደረገው ጥረት በቂ አይደለም ያለ ሲሆን የጎረቤት ወረዳዎች ማለትም የኮነባ፣ አብዓላ፣ ዔረብቲ፣ ወሰማ እና የአፍዴራ ሕዝብ እንዲሁም ሌሎች የክልሉ የሕብረተሰብ ክፍሎች በጋራ በመረባረብና በቅንጅት በመስራት አደጋውን እንዲከላከሉ እና እግዛ እንድያደርጉለት ጥሪ ቀርቧል።
አደጋውን ለመቀልበስ የሚያስችል የተቀናጀ የሰው ኃይል ድጋፍ አሁንም ወሳኝ በመሆኑ ሁሉም አካላት በኃላፊነት ሊንቀሳቀሱ ይገባል ያለ ሲሆን በአካባቢው ያለውን ከፍተኛ የሙቀት መጠን ከግምት በማስገባት በደን ውስጥ በሚፈጠሩ የተፈጥሮ ግጭቶች የእሳት አደጋ ሊቀሰቀስ ስለሚችል ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስቧል።
ክልሉ አክሎም በስፋት እየተከናወነ ካለው የንብ ማነብ ተግባር ጋር ተያይዞ የእሳት አደጋ ሊከሰት ስለሚችል አርሶና አርብቶ አደሩ እሳትን በሚጠቀምበት ወቅት ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ እንዲንቀሳቀስ የሚመለከተው ቢሮ በአጽንኦት ማሳሰቢያ ሰጥቷል።
በተለያዩ አካባቢዎችም የደን ቃጠሎ በሚከሰቱበት ወቅት ለመቆጣጠር አዳጋች መሆናቸውንም ይህ የመጀመሪያው አይደለም።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 216 |
| 13 | بدون متن... | 2 059 |
| 14 | ኦፌኮ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ “አምባገነናዊነትን ሕጋዊ ለማድረግ የተወጠነ የፖለቲካ ድራማ” ሲል ኮነነ
ሐሙስ፣ ሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተካሄደውን 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ በትናንትናው ዕለት ባወጣው መግለጫ፤ ሂደቱ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን፣ መረጋጋትንና ዴሞክራሲያዊ አስተዳደርን እንደማያመጣ በጽኑ እንደሚያምን አስታወቀ።
ፓርቲው በተደጋጋሚ በግልጽ ማሳሰቡን ባስታወሰበት በዚሁ መግለጫው፤ ሰፋፊ የሀገሪቱ ክልሎች ውስጥ አውዳሚ የእርስ በእርስ ጦርነት እየተካሄደ ባለበት፣ ሰፊ የፖለቲካ ጭቆና በነገሰበት እና የፖለቲካ ምህዳሩ በተዘጋበት ሀገር ላይ በግድ የተጫነ የምርጫ ሂደት የዴሞክራሲ ምዕራፍ ሳይሆን “አምባገነናዊነትን ሕጋዊ ለማድረግ የተወጠነ የፖለቲካ ድራማ” መሆኑን አስገንዝቧል።
ኦፌኮ በመግለጫው እንዳብራራው፣ ፓርቲውን ጨምሮ እውነተኛ ያላቸው ተቃዋሚ ፓርቲዎች ነፃ፣ ፍትሐዊ እና ታማኝ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስፈልጉ መሠረታዊ ቅድመ ሁኔታዎችን ከአንድ ዓመት በላይ በግልጽ ሲጠይቁ ቆይተዋል። ከእነዚህም መካከል፤ ግጭቶች በአስቸኳይ እንዲቆሙ፣ የፖለቲካ እስረኞች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ፣ የተዘጉ የፓርቲ ጽሕፈት ቤቶች እንዲከፈቱ፣ አፋኝ የሚዲያ እና የሲቪል ማኅበረሰብ ሕጎች እንዲሰረዙ፣ እንዲሁም ገለልተኛና በጋራ መግባባት ላይ የተመሠረተ የምርጫ ቦርድና የጸጥታ አካላት እንዲዋቀሩ የሚሉት ይገኙበታል።
