ch
Feedback
ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

前往频道在 Telegram

በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡

显示更多

📈 Telegram 频道 ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ 的分析概览

频道 ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (@beteafework) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 54 121 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 994,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 584

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 54 121 名订阅者。

根据 30 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 719,过去 24 小时变化为 3,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 21.86%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.85% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 11 826 次浏览,首日通常累积 4 788 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 196

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡

凭借高频更新(最新数据采集于 01 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

54 121
订阅者
+324 小时
+967
+71930

数据加载中...

吸引订阅者
七月 '26
七月 '26
+30
在3个频道中
六月 '26
+809
在29个频道中
Get PRO
五月 '26
+1 053
在45个频道中
Get PRO
四月 '26
+1 078
在68个频道中
Get PRO
三月 '26
+664
在42个频道中
Get PRO
二月 '26
+1 024
在54个频道中
Get PRO
一月 '26
+584
在42个频道中
Get PRO
十二月 '25
+850
在42个频道中
Get PRO
十一月 '25
+706
在58个频道中
Get PRO
十月 '25
+669
在64个频道中
Get PRO
九月 '25
+395
在61个频道中
Get PRO
八月 '25
+676
在49个频道中
Get PRO
七月 '25
+724
在68个频道中
Get PRO
六月 '25
+433
在39个频道中
Get PRO
五月 '25
+523
在12个频道中
Get PRO
四月 '25
+1 215
在59个频道中
Get PRO
三月 '25
+1 654
在82个频道中
Get PRO
二月 '25
+1 022
在38个频道中
Get PRO
一月 '25
+2 106
在70个频道中
Get PRO
十二月 '24
+2 118
在57个频道中
Get PRO
十一月 '24
+2 209
在74个频道中
Get PRO
十月 '24
+1 841
在92个频道中
Get PRO
九月 '24
+1 381
在89个频道中
Get PRO
八月 '24
+1 550
在51个频道中
Get PRO
七月 '24
+475
在15个频道中
Get PRO
六月 '24
+517
在18个频道中
Get PRO
五月 '24
+989
在26个频道中
Get PRO
四月 '24
+875
在26个频道中
Get PRO
三月 '24
+998
在20个频道中
Get PRO
二月 '24
+335
在14个频道中
Get PRO
一月 '24
+422
在12个频道中
Get PRO
十二月 '23
+326
在19个频道中
Get PRO
十一月 '23
+282
在11个频道中
Get PRO
十月 '23
+148
在5个频道中
Get PRO
九月 '23
+172
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+174
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+498
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+525
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+546
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+617
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+367
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+500
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+504
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+307
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+286
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+296
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+440
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+380
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+680
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+378
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+443
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+514
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+395
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+245
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+222
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+203
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+254
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+390
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+409
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+461
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+594
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+684
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+622
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+789
在0个频道中
Get PRO
三月 '21
+719
在0个频道中
Get PRO
二月 '21
+539
在0个频道中
Get PRO
一月 '21
+505
在0个频道中
Get PRO
十二月 '20
+19 882
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
01 七月+30
频道帖子
ሰላም ቤተሰቦች ➛ 1 ተአምረ ማርያም ባለ 366ቱ ተአምር ➛ 1 ተአምረ ኢየሱስ እና ➛ 1 ስንክሳር የዓመቱ ➛ 1 ሃይማኖተ አበው ➛ አጣን ➛ ዘቢብ ➛ የሰም ጧፍ ለእመቤታችን ቤተክርስቲያን ያስፈልጋል! ፈቃደኛ የሆነ በውስጥ መስመር @natansolo አናግሩን።

2
"የተወደዳችሁ አሁንም ዕድል ስላላችሁ ወደ ክርስቶስ በተሰበረ ልብ በንስሐ ተመለሱ።" አባ ሙሴ ጸሊም
1 086
3
"አንድ ሰው የራሱን ኃጢአት ሁልጊዜ በፊቱ የሚያይና የሚመረምር ከሆነ፣ በሌላው ሰው ላይ ያለውን ድክመትና ኃጢአት ለማየት አይፈልግም። የገዛ ራሱን ሙት (ኃጢአቱን) ትቶ የሌላውን ሰው ሙት ሊቀብር የ
"አንድ ሰው የራሱን ኃጢአት ሁልጊዜ በፊቱ የሚያይና የሚመረምር ከሆነ፣ በሌላው ሰው ላይ ያለውን ድክመትና ኃጢአት ለማየት አይፈልግም። የገዛ ራሱን ሙት (ኃጢአቱን) ትቶ የሌላውን ሰው ሙት ሊቀብር የሚሄድ ሰው የለምና። አንተም የራስህን በደል እያሰብህ የምታለቅስ ከሆነ፣ በሌላው ወንድምህ ላይ ለመፍረድና እርሱን ለማሳነስ ጊዜ አይኖርህም። በሰዎች ላይ ከመፍረድ ይልቅ ራስን መውቀስ፣ ከጥላቻ ይልቅ ፍቅርን መምረጥ የእውነተኛ ክርስትና መጀመሪያ ነው።"      አባ ሙሴ ጸሊም #ሰኔ_24 አባ ሙሴ ጸሊም (ጥቁሩ ሙሴ) አስቀድሞ ኃይለኛ፣ ነፍሰ ገዳይ፣ ቀማኛና የጣዖት አምላኪ የነበረ ኋላም የእግዚአብሔርን መንገድ ፍለጋ ወደ አስቄጥስ ገዳም በመሄድ ንስሐ ገብቶ የመነኰሳት አባት (አበ ምኔት) ለመሆን የበቃ የታላቅ አባት ነው። እርሱም በጸሎቱ ዝናምን ከሰማይ የሚያዘንብ፣ በትሕትናውና በጽኑዕ ገድሉ የከበረና "በሰይፍ የገደለ በሰይፍ ይገደላል" የሚለውን የጌታ ቃል ለመፈጸም የበርበር ሰዎችን ሰይፍ በደስታ በመቀበል ሰኔ 24 ቀን ከሰባት መነኰሳት ጋር በሰማዕትነት አርፏል፣ ቅዱስ ሙሴ ጸሊም የንስሐ ኃይል ምን ያህል ታላቅ እንደሆነና ሰውን ከኃጢአት ጥልቁ አውጥቶ ወደ ቅድስና ማማ እንደሚያደርስ ያየንበት አባት ነው። በረከቱ ይደርብን!
