Addis Maleda - አዲስ ማለዳ
📈 Análisis del canal de Telegram Addis Maleda - አዲስ ማለዳ
El canal Addis Maleda - አዲስ ማለዳ (@addismaleda) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 33 035 suscriptores, ocupando la posición 7 619 en la categoría Noticias y medios y el puesto 1 055 en la región Etiopía.
📊 Métricas de audiencia y dinámica
Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 33 035 suscriptores.
Según los últimos datos del 02 septiembre, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 477, y en las últimas 24 horas de 28, conservando un alto alcance.
- Estado de verificación: No verificado
- Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 14.76%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 9.98% de reacciones respecto al total de suscriptores.
- Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 877 visualizaciones. En el primer día suele acumular 3 298 visualizaciones.
- Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 11.
📝 Descripción y política de contenido
El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“ዜና ከምንጩ”
Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 03 septiembre, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Noticias y medios.
Carga de datos en curso...
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 04 septiembre | +7 | |||
| 03 septiembre | +15 | |||
| 02 septiembre | +28 | |||
| 01 septiembre | +10 |
| 2 | Sin texto... | 777 |
| 3 | ኖርዌይ የሩሲያን መርከብ በዩክሬን የነዳጅ ኩባንያ ጥያቄ በመያዝ ሞስኮን አስቆጣች
ዓርብ፣ ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
ኖርዌይ፤ በአርክቲክ ስትንቀሳቀስ የነበረች የሩሲያን መርከብን በዩክሬን የነዳጅ ካምባኒ ናፍቶጋዝ ጥያቄ መሰረት የያዘች ሲሆን፣ ይህም ሞስኮን ክፉኛ አስቆጥቷል ተባለ።
በአርክቲክ ስቫልባርድ በተሰኘ ቦታ ላይ በሚገኘው የባሬንትስበርግ ወደብ፣ የነበረችው ፕሮፌሰር ሞልቻኖቭ የተሰኘቸው መርከብ እንደሆነች ተገልጿል። ሩሲያ አለኝ ያለችውን አማራጭ ሁሉ ልትጠቀም እንደምትችል አስታውቃለች።
እርምጃው የተወሰደው የዩክሬን ብሔራዊ የነዳጅ እና ጋዝ ኩባንያ ናፍቶጋዝ ባቀረበው የህግ ጥያቄ መሰረት እንደሆነ ተገልጿል።
