Addis Maleda - አዲስ ማለዳ
📈 تحلیل کانال تلگرام Addis Maleda - አዲስ ማለዳ
کانال Addis Maleda - አዲስ ማለዳ (@addismaleda) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 32 339 مشترک است و جایگاه 7 791 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 1 047 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 32 339 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 23 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 349 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 20 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 13.16% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.32% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 4 254 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 3 012 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 11 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“ዜና ከምንጩ”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 24 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 24 ژوئیه | +31 | |||
| 23 ژوئیه | +22 | |||
| 22 ژوئیه | +33 | |||
| 21 ژوئیه | +7 | |||
| 20 ژوئیه | +5 | |||
| 19 ژوئیه | +13 | |||
| 18 ژوئیه | +10 | |||
| 17 ژوئیه | +6 | |||
| 16 ژوئیه | +10 | |||
| 15 ژوئیه | +31 | |||
| 14 ژوئیه | +24 | |||
| 13 ژوئیه | +31 | |||
| 12 ژوئیه | +9 | |||
| 11 ژوئیه | +23 | |||
| 10 ژوئیه | +27 | |||
| 09 ژوئیه | +6 | |||
| 08 ژوئیه | +18 | |||
| 07 ژوئیه | +16 | |||
| 06 ژوئیه | +18 | |||
| 05 ژوئیه | +7 | |||
| 04 ژوئیه | +11 | |||
| 03 ژوئیه | +21 | |||
| 02 ژوئیه | +29 | |||
| 01 ژوئیه | +10 |
| 2 | بدون متن... | 1 765 |
| 3 | በትግራይ የሚገኙ የተፈናቃይ ጣቢያዎች ውስጥ 95 በመቶ የሚሆኑት ለምግብ እጥረት መጋለጣቸውን ሪፖርት አመላከተ
ዓርብ፣ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በትግራይ ክልል የሚገኙ 95 በመቶ የሚሆኑት የተፈናቃይ ጣቢያዎች የምግብ እጥረት ያጋጥማቸዋል ሲል አዲስ የወጣ ሰብዓዊ ድጋፍ ፍላጎት ግምገማ አመላከተ፡፡
ግምገማውን ያወጣው በመጠለያ እና በሰብዓዊ ድጋፍ ላይ የሚሰራው ሼልተር ክላስተር የተሰኘው ተቋም ሲሆን ከተለያዩ አካላት ጋር በትብብር አካሂጄዋለሁ ያለው የጣቢያዎች ጥናት በትግራይ በሚገኙ በ5 ዞኖችና በ21 ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ 78 የተፈናቃይ ጣቢያዎችን መገምገሙን አስታውቋል።