4 458
4
"ፈተና ሲገጥመን ውስጣችን ሊረበሽ ወይም በቀቢጸ ተስፋ ሊያዝ አይገባውም፡፡ ወርቅን የሚያነጥር ሰው በእሳት ውስጥ የጨመራትን የወርቅ ቅንጣት እዚያ ውስጥ ምን ያህል ጊዜ መቆየት እንዳለባት ያውቃል፤ መቼ ከእሳቱ ሊያወጣት እንደሚገባውም ያውቃል፡፡ እንዲሁ እስከ መጨረሻው በእሳቱ ውስጥ ተጥላ እንድትቀርና በዚያ እንድትቃጠል አይፈቅድም፡፡ እግዚአብሔር ደግሞ ይህን ከወርቅ አንጣሪው በላይ ያውቃል፡፡ መቼ ከርኩሰታችን እንደምንነጻ ያውቃል፡፡ በመኾኑም ራሳችንን በመጣልና ተስፋ በመቁረጥ በክፋት ላይ ክፋት እየጨመርን እንዳንኼድ ሽቶ መቼ ከዚያ ፈተና እንደሚያወጣን ያውቃል፡፡ ስለዚህ ድንገት ያላሰብነው ነገር ቢገጥመን በፍጹም የምናማርር፣ ወይም ተስፋ የምንቆርጥ ልንኾን አይገባንም፡፡ ከዚህ ይልቅ የእነዚህ ነገሮች ምንነትን የሚያውቅ እግዚአብሔርን መጠበቅ፣ እርሱ እስከ ፈቀደው ጊዜ ድረስም ልቡናችንን በእሳት እንዲፈተን ማድረግ ይገባናል። ምክንያቱም ይህ ነገር በእኛ ላይ እንዲኾን (እንዲመጣ) የፈቀደው ለእኛ ጥቅምና በዚያ ውስጥ ኾነን በምናሳየው ጥረት ይበልጥ ሊያከብረን ስለሚወድ ነው፡፡" ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ወደ ኦሎምፒያስ ከላከው መልእክት የተቀነጨበ
5 279
5
"በማዕበል መሀል እንዳለች ታንኳ ልብህ በጭንቀት ስትናወጥ፣ ማዕበሉን ጸጥ ማድረግ ወደሚችለው ወደ ክርስቶስ ፊት ቅረብ። ጭንቀትህ የቱንም ያህል ከባድ ቢሆን፣ የእግዚአብሔር ቸርነት ግን ከዚያ ይበልጣል። እርሱ ስለ አንተ የሚያስብ አባት ነውና ነገ ምን እሆናለሁ ብለህ አትጨነቅ፤ የዛሬን ቀን የሰጠህ አምላክ የነገውንም ማዕበል በጥበቡ ያሳልፈዋል። ብዙ ጊዜ የምንጨነቀው ሁሉንም ነገር በራሳችን አቅም ለመወጣት ስንሞክር ነው፤ ነገር ግን ሸክምህን በጸሎት ወደ እርሱ ስትጥለው፣ እርሱ በልብህ ውስጥ ሰላምን ያሳድራል። ቅዱሳን ሐዋርያት በዓለም ሳሉ ብዙ መከራና ጭንቀት ገጥሟቸዋል፤ ነገር ግን ልባቸው አልፈራም፤ ምክንያቱም ከእነርሱ ጋር ያለው ጌታ ከዓለም ሁሉ እንደሚበልጥ ያውቁ ነበርና። አንተም ዛሬ ሸክምህን ለእርሱ ስጥ፤ እርሱ ደግሞ ዕረፍትን ይሰጥሃል።" (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
6 445
6
የድጋፍ ጥሪ "ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።" ላለፉት ዓመታት በፈለገ ሰላም ሰንበት ትምህርት ቤት በልዩ ልዩ የአገልግሎት ክፍሎች በትጋት ሲያገለግል የቆየው ወንድማችን ዲ/ን እሸቱ ኤፍሬም (ሀብተ ወልድ)፤ አሁን ላይ ለበለጠና ለተሻለ አገልግሎት ለማዘጋጀት አስቧል። በመሆኑም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በታላቁ የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለመማር ተመዝግቧል። የወንድማችን አጠቃላይ የትምህርት ክፍያ (Tuition Fee) በስፖንሰር የተሸፈነ ሲሆን፣ ትምህርቱን በጉባኤ ቤት ሆኖ ለመከታተል ግን የዓመት ቀለብ (የምግብ ወጪ) ድጋፍ ያስፈልገዋል። ይህንን በጎ አገልግሎት በመረዳት ወንድማችንን በዕውቀት ተኮትኩቶ ለቤተ ክርስቲያን እንዲተርፍ ማገዝ የምትፈልጉ ወንድሞችና እህቶች በሚከተለው አካውንት እንድታግዙት ከታላቅ አክብሮት ጋር በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ➛ ለእሸቱ ኤፍሬም                1000327329492 ስልክ ➛ 0985650289 "እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፥ እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና።" (፪ኛ ቆሮ ፱፥፯)
