ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡
Ko'proq ko'rsatish📈 Telegram kanali ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ analitikasi
ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (@beteafework) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 55 406 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 928-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 585-o'rinni egallagan.
📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika
невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 55 406 obunachiga ega bo‘ldi.
29 Avgust, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 692 ga, so‘nggi 24 soatda esa 26 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.
- Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
- Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 17.64% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 8.32% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
- Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 9 772 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 4 611 ta ko‘rish yig‘iladi.
- Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 148 ta reaksiya keladi.
📝 Tavsif va kontent siyosati
Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡”
Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 30 Avgust, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.
Ma'lumot yuklanmoqda...
| Sana | Obunachilarni jalb qilish | Esdaliklar | Kanallar | |
| 30 Avgust | +8 | |||
| 29 Avgust | +28 | |||
| 28 Avgust | +34 | |||
| 27 Avgust | +33 | |||
| 26 Avgust | +17 | |||
| 25 Avgust | +20 | |||
| 24 Avgust | +27 | |||
| 23 Avgust | +7 | |||
| 22 Avgust | +26 | |||
| 21 Avgust | +9 | |||
| 20 Avgust | +3 | |||
| 19 Avgust | +26 | |||
| 18 Avgust | +21 | |||
| 17 Avgust | +16 | |||
| 16 Avgust | +21 | |||
| 15 Avgust | +8 | |||
| 14 Avgust | +8 | |||
| 13 Avgust | +26 | |||
| 12 Avgust | +37 | |||
| 11 Avgust | +47 | |||
| 10 Avgust | +21 | |||
| 09 Avgust | +50 | |||
| 08 Avgust | +61 | |||