ጥናት ከተደረገባቸው ጣቢያዎች መካከል 84 በመቶ ማለትም 67 ጣቢያዎች የጋራ ማዕከላት ሲሆኑ በዋናነት ትምህርት ቤቶች እና ሌሎች የህዝብ ህንጻዎችን ሲያካትቱ ደግሞ 14 በመቶ ወይም 11 ጣቢያዎች የታቀዱ የተፈናቃይ ጣቢያዎች መሆናቸው ሲጠቆም የተቀሩት ደግሞ ማህበረሰቦች ውስጥ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
ግምገማው “እጅግ በጣም ደካማ የሆነ ሰብአዊ እርዳታ ምላሽ” መኖሩን ያመላከተ ሲሆን የምግብ ድጋፍ እጥረት ከፍተኛ ክፍተት ሆኖ ተገኝቷል።
ከተዳሰሱት ጣቢያዎች 95 በመቶ የሚሆኑት የምግብ እርዳታ ቢኖርም ፍላጎቱን ለማሟላት በቂ አለመሆኑን በተካሄደው ጥናት ላይ ተመላክቷል፡፡
ይህ እጥረት በአብዛኞቹ ጣቢያዎች በቂ ያልሆነ የአመጋገብ፣ የጤና እንዲሁም ከንጽህና ጋር የተያየዙ አገልግሎቶች ናቸው። ይህም ማለት 74 በመቶ የሚሆኑት ጣቢያዎች የምግብ አገልግሎት፣ በ73 በመቶ የጤና አገልግሎት፣ በ62 በመቶው የንጽህና ፣ በ59 በመቶ ትምህርት እንዲሁም በ55 በመቶው መጠለያ አገልግሎት በቂ አለመሆኑ ጥናቱ ጠቁሟል።
በግምገማው 10 የሚሆኑ ጣቢያዎችን ለከፋ የሰብአዊ ቀውስ መጋለጣቸውን በመጥቀስ 22ቱን “ከፍተኛ አደጋ” ውስጥ የሚገኙ ሲል መድቧል።
በአጠቃላይ ከተገመገሙት ወረዳዎች ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ከንጽህና፣ መጠለያ፣ ጤና እና አመጋገብ ዘርፎች በቂ ሁኔታ ያሟላ አንድም ጣቢያ እንዳልነበራቸዉ አይቻለሁ ያለ ሲሆን ይህም ዘላቂ የብዝሃ-ዘርፍ ሰብአዊ እርዳታ አስፈላጊነት እንዲጎላ ያደርጋል ተብሏል፡፡
ጥናቱ አከሎም የጣቢያ አስተዳደር አቅምን ማስቀጠል፣ የብዝሃ-ዘርፍ ድጋፍን ማጠናከር፣ የመጠለያ ሁኔታዎችንና የጣቢያ መሠረተ ልማቶችን ማሻሻል ያስፈልጋል ብሏል።
በተጨማሪም ጥበቃን ማካተትን እና ማሳደግ እንዲሁም ለወቅታዊ የጎርፍ እና ለሌሎች በጣቢያ ደረጃ ለሚከሰቱ አደጋዎች ዝግጁነትን ማጠናከር ግምገማው ቅድሚያ ሊሰጣቸው ይገባል ካላቸው ተግባራት ዉስጥ ይገኙበታል። ተቋሙ በክልሉ የሰብዓዊ ድጋፍ ከሚያቀርቡት ዉስጥ አንዱ መሆኑ ይታወቃል።
ምስል _ከ ሪፕርቱ ላይ የተወሰደ
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 |
| 4 | بدون متن... | 2 |
| 5 | “በፖሊስ ታስረን ነበር” ራሔል ባፌ(ዶ/ር)
የኢትዮጵያ ሶሻል ዲሞክራቲክ ፓርቲ(ኢሶዴፓ) ም/ሊቀመንበር ራሔል ባፌ(ዶ/ር) የዚህ ሳምንት የአዲስ ማለዳ፣ ወቅታዊ ዝግጅት እንግዳ ናቸው።
ዶክተር ራሔል የሚመሩት ፓርቲ “በምርጫ ቦርድ ተፈጽሞብናል” ባሉት ‛ጣልቃ ገብነት’ ምክንያት 309 እጩዎችን ቢያቀርብም ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም በተካሄደው ምርጫ አልተወዳደረም።
በምርጫው አለመወዳደሩ ብቻ ሳይሆን፣ ዋና ዋና አመራሮችም “በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው” እንደነበረ አስረድተዋል።
ምክትል ሊቀመንበሯ ከአዲስ ማለዳ ጋር በነበራቸው ዘለግ ያለ ቃለምልልስ፣ “በምርጫ ቦርድ፣ በፍትሕ ሥርዓቱና በሌሎች የመንግስት ተቋማት” ደርሰውብናል ያሏቸውን “በደሎች” በሰፊው ከማብራራታቸው ባሻገር በሌሎች ወቅታዊ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለቀረበላቸው ጥያቄ “ምላሽ” ያሉትን ሰጥተዋል።