ይህ የመርከብ መያዝ ከካሣ ጋር የሚያያዝ ሲሆን እ.አ.አ. በ2014 ሩሲያ፤ ክሬሚያን በኃይል በያዘችበት ወቅት፣ የናፍቶጋዝን የነዳጅ እና የጋዝ መሰረተ ልማቶች በህገ ወጥ መንገድ ስለወሰደችበት ነው ተብሏል።
በሄግ የሚገኘው ዓለም አቀፍ የግልግል ዳኝነት ፍርድ ቤት እ.ኤ.አ. በ2023 ሩሲያ ለናፍቶጋዝ 4.22 ቢሊዮን ዶላር የካሳ ክፍያ እንድትፈጽም ውሳኔ ሰጥቶ እንደነበር ይታወሳል።
ሞስኮ ክፍያውን ለመፈጸም ፈቃደኛ ባለመሆኗ፣ የኖርዌይ ኖርድ-ትሮሚስ እና ሴንያ የዲስትሪክት ፍርድ ቤት ከሶስት ቀን በፊት መርከቧ እንድትያዝ ትዕዛዝ አስተላልፏል ተብሏል። አሁን ላይ መርከቧ ስድስት ቢሊዮን ዶላር ታወጣለች ተብሏል።
መርከቧ፤ በዋናነት ለንግድ እና ለምርምር ጉዞዎች የምታገለል ስትሆን፣ ከቦታዋ እንዳትንቀሳቀስ እገዳ ተጥሎባት በውስጧ ያሉትን ተሳፋሪዎች እና ሰራተኞች ሁኔታ የኖርዌይ ባለስልጣናት ይዘውታል ተብሏል።
የናፍቶጋዝ ኩባንያ ጊዜያዊ ስራ አስፈጻሚ፤ ሩሲያ የዓለም አቀፍ የፍርድ ቤት ውሳኔን ባለመቀበል ብቻ ከተጠያቂነት ማምለጥ እንደማትችል አንስተው የካሳ ክፍያው እስከሚከፈላቸው ድረስ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ የሩሲያ ሀብቶችን ማደናቀፋችንን እንቀጥላለን ብለዋል ሲል ሮይተርስ ዘግቧል። ይሁን እንጂ ሩሲያ የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ እውቅና እንደማትሰጠው አስታውቃለች።
የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና የሩሲያ ባለስልጣናት የኖርዌይን እርምጃ “የባህር ላይ ዘረፋ” እና “ዓለም አቀፍ ህግን የጣሰ ፖለቲካዊ ውሳኔ” ሲሉ ያወገዙት ሲሆን ሩሲያ ውሳኔውን በህግ እንደምትታገል አስታውቃለች።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 1 316 |
| 4 | Sin texto... | 1 251 |
| 5 | በኮንጎ ኢቦላ በተስፋፋባቸው አካባቢዎች ትምህርት ቤቶችን እንደገና በመክፈት በርቀት ትምህርት ለመስጠት ተይዞ የነበረውን ደንብ መሰረዙ ተገለጸ
ሐሙስ፣ ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በኢቦላ በከፍተኛ ሁኔታ ጉዳት ባደረሰባቸው አካባቢዎች ትምህርት ቤቶች በዚህ ሳምንት የተከፈቱ ሲሆን ከዚህ ቀደም ትምህርት በርቀት እንደሰጥ የነበረው ደንብ እንደተሰረዘ ተገለጸ።
የሀገሪቱ ባለስልጣናትም የበሽታው የመተላለፍ አደጋ ተማሪዎች በርቀት ትምህርት ሲማሩ ከሚያጋጥማቸው አደጋ ያነሰ ነው የሚል ዉሳኔ ላይ መድረሳቸዉን አስታዉቀዋል፡፡
በሀገሪቱ በረዥም ጊዜ ታሪኳ ባጋጠማት የኢቦላ ወረርሽኝ የሞቱ ሰዎች ቁጥ ከ3 ሺ ያለፈ ሲሆን፤ ይህ የሀገሪቱ መንግስት ባወጣዉ መረጃ መሰረት ሲሆን በሽታው በስድስት ግዛቶች ተሰራጭቶ የሟች መጠኑ ደግሞ 48.6 መቶ እንደሆነ ሲንቢሲ አፍሪካ ሮይተርስን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።
የሀገሪቱ የትምህርት ሚኒስቴር ሰነድ መሰረት በኢቱሪ ከ1ሺ በላይ ትምህርት ቤቶች “ቀይ ዞን” ውስጥ ሲመደቡ ይህም ማለት ደግሞ ለኢቦላ በከፍተኛ ተጋላጭ ዞን ያለበት አልያም ከፍተኛ የመተላለፍ ሁኔታ ያለበት ቦታ ነዉ፡፡
እ.አ.አ ነሐሴ 19 ቀን 2026 የታተመው የሚኒስቴሩ ደንቦብ እንደሚያመልክተው በቀይ ዞን ያሉ ትምህርት ቤቶች የአካል ትምህርትን በጊዜያዊነት “በርቀት ትምህርት” እንደሚተኩ ደንግገዋል፡፡ ይህም በየሁለት ሳምንቱ በሬዲዮ እና በቴሌቪዥን የሚተላለፉ ፕሮግራሞችን እንደሚያካትት ተገልጻል። ነገር ግን በዚህ ሳምንት በኢቱሪ ያሉ ትምህርት ቤቶች እንደተለመደው እንደተከፍቱ የትምህርት ሚኒስቴር ባለስልጣናት አረጋግጠዋል፡፡ ።