| 07 Avgust | +31 | |||
| 06 Avgust | +11 | |||
| 05 Avgust | +16 | |||
| 04 Avgust | +23 | |||
| 03 Avgust | +46 | |||
| 02 Avgust | +61 | |||
| 01 Avgust | +21 |
| 2 | Matn yo'q... | 4 303 |
| 3 | #ነሐሴ_24 በዚህች ቀን የአባታችን ተክለሃይማኖት ዕረፍት እና የቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የዕረፍቷ መታሰቢያ ነው።
#ጻድቁ_አቡነ_ተክለሃይማኖት
ነሐሴ ሃያ አራት በዚህችም ቀን ታላቅ የከበረ ሐዲስ ሐዋርያ የትሩፋትም መምህር የሆነ አባታችን ተክለሃይማኖት ዐረፈ።
ከካህኑ ጸጋ ዘአብ እና ከእግዚእ ኀረያ ተወልደው፤ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአካል ተገልጦ የታያቸው ኢትዮጵያዊ ሐዋርያ ናቸው። ጻድቁ በሸዋ እና በዳሞት ምድር ተዘዋውረው ጣዖታትን በማጥፋት ጨካኙን ገዥ ሞተለሚን ጨምሮ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን ወደ ክርስትና መልሰው አጥምቀዋል።
በሐይቅ እና በደብረ ዳሞ ገዳማት ሥርዓተ ምንኵስናን ከተማሩ በኋላ፣ ግራርያ (ደብረ ሊባኖስ) አካባቢ በሚገኝ ዋሻ ውስጥ እግራቸው እስኪሰበር ድረስ ለሰባት ዓመታት ቆመው በመጸለይ በጽኑ ተጋድለዋል። በመጨረሻም ከጌታችን ታላቅ የድኅነት ቃል ኪዳን ተቀብለው በ99 ዓመት ከ8 ወር ዕድሜያቸው በክብር ዐርፈዋል።
#ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ
ዳግመኛም በዚህች ቀን ኢትዮጵያዊት የሆነች ተጋዳይ የከበረች ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የዕረፍቷ መታሰቢያ ነው፡፡
ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በቡልጋ (ቅዱስ ጌዬ) በሀብትና በምግባር ከበሩ ወላጆች ተወልዳ በሥርዓተ እግዚአብሔር አደገች፤ በኋላም ለሠምረ ጊዮርጊስ ተሞሽራ 11 ልጆችን ወለደች። ቅድስናዋ በንጉሥ ገብረ መስቀል ዘንድ ታውቆ ታላቅ ክብር ተሰጥቷት የነበረ ቢሆንም፣ ከአገልጋዮቿ መካከል በአንዷ ላይ በደረሰ አጋጣሚ ቁጣ ምክንያት አገልጋይዋ ልትሞትባት ችላለች። በዚህም እጅግ ደንግጣና ተጸጽታ "አገልጋዬን ከሞት ብታስነሳልኝ ቤቴንና ንብረቴን ትቼ አንተን እከተላለሁ" ብላ ተስላ በጸሎቷ አገልጋይዋ ስለተነሳችላት፣ የገባችውን ቃል በመጠበቅ ሀብቷንና ቤተሰቧን ትታ ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም በመሄድ መንኮሰች።
በገዳም ተጋድሎዋ ወቅት ስለ ፍጥረታት ምሕረት ስትጸልይ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጦላት ዲያብሎስ ንስሐ እንዲገባና የሰው ልጆች ከኰነኔ እንዲድኑ ለመነች። ዲያብሎስ ለምሕረት እምቢ ብሎ ቢያጠቃትም፣ በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል ረዳትነት 10,000 የሚሆኑ የሰው ነፍሳትን ከሲዖል ማረከች። በዚህ ታላቅ የመስዋዕትነት ተጋድሎ ከእግዚአብሔር ዘንድ የብርሃን አክሊላትና ቃልኪዳን የተሰጧት እናት ነች፤ የዕረፍቷም መታሰቢያ ነሐሴ 24 ቀን ይከበራል። | 4 303 |
| 4 | "ትእምርተ ሰላምነ ዘኪያሁ ንትአመን እብነ ሕይወት ወርእሰ ማዕዘንት ውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ፡፡"
"የሰላማችን ምልክት የምንታመንበት የሕይወት ድንጋይ (መሠረት) የማዕዘን ራስ እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡” | 4 767 |
| 5 | ...እስኪ ንገረኝ በዚህ ምድር የምታጣጥመው ደስታ ምን ዓይነት ነው? እኔ ያስተማርኩህንስ ደስታ በዚህ ዓለም ሳለን ማጣጣም አይቻለንምን? ምን ዓይነት ነፃነትን እንደምታገኝ ልብ በል፤ በጽድቅ የምትመላለስ ከሆነ የትኛውም ሰው ቢሆን አያስፈራህም ወይም አያሸብርህም፤ ጠላትም ቢሆን ወይም በአንተ ላይ የሚሸምቍትም ቢሆኑ ወይም ነገር ሰሪም ቢሆን አበዳሪም ቢሆን ፆታዊ ፍቅርም ቢሆን ክፉ ሰዎችም ቢሆኑ ድህነትም ቢሆን በሽታም ቢሆን ሌሎችም በሰው ላይ የሚመጡ ሁሉ አያስፈሩህም።
ነገር ግን እንደ ልብህ ምኞት ሀብትህ እንደ ጅረት ሆኖ ቢፈስ በዚህ ምክንያት በአንተ ላይ ከሚመጡት ሁከቶች፤ ዓመፃዎችና እንቅፋቶች እንዲሁም ጠቦች ሕይወታቸው በጋለሞታ ከሚመሰቃቀልባቸው ሰዎች ይልቅ የታወከ ነው፡፡ በጋለሞታይቱ ሕይወቱ የተመሰቃቀለበት ያ ሰው ራሱን በከንቱ የሚያስታብይ ክብረ ቢስ ሰው ነው፡፡ ስለዚህ እርሷን ለመማረክ ሲል የፋመ ጠብ ውስጥ ይገባል፡፡ ይህ በብዙ ሺህ እጥፍ ከሞት ይልቅ የከፋ ነው፡፡ ቅጣቱም የሚቋቋሙት አይደለም፡፡ በመንፈሳዊነት ውስጥ ግን እነዚህን የመሰሉ ነገሮች ፈጽሞ የሉም፡፡ ፍሬዎቹም መጽሐፍ እንደሚነግረን፡-“ፍቅር፣ ደስታ፣ ሰላም” ናቸው፡፡
በመንፈሳዊው ሕይወት ውስጥ ይህን የመሰለ ሁከት የለም፤ ወይም ያለ ምክንያት የሚባክን ገንዘብ ወይም ያለአግባብ የሚወጣ ወጪ የለም፤ እንዲሁም ጥቂት ሳንቲም ወይም ቁራሽ እንጀራ ወይም ቀዝቃዛ ውኃ ብትስጥ እርሱ በዝቶ ይሰጥሃል፡፡ እርሱም ቢሆን አንተን የሚያስጨንቅ የሚጎዳ ነገር አያመጣብህም፤ ነገርን በሁሉ ትከብር ዘንድ ይፈልጋል፤ ከሚያዋርድ ነገር ሁሉ ነፃ ያወጣሃል፡፡ የክፋት ሥራዎችን ካልተውናቸው ግን ስለመተላለፋችን ምን መከላከያ ልናቀርብ ይቻለናል? ምን ዓይነት ይቅርታስ እናገኛለን? እኛ ከተፈጥሮአችን በተቃራኒ ለሆነ ሥራ ራሳችንን አሳልፈን ሰጥተናልና ከሚንቀለቀል ዘለዓለማዊ እሳት ውስጥ እንጣላለን፡፡ ስለዚህም በዚህ ደዌ የተያዙ ወገኖች ከዚህ ክፉ ሕማም ራሳቸውን እንዲያርቁ ወደ ጤናቸውም እንዲመለሱና ራሳቸውን ለጥፋት አጋልጠው እንዳይሰጡ እመክራቸዋለሁ::
ያ የጠፋው ልጅ በጣም በተጎሳቆለ ሕይወት ውስጥ ይኖር ነበር፤ ወደ አባቱ ቤት በተመለሰ ጊዜ ግን የቀደመ ክብሩ ተመለሰለት፡፡ ከወንድሙ በላይ ከዚህ በፊት ፈጽሞ ታይቶ በማይታወቅ ፍጹም ደስታ ደስ ተሰኘ፡፡ እኛም እርሱን እንምሰለው፤ ከመንፈሳዊው ሕይወት ርቀን ከሆነ ወደ አባታችን ቤት ለመመለስ እንፋጠን፤ በመንግሥቱ በደስታ መኖርን ገንዘብ ለማድረግ ለኀጢአት ባሪያ ከመሆን እንለይ፤ ራሳችንንም ነፃ እናውጣ፡፡
(የዮሐንስ ወንጌል በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅጽ 2 ገጽ 321-322 በዲያቆን ሽመልስ መርጊያ የተተረጎመ) | 5 875 |
| 6 | #ወንድሞቼ ከእናንተ መካከል አንድ አይነ ሥውር ሰው ወደ ጉድጓድ ገብቶ ሊወድቅ ሲል እጁን ዘርግቶ የማይደግፈው ማን ነው? ታድያ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በልቡናቸው ታውረው ወደ ሲዖል ጉድጓድ ለዘለዓለም ሲወድቁ እንደ ምን እጃችንን የበለጠ አይዘረጋም?
#ወገኖቼ በነፍስም በሥጋም የታመመ ሰውን ስታዩ "ይህ የእኔ ሥራ አይደለም የቀሳውስትና የመነኮሳት ሥራ እንጂ፤ ምክንያቱም ሚስት አለችኝ ልጆችንም አሳድጋለሁ" አትበሉ፡፡
እስኪ ምሳሌ መስዬ ልጠይቃችሁ እናንተም መልሱልኝ፡፡ አንድ ትልቅ በወርቅ የተሞላ ሳጥን ወድቆ ብታዩ "ይህ እኔን አይመለከተኝም ሌሎች መጥተው ያንሡት እንጂ" ትላላችሁን? ግራ ቀኛችሁን አይታችሁ በፍጥነት የምታነሡት አይደለምን?
