Addis Maleda - አዲስ ማለዳ
📈 تحلیل کانال تلگرام Addis Maleda - አዲስ ማለዳ
کانال Addis Maleda - አዲስ ማለዳ (@addismaleda) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 32 026 مشترک است و جایگاه 7 758 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 1 057 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 32 026 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 02 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 177 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 29 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 14.03% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.30% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 4 494 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 2 980 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 9 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“ዜና ከምንጩ”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 03 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 02 ژوئیه | +29 | |||
| 01 ژوئیه | +10 |
| 2 | بدون متن... | 1 825 |
| 3 | በዘይሴ ወረዳ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች በተፈጸመ ጥቃት 10 ሰዎች መሞታቸውን ኢሰመጉ ገለጸ
ሐሙስ፣ ሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ዘይሴ ወረዳ በመንግሥት ታጣቂ ኃይሎች በተፈጸመ ጥቃት የ10 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የገለጸው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ)፤ ድርጊቱን በአስቸኳይ እንዲቆም ጥሪ አቀረበ።
ኢሰመጉ ዛሬ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቀው፤ በዘይሴ ወረዳ በሚገኙ በተለያዩ ቀበሌዎች ውስጥ ከሰኔ 11 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በመንግሥት የታጠቁ ኃይሎች በተፈጸመ ጥቃት የ10 ሰዎች ሕይወት አልፏል።
በተጨማሪም በ3 ግለሰቦች ላይ የአካል ጉዳት፣ ጾታዊ ጥቃት፣ የንብረት ዘረፋና ውድመት እንዲሁም የጅምላ እስር መፈጸሙን ድርጅቱ ከአካባቢው ካሰባሰበው መረጃ ለማረጋገጥ መቻሉን ገልጿል።
ከአካባቢው በተነሱና ምላሽ ባላገኙ የማኅበረሰብ ጥያቄዎች ሳቢያ እየተባባሰ በመጣው በዚህ ጥቃት ምክንያት፣ በርካታ ነዋሪዎች ሕይወታቸውን ለማዳን ሲሉ መኖሪያ ቤታቸውን ለቀው ለመሰደድ መገደዳቸውን መግለጫው ያስረዳል።
ኢሰመጉ ቀደም ሲል በየካቲት ወር 2018 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ጥሪ አቅርቦ የነበረ ቢሆንም፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰቱ አሁንም ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል።
