Addis Maleda - አዲስ ማለዳ
📈 تحلیل کانال تلگرام Addis Maleda - አዲስ ማለዳ
کانال Addis Maleda - አዲስ ማለዳ (@addismaleda) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 33 170 مشترک است و جایگاه 7 574 را در دسته اخبار و رسانهها و رتبه 1 059 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 33 170 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 19 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 290 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -6 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 14.06% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 9.30% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 4 664 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 3 085 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 10 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“ዜና ከምንጩ”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 20 سپتامبر, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته اخبار و رسانهها تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 20 سپتامبر | 0 | |||
| 19 سپتامبر | +1 | |||
| 18 سپتامبر | +20 | |||
| 17 سپتامبر | +17 | |||
| 16 سپتامبر | +5 | |||
| 15 سپتامبر | +23 | |||
| 14 سپتامبر | +16 | |||
| 13 سپتامبر | +11 | |||
| 12 سپتامبر | +18 | |||
| 11 سپتامبر | +21 | |||
| 10 سپتامبر | +13 | |||
| 09 سپتامبر | +7 | |||
| 08 سپتامبر | +23 | |||
| 07 سپتامبر | +14 | |||
| 06 سپتامبر | +6 | |||
| 05 سپتامبر | +1 | |||
| 04 سپتامبر | +24 | |||
| 03 سپتامبر | +15 | |||
| 02 سپتامبر | +28 | |||
| 01 سپتامبر | +10 |
| 2 | بدون متن... | 2 524 |
| 3 | በእንግሊዝ ወታደሮች የተዘረፈው የአፄ ቴዎድሮስ የብራና መጽሐፍ ቅዱስ ለሽያጭ በጨረታ መልክ መቅረቡ ውዝግብ አስነሳ
ቅዳሜ ፣ መስከረም 09 ቀን 2019 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በ19ኛው ክፍለ ዘመን በብሪታንያ ኃይሎች ከአጼ ቴዎድሮስ ቤተ መንግሥት የተዘረፈውና “የጎንደር ወንጌል” በመባል የሚታወቀው ጥንታዊ የብራና መጽሐፍ ከ160 ዓመታት ገደማ በኋላ በጨረታ ካታሎግ ላይ ለሽያጭ መቅረቡን ተከተሎ የይመለስልን ጥያቄ ውዝግብ አስነስቷል።