ሆኖም መንግሥት እነዚህን ጥሪዎች ወደ ጎን በመተው ምርጫውን ለይስሙላ ለማካሄድ በመወሰኑ፣ ፓርቲው ሕጉን ለማክበር ሲል ብቻ ጥቂት ዕጩዎችን በማቅረብ እጅግ የተገደበና ተምሳሌታዊ ተሳትፎ ማድረጉን ገልጿል።
የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ ምርጫው በዜጎች የመምረጥ መብት ላይ ከፍተኛ ገደብ የጣለ መሆኑን ጠቅሶ፣ በተለይም በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ባለው አውዳሚ ጦርነት ምክንያት ሂደቱ በከፍተኛ ወታደራዊ ጥበቃ ስር ባሉ ዋና ዋና ከተሞች ብቻ የተገደበ እንደነበርና የትግራይ ክልል ደግሞ ሙሉ በሙሉ እንዳልተካተተበት ገልጿል።
ሂደቱ በተከናወነባቸው አካባቢዎችም የምርጫ አስፈጻሚዎች ግልጽ አድሏዊነት፣ በመራጮች ላይ ማስፈራራት እንዲሁም የተቃዋሚ ተወካዮችን ከምርጫ ጣቢያ በኃይል የማስወጣት ሕገ-ወጥ ድርጊቶች መታዘቡን ጠቅሶ ፓርቲው ከስሷል።
የዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ ታዛቢዎችን ተሳትፎ በተመለከተም ኦፌኮ ጠንካራ ትችት ሰንዝሯል፡፡
የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ልዑካን አቋም በተመለከተ፤ ከ52,000 በላይ የምርጫ ጣቢያዎች ባሉባት ሀገር 100 የማይሞሉ ታዛቢዎችን በማሰማራት፣ ደህንነታቸው በተጠበቁ 208 (0.4%) ጣቢያዎች ላይ ብቻ በመገኘት ያወጡት የ“ሰላማዊና ግልጽነት” ሪፖርት “የምርጫ ዕለት ቱሪዝም” እንጂ እውነተኛ የታዛቢነት ሚና አይደለም ብሎታል።
የአውሮፓ ኅብረት አቋምን ደግሞ፤ በአካል ታዛቢ ሳይሰማራ፣ በርቀት ሆኖ ምርጫውን በበጎ መመልከቱ የኅብረቱን የዴሞክራሲ እሴቶች የሚጻረርና “የዲፕሎማሲ ማባበያ” ነው ሲል ኮንኖታል።
ኦፌኮ የሀገሪቱ ጥልቅ የፖለቲካ፣ የማኅበራዊና የኢኮኖሚ ስብራት ነፃና ፍትሐዊ ባልሆነ ምርጫ ሊጠገን እንደማይችል በመግለጽ፣ ብቸኛው አዋጭ መንገድ “ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ውይይት” ማካሄድ ብቻ መሆኑን አጽዕኖት ሰጥቷል። ይህ ውይይት በአሁኑ ወቅት ከመንግሥት ጋር በጦርነት ላይ ያሉ ታጣቂ ኃይሎችን ጨምሮ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ያካተተና በድርድር ላይ ለተመሠረተ አዲስ የፖለቲካ ስምምነት ፍኖተ ካርታ መሰረት የሚጥል መሆን እንዳለበት አሳስቧል።
በመጨረሻም ፓርቲው ሦስት አስቸኳይ ጥሪዎችን አስተላልፏል፤ ለኢትዮጵያ መንግሥት፤ የፖለቲካ ልዩነቶችን በወታደራዊ ኃይል የመፍታት ስልት እንደማይሠራ ተገንዝቦ፣ ግጭቶችን በአስቸኳይ እንዲያቆም፣ የፖለቲካ እስረኞችን እንዲፈታና ለሁሉን አቀፍ ውይይት እርምጃ እንዲወስድ፤