ክፍል አንዱን ቀጣይ በሚገኘው ማስፈንጠሪያ ያገኙታል፦
https://youtu.be/IzPTBEcqd8k?si=t7ZWjGYjA_YyGDpq | 2 373 |
| 6 | በሀዲያ ዞን በአንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ይዞታ እና ተከታዮች ላይ በሌላ ሀይማኖት ተከታዮች ጥቃትንና ውድመት መድረሱን ተከትሎ የአመካ ወረዳ ቤተክህነት የሕግ የበላይነት ይከበር ሲል ጥሪ አቀረበ
ዓርብ፣ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የአመካ ወረዳ ቤተ-ክህነት ጽሕፈት ቤት በ ወረዳው “የታኛኛው በታራ” በተባለ ልዩ ቦታ በሚገኝ የቤተ ክርስቲያን ይዞታ ላይ ጥቃትና የንብረት ውድመት “በፕሮቴስታንት አማኞች” ደርሷል ሲል አስታወቀ።
ጉዳዩን አስመልክቶ ይፋዊ አቤቱታው በደብዳቤ ለተለያዩ ተቋማት ልኳል። የወረዳው ቤተክህነት በደብዳቤው ላይ እንደገለጸው በቦታው የሚኖሩ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከተዮች ለዘመናት ሲጠቀሙበት የነበረውንና በአሁኑ ወቅት ቁጥራቸው ከ300 በላይ ለሚሆኑ ምዕመናን አገልግሎት የሚሰጠውን የጸሎት፣ የመሰብሰቢያና የመቃብር ስፍራ በሕጋዊ መንገድ አጥር በማጠርና ለበጎ አድራጎት ሥራዎች በማዋል ሰላማዊ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ቆይተዋል።
ቦታው ከሌሎች የእምነት ተቋማት ጋር የድምጽ መረባበሽ እንዳይኖር ርቀቱን ጠብቀው በስጦታ ባገኙት ቦታ ላይ የተገነባ መሆኑን ገልፆ ይሁን እንጂ የሌሎች እምነት ተከታዮች ለወረዳው ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ተቃውሟቸውን አቅርበዋል ብሏል።
አክሎም በአካባቢው የሚኖሩ የልዩ ልዩ ሃይማኖት ተከተዮች እርስ በእርስ በመከባበርና በሰላም አብረው የሚኖሩ ቢሆንም፣ የአመካ ወረዳ የሰላምና ፀጥታ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የፕሮቴስታንት እምነት ተከተይ በመሆናቸው እና “ከፍተኛ የሃይማኖት ጥላቻን” በሚገልጽ መልኩ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አጥር እንድታፈርስና በአካባቢው ምንም ዓይነት ልማት እንዳይካሄድበት በማድረግ ከፍርድ ቤት አሰራር ውጪ እና ያለ አግባብ ሥልጣናቸውን በመጠቀም ፍትሕ እንዳናገኝ አድርገዋል ሲል አስታውቋል።
ይህንንም ተከትሎ ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ሰዓት ላይ የተደራጁ ‛‛የፕሮቴስታንት እምነት ተከተዮች ይዞታውንና ንብረቱን ይጠብቁ በነበሩ 6 የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከተዮች ላይ ድገተኛ ጥቃት በመሰንዘር "ከፍተኛ አካላዊ ድብደባ’’ ፈጽመውባቸዋል ሲል ገልጿል።
በተጨማሪም “ድምጽ በሌለው መሣሪያ” አማካይነት ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል ያለ ሲሆን፣ በቦታው ላይ የነበረውን ሕንፃ በማፍረስና ንብረቱንም “ሙሉ በሙሉ” በማፍረስ ከፍተኛ ውድመት አድርሰዋል ብሏል።
በመሆኑም የወረዳው አስተዳደር ጽሕፈት ቤት በድርጊቱ ላይ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ወንጀለኞችን በፍጥነት ለሕግ እንዲያቀርብና ተገቢው አስተማሪ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ይገባል ሲል ጠይቋል።
