ru
Feedback
ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

Открыть в Telegram

በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

Канал ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (@beteafework) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 54 659 подписчиков, занимая 957 место в категории Религия и духовность и 586 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 54 659 подписчиков.

Согласно последним данным от 29 июля, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 559, а за последние 24 часа — 25, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 16.70%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 7.96% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 9 128 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 4 350 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 114.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 30 июля, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

54 659
Подписчики
+2524 часа
+1547 дней
+55930 день
Архив постов
የኅሊና ዳኛ እግዚአብሔር በእያንዳንዳችን ኅሊና ውስጥ፣ ኹል ጊዜ ንቁና ትጉ የኾነ ዳኛ ያስቀመጠው ስለ ምንድን ነው ብለኅ ብትጠይቀኝ፣ ከሰው ወገን ይኽን የ'ኅሊና ዳኛ'ን የመሰለ፣ እንቅልፍ የለሽ ዳኛ ስለሌለ ነው ብዬ እመልስልሃለኹ፤ ዳግመኛም፣ የውጪ ዳኞች በገንዘብ፣ በውሸት በመደለል፣ የሐሰት ፍርድ እንዲሰጡ በማስፈራራት፣ እንዲኹም በሌሎች መጠነ ብዙ ምክንያቶች፣ ርቱዕ የኾነ (ያልተዛባ) ውሳኔአቸውን ሊያጣምሙ ይችላሉ፤ የ'ኅሊና ዳኛ'ን ግን በእነዚኽ በገለጽናቸው ምክንያቶች በምንም መንገድ የሚደለል አይደለም፤ ጉቦ ብንሰጠው፣ ልንዋሸው ብንሞክር፣ ብናስፈራራው፣ ሌላ ሌላም ብናደርግ እንኳ፣ ይኽ የ'ኅሊና ዳኛ' ለምናስበውና ለምንሠራው ኀጢአት ምንም ሳይጠመዝዝ እውነተኛ ፍርድን ይሰጣል፤ ኀጢአት የሠራ ሰው፣ ሌላ ሰው ባይወቅሰውም እንኳ፣ ርሱ ራሱ ራሱን ይወቅሳል፤ አንዴ ወይም ኹለቴ ብቻ አይደለም፣ መላ ዘመኑን እየደጋገመ ኅሊናው ይወቅሰዋል፤ ኅጢአት የሠራነው ከረዥም ዘመናት በፊት ሊኾን ይችላል፤ የኅሊናችን ዳኛ ግን ያን የሠራነው ጥፋት ፈጽሞ አይረሳውም። የኅሊና ዳኛ ኀጢአት ከመሥራታችን በፊትም ይኹን በኋላ ምንም ሳይሸፋፍን በግልጽ ይወቅሰናል፡፡ በተለይ ደግሞ ከሠራነው በኋላ፡፡ ኀጢአት በምንሠራበት ሰዓት ግን ይኸን ዳኛ አጥርተን አንሰማውም፡፡ ይኸውም በምንሠራው ክፉ ሥራ ስለምንሰክር ነው፡፡ ኀጢአት መሥራታችንን ባቆምን ጊዜ ግን ወድያው የጸጸት ሽመሉን ይመዠልጣል፡፡ ይኽም በቀጥታ ምጥ ከያዛት ሴት ጋር ተቃራኒ ነው፡፡ እርጉዝ ሴት ምጥ የያዛት ጊዜ እጅግ አስጨናቂ የኾነ ሕመም ይሰማታል፡፡ ከወለደች በኋላ ግን በቃላት ሊገለጽ የማይችል ዕረፍት ይሰማታል፡፡ በወለደችው ልጅ ታላቅ ሐሴት ይሰማታል፡፡ ኀጢአት ስንሠራ ግን ከዚኹ ተቃራኒ ነው፡፡ በሐሳብ የፀነስነውን ኀጢአት በግብር እስክንወልደው ድረስ “ደስታ" ይሰማናል፡፡ ከፉው ልጃችንን (ኀጢአታችንን) በግብር ከወለድነው በኋላ ግን በልጃችን ፊት ከፍተኛ ሐፍረት ይሰማናል፡፡ ምጥ ከያዛት ሴት በላይም ያሰቃየናል፡፡ ስለዚኽ ልጆቼ! ይኽን ከፉ መሻት ከመዠመርያ አንሥተን ከመቀበል እንከልከል፡፡ ከተቀበልነው እንኳ ገና ፍሬ ሳያፈራ ሳለ ከውስጣችን (በገቢር ሳንገልጥ) እንግደለው፡፡ ይኽን ማድረግ ሳንችል ቀርተን ልጃችንን በገቢር ከወለድነው ግን በንስሐና በዕንባ እንዲኹም ራሳችንን በመውቀስ እንግደለው፡፡ (ሰማዕትነት አያምልጣችሁ እና ሌሎች፣ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ገጽ 49-50)

"ዲያብሎስ በእናንተ ላይ እጅግ ክፉ ነገርን በማምጣት አሳዝኖአችኋልን? እናንተም ኢዮብን አብነት አድርጋችሁ እግዚአብሔር ይመስገን በማለት አሳዝኑት፡፡ ዲያብሎስን ድል ማድረግ ስትሹ ይህን መሣርያ ዘወትር ያዙ፤ ምስጋና፡፡" ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