5 669
7
እንደ ኃጢአት አዋራጅ የለም እንደ ኃጢአት አዋራጅ የለም፡፡ ኃጢአትን የሚያደርግ ሰው በሐፍረት ካባ ብቻ የሚከናነብ አይደለም፤ አስቀድሞ ከነበረው ማስተዋልና ማገናዘብም ይዋረዳል እንጂ፡፡ ይህንንም ለመረዳት የአዳም የቀድሞ ክብሩን ማሰብ እንቸችላለን፡፡ ዳግመኛም ኃጢአትን ከሠራ በኋላ ያገኘውን ውርደት እንመልከተው፡፡ “በሰርክ ጊዜ ጌታ በገነት ውስጥ ድምፀ ሰናኮ ብእሲ እያሰማ ወደነርሱ ሲመጣ በሰሙ ጊዜ አዳምና ሔዋን ከእግዚአብሔር ፊት በገነት ዕንጨት መካከል ተሰወሩ” (ዘፍ.3፥8)፡፡ በዚህስ አዳም እንደ ምን ባለ ውርደት እንደ ተያዘ ታስተውላላችሁን? ምሉእ በኩለሄ ከኾነው፣ ፍጥረታትን ካለ መኖር ወደ መኖር ካመጣው፤ የተሰወረውን ኹሉ ከሚያውቀው፤ የሰውን ልቡና የፈጠረና በኀልዮ የሠሩትን ዐውቆ ከሚፈርደው (መዝ.33፥15)፤ ልብ ያሰበውን ኩላሊት ያጤሰውን መርምሮ ከሚያውቀው (መዝ.7፥9)፤ ልቡናችን ያሰበውን ከሚያውቀው (መዝ.44፥21) ከእግዚአብሔር ሊሸሸግ መውደዱ ከማወቅ ወደ ድንቁርና ከክብር ወደ ኃሣር እንደ ኼደ ያመለክታል፡፡ እኛም ኃጢአት ስንሠራ እንደዚህ ነው፡፡ መሸሸግ ባንችል እንኳን መሰወርን እንሻለን፡፡ ይህን ማድረጋችንም በኃጢአታችን ምክንያት ክብራችን እንደ ምን እንዳጣን፤ ሐፍረታችንን መሸፈንም እንደ ምን እንዳቃተን ያስረዳል፡፡ ነገር ግን ኃጢአትን የሠራ ሰው እንኳንስ በረኻ በኾነች በዚህች ምድር በገነት መካከልም መደበቅ አይችልም፡፡ ("የክርስቲያን መከራ እና ሌሎች" በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ገጽ 81 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)
5 782
8
ማስታወቂያ ፈጣን፣ አስተማማኝ እና ህጋዊ የዕቃ ማድረስ አገልግሎት! በልዩ ባስ ክፍለሀገር ተሳፋሪ መኪና ላይ የምሰራ አስተናጋጅ ነኝ። ህጋዊ ደረሰኝ ያላቸውን የእርስዎን ውድ ዕቃዎች፣ መልዕክቶች እና ፖስታዎች ካሉበት ቦታ ተቀብለን በታማኝነት እና በፍጥነት ወደ መዳረሻቸው እናደርሳለን! የምንሰጣቸው አገልግሎቶች ➛ ማናቸውንም መልዕክቶች እና ፖስታዎች ማድረስ ➛ ማንኛውንም ዓይነት ዕቃዎች በታማኝነት ማጓጓዝ የምንደርስባቸው ዋና ዋና መስመሮች እና ከተሞች 1ኛ መስመር (ወደ መቀሌ)፦ ቆቦ ➔ አላማጣ ➔ መሆኒ ➔ አቢኣዲ ➔ አድዋ ➔ ሽሬ ... እና መቀሌ 2ኛ መስመር (ወደ ሞያሌ)፦ ሀዋሳ ➔ ዲላ ➔ ሀገረ ማርያም ➔ ቡሌሆራ ➔ ያቤሎ ➔ ሜጋ ... እና ሞያሌ 3ኛ መስመር፦ ነቀምቴ ➔ ደምቢዶሎ ... 4ኛ መስመር፦ ድሬዳዋ 5ኛ መስመር፦ ወላይታ ➔ አርባ ምንጭ 6ኛ መስመር፦ ጅማ እና ሚዛን 7ኛ መስመር፦ ደብረ ብርሃን ➛ ደሴ ➛ ወልድያ 8ኛ መስመር፦ ደብረ ማርቆስ ➛ ባህር ዳር➛ ጎንደር➛ ደብረ ታቦር "ታማኝነት መለያችን ነው፤ ዕቃዎትን ካሰቡበት እናደርሳለን!" አሁኑኑ ስልክ ቁጥሮች ይደውሉልን! 0921799534 0907851185 0786799534
5 694
9
አንዱ ፈረንጅ ነው አሉ... አንድ ጥናት ሊያጠና ወደ ኢትዮጵያ ይመጣል፤ ጥናቱን እያጠናም ኢትዮጵያውያን ለድንግል ማርያም ያለን ፍቅር በጣም ያስገርመው ነበር፤ በየሔደበት የሀገራችን ክፍል ኹሉ ሕጻና
አንዱ ፈረንጅ ነው አሉ... አንድ ጥናት ሊያጠና ወደ ኢትዮጵያ ይመጣል፤ ጥናቱን እያጠናም ኢትዮጵያውያን ለድንግል ማርያም ያለን ፍቅር በጣም ያስገርመው ነበር፤ በየሔደበት የሀገራችን ክፍል ኹሉ ሕጻናት በጨዋታ መኻል 'የማርያም መንገድ ስጠኝ' ሲሉ፣ እናቶች ሲወልዱ 'ማርያም ማርያም' ሲሉ፣ የወላድ ጠያቂዎችም 'እንኳን ማርያም ማረችሽ' ሲሉ፣ የኔ ቢጤ ሲለምን 'በእንተ ማርያም' ሲል፣ ሰውነት ላይ ያለ ጥቁር ምልክት ሲታይ 'ማርያም የሳመችኝ' ተብሎ ሲገለጽ....ይሰማል  ያያል እናም 'እነዚህ ሰዎች ለማርያም ምን ያክል ፍቅር ቢኖራቸው ነው' እንዲህ የሚሉትና የሚያደርጉት ብሎ ተደነቀ። በመጨረሻም ጥናቱን አጠቃሎ ወደ መጣበት ሲመለስ፦ "ኢትዮጵያውያን ከአካል ክፍላቸው አንዱ ቦታ ቢቆረጥና ቢደማ በደማቸው ውስጥ 'ማርያም ማርያም ማርያም' የሚል ጽሑፍ ተጽፎ ይገኛል" አለ ይባላል፡፡