ጉዳዩን አስመልክቶ ከአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር መረጃ ለማግኘት የተደረገው ጥረት እስካሁን ባይሳካም፣ ወደፊት ተጨማሪ ምርመራዎችን በማድረግና የወረዳውን ምላሽ በማካተት ዝርዝር መረጃዎችን ይፋ የሚያደርግ መሆኑን አስታውቋል።
በመጨረሻም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) የተለያዩ ጥሪዎችን አስተላልፏል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልና የጋሞ ዞን የጸጥታ አካላት የንጹኃንን ደህንነት የመጠበቅና የሰብዓዊ መብቶችን የማክበር ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ፣
የጸጥታ አካላት በወንጀል የሚፈልጓቸውን ግለሰቦች በቁጥጥር ስር አውለው ፍትህ የማግኘት መብታቸውን እንዲያከብሩ፣
በክልሉ የሚነሱ ጥያቄዎች ሕግን በተከተለና ማኅበረሰቡን ባሳተፈ ሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ፣
በዘይሴ ማኅበረሰብ ላይ እየተፈጸመ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት በአስቸኳይ እንዲቆም ተገቢው ትኩረት ተሰጥቶ፣ በአካባቢው በደረሱት ጥሰቶች ላይ አፋጣኝ ማጣራት ተደርጎ ጥፋተኞች ለሕግ እንዲቀረቡ አበክሮ ጠይቋል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 714 |
| 4 | بدون متن... | 2 380 |
| 5 | የአዲስ አበባ እና ድሬዳዋ አጀንዳነት ከመንግስት መዋቅር ከሚለው ወጥተው ራሳቸውን የቻሉ አጀንዳ መሆናቸው እንዲሁም ሙስና አጀንዳ ሁኖ መቅረቡ ጥያቄ ተነሳበት
ሐሙስ፣ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የአዲስ አበባ እና የድሬድዋ ጉዳይ ራሱን ችሎ አጀንዳ ከመሆን የመንግስት አወቀቀር በሚለው አጀንዳ ስር መካተት ነበረባቸው የተባለ ሲሆን ሙስናን ደግሞ ሁሉም የሚጸየፈው እና በመኖሩ የሚስማማ ስለሌለ በምን አግባብ እና ሁኔታ አጀንዳ ሆነ ቀረብ ሲሉ የምክክር ጉባኤ ላይ ሃሳብ የሚያቀርቡ ምሁራን ምክክር ኮሚሽኑን ጠየቁ።
ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በምክክር ጉባኤው ላይ ሙያዊ ማብራሪያ ላይ የሚያቀርቡ ምሁራን ሚናን በተመለከተ በዛሬው ዕለት በስካይላይት ሆቴል በተደረገው የጋራ ውይይት የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተሞች አስተዳደራዊ መዋቅር፣ የሙስናና መልካም አስተዳደር አጀንዳ እንዲሁም የወጣቱ ትውልድ ሚና ተዳሰውበታዋል።
በመድረኩ ላይ የተሳተፉ አንድ ባለሙያ በአጀንዳ ቁጥር ሶስት ላይ የተቀመጠው ላይ ትችት ሰንዝረዋል። ይህም ትችት የተነሳው የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ጉዳይ ራሱን ችሎ በአጀንዳነት መቅረቡን ተከትሎ ነው።
እንደ ባለሙያው ገለጻ የከተሞቹ ጉዳይ በሀገሪቱ “የመንግስት መዋቅር ውስጥ ተካትቶ ሊታይ የሚገባው እንጂ እንዴት በተናጠልና ራሱን ችሎ ገለልተኛ አጀንዳ ሊሆን እንደቻለ” ግልጽ እንዳልሆነላቸው ጠንከር ያለ ጥያቄ አንስተዋል። ባለሙያው አክለውም ይህንን ያሉበትን ምክንያት ሲያስረዱ የመንግስት መዋቅር በዋናነት እንደዚህ ዓይነት ጉዳዮችን የሚመለከት በመሆኑ ነው ብለዋል።
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በበኩሉ የአዲስ አበባ እና ድሬድዋ ጉዳይ ራሱን ችሎ በአጀንዳነት እንዲቀርብ ብዙ ጊዜ የሚነሱ እና ግፊት የተደረገባቸው ከሆኑ ራሳቸውን ችለው እንዲቆሙ ይደረጋል ሲል ምላሽ ሰጥቷል።