በጸሎት ኃይል የሚያምን አንድ ጽኑዕ ክርስቲያን ነበር፡፡ ይህም ክርስቲያን ጥሪት የሌለው ደሃ፣ የሚበላ የሚቸግረው ረሃብተኛ፣ ልብሱ በላዩ ላይ አልቆ የታረዘ ምስኪን ነው፡፡ ከእለታት አንድ ቀን በጸሎት ሕይወቱ የነበረውን ትጋት በቅርበት ያውቅ የነበረው አንድ ወዳጁ እየተቆጣ 'ቢያንስ ለረሃብህ ማስታገሻ ቁራሽ ዳቦ እንኳን ማሰጠት ካልቻለ የአንተ ጸሎት ፋይዳው ምንድር ነው? ይቅርብህ በቃ! ፈጣሪህ አይሰማህም ማለት ነው' ሲል ተስፋ በሚያስቆርጥ ቃል ተናገረው፡፡ ያም ምስኪን ክርስቲያን እንዲህ ሲል መለሰለት፦ 'እግዚአብሔርማ አልረሳኝም። ለአንዱ ሰው ከዕለት እንጀራው የበለጠ አትርፎ በመስጠት ለእኔ እንዲያካፍለኝ መልእክተኛ አድርጎት ነበር፡፡ ነገር ግን ይህን አደራ የተቀበለው ሰው ዘነጋኝ፡፡ ስለዚህ እግዚአብሔር ሳይሆን አድራሹ ሰው ረስቶኛል!' መጻሕፍት እንደሚያስተምሩን "የዕለት እንጀራችንን ስጠን" የሚለው ጸሎት ለመነኮሳት ሲሆን "ለዕለት"፣ በዓለም ለሚኖሩ ሰዎች ሲሆን ደግሞ "ለዓመት" የሚሆን እንጀራ ስጠን ማለት ነው። ታዲያ ለምን አንዳንዶች ከዓመት የሚተርፍ ብዙ እንጀራ ሲያገኙ፣ ሌሎች ደግሞ ለዕለት እንኳን የሚሆን ቁራሽ ያጣሉ ? መቼም 'ለሰው ፊት የማያዳላ' እግዚአብሔር "አድልዎ ቢኖርበት ነው" ብለን የድፍረት ቃል በእርሱ ላይ አንናገርም። (ሐዋ 10፥34) ይህ የሆነው እንደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርት አትርፈው ያገኙ ሰዎች ምንም የሌላቸውን እንዲረዱ እና መግቦት የባሕርይው የሆነውን አምላካቸውን በጸጋ እንዲመስሉት ነው። በዚሁም ላይ በፈጠራቸው ሰዎች መካከል ያለውን የመተዛዘንና የፍቅር ትስስር የበለጠ ለማጠናከር ነው፡፡ 'የዕለት እንጀራችንን ስጠን ለዛሬ' ብለን የለመንነው አምላክ ከዓመት እንጀራችን በላይ አትርፎ የሚሰጠን፣ የሚበቃንን ያህል ተመግበን በቀረው ለሌሎች አድራሽ መልእክተኞች እንድንሆን ነው። ስለዚህ ይህን የተጣለብንን አምላካዊ አደራ ባለመወጣት ድሆችን አንበድል፤ ተማርረው ከፈጣሪያቸውም ጋር እንዲጣሉ አናድርጋቸው። (ዲያቆን አቤል ካሳሁን)

«ወጣቶች ሆይ፥ ይኸውላችሁ እኔ የማስበውንና ከቀደሙት ሰዎች ትምህርት እንዲሁም ከተፈጥሮ ተሞክሮ ያገኘሁትን ለሕይወታችሁ የሚጠቅም ምክር እነግራችኋለሁ፤ እናንተም ተቀበሉት። ወደዚህ ዓለም ስንመጣ ለዚህ ጊዜያዊ ሕይወት ብቻ አልተፈጠርንም፤ ይልቁንም ዘላለማዊ ለሆነው ሌላው ሕይወት እየተዘጋጀን እንጂ። መጻሕፍትም ቢሆኑ ስለዚሁ ሕይወት ያስተምሩናል። በእርግጥ ከቅዱሳት መጻሕፍት ምስጢራት ጋር እስክንተዋወቅ ድረስ፥ ሙሉ በሙሉ ባይሆንም እንኳ ልክ እንደ ጥላና እንደ መስታወት አድርገን በውጭ ባሉ ዓለማዊ መጻሕፍት (በግሪክ ሥነ-ጽሑፍና ፍልስፍና) አእምሮአችንን እናሰለጥናለን። ስለሆነም የእነዚህን ጸሐፊዎች ጽሑፍ ስታነቡ ወይም ስትሰሙ እንደ ንብ ሁኑ። ንቦች ወደ አበቦች ሲሄዱ ሁሉንም የአበባው ክፍል አይበሉም፤ ወይም አበቦቹ ያሉበትን ቦታ ሁሉ አያጠፉም። ይልቁንም ከእነርሱ መካከል ለማር የሚሆነውን ጣፋጭ ወለላ ብቻ መርጠው ይወስዳሉ፤ ሌላውን ግን ይተውታል። እናንተም እንዲሁ ከዓለማዊ መጻሕፍትና ከፈላስፎች ትምህርት ለነፍሳችሁ የሚጠቅመውን፣ በእውነትና በበጎ ምግባር የሚያንጸውን ብቻ ውሰዱ፤ ወደ እኩይ ተግባርና ወደ ውሸት የሚመራችሁን ግን ወደ ጎን ተዉት። ዛፎች ቅጠል የሚያወጡት ፍሬ ለማፍራት እንደሆነ ሁሉ፥ የሰው ልጅ አእምሮም በእውቀት የሚያብበው በበጎ ምግባር ፍሬ ለማፍራት ነው። ስለሆነም ከእነዚህ ሥነ-ጽሑፎች መልካም አርአያዎችን፣ የጀግኖችን ትዕግሥት፣ የእውነተኛ ሰዎችን ፍትሃዊነትና ትሕትና ተማሩ። አእምሮአችሁን በሚጠቅም እውቀት አበልፅጉት፤ ነገር ግን ዋናው ግባችሁና የእውቀታችሁ ዘውድ የእግዚአብሔርን ሕግ መከተልና ነፍሳችሁን ለዘላለም ሕይወት ማዘጋጀት እንደሆነ ከቶ አትርሱ።» "ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ፣ 'ወጣቶች መጻሕፍትን እንዴት በአግባቡ መጠቀም እንደሚገባ ያስተማረበት ድርሳን' የተወሰደ"