6 708
10
ለነፍሳችን ኹለተኛዋ ነፍስ ወዳጄ ሆይ! እምነት ለነፍስህ ኹለተኛዋ ነፍስ እንደሆነች መርምርና እወቅ፡፡ ሥጋ በነፍስ እንድትቆም የነፍስም በሕይወት መኖር በእምነትህ ላይ የተንጠለጠለ ነው፡፡ እምነትህን ብትክድ ወይም ከራስህ ብታርቃት ነፍስህ ምውት ትሆናለች፡፡ በዚህም መሠረት የሚሞት ሥጋችን በነፍስ ላይ ጥገኛ እንደሆነች ነፍሳችንም በእምነት ላይ ጥገኛ ናት፡፡ እምነትም በእግዚአብሔር አብና በመንፈስ ቅዱስ ሕያዋን ባደረገን በእውነተኛ ልጁ ላይ ጥገኛ ናት፡፡ በዚህም እውነት ሰው ነፍሱን በሰማያት ካሉት ጋር ያገናኛታል፡፡ እንዲህ ዓይነት ሰው በነፍሱ በሕይወት ይኖራል፡፡ በሥጋ ሰውነቱም ያያል ይመለከታል። እንዲሁ እኛም በእምነት በፍቅርና በጥበብ የእግዚአብሔር መልክ ገንዘባችን አድርገን ከመለኮቱ ተካፋይ እንሆናለህ። ስለዚህም በነፍሳችን የሞትን እንዳንሆን ይህን ድንቅ የሆነ ማሰሪያ እንዳንበጥስ ወይም ነፍሳችን ከእምነት ባዶ እንዳናደርጋት እንጠቀቅ፡፡ ጌታችን ይህን አስመልከቶ እንዲህ ብሎ አስተምሮናልና “ሙታናቸውንም እንዲቀብሩ ሙታንን ተዋቸው።” (ማቴ.8፥22) ይህ አየር በእኛ ላይ በንፍሐት እፍ ሳይባልብን ሥጋችንን በሕይወት የሚያቆያት ነው፡፡ የምንተነፍሰው አየር የተቋረጠበት ሰው ሕይወቱ ትቆማለች፤ በሥጋው የሞተ ይሆናል፡፡ እንዲሁ ራሱን ከእውነተኛ ልጁ ከእግዚአብሔር ቃል የለየ ሰውም በነፍሱ የሞተ ይሆናል፡፡ እኔ ሕይወትን የሚሰጠው የእውነተኛ ልጁን ምስክርነት ሳያገኝ ለሞተ ሰው አዝናለሁ፡፡ ልክ እንደ ውቅያኖስ እርሱ የሕይወት ምንጭ ነውና፡፡ እርሱ ሰው በመሆን ፈቃዱን እንድናውቀው አደረገን፡፡ ሞትን ድል ለመንሳት ሲል እጅግ መጠማቱ ለእኛ ያለውን ፍቅር አረጋገጠልን። መጽሐፍ ቅዱስ በእምነት ጻድቅ የሆነ እርሱ በሕይወት እንዲኖር አትሞልናል፡፡ እውነት የተባለው እርሱ ራሱን ዋናው ሥር በማድረግ በጎ ምግባራትን ደግሞ በእርሱ ላይ ባለን እምነት ላይ የተንጠለጠሉ ፍሬዎች አደረጋቸው፡፡ እነሆ መልካም ምግባሮቻችን በእውነትኛው ግንድ በእርሱ ቅርንጫፎች ሆነው በዝተው ፍሬን ይሠጣሉ፡፡ እነሆ በሚታይ ምሳሌ የተሰወሩ ምሥጢራት በዓይን እንደሚታዩ ሆነው ተገለጡ። ሥጋ ልክ ትርፉን ለማግኘት እንደጓጓ ነጋዴ ነው እንዲሁ ሕሊናም ከእርሱ ጋር በእምነትን በሕይወት መርከብ ትርፍን እንደሚሰብስብ መርከበኛ ነው፡፡ ሥጋ በነፍስ እንዲቆም ነፍስም ምንም እንኳ ሕያዊት ብትሆን ያለ በጎ ሥራ ሕይወት እንደሌላት፤ ነፍስ በእምነት በሚሠራ የጽድቅ ሥራ በሕይወት እንደምትኖር መጽሐፍ ቅዱስ መስክሮልናል፡፡ በክርስቶስ አምኖ የነበረው አልዓዛር ለዚህ ለምንለው እውነተኛ ምስክር ይሆን ዘንድ ሕያው ሆኖ ተነሣ፡፡ እርሱ ከመቃብር በጠራው በጌታችን ቃል ሕይወቱ ጣፍጣ ሕያው ሆነ፡፡ እንዲሁ በአልዓዛር ምሳሌ አህዛብ በሕቡዕ በሚኖረው ሕይወት ሕያዋን ሆኑ፡፡ በተቃራኒው ደግሞ በአይሁድ ሥራ ምሳሌ ወንበዴው ራሱን ሰቀለ እንደ ውርስ አድርጎ ሞቱን ለጸሐፍት ፈሪሳዊያን ተወላቸው፡፡ እግዚአብሔር አምላክ በእርሱ ላይ ባለን እምነት በመንፈስ ቅዱስ ሕያዋን ሆነን እምነታችንን ጠብቀን እንድንኖር ይርዳን፡፡ (ቅዱስ ኤፍሬም - ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ)
7 022
11
የሕይወትህን መንገድ ወደ እግዚአብሔር ብታደርግ ያን ጊዜ እውነተኛውን እረፍት ታገኛለህ። አባ ሙሴ ጸሊም
6 411
12
没有文字...
