ar
Feedback
ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

الذهاب إلى القناة على Telegram

በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

تُعد قناة ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (@beteafework) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 55 363 مشتركاً، محتلاً المرتبة 932 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 587 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 55 363 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 27 أغسطس, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 707، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 33، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 17.92‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 8.27‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 9 919 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 4 576 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 159.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 28 أغسطس, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

55 363
المشتركون
+3324 ساعات
+957 أيام
+70730 أيام

جاري تحميل البيانات...

سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
أغسطس '26
أغسطس '26
+715
في 39 قنوات
يوليو '26
+737
في 30 قنوات
Get PRO
يونيو '26
+809
في 30 قنوات
Get PRO
مايو '26
+1 053
في 46 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+1 078
في 69 قنوات
Get PRO
مارس '26
+664
في 44 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+1 024
في 55 قنوات
Get PRO
يناير '26
+584
في 42 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+850
في 42 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+706
في 59 قنوات
Get PRO
أكتوبر '25
+669
في 64 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+395
في 61 قنوات
Get PRO
أغسطس '25
+676
في 49 قنوات
Get PRO
يوليو '25
+724
في 68 قنوات
Get PRO
يونيو '25
+433
في 39 قنوات
Get PRO
مايو '25
+523
في 12 قنوات
Get PRO
أبريل '25
+1 215
في 59 قنوات
Get PRO
مارس '25
+1 654
في 82 قنوات
Get PRO