በሩዋንዳ የሚደገፉት የኤኤፍሲ/ኤም23 አማፂያን ባለፈው አመት በክልሉ ባካሄዱት ፈጣን ጥቃት በቁጥጥር ስር ባሉ የሰሜን ኪቩ እና ደቡብ ኪቩ ግዛቶችም ትምህርት ቤቶች መከፈታቸዉን የአማፂያን ሀላፊዎች ገልጸዋል። ሀላፊዎቹ በክፍሎች ውስጥ የእጅ መታጠብ እና ማህበራዊ ርቀትን መጠበቅን ግድታ ማድረጋቸዉ ተጠቁሟል፡፡
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 647 |
| 6 | Sin texto... | 2 420 |
| 7 | #ቃለመጠይቅ #ብርሃኑ_ሌንጂሶ(ዶ/ር) የአዲስ ማለዳ እንግዳ ሆነዋል። ዶክተር ብርሃኑ በአካዳሚክ፣ በምርምር፣ በመገናኛ ብዙኃን እና በሕዝብ አገልግሎት ዘርፎች ሰፊ ልምድ ያላቸው የሶሺዮሎጂ ባለሙያ፣ የአደባባይ ምሁር እና የፖሊሲ አውጭ ናቸው።
በልማት ጥናት ላይ ልዩ ትኩረት ያደረጉ የሶሺዮሎጂ ባለሙያ ሲሆን፣ በአምቦ ዩኒቨርሲቲ እና በዓለም አቀፍ የእንስሳት ሀብት ምርምር ተቋም (ILRI) በመሳሰሉ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ውስጥ በማስተማር እና በመሥራት ልምድ አክብተዋል።
“ብሔርተኝነት” የተሰኘ መጽሐፍ በ2016፤ እንዲሁም በቅርቡ ደግሞ “Water: Ethiopia's Gateway to Prosperity” የተሰኘ ሌላ መጽሐፍ ለንባብ አብቅተዋል።
ብርሃኑ በሁለት ክፍል ከአዲስ ማለዳ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ስለብሔርተኝነት፣ ስለሀገረ መንግስት ግንባታና በሌሎች ጉዳዮች ላይ ለተነሳላቸው ጥያቄ ምላሽ ያሉትን ሰጥተዋል።
ክፍል አንዱን በተከታዩ ማስፈንጠሪያ ያገኙታል፦
https://youtu.be/VaoZbGKBJeA?si=X_Njj7gFq8VqBtpi | 3 065 |
| 8 | ሩሲያ በዴንማርክ መከላከያ ኢንዱስትሪ ላይ የማጥፋት ዘመቻ ለማካሄድ እየተዘጋጀች መሆኗን የዴንማርክ የመረጃ ተቋም አስታወቀ
ሐሙስ፣ ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የሩሲያ የመረጃ እና ደህንነት አገልግሎቶች በዴንማርክ የመከላከያ ኢንዱስትሪ ላይ የማጥፋት እና የማውደም ድርጊቶችን ለማካሄድ በንቃት እየተዘጋጁ መሆኑን የዴንማርክ የደህንነትና የመረጃ አገልግሎት ገልጿል ።
አናዶሉ የዴንማርክ የሕዝብ ሚዲያ መረጃን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ የሩሲያ የመረጃ አገልግሎቶች ከዩክሬን ጋር በተያያዙ የመከላከያ ድጋፎች ጋር የዴንማርክ ኩባንያዎች ላይ ሊያካሂዱ የሚችሉትን የማጥፋት ድርጊት እያቀዱ ነው ብሏል ።
የፀረ-መረጃ ሥራ ኃላፊ ኤሚል ግሬስሆልም እንደገለፁት ከሆነ የዴንማርክ ኩባንያዎችም ለተወሰኑ የሩሲያ የጥፋት ዕቅዶች ዒላማ እየሆኑ መሆኑን ጠቁመዋል ። አከውም የሩሲያ የመረጃ አገልግሎቶችም በዴንማርክ የመከላከያ ኢንዱስትሪን ዒላማ ያደረጉ የማጥፋት ድርጊቶችን ለመፈጸም በንቃት እየተንቀሳቀሱ ነው ብለዋል።
ግሬስሆልም ለዴንማርክ ጋዜጣ እንደገለጹት፣ የሀገሪቱ ባለሥልጣናት በዴንማርክ በሚገኙ ኩባንያዎች ላይ ከባድ ጥፋት ለመፈፀም የተዘጋጁ የሩሲያ ዕቅዶችን ለይተው እንዳገኙ በመግለጽ “ይህ አንድ ቀን ወደ ዴንማርክ ሊደርስ የሚችል ስጋት ብቻ አይደለም፣ ዕቅዱ አሁን እየተዘጋጀ መሆኑን በተጨባጭ እያየን ነው” በማለት ተናግረዋል ።