8 171
13
#ሰኔ_21 #እመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም (ህንጸተ ቤተክርስቲያን) ሰኔ ሃያ አንድ በዚች ዕለት የአዳምና የዘሩ ድኅነት የተደረገባት አምላክን የወለደች የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የታላቁ በዓል መታሰቢያና በዓለም ሁሉ የቤተ ክርስቲያን መታነፅ መታሰቢያ ነው። ከሁሉ አስቀድሞ ያቺ ቤተ ክርስቲያን በሐዋርያት ዘመን ብቻዋን ታነፀች። ይኸውም ጳውሎስና በርናባስ በአሕዛብ ውስጥ በሰበኩ ጊዜ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ ከሰዎች ቤቶች በቀር ቅዱስ ቊርባንን የሚቀበሉበት ቤተ ክርስቲያንም አልነበራቸውም ነበር። ስለዚህም ወደ ጴጥሮስና ወደ ሐዋርያት ሁሉ ስለ ቤተ ክርስቲያን መታነፅ ጉዳይ እየለመኑ መልእክትን ላኩ። ሐዋርያትም እንዲህ ብለው መለሱላቸው ክብር ይግባውና ያለ ጌታችን ፈቃድ እኛ ምንም ምን አንሠራም። ነገር ግን የምንሠራውን እስኪያስረዳን ድረስ ወደ እግዚአብሔር እየጸለዩና እየማለዱ አንድ ሱባኤ ይጾሙ ዘንድ ወደ ሃይማኖት የተመለሱ አሕዛብን እዘዙአቸው እንዲህም አዘዙአቸው። በሱባዔውም ፍጻሜ ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገለጸላቸው ሐዋርያትንም ሁሉ ከየአገሮች ሁሉ እስከ ፊልጵስዮስ በደመና ሰበሰባቸው ከእርሳቸውም ጋር ጳውሎስና በርናባስ ነበሩ ጌታችንም ባረካቸው እንዲህም ብሎ ነገራቸው "ይቺ ዕለት በእናቴ በማርያም ስም በአራቱ ማእዘነ ዓለም አብያተ ክርስቲያናት እንድታንፁ የፈቀድኩባት ናት።" ይህንንም ብሎ ከከተማዋ በስተ ምሥራቅ በኲል አወጣቸው የቤተ ክርስቲያኒቱንም ቦታና መሠረቷን ወሰነላቸው ከእርሳቸውም ጋራ የእግዚአብሔር ኃይል ነበረ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሕንፃዋ እስከ ተፈፀመ ድረስ ደንጊያዎች በሐዋርያት እጆች ውስጥ ይለመልሙ ነበረ ጌታችንም ነዋየ ቅድሳቷን አልባሳትዋንና መሠዊያዋን አዘጋጀ። ከዚህ በኋላ ጌታችን እጁን በጴጥሮስ ራስ ላይ ጭኖ በአራቱ ማእዘነ ዓለም ውስጥ "አርሳይሮስ" ብሎ ሾመው ይህም "ሊቀ ጳጳሳት" ማለት ነው። ለሐዋርያት አለቃ ጴጥሮስ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የጳጳሳት አለቃ ይሆን ዘንድ ይገባዋል ይገባዋል ይገባዋል እያሉ ሰማያውያን መላእክትና ምድራውያን ሰዎች ሦስት ጊዜ አሰምተው ተናገሩ። ከዚህም በኋላ ጌታችን ሐዋርያትን የቊርባኑን ቅዳሴ ሥርዓት ያከናውኑ ዘንድ ለሕዝቡም ሥጋውን ደሙን ያቀብሏቸው ዘንድ አዘዛቸው እንዲህም የሚል አለ ራሱ መድኃኒታችን ቀድሶ ሥጋውንና ደሙን ለሐዋርያት አቀበላቸው። እንዲህም አላቸው በዚች ቀን የእጃቸውን ሥራ እንዳይሠሩ ሕዝቡን ሁሉ እዘዙአቸው ይኸውም በሰኔ ወር ሃያ አንድ ቀን ነው። ከዚህም በኋላ መድኃኒታችን ከእርሳቸው ዘንድ በታላቅ ክብር ወደ ሰማያት ዐረገ። ከዚያችም ቀን ጀመሮ አባቶቻችን ሐዋርያት በዓለሙ ሁሉ ውስጥ አምላክን በወለደች በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም ቤተ ክርስቲያን የሚያሳንፁ ሆኑ። በቂሣርያው ሊቀ ጳጳሳት በባስልዮስ ዘመን እንዲህ ሆነ በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ስም ቤተ ክርስቲያን በሠራ ጊዜ በውስጡ የእመቤታችን የማርያምን ሥዕል ይሥልበት ዘንድ ሠሌዳ ፈለገ ሰዎችም በአንድ ባለጸጋ ዘንድ ስለ አለ አንድ መልካም ሠሌዳ ነገሩት። ቅዱስ ባስልዮስም ሠሌዳውን እንዲሰጠው ወደ ባለጸጋው ላከ ባለጸጋውም ይህ ሠሌዳ ለልጆቼ ነው አለ እንጂ ፈቃደኛ አልሆነም። ከዚያም አልፎ በመድፈር በእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ላይ የስድብ ቃል ተናገረ ወዲያውኑም በድንገት ወድቆ ሞተ ልጆቹም ፈሩ ያንንም ሠሌዳ ከብዙ ወርቅና እንቊ ጋራ ወደ ቅዱስ ባስልዮስ አምጥተው የአባታቸውን በደል ያቃልልለት ዘንድ ለመኑት። ቅዱስ ባስልዮስም ያንን ሠሌዳ ወስዶ የእመቤታችንን ሥዕል ይሥልበት ዘንድ ለሠዓሊ ሰጠው። እመቤታችንም