ኮሚሽኑ አክሎም አሳማኝ ሃሳብ ያለው እና በአጀንዳ መቅረጹ ሂደት ውስጥ ብዙ ጊዜ ከተወያየበት በኋላ በአጀንዳነት እንደቀረፀው አስታውቋል።
ባለሙያው፣ ሙስና ለምን በአጀንዳነት ተካተተ ባይ ናቸው። የሙስና እና የመልካም አስተዳደር ጉዳይ ላይ የውይይቱ ፍሬ ነገር ምን ሊሆን እንደሚችል ብዥታ እንደተፈጠረባቸው ጠቁመዋል።
“የትኛውም የሀገራችን ክፍል ቢመጣ ሙስናን ማንም አይፈልግም፤ ይጸየፋል” ያሉት ባለሙያው እንደ ሀገራዊ መዋቅር ያሉ አጀንዳዎች “ይሄ ይሁን ወይስ ያኛው” ተብሎ አማራጭ የሚቀረብላቸው ሲሆን ሙስና ግን በተቃራኒው የሚቆምለት ሌላ ወገን የሌለው በመሆኑ በውይይቱ ላይ በምን መልኩ ተደርጎ ሊቀርብ እንደታሰበ ማብራሪያ ጠይቀዋል።
ሙስና የህግ ማሻሻያ ሁሉ የተጠየቀበት ጉዳይ ነው ያለው ኮሚሽኑ አጀንዳ ሁኖ መቅረቡ አዋጭ ነው ሲል ሞግቷል። እንዲሁም አሁን ላይ ሙስናን የሚመለከቱ ህግጋት ተፈጻሚነታቸው አነስተኛ እና ያለው ህግም በቂ ባለመሆኑ በአጀንዳነት እንዲቀረጽ ምክንያት ሁኗል ብሏል። ሐምሌ ስምንት በአዲስ ኮንቬንሽን ማዕከል የሚካሄደው የምክክር ጉባኤ 4000 የሚሆኑ ተሳታፊዎች እንደሚገኙበት ይጠበቃል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የምክክሩን ሂደት ወቅታዊ እና ሁለንተናዊ ይዘት መዳሰስ ያስፈልጋል ያሉት ሌላው ባለሙያ የማህበራዊ እና የወጣቶች ጉዳይ አንስተዋል። አሁን ያለው የኢትዮጵያ ወጣት ትውልድ በጦርነትና በግጭት አውድ ውስጥ ያደገ መሆኑን በማስታወስ ይህንን የጦርነት ባህል ወደ ሰላማዊ የውይይት ባህል ለመቀየር ትልቅ የአዕምሮ ለውጥ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል።
አያይዘውም፣ ወጣቱ ትውልድ የችግሮቹና የጉዳቶቹ ቀዳሚ ገፈት ቀማሽ ቢሆንም በጉባኤው ተሳታፊዎች ዘንድ ያለው ውክልና ግን አነስተኛ ሊሆን ይችላል የሚል ስጋት እንደገባቸው አመልክተዋል።
በመሆኑም በምክክሩ ሂደት ውስጥ ወጣቶች የራሳቸውን ተጨባጭ እውነታዎች በራሳቸው አንደበት ማስረዳት እንዲችሉና ውይይቱ በተወሰኑ አካላት ብቻ የበላይነት እንዳይያዝ የወጣቱ ትርጉም ያለው ተሳትፎ ሊረጋገጥ እንደሚገባ አሳስበዋል። ባለሙያው ይህንን ሊሉ የቻሉት በምክክሩ ላይ የሚሳተፉ ግለሰቦች ወጣቶችን ያላካተተ እንዳይሆን በመስጋት ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ ሃሳቡን የሰጠው ምክክሩ ወጣቶችን እና ሁሉንም ማህበረሰብ በአካታችነት ያቀፈ ነው ሲል ለባለሙያዎቹ አረጋግጧል።
ይህ የውይይት መድረክ በከተሞች መዋቅርና በሙስና አቀራረብ ላይ ያሉ መሰረታዊ የሃሳብ ማዕቀፍ ከመፍታት ባለፈ የወደፊቷን ሀገር የሚረከበው ወጣት ትውልድ በሰላም ግንባታው ሂደት ውስጥ የበኩሉን ሚና እንዲጫወት ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ ተገልጿል። ወጣቱ የሁሉም ገፈት ቀማሽ ሁኖ በቀዳሚነት የሚገኝ በመሆኑ በሰፊው ሊሳተፍ ይገባል ተብሏል።
ኮሚሽኑ ለሃሳብ አቅራቢ ምሁራን፣ ምክክር ጉባኤው ላይ የሚሳተፉ ሰዎች ስሜታዊ ሊሆኑ የሚችሉበት ሁኔታ ሰፊ ስለሆነ ሌላ ችግር እንዳይፈጠር ሙያዊ የሆነ ሃሳብ በማቅረብ የማረጋጋት ሃላፊነት አለባቸው ብሏል።
ምስል_ ከ ኮሚሽኑ የተወሰደ
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 847 |
| 6 | بدون متن... | 2 444 |
| 7 | ሩሲያ በኪቭ ላይ በፈጸመችው የሰው አልባ የጦር አውሮፕላን እና የሚሳኤል ጥቃት ቢያንስ 13 ሰዎች ተገደሉ
ሐሙስ፣ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