ይህ ወደ ዘለዓለም ጉድጓድ እየወደቀ ያለው ወንድማችሁም ከዚያ ወርቅ በላይ ውድ የእግዚአብሔር ሀብት ነውና አንሡት እንጂ የበለጠ እንዲወድቅ አትግፋት።
እግዚአብሔር ይህን በተመለከተ በአፈ ያዕቆብ እንዲህ ብሏልና፡- "ወንድሞቻችን ሆይ ከእናንተ ወገን ከጽድቅ ወጥቶ የበደለ ቢኖር መክሮ አስተምሮ ከበደሉ የመለሰው ቢኖር ራሱን አንድም ወንድሙን ከሞት እንዳዳነ ይወቅ፡፡ የራሱን አንድም የወንድሙን ብዙ ኃጢአቱን እንዳስተሠረየ ይወቅ፡፡ አንድም የወንድሙን ነፍስ እንዳዳነ ይወቅ።" (ያዕ. 5፥19-20)
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ | 6 083 |
| 7 | መልካም አድርግና እርሳው!
ስላደርግኸው ስለዚህ ነገር ማንኛውንም ዓይነት ውዳሴም ሆነ ሙገሳ አትሻ። መልካም ያደረግህለት ሰው አንተ እንዳደረግህለት ለአንተ መልካም የሆነውን አጸፋ እንዲመልስልህ ወይም አንተ አንደተንከባከብከው እርሱም እንዲንከባከብህ አትጠብቅ።
መልካም ስታደርግ በምላሹ መልካም ዋጋ አገኛለሁ ብለህ በመጠበቅ ላለመሆኑ እርግጠኛ ሁን! መልካም የምታደርገው መልካም ማድርግን ስለምትወድ ወይም መልካም ከማድረግ መከልከል ስለማትችል ለመሆኑ እርግጠኛ ሁን። መልካም መሆን በውስጥህ ያለ ጠባይ ይሁን። መልካም ጠባይ እንደ መተንፈስ ምንም ዓይነት ጥረት የማይጠይቅ ግብታዊ ነገር ይሁን።
እንዲህ ያለውን ነገር የምትረሳው ከሆነ እግዚአብሔር በዚህ ምድርም ሆነ በሚመጣው ዓለም ያስታውስሃል። መልካም ማድረግህን የምታስታውሰውና በውስጥህ ይዘኸው የምትቆይ ከሆነ ግን ታጣዋለህ።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ | 5 768 |
| 8 | ትንሿ ቤተክርስቲያን በኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ
ባለትዳሮች በቤታቸው ውስጥ ማድረግ ያለባቸው ቤተ ክርስቲያን መጥተው ያዩትን ነው፡፡ ለምሳሌ፦
👉 ቤተክርስቲያን ውስጥ የጠዋትና የሰርክ ጸሎት እንዳለ ኹሉ እነዚህ ባለ ትዳሮችም የጠዋትና የሰርክ ጸሎት በቤታቸው ውስጥ ሊኖራቸው ይገባል፡፡
👉 በቤተክርስቲያን ያለው የኅብረትና የአንድነት ጸሎት እንደ ኾነ ኹሉ፥ ባልና ሚስት ልጆችም ሳይለያዩ አብረው መጸለይ አለባቸው፡፡
👉 በቤተክርስቲያን ውስጥ ከቅዳሴ በኋላ ትምህርተ ወንጌል እንዳለ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም እራት ከበሉ በኋላ ቃለ እግዚአብሔር ሊማማሩ ይገባቸዋል፡፡
👉 በቤተክርስቲያን ውስጥ ራሳቸውን ገዝተው የሚኖሩ ትጉሃን መነኰሳት እንዳሉ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም ይህን ትግሃትና ምስጋና ወደ ቤታቸው ይዘዉት ሊኼዱ ይገባቸዋል፡፡