ቅድስት ድንግል ማርያም በሌሊት ራእይ ለቅዱስ ባስልዮስ ተገለጸችለት ሥዕሏንም በዚያ ሠሌዳ ላይ እንዳይሥል ከለከለችው። ከዐመፀኛ ሰው እጅ ወስዶታልና። እጅግም ያማረ የእመቤታችን ሥዕሏ የተሣለበት የሁለት ደናግልም ሥዕል ያንዲቱ በቀኝ ያንዲቱ በግራ ሆኖ የተሣለበት ቀይ ሠሌዳ ያለበትን ቦታ ነገረችው። ቅዱስ ባስልዮስም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ወደ አመለከተችው ወደዚያ ቦታ ሔደ ያንንም ሠሌዳ አገኘው ወደዚያች ቤተ ክርስቲያንም በታላቅ ደስታ አመጣው። ከዚህም በኋላ ዳግመኛ በአንድ ጣዖት ቤት ሁለት ምሰሶዎች እንዳሉ አስረዳቸው እነርሱንም አምጥቶ በመቅደሱ ፊት ለፊት እንዲአቆማቸው በላያቸውም ሥዕሏን እንዲያኖር አዘዘችው። ቅዱስ ባስልዮስም እነዚያን ምሰሶዎች ያመጣቸው ዘንድ ሔደ መሠርያኑም ሊከለክሉት ፈለጉ ጌታችንም ኃይላቸውን ደመሰሰ እነዚያንም ምሰሶዎች አምጥቶ በቤተ መቅደሱ ፊት ለፊት አቆማቸው በላያቸውም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕሏን አስቀመጠ እግዚአብሔርም ከእነዚያ ምሰሶዎች በታች የውኃ ምንጭ አፈለቀ በውስጥዋም የሚታጠብ ሁሉ ከአለበት ደዌ ሁሉ የሚድን ሆነ። እንዲሁም ከእመቤታችን ማርያም ሥዕል በሽተኞችን ሁሉ የሚፈውስ የዘይት ቅባት ፈሰሰ ይህ ሁሉ የሆነ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን በከበረችበት በሰኔ ወር በሃያ አንድ ቀን ነው። በዚያችም ቀን እንዲህ ሆነ አንዲት ሴት መጥታ ታጠበች ወዲያውኑም ሁለመናዋ በለምጽ ተሸፈነ ቅዱስ ባስልዮስም ወደርሱ አስቀርቦ በእርሷ ላይ የሆነውን ጠየቃት እርሷም የእኅቷን ባል እንደወደደችና እኅቷን በመርዝ ገድላ እንዳገባችው ነገረችው። ቅዱስ ባስልዮስም ታላላቅ ሦስት ኃጢአቶችን ሠራሽ ግን ወደ እግዚአብሔር ንስሐ ግቢ ምንአልባት በደልሽን ይቅር ይልሽ እንደ ሆነ አላት በዚያን ጊዜም ምድር ተሠንጥቃ እንደ ዳታን ዋጠቻት እርሷ የረከሰች ስትሆን ወደ ቤተ ክርስቲያን መግባትን ደፍራለችና። እኛ ሁላችን የክርስቲያን ወገኖች አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለከበረች ድንግል ማርያም ለመታሰቢያዋ መንፈሳዊ በዓልን ልናደርግ ይገባናል ሰለ እርሷ ለአዳምና ለሁላችን ለልጆቹ ድኅነት ሆኖአልና ይህንንም በዓል ለማድረግ የሚተጋ የተመሰገነ ነው። እርሷን ለመረጣትና ለወደዳት በሥጋም እንድትወልደው ላደረግ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእርሷ በእመቤታችን ድንግል ማርያም አማላጅነት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን ። (#ስንክሳር_ዘወርኀ_ሰኔ )
8 444
14
ከእራት በኋላ  ያለው ጊዜ የምስጋና ጊዜ ነው፡፡ ምስጋናን የሚያቀርብ ደግሞ ንቁና የተረጋጋ ይሆናል፡፡ ከእራት በኋላ ወደ ጸሎት እንጂ ወደ መኝታ አንሂድ፡፡ ያለበለዚያ ግን በደመ ነፍስ ከሚመሩት አውሬዎች የበለጠ በደመ ነፍስ የምንመራ እንሆናለን፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
6 706
15
የድጋፍ ጥሪ "ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።" ላለፉት ዓመታት በፈለገ ሰላም ሰንበት ትምህርት ቤት በልዩ ልዩ የአገልግሎት ክፍሎች በትጋት ሲያገለግል የቆየው ወንድማችን ዲ/ን እሸቱ ኤፍሬም (ሀብተ ወልድ)፤ አሁን ላይ ለበለጠና ለተሻለ አገልግሎት ለማዘጋጀት አስቧል። በመሆኑም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በታላቁ የሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ ለመማር ተመዝግቧል። የወንድማችን አጠቃላይ የትምህርት ክፍያ (Tuition Fee) በስፖንሰር የተሸፈነ ሲሆን፣ ትምህርቱን በጉባኤ ቤት ሆኖ ለመከታተል ግን የዓመት ቀለብ (የምግብ ወጪ) ድጋፍ ያስፈልገዋል። ይህንን በጎ አገልግሎት በመረዳት ወንድማችንን በዕውቀት ተኮትኩቶ ለቤተ ክርስቲያን እንዲተርፍ ማገዝ የምትፈልጉ ወንድሞችና እህቶች በሚከተለው አካውንት እንድታግዙት ከታላቅ አክብሮት ጋር በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን። የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ➛ ለእሸቱ ኤፍሬም                1000327329492 ስልክ ➛ 0985650289 "እያንዳንዱ በልቡ እንዳሰበ ይስጥ፥ እግዚአብሔር በደስታ የሚሰጠውን ይወዳልና።" (፪ኛ ቆሮ ፱፥፯)