ሩሲያ ሐሙስ ማለዳ በዩክሬን መዲና ኪቭ ላይ በሰነዘረችው ከፍተኛ የድሮን እና የሚሳኤል ጥቃት፤ በትንሹ 13 ሰዎች ሲገደሉ በደርዘን የሚቆጠሩ ደግሞ መቁሰላቸውን የአካባቢው ባለሥልጣናት አስታወቁ።
በዋና ከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች ቃጠሎዎች ይስተዋሉ የነበረ ሲሆን፣ የሚሳኤል ጥቃቶች ወይም የተመቱ ሚሳኤሎች ስብርባሪዎች በበርካታ ስፍራዎች በሚገኙ የመኖሪያ ሕንጻዎች እና በማዕከላዊ የኪቭ አደባባይ ላይ በሚገኝ አንድ ሆቴል ላይ አርፈዋል።
እንደ ዘ ጋርዲያን ዘገባ፣ የአካባቢው የአደጋ ጊዜ አገልግሎት 86 ሰዎች መቁሰላቸውንና ከእነዚህ ውስጥ 70 የሚሆኑት ሆስፒታል ህክምናቸውን እየተከታተሉ መሆናቸውን የገለጸ ሲሆን፣ በዚህም ምክንያት የሟቾች ቁጥር ከ13ም በላይ ሊያሻቅብ እንደሚችል ተነግሯል።
የተሰማሩት ድሮኖች እንዲሁም የክሩዝ እና ባሊስቲክ ሚሳኤሎች ወደ ዋና ከተማዋ ሲተሙና የዩክሬን የአየር መከላከያ ሥርዓት ሊመታቸው ሲሞክር የነበረው ከፍተኛ ፍንዳታ መዲናዋን ለሰዓታት አናውጧታል።
የኪቭ ከንቲባ ቪታሊ ክሊትስኮ በቴሌግራም ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ በአንድ አካባቢ የሚገኝ የመኖሪያ ሕንጻ በቀጥታ በመመታቱ ከአንደኛ እስከ ስድስተኛ ወለል(ፎቅ) ያለው አካል ሙሉ በሙሉ ተደርምሷል። በሌላ ስፍራ ደግሞ አፓርታማው በከፊል ከተደረመሰ በኋላ ሰዎች ከፍርስራሹ ስር ወጥተዋል።
ሩሲያ በዩክሬን ዋና ከተማ ላይ የሚሳኤል እና የድሮን የተቀናጀ ጥቃቶችን በየጊዜው የምትሰነዝር ሲሆን፣ ሌላ ተመሳሳይ ከፍተኛ ጥቃት ሊሰነዘር እንደሚችል ባለፉት ቀናት ግምቶች ነበሩ።
ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ በደብሊን ባደረጉት ጉብኝት ወቅት፣ ረቡዕ ዕለት ለዩክሬናውያን በሰጡት ማስጠንቀቂያ ጥቃቱ በዚያኑ ምሽት ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው ነበር።
“ሕዝባችን ሁሉ ልዩ ጥንቃቄ እንዲያደርግ፣ ራሳቸውንና ልጆቻቸውን እንዲጠብቁ እና የመጠለያ ቦታዎችን እንዲጠቀሙ እጠይቃለሁ፤ ይህ በጣም ወሳኝ ነው” ብለው ነበር።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 3 084 |
| 8 | بدون متن... | 2 784 |
| 9 | የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት (አይ.ሲ.ሲ)፤ ማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒጀር ከተቋሙ አባልነት መውጣታቸው ፍትህን ያዳክማል ሲል ገለጸ
ሐሙስ፣ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት (አይ.ሲ.ሲ) ሥራ አስፈጻሚ ማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒጀር በቅርቡ ከተቋሙ አባልነት ለመውጣት ያደረጉትን እንቅስቃሴ አስመልክቶ ያለውን ስጋት አስታወቀ። ድርጊቱ ዓለም አቀፋዊ ፍትህን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት ያዳክማል ሲልም አክሏል።
በወታደራዊ አገዛዝ የሚተዳደሩት እነዚህ የምዕራብ አፍሪካ አገራት፣ እ.አ.አ በመስከረም 2025 ላይ ግለሰቦችን በጦርነትና በሰብአዊነት ላይ በሚፈጸሙ ወንጀሎች የሚከስሰውን ይህንን ፍርድ ቤት ጥለው ለመውጣት መወሰናቸውን ማስታወቃቸው ይታወሳል። ሦስቱ አገራት ባለፈው ዓመት ባወጡት የጋራ መግለጫ፣ መቀመጫውን በሄግ ያደረገው ፍርድ ቤት “በኢምፔሪያሊስቶች እጅ የሚገኝ የኒዮ ሊበራል ጭቆና መሣሪያ ነው” ሲሉ ወንጅለውታል።