فبراير '25
+1 022
في 38 قنوات
Get PRO
يناير '25
+2 106
في 70 قنوات
Get PRO
ديسمبر '24
+2 118
في 57 قنوات
Get PRO
نوفمبر '24
+2 209
في 74 قنوات
Get PRO
أكتوبر '24
+1 841
في 92 قنوات
Get PRO
سبتمبر '24
+1 381
في 89 قنوات
Get PRO
أغسطس '24
+1 550
في 51 قنوات
Get PRO
يوليو '24
+475
في 15 قنوات
Get PRO
يونيو '24
+517
في 18 قنوات
Get PRO
مايو '24
+989
في 26 قنوات
Get PRO
أبريل '24
+875
في 26 قنوات
Get PRO
مارس '24
+998
في 20 قنوات
Get PRO
فبراير '24
+335
في 14 قنوات
Get PRO
يناير '24
+422
في 12 قنوات
Get PRO
ديسمبر '23
+326
في 19 قنوات
Get PRO
نوفمبر '23
+282
في 11 قنوات
Get PRO
أكتوبر '23
+148
في 5 قنوات
Get PRO
سبتمبر '23
+172
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '23
+174
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '23
+498
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '23
+525
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '23
+546
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '23
+617
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '23
+367
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '23
+500
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '23
+504
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '22
+307
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '22
+286
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '22
+296
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '22
+440
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '22
+380
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '22
+680
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '22
+378
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '22
+443
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '22
+514
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '22
+395
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '22
+245
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '22
+222
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '21
+203