8 153
16
የጸሎት ጥበብ -፪ ስለዚህ ከእግዚአብሔር ጋር እንዴት ልንነጋገር እንደሚገባን እንወቅ፡፡ ጸሎት ማድረስ ያለብን እንዴት እንደ ኾነ እንረዳ፡፥ ይህን ለማወቅ ወዶ ቤተ መጻሕፍት መኼድ፤ ወይም ገንዘብ መክፈል፤ ወይም የንግግር ክህሎትን ለመማር ጊዜ መመደብ አያሻንም፡፡ የተገባ ጸሎትን ስማድረስ መሻት ብቻ በቂ ነው፤ ክህሎቱ በራሱ ይመጣልና። በዚህ [መንፈሳዊ] ችሎት ፊት የምትናገረውም ለራስህ ብቻ አይደለም! ለሌሎች ለብዙ ሰዎችም ጭምር ነው እንጂ፡፡ በጸሎት ውስጥ ሊኖር የሚገባው ክህሎትስ ምንድን ነው? የጸሎት ጥበብ፥ ይኸውም፦፡ የተዋረደ ልብና የተሰበረ መንፈስ መያዝ፤ በውሒዘ አንብዕ (በዕንባ ጅረት) መቅረብ፤ ከዚህ ዓለም የኾነውን ምንም ነገር አለመሻት፤ የወዲያኛው ዓለም የኾኑ ነገሮችን (ክብሮችን) መሻት፣ መንፈሳዊ ምግባራትን መለመን፤ እግዚአብሔር በጠላቶቻችን ላይ መዓት እንዲያዘንብ አለመለመን፤ ቂም በቀልን ማራቅ፤ [ሥጋዊ] ሁከትን ኹሉ ከነፍስ ማስወገድ፣፤ በተሰበረ ልብ መቅረብ፣ ትሑት መኾን፤ የውሃትን እጅግ መለማመድ፣ ስለ ሌሉች ሰዎች ስንናገር በጎ በጎውን መናገር፤ ከክፉዎች ኅብረት መለየት፣ የዓለም (የሰው) ኹሉ ጠላት ከኾነው ከዲያብሎስ ጋር ምንም ምን አንድነት አለማድረግ ነው፡፡ የዚህ ዓለም ሕጎች እንኳን ሳይቀሩ አንድ ሰው ስለ ንጉሥ ለሌሎች የሚናገር፤ በተለይም ከንጉሥ ጠላቶች ጋር የሚገናኝ ከኾነ ጽኑ ቅጣት ያገኘዋል፡፡ ስለዚህ አንተም ከእግዚአብሔር ጋር ስለ ራስህና ስለ ሌሎች ስትነጋገር የሰዎች ኹሉ ጠላት ከኾነው ከዲያብሎስ ጋራ ምንም ምን አንድነት ሊኖርህ አይገባም፡፡ ስለዚህ የጸሎትን ጥበብ ገንዘብ አድርግ፡፡ ይህንን ጥበብም (ከቀራጩ) ከመጸብሐዊው ተማር፤ እርሱን መምህር አድርገህ ለመቀበልም አታወላውል፡፡ እርሱ ከአፍአ ሲመረመሩ እዚህ ግባ የማይባሉ ቃላትን በመናገር ማግኘት ያለበትን ኹሉ ለማግኘት የተገባ ኾኗልና (ሉቃ.18፥9-14)፡፡ ተመልከት! በጽርይት ሕሊና በንጽህት ልቡና ስለ ቀረበ አንዲቱ ቃሉ ብቻ ደጀ ሰማያትን ለመክፈት በቂ ነበረች፡፡ ይህችንስ እንዴት ነበር ያቀረባት? ➛ኃጢአቱን በማመን፤ ➛ ደረቱን በመድቃት፤ ➛ዓይኑን እንኳን ወደ ላይ ወደ ሰማይ ቀና ባለማድረግ! አንተም እንደዚህ ብትጸልይ ጸሎትህ ፈጥና ግዳጅ የምትፈጽም ትኾንልሃለች፡፡ ኃጥኡ እንደዚህ በመጸለዩ ጻድቅ ከኾነ፥ ጻድቅ ሰው እንደዚህ አድርጎ ጸሎት ማድረስን ቢያወቅ ደግሞ እንደ ምን ያማረ የተወደደ ሊኾን አንደሚችል ልብ ብለህ አስተውል፡፡ ("የክርስቲያን መከራ እና ሌሎች" በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ገጽ 20-21 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)
8 137
17
"ተስፋ ማለት 'ቢሆንስ' ብሎ መመኘት ሳይሆን፣ የሚታየው ዓለም ቢፈርስ እንኳን በማይታየው አምላክ ላይ ለመደገፍ የሚወሰን ጽኑ ውሳኔ ነው። ተስፋ አትቁረጥ፤ እግዚአብሔር አንተ በማታያቸው ነገሮች ላይ አሁን እየሠራ ነውና። መዘግየቱ መከልከል አይደለም።" (አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ)
8 267
18