የፍርድ ቤቱን መሥራች አገራት የሚወክለው የአይ.ሲ.ሲ አባል አገራት ጉባኤ፣ “ጉዳዩን በከፍተኛ ስጋት ተመልክተነዋል” ማለቱንና አገራቱ ከአባልነት ለመውጣት በመወሰናቸው ማዘኑን ገልጿል። መግለጫው አክሎም፣ ከአይ.ሲ.ሲ የሚወጡ አገራት “የጋራ የፍትህ ጥረትን የማዳከም እና ወንጀለኞች ያለቅጣት እንዲያመልጡ የማድረግ አደጋ ያመጣሉ” ብሏል።
ይህ ተቋም እንደ መጨረሻ አማራጭ ፍርድ ቤት ሆኖ የሚሠራ ሲሆን፣ አንድ አገር ከባድ የሆኑ ዓለም አቀፍ ወንጀሎችን የፈጸሙ ግለሰቦችን ለፍርድ ማቅረብ ሳትችል ወይም ፈቃደኛ ሳትሆን በሚቀርብበት ወቅት ጣልቃ በመግባት ክስ ይመሰርታል።
በአጠቃላይ 125 አገራት የአይ.ሲ.ሲ አባል ቢሆኑም፣ ቻይና፣ ሕንድ፣ እስራኤል፣ ሩሲያ እና አሜሪካን ጨምሮ በርካታ የዓለም ኃያላን አገራት ተቋሙን አልተቀላቀሉም።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 993 |
| 10 | بدون متن... | 2 630 |
| 11 | የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት (አይ.ሲ.ሲ)፤ ማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒጀር ከተቋሙ አባልነት መውጣታቸው ፍትህን ያዳክማል ሲል ገለጸ
ሐሙስ፣ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት (አይ.ሲ.ሲ) ሥራ አስፈጻሚ ማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒጀር በቅርቡ ከተቋሙ አባልነት ለመውጣት ያደረጉትን እንቅስቃሴ አስመልክቶ ያለውን ስጋት አስታወቀ። ድርጊቱ ዓለም አቀፋዊ ፍትህን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት ያዳክማል ሲልም አክሏል።
በወታደራዊ አገዛዝ የሚተዳደሩት እነዚህ የምዕራብ አፍሪካ አገራት፣ እ.አ.አ በመስከረም 2025 ላይ ግለሰቦችን በጦርነትና በሰብአዊነት ላይ በሚፈጸሙ ወንጀሎች የሚከስሰውን ይህንን ፍርድ ቤት ጥለው ለመውጣት መወሰናቸውን ማስታወቃቸው ይታወሳል። ሦስቱ አገራት ባለፈው ዓመት ባወጡት የጋራ መግለጫ፣ መቀመጫውን በሄግ ያደረገው ፍርድ ቤት “በኢምፔሪያሊስቶች እጅ የሚገኝ የኒዮ ሊበራል ጭቆና መሣሪያ ነው” ሲሉ ወንጅለውታል።
የፍርድ ቤቱን መሥራች አገራት የሚወክለው የአይ.ሲ.ሲ አባል አገራት ጉባኤ፣ “ጉዳዩን በከፍተኛ ስጋት ተመልክተነዋል” ማለቱንና አገራቱ ከአባልነት ለመውጣት በመወሰናቸው ማዘኑን ገልጿል። መግለጫው አክሎም፣ ከአይ.ሲ.ሲ የሚወጡ አገራት “የጋራ የፍትህ ጥረትን የማዳከም እና ወንጀለኞች ያለቅጣት እንዲያመልጡ የማድረግ አደጋ ያመጣሉ” ብሏል።
ይህ ተቋም እንደ መጨረሻ አማራጭ ፍርድ ቤት ሆኖ የሚሠራ ሲሆን፣ አንድ አገር ከባድ የሆኑ ዓለም አቀፍ ወንጀሎችን የፈጸሙ ግለሰቦችን ለፍርድ ማቅረብ ሳትችል ወይም ፈቃደኛ ሳትሆን በሚቀርብበት ወቅት ጣልቃ በመግባት ክስ ይመሰርታል።
በአጠቃላይ 125 አገራት የአይ.ሲ.ሲ አባል ቢሆኑም፣ ቻይና፣ ሕንድ፣ እስራኤል፣ ሩሲያ እና አሜሪካን ጨምሮ በርካታ የዓለም ኃያላን አገራት ተቋሙን አልተቀላቀሉም።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 1 |
| 12 | بدون متن... | 1 |
| 13 | የምርጫውን ውጤት ተከትሎ ሁለት የፖለቲካ ፓርቲዎች ለቦርዱ አቤቱታ ማስገባታቸውን ለአዲስ ማለዳ ገለጹ
ሐሙስ ፣ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ መጠናቀቁንና ውጤቱ ይፋ መደረጉን ተከትሎ፣ የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) እና የመላው የሲዳማ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ፓርቲ (መሲህዴአፓ) በምርጫው አጠቃላይ ሂደትና በምርጫ ቦርድ አሰራር ላይ ያላቸውን ከፍተኛ ቅሬታ ለአዲስ ማለዳ ገለጹ። ፓርቲዎቹ ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ እንዳልነበር በመጥቀስ፣ ቦርዱ ያቀረቡትን አቤቱታ በተገቢው መንገድ አላስተናገደም ሲሉ ወቅሰዋል።
የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የምርጫ አስተባባሪ ሲሳይ ነጋሽ ለአዲስ ማለዳ እንደተናገሩት፣ ምርጫው እንደሚወራው ነጻ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ አልነበረም። “ገዢው ፓርቲ የሚፈልገውን ቦታ ለሚፈልገው ፓርቲ አሳልፎ ስለሰጠ፣ ፓርቲያችን ሊያገኝ የሚገባውን ትክክለኛ ውጤት አላገኘም” ብለዋል።
ይሁን እንጂ በምርጫው ሂደት ያጋጠሙትን ጥሰቶች በመገምገም ለቀጣይ ትግል ትልቅ ግንዛቤና ልምድ የተጨበጠበት በመሆኑ ሂደቱን እንደ አንድ ስኬት እንደሚቆጥሩት ገልጸዋል።
“ፓርቲው ያለውን ቅሬታ በወቅቱ ቢያቀርብም፣ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከገዢው ፓርቲ ጉያ ባለመውጣቱ ምክንያት ነገሮች ተሸፋፍነው እንዲቀሩ ተደርጓል” ሲሉ ወንጅለዋል።
በምርጫው ወቅት ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር በጥምረት ለመሥራት የተደረገው ጥረት ባይሳካም፣ በቀጣይ ፓርቲው ባዘጋጀው ፕሮግራም መሠረት ውይይት በማድረግ አብሮ ለመሥራት ጥሪ ማቅረባቸውን ጠቁመው፣ ነገር ግን አብሮ መሥራት እንደሚወራው ቀላል እንዳልሆነ አክለዋል።
ፓርቲው በአጠቃላይ 35 ወንበሮችን ማሸነፉን ተከትሎ በቀጣይ ከተመሠረተው መንግሥት ጋር ስለሚኖረው የሥራ ግንኙነት ሲያብራሩም፣ “በብሔራዊ ጥቅም ላይ አንደራደርም፤ ገዢው ፓርቲ የፖለቲካ ምህዳሩን እንዲያሰፋ እንታገላለን። ያሉ ችግሮች ተቀርፈው ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች እኩል መንቀሳቀስ የሚችሉበት ሜዳ እንዲፈጠር እንሠራለን እንጂ ከመንግሥት ጋር አናጨበጭብም” ብለዋል።
ሌላኛው ለአዲስ ማለዳ የድህረ ምርጫ አስተያየታቸውን የሰጡት የመላው የሲዳማ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ተስፋማርያም ጉጃ በበኩላቸው፣ ፓርቲያቸው በምርጫው ወቅት የተፈጸሙ ጥሰቶችን አስመልክቶ በ11 የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ቅሬታ ቢያቀርብም ምላሽ ያገኘው በሁለት ጣቢያዎች ላይ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል።
ፓርቲው ለመጀመሪያ ጊዜ በምርጫው መሳተፉን የገለጹት ሊቀመንበሩ፣ ያገኙት አንድ ወንበር የሲዳማ ሕዝብ ለፓርቲው የሰጠውን እውነተኛ ድምፅና ፍላጎት እንደማያንጸባርቅ ገልጸዋል። አክለውም ምርጫው “አሳታፊ” ለማለት የሚጎድሉት በርካታ ነገሮች እንዳሉ ጠቁመው፣ “ተአማኒ ነበር” ብሎ ማሰብ ግን በፍጹም የማይታሰብ ነው ሲሉ ሂደቱን ነቅፈዋል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 3 135 |
| 14 | بدون متن... | 2 775 |
| 15 | የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዲሱ የበጀት ዓመትም አምስት አዳዲስ መዳረሻዎችን እጨምራለሁ፤ 17 ኤር ባስ አውሮፕላኖችንም አዝዣለሁ አለ
ሐሙስ ፣ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአዲሱ የበጀት ዓመት አምስት አዳዲስ ዓለም አቀፍ የበረራ መዳረሻዎችን ወደ በረራ መዳረሻ ለመቀላቀል ማቀዱን ያስታወቀ ሲሆን የጀመረውም ወደ ፈረንሳይ ሊዮን ከተማ መሆኑን ገለጸ።