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '21
+254
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '21
+390
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '21
+409
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '21
+461
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '21
+594
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '21
+684
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '21
+622
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '21
+789
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '21
+719
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '21
+539
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '21
+505
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '20
+19 882
في 0 قنوات
التاريخ
نمو المشتركين
الإشارات
القنوات
28 أغسطس+22
27 أغسطس+33
26 أغسطس+17
25 أغسطس+20
24 أغسطس+27
23 أغسطس+7
22 أغسطس+26
21 أغسطس+9
20 أغسطس+3
19 أغسطس+26
18 أغسطس+21
17 أغسطس+16
16 أغسطس+21
15 أغسطس+8
14 أغسطس+8
13 أغسطس+26
12 أغسطس+37
11 أغسطس+47
10 أغسطس+21
09 أغسطس+50
08 أغسطس+61
07 أغسطس+31
06 أغسطس+11
05 أغسطس+16
04 أغسطس+23
03 أغسطس+46
02 أغسطس+61
01 أغسطس+21
منشورات القناة
...እስኪ ንገረኝ በዚህ ምድር የምታጣጥመው ደስታ ምን ዓይነት ነው? እኔ ያስተማርኩህንስ ደስታ በዚህ ዓለም ሳለን ማጣጣም አይቻለንምን? ምን ዓይነት ነፃነትን እንደምታገኝ ልብ በል፤ በጽድቅ የምትመላለስ ከሆነ የትኛውም ሰው ቢሆን አያስፈራህም ወይም አያሸብርህም፤ ጠላትም ቢሆን ወይም በአንተ ላይ የሚሸምቍትም ቢሆኑ ወይም ነገር ሰሪም ቢሆን አበዳሪም ቢሆን ፆታዊ ፍቅርም ቢሆን ክፉ ሰዎችም ቢሆኑ ድህነትም ቢሆን በሽታም ቢሆን ሌሎችም በሰው ላይ የሚመጡ ሁሉ አያስፈሩህም። ነገር ግን እንደ ልብህ ምኞት ሀብትህ እንደ ጅረት ሆኖ ቢፈስ በዚህ ምክንያት በአንተ ላይ ከሚመጡት ሁከቶች፤ ዓመፃዎችና እንቅፋቶች እንዲሁም ጠቦች ሕይወታቸው በጋለሞታ ከሚመሰቃቀልባቸው ሰዎች ይልቅ የታወከ ነው፡፡ በጋለሞታይቱ ሕይወቱ የተመሰቃቀለበት ያ ሰው ራሱን በከንቱ የሚያስታብይ ክብረ ቢስ ሰው ነው፡፡ ስለዚህ እርሷን ለመማረክ ሲል የፋመ ጠብ ውስጥ ይገባል፡፡ ይህ በብዙ ሺህ እጥፍ ከሞት ይልቅ የከፋ ነው፡፡ ቅጣቱም የሚቋቋሙት አይደለም፡፡ በመንፈሳዊነት ውስጥ ግን እነዚህን የመሰሉ ነገሮች ፈጽሞ የሉም፡፡ ፍሬዎቹም መጽሐፍ እንደሚነግረን፡-“ፍቅር፣ ደስታ፣ ሰላም” ናቸው፡፡ በመንፈሳዊው ሕይወት ውስጥ ይህን የመሰለ ሁከት የለም፤ ወይም ያለ ምክንያት የሚባክን ገንዘብ ወይም ያለአግባብ የሚወጣ ወጪ የለም፤ እንዲሁም ጥቂት ሳንቲም ወይም ቁራሽ እንጀራ ወይም ቀዝቃዛ ውኃ ብትስጥ እርሱ በዝቶ ይሰጥሃል፡፡ እርሱም ቢሆን አንተን