በግዕዝ ቋንቋ የተጻፈውና በ1730ዎቹ በጎንደር ከተማ እንደተፃፉ የሚገመተው ይህ ብርቅዬ የቅዱሳት መጻሕፍት ስብስብ፣ የሉቃስና የዮሐንስ ወንጌልን የያዘ ሲሆን 235 በቀለማት ያሸበረቁ ስዕሎችን ያካተተ እንደሆነ አልጀዚራ ዘግቧል።
መጽሐፉ በአቡ ዳቢ ዓለም አቀፍ የመጽሐፍ ኤግዚቢሽን ላይ በቬና ኢንሊብሪስ በተባለ መጻሕፍት አከፋፋይ ድርጅት በኩል በ250 ሺህ ዶላር ለሽያጭ ቀርቧል።
የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው ለድርጅቱ በላኩት ደብዳቤ፣ የተዘረፉ ታሪካዊ ቅርሶችን ለሽያጭ ማቅረብ በሞራልና በሥነ-ምግባር ደረጃ ተቀባይነት የሌለው መሆኑን በመግለፅ መጽሐፉ ከሽያጭ ተሰርዞ ወደ ባለቤቱ ኢትዮጵያ እንዲመለስ ጠይቀዋል።
በተቃራኒው የኢንሊብሪስ ድርጅት ኃላፊ ሁጎ ቨርትሸርክ ደግሞ ቅርሱ ከመቶ ዓመታት በፊት በወታደራዊ ግጭት ወቅት የተወሰደ በመሆኑ አሁን ባለው የሕግ አሰራር የመመለስ ግዴታ የለብንም ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
ድርጅቱ መጽሐፉን ለሽያጭ ያቀረበው በግል ባለቤቱ ስም እንደሆነ በመግለፅ “የሕግ መሠረት ከሌለ በስተቀር” መጽሐፉን መስጠት እንደማይቻል ገልጿል። ነገር ግን ቅርሱን የኢትዮጵያ ተቋማት በቅናሽ ዋጋ ለመግዛት ከፈለጉ ለመደራደር ፈቃደኛ እንደሆኑ ጠቁመዋል።
የታሪክ ተመራማሪዎችና የሥነ ጥበብ ባለሙያዎች በበኩላቸው ይህ ቅርስ የሃይማኖት መጽሐፍ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ጥንታዊ የጽሁፍ፣ የጥበብና ታሪካዊ ሁነቶች የያዘ እና የሚያስረዳ ትልቅ ሀብት በመሆኑ በንግግርና በስምምነት መፍትሔ ሊበጅለት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ይህ ውዝግብ ኢትዮጵያ በ1860ዎቹ በመቅደላ ውጊያ ወቅት በብሪታንያ ኃይሎች የተዘረፉ በርካታ ታሪካዊ ቅርሶቿንና ንብረቶቿን ለማስመለስ የምታደርገውን አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ጥረት እንደገና ቀስቅሶታል ሲል ዘገባው አውስቷል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲t.ly/mxA | 2 912 |
| 4 | بدون متن... | 2 617 |
| 5 | የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሁቲዎች በቀይ ባህር እያደረጉት ያለው እንቅስቃሴ የአፍሪካ ሀገራትን ጥቅም የሚነካ ነው አለ
ዓርብ ፣ መስከረም 08 ቀን 2019 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን፤ የሁቲ ኃይሎች በሳውዲ ዓረቢያ እና በቀይባህር ላይ በሚንቀሳቀሱ የንግድ መርከቦች ላይ የሚሰነዝራቸውን ጥቃት በማውገዝ፣ ጥቃቱ የአፍሪካን ሀገራት ጥቅም የሚነካ በመሆኑ ጦርነቱ እንዳይስፋፋ ፖለቲካዊ መንገዶች ሊበጅለት ይገባል ሲል አሳሰበ።
ህብረቱ፤ በቅርቡ በቀይ ባህር ላይ እየታየ ያለው ወታደራዊ ውጥረት መባባስ፣ የሳዑዲ ዓረቢያ መንግሥትን ግዛት እንዲሁም ዓለም አቀፍ የባህር መርከብ እንቅስቃሴን ዒላማ ያደረጉ ጥቃቶችን ጨምሮ በከፍተኛ ስጋትነት እየተከታተለ መሆኑን ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