ለኢትዮጵያ ሕዝቦች፤ መሠረታዊ ችግሮች በዚህ ምርጫ እንደማይፈቱ በመረዳት፣ ለእውነተኛ ራስን በራስ ማስተዳደር፣ ለፍትሕ እና ለእውነተኛ ሕብረ-ብሔራዊ ፌዴራሊዝም በሚደረገው ሰላማዊ ትግል ላይ እንዲጸኑ፤
ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ፤ ሂደቱ ነፃና አካታች እንዳልነበር በመገንዘብ፣ መንግሥት ሐቀኛና ሁሉን አቀፍ ሀገራዊ ውይይት እንዲያካሂድ ትርጉም ያለው ጫና እንዲያሳድር ጥሪ አቅርቧል። በመጨረሻም የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ዴሞክራሲያዊት እና ሰላማዊት ፌዴራል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ትግሉን በቁርጠኝነት እንደሚቀጥል በመግለጫው ማጠቃለያ አስታውቋል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 499 |
| 15 | بدون متن... | 2 519 |
| 16 | የቻይናው ፕሬዝዳንት ሰሜን ኮሪያን መጎብኘታቸውን ተከትሎ ሁለቱ ሀገራት ከሉዓላዊነት መከበር እስከ ኢኮኖሚ ትብብር የሚዘልቅ አጋርነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ
ረቡዕ፣ ሰኔ 03 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ በሰሜን ኮሪያ ፒዮንግያንግ ባደረጉት ጉብኝት፣ ከሀገሪቱ መሪ ኪም ጆንግ ኡን ጋር በመሆን ስልታዊ ትብብራቸውን ይበልጥ ለማሳደግ ቃል ገብተዋል። በፒዮንግያንግ በተካሄደው በዚህ ጉባኤ መሪዎቹ ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጥበቅ የተስማሙ ሲሆን፣ ሰሜን ኮሪያ ታይዋን፣ የቻይና ጠቅላላ የግዛት አካል መሆኗን በድጋሚ አረጋግጣለች።
የሰሜን ኮሪያ ብሔራዊ የዜና አገልግሎት እንደዘገበው፤ ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። መሪዎቹ ይበልጥ የተቀራረበ ስልታዊ ግንኙነት ለመፍጠር በተስማሙበት ወቅት ኪም ጆንግ ኡን በበኩላቸው፤ ከቻይና ጋር ያለውን ወዳጅነት ማስቀጠል ለሰሜን ኮሪያ “ከሁሉም በላይ ቅድሚያ የሚሰጠው ስልታዊ ተግባር” መሆኑን ገልጸዋል።
ኪም ጆንግ ኡን ፕሬዝዳንት ሺን “የላቀ የሀገር እንግዳ” በማለት የጠሯቸው ሲሆን፣ ሺ እ.አ.አ. 2026 የመጀመሪያ የውጭ ሀገር ጉዟቸውን ወደ ሰሜን ኮሪያ ማድረጋቸው ለሀገራቸው የተደረገ “ትልቅ ድጋፍ” መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም ፒዮንግያንግ ቤጂንግ ለምትከተለው “አንድ ቻይና መርህ” እና ታይዋን የቻይና የማይነጠል አካል ናት ለሚለው አቋም ያላትን ጽኑ ድጋፍ በድጋሚ ገልጻለች።
በሌላ በኩል የቻይናው ብሔራዊ ቴሌቪዥን እንደዘገበው፤ ቻይና በንግድ፣ በግብርና፣ በኮንስትራክሽን እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች ጭምር ከሰሜን ኮሪያ ጋር ያላትን ትብብር ለማስፋፋት ፍላጎት እንዳላት ፕሬዝዳንት ሺ አስታውቀዋል።