በተጨማሪም የመረጃ ተቋሙ እንዳለው ከሆነ ሩሲያ በማኅበራዊ ሚዲያና ሌሎች የኦንላይን መድረኮችን በመጠቀም ተራ የዴንማርክ ዜጎችን ለመመልመል እየሞከረች እንደሆነ እና ይህም ተጨባጭ መረጃ እንደሆነ ለይቻለሁ ብሏል ።
እነዚህ ሰዎች የማጥፋት ድርጊት ዕቅድ ለማውጣት እንዲያግዝ የኩባንያዎችን ወይም የተቋማትን ፎቶ እንዲያነሱ ያሉ ሥራዎችን ሊሰጣቸው እንደሚችል ተቋሙ ገልጿል።
ግሬስሆልም፣ “ተራ የዴንማርክ ዜጎች ሆን ብለውም ሆነ ሳያውቁ ለሩሲያ የመረጃ አገልግሎቶች እገዛ እንዳያደርጉ አፅንኦት ሰጥተው አሳስበዋል ።
የመርጃ ተቋሙ ከዴንማርክ የመከላከያ መረጃ አገልግሎት እና ከዴንማርክ የማኅበራዊ ዋስትናና ዝግጁነት ኤጀንሲ ጋር በቅርበት እንደሚሠራ ገልጿል።
ተቋሙ በተጨማሪም ስለስጋቱ ያለውን ግምገማ ለፖሊስ ክልሎች በየጊዜው እንደሚያሳውቅ የገለፀ ሲሆን
ግሬስሆልም እንደገለጹት፣ ባለሥልጣናት ለተመረጡ ኩባንያዎችና የኢንዱስትሪ ድርጅቶች ስለስጋቱ በተደጋጋሚ መረጃ ሰጥተዋል፤ ከሌሎች ተቋማት ጋርም በመተባበር የተለያዩ የደህንነት እርምጃዎችን መክረዋል።
የመከላከያ ኢንዱስትሪውም ራሱን ለመጠበቅ “አስፈላጊውን የደህንነት እርምጃ” መውሰድ እንዳለበት ግሬስሆልም አሳስበዋል። ይህ ስጋትም ለህዝብ ይፍ እየተደረገ መሄዱን ተወድሷል።
የዴንማርክ ኢንዱስትሪ ማኅበር በበኩሉ የመረጃ ተቋሙን ግምገማ በቁም ነገር እንደሚወስድና ከሚመለከታቸው ባለሥልጣናት ጋር በቅርበት እንደሚሠራ ገልጿል። የኢንዱስትሪ ማህበሩም ሆነ የሀገሪቱ ባለስልጣናት መጣ የተባለውን ስጋት ለመቋቋም የበለጠ ትክርት እንደሚሻ በማንሳት በመረጋጋት ተመጣጣኝ እርምጃ ያስፈልጋል ብለዋል። በተጨማሪም የደህንነት እና የአደጋ ጊዜ ስርዓቶች ዝግጁነት በትክክል እየሰሩ መሆኑን መፈተሽ እንዳለበት አስጠንቅቀዋል።
የዴንማርክ ዓለም አቀፍ ጥናት ተቋም ከፍተኛ ተመራማሪ ፍሌሚንግ ስፕሊ ድስቦል በብኩሉ የተቋሙን ማስጠንቀቂያ “አሳሳቢ” በማለት ገልጸው ስጋቱ “አዲስ፣ ተጨባጭ እና የተራቀቀ” መሆኑን ተናግረዋል።
የቀድሞው የዴንማርክ የመከላከያ መረጃ አገልግሎት ዋና ተንታኝ ያኮብ ካርስቦ በበኩላቸው የመርጃ ተቋሙ ጉዳዩን በይፋ ለማሳወቅ መወሰኑ የዴንማርክ ባለሥልጣናት የሩሲያን እንቅስቃሴ እንደሚያውቁ ለሩሲያ ለማሳየት የታለመ ሊሆን እንደሚችል መግለፁን ተዘግቧል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 735 |
| 9 | Sin texto... | 2 301 |
| 10 | የከፍተኛ ፍርድ ቤት በኢሕአፓ አመራሮች የዋስትና ጥያቄ እና የፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ላይ ነገ ውሳኔ እንደሚሰጥ ጠበቃቸው ለአዲስ ማለዳ ተናገሩ
ሐሙስ፣ ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በእስር ላይ በሚገኙት የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ)አመራሮች እና አባላት የዋስትና መብት፣ እንዲሁም ፖሊስ ባቀረበው ተጨማሪ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ ጥያቄ ላይ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ነገ ነሐሴ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ውሳኔ እንደሚሰጥ የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ ለአዲስ ማለዳ ገለጹ።