በተጨማሪም መካንና ሌሎች የሳዑዲ ዓረቢያ ወስጥ ያሉ ቅዱሳን ከተሞችን ለጥቃት ዒላማ ለማድረግ የተደረጉ ሙከራዎችን የሚገልጹ ዘገባዎች፣ ቅዱሳን ቦታዎች ላይ ስጋት መደቀናቸዉን እንዲሁም እነሱን የሚጎበኙ ሰላማዊ ሰዎችና ሐጃጆች ሙሉ በሙሉ መጠበቅ እንዳለባቸውና በማንኛውም ሁኔታ የወታደራዊ እርምጃ ዒላማ መሆን የለባቸውም ብሏል፡፡
ተቋሙ፤ በተጨማሪም በቀይ ባህርና በባቤል መንደብ የባህር መተላለፊያ ውስጥ በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት የመርከብ ነጻነት መርህን በጽኑ ሲያረጋግጥ ስትራቴጂካያዊ የባህር መስመር ላይ የመርከብ እንቅስቃሴን ለማደናቀፍ ወይም ለማስፈራራት የሚደረግ ማንኛውም እርምጃ አግባብ አይደለም ብሏል።
ይህም በባህር ዳርቻ ላሉ መንግሥታት ብቻ ሳይሆን ለዓለም አቀፍ ንግድ እና የአቅርቦት ሰንሰለቶች፣ ለኢነርጂ ደኀንነት እና ለአፍሪካ ኢኮኖሚም ከባድ አደጋ ያስከትላል ሲል አስጠንቅቋል፡፡
ኮሚሽኑ የቀይ ባህርን እና የባቤል መንደብ የባህር መተላለፊያ ደኀንነት ለአፍሪካ፣ በተለይም ለአፍሪካ ቀንድ መንግሥታት እና ለቀይ ባህር ዳርቻ ላሉ መንግሥታት ትልቅ ስትራቴጂያዊ ጥቅም ያለው በመሆኑ ከጥቃት ውጭ መሆን እንዳለባቸው አስታውቋል።
የአፍሪካ ህብረት በመካከለኛው ምስራቅ እየተካሄዱ ያሉት ግጭቶች የበለጠ ቀጣናዊ ስፋት የመያዝ አደጋ የደቀኑ በመሆናቸው የደኀንነት፣ የሰብዓዊ እና የኢኮኖሚ ውጤቶቹ በቀጥታ አፍሪካን ይነካሉ ብሏል፡፡
ህብረቱ በሲቪሎች፣ በሲቪል እና በኢኮኖሚያዊ መሠረተ ልማት እዲሁም በንግድ መርከብ ላይ የሚደረጉ ጥቃቶች ወዲያውኑ እንዲቆሙ እና የመርከብ ነጻነት እንዲከበር እንድሁም ውጥረቱ አስቸኳይ በሆነ መንገድ እንዲቃለል አሳስቧል፡፡
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲t.ly/mxA | 3 665 |
| 6 | بدون متن... | 3 151 |
| 7 | በደቡብ ሱዳን በተቀሰቀሰ የጎሳ ግጭት ቢያንስ 26 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ
ዓርብ ፣ መስከረም 08 ቀን 2019 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በደቡብ ሱዳንና በሱዳን ድንበር ላይ በምትገኘው አቢዬ ከተማ በሁለት ተቀናቃኝ ጎሳዎች መካከል በተካሄደ ግጭት ቢያንስ 26 ሰዎች ሲገደሉ፣ 82 ሰዎች መቁሰላቸውን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ባወጣው መግለጫ አመለከተ፡፡
ግጭቱ በአቢዬ ከተማ በሚገኘው የአሚየት የጋራ ገበያ ላይ የተከሰተ ሲሆን፣ በንጎክ ዲንቃ እና በሚሴሪያ ጎሳዎች አባላት መካከል መሆኑ ተመላክቷል።
ግጭቱ የተቀሰቀሰው ሰኞና ማክሰኞ በሁለቱም ጎሳዎች የተወጣጡ ሁለት ሰዎች በተናጠል መገደላቸውን ተከትሎ ነው።
የተባበሩት መንግሥታት ጊዜያዊ የአቢዬ ደህንነት ኃይል እንዳስታወቀው፤ በገበያው ዙሪያ የተፈጠረው ውጥረት በሁለቱ ማኅበረሰቦች መካከል ወደ ከባድ ግጭት እንደተቀየረ አስታውቆ የአሚየት ገበያ በአካባቢው ዋነኛ የንግድ ማዕከል መሆኑም ተገልጿል።
በመግለጫው፣ “ከከባድ ጥቃቱ በኋላ በገበያውና በአካባቢው ያለውን የጸጥታ ኃይል ወዲያውኑ አጠናክረናል፤ ሁኔታውን ለማርገብም ተጨማሪ ኃይሎችን አሰማርተናል” ማለቱን ሮይተርስ ዘግቧ።
ንጎክ ዲንቃ እና ሚሴሪያ ጎሳዎች ለረዥም ጊዜ በግጭት ውስጥ የቆዩ ሲሆኑ፣ በግጦሽ መሬትና በእንስሳት መጠጫ ውኃ ስፍራዎች ላይ በሚነሱ ክርክሮች ምክንያት ቀደም ሲልም ለሞት የሚዳርጉ ግጭቶች ተከስተው ነበር።