አየር መንገዱ ይህንን ይፋ ያደረገው በትናንትናው ዕለት ወደ ሊዮን፣ ፈረንሳይ የጀመረውን አዲስ የኮሜርሻል መንገደኞች በረራ በይፋ ባሳወቀበት ወቅት ነው።
አዲሱ የሊዮን በረራ አየር መንገዱ በአውሮፓ የሚያደርሰውን የበረራ መዳረሻ ቁጥር ወደ 21 ከፍ ያደረገዋል የተባለ ሲሆን ይህም በፈረንሳይ ከፓሪስ እና ማርሴይ በመቀጠል ሦስተኛው መዳረሻው መሆኑ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሁኑ ወቅት 26 ዘመናዊ የሆኑ የኤርባስ ኤ350 አውሮፕላኖችን በማንቀሳቀስ ላይ ነኝ ያለ ሲሆን ተጨማሪ 17 ተመሳሳይ አውሮፕላኖችን ለመግዛት ትዕዛዝ መስጠቱንም ገልጿል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚው መስፍን ጣሰው እንደተናገሩት ሊዮን የፈረንሳይ የኢኮኖሚ፣ የባህል እና የፈጠራ ማዕከል በመሆኗ የአፍሪካ የዲፕሎማሲ መዲና ከሆነችው አዲስ አበባ ጋር ማስተሳሰሩ ለአህጉራዊ ትስስር ትልቅ ምዕራፍ ነው፡፡
አክለውም አየር መንገዱ አህጉራትን እና አገራትን የማገናኘት ዓለም አቀፍ ተደራሽነቱን ይበልጥ ለማስፋፋት ቁርጠኛ ነው ያሉ ሲሆን በዚህም መሠረት ከአዲሱ የበጀት ዓመት አንስቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ አምስት አዳዲስ ዓለም አቀፍ መዳረሻዎች በይፋ ሥራ ይጀምራል ሲሉ ተናግረዋል።
አየር መንገዱ ከፈረንሳይ ጋር ያለውን የኢኮኖሚ አጋርነት ያነሱት ሥራ አስፈፃሚው የአየር መንገዱ የቦይንግ 737 አውሮፕላኖች ሞተሮች የሚመረቱት 'ሴኤፍኤም' በተባለው የፈረንሳይ ኩባንያ ሲሆን መሆኑን በማንሳት የአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ ኤርፖርት የመጀመሪያ ደረጃ የአቅም ጥናትና ማስተር ፕላን የተዘጋጀው ኤዲፒ በተባለ የፈረንሳይ ተቋም መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ወደፊት የፈረንሳይ የፋይናንስ ተቋማት እና የኮንስትራክሽን ኩባንያዎች ኤርፖርት የልማት ፕሮጀክቶች ላይ እንዲሳተፉም ጥሪ አቅርበዋል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 3 264 |
| 16 | بدون متن... | 2 958 |
| 17 | የቦኮሀራም ክንፍ በናይጄሪያ እንደከዚህ ቀደሙ ከትምህርት ቤት ተማሪዎችን አፍኖ መውሰዱ ተገለፀ
ረቡዕ፣ ሰኔ 2ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ የታጠቁ አማፂያን በአንድ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ላይ በፈጸሙት ድንገተኛ ጥቃት በትንሹ 37 ተማሪዎች የታገቱ ሲሆን አሁንም ድረስ የት እንዳሉ እንደማይታወቅ የአካባቢው ባለስልጣናት ገለፀ። ናይጀሪያ የተማሪዎች እገታ በተለይም ሴቶች ላይ በተደጋጋሚ የሚከስትባት እየሆነች መጥታለች።
ጥቃቱ የተፈጸመው ባለፈው በትላንትላው ዕለት በቦርኖ ግዛት፣ ላሳ በተባለች ከተማ በሚገኝ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ ተማሪዎች ፈተና እየተፈተኑ በነበረበት ወቅት መሆኑ ተገልጿል ። ጥቃቱን ፈፃሚው እራሱን "የእስላማዊ መንግስት የምዕራብ አፍሪካ ክፍለ ሀገር" ብሎ የሚጠራው የሽብር ቡድን አባላት መሆናቸው የሀገሪቱ ባልስልጣን አስተውቀዋል።
በወቅቱ በነበረው የተኩስ ልውውጥ አንድ ወታደር እና አንድ መምህርን ጨምሮ ቢያንስ ሶስት ሰዎች መገደላቸው የታወቀ ሲሆን ወታደራዊ ኃይሉ መጀመሪያ ላይ 10 ተማሪዎችን ማዳን መቻሉንና የጠፋው አንድ ተማሪ ብቻ እንደሆነ ገልጾ የነበረ ቢሆንም ቆይቶ የወጣው መረጃ ግን የጠፉት ተማሪዎች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑን አሳይቷል ሲል አልጀዚራ አጃን ፈራንስ ፕረስን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