ዛሬ በዋለው ችሎት፤ የፖሊስ የምርመራ ቡድን ከፎረንሲክ እና ቴክኒክ ምርመራዎች ጋር የተያያዙ ውጤቶችን ለማጠናከር፣ ተጨማሪ ምስክሮችን ለመቀበል እና የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶችን በኤግዚቢትነት ለመያዝ በሚል ተጨማሪ የ14 ቀን የምርመራ ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል።
በተጨማሪም ተጠርጣሪዎቹ በዋስ ቢለቀቁ ምስክሮችን ሊደልሉ ወይም ከሀገር ሊሸሹ ይችላሉ የሚል ስጋት ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል።
በሌላ በኩል የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ በሰጡት ምላሽ፣ ፖሊስ ከዚህ ቀደም የቴክኒክ እና የፎረንሲክ ምርመራ ውጤቶችን አቅርቦ በቂ ማስረጃ የተሰበሰበ በመሆኑ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንደማያስፈልገው ተከራክረዋል።
ከሀገር ሊሸሹ ይችላሉ የሚለውን የፖሊስ ስጋት በተመለከተም ተጠርጣሪ አበበ አካሉ ፓስፖርት የሌላቸው መሆኑን፣ ሌሎች ፓስፖርት ያላቸው ቢኖሩ እንኳ ለኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ማሳወቅ እንደሚቻል በመግለጽ ተጠርጣሪዎቹ በዋስትና እንዲለቀቁ ጠይቀዋል።
ፍርድ ቤቱ የሁለቱንም ወገን ክርክር ካዳመጠ በኋላ ፖሊስ የጠየቀውን ተጨማሪ 14 የምርመራ ቀናት መፍቀድ እና ለተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብት መስጠት በሚለው ላይ ውሳኔ ለመስጠት ለነገ ቀጠሮ ሰጥቷል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 742 |
| 11 | Sin texto... | 2 419 |
| 12 | ኢትዮ ቴሌኮም በተያዘው የበጀት ዓመት ትኩረቱን ኢንተርኔት ላይ በማድረግ 295 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ማቀዱን አስታወቀ
ሐሙስ፣ ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
ኢትዮ ቴሌኮም፤ በተያዘው የ2019 ዓ.ም የበጀት ዓመት 295 ቢሊዮን ብር ለመሰብሰብ ያቀደ ሲሆን ፥ ይህም ከፍተኛ የገቢ ድርሻውን የሚይዘው የዳታ እና ኢንተርኔት አገልግሎት እንደሆነ አስታውቋል።
ይህም አጠቃላይ ከሚገኘው ገቢ 34.6 በመቶ የሚያዝ ሲሆን የድምጽ አገልግሎት ደግሞ 20 በመቶ በመያዝ ይከተላል። ተቋሙ ከዚህ በተጨማሪ በበጀት ዓመቱ 83.8 ቢሊዮን ብር ግብር እንደሚከፍል እና ከ43 ቢሊዮን ብር በላይ ለአክሲዮን ባለድርሻ ባለቤቶች እንደሚከፍል አስታውቋል።
ዋና ስራ አስፈፃሚዋ፤ የኔትዎርክ መቆረረጥን ችግር የጠቀሱ ሲሆን ይህም ከቴክኖሎጂው ጋር የተያያዘ መሆኑን አንስተዋል። ደንበኛ ጥሩ የሚባል ኔትዎርክ እንደሚፈልግ ያነሱት ፍሬሕይወት ታምሩ፤ ነገር ግን ቴክኖሎጂው እየዘመነ በመሄዱ የምንጠቀምበት መሳሪያ ጋር አለመናበብ እንደሚፈጥር አንስተዋል።
ከዚህ እተጨማሪም ከዚህ ቀደም የነበረው ተጠቃሚ ኢንተርኔትን የሚጠቀመው ለማውረድ(ዳውንሎድ ለማድረግ) እንደነበር አንስተው አሁን ላይ ግን ለመጫን (ስትሪሚንግ) እየተገለገበት መሆኑን ተናግረዋል።
እንዲሁም 150 ሺህ ደንበኞችን ከኮፐር ወደ ፋይበር እንደሚቀይር ያስታወቀ ሲሆን በዚህ ምክንያት የኢንተርኔት አገልግሎት እንደሚቆራረጥ ተገልጿል።
የተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬይይወት ታምሩ፤ በዛሬው ዕለት የቀጣይ አድማስ ስትራቴጅን ሁለተኛ ዓመት የቢዝነስ እቅድን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡ ሲሆን የደንበኞቹን ቁጥር ደግሞ አሁን ላይ ካለበት 90.1 ሚሊዮን ከ96 ሚሊዮን ለማድረስ እንዳቀደ አንስተዋል።
ከዚህ በተጨማሪም በበጀት ዓመቱ 1,628 አዳዲስ የሞባይል ጣቢያዎች እንደሚገነቡ የገለጹ ሲሆን ፥ አጠቃላይ የሞባይል ጣቢያዎች ብዛት 12,838 እንደሚደርስ ዋና ስራ አስፈጻሚዋ ተናግረዋል። ከእነዚህም መካከል 605 ያህሉ በገጠራማ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገነቡ ናቸው።
ዋና ስራ አስፈጻሚዋ አክለውም የ4ጂ አገልግሎት ተጨማሪ 300 ከተሞችን ተደራሽ በማድረግ የሽፋን መጠኑን 95 በመቶ የሚያደርስ ሲሆን ፥ የ5ጂ አገልግሎት ደግሞ ተጨማሪ 40 ከተሞችን በመሸፈን አጠቃላይ ተጠቃሚ ከተሞችን ቁጥር ወደ 83 ያሳድጋል ብለዋል።
በተጨማሪ 20 ሚሊዮን ደንበኞችን ማስጠቀም የሚችል የዋየርለስ(ገመድ-አልባ) ሞባይል መረብ በመገንባት በአጠቃላይ የ2019 በጀት ሲጠናቀቅ ደንበኞችን የማስተናገድ አቅምን ወደ 135.7 ሚሊዮን ያሳድገዋል ብለዋል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 2 831 |
| 13 | Sin texto... | 2 826 |
| 14 | የኮማንዶ ክፍለ ጦሩ ዝግጁ መሆኑን የክፍለ ጦሩ አዛዥ አስታወቁ
ሐሙስ፣ ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት የኮማንዶ ክፍለ ጦር በማንኛውም ጊዜ የሚሰጠውን ግዳጅ ለመፈፀም ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ።
የኮማንዶ ክፍለ ጦር አዛዥ የሆኑት ኮሎኔል ሰለሞን ፀጋዬ እንደተናገሩት ከሆነ ክፍለ ጦሩ በቅርቡ “የጥፋት ኃይሎችን በመመንጠር ታላቅ ድል” አስመዝግቧል ብለዋል።
አክለውም የሀገርን ሰላምና ሉዓላዊነት ለማስከበር ያለውን ፅናት ያሳየበት ነው ያሉ ሲሆን ይህም ውጤት “ወታደራዊ ግዳጅን በስኬት መወጣት ብቻ ሳይሆን፣ የአባላቱን የላቀ የውጊያ ጥበብ” በሚገባ ያሳየ ነው ማለታቸውን፣ የመከላከያ ሰራዊት ያጋራው መረጃ ያመለክታል።
በተጨማሪም ክፍለ ጦሩ፤ አስቸጋሪ በሆነ መልክዓ ምድር ውስጥ “የጠላትን የጥፋት መረብ በመስበር እና በመበጣጠስ” በኩል የነበረው ሚና የተጣለበትን ሀገራዊ ግዳጅ የመፈፀም አቅሙን ያረጋገጠበት ነው ብለዋል።
አዛዡ ይህ በውጤት የታጀበ ስምሪት ነው ያሉት ሲሆን የክፍለጦሩ ሠራዊት በአካልና በታክቲክ ከፍተኛ የብቃት ደረጃ እንደደረሰ ያሳያል ሲሉ ተናግረዋል።
በተጨማሪም ኮሎኔሉ የክፍለጦሩ ሠራዊት ዝግጁነት ባረጋገጠበት ወቅት የክፍለ ጦሩ “አስደማሚ ድልና ለአፍታም ቢሆን የማይላላው” ወታደራዊ ዝግጁነት አስተማማኝ የሀገር ደህንነት ዋስትና አረጋግጠዋል ተብሏል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 3 608 |
| 15 | Sin texto... | 3 204 |
| 16 | እስራኤል አሁንም ፍልስጤማውያንን ከጋዛ የማስወጣት እቅድ እንዳላት የመከላከያ ሚኒስትሩ አስታወቁ
ሐሙስ፣ ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የእስራኤል የመከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ፤ ሀገራቸው አሁንም ቢሆን ፍልስጤማውያንን ከጋዛ ለቅቀው እንዲወጡ ወይም የማስወጣት ፍላጎት እንዳላት ተናገሩ።