ደቡብ ሱዳን እ.ኤ.አ. በ2018 የተፈረመው የሰላም ስምምነት አምስት ዓመታትን የዘለቀውን ጦርነት ካቆመ በኋላ በአብዛኛው በሰላም ቆይታለች።
በዚያ ግጭት በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የተገደሉ ሲሆን በአገሪቱ ከነፃነቷ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄዱት አጠቃላይ ምርጫዎች በታህሣሥ ወር እንዲካሄዱ እቅድ መያዙም በዘገባው ተካትቷል ።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲t.ly/mxA | 3 113 |
| 8 | بدون متن... | 2 701 |
| 9 | የኤን.ቢ.ሲ ጋዜጠኛው ታደሰ ዳኛቸው ከእስር መለቀቃቸውን ጠበቃቸው ሀይሉ ታደሰ ለአዲስ ማለዳ ተናገሩ።
ዓርብ ፣ መስከረም 08 ቀን 2019 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የተለያዩ የጊዜ ቀጠሮዎች እየተሠጡት እና ፖሊስም በተደጋጋሚ ምርመራዬን አልጨረስኩም በማለቱ በከፍተኛ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ መሠረት በእስር ለይ የቆየው ታደሰ ዳኛቸው ለመስከረም 6 ቀን 2019 የመጨረሻ ቀጠሮ ተሠጥቶት እንደነበር አዲስ ማለዳ መዘገቧ ይታወሳል።
በዕለቱም ማለትም መስከረም 6 ቀን 2019 ዓ.ም ጠበቃቸው እንደገለፁት " የዋስትና መብቱ ተጠብቆለታል በ10 ሺ ብር ዋስትና እንዲለቀቅ ተወስኗል" በማለት መስከረም 6 ቀን 2019 ዓ.ም ከሰዓት ሊፈታ እንደሚችል ጠበበቃቸው ነግረውን መዘገባችን አይዘገነጋም ።
በዚሁ መሠረትም ታደሰ መስከረም 6 ቀን 2019 ዓ.ም ከከሰዓት በኋላ የዋስተና መብቱ ጠብቆ በ10 ሺ ብር ዋስትና መለቀቁን ጠበቃቸው ዛሬ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል ።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲t.ly/mxA | 2 945 |
| 10 | بدون متن... | 2 655 |
| 11 | ኢትዮጵያ የማንንም ሉዓላዊ ሀገር የመውረር ፍላጎት የላትም ሲሉ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ተናገሩ
ዓርብ ፣ መስከረም 08 ቀን 2019 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል ዲና ሙፍቲ ይህንን የገለጹት፤ ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነቷን ማስጠበቅ እንዳለባት በተናገሩበት መድረክ ነው።
በንግግራቸውም ኢትዮጵያ የባህር በሯን ማስመለስ ያስፈለገበት ዋነኛ ምክንያቶችን ዘርዝረዋል፡፡
ከነዚህም መካከል በታሪክ የባህር በር የነበራት ሀገር በመሆኗ፣ መልካምድራዊ አቀማመጧ የባህር በር አጠገብ ያለች ሀገር በመሆኗ፣ የባህር በር ከሌላቸው ትላልቅ ሀገራት መካከል በግንባር ቀደምነት ኢትዮጽያ ስለምትገኝ ፣ እንዲሁም የደኀንነት እና የፀጥታ ጉዳይ ማለትም በባህር ላይ የባህር ውንብድና በመኖሩ ይሄንን ለመከላከል እና ለመሠል ሀገራዊ ጉዳዮች ሀገሪቷ የባህር በር እንድታገኝ ምክንያቶች ናቸው ሲሉ ተናግረዋል ።