አክሎም ጉዳት የደረሰባቸው ምዕመናን አስፈላጊውን ሕክምና እንዲያገኙና ለወደመው ንብረት ተመጣጣኝ ካሣ በሕግ አግባብ እንዲከፈላቸው እንዲሁም በፈረሰው ቤት ምትክ ሌላ ቤት ተገንብቶ ለአገልግሎት እንዲበቃ ቤተ-ክህነቱ ጠይቋል።
በመጨረሻም የሃይማኖት እኩልነትና ነፃነት እንዲረጋገጥ፣ የሕግ የበላይነት እንዲከበርና ለቤተ ክርስቲያኗና ለምዕመናን ተገቢው የሕግ ከለላ እንዲሰጥ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን ይህ አቤቱታውንም ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ፣ ለክልሉ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ፣ ለሀዲያ ዞን ሰላም እና ጸጥታ መመሪያ፣ ለዞኑ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እንዲሁም ለሀዲያ እና ስልጤ ሀገረስብከት ግልባጭ እንደላከ በደብዳቤው ጠቅሷል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 3 907 |
| 7 | بدون متن... | 2 345 |
| 8 | በትግራይ የሚገኙ የተፈናቃይ ጣቢያዎች ውስጥ 95 በመቶ የሚሆኑት ለምግብ እጥረት መጋለጣቸውን ሪፖርት አመላከተ
ዓርብ፣ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በትግራይ ክልል የሚገኙ 95 በመቶ የሚሆኑት የተፈናቃይ ጣቢያዎች የምግብ እጥረት ያጋጥማቸዋል ሲል አዲስ የወጣ ሰብዓዊ ድጋፍ ፍላጎት ግምገማ አመላከተ፡፡
ግምገማውን ያወጣው በመጠለያ እና በሰብዓዊ ድጋፍ ላይ የሚሰራው ሼልተር ክላስተር የተሰኘው ተቋም ሲሆን ከተለያዩ አካላት ጋር በትብብር አካሂጄዋለሁ ያለው የጣቢያዎች ጥናት በትግራይ በሚገኙ በ5 ዞኖችና በ21 ወረዳዎች ውስጥ የሚገኙ 78 የተፈናቃይ ጣቢያዎችን መገምገሙን አስታውቋል።
ጥናት ከተደረገባቸው ጣቢያዎች መካከል 84 በመቶ ማለትም 67 ጣቢያዎች የጋራ ማዕከላት ሲሆኑ በዋናነት ትምህርት ቤቶች እና ሌሎች የህዝብ ህንጻዎችን ሲያካትቱ ደግሞ 14 በመቶ ወይም 11 ጣቢያዎች የታቀዱ የተፈናቃይ ጣቢያዎች መሆናቸው ሲጠቆም የተቀሩት ደግሞ ማህበረሰቦች ውስጥ እንደሚገኙ ተገልጿል፡፡
ግምገማው “እጅግ በጣም ደካማ የሆነ ሰብአዊ እርዳታ ምላሽ” መኖሩን ያመላከተ ሲሆን የምግብ ድጋፍ እጥረት ከፍተኛ ክፍተት ሆኖ ተገኝቷል።
ከተዳሰሱት ጣቢያዎች 95 በመቶ የሚሆኑት የምግብ እርዳታ ቢኖርም ፍላጎቱን ለማሟላት በቂ አለመሆኑን በተካሄደው ጥናት ላይ ተመላክቷል፡፡
ይህ እጥረት በአብዛኞቹ ጣቢያዎች በቂ ያልሆነ የአመጋገብ፣ የጤና እንዲሁም ከንጽህና ጋር የተያየዙ አገልግሎቶች ናቸው። ይህም ማለት 74 በመቶ የሚሆኑት ጣቢያዎች የምግብ አገልግሎት፣ በ73 በመቶ የጤና አገልግሎት፣ በ62 በመቶው የንጽህና ፣ በ59 በመቶ ትምህርት እንዲሁም በ55 በመቶው መጠለያ አገልግሎት በቂ አለመሆኑ ጥናቱ ጠቁሟል።
በግምገማው 10 የሚሆኑ ጣቢያዎችን ለከፋ የሰብአዊ ቀውስ መጋለጣቸውን በመጥቀስ 22ቱን “ከፍተኛ አደጋ” ውስጥ የሚገኙ ሲል መድቧል።
በአጠቃላይ ከተገመገሙት ወረዳዎች ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ከንጽህና፣ መጠለያ፣ ጤና እና አመጋገብ ዘርፎች በቂ ሁኔታ ያሟላ አንድም ጣቢያ እንዳልነበራቸዉ አይቻለሁ ያለ ሲሆን ይህም ዘላቂ የብዝሃ-ዘርፍ ሰብአዊ እርዳታ አስፈላጊነት እንዲጎላ ያደርጋል ተብሏል፡፡