ሰውን የሚያረክሱትን ነገሮች የትኛዎቹ እንደኾኑ እንረዳ እና አንዴ ከተረዳንም በኋላ እንራቃቸው፡: በቤተ ክርስቲያን ውስጥ፤ አብዛኛዎቹ ሰዎች የውጫቸው ንጹህ ኾኖ መታየት እንደሚያሳስባቸው እናያለን፤ ነገር ግን ስለ ንጹህ ልብስ እንጂ በእግዚአብሔር ፊት ንጹህ ልባቸውን ስለማቅረብ አያስቡም፡፡ እጃችሁን ወይም አፋችሁን አትታጠቡ እያልኩ አይደለም ነገር ግን በትክክለኛው መንገድ በመልካም ተግባርና በጎነት ብትታጠቡ ይሻላል፡፡ ስለሌሎች መጥፎ መናገር፤ ጸያፍ ቋንቋ መጠቀም፤ ተገቢ ባልኾኑ ቀልዶች መሳቅ እነዚህ ነገሮች ልብን ያቆሽሹታል፡፡ እንግዲያው፣ ከእነዚህ ነገሮች አንዱንም ካላደረጋችሁ፤ በቅን ልብ ወደ እግዚአብሔር መቅረብ ትችላላችሁ፡፡ እነዚህን ነገሮች ካደረጋችሁ ግን ጸሎታችሁ ትርጉም አይኖረውም፡፡ ርኩሰት የተሸከመ ምላስህንም በውኃ ማጠብህ ትርጉም አይኖረውም። ይህን አስቡ በእጃችሁ ላይ ጭቃ ወይም እበት ቢኖርባችሁ ለመጸለይ ትደፍራላችሁ? በጭራሽ። ነገር ግን የእጅ መቆሸሽ ከልብ መቆሸሽ በላይ የሚያጸይፍ መሆን የለበትም፡፡ ለምንድነው አላስፈላጊ ለኾኑ ነገሮች ትኩረት የምትሰጡት እና አስፈላጊ የኾኑትን ችላ የምትሉት? “አትጸልዩ ነው ወይ የምትለን" ብላችሁ ትጠይቁ ይሆናል። አይ፤ መጸለያችሁን ማቆም የለባችሁም፣ ግን በዚህ ቆሻሻ ሁኔታ ውስጥ መሆን የለበትም፡፡ “ሳላውቅ ኃጢአትን ብሰራ፣ ስህተት ካደረኩ ምን ማድረግ አለብኝ?" እራስህን አጽዳ፡፡ እንዴት? ተጸጸት፣ ለድሆች ስጥ፣ የሰደብከውን ስው ይቅርታ ጠይቅ፣ የበደሉህንም ይቅርታ አድርግላቸው፡፡ እግዚአብሔርን አብዝተህ እንዳታስቆጣ አንደበትህን አጽዳ፡፡ በእጆቹ ጭቃ የያዘ ሰው እግርህን ቢይዝና ገንዘብ ቢጠይቅህ፣ አትሰማውም፤ እንዲያውም ልትገፋው ትችላለህ፡፡ ታዲያ ለምን በዚህ መንገድ ወደ እግዚአብሔር ትቀርባለህ? የሚጸልዩ ሰዎች አንደበት የእግዚአብሔርን ጉልበት እንደሚነካ እጅ ነው፡፡ ስለዚህ አንደበታችሁን አታርክሱ፣ አለዚያ እግዚአብሔር ጸሎታችሁን አልሰማም ይላል፡፡ አንደበት የሕይወትና የሞት ኃይል አለው። ቃላትህ ሊያጸድቁህ ወይም ሊያስኮንኑህም ይችላሉ፡፡ ስለዚህ ምላስህን ከዓይኖችህ የበለጠ በጥንቃቄ ጠብቅ። አንደበት ለንጉሥ እንደ ፈረስ ነው፤ በእርሱም ላይ ልጓም ቢደረግበት፣ ከተቆጣጠሩት እና ከገሩት ለንጉሡ የታመነ ይኾናል፡፡ ነገር ግን እንዲሁ እንዲሮጥ ከፈቀድክ የዲያብሎስ መሳሪያ ይሆናል፡፡ አንደበትህን አታርክሰው፣ በየዋህነት እና በትህትናም አስጊጠው:: ለእግዚአብሔር የሚገባውን አድርጉ፣ አንደበታችሁ በመልካም ቃላት ይሞሉ፤ መልካም ቃል ከስጦታ ይሻላልና፡፡ ለድሆች በደግነትና በቅንነት መልሱ፡፡ የቀረውን ጊዚያችሁን ስለ እግዚአብሔር ሕግጋትና ትምህርቶች በማሰብ አሳልፉ፡፡ ንግግሮቻችሁ ኹሉ በልዑል እግዚአብሔር ህግጋት የተገሩ ይሁኑ፡፡ ራሳችንን አስጊጠን ወደ ንጉሡ እንውጣና በእግሩ ሥር እንውደቅ፣ በአካል ብቻ ሳይኾን በአዕምሯችንም፡፡ ወደ ማን እንደምንሄድ፣ ለምን ዓላማ እና ምን ማከናወን እንደምንፈልግ እንመርምር፡፡ ሱራፌልና ኪሩቤል በዓይናቸው የማያዩት፤ ግርማውን መሸከም ያቃታቸው፣ መዳረሻ አልባ ብርሃን ወደሆነው ወደ እግዚአብሔር እንሄዳለን፡፡ ከገሃነም ለማምለጥ፤ ለኃጢአታችን ይቅርታ ለመጠየቅ፤ ከቅጣት ለመራቅ እና ወደ መንግሥተ ሰማያት (እና በረከቶቿ ኹሉ) ለመግባት ወደ እርሱ እንሄዳለን፡፡ ምንጭ፦ (#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ - #የነፍስ_ምግብ ገጽ 60-62 #በፍሉይ_ዓለም_የተተረጎመ)