ይሁንና የባህር በሩን ለማግኘት የሰጥቶ መቀበል መርህን መከተል ዋነኛ አማራጭ እንደሆነ አንስተው፤ ሰላማዊ እና ዲፕሎማሲያዊ በሆነ መንገድ ማግኘት ይቻላል በማለት ኢትዮጵያ የማንንም ሉዓላዊ ሀገር የመውረር ፍላጎት የላትም ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ እንዲህ ዓይነት ታሪክ ያላት ሀገር አይደለችም የሚሉት ዲና፤ በሰጥቶ መቀበል መርህ፣ በስምምነት፣ በመደጋገፍ ብቻ ነው የባህር በር ፍላጎቷን ማርካት የምትችለው ሲሉ ተደምጠዋል ።
ይህ ጉዳይ ጊዚያዊ እና ቀላል አጀንዳ አይደለም ያሉት አምባሳደሩ ብሔራዊ እና በዜግነት ግዴታ የሚጋሩት አጀንዳ መሆኑን አስታውሰዋል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲t.ly/mxA | 3 072 |
| 12 | بدون متن... | 2 541 |
| 13 | መከላከያ ሰራዊት በርካታ ታጣቂዎች ህወሓትን በመቃወም እና ከመከላከያ ጋር ቀድመው በመሰረቱት ግንኙነት እጅ መስጠታቸውን አስታወቀ
ዓርብ ፣ መስከረም 08 ቀን 2019 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት 300 የሚሆኑ የህወሓት ታጣቂዎች በቀጣናው ከሚገኘው መከላከያ ሠራዊት ጋር ቀደም ብለው በመሠረቱት ግንኙነት አማካይነት በመነጋገር እና መንገድ በማመቻቸት በተከዜ አካባቢ ለሚገኘው ለሰሜን ምዕራብ ዕዝ እጅ መስጠታቸውን አስታወቀ።
መከላከያ እንደገለፀው ከሆነ፤ በምዕራብ ግንባር ተከዜ አካባቢ ልዩ ቦታው በተከዜ ድልድይ ግራና ቀኝ አቅጣጫ ለዕዙ እጅ ሰጥተዋል ያለቸው የህወሓት ታጣቂዎች “የኢትዮጵያና የትግራይ ህዝብ ጠላት” በመሆን የትግራይን ህዝብ “ሲጨፈጭፍ” ከነበረው ሻዕቢያ ጋር “ጽምዶ” በሚል ጥምረት ፈጥሯል ብለዋል።
አክሎም ይህን “የፅምዶ”ን እሳቤ የፈጠሩት ጥምረት ለትግራይ ህዝብ የማይጠቅምና የሚጎዳ መሆኑን ተገንዝበው በቀጣናው ለሚገኘው መከላከያ ሠራዊት ጋር ቀድመው በመሰረቱት ግንኙነት መሰረት እጅ መሥጠት እንደቻሉ ተናግረዋል ብሏል።
በተጨማሪም “የትግራይ ህዝብ ጥያቄ የሚፈታው በጠብመንጃ ሳይሆን በመነጋገር እና በመግባባት ነው” የሚል እምነት እንደያዙ በመግለጽ ለሰሜን ምዕራብ ዕዝ እጅ መስጠታቸውን ገልጿል።
ታጣቂዎች ከ285 በላይ የነፍሰ ወከፍና የቡድን መሣሪያዎች፣ በርካታ የተለያዩ ዓይነት ተተኳሾች፣ የጦር ሜዳ መነፅርና ልዩ ልዩ ሰነዶችን ይዘው መግባታቸውንም ገልጿል።
ታጣቂዎቹ “ራሳቸውን ከተጠያቂነት ለማዳን” እንዲሁም “ሰላማዊውን የትግራይን ህዝብ ወጣት በማፈስ ወደ ጦርነት ለመማገድ የሚሠሩ ዘራፊ እና ወርቅ አውጪ የህወሓት አመራሮችን ፍላጎት በመቃወም” እጅ እንደሰጡ በመግለጽ ታጣቂዎቹ፣ አሁንም ቢሆን አለመግባባቱ ሊፈታ የሚችለው “በጥቂት ጨቋኝ የህወሓት አመራሮች ፍላጎት ሳይሆን በመነጋገር ብቻ ነው” የሚል ሙሉ እምነት ይዘው እጅ መሥጠታቸውንም ተናግረዋል ብሏል።
እንደ መከላከያ መረጃ ከሆነ፤ ከታጣቂዎች መካከል ከክፍለ ጦር አዛዥ ጀምሮ በየደረጃው የሚገኙ የሻለቃና የሻምበል አመራሮች እንደሚገኙበት ያመለክታል። አክሎም እየተዋጋ የነበረው በህወሓት አገዛዝ አሥገዳጅነት እንደነበርም አስታውቋል።
እጅ የሰጡት ታጣቂዎች “ህወሓት ከጦርነት አዙሪት የመውጣት ፍላጎት የሌለው” በማለት “ፅምዶ” በሚል እየሄደበት ያለው “ህዝቡን አሁንም ወደ ከፋ ችግር ውስጥ ለመክተት የሚጥር፤ የሚያደርገው እንቅስቃሴ ለሠላም የማይመች፤ የቀረበለትን የሠላም አማራጭ የማይቀበል” በመሆኑ በትግራይ ህዝብ ዘንድ ተቀባይነት አጥቷል ብለዋል ሲል መከላከያ ዘግቧል።