ጥናቱ አከሎም የጣቢያ አስተዳደር አቅምን ማስቀጠል፣ የብዝሃ-ዘርፍ ድጋፍን ማጠናከር፣ የመጠለያ ሁኔታዎችንና የጣቢያ መሠረተ ልማቶችን ማሻሻል ያስፈልጋል ብሏል።
በተጨማሪም ጥበቃን ማካተትን እና ማሳደግ እንዲሁም ለወቅታዊ የጎርፍ እና ለሌሎች በጣቢያ ደረጃ ለሚከሰቱ አደጋዎች ዝግጁነትን ማጠናከር ግምገማው ቅድሚያ ሊሰጣቸው ይገባል ካላቸው ተግባራት ዉስጥ ይገኙበታል። ተቋሙ በክልሉ የሰብዓዊ ድጋፍ ከሚያቀርቡት ዉስጥ አንዱ መሆኑ ይታወቃል።
ምስል _ከ ሪፕርቱ ላይ የተወሰደ
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 685 |
| 9 | بدون متن... | 2 216 |
| 10 | ተከሳሾች ከማረሚያ ቤት ባለመቅረባቸው በእነ ዮሐንስ ቧያሌው መዝገብ ላይ ብይን ለመስጠት ለጥቅምት ተቀጠረ
ዓርብ፣ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ዮሐንስ ቧያሌው የክስ መዝገብ ላይ ተከሳሾች እንዲከላከሉ ወይም በነፃ እንዲሰናበቱ ብይን ለመስጠት ለዛሬ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጥሮ የነበረ ቢሆንም፣ የተወሰኑ ተከሳሾች በችሎት ባለመገኘታቸው ብይኑን ለማንበብ ለጥቅምት 6 ቀን 2019 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ መስጠቱን የተከሳሾች ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ ለአዲስ ማለዳ ገለጹ።
ፍርድ ቤቱ ባስቻለው ችሎት የብይኑ ውሳኔ ተዘጋጅቶ የደረሰ ቢሆንም፣ ከማረሚያ ቤት መቅረብ የነበረባቸው የተወሰኑ ተከሳሾች ባለመገኘታቸው ምክንያት ብይኑ ሳይነበብ ቀርቷል።
ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ እንዳሉት፣ ተከሳሾቹ ወደ ችሎት ያልቀረቡበት ምክንያት ያልተገለጸ ሲሆን፤ በዕለቱ በችሎት ካልተገኙት መካከል ዶ/ር ዘሪሁን፣ ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ፣ መርጌታ በላይ አዳሙ እና ተከሳሽ ታደለ ይገኙበታል።
በሌላ በኩል፣ የዶ/ር ካሳ ተሻገር እና የጋዜጠኛ ቴዎድሮስን የስልክ ቁጥር “ሌላ ሰው እየተጠቀመበት ነው” በሚለው ክስ ላይ ኢትዮ ቴሌኮም ማጣራት አድርጎ በዕለቱ ምላሹን ለችሎቱ አቅርቧል።
ኢትዮ ቴሌኮም ለፍርድ ቤቱ በላከው ምላሽ፤ የሁለቱ ተከሳሾች የስልክ ቁጥሮች አገልግሎት ጊዜያቸው በማለፉ ምክንያት በተቋሙ ሕግና ደንብ መሠረት ለሦስተኛ ወገን መተላለፋቸውን ገልጾ፣ ቁጥሮቹን የተቀበሉትን ሰዎች ሙሉ ስም ከአያት ጋር አያይዞ ማሳወቁን ጠበቃ ሰለሞን አብራርተዋል።
በዚህም መሠረት ፍርድ ቤቱ በእነ ዮሐንስ ቧያሌው መዝገብ ላይ የቀረበውን ብይን ለማንበብ ለጥቅምት 6 ቀን 2019 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 466 |
| 11 | بدون متن... | 2 394 |
| 12 | እናት ፓርቲ በዓባይ ቅድስት አርሴማ ገዳም ላይ የተፈጸመውን የድሮን ጥቃት “የሽብር፣ የ አጥፍቶ ጠፊነት ተግባር” ነው በማለት አወገዘ
ዓርብ፣ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ቦረና ወረዳ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዓባይ ቅድስት አርሴማ ገዳም ላይ በተፈጸመ የድሮን ጥቃት የሰዎች ሕይወት ያለፈበት እና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን በመግለጽ እናት ፓርቲ ጥቃቱን አወገዘ።