#ስለ_ሐሜት_መጥፎነት_ቅዱስ_ኤፍሬም_ያስተማረው የመፍረድ ስልጣን ሳይኖረው በሰው ላይ የሚፈርድ በተመለከተ ጌታችን፡- “እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ በምትፈርዱበት ሰውን ፍርድ ይፈረድባችኋሁ በምትሰፍሩትም መስፈሪያ ይሰፈርባችኋልና” በማለት አስተምሮናል፡፡ (ማቴ.7፥1-2) እንዲሁ የጌታ ወንድም ያዕቆብ “ወንድሞች ሆይ፥ እርስ በርሳችሁ አትተማሙ። ወንድሙን የሚያማ በወንድሙም የሚፈርድ ሕግን ያማል በሕግም ይፈርዳል” (ያዕ.4፥11) ብሎ ጽፎልናል፡፡ ተወዳጆች ሆይ ከጌታ ቃልና ከጌታ ወንድም ከያዕቆብ ምን ተማራችሁ? ጻድቁ ሎጥ በሰዶም ተቀምጦ ነበር፤ ነገር ግን “ጻድቅ ሎጥም በመካከላቸው ሲኖር እያየና እየሰማ ዕለት ዕለት በዓመፀኛ ሥራቸው ጻድቅ ነፍሱን አስጨንቆ ነበር” (2ጴጥ.2፥7-8) ተብሎ እንደተጻፈልን ራሱን በጽድቅ አስጨንቆ ይኖር ነበር እንጂ በማንም ላይ እጁን አልጠቆመም ነበር፡፡ ሐሜት በሰው ላይ መፍረድ ነውና፡፡ ነገር ግን ሐዋርያው ይህን ከጻፈልን በኋላ “ጌታ እግዚአብሔርን የሚያመልኩትን ከፈተና እንዴት እንዲያድን፥ በደለኞችንም ይልቁንም በርኵስ ምኞት የሥጋን ፍትወት እየተከተሉ የሚመላለሱትን ጌትነትንም የሚንቁትን እየቀጣቸው ለፍርድ ቀን እንዴት እንዲጠብቅ ያውቃል” (2ጴጥ.2፥9-10) በማለት ፍርድን መስጠት የእግዚአብሔር ድርሻ እንደሆነ እርሱም በኃጢአተኞችና በዓመፀኞች ላይ አንደሚፈርድባቸው ጽፎልናል፡፡ ስለዚህ ራስን በመግዛትና በትሕትና መመላለስ ጊዜ የሚሰጠው ጉዳይ አይደለም፤ ጊዜውም ዛሬ ነው፡፡ ነገር ግን ሴሰኝነትና ሐሜት ነገ ጽኑ ቅጣትን ይዘው ይመጣሉ፡፡ ጽናትን፣ ትጋትን፣ ራስን በአምላክ ፊት ማዋረድ ዛሬ ገንዘብህ አድርግ፡፡ የድፍረት ኃጢአትን፣ እንቅልፍ መውደድን፣ አለመታዘዝ እነዚህን የመሳሰሉ ነገ ጽኑ ቊጣን የሚያመጡ ናቸውና ካንተ አርቃቸው፤ ከዓለም መለየት፣ ምድራዊ ፈቃዶችን መተው፣ ከጌታ ያለውን ተስፋ ለማግኘት ብለን ከትውልድ ሥፍራችን፣ ከዘመድና፣ ከወዳጅ መለየት ለነገ የማንተዋቸው የዛሬ ተግባራቶቻችን ናቸው፡፡ ሀገር፣ የትውልድ ሥፍራና ርሥት ጉልትን መሻት በብዙ ክፋቶች ውስጥ እንድናልፍ የሚያደርጉን ናቸውና ነገ ክፉ ብድራትን ይዘው እንዳይመጡብን እነዚህን ከመሻት እንራቅ፡፡ የሎጥ ሚስት ወደ ኋላ በመመልከትና በእግዚአብሔር ፍርድ ላይ የማይገባ በመናገሯ የጨው ሐውልት ሆና ቀርታለች፡፡ ይህ በእኛም ላይ እንዳይመጣ ጌታችን "ማንም ዕርፍ በእጁ ይዞ ወደ ኋላ የሚመለከት ለእግዚአብሔር መንግሥት የተገባ አይደለም።" በማለት አስጠንቅቆናልና ጥለነው ወደመጣነው ነገር አንመለስ፡፡ (ሉቃ.9፥62) ስለዚህ ከሁሉ በፊት ሁል ጊዜም ቢሆን ጽድቁንና መንግሥቱን ልታስቀድሙ ይገባችኋል፡፡ ስለ ጌታ ስትሉ ዓለምንና ፈቃዷን ልትተዉ፣ እግዚአብሔር መፍራት በውስጣችሁ ሊያድር፣ በመንፈስም ልትቃጠሉ ይገባችኋል፡፡ ይህን እስከ ዕድሜ ፍጻሜአችሁ ድረስ ጠብቁት፡፡ ቃሉ እንደመሰከረው እስከ መጨረሻ የሚጸና እርሱ ይድናል፡፡ ወደ ኋላ ሳትመለከቱ የሰውን ሳይሆን የራሳችሁን ጉድፍ የምታወጡና በጽናት የምትመላለሱ ከሆነ ስለ ጽናታችሁ ዘለዓለማዊ ሕይወት ዋጋ ሆኖ ይሰጣችኋል። ምክንያቱም ሁሉን ነገር በመናቅ እውነተኛ አምላክ ወደ ሆነው ክርስቶስ ቀርባችኋልና፡፡ ለእርሱ ክብር ይሁን ዛሬም ዘወትርም ለዘለዓለሙ አሜን፡፡ (የትሕርምት ሕይወት ቅዱስ ኤፍሬም እንዳስተማረው ገጽ 95-97 - በመምህር ሽመልስ መርጊያ)