እንደመረጃው ከሆነ አሁን ላይ ሌሎች የህወሓት ታጣቂዎች “ተገድዶ የገባው የትግራይ ወጣት” ይህን አውቆ እና ተረድቶ ጊዜና ሁኔታው ሲመቻችለት እጅ ለመስጠት ዝግጁ መሆኑን ታጣቂዎቹ ገልፀዋል ብሏል። ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ አዲስ ማለዳ በህወሓት በኩል ይህንን የተመለከተ መረጃ አልተመለከተችም።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲t.ly/mxA | 2 913 |
| 14 | بدون متن... | 2 667 |
| 15 | ቻይና የሳዑዲ ዓረቢያ የድጋፍ ጥሪ ተከትሎ ኢራን ሁቲ ላይ ያላትን ተፅዕኖ በመጠቀም ጫና እንድታደርግ በምስጢር መጠየቋ ተሰማ
ዓርብ ፣ መስከረም 08 ቀን 2019 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
ቻይና፤ አራን፣ የየመኑ የሁቲ አማፅያን የሚያደርሱትን ጥቃት እና ወታደራዊ እንቅስቃሴ እንዲገታ ተፅዕኖዋን እንድትጠቀም በምስጢር መጠየቋ ተገለጸ።
ኢራን ከቻይና ለቀረበላት ጥያቄ በሰጠችው ምላሽ፣ በቀጣናው ያለው ሰላም እና መረጋጋት ሊመጣ የሚችለው አሜሪካ እና እስራኤል በኢራን ላይ የሚያደርጉትን ጦርነት እና ጥቃት ሲያቆሙ ብቻ እንደሆነ ገልጻለች።
ይህንን የዘገበው ደግሞ ሮይተርስ ከጉዳዩ ጋር ቅርበት አላቸው ያላቸው ሦስት የኢራን ምንጮቹን ጠቅሶ ነው።
ቻይና በይፋዊ መግለጫዎቿ በኩል ሁሉም ወገኖች እንዲረጋጉ እና ውይይት እንዲያደርጉ እንዲሁም ውጥረቱን እንዲያረግቡ ጥሪ ያቀረበች ቢሆንም፣ ለቴህራን በምስጢር አስተላልፋዋለች በተባለው መልዕክት ኢራን በሁቲዎች ላይ ያላትን ተፅዕኖ ተጠቅማ በዓለም አቀፍ የኃይል አቅርቦት መስመሮች ላይ የተደቀነውን አደጋ እንድታስቆም መጠየቋ ተሰምቷል።
የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ ለሮይተርስ እንደተናገረው ከሆነ፤ ቻይና የቀጣናው ውጥረት ወደ የመን እና ቀይ ባሕር ሲስፋፋ ማየት አትፈልግም ያለ ሲሆን የሁሉም ሀገራት ሉዓላዊነት እና ደኀንነት መከበር እንዳለበት ተናግሯል።
ይህ የቻይና ምስጢራዊ እርምጃ የመጣው ሳዑዲ ዓረቢያ በሁቲዎች በኩል ቀይ ባሕር እና በባቤል መንደብ ወሽመጥ አካባቢ ያደረገው ፈጣን ወታደራዊ እንቅስቃሴ ስጋት ውስጥ በመውደቋ ለቤጂንግ የእርዳታ ጥሪ ካቀረበች በኋላ ነው።
የሁቲዎች እንቅስቃሴ የሳዑዲ ዓረቢያን የነዳጅ ገበያን እና የባሕር ትራንስፖርት ደህንነት አደጋ ላይ መጣሉ ብቻ ሳይሆን ሁቲን ስትደበደብ የኖረችው አሜሪካም ሳዑዲ ዓረቢያን ላለመደገፍም መወሰኗ ይታወሳል።
በዓለም ላይ ትልቅ ኢኮኖሚ ያላት እና ሁለተኛ ደረጃን የምትይዘው ቻይና አብዛኛውን የነዳጅ ፍላጎቷን የምታሟላው ከመካከለኛው ምስራቅ በመሆኑ የሆርሙዝ እና የባብ ኤል መንደብ መስመሮች መዘጋት ወይም መታወክ በኢኮኖሚዋ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል።
ቻይና ለኢራን ከፍተኛ የነዳጅ ገዢ እና የንግድ አጋር በመሆኗ በቴህራን ላይ ዲፕሎማሲያዊ ተፅዕኖ ማሳደር ከሚችሉ ጥቂት ሀገራት አንዷ ብትሆንም፣ በሁቲዎች አቋም ላይ ፈጣን ለውጥ ማምጣት እንደምትችል ገና አልተረጋገጠም ሲል የሮይተርስ ዘገባ አመልክቷል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲t.ly/mxA | 3 196 |
| 16 | بدون متن... | 3 094 |