ፓርቲው አክሎም ህዝብ ለማገልገል የተቋቋሙ ተቋማት ለህዝቡ “ጅምላ ጨራሽ” እየሆኑ ነው ብሏል።
ፓርቲው በዛሬው ዕለት ባወጣው ወቅታዊ መግለጫ እንዳመለከተው፣ ጥቃቱ የተፈጸመው ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ረፋድ አራት ሰዓት ላይ እንደሆነም ገልጿል።
በጥቃቱ ምክንያት ሁለት መነኮሳት እናቶች ወዲያውኑ ሕይወታቸው አልፏል ያለ ሲሆን፣ 14 እናቶች ደግሞ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው በመካነ ሰላም እና ደሴ ሆስፒታል ህክምና እየተከታተሉ ይገኛሉ ብሏል።
አክሎም በገዳሙ የተከማቸ የዓመት ቀለብ እህልና ጥራጥሬ ሙሉ በሙሉ፣ ማዕድ ቤት፣ የውሃ ማጠራቀሚያ የፕላስቲክ ታንከሮች፣ የውሃ ማስተላለፊያ ቱቦዎችና ሌሎች ቁሳቁሶች ሙሉ በሙሉ መውደማቸው አስታውቋል።
ገዳማውያኑ ጥቃቱ ከመፈጸሙ በፊት የድሮን ድምጽ ሰምተውና ተመልክተው እንደነበረ የገለፀው ፓርቲው “እኛ ገዳማውያን ነን፤ ቴክኖሎጂ ነው ብለን የምንፈራውና የምንጠራጠረው ነገር የለም” በማለት ሥራቸውን ሲቀጥሉ ድንገት ቦንብ እንደወረደባቸውና በርካቶች መጎዳታቸውን እንደነገሩት አመልክቷል።
ፓርቲው ተመሳሳይ ድርጊቶች በታጣቂዎች ሽፋን በእምነቱ ተከታዮች፣ አገልጋዮች፣ ገዳማት ላይ እየተፈፀመ ያለ ጥቃት “ተራ ጥቃት ስህተት ሳይሆን ስርዓታዊ እና ከጥላቻ የመነጨ” ነው ያለ ሲሆን ይህም “አጥፍቶ የመጥፋት” ተግባር መሆኑን እንደሚያምን በመግለፅ በጽኑ አወግዘዋለሁ ብሏል።
እናት ፓርቲ ድርጊቱን “በእምነት ተቋማትና በገዳማት ላይ የሚፈጸም አጥፊና ስርዓት አልበኝነት የተሞላበት ተግባር” ሲል የኮነነው ሲሆን መንግስት ኃላፊነቱን እንድወስድ ጥሪ አቅርቧል።
መንግሥት ሙሉ ኃላፊነቱን እንዲወስድ እና ድርጊቱ ሲፈጸም የሚያሳይ ምስል እና ቪድዮ ለሕዝብ ይፋ እንዲያደርግ አጥብቀን እንጠብቃለን ብሏል።
አክሎም ሙሉው ኢትዮጵያውያን “ይህንን አጥፍቶ ጠፊ የሽብር ድርጊት” በአንድነት ማውገዝ እንደላበት ጥሪ አቅርቧል።
ፓርቲው ሀገርን ከጥቃት ለመጠበቅ የተቋቋሙ ተቋማት “ሕዝብን ጅምላ ጨራሽ ወደ መሆን መሸጋገራቸውን” ህዝቡ እና ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ እንዲያውቀውና አጥፊው አካል ተጠያቂ መደረግ አለበት ብሏል።
በመጨረሻም ፓርቲው የቆሰሉ ገዳማውያን፣ በበረሃና በቅዝቃዜ ውስጥ የቀሩትና ቀለባቸው የወደመባቸው አባቶችና እናቶች “በረሃብ ና ውሃ ጥም ከማለቃቸው በፊት” አስቸኳይ ድጋፍ እንዲደረግላቸው።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 766 |
| 13 | بدون متن... | 2 431 |
| 14 | እስራኤል በ ጋዛ “ለቃችሁ ዉጡ” የሚል ትዕዛዝ ካስተላለፈች በኋላ ባደረሰችዉ የቦምብ ጥቃት ሁለት ፍልስጤማውያን ተገደሉ
ዓርብ፣ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
እስራኤል በበርካታ አካባቢዎች የጋዛ ተፈናቃዮችን ለቀው እንድወጡ ትዕዛዝ ካስተላለፈች በኋላ ባደረሰችው የቦምብ ጥቃት በመሰንዘሯ ምክንያት ሁለት ሰዎች መገደላቸውን የህክምና ምንጮች መግለፃቸዉን አልጀሪያ ዘግቧል፡፡
በትናንትናው ዕለት ተፈፅሟል የተባለው ጥቃት ባለፈው ዓመት በአሜሪካ አደራዳሪነት ወደ ሥራ የገባው “የተኩስ አቁም” ስምምነት ቢኖርም በእስራኤል ጦር እየተፈጸመ ያለው የከባድ እርምጃዎች አካል ነው ተብሏል።