የሚያስጨንቅ የሚጎዳ ነገር አያመጣብህም፤ ነገርን በሁሉ ትከብር ዘንድ ይፈልጋል፤ ከሚያዋርድ ነገር ሁሉ ነፃ ያወጣሃል፡፡ የክፋት ሥራዎችን ካልተውናቸው ግን ስለመተላለፋችን ምን መከላከያ ልናቀርብ ይቻለናል? ምን ዓይነት ይቅርታስ እናገኛለን? እኛ ከተፈጥሮአችን በተቃራኒ ለሆነ ሥራ ራሳችንን አሳልፈን ሰጥተናልና ከሚንቀለቀል ዘለዓለማዊ እሳት ውስጥ እንጣላለን፡፡ ስለዚህም በዚህ ደዌ የተያዙ ወገኖች ከዚህ ክፉ ሕማም ራሳቸውን እንዲያርቁ ወደ ጤናቸውም እንዲመለሱና ራሳቸውን ለጥፋት አጋልጠው እንዳይሰጡ እመክራቸዋለሁ:: ያ የጠፋው ልጅ በጣም በተጎሳቆለ ሕይወት ውስጥ ይኖር ነበር፤ ወደ አባቱ ቤት በተመለሰ ጊዜ ግን የቀደመ ክብሩ ተመለሰለት፡፡ ከወንድሙ በላይ ከዚህ በፊት ፈጽሞ ታይቶ በማይታወቅ ፍጹም ደስታ ደስ ተሰኘ፡፡ እኛም እርሱን እንምሰለው፤ ከመንፈሳዊው ሕይወት ርቀን ከሆነ ወደ አባታችን ቤት ለመመለስ እንፋጠን፤ በመንግሥቱ በደስታ መኖርን ገንዘብ ለማድረግ ለኀጢአት ባሪያ ከመሆን እንለይ፤ ራሳችንንም ነፃ እናውጣ፡፡ (የዮሐንስ ወንጌል በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅጽ 2 ገጽ 321-322 በዲያቆን ሽመልስ መርጊያ የተተረጎመ)

2
#ወንድሞቼ ከእናንተ መካከል አንድ አይነ ሥውር ሰው ወደ ጉድጓድ ገብቶ ሊወድቅ ሲል እጁን ዘርግቶ የማይደግፈው ማን ነው? ታድያ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በልቡናቸው ታውረው ወደ ሲዖል ጉድጓድ ለዘለዓለም ሲወድቁ እንደ ምን እጃችንን የበለጠ አይዘረጋም? #ወገኖቼ በነፍስም በሥጋም የታመመ ሰውን ስታዩ "ይህ የእኔ ሥራ አይደለም የቀሳውስትና የመነኮሳት ሥራ እንጂ፤ ምክንያቱም ሚስት አለችኝ ልጆችንም አሳድጋለሁ" አትበሉ፡፡ እስኪ ምሳሌ መስዬ ልጠይቃችሁ እናንተም መልሱልኝ፡፡ አንድ ትልቅ በወርቅ የተሞላ ሳጥን ወድቆ ብታዩ "ይህ እኔን አይመለከተኝም ሌሎች መጥተው ያንሡት እንጂ" ትላላችሁን? ግራ ቀኛችሁን አይታችሁ በፍጥነት የምታነሡት አይደለምን? ይህ ወደ ዘለዓለም ጉድጓድ እየወደቀ ያለው ወንድማችሁም ከዚያ ወርቅ በላይ ውድ የእግዚአብሔር ሀብት ነውና አንሡት እንጂ የበለጠ እንዲወድቅ አትግፋት። እግዚአብሔር ይህን በተመለከተ በአፈ ያዕቆብ እንዲህ ብሏልና፡- "ወንድሞቻችን ሆይ ከእናንተ ወገን ከጽድቅ ወጥቶ የበደለ ቢኖር መክሮ አስተምሮ ከበደሉ የመለሰው ቢኖር ራሱን አንድም ወንድሙን ከሞት እንዳዳነ ይወቅ፡፡ የራሱን አንድም የወንድሙን ብዙ ኃጢአቱን እንዳስተሠረየ ይወቅ፡፡ አንድም የወንድሙን ነፍስ እንዳዳነ ይወቅ።" (ያዕ. 5፥19-20) #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
2 618
3
መልካም አድርግና እርሳው! ስላደርግኸው ስለዚህ ነገር ማንኛውንም ዓይነት ውዳሴም ሆነ ሙገሳ አትሻ። መልካም ያደረግህለት ሰው አንተ እንዳደረግህለት ለአንተ መልካም የሆነውን አጸፋ እንዲመልስልህ ወይም አንተ አንደተንከባከብከው እርሱም እንዲንከባከብህ አትጠብቅ። መልካም ስታደርግ በምላሹ መልካም ዋጋ አገኛለሁ ብለህ በመጠበቅ ላለመሆኑ እርግጠኛ ሁን! መልካም የምታደርገው መልካም ማድርግን ስለምትወድ ወይም መልካም ከማድረግ መከልከል ስለማትችል ለመሆኑ እርግጠኛ ሁን። መልካም መሆን በውስጥህ ያለ ጠባይ ይሁን። መልካም ጠባይ እንደ መተንፈስ ምንም ዓይነት ጥረት የማይጠይቅ ግብታዊ ነገር ይሁን። እንዲህ ያለውን ነገር የምትረሳው ከሆነ እግዚአብሔር በዚህ ምድርም ሆነ በሚመጣው ዓለም ያስታውስሃል። መልካም ማድረግህን የምታስታውሰውና በውስጥህ ይዘኸው የምትቆይ ከሆነ ግን ታጣዋለህ። ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