ሚኒስትሩ፤ ይህ ሳይሆን የቆየበትን ምክንያት ሲያስረዱ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ ዕቅዱን ጊዜያዊ እገዳ ስላደረጉበት እንጂ አልተሰረዘም ብለዋል።
ካትዝ፤ “ዋይ ኔት” የተሸኘ የእስራኤል መገናኛ ብዙኃን ባዘጋጀው ጉባኤ ላይ እንዳሉት ከሆነ ፍልስጤማውያንን ከጋዛ ማስለቀቅ ወይም ማጽዳት “ብቸኛውና ዘላቂው መፍትሔ” ነው።
እንደ ካትዝ ገለጻ ከሆነ፤ እቅዱ በየጊዜው ውይይት እንደሚደረግበት አንስተው፣ እቅዱም ሙሉ በሙሉ አልተሰረዘም ብለዋል። ይህንን ተግባራዊ ለማድረግም የዋሽንግተን ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ያነሱት ካትዝ፤ “ያ ጊዜ ደግሞ ይመጣል”ሲሉ ፍልስጤማውያን ጋዛን ለቅቀው የሚወጡበት ቀን እንዳለ ጠቁመዋል።
እስራኤል ፍልስጤማውያንን በባህር፣ በአየርና በሌሎች መንገዶች ለማስወጣት ዝግጁ ብትሆንም፤ ከጋዛ ጋር የምትዋሰነው ጎረቤት ሀገር ግብፅ የፍልስጤም ተፈናቃዮችን አልቀበልም ማለቷ እና ሌሎች ተቀባይ ሀገራት የአሜሪካን ድጋፍ የሚሹ በመሆናቸው እቅዱ እንዲዘገይ እንዳደረገው ይታወሳል።
የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ይህ እርምጃ “የዘር ማጽዳት ወንጀል ነው” ሲሉ የኮነኑት ሲሆን፤ የአሜሪካው ሴናተር ክሪስ ቫን ሆለን ደግሞ፣ የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር ንግግርን ሀገሪቱ “የዘር ማጽዳት እቅድ እንዳላት ማረጋገጫ ነው” ሲሉ አሜሪካ ከዚህ ድርጊት ጋር ያላትን አጋርነት ማቆም አለባት ሲሉ መናገራቸውን አልጀዚራ ዘግቧል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 3 518 |
| 17 | Sin texto... | 3 233 |
| 18 | ኤል ኒኖ በምስራቅ እና በደቡብ አፍሪካ 162 ሚሊዮን ህጻናት ላይ አደጋ መደቀኑ ተገለፀ
ረቡዕ፣ ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በምስራቅ እና በደቡብ አፍሪካ ከ162 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ህጻናት እየጠነከረ ባለው የ2026/2027 የኤል ኒኖ ክስተት ተጽዕኖ በተጋለጡ አካባቢዎች እየኖሩ ነው ሲል የተባባሩት መንግስታት የህጻናት መርጃ ድርጅት (ዩ.ኒ.ሴፍ) አስጠነቀቀ። ይህም በስፋራው ካሉት አጠቃላይ ህጻናት ከሁለት ሶስተኛ በላይ የሚሆኑት ናቸው ተብሏል።
እየተባባሰ ያለው የመጣው ድርቅ በከፍተኛ ሙቀት እና ጎርፍ የህጻናትን አመጋገብ፣ ጤና፣ የንፁህ ውሃ እና የንፅህና አጠባበቅ ተደራሽነት፣ ትምህርት እና ደህንነትን አደጋ ላይ ይጥላል ተብሏል ። ትንበያዎች እንደሚያሳዩት ከሆነ በጣም ከባድ መዘዞች ከመሰማታቸው በፊት እርምጃ ለመውሰድ ጠባብ ቢሆንም ወሳኝ የሆነ እድል ይሰጣሉ ተብሏል።
“ከኤል ኒኖ የሚያመጣዉ ስጋት እያደገ ሲሆን ለህጻናቱ የሚደርሰው አደጋም ቀድሞውንም ግልጽ ነው” ሲሉ የዩኒሴፍ የምስራቅ እና ደቡብ አፍሪካ ክልላዊ ዳይሬክተር ኤትሌቫ ካዲሊ ተናግረዋል።
በቀጠናዉ ውስጥ ህጻናት የምግብ እና የውሃ እጥረት እንድሁም ከአቅም በላይ የሆነ የጤና አገልግሎት ጫና እና የትምህርት መስተጓጎል እያጋጠማቸው እንደሆነ ገልጸዋል። በተጨማሪም “ከባድ የአየር ንብረት ቀውሶች ህጻናትን እና እነርሱ ላይ መሰረት ያደረጉ ስርዓቶች ላይ እስከ መፈራረስ ድረስ ሊያደርሱ ይችላሉ።” ብለዋል፡፡