"ከዕለት ጉርስኽ የተረፈኽ ቢኖር ለደኻ ስጠው። . . . ክብር ይግባውና ወደ ፈጣሪ ለመቅረብ እንደ ምጽዋት ክሂል የሚሰጥ የለም። ከሥራም ወገን ወድዶ ሰጥቶ እንደመቸገር በልቡና ኅድዓት (ፀጥታ ፣ ዕረፍት ፣ ሠላም) የሚያደርግ የለም። ሰጥተኽ መጽውተኽ አጥተኽ 'አላዋቂ' ቢሉኽ ይሻልኻል። ጨብጠኽ ይዘኽ አስተዳደር ዐዋቂ ከሚሉኽ።. . . ኅብስቱን ከውሃ ጣለው ብሎ ተናግሯልና። ከውሃ የጣሉት እንዳይመለስ ፣ 'ይ 'ሰጠኛል' ብለኽ አትስጥ ሲል ነው። አንድም ኀብስቱን ከእግዚአብሔር ፊት አኑረው ሲል ነው። በፍጻሜ ዘመንኽ ዋጋኽን ታገኛለኽ። ባለጸጋውን ለይተኽ ለድኻ አትስጥ። 'ይኽ ይገባዋል ይኽ አይገባውም' አትበል። አላ ኩሉ ሰብእ ይኩኑ ዕሩያነ በኅቤከ -በምትመጸውትበት ጊዜ አስተካክለኽ መጽውት እንጂ! አስተካክለኽ በመስጠትኽ ወደ በጎ ሥራ ለማቅረብ ትችላለኽ። ምንም የበቁ ባይኾኑ ነፍስ በመብል በመጠጥ ምክንያት ወደ ክቡር እግዚአብሔር ትሳባለችና! በምጽዋት ጊዜ 'ይኽ አይሁዲዊ ነው። ይኽ ከሀዲ ነው' አትበል። 'ይኽ ነፍሰ ገዳይ ነው' አትበል። ይልቁንስ ብታስታውለው ወንድምኽ ነው እንጂ። አእምሮ አጥቶ ከሃይማኖት ተለየ እንጂ።ከበጎው ነገር ወገን ለሰው ያደረግኽ እንደኾነ መክፈልን አትውደድ።. . . መጽውተኽ ብትቸገር ክብር ይግባውና በእግዚአብሔር ቸርነት ከትካዝ ሥጋዊ ትድናለኽ! ከኹሉ በላይ ትኾናለኽ! ሰው ኹሉ ለገንዘቡ ሲገዛ እሱ ለእግዚአብሔር ይገዛልና። . . . 'በዝናም ያበቀለው በፀሓይ ያበሰለው የእግዚአብሔር ገንዘብ ነው' ብለኽ ምጽዋትኽን በትሕትና መጽውት። ጻድቃን በሚከብሩበት ጊዜ ይቅርታን ታገኛለኽ" (ምንጭ፦ ከመጽሐፍተ መነኮሳት (ማር ይስሐቅ) አንቀጽ ፩ ፣ ምዕ.፲፪፣ ገጽ ፳፩ - ፳፫)