ይህ የቻይናው ፕሬዝዳንት የሰሜን ኮሪያ ጉብኝት ከሰባት ዓመታት በኋላ የተደረገ የመጀመሪያው ሲሆን፣ የሁለቱን ሀገራት የወዳጅነት ስምምነት 65ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ግንኙነታቸው “አዲስ ታሪካዊ መነሻ” ላይ መድረሱን መሪዎቹ በጋራ አውጀዋል።
ሰሜን ኮሪያ ከሩሲያ ጋር ያላት ወታደራዊና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እያደገ ቢመጣም፣ ለህልውናዋ ግን አሁንም በዋናነት በቻይና ላይ ጥገኛ መሆኗን ስለምታውቅ ከቤጂንግ ጋር ያላትን ትስስር ማጠናከር እንደምትፈልግ የፖለቲካ ተንታኞች ያነሳሉ።
ቻይናም በበኩሏ በስትራቴጂካዊ መልኩ ወሳኝ በሆነችው ሰሜን ኮሪያ ላይ ያላትን ተፅዕኖ በድጋሚ ለማረጋገጥ እና ከአሜሪካ ጋር ለምታደርገው ዓለም አቀፋዊ ፉክክር ይህንን ግንኙነት ይበልጥ ተጽዕኖ ለማሳደር እየተጠቀመችበት እንደሆነ ባለሙያዎች ይገመግማሉ።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 3 763 |
| 17 | بدون متن... | 3 544 |
| 18 | ኢራን በዮርዳኖስ፣ ኩዌትና ባህሬን በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ ጥቃት ሰነዘረች
ረቡዕ፣ ሰኔ 03 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
ኢራን በዮርዳኖስ በሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር እና በፋርስ ባህረ ሰላጤ ዙሪያ ባሉ ሌሎች 21 ኢላማዎች ላይ ጥቃት ሰነዘረች፡፡ ይህም ትራምፕ በሆርሙዝ ወሽመጥ አካባቢ ጥቃት እንዲሰነዘር ካዘዙ በኋላ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
የኢራን መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት የኢራን አብዮታዊ ዘብ ኃይሎች አሜሪካ ጥቃት ማድረሷን ተከትሎ በዮርዳኖስ በሚገኝ የአሜሪካ ጦር ሰፈር እና በፋርስ ባህረ ሰላጤ በሚገኙ 21 ሌሎች ኢላማዎች ላይ ረቡዕ ቀን የአጸፋ ጥቃት ሰንዝሯል። ግጭቱ ሁለቱ አገራት እንደ እ.አ.አ 2026 በሚያዝያ ወር ስምምነት ላይ ከደረሱ በኋላ ከተከሰቱት ከፍተኛ ጥቃቶች አንዱ ነው።
የኢራን ጥቃት በኩዌት እና በባህሬን ላይ የተፈሙ ጥቃቶችን ያካተተ ሲሆን ይህም የመጣው የአሜሪካ ጦር በኤክስ ገጹ ላይ ባወጣው መግለጫ በወሽመጡ አካባቢ የኢራን የአየር መከላከያ፣ የመሬት ቁጥጥር ጣቢያዎች እና የስለላ ራዳር ቦታዎች ላይ ጥቃት መሰንዘሩን መናገሩን ተከትሎ ነው።
የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጥቃቱ የተፈጸመው ማክሰኞ ዕለት አንድ የአሜሪካ አፓቼ ሄሊኮፕተር በኢራን ተመትቶ በመውደቁ ምክንያት ነው ብለዋል። ትራምፕ ለኤቢሲ ኒውስ እንደተናገሩት “ምላሹ በጣም ጠንካራ፣ በጣም ኃያል መሆን አለበት፤ የሆነውም እሱ ነው” ብለዋል።