3 624
4
ትንሿ ቤተክርስቲያን በኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ ባለትዳሮች በቤታቸው ውስጥ ማድረግ ያለባቸው ቤተ ክርስቲያን መጥተው ያዩትን ነው፡፡ ለምሳሌ፦ 👉 ቤተክርስቲያን ውስጥ የጠዋትና የሰርክ ጸሎት እንዳለ ኹሉ እነዚህ ባለ ትዳሮችም የጠዋትና የሰርክ ጸሎት በቤታቸው ውስጥ ሊኖራቸው ይገባል፡፡ 👉 በቤተክርስቲያን ያለው የኅብረትና የአንድነት ጸሎት እንደ ኾነ ኹሉ፥ ባልና ሚስት ልጆችም ሳይለያዩ አብረው መጸለይ አለባቸው፡፡ 👉 በቤተክርስቲያን ውስጥ ከቅዳሴ በኋላ ትምህርተ ወንጌል እንዳለ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም እራት ከበሉ በኋላ ቃለ እግዚአብሔር ሊማማሩ ይገባቸዋል፡፡ 👉 በቤተክርስቲያን ውስጥ ራሳቸውን ገዝተው የሚኖሩ ትጉሃን መነኰሳት እንዳሉ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም ይህን ትግሃትና ምስጋና ወደ ቤታቸው ይዘዉት ሊኼዱ ይገባቸዋል፡፡ 👉 ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማታ ላይ ኅብስቱን አበርክቶ ሕዝቡን ከመገባቸው በኋላ ወዲያው ወደ መኝታ እንዲኼዱ እንዳላደረገ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም ወደ መኝታቸው ከመኼዳቸው በፊት የቀን ውሎአቸውን መገምገም አለባቸው፡፡ 👉 ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሌሊት ሌሊት ሲጸልይ ያድር እንደ ነበረ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም ሌሊት ላይ ነቅተው መጸለይ ይገባቸዋል፡፡ ሕፃናት ካሉም አብረዋቸው እንዲነሡ ማድረግ ይገባቸዋል፡፡ 👉 በቤተክርስቲያን ጾም እንደሚታወጅ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም በቤተ ክርስቲያን ከሚታወጀው ጾም በተጨማሪ ከንስሐ አባቶቻቸው ጋር ተመካክረው በፈቃዳቸው ሊጾሙ ይገባቸዋል፡፡ 👉 በቤተክርስቲያን ውስጥ እንዳለው፥ ባልና ሚስትም የቤታቸውን ግድግዳ፣ መስኮትና በር በመስቀል ሊያስጌጡት ይገባቸዋል፡፡ ማማተብ በማይችሉ ልጆቻቸው ግንባርም አድገው ራሳቸው ማማተብ እስኪችሉ ድረስ እነርሱ ያማትቡላቸው፡፡ ቅዱሳት ሥዕላትም በቤታቸው ውስጥ ሊኖሩ ይገባል፡፡ ቤታቸው ትንሿ ቤተ ክርስቲያን የምትኾነው በዚህ መንገድ ነው፡፡ (ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ገጽ 60 - 61)
4 924
5
https://youtu.be/oHiEAp2zfxE?si=4r2jqvucqX7CatmP
4 608
6
ኹሉንም ነገር ለእግዚአብሔር እንስጠው ወርቅን የሚያነጥር ሰው አንዲትን የወርቅ ቅንጣት ወደ እሳት ውስጥ ጨምሮ እጅግ ንጹህ እስክትኾን ድረስ ይጠብቃታል፡፡ እግዚአብሔርም ልክ እንደዚሁ ሰዎች እስኪነጹ፣ እስኪለወጡና ባገኛቸው ነገር ጥቅም እስኪያገኙ ድረስ ፈተና ውስጥ እንዲቆዩ ይፈቅዳል፡፡ ይህ ደግሞ ከጥቅምም እጅግ ከፍ ያለ ጥቅም ነው፡፡ ስለዚህ ፈተና ሲገጥመን ውስጣችን ሊረበሽ ወይም ተስፋ ሊቈርጥ አይገባውም፡፡ ያ ወርቅን የሚያነጥር ሰው በእሳት ውስጥ የጨመራትን የወርቅ ቅንጣት እዚያ ውስጥ ምን ያኽል ጊዜ መቆየት እንዳለባት ያውቃል፤ መቼ ከእሳቱ ሊያወጣት እንደሚገባውም