በዩኒሴፍ ግምገማ መሰረት በጅቡቲ፣ ኤርትራ፣ ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ማዳጋስካር፣ ማላዊ፣ ሞዛምቢክ፣ ሶማሊያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ሱዳን፣ ኡጋንዳ፣ ዛምቢያ እና ዚምባብዌ ላሉ ህጻናት አስቸኳይ እና ተደራራቢ አደጋዎችን እንዳሉ አመላክቷል።
እንደምሳሌ በሶማሊያ ጎርፍ በጣም አስከፊ ሁኔታ ዉስጥ የሚገኙ እስከ 2.5 ሚሊዮን ሰዎችን በቀጥታ ሊጎዳ ይችላል ብሏል፡፡ ይህም ተጨማሪ መፈናቀልን በማስከተል የህጻናትን የምግብ፣ የጤና እንክብካቤ፣ የንፁህ ውሃ እና የትምህርት ተደራሽነት ላይ ተጽዕኖ ያሳድራል፡፡
ተቋሙ በተለይም በኢትዮጵያ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ህጻናት ከፍተኛ የምግብ እጥረት እና ተጋላጭነት ባለባቸው አካባቢዎች የመጎዳት አላቸው ብሏል። አክሎም በደቡብ ሱዳን ደግሞ ኢል ኒኖ ድርቅ፣ ከፍተኛ ሙቀት እና አካባቢያዊ ጎርፍን ጨምሮ የምግብ እጥረትን አልያም የተመጣጠነ ምግብ እጥረትን የበለጠ ሊባባስ ይችላል ብሏል። ይህም የበሽታ መስፋፋትን ሊጨምሩ እና የረሃብ አደጋን እና ሰፊ መፈናቀልን ሊያባብሱ ይችላሉ ብሏል።
ይሁን እንጂ ከዓለም አቀፍ የሰብዓዊ እርዳታ ዉስጥ ከአንድ በመቶ ያነሰ ለቅድመ ዝግጅት እርምጃ መዋል እንደሚቻል ተናግሮ ይህም የነፍስ አድን ፣ሰብዓዊ ፍላጎቶችን ለመቀነስ እና በአስቸጋሪ ሁኔታ ዉስጥ የተገኙ ውጤቶችን ለመጠበቅ ቁልፍ ሚና ይኖረዋል ተብሏል፡፡
ዩኒሴፍ 13 ቅድሚያ በተሰጣቸው ሀገሮች ለህጻናት እና ቤተሰቦች ቅድመ ዝግጅት እና ህይወት አድን እርዳታ ለማድረስ በነባሩ እ.አ.አ በ2026 ለህጻናት ድጋፍ የሚዉል 173 ሚሊዮን ዶላር አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ ያስፈልገኛል ብሏል፡፡
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 3 922 |
| 19 | Sin texto... | 3 457 |
| 20 | ተጠርጣሪ ጋዜጠኛ ታደሠ ዳኛቸው የዋስትና መብቱ እንዲከበር ሊጠይቁ እንደሆነ ጠበቃቸው ለአዲስ ማለዳ ገለጹ
ረቡዕ፣ ነሐሴ 27 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
የኤን.ቢ.ሲ ጋዜጠኛው ታደሠ ዳኛቸው ምክንያቱ በውል ባልታወቀ ጉዳይ እንደታሠረ አዲስ ማለዳ የጋዜጠኛውን ባለቤት አነጋግራ እንደዘገበች ይታወሳል ።
በዚሁ መሠረትም አዲስ ማለዳ የጋዜጠኛውን ጠበቃ ያነጋገረች ሲሆን ጠበቃው እንዳሉትም ጋዜጠኛው የታሠረበትም ምክንያት “ፍሬ አልባ ነው” ያሉ ሲሆን ሁነቱንም ሲገልፁት ግልፅ የሆነ ምክንያት የለም ብለዋል ።
ሆኖም ፖሊስ ጋዜጠኛውን በተመለከተ ምርመራ እያደረገ እንደሆነ እና ፍርድ ቤትም ለምርመራ ጊዜ 11 ቀናትን በመስጠት ለጳጉሜ 2 ቀን ቀጠሮ መሠጠቱን ጠበቃው ተናግረዋል ።
ፍርድ ቤቱ ቀጠሮ በሰጠበት ቀን ጋዜጠኛው ከእስር እንዲወጣ እና የዋስትና መብቱ እንዲጠበቅ ለማድረግ እንዳሰቡ ጠበቃ ሀይሉ ታደሠ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል ።
ጋዜጠኛ ታደሠ ዳኛቸው የታሠረው በጥርጣሬ ደረጃ እንጂ በግልፅ ይህ ነው የተባለ ነገር አለመኖሩንም ጭምር ጠበቃው ተናግረዋል ።
ሆኖም በጳጉሜ ሁለት የተቀጠረው ቀጠሮ ላይ ፖሊስ ምርመራውን ጨርሶ ውጤት ያቀርባል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልፀዋል ።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA | 4 000 |