👉 ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማታ ላይ ኅብስቱን አበርክቶ ሕዝቡን ከመገባቸው በኋላ ወዲያው ወደ መኝታ እንዲኼዱ እንዳላደረገ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም ወደ መኝታቸው ከመኼዳቸው በፊት የቀን ውሎአቸውን መገምገም አለባቸው፡፡
👉 ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሌሊት ሌሊት ሲጸልይ ያድር እንደ ነበረ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም ሌሊት ላይ ነቅተው መጸለይ ይገባቸዋል፡፡ ሕፃናት ካሉም አብረዋቸው እንዲነሡ ማድረግ ይገባቸዋል፡፡
👉 በቤተክርስቲያን ጾም እንደሚታወጅ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም በቤተ ክርስቲያን ከሚታወጀው ጾም በተጨማሪ ከንስሐ አባቶቻቸው ጋር ተመካክረው በፈቃዳቸው ሊጾሙ ይገባቸዋል፡፡
👉 በቤተክርስቲያን ውስጥ እንዳለው፥ ባልና ሚስትም የቤታቸውን ግድግዳ፣ መስኮትና በር በመስቀል ሊያስጌጡት ይገባቸዋል፡፡ ማማተብ በማይችሉ ልጆቻቸው ግንባርም አድገው ራሳቸው ማማተብ እስኪችሉ ድረስ እነርሱ ያማትቡላቸው፡፡ ቅዱሳት ሥዕላትም በቤታቸው ውስጥ ሊኖሩ ይገባል፡፡
ቤታቸው ትንሿ ቤተ ክርስቲያን የምትኾነው በዚህ መንገድ ነው፡፡
(ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ገጽ 60 - 61) | 6 397 |
| 9 | https://youtu.be/oHiEAp2zfxE?si=4r2jqvucqX7CatmP | 5 584 |
| 10 | ኹሉንም ነገር ለእግዚአብሔር እንስጠው
ወርቅን የሚያነጥር ሰው አንዲትን የወርቅ ቅንጣት ወደ እሳት ውስጥ ጨምሮ እጅግ ንጹህ እስክትኾን ድረስ ይጠብቃታል፡፡ እግዚአብሔርም ልክ እንደዚሁ ሰዎች እስኪነጹ፣ እስኪለወጡና ባገኛቸው ነገር ጥቅም እስኪያገኙ ድረስ ፈተና ውስጥ እንዲቆዩ ይፈቅዳል፡፡ ይህ ደግሞ ከጥቅምም እጅግ ከፍ ያለ ጥቅም ነው፡፡
ስለዚህ ፈተና ሲገጥመን ውስጣችን ሊረበሽ ወይም ተስፋ ሊቈርጥ አይገባውም፡፡ ያ ወርቅን የሚያነጥር ሰው በእሳት ውስጥ የጨመራትን የወርቅ ቅንጣት እዚያ ውስጥ ምን ያኽል ጊዜ መቆየት እንዳለባት ያውቃል፤ መቼ ከእሳቱ ሊያወጣት እንደሚገባውም ያውቃል፡፡ እንዲሁ እስከ መጨረሻው በእሳቱ ውስጥ ተጥላ እንድትቀርና በዚያ እንድትቃጠል አይፈቅድም፡፡ እግዚአብሔር ደግሞ ይህን ከወርቅ አንጣሪው በላይ ያውቃል፡፡ መቼ ከርኵሰታችን እንደምንነጻ ያውቃል፡፡ በመኾኑም ራሳችንን በመጣልና ተስፋ በመቁረጥ በክፋት ላይ ክፋት እየጨመርን እንዳንሔድ ሽቶ መቼ ከዚያ ፈተና እንደሚያወጣን ያውቃል፡፡ ስለዚህ ድንገት ያላሰብነው ነገር ቢገጥመን በፍጹም የምናማርር፣ ወይም ተስፋ የምንቈርጥ ልንኾን አይገባንም፡፡ ከዚህ ይልቅ የእነዚህ ነገሮች ምንነትን የሚያውቅ እግዚአብሔርን መጠበቅ፣ እርሱ እስከ ፈቀደው ጊዜ ድረስም ልቡናችንን በእሳት እንዲፈተን ማድረግ ይገባናል፡፡ ምክንያቱም ይህ ነገር በእኛ ላይ እንዲኾን የፈቀደው ለእኛ ጥቅምና በዚያ ውስጥ ኾነን በምናሳየው ጥረት ይበልጥ ሊያከብረን ስለሚወድ ነው፡፡
