ru
Feedback
ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

Открыть в Telegram

በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡

Больше

📈 Аналитический обзор Telegram-канала ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

Канал ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (@beteafework) языкового сегмента Амхарский является активным участником. Сейчас сообщество объединяет 55 344 подписчиков, занимая 932 место в категории Религия и духовность и 587 место в регионе Эфиопия.

📊 Показатели аудитории и динамика

С момента создания невідомо проект демонстрирует стремительный рост, собрав аудиторию из 55 344 подписчиков.

Согласно последним данным от 27 августа, 2026, канал показывает стабильную активность. За последние 30 дней изменение числа участников составило 707, а за последние 24 часа — 33, при этом общий охват остаётся высоким.

  • Статус верификации: Не верифицирован
  • Уровень вовлечённости (ER): Средний показатель вовлечённости аудитории составляет 17.92%. В первые 24 часа после публикации контент обычно набирает 8.27% реакций от общего числа подписчиков.
  • Охват публикаций: В среднем каждый пост получает 9 919 просмотров. В течение первых суток публикация набирает 4 576 просмотров.
  • Реакции и взаимодействия: Аудитория активно поддерживает контент: среднее количество реакций на один пост — 159.

📝 Описание и контентная политика

Автор описывает ресурс как площадку для выражения субъективного мнения:
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡

Благодаря высокой частоте обновлений (последние данные получены 28 августа, 2026) канал поддерживает актуальность и высокий уровень охвата публикаций. Аналитика показывает, что аудитория активно взаимодействует с контентом, что делает его важной точкой влияния в категории Религия и духовность.

55 344
Подписчики
+3324 часа
+957 дней
+70730 день
Архив постов
ትንሿ ቤተክርስቲያን በኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ ባለትዳሮች በቤታቸው ውስጥ ማድረግ ያለባቸው ቤተ ክርስቲያን መጥተው ያዩትን ነው፡፡ ለምሳሌ፦ 👉 ቤተክርስቲያን ውስጥ የጠዋትና የሰርክ ጸሎት እንዳለ ኹሉ እነዚህ ባለ ትዳሮችም የጠዋትና የሰርክ ጸሎት በቤታቸው ውስጥ ሊኖራቸው ይገባል፡፡ 👉 በቤተክርስቲያን ያለው የኅብረትና የአንድነት ጸሎት እንደ ኾነ ኹሉ፥ ባልና ሚስት ልጆችም ሳይለያዩ አብረው መጸለይ አለባቸው፡፡ 👉 በቤተክርስቲያን ውስጥ ከቅዳሴ በኋላ ትምህርተ ወንጌል እንዳለ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም እራት ከበሉ በኋላ ቃለ እግዚአብሔር ሊማማሩ ይገባቸዋል፡፡ 👉 በቤተክርስቲያን ውስጥ ራሳቸውን ገዝተው የሚኖሩ ትጉሃን መነኰሳት እንዳሉ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም ይህን ትግሃትና ምስጋና ወደ ቤታቸው ይዘዉት ሊኼዱ ይገባቸዋል፡፡ 👉 ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማታ ላይ ኅብስቱን አበርክቶ ሕዝቡን ከመገባቸው በኋላ ወዲያው ወደ መኝታ እንዲኼዱ እንዳላደረገ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም ወደ መኝታቸው ከመኼዳቸው በፊት የቀን ውሎአቸውን መገምገም አለባቸው፡፡ 👉 ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሌሊት ሌሊት ሲጸልይ ያድር እንደ ነበረ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም ሌሊት ላይ ነቅተው መጸለይ ይገባቸዋል፡፡ ሕፃናት ካሉም አብረዋቸው እንዲነሡ ማድረግ ይገባቸዋል፡፡ 👉 በቤተክርስቲያን ጾም እንደሚታወጅ ኹሉ፥ ባልና ሚስትም በቤተ ክርስቲያን ከሚታወጀው ጾም በተጨማሪ ከንስሐ አባቶቻቸው ጋር ተመካክረው በፈቃዳቸው ሊጾሙ ይገባቸዋል፡፡ 👉 በቤተክርስቲያን ውስጥ እንዳለው፥ ባልና ሚስትም የቤታቸውን ግድግዳ፣ መስኮትና በር በመስቀል ሊያስጌጡት ይገባቸዋል፡፡ ማማተብ በማይችሉ ልጆቻቸው ግንባርም አድገው ራሳቸው ማማተብ እስኪችሉ ድረስ እነርሱ ያማትቡላቸው፡፡ ቅዱሳት ሥዕላትም በቤታቸው ውስጥ ሊኖሩ ይገባል፡፡ ቤታቸው ትንሿ ቤተ ክርስቲያን የምትኾነው በዚህ መንገድ ነው፡፡ (ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ገጽ 60 - 61)