"ጌታ ሆይ እርሻውን አቃጥለህ ሰብሉን ብትባርክ ምን ይጠቅማል? ዛፉንስ ቆርጠህ ቅርንጫፉን ብትባርክ ምን ይረባል? እናቴ እርሻ ናት እኔ ሰብል ነኝ:: እናቴ ዛፍ ናት እኔ ቅርንጫፍ ነኝ:: እባክህን
"ጌታ ሆይ እርሻውን አቃጥለህ ሰብሉን ብትባርክ ምን ይጠቅማል? ዛፉንስ ቆርጠህ ቅርንጫፉን ብትባርክ ምን ይረባል? እናቴ እርሻ ናት እኔ ሰብል ነኝ:: እናቴ ዛፍ ናት እኔ ቅርንጫፍ ነኝ:: እባክህን እናቴ ብትክድ እኔ ባምን ምን ይጠቅማል:: ጌታ ሆይ የእናቴን ልብ በሃይማኖት አጽናልኝ" (ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ስለ እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ የጸለየው ጸሎት) ቅዱስ ቂርቆስ ሆይ አንተ ሕፃን ሆነህ ትልቅ ነበርክ:: ትልቅ ሆነን ሕፃን የሆንን እኛን በምልጃህ አስበን! "የእግዚአብሔር ምስክር የታመነ ነው፤ ሕፃናትን ጠቢባን ያደርጋል" መዝ 19፥7 (#ከዲያቆን_ሄኖክ_ኃይሌ_የተወሰደ)

ቅድስት ኢየሉጣን አላዊው ንጉሥ እስክንድሮስ "ስምሽ ማን ይባላል?" ባላት ጊዜ "#ክርስቲያን እባላለሁ፤ መዋቲ ስሜን ከፈለግህ ግን ኢየሉጣ ይባላል" አለችው። ልጇም ቅዱስ ቂርቆስም ተመሳሳይ ጥያቄ በ
ቅድስት ኢየሉጣን አላዊው ንጉሥ እስክንድሮስ "ስምሽ ማን ይባላል?" ባላት ጊዜ "#ክርስቲያን እባላለሁ፤ መዋቲ ስሜን ከፈለግህ ግን ኢየሉጣ ይባላል" አለችው። ልጇም ቅዱስ ቂርቆስም ተመሳሳይ ጥያቄ በተጠየቀ ጊዜ "ከማይደፈርስ ከንጹህ ምንጭ የተቀዳ ጥሩ ምንጭ ስሜ #ክርስቲያን ይባላል፤ መዋቲ ስሜን ከፈለግክ ግን ቂርቆስ ይባላል" አለ። እኛም ሕያው ስማችንን በገቢር መስክረን ርስተ መንግሥተ ሰማያትን እንድንወርስ አምላከ ኢየሉጣ ወቂርቆስ ይርዳን!!

photo content

#ቅዱስ_ቂርቆስና_እናቱ_ቅድስት_ኢየሉጣ (#ሐምሌ_19) ሐምሌ ዐሥራ ዘጠኝ በዚህች ቀን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ በሰማዕትነት መከራ ተቀበሉ። ይህም ሕፃን ዕድሜው ሦስት ዓመት ሲሆነው ከሮሜ አገር ወደሌላ ሀገር እናቱ ይዛው ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኰንን አገኘችው። ሰዎችም ነገር ሠሩባት ወደርሱ አስቀረባትና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኰንን ሆይ ዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነው ሕፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እርሱን ጠይቅ አለችው። ሕፃኑም ወደአለበት ጭፍራውን ልኮ ወደርሱ አስመጣው ሕፃኑንም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ሕፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው። ሕፃኑም መልሶ አዎ ለእኔ ደስታ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ኀዘንና ልቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏልና አለው እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስከ አስደነገጣቸው ድረስ ንጉሡን መኳንንቱንና ጣዖታቱን ረገማቸው ከብርታቱም የተነሣ አደነቁ። መኰንኑም በአፈረ ጊዜ በየአይነቱ በሆነ ሥቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ሥቃይን አሠቃየው እናቱንም ከርሱ ጋር እንደ እርሱ አሠቃያት እግዚአብሔርም ያለምንም ጉዳት ያነሣቸው ነበር። ብዙዎች አሕዛብም ይህን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማዕትነት ሞቱ የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበሉ። በሕፃኑ ላይም የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት። ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው። ከዚህም በኋላ መኰንኑ በታላቅ የናስ ጋን ውስጥ ውኃ ጨምረው በእሳት ያፈሉት ዘንድ አዘዘ የፍላቱም ድምጽ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ሆነ ያን ጊዜም ፍርሀትና የሃይማኖት ጉድለት በእናቱ ላይ ደረሰባት ሕፃኑም ስለ እናቱ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ። ያን ጊዜ ጌታችን ልቧን ወደ ሰማይ አሳርጎ ለቅዱሳን ሰማዕታት የተዘጋጁ የብርሃን ማደሪያዎችን አየች ከዚህም በኋላ ጸናች እግዚአብሔርንም አመሰገነችው ልጅዋንም ልጄ ሆይ ከእንግዲህ አንተ አባቴ ነህ እኔም ልጅህ ነኝ አለችው። ያቺ ከኔ የተወለድክባትም ቀን የተባረከች ናት አለች ወደዚያ ወደ ጋኑ ውስጥ በገቡ ጊዜም የውኃው ፍልሐት እንደ ንጋት ጊዜ ውርጭ ቀዘቀዘ ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኃይል አቀዝቅዞታልና። ከዚህም በኋላ መኰንኑ ሥጋቸው ተቆራርጦ እስከሚወድቅ ድረስ በመቃጥን ውስጥ አድርገው እንዲጐትቷቸው አዘዘ ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ አዳናቸው መኰንኑም በታላቅ ሥቃይ ያሠቃያቸው ዘንድ አስቦ እስኪመክር ድረስ በወህኒ ቤት ዘጋባቸው። ያን ጊዜም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሕፃኑ ቂርቆስ ወርዶ አጽናናው አረጋጋውም። ስሙን ለሚጠራና መታሰቢያውን ለሚያደርግ ቃል ኪዳን ሰጠው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ሰማዕታት በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። (#ስንክሳር_ዘወርኀ_ሐምሌ ➛ስንክሳር ዘተዋሕዶ ፌስቡክ ገጽ የተወሰደ)