የቦርኖ ግዛት የትምህርት ኮሚሽነር ላዋን አባ ዋኪልቤ በሰጡት መግለጫ በአሁኑ ወቅት 25 ሴት ተማሪዎች፣ 11 ወንድ ተማሪዎች እና አንድ የትምህርት ቤቱ ሰራተኛ አሁንም በአማፂያኑ እጅ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል።
በተጨማሪም የትምህርት ቤቱ ምክትል ርዕሰ መምህርን ጨምሮ ስምንት ሰዎች ግን መለቀቅ መቻላቸውን ገልጸዋል።
የአካባቢው የምክር ቤት አባል በበኩሉ የታጋቾቹን ዝርዝር፣ ጾታ እና የወላጆቻቸውን ስልክ ቁጥር የያዘ ሰነድ በቦታው ለተገኙ ለጋዜጠኞች ይፋ አድርጓል ሲል ዘገባው አክሏል ።
በናይጄሪያ በግጭት በሚታመሱት የሰሜናዊ እና ማዕከላዊ አካባቢዎች ሰዎችን ገንዘብ ለመቀበል ማገት፣ በተለይም ደግሞ ተማሪዎችን በጅምላ ማሰር በታጠቁ እና የወንበዴ ቡድኖች ዘንድ እንደ ዋነኛ ስልት አድርገው እየተገበሩት ነው ተብሏል።
እ.ኤ.አ. በ2014 በቦኮ ሀራም የሽብር ቡድን በቺቦክ ከተማ የተፈጸመው የሴት ተማሪዎች እገታ በሀገሪቱ ታሪክ እጅግ አሳዛኝና ታዋቂው ቢሆንም፣ አሁንም ድረስ በትምህርት ቤቶች ላይ የሚፈጸሙ መሰል ጥቃቶችና እገታዎች በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመሩ ቀጥለዋል።
በተጨማሪም በዚሁ የቦርኖ ግዛት ሙሳ በተባለች መንደር ባለፈው ግንቦት ወር ላይ ብቻ ከ40 በላይ ተማሪዎች ታግተው እስካሁን ድረስ በአማፂያኑ እጅ መሆናቸው የሚታወስ ነው።
ናይጄሪያ እ.አ.አ ከ2009 ጀምሮ በሰሜን ምስራቅ አካባቢው ከተቀሰቀሰ ታጣቂ አማፂ ቡድን ጋር ከፍተኛ ውጊያ እያደረገች የምትገኝ ሲሆን ባለፉት ዓመታት ደግሞ ጥቃቶቹ ቀነስ ብለው የነበረ ቢሆንም ካለፈው ዓመት ወዲህ ግን እንደገና እያገረሹ መምጣታቸውን ተንታኞች ያነሳሉ።
ምስል _ከሮይተርስ የተወሰደ
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 3 537 |
| 18 | بدون متن... | 3 153 |
| 19 | መልካሙ ዓለሙ በደቡብ አፍሪካ ደርባን ከተማ በንግድ ስራ ላይ ተሰማርተው የሚኖሩ እና የኢትዮጵያ ማህበረሰብ አባል ናቸው። በትናንትላው ዕለት በመላው ሀገሪቱ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ በሚካሄድበት ወቅት እሳቸው እና ጓደኞቻቸው ቤታቸውን ዘግተው ውለዋል።
በደርባን አካባቢ ባሉ ገጠራማ አካባቢዎች ሱቆች መዘረፋቸውን አንስተዋል። ከወራት በኋላ ደቡብ አፍሪካ ምርጫ እንደምታካሂድ ያነሱት መልካሙ ያንን ተከትሎ ትልቅ ፍራቻ አለን ብለዋል። ኢትዮጵያውያን ጠንካራ ሰራተኞች ናቸው፤ እንደ ሌሎቹ በድብቅ ሳይሆን በይፋ ስለሚሰሩ ሁሉም ሰው እንደሚያውቃቸው እና በገጠራማው አካባቢ ኢትዮጵያውያን የሌሉበት ቦታ እንደሌለ አንስተዋል። በዚህም ምክንያት ከሌላው ማህበረሰብ ይልቅ ትኩረት ይደረግባቸዋል ብለዋል።
ምርጫውን ተከትሎ ሊመጣ የሚችለውን ፍራቻ መንግስት ከአሁኑ አስቀድሞ ድፕሎማሲያዊ ስራ በመስራት ከደቡብ አፍሪካ መንግስት የተሻለ ግንኙነት ሊፈጥርልን ይገባልም ባይ ናቸው ።
አዲስ ማለዳ የትናንቱን አስፈሪ ውሎና አመሻሽ እንዲሁም ስለዛሬ ረቡዕ መደበኛ እንቅስቃሴዎች አነጋግራቸዋለች፡፡ ሙሉ ዘገባውን በዚህ ያገኙታል።
https://youtu.be/PIo2EsHd9ZM | 3 472 |
| 20 | بدون متن... | 3 247 |
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