ኹሉንም ነገር ለእግዚአብሔር እንስጠው ወርቅን የሚያነጥር ሰው አንዲትን የወርቅ ቅንጣት ወደ እሳት ውስጥ ጨምሮ እጅግ ንጹህ እስክትኾን ድረስ ይጠብቃታል፡፡ እግዚአብሔርም ልክ እንደዚሁ ሰዎች እስኪነጹ፣ እስኪለወጡና ባገኛቸው ነገር ጥቅም እስኪያገኙ ድረስ ፈተና ውስጥ እንዲቆዩ ይፈቅዳል፡፡ ይህ ደግሞ ከጥቅምም እጅግ ከፍ ያለ ጥቅም ነው፡፡ ስለዚህ ፈተና ሲገጥመን ውስጣችን ሊረበሽ ወይም ተስፋ ሊቈርጥ አይገባውም፡፡ ያ ወርቅን የሚያነጥር ሰው በእሳት ውስጥ የጨመራትን የወርቅ ቅንጣት እዚያ ውስጥ ምን ያኽል ጊዜ መቆየት እንዳለባት ያውቃል፤ መቼ ከእሳቱ ሊያወጣት እንደሚገባውም ያውቃል፡፡ እንዲሁ እስከ መጨረሻው በእሳቱ ውስጥ ተጥላ እንድትቀርና በዚያ እንድትቃጠል አይፈቅድም፡፡ እግዚአብሔር ደግሞ ይህን ከወርቅ አንጣሪው በላይ ያውቃል፡፡ መቼ ከርኵሰታችን እንደምንነጻ ያውቃል፡፡ በመኾኑም ራሳችንን በመጣልና ተስፋ በመቁረጥ በክፋት ላይ ክፋት እየጨመርን እንዳንሔድ ሽቶ መቼ ከዚያ ፈተና እንደሚያወጣን ያውቃል፡፡ ስለዚህ ድንገት ያላሰብነው ነገር ቢገጥመን በፍጹም የምናማርር፣ ወይም ተስፋ የምንቈርጥ ልንኾን አይገባንም፡፡ ከዚህ ይልቅ የእነዚህ ነገሮች ምንነትን የሚያውቅ እግዚአብሔርን መጠበቅ፣ እርሱ እስከ ፈቀደው ጊዜ ድረስም ልቡናችንን በእሳት እንዲፈተን ማድረግ ይገባናል፡፡ ምክንያቱም ይህ ነገር በእኛ ላይ እንዲኾን የፈቀደው ለእኛ ጥቅምና በዚያ ውስጥ ኾነን በምናሳየው ጥረት ይበልጥ ሊያከብረን ስለሚወድ ነው፡፡ ይህን በማስመልከትም ጠቢቡ ሰው እንደዚህ ሲል መክሮናል፡- “ልጄ ሆይ! ለእግዚአብሔር ትገዛ ዘንድ ብትሔድ ሰውነትህን ለመከራ አዘጋጅ፤ ልብህን አቅና፤ ኹልጊዜ ታገሥ፤ አታወላውልም፤ በመከራ ብትጨነቅም አትጠራጠር” /ሲራ.2፥1-2/፡፡ “ኹሉንም ነገር ለእግዚአብሔር ስጠው፡፡” ለምን? እግዚአብሔር ከዚያ መከራ መቼ እኛን ማውጣት እንዳለበት ያውቃልና፡፡ ስለዚህ ኹሉንም ለእርሱ ልንሰጥ፣ ዘወትር እርሱን ልናመሰግን፣ ኹሉንም ነገር  ጥቅምም ይኹን ቅጣት በአኰቴት ልንቀበል ይገባናል፤ ይህም ቢኾን ለእኛ ረብሕ የሚኾን ነውና