ይህን በማስመልከትም ጠቢቡ ሰው እንደዚህ ሲል መክሮናል፡- “ልጄ ሆይ! ለእግዚአብሔር ትገዛ ዘንድ ብትሔድ ሰውነትህን ለመከራ አዘጋጅ፤ ልብህን አቅና፤ ኹልጊዜ ታገሥ፤ አታወላውልም፤ በመከራ ብትጨነቅም አትጠራጠር” /ሲራ.2፥1-2/፡፡ “ኹሉንም ነገር ለእግዚአብሔር ስጠው፡፡” ለምን? እግዚአብሔር ከዚያ መከራ መቼ እኛን ማውጣት እንዳለበት ያውቃልና፡፡ ስለዚህ ኹሉንም ለእርሱ ልንሰጥ፣ ዘወትር እርሱን ልናመሰግን፣ ኹሉንም ነገር ጥቅምም ይኹን ቅጣት በአኰቴት ልንቀበል ይገባናል፤ ይህም ቢኾን ለእኛ ረብሕ የሚኾን ነውና፡፡
አንድ ሐኪም፥ ሐኪም የሚባለው ታካሚውን ገላዉን ሲያጥበውና ሲመግበው እንዲሁም ደስ ወደሚያሰኝ ስፍራ ሲወስደው ብቻ አይደለም፤ በእርሱ (በታማሚው) ሰውነት ላይ የቀዶ ጥገና ምላጭና ቢላ ሲያሳርፍም ጭምር ሐኪም ነው፡፡ አባትም አባት የሚባለው ልጁን ሲንከባከብ ብቻ አይደለም፤ የገዛ ልጁን ከቤት ሲያስወጣው፣ ሲገሥጸው፣ ሲገርፈውም ያው አባት ነው፡፡ ስለዚህ እኛም እግዚአብሔር ከሐኪሞችም በላይ ሰውን ወዳጅ እንደ ኾነ በማወቅ፥ ምን ዓይነት የሕክምና ዓይነት እንደሚሰጠን በጥልቀት አንጠይቅ፤ ወይም ደግሞ ለደረሰብን መከራ እርሱን ተጠያቂ አናድርግ፡፡ ከዚህ ይልቅ እርሱ የወደደውን ነገር ቅጣትም ይኹን ቅጣት የሌለው ነገር ብቻ ምንም ይኹን ምን በአኰቴት ልንቀበል ይገባናል፡፡
በየትኛውም መንገድም ቢኾን የእርሱ ፈቃድ እኛ እንድንድንና ከእርሱ ጋር አንድ እንድንኾን ነውና፡፡ የትኛው መንገድ ለእኛ እንደሚጠቅምም እርሱ ያውቋል፡፡ እያንዳንዱ ሰው የትኛው መንገድ ወደ እርሱ እንደሚመልሰው ያውቃል፡፡ ኹላችንም እንዴትና በምን ዓይነት መንገድ ልንድን እንደምንችል ያውቃል፡፡ በመኾኑም የሚመራን በዚህ እኛ በምንድንበት መንገድ ነው፡፡ ስለዚህ ወደየትኛውም መንገድ ቢወስደንም ልክ እንደ መጻጉዑ እርሱ እንደሚያዘ’ን ተከትለን መሔድ እንጂ ትልቁ ጉዳያችን በለስላሳና በቀላል አልያም ደግሞ በከባድና በሸካራ ጎዳና እንድንሔድ የሚያዘ’ንን ትእዛዝ መኾን የለበትም (ልንሔድበት የሚገባ’ው መንገድ እርሱ ስለሚያውቀው እንዲሁ መታዘዝ እንጂ የመንገዱን ከባድነት ወይም ቀላልነት የእኛ አጀንዳ ሊኾን አይገባውም፡፡)
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ወደ ኦሎምፒያስ የተላኩ መልእክታት - በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ) | 7 114 |
| 11 | ሁሌም ለጸሎት ስንቆም ይህንን ማለት አንዘንጋ
"እመቤቴ ሆይ ልጅሽ ሲታገሰኝ ልቤ የደነደነብኝ እኔን በምልጃሽ አስቢኝ።" | 6 894 |
| 12 | "መላው ዓለምን ያስደነገጡ ታላላቅ መከራዎች ኹሉ መነሻቸው ትዕቢት ነው፡፡"
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ | 7 284 |