"ለነፍስህ የምታደርግላት ታላቅ ነገር አለ ይኼውም ራስህን በሚገባ መርምረህ ማወቅ ነው።" ቅዱስ ጎርጎርዮስ

ተስፋ መቁረጥና ስንፍና ተስፋ መቁረጥና ስንፍና እጅግ ክፉዎች ናቸውና ከእነዚህ እንራቅ፡፡ “ክፋታቸውስ እንደምን ያለ ነው?” ያልከኝ እንደ ኾነም እንዲህ ብዬ እመልስልሃለሁ፡- ተስፋ መቁረጥ የወደቀው ሰው እንደ ገና እንዲነሣ አይፈቅድለትም፤ ስንፍናም የቆመው ሰው እንዲወድቅ ያደርጓል፡፡ ስንፍና ገንዘብ ያደረግናቸውን መልካም ነገሮች ከማሳጣቱም በላይ ሊመጡ ካሉ ክፉ ነገሮች እንዳንጠበቅ ያደርገናል፡፡ ስንፍና ከሰማያትም ቢኾን ይጥለናል፤ ቀቢጸ ተስፋም ወደ ክፋት ዐዘቅት እንድንሰጥም ያደርገናል፡፡ በእውነት በቀቢጸ ተስፋ ካልተያዝን ከጽኑ ክፋት መመለስ ይቻለናል፡፡ እነዚህ ኹለቱ ምን ያህል ኃይል እንዳላቸው ይበልጥ ታውቅ ትረዳ ዘንድ ምሳሌ ጠቅሼ ልንገርህን? መልካም! ዲያብሎስ መጀመሪያ ላይ መልካም ነበር፤ ከስንፍናና ከቀቢጸ ተስፋ የተነሣ ግን እንደ ገና የማይነሣ ኾኖ ወደ ክፋት ወደቀ፡፡ ዲያብሎስ ጥንቱ መልካም እንደ ነበረ ሲናገር መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ያለውን አድምጥ፡- “ሰይጣን እንደ መብረቅ ከሰማይ ሲወድቅ አየሁ” (ሉቃ.10፡18)፡፡ መብረቅ የሚለው አገላለጽ ዲያብሎስ ከመውደቁ በፊት ምን ያህል ብሩህ ሕይወት እንደ ነበረውና በምን ያህል ቅጽበት እንደ ወደቀ የሚያመለክት ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ ተሳዳቢ፣ አሳዳጅና ነውርን የማያውቅ ሰው ነበር (1ኛ ጢሞ.1፡13)፡፡ ነገር ግን ቀናተኛ ስለ ነበርና ተስፋ ስላልቈረጠ ተነሥቶ መላእክትን የሚተካከል ኾነ፡፡ ይሁዳ ሐዋርያ ነበር፤ ነገር ግን በስንፍና ምክንያት ጌታውን አሳልፎ ሰጠ፡፡ ፈያታዊ ዘየማን ደግሞ እንደዚያ እጅግ ክፉ የነበረ ሰው ቢኾንም ቅሉ ተስፋ ስላልቈረጠ ኹሉንም ቀድሞ ገነት ገባ፡፡ ፈሪሳዊው ሰው ራሱን ከፍ ከፍ ያደርግ ስለ ነበር ከምግባር ማማ ላይ ወደቀ፡፡ ቀራጩ ግን ተስፋ ስላልቈረጠ ከፈሪሳዊውም በልጦ ወደ ምግባር ሰገነት ወጣ፡፡ ስለዚህ ይህን ዐውቀን ዘወትር ከስንፍናና ተስፋ ከመቁረጥ እንራቅ! ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ኃጥእ በደለኛ ነህን? ተስፋ አትቁረጥ! ወደ ቤተክርስቲያን መጥተህም ንስሓ ግባ፡፡ ኃጢአት ሠርተሃልን? እግዚአብሔርን “በድያለሁ” በለው፡፡ “በድያለሁ” ብለህ ለመናዘዝ የሚጠይቅህ ድካምና ጥረት እንደ ምን ያለ ነው? “በድያለሁ [ይቅር በለኝ]” ለማለት የሚጠይቅህ ዓይነት የሕይወት መንገድ ወይም እንደ ምን ያለ መከራ ነው? “በድያለሁ” ብሎ አንዲት ቃል ለመናገር ክብደቱ ምኑ ላይ ነው? ምናልባት ኃጥእ ነኝ ብለህ ራስህን ባትጠራ፥ ዲያብሎስ በዚህ እንደማይነቅፍህ አስበህ ነውን? በፍጹም! እንዲያውም ንስሓ ባትገባ ይህን ከዲያብሎስ የሚመጣ ነቀፋ እንደሚኖር ጠብቅ፡፡ የከሳሽ ግብሩ ንስሓ እንዳትገባ መከልከል በዚያ ንስሓ ባልገባህበት በደልም አንተን መውቀስ ነውና ንስሓ ባትገባ ይህን ጠብቅ፡፡ ስለዚህ ለቅጽበት ያህልስ እንኳን የማይተኛ ከሳሽ እንዳለህ ዐውቀህ ለምን እንዳይወቅስህ አትከለክለውም? ለምን በደልህን ተናዝዘሃት አታስወግዳትም? ኃጢአት ሠርተሃልን? ወደ ቤተ ክርስቲያን ና፡፡ “በድያለሁ” ብለህ ለእግዚአብሔር ንገረው፡፡ እኔ ከዚህ ውጪ ከአንተ የምፈልገው ሌላ ምንም ነገር የለኝም፡፡ መጽሐፍ ሲናገር፡- “ትከብር ዘንድ አንተ አስቀድመህ ኃጢአትህን ተናገር” ይላል (ኢሳ.43፡26)፡፡ ስለዚህ ኃጢአትህን ታስወግዳት ዘንድ ተናዘዛት፡፡ ይህን ለማድረግ ድካም ጥረት አይጠይቅህም፡፡ አንደበተ ርቱዕ መኾን አያሻህም፡፡ ገንዘብ መክፈል አያስፈልግህም፡፡ ወይም እነዚህን የመሰሉ ሌሎች ነገሮች አያስፈልጉህም። አስቀድመህ በደልህን በሰቂለ ሕሊና በነቂሐ ልቡና ኾነህ አስባትና አንዲት ቃል ተናገር፡- “በድያለሁ” ብለህ ተናዘዛት፡፡ (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ "ንስሐና ምጽዋት" ገጽ 28 በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)