የጥቃቱን ሁኔታ ከጋዛ ከተማ ሪፖርት ያደረጉት የአልጀዚራ ዘጋቢ የሆኑት ኢብራሂም አል-ኻሊሊ እንዳሉት ከሆነ የእስራኤል ጦር በአራት የተለያዩ አካባቢዎች ለሚገኙ ሰዎች ለቀው እንወጡ ማስጠንቀቂያ ከሰጠ በኋላ ጋዛን በቦምብ ደብድቧል፡፡
“በተለይ አሳሳቢው ነገር እነዚህ ማስጠንቀቂያዎች ሰዎች እንድሸሹባቸው በተነገራቸው አካባቢዎች ላይ ጥቃት መሰንዘሩ ነው” ሲል በቦታው ያለዉን ሁኔታ አስረድተዋል። አክሎም በጋዛ ከተማ ላይ የተሰነዘረው ጥቃት ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ ማስነሳቱንና የሲቪል መከላከያ ባለሙያዎች እሳቱን ለማጥፋት ጥረት እያደረጉ መሆኑንም ጨምሮ ገልጿል፡፡
በቡሬጅ እና በጃባሊያ የስደተኞች መጠለያ ካምፖች እንዲሁም በጋዛ ከተማ ዘይቱን እና ታል አል-ሃዋ በ ተሰኙ ሰፈሮች ላይ በእስራኤል አየር ጥቃቶች ምክክያት ቤቶች ፈራርሰዋል ተብሏል።
በተመሳሳይ በከተማዋ ደቡብ ምስራቅ ላይ በዘይቱን ሰፈር ህንፃ ላይ በ ደረሰ የ ቦንብ ጥቃት በርካታ ሰዎችን እንዳቆሰለ ሲሉ የአል አህሊ ሆስፒታል ምንጭ ለአልጀዚራ ተናግረዋል።
“እዚህ ላሉ ቤተሰቦች የለቃችሁ ዉጡ ትዕዛዝ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ከመዘዋወር በላይ ትርጉም አለው፡፡” ያሉ ሲሆን “ብዙ ጊዜ በሌሊት እና በድንጋጤ ውስጥ ሆነዉ” የሚኖሩነትን መጠለያ ጥለዉ መሄድ ከባድ እንደሆነ በማሳት ብዙ ሰዎች የሚሄዱበት ሌላ ቦታ ስለሌላቸው በጎዳና ላይ ለመውጣት እንደሚገደዱ ከ ቦታው የነበሩት ዘጋቢ ገልጸዋል፡፡
እስራኤል በጋዛ ላይ እያካሄደችው ባለው ጥቃት ቢያንስ 73,311 ፍልስጤማውያንን መግደሉን የሚገልጹት የአካባቢው የጤና ባለስልጣናት ከነዚህም ውስጥ እ.አ.አ ከጥቅምት 2025 የ “ተኩስ አቁም” ስምምነት ወዲህ ከ1,185 የሚበልጡ ሰዎች ይገኙበታል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 741 |
| 15 | بدون متن... | 2 502 |
| 16 | በካርቱም 74 የውጭ ዜጎች ከህገወጥ ሰው ዝውውር ቡድን ነፃ ወጡ
ዓርብ፣ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የሱዳን የጸጥታ ኃይል በዋና ከተማዋ ካርቱም 74 የውጭ ዜጎችን በሰው ዝውውር እና በሕገ-ወጥ እገታ የተሰማራ ወንጀለኛ ቡድን እጅ ከነበሩበት ሁኔታ ነፃ ማውጣቱን አስታወቀ።
በተቀናጀ የጸጥታ ዘመቻ የተካሄደው እርምጃ በካርቱም ከተማ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ህገወጥ የሰው ዝውውር መረቦችን ለመበተን የተደረገ መሆኑ ተገልጿል።
የሀገሪቱ ባለሥልጣናት እንደገለጹት፣ በዘመቻው ወቅት በርካታ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ ከፍተኛ መጠን ያለው የጦር መሳሪያም ተይዟል፤ ከተያዙት መካከል ሶስት ዲኤስኤችኬ ከባድ መትረየሶች፣ ሁለት ፒኬ መትረየሶች፣ 16 ካላሽኒኮቭ እና ስናይፐር ጠብ-መንጃዎች፣ አምስት ሽጉጦች፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ጥይቶች እንዲሁም ስድስት የአር.ፒ.ጂ.ሮኬቶች ሊገኝ እንደቻለ መግለፃቸውን ቢቢሲ ዘግቧል ።
የጸጥታ ኃይሎቹ በተጨማሪ አራት የስታርሊንክ የሳተላይት ኢንተርኔት መሳሪያዎችን እና ሁለት ተሽከርካሪዎችን መያዛቸውን አስታውቀዋል ።