| 13 | "ከራሳቸው ውጪ ደስታን የሚፈልጉ እንደምን ምስኪኖች ናቸው? ደስታን በባእድ ምድር በጉዞ የሚፈልጉ አሉ። በሀብትና በዝና መካከል የሚፈልጉ ወገኖች አሉ፤ በታላቅ ይዞታና በንብረት መካከል የሚፈልጉ አሉ፤ መራራ ፍፃሜ ባላቸው በውበትና በተቃራኒ ፆታ መካከል የሚፈልጉ አሉ። በተመሳሳይ ሁኔታ ደስታን ከራሳችን ውጪ ለመገንባት መሞከር በተደጋጋሚ በመሬት ርእደት በሚናወጥ ሥፍራ ላይ እንደ መገንባት ነው።
ደስታ የሚገኘው በእኛው ውስጥ እንጂ ከእኛ ውጪ አይደለም። ምስጉን ማለት ይህን ሁኔታ የተገነዘበ ሰው ነው። ደስታ ማለት የልብ ንፅህና ነው፤ እንዲህ አይነቱን ልብ እግዚአብሔር ማደሪያ ያደርገዋልና። ስለዚህ ንፁህ ልብ ያላቸው ወገኖች ክርስቶስ እንዲህ ይላቸዋል፦ በእነሱ እኖራለሁ፣ በመካከላቸውም እመላለሳለሁ፥ አምላካቸው እሆናለሁ እነሱም ሕዝቤ ይሆናሉ። 2ኛ ቆሮ. 6፥16 እንዲህ አይነት ወገኖች ምን ይጎድልባቸዋል? ምንም። "
(አባ ሳራባሙን - የበረሃ ፈርጦች መጽሐፍ ገጽ 14 በመምህር ምትኩ አበራ) | 9 383 |
| 14 | ሦስቱ ጠቢባን
ልጄ ሆይ እነርሱ ይጠብቁህ ዘንድ፤ ሕግጋትን ጠብቅ፡፡ ልጄ ሆይ በኃያላንና በጠቢባን ዘንድ ክብር ይሆንልህ ዘንድ በወጣትነት ዘመንህ ታገሥ፡፡ ልጄ ሆይ ሞገስን ይሆንህ ዘንድ የሰማኸውን ነገር ጠብቅ፡፡ ልጄ ሆይ መንፈሳዊ አባትህን ጠይቀው፡፡ እርሱም ጽድቅንና እውነትን ይነግርሃል።
ልጄ ሆይ በተሾምክበት ወራት ለድኾች ፍርድ አታጉድል፤ ሰውን ባለጸጋ ነው ብለህ አትፍራው ለዘመዶችህም ፍርድ አታድላ፡፡ ለባለጸጎችም ቢሆን የሰው ሀብቱ ንብረቱ መብዛቱ እያስፈራህ፡፡ እሰከ ዕለተ ሞትህ ድረስ እውነትን ተናገር ጠቢብ ሲራክ እንዲህ አለ፦ ለሰነፍ ራስህን ዝቅ አታድርግ፡፡ እንደ ሀብቱ ብዛት ኃጢአቱም ብዙ ነው፤ በንግግሩ ብዛት ሐሰቱ ይበዛልና፡፡
ከእግዚአብሔር እንዳትለይ ድኻውን አትግፋው፡፡ ሦስት ጠበብቶች አሉ፥ አንዱ እንደተቻለው የሚተው የሚታገሥ ነገር ኃላፊ ልበ ሰፊ ነው፡፡ ሁለተኛው እያወቀ ዝም የሚል ሦስተኛው ጠቢብ ሲሆን የዋህ ነው፡፡ ልጄ ሆይ ቸኩለህ አትናገር። ነቢይ "ቀባጣሪ አንደበት ሞትን ትጠራለች" ብሏልና፡፡ ወንድሜ ሆይ በአንደበትህ በነገር እንዳትሰናከል ተጠንቀቅ፡፡ በአንደበትህ ከምትወድቅ ወደ ገደል ብትወድቅ ይሻልሃልና፡፡ ቀባጣሪ አንደበት ብዙዎችን አወከቻቸው ከትዳራቸውም ለየቻቸው፡፡ ብዙዎችም ከቤታቸው ወጡ፤ ከሀገራቸው ተሰደዱ ከክብራቸው አነሱ፡፡
(አባ ገብረ ኪዳን - መጽሐፈ ወግሪስ ገጽ 86-84) | 8 606 |
| 15 | በቤትህ ያለው ዳቦ ለተራበው ሰው የሚውል(ንብረቱ) ነው፥ በልብስ ማስቀመጫህ ውስጥ ያለው የማትጠቀመው ኮት የችግረኛው ገንዘቡ ነው፥ በጫማ ማስቀመጫህ ውስጥ አልፈልገውም ብለህ ሊበላሽብህ የሆነው ጫማ የደሃው ጫማ (ጫማ ለሌለው ገንዘቡ) ነው ፥ ያከማቸኸው ገንዘብ ለድሃው የሚገባው ነው....