| 17 | በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመረጃ ውስንነት እና የግንዛቤ ማነስ በተፈናቃዮች ላይ ተጽዕኖ ማሳደሩ ተገለጸ
ሐሙስ ፣ መስከረም 07 ቀን 2019 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ድርጅቶች ህብረት(ኢሰመድህ) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ወቅት በሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች ተሳትፎ ላይ የመረጃ ውስንነት እንደነበረ፣ ማለትም እነመርጣለን አንመርጥም የሚለው ተፅዕኖ እንዳሰደረ እና መራጮች ድምፅ መስጠታቸው የሚያመጣውን ለውጥ በሚመለከት በቂ እምነትና ድፍረት እንዳልነበራቸው ተገለፀ።
የህብረቱ ዳይሬክተር መስዑድ ገበየሁ በዛሬው ዕለት ምርጫውን አስመልክቶ በዛሬው ዕለት በተዘጋጀው የውይይት መድረከሰ እንደተናገሩት፤ በምርጫው ወቅት በተፈናቃይ ጣቢያዎች ውስጥ የነበረው የመረጃ ተደራሽነት ማነስ በዜጎች ተሳትፎ ላይ ተጽዕኖ አሳድሯል።
መስዑድ አያይዘውም “ተፈናቃዮች መረጃ ሳይኖራቸው ሲቀር ሳይሳተፉ ይቀራሉ፤ ይህም የፖለቲካ መገለልን ያስከትላል” በማለት የነበረውን ሁኔታ አስረድተዋል።
በተጨማሪም በተፈናቃይ ጣቢያዎች በኩል የተወሰኑ ስጋቶች ነበሩ ሲሉ የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ “ባንሳተፍ አሁን የምናገኛቸውን ድጋፎች ላናገኝ እንችላለን በሚል ስጋት ወደ ምርጫው የመጡ መራጮች ነበሩ” ሲሉ በማስረዳት የነበረውን ሁኔታ አንስተዋል።
ይሁንና በእጩዎች ወይም በገዥው ፓርቲ በኩል የተደረገ ግልጽ የሆነ አስገዳጅነት ወይም ተጽዕኖ እንደሌለ ተናግረዋል።
ኢሰመድህ ተፈናቃዮች ባሉባቸው ቦታዎች፤ በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ እና በሶማሌ ክልል ጎሌጅ ካምፕ ታዛቢዎችን አሰልጥኖ ዝግጁ አድርጎ የነበረ ቢሆንም፣ በልዩ ምርጫ ጣቢያዎቹ የምርጫው ቀን ቀደም ብሎ በቂ መረጃ ባለመኖሩ ምክንያት ጉልህ ክፍተቶች እንደነበሩ ገልጿል።
በሌላ በኩል ደግሞ በተፈናቃይ ጣቢያዎች የምርጫ ትምህርት በአግባቡ ባለመሰጠቱ ምክንያት፣ መራጮች ድምፅ መስጠታቸው የሚያመጣውን ለውጥ በሚመለከት በቂ እምነትና ድፍረት እንዳልነበራቸው አንስተዋል።
መስዑድ አክለውም አዲስ መንግስት ለመመስረት ቀናት እንደቀሩት አስታውሰው የተመረጡ እንደራሴዎች በቅስቀሳ ወቅት የገቡትን ቃል እንዲፈጽሙ ለማድረግ የመራጩ ህዝብ ንቃት የሲቪል ማህበራት ክትትል እና ሚዲያዎች የገቡትን ቃል መፈፀማቸውን የሚመለከቱ ዘገባዎች ወሳኝ ሚና እንዳላቸው አመልክተዋል።
ለ8ኛው ጠቅላላ ምርጫ፤ የምርጫ ቦርድን ተቋማዊ ነፃነትና አቅም ማጠናከር የኤሌክትሮኒክ አሰራርን በስፋት ስራ ላይ ማዋል እና የባለድርሻ አካላትን የምክክር መድረኮች አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ተገልጿል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲t.ly/mxA | 3 819 |
| 18 | بدون متن... | 3 553 |
| 19 | አሜሪካ በየመን ከሁቲ መሪዎች ጋር ምስጢራዊ ውይይት ካደረገች በኋላ ለሳዑዲ አረቢያ ወታደራዊ ድጋፍ ላለማድረግ ወሰነች