እነዚህ መሳሪያዎች የወንጀለኛ ቡድኖች በግንኙነት እና በእንቅስቃሴ ለመጠቀም ይገለገሉ እንደነበር የተጠቆመ ሲሆን ባለሥልጣናቱ እንደሚሉት፣ በሱዳን በቀጠለው የጸጥታ ችግር እና ግጭት ሳቢያ የተፈጠረውን የጸጥታ ክፍተት ተጠቅመው የሰው ዝውውር፣ ሕገ-ወጥ ስደት እና ሌሎች የተደራጁ ወንጀሎች በአንዳንድ አካባቢዎች እየተስፋፉ መምጣታቸው ትልቅ ስጋት ሆኗል ብለዋል።
በዚህም ምክንያት የጸጥታ ኃይሎች ተመሳሳይ ወንጀለኛ አውታሮችን ለማጥፋት የተጠናከረ ዘመቻ እያካሄዱ መሆኑን ገልጸዋል።
የሱዳን የጉምሩክ ኃይል ዋና ዳይሬክተር ሌተናል ጄኔራል ሳላህ አህመድ ኢብራሂም በዘመቻው የተሳተፉትን ኃይሎች አድንቀው፣ ከወታደራዊ ፖሊስ ጋር በተደረገው ቅንጅት 74ቱን ታጋቾች በሰላም ማስለቀቅ እና የሰው ዝውውር ቡድኑን ተጠርጣሪዎች ማሰር መቻሉ የጸጥታ ተቋማት በጋራ ሲሰሩ ውጤታማ እንደሚሆኑ ያሳያል ብለዋል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 947 |
| 17 | ነፃ የ ወጡት የዉጭ ዜጎች | 1 |
| 18 | بدون متن... | 2 719 |
| 19 | ፊሊፒንስ፣ ቤጂንግ በደቡብ ቻይና ባሕር ላይ መርከቦቸ ላይ በአደገኛ አቀራረብ ተኩስ ከፍታብኛለች ስትል ከሰሰች
ዓርብ፣ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የፊሊፒንስ የባሕር ላይ ጥበቃ ኃይል “ኮስት ጋርድ” የቻይና የባሕር ጥበቃ መርከቦች በግዛት ውዝግብ ውስጥ በሚገኘው የደቡብ ቻይና ባህር ስካርቦሮ ሾል በተባለ አካባቢ በሚንቀሳቀሱ የፊሊፒንስ መንግሥት መርከቦች ላይ ለሁለት ተከታታይ ቀን የውሃ ጠብ-መንጃ መተኮሳቸውንና አደገኛ የተባለ እንቅስቃሴ ማድረጋቸውን አስታወቀ።
ንብረትነታቸው የፊሊፒንስ የባሕር ጥበቃ እና የዓሣ ሀብት ቢሮ የሆኑ መርከቦች በአካባቢው ለሚገኙ ፊሊፒንሳውያን ዓሣ አጥማጆች የነዳጅ ድጎማና ሰብዓዊ እርዳታ ለማቅረብ በተሰማሩበት ወቅት የቻይና መርከቦች መንገዳቸውን ለመዝጋት ሞክረዋል ያለ ሲሆን ቻይና ደግሞ ክሱን ሀሰተኛ ስትል ወውድቅ አድርጋዋለች። የውሃ ጠብ-መንጃ በከፍተኛ ግፊት የሚረጭ ሲሆን ትንንሽ መርከቦች አቅጣጫቸውን እንዲቀይሩ እና አደጋ ሊደርስባቸው የሚያስችል ኃይል አለው።
የሮይተርስ ዘገባ፤ የቻይና መርከቦች እስከ 7 ሜትር ያህል ቀርበው አደገኛ እንቅስቃሴ ማድረጋቸው የባሕር ላይ ሕግጋትን የሚጥስና ያልተገባ ድርጊት ነው ሲል የፊሊፒንስ የባሕር ላይ ጥበቃ ኃይሉ መናገሩን አመልክቷል።
የቻይና የባሕር ጥበቃ ኃይል በበኩሉ በሕገ ወጥ መንገድ ወደ ቻይና ግዛት ገብተዋል ያላቸውን የፊሊፒንስ መርከቦች ለማስወጣት ሕጋዊ “የቁጥጥር እርምጃ” ወስጃለሁ ሲል አስታውቋል። ሁለቱ ሀገሮች እንዲህ አይነት ግጭቶችን ማካሄዳቸው የተለመደ ሲሆን ድርጊቱም ለበርካታ ቀናት ሲደረግ እንደነበረ መረጃዎች ያሳያሉ። ሁለቱ ሀገሮች በደቡብ ቻይና ባህር አካባቢ ይገባኛል ጥያቄ የሚያነሱበት ሲሆን ለግጭቱ መንስኤም የዚሁ ቦታ ጉዳይ ነው።
ይህ ሁነት የተከሰተው በማኒላ የደቡብ ምሥራቅ እስያ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስብሰባ በሚካሄድበት እና የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ የቻይናን እንቅስቃሴ በኮነኑበት ወቅት መሆኑ ሌላ መልክ እንዲይዝ አድርጎታል፡፡
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 3 203 |
| 20 | بدون متن... | 3 078 |