ዛፍ በፍሬው ይታወቃል፥ ሰውም በድርጊቱ፡፡ መልካም ስራ መቼም አይጠፋም፡፡ መልካም እርዳታን የሚዘራ፥ ወዳጅነትን ያጭዳል፡፡ ደግነትን የሚተክል ፍቅርን ይሰበስባል፡፡
"ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ ብቻ የለብንም፥ ነገር ግን ካነበብነው ተምረን ማደግ አለብን፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ምንም የማይጠቅም ነገር እንዳልተጻፈ ተገንዘብ፡፡
አሁንም ለጥንካሬ፣ ለመታገስ፣ለመዳን፣ለመለወጥ ጊዜ አለህ! ተኝተሃልን? ንቃ! ኃጢአት ሰርተሃልን? እንግዲያውስ መስራቱን አቁም፡፡
ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ | 10 158 |
| 16 | እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ ከሁለቱ እህትና ወንድም ውጭ እስከ አሁን ሌላ በጎ አድራጊ አልተገኘም። | 1 762 |
| 17 | “የምትበላውን ምግብ እንደምትመርጥ ሁሉ፣ የምትናገረውንም ቃል ምረጥ፤ መጥፎ ምግብ ሥጋን እንደሚመርዝ፣ መጥፎ ቃልም ነፍስን ይመርዛል።’
አባ ጴሜን | 11 004 |
| 18 | ሰላም
አንዲት እህት እና አንድ ወንድም ለደብረ ዘመዳ (ጀመዶ ማርያም) ገዳም መነኮሳት የሚሆን የልብስ ንጽህና መጠበቂያ ሳሙና የሚገዛ ገንዘብ አስረክበውኛል።
ይሁን እንጂ የገዳሙን መነኮሳት ግምት ውስጥ በማስገባት የተላከውን መጠን ጨምረን መላክ ብንችል መልካም በመሆኑ፣ እንደተለመደው የበረከቱ ተካፋይ በመሆን የበኩላችሁን እንድታበረክቱ እጠይቃለሁ።
ለበለጠ በውስጥ መስመር @natansolo ማናገር ይቻላል | 4 844 |
| 19 | "ዛሬን ለሰይጣን ነገን ደግሞ ለእግዚአብሔር አትስጡ!"
ታላቁ ቅዱስ ጎርጎርዮስ | 12 220 |
| 20 | ሰላም እንደምን ዋላችሁ/አደራችሁ?
አንዲት እህት እና አንድ ወንድም ለደብረ ዘመዳ (ጀመዶ ማርያም) ገዳም መነኮሳት የሚሆን የልብስ ንጽህና መጠበቂያ ሳሙና የሚገዛ ገንዘብ አስረክበውኛል።
ይሁን እንጂ የገዳሙን መነኮሳት ግምት ውስጥ በማስገባት የተላከውን መጠን ጨምረን መላክ ብንችል መልካም በመሆኑ፣ እንደተለመደው የበረከቱ ተካፋይ በመሆን የበኩላችሁን እንድታበረክቱ እጠይቃለሁ። | 5 903 |