ያውቃል፡፡ እንዲሁ እስከ መጨረሻው በእሳቱ ውስጥ ተጥላ እንድትቀርና በዚያ እንድትቃጠል አይፈቅድም፡፡ እግዚአብሔር ደግሞ ይህን ከወርቅ አንጣሪው በላይ ያውቃል፡፡ መቼ ከርኵሰታችን እንደምንነጻ ያውቃል፡፡ በመኾኑም ራሳችንን በመጣልና ተስፋ በመቁረጥ በክፋት ላይ ክፋት እየጨመርን እንዳንሔድ ሽቶ መቼ ከዚያ ፈተና እንደሚያወጣን ያውቃል፡፡ ስለዚህ ድንገት ያላሰብነው ነገር ቢገጥመን በፍጹም የምናማርር፣ ወይም ተስፋ የምንቈርጥ ልንኾን አይገባንም፡፡ ከዚህ ይልቅ የእነዚህ ነገሮች ምንነትን የሚያውቅ እግዚአብሔርን መጠበቅ፣ እርሱ እስከ ፈቀደው ጊዜ ድረስም ልቡናችንን በእሳት እንዲፈተን ማድረግ ይገባናል፡፡ ምክንያቱም ይህ ነገር በእኛ ላይ እንዲኾን የፈቀደው ለእኛ ጥቅምና በዚያ ውስጥ ኾነን በምናሳየው ጥረት ይበልጥ ሊያከብረን ስለሚወድ ነው፡፡ ይህን በማስመልከትም ጠቢቡ ሰው እንደዚህ ሲል መክሮናል፡- “ልጄ ሆይ! ለእግዚአብሔር ትገዛ ዘንድ ብትሔድ ሰውነትህን ለመከራ አዘጋጅ፤ ልብህን አቅና፤ ኹልጊዜ ታገሥ፤ አታወላውልም፤ በመከራ ብትጨነቅም አትጠራጠር” /ሲራ.2፥1-2/፡፡ “ኹሉንም ነገር ለእግዚአብሔር ስጠው፡፡” ለምን? እግዚአብሔር ከዚያ መከራ መቼ እኛን ማውጣት እንዳለበት ያውቃልና፡፡ ስለዚህ ኹሉንም ለእርሱ ልንሰጥ፣ ዘወትር እርሱን ልናመሰግን፣ ኹሉንም ነገር  ጥቅምም ይኹን ቅጣት በአኰቴት ልንቀበል ይገባናል፤ ይህም ቢኾን ለእኛ ረብሕ የሚኾን ነውና፡፡ አንድ ሐኪም፥ ሐኪም የሚባለው ታካሚውን ገላዉን ሲያጥበውና ሲመግበው እንዲሁም ደስ ወደሚያሰኝ ስፍራ ሲወስደው ብቻ አይደለም፤ በእርሱ (በታማሚው) ሰውነት ላይ የቀዶ ጥገና ምላጭና ቢላ ሲያሳርፍም ጭምር ሐኪም ነው፡፡ አባትም አባት የሚባለው ልጁን ሲንከባከብ ብቻ አይደለም፤ የገዛ ልጁን ከቤት ሲያስወጣው፣ ሲገሥጸው፣ ሲገርፈውም ያው አባት ነው፡፡ ስለዚህ እኛም እግዚአብሔር ከሐኪሞችም በላይ ሰውን ወዳጅ እንደ ኾነ በማወቅ፥ ምን ዓይነት የሕክምና ዓይነት እንደሚሰጠን በጥልቀት አንጠይቅ፤ ወይም ደግሞ ለደረሰብን መከራ እርሱን ተጠያቂ አናድርግ፡፡ ከዚህ ይልቅ እርሱ የወደደውን ነገር  ቅጣትም ይኹን ቅጣት የሌለው ነገር ብቻ ምንም ይኹን ምን በአኰቴት ልንቀበል ይገባናል፡፡ በየትኛውም መንገድም ቢኾን የእርሱ ፈቃድ እኛ እንድንድንና ከእርሱ ጋር አንድ እንድንኾን ነውና፡፡ የትኛው መንገድ ለእኛ እንደሚጠቅምም እርሱ ያውቋል፡፡ እያንዳንዱ ሰው የትኛው መንገድ ወደ እርሱ እንደሚመልሰው ያውቃል፡፡ ኹላችንም እንዴትና በምን ዓይነት መንገድ ልንድን እንደምንችል ያውቃል፡፡ በመኾኑም የሚመራን በዚህ እኛ በምንድንበት መንገድ ነው፡፡ ስለዚህ ወደየትኛውም መንገድ ቢወስደንም ልክ እንደ መጻጉዑ እርሱ እንደሚያዘ’ን ተከትለን መሔድ እንጂ ትልቁ ጉዳያችን በለስላሳና በቀላል አልያም ደግሞ በከባድና በሸካራ ጎዳና እንድንሔድ የሚያዘ’ንን ትእዛዝ መኾን የለበትም (ልንሔድበት የሚገባ’ው መንገድ እርሱ ስለሚያውቀው እንዲሁ መታዘዝ እንጂ የመንገዱን ከባድነት ወይም ቀላልነት የእኛ አጀንዳ ሊኾን አይገባውም፡፡) (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ወደ ኦሎምፒያስ የተላኩ መልእክታት - በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)
5 565
7
ሁሌም ለጸሎት ስንቆም ይህንን ማለት አንዘንጋ "እመቤቴ ሆይ ልጅሽ ሲታገሰኝ ልቤ የደነደነብኝ እኔን በምልጃሽ አስቢኝ።"
5 822
8