የጥቃት መጠኑ መጨመር እ.አ.አ 2026 የካቲት 28 ቀን አንስቶ በአሜሪካ እና በእስራኤል በኢራን ላይ በጋራ በተሰነዘሩ ጥቃቶች የተጀመረውን ጦርነት ለማስቆም ሊደረስ የሚችለውን ስምምነት ጥርጣሬን ላይ ጥሎታል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 3 671 |
| 19 | بدون متن... | 3 366 |
| 20 | የአውሮፓ ህብረት ኮሚሽን በኢትዮጵያ የቡና ልማት መርሃ ግብሮች ላይ መረጃ አልሰጥም በማለቱ የህብረቱ እንባ ጠባቂ ተቋም አስተዳደራዊ በደል እየፈፀመ ነው አለ
ዕሮብ፣ ሰኔ 03 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የአውሮፓ ህብረት እንባ ጠባቂ ተቋም የአውሮፓ ኮሚሽን በኢትዮጵያ ከሚከናወኑ የቡና ልማት መርሃ ግብሮች ጋር የተያያዙ ሰነዶችን ለህዝብ ግልጽ እንዲያደርግ በቀረበለት ጥያቄ ላይ ወቅታዊ ምላሽ መስጠት ባለመቻሉ የህግ ጥሰት ፈፅሟል በሚል የህብረቱን መርህ የጣሰ ነው በሚል ውሳኔ አሳልፏል።
ይህ ውሳኔም የአውሮፓ ህብረት ተቋማት ግልጽነትና ተጠያቂነት እንዲሰፍን የሚጠይቀውን መመሪያ መሰረት በማድረግ በቀረበ አቤቱታ ላይ የተሰጠ ውሳኔ ነው ተብሏል።
አቤቱታ አቅራቢው አካል በአውሮፓ ኮሚሽን እጅ የሚገኙ እና በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚተገበሩ የቡና ልማት ፕሮጀክቶች ጋር የተያያዙ የህዝብ ሰነዶችን ለማግኘት ጥያቄ አቅርቧል።ይሁን እንጂ የአውሮፓ ኮሚሽን በተቀመጠው ህጋዊ የጊዜ ገደብ ውስጥ ምላሽ ሳይሰጥ በመቅረቱ ጉዳዩ ወደ አውሮፓ እንባ ጠባቂ ተቋም ሊያመራ ችሏል ብሏል።
እንባ ጠባቂ ተቋሙም ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ ኮሚሽኑ የአስተዳደር በደል ፈፅሟል ሲል ወስኗል። ኮሚሽኑ ለቀረበለት የሰነድ ፍለጋ ጥያቄ በተገቢው ጊዜ ምላሽ አለመስጠቱ አግባብ ያልሆነ አሰራር እና ህዝባዊ መረጃን የማግኘት መብትን የገደበ መሆኑን ገልጿል።
በሌላ በኩል ደግሞ የአውሮፓ ህብረት ተቋማት ከሶስተኛ ወገን ሀገራት ጋር የሚያደርጓቸውን የልማት ስምምነቶች እና የገንዘብ ድጋፎች ለህዝብና ለሲቪል ማህበረሰቡ ግልጽ ማድረግ እንዳለባቸው የህግ ማዕቀፍ ያለ ቢሆንም ከ ኢትዮጵያ ጋር ያለውን ስምምነት ግለፅ ባለመድረጉ ህጉን ጥሷል ተብሏል።
ይህ ውሳኔ በተለይ የአውሮፓ ህብረት አዲስ ያወጣው "ከደን መጨፍጨፍ ነጻ የሆኑ ምርቶች መመሪያ" በኢትዮጵያ የቡና ዘርፍ ላይ ሊያመጣ የሚችለውን ተፅዕኖ ተከትሎና በኢትዮጵያ የቡና ልማት ዙሪያ የሚደረጉ ድጋፎችና እንቅስቃሴዎች ላይ የሲቪል ማህበረሰቡ ክትትል ለማድረግ የሚረዳውን መረጃ ለማግኘት ትልቅ ፋይዳ አለው ተብሏል።
ኮሚሽኑ በቀጣይ የተጠየቁትን ሰነዶች በአስቸኳይ እንዲመረምርና ለአቤቱታ አቅራቢው ምላሽ እንዲሰጥ እንባ ጠባቂው ወስኗል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 3 820 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