ማስታወቂያ ፈጣን፣ አስተማማኝ እና ህጋዊ የዕቃ ማድረስ አገልግሎት! በልዩ ባስ ክፍለሀገር ተሳፋሪ መኪና ላይ የምሰራ አስተናጋጅ ነኝ። ህጋዊ ደረሰኝ ያላቸውን የእርስዎን ውድ ዕቃዎች፣ መልዕክቶች እና ፖስታዎች ካሉበት ቦታ ተቀብለን በታማኝነት እና በፍጥነት ወደ መዳረሻቸው እናደርሳለን! የምንሰጣቸው አገልግሎቶች ➛ ማናቸውንም መልዕክቶች እና ፖስታዎች ማድረስ ➛ ማንኛውንም ዓይነት ዕቃዎች በታማኝነት ማጓጓዝ የምንደርስባቸው ዋና ዋና መስመሮች እና ከተሞች 1ኛ መስመር (ወደ መቀሌ)፦ ቆቦ ➔ አላማጣ ➔ መሆኒ ➔ አቢኣዲ ➔ አድዋ ➔ ሽሬ ... እና መቀሌ 2ኛ መስመር (ወደ ሞያሌ)፦ ሀዋሳ ➔ ዲላ ➔ ሀገረ ማርያም ➔ ቡሌሆራ ➔ ያቤሎ ➔ ሜጋ ... እና ሞያሌ 3ኛ መስመር፦ ነቀምቴ ➔ ደምቢዶሎ ... 4ኛ መስመር፦ ድሬዳዋ 5ኛ መስመር፦ ወላይታ ➔ አርባ ምንጭ 6ኛ መስመር፦ ጅማ እና ሚዛን 7ኛ መስመር፦ ደብረ ብርሃን ➛ ደሴ ➛ ወልድያ 8ኛ መስመር፦ ደብረ ማርቆስ ➛ ባህር ዳር➛ ጎንደር➛ ደብረ ታቦር "ታማኝነት መለያችን ነው፤ ዕቃዎትን ካሰቡበት እናደርሳለን!" አሁኑኑ ስልክ ቁጥሮች ይደውሉልን! 0921799534 0907851185 0786799534
8 732
19
“መጽሐፍ ቅዱስን አለማወቅ የእግዚአብሔርን ፍቅር ችላ ማለት ነው።” “የመዳን ራስ” የሚቀድሰውና የሚቀደሱት ከአንድ ናቸው…? የታመነ ሊቀ ካህናት… የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ወደ ዕብራውያን ሰዎች ተከታታይ ጥናት👇 ክፍል 6 ተለቋል https://youtu.be/U6dhGU76uNU?si=iQnaJ5bi5cRHRd-_
7 645
20
የጸሎት ጥበብ - ፩ ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገርን የተረዳ ያወቀ ሰው እግዚአብሔርን እንደሚገባ'ው አድርጎ ሲያነጋግረው ከዚያን ጊዜ አንሥቶ መልአክ ይኾናል፡፡ ነፍስ ከፈቃዳተ ሥጋ ሰንሰለት ነጻ የምትወጣው በዚህ መንገድ ነውና፤ ሕሊና ከፍ ከፍ የሚለው በዚህ መንገድ ነውና! ማደሪያችን ወደ ሰማይ የሚሻገረው በዚህ መንገድ ነውና፤ አንድ ሰው ግብረ ዓለምን የሚንቀው በዚህ መንገድ ነውና፤ አንድ ሰው የቱንም ያህል ነዳይ ወይም ባሪያ ወይም ተራ ወይም ዝቅ ያለ ቢኾንም እንኳን በንጉሥ ዙፋን ፊት የሚቆመው በዚህ መንገድ ነውና፡፡ እግዚአብሔር የሚመለከተው የንግግርን ውበት ወይም የቃልን ርቱዕነት ሳይኾን የመንፈስን ንጹህነት ነውና፡፡ በዚህ መንገድ መጥተን ወደ አእምሮአችን የመጣውን ብንናገርም እንኳን፥ ጸሎታችን ግዳጅ የሚፈጽም ኾኖናልን እንመለሳለን፡፡ እንግዲህ ይህን ማድረግ ምን ያህል ቀላል እንደ ኾነ ታስተውላለህን? በዚህ ዓለም ሰዎች ዘንድ አንድ ሰው ሌላውን ሰው ለመለመን የንግግር ክህሎት (ብልሐት) ያሻዋል፡፡ የሚለመነው ሰው በቀላሉ የማይገኝ ከኾነ ደግሞ አጃቢዎቹን ማሳመን ይኖርበታል፡፡ ጥሮ ለፍቶ ካገኘው በኋላም ጉዳዩን በዝርዝር ማስረዳት ይጠበቅበታል፡፡ እግዚአብሔርን ለማናገር ግን የዚሁ ተቃራኒ ነው፡፡ ከተሰበረ ልብ በቀር ሌላ ምንም ምን አያስፈልግም፤ ወደ እርሱ ለመቅረብም የሚከለክል ማንም አይኖርም፡፡ “እኔ የቅርብ አምላክ ነኝ እንጂ ሩቅ አምላክ አይደለሁም” ይላልና (ኤር.23፥23)፤ የምንርቀው እኛ ነን እንጂ እርሱ ዘወትር ቅርብ ነው፡፡ እግዚአብሔርን ለማነጋገር የንግግር ክህሎት (ብልሐት) አያስፈልገንም የምለውስ ለምንድን ነው? እንዲያውም ብዙ ጊዜ ድምፅም ቢኾን አያስፈልገንም፡፡ አንተ በልብህ ብትናገርና እግዚአብሔርን ማናገር እንዲገባ'ህ ብታናግረው እርሱ ጸሎትህን ለመስማት ዘንበል ይላል፡፡ ሙሴ ጸሎቱ የተሰማው በዚህ መንገድ ነውና፤ ሐና ጸሎትዋ የተሰማው በዚህ መንገድ ነውና፡፡ ወደ እግዚአብሔር እንዳይቀርቡ ብሎ ሕዝቡን ለማራቅ የሚቆም ወታደር የለም፤ አሁን ሰዓቱ አይደለም ብሎ የሚከለክል ዘበኛም የለም፡፡ እግዚአብሔርም፦ “አሁን ላነጋግርህ አልችልም፤ ሌላ ጊዜ ተመለስ” አይልም፡፡ ይልቅ ልታነጋግረው በመጣህበት ቅጽበት አንተን ለመስማት ይቆማል የምሳ ሰዓትም ቢኾን፣ የአራት ሰዓትም ቢኾን፤ እጅግ አስቸጋሪ ጊዜም ቢኾን፣ በገበያ ቦታም ቢኾን፣ በመንገድ ላይም ቢኾን፤ በባሕር ውስጥም ቢኾን፣፤ በዳኛ ፊት በምትቆምበት በችሎት ፊትም ቢኾን፥ እግዚአብሔርን ብትጠራው መጥራት እንደሚገባህ አድርገህ እስከ ጠራኸው ድረስ ጸሎትህን እንዳይሰማ የሚከለክለው ግድግዳ የለም፡፡....... ("የክርስቲያን መከራ እና ሌሎች" በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ገጽ 18-19 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)
8 371