"መላው ዓለምን ያስደነገጡ ታላላቅ መከራዎች ኹሉ መነሻቸው ትዕቢት ነው፡፡" #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
5 894
9
"ከራሳቸው ውጪ ደስታን የሚፈልጉ እንደምን ምስኪኖች ናቸው? ደስታን በባእድ ምድር በጉዞ የሚፈልጉ አሉ። በሀብትና በዝና መካከል የሚፈልጉ ወገኖች አሉ፤ በታላቅ ይዞታና በንብረት መካከል የሚፈልጉ አሉ፤ መራራ ፍፃሜ ባላቸው በውበትና በተቃራኒ ፆታ መካከል የሚፈልጉ አሉ። በተመሳሳይ ሁኔታ ደስታን ከራሳችን ውጪ ለመገንባት መሞከር በተደጋጋሚ በመሬት ርእደት በሚናወጥ ሥፍራ ላይ እንደ መገንባት ነው። ደስታ የሚገኘው በእኛው ውስጥ እንጂ ከእኛ ውጪ አይደለም። ምስጉን ማለት ይህን ሁኔታ የተገነዘበ ሰው ነው። ደስታ ማለት የልብ ንፅህና ነው፤ እንዲህ አይነቱን ልብ እግዚአብሔር ማደሪያ ያደርገዋልና። ስለዚህ ንፁህ ልብ ያላቸው ወገኖች ክርስቶስ እንዲህ ይላቸዋል፦ በእነሱ እኖራለሁ፣ በመካከላቸውም እመላለሳለሁ፥ አምላካቸው እሆናለሁ እነሱም ሕዝቤ ይሆናሉ። 2ኛ ቆሮ. 6፥16 እንዲህ አይነት ወገኖች ምን ይጎድልባቸዋል? ምንም። " (አባ ሳራባሙን - የበረሃ ፈርጦች መጽሐፍ ገጽ 14 በመምህር ምትኩ አበራ)
7 574
10
ሦስቱ ጠቢባን ልጄ ሆይ እነርሱ ይጠብቁህ ዘንድ፤ ሕግጋትን ጠብቅ፡፡ ልጄ ሆይ በኃያላንና በጠቢባን ዘንድ ክብር ይሆንልህ ዘንድ በወጣትነት ዘመንህ ታገሥ፡፡ ልጄ ሆይ ሞገስን ይሆንህ ዘንድ የሰማኸውን ነገር ጠብቅ፡፡ ልጄ ሆይ መንፈሳዊ አባትህን ጠይቀው፡፡ እርሱም ጽድቅንና እውነትን ይነግርሃል። ልጄ ሆይ በተሾምክበት ወራት ለድኾች ፍርድ አታጉድል፤ ሰውን ባለጸጋ ነው ብለህ አትፍራው ለዘመዶችህም ፍርድ አታድላ፡፡ ለባለጸጎችም ቢሆን የሰው ሀብቱ ንብረቱ መብዛቱ እያስፈራህ፡፡ እሰከ ዕለተ ሞትህ ድረስ እውነትን ተናገር ጠቢብ ሲራክ እንዲህ አለ፦ ለሰነፍ ራስህን ዝቅ አታድርግ፡፡ እንደ ሀብቱ ብዛት ኃጢአቱም ብዙ ነው፤ በንግግሩ ብዛት ሐሰቱ ይበዛልና፡፡ ከእግዚአብሔር እንዳትለይ ድኻውን አትግፋው፡፡ ሦስት ጠበብቶች አሉ፥ አንዱ እንደተቻለው የሚተው የሚታገሥ ነገር ኃላፊ ልበ ሰፊ ነው፡፡ ሁለተኛው እያወቀ ዝም የሚል ሦስተኛው ጠቢብ ሲሆን የዋህ ነው፡፡ ልጄ ሆይ ቸኩለህ አትናገር። ነቢይ "ቀባጣሪ አንደበት ሞትን ትጠራለች" ብሏልና፡፡ ወንድሜ ሆይ በአንደበትህ በነገር እንዳትሰናከል ተጠንቀቅ፡፡ በአንደበትህ ከምትወድቅ ወደ ገደል ብትወድቅ ይሻልሃልና፡፡ ቀባጣሪ አንደበት ብዙዎችን አወከቻቸው ከትዳራቸውም ለየቻቸው፡፡ ብዙዎችም ከቤታቸው ወጡ፤ ከሀገራቸው ተሰደዱ ከክብራቸው አነሱ፡፡ (አባ ገብረ ኪዳን - መጽሐፈ ወግሪስ ገጽ 86-84)
7 479
11
በቤትህ ያለው ዳቦ ለተራበው ሰው የሚውል(ንብረቱ) ነው፥ በልብስ ማስቀመጫህ ውስጥ ያለው የማትጠቀመው ኮት የችግረኛው ገንዘቡ ነው፥ በጫማ ማስቀመጫህ ውስጥ አልፈልገውም ብለህ ሊበላሽብህ የሆነው ጫማ የደሃው ጫማ (ጫማ ለሌለው ገንዘቡ) ነው ፥ ያከማቸኸው ገንዘብ ለድሃው የሚገባው ነው.... ዛፍ በፍሬው ይታወቃል፥ ሰውም በድርጊቱ፡፡ መልካም ስራ መቼም አይጠፋም፡፡ መልካም እርዳታን የሚዘራ፥ ወዳጅነትን ያጭዳል፡፡ ደግነትን የሚተክል ፍቅርን ይሰበስባል፡፡ "ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ ብቻ የለብንም፥ ነገር ግን ካነበብነው ተምረን ማደግ አለብን፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ምንም የማይጠቅም ነገር እንዳልተጻፈ ተገንዘብ፡፡ አሁንም ለጥንካሬ፣ ለመታገስ፣ለመዳን፣ለመለወጥ ጊዜ አለህ! ተኝተሃልን? ንቃ! ኃጢአት ሰርተሃልን? እንግዲያውስ  መስራቱን አቁም፡፡ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ
8 308
12
እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ ከሁለቱ እህትና ወንድም ውጭ እስከ አሁን ሌላ በጎ አድራጊ አልተገኘም።
1 762
13
“​​​​የምትበላውን ምግብ እንደምትመርጥ ሁሉ፣ የምትናገረውንም ቃል ምረጥ፤ መጥፎ ምግብ ሥጋን እንደሚመርዝ፣ መጥፎ ቃልም ነፍስን ይመርዛል።’ አባ ጴሜን
9 844
14
ሰላም ​አንዲት እህት እና አንድ ወንድም ለደብረ ዘመዳ (ጀመዶ ማርያም) ገዳም መነኮሳት የሚሆን የልብስ ንጽህና መጠበቂያ ሳሙና የሚገዛ ገንዘብ አስረክበውኛል። ​ይሁን እንጂ የገዳሙን መነኮሳት ግምት ውስጥ በማስገባት የተላከውን መጠን ጨምረን መላክ ብንችል መልካም በመሆኑ፣ እንደተለመደው የበረከቱ ተካፋይ በመሆን የበኩላችሁን እንድታበረክቱ እጠይቃለሁ። ለበለጠ በውስጥ መስመር @natansolo ማናገር ይቻላል
4 844
15
"ዛሬን ለሰይጣን ነገን ደግሞ ለእግዚአብሔር አትስጡ!" ታላቁ ቅዱስ ጎርጎርዮስ
10 949
16
ሰላም እንደምን ዋላችሁ/አደራችሁ? ​አንዲት እህት እና አንድ ወንድም ለደብረ ዘመዳ (ጀመዶ ማርያም) ገዳም መነኮሳት የሚሆን የልብስ ንጽህና መጠበቂያ ሳሙና የሚገዛ ገንዘብ አስረክበውኛል። ​ይሁን እንጂ የገዳሙን መነኮሳት ግምት ውስጥ በማስገባት የተላከውን መጠን ጨምረን መላክ ብንችል መልካም በመሆኑ፣ እንደተለመደው የበረከቱ ተካፋይ በመሆን የበኩላችሁን እንድታበረክቱ እጠይቃለሁ።
5 903
17
ይህ እንዴት ይሆናል https://youtu.be/1Su_MUsFCZU?si=Zqj_WiKqwraTbrT2
11 293
18
"ለበጎ ነው" "አንድ ንጉስ ከአጃቢው ጋር በመሆን ለአደን ይወጣል። ለአደን ሲወጡ ንጉሱ ወጥመድ እያጠመደ እያለ ወጥመዱ አምልጦት እጁን ቆረጠው። በዚህም አጃቢው በማዘን "አይዞህ ንጉስ ሆይ ሁሉ ነገር ለበጎ ነው!" ይለዋል። በዚህም ንጉሱ በንዴት እየጦፈ "የኔ እጅ መቆረጥ ነው ለበጎ?" ይለውና እስር ቤት አሳሰረው። ከብዙ ጊዜ በኋላ ንጉሱ ብቻውን ሀገሩን ሲዞር ሰው አርደው ለጣዖት መሰዋት የሚያደርጉ ጨካኝ ሰዎች ያዙትና አርደው መሰዋት ሊያደርጉት ሲሉ ቆራጣ እጁን አዩት። በእነሱ ህግ መሰዋት የሚያደርጉት ሰዉ ሙሉ ጤነኛ መሆን ስላለበት ለቀቁት። ንጉሱ አጃቢው 'ሁሉ ነገር ለበጎ ነው!' ያለው ትዝ አለውና እስር ቤት ሄዶ ስላሰርኩህ ይቅርታ አርግልኝ! ብሎ ታሪኩን አጫወተው። አጃቢውም "ማሰርህ ለበጎ ነበር! እኔም መታሰሬ ጠቅሞኛል።" አለው። ንጉሱ "እንዴት?" አለው አጃቢውም "ባልታሰር ኖሮ ከአንተ ጋር እሄድና አንተ ቆራጣ መሆንህን ሲያውቁ ይለቁህና አኔን ይገሉኝ ነበር" አለው። ስለዚህ ሁላችንም ስለተደረገልንም ሆነ ስላልተደረገልን እንዲሁም ስለሆነውም ሆነ ስላልሆነው ነገር ሁሉ "ለበጎ ነው" ማለት ይልመድብን፡፡
10 968
19
"ከሐዋርያት ጋር ሆኜ የእመቤታችንን የዕረፍቷንና የክብሯን ነገር በተመለከትኩ ጊዜ፡ ከሰው ህሊና በላይ የሆነ ታላቅ የብርሃንና የመላእክት ምስጋና አየሁ። ሥጋዋም በክብር ወደ ሰማይ ተወሰደ።" (ቅዱስ
"ከሐዋርያት ጋር ሆኜ የእመቤታችንን የዕረፍቷንና የክብሯን ነገር በተመለከትኩ ጊዜ፡ ከሰው ህሊና በላይ የሆነ ታላቅ የብርሃንና የመላእክት ምስጋና አየሁ። ሥጋዋም በክብር ወደ ሰማይ ተወሰደ።" (ቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘአርዮስፋጎስ)
11 541
20
لا يوجد نص...
9 817