ሐሙስ ፣ መስከረም 07 ቀን 2019 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የአሜሪካ ባለሥልጣናት በኦማን ሙስካት ከሁቲ መሪዎች ጋር ያደረጉትን ምስጢራዊ ስብሰባ ተከትሎ፣ የዋሽንግተን አስተዳደር ሁቲዎች በየመን የሚያደርጉትን የግዛት መስፋፋት ለመግታት ሳዑዲ አረቢያ የምታደርገውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ ላለመደገፍ መወሰኑ ተገለጸ።
እንደ ዘጋርዲያን ዘገባ ከሆነ፤ በኢራን የሚደገፉት ሁቲዎች በኦማን በሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ በተካሄደው ውይይት በ2025 እ.ኤ.አ. የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት አሁንም እንደሚፀና እና በቀይ ባሕር ላይ ባሉ የአሜሪካ መርከቦች ላይ ጥቃት የማድረስ ፍላጎት እንደሌላቸው ለአሜሪካ ማረጋገጫ ሰጥተዋል።
ሁቲዎቹ አክለውም በየመን ላይ በተጣለው እገዳ ምክንያት ከሳዑዲ አረቢያ ጋር የተያያዙ የነዳጅ እና የንግድ መርከቦች ብቻ ኢላማ እንደሚደረጉ አስታውቀዋል።
ይህ ውይይት የትራምፕ አስተዳደር ሁቲዎች በየመን ምዕራባዊ የባሕር ዳርቻ ያደረጉትን ግስጋሴ እና በባቤል መንደብ ላይ የደገኑትን ስጋት ቢያወግዝም፣ ሪያድን ለመደገፍ ወታደራዊ እርምጃ ከመውሰድ የተቆጠበበትን ምክንያት እንደሚያስረዳ ተጠቁሟል።
አሜሪካ ከሁቲዎች ጀርባ ከምትቆመው ኢራን ጋር ውድ እና ሀብት የሚያሟጥጥ ግጭት ውስጥ በመሆኗ ተጨማሪ ወታደራዊ እርምጃ መውሰድ አልፈለገችም።
አሜሪካ በየመን ቀጥተኛ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት ላለማድረግ የወሰደችው አቋም፣ ሳዑዲ አረቢያ ከሁቲዎች ጋር የዲፕሎማሲ መፍትሔ እንድትፈልግ ወይም እንቅስቃሴያቸውን ለመግታት ከፓኪስታን እና ቱርክ ጋር ቀጣናዊ ጥምረት እንድትፈጥር ጫና አሳድሮባታል።
ባለፈው ሳምንት ሁቲዎች ባካሄዱት ፈጣን ማጥቃት በምዕራብ የመን የቀይ ባሕር ዳርቻ የሚገኙ ሰፊ ቦታዎችን መቆጣጠራቸው ይታወሳል።
የቀድሞው የአሜሪካ ምክትል አምባሳደር ናቢል ኹሪ እንደገለጹት፤ በዋሽንግተን እና በሁቲዎች መካከል የስውር መግባባት ስምምነት ተደርሷል። ሁቲዎች የአሜሪካና የዓለም አቀፍ መርከቦች ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንደማይስተጎል ቃል የገቡ ሲሆን፣ ስጋቱ በሳዑዲ መርከቦች ላይ ብቻ የተወሰነ እንደሚሆን ተናግረዋል።
በሌላ በኩል፣ ሳዑዲ አረቢያ የሕዝብ ድጋፍ ለማስገኘት ሲሉ ሁቲዎች በመካ ከተማ ላይ የድሮን ጥቃት ለመፈጸም ሞክረዋል ብላ የከሰሰች ሲሆን፣ ሁቲዎች ግን ይህንን ክስ «የክፍለ ዘመኑ ውሸት» ሲሉ አስተባብለውታል፡፡
በተመሳሳይ ጊዜ ሁቲዎች የሳዑዲን ኤፍ-15 የጦር አውሮፕላን መጣላቸውን እና በያንቡ ወደብ በሚገኘው የአራምኮ ተቋም ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን ገልጸዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ አሜሪካ፣ እስራኤል እና በርካታ የዓረብ ሀገራት (ሳዑዲ አረቢያ፣ ኤምሬትስ፣ ባህሬን፣ ኩዌት፣ ካታር፣ ዮርዳኖስ እና ግብፅን ጨምሮ) በጀርመን ምስጢራዊ የወታደራዊ መሪዎች ስብሰባ ማካሄዳቸው የተሰማ ሲሆን፣ እስራኤል በየመን ውስጥ በሳዑዲ በኩል ጣልቃ ለመግባት ጥያቄ ማቅረቧ ተጠቅሷል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲t.ly/mxA | 4 154 |
| 20 | بدون متن... | 3 543 |