ለጾመ ፍልሰታ የፊታችን ነሐሴ ፩ ለሚጀምረው #ጾመ_ፍልሰታ ለአገልግሎት የሚሆን የመባ እጥረት ላለባቸው 4 የገጠር አብያተ ክርስቲያናት የሚውል መባ መለገስ የሚፈልግ በውስጥ መስመር @natansolo ማናገር ይችላል። እግዚአብሔር ይመስገን..በቻናላችን ቤተሰቦች እስከ አሁን 25453 ብር ደርሶልናል።

"ንስሓ ማለት አንድን ምኞት በሌላ መለወጥ ነው።  የኃጢአትንና ሥጋዊ ምኞትን ትቶ ከእግዚአብሔር ጋር ለመኖር መመኘት ነው!"   ብፁዕ አቡነ ሽኖዳ ሣልሳዊ

ለጾመ ፍልሰታ የፊታችን ነሐሴ ፩ ለሚጀምረው #ጾመ_ፍልሰታ ለአገልግሎት የሚሆን የመባ እጥረት ላለባቸው 4 የገጠር አብያተ ክርስቲያናት የሚውል መባ መለገስ የሚፈልግ በውስጥ መስመር @natansolo ማናገር ይችላል። እግዚአብሔር ይመስገን..በቻናላችን ቤተሰቦች እስከ አሁን 15453 ብር አግኝተናል።

ወንድሞቼ ከእናንተ መካከል አንድ አይነ ሥውር ሰው ወደ ጉድጓድ ገብቶ ሊወድቅ ሲል እጁን ዘርግቶ የማይደግፈው ማን ነው? ታድያ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በልቡናቸው ታውረው ወደ ሲዖል ጉድጓድ ለዘለዓለም ሲወድቁ እንደ ምን እጃችንን የበለጠ አይዘረጋም? ወገኖቼ በነፍስም በሥጋም የታመመ ሰውን ስታዩ "ይህ የእኔ ሥራ አይደለም የቀሳውስትና የመነኮሳት ሥራ እንጂ፤ ምክንያቱም ሚስት አለችኝ ልጆችንም አሳድጋለሁ" አትበሉ፡፡ እስኪ ምሳሌ መስዬ ልጠይቃችሁ እናንተም መልሱልኝ፡፡ አንድ ትልቅ በወርቅ የተሞላ ሳጥን ወድቆ ብታዩ "ይህ እኔን አይመለከተኝም ሌሎች መጥተው ያንሡት እንጂ" ትላላችሁን? ግራ ቀኛችሁን አይታችሁ በፍጥነት የምታነሡት አይደለምን? ይህ ወደ ዘለዓለም ጉድጓድ እየወደቀ ያለው ወንድማችሁም ከዚያ ወርቅ በላይ ውድ የእግዚአብሔር ሀብት ነውና አንሡት እንጂ የበለጠ  እንዲወድቅ አትግፋት። እግዚአብሔር ይህን በተመለከተ በአፈ ያዕቆብ እንዲህ ብሏልና፡- "ወንድሞቻችን ሆይ ከእናንተ ወገን ከጽድቅ ወጥቶ የበደለ ቢኖር መክሮ አስተምሮ ከበደሉ የመለሰው ቢኖር ራሱን አንድም ወንድሙን ከሞት እንዳዳነ ይወቅ፡፡ የራሱን አንድም የወንድሙን ብዙ ኃጢአቱን እንዳስተሠረየ ይወቅ፡፡ አንድም የወንድሙን ነፍስ እንዳዳነ ይወቅ።"  (ያዕ. 5፥19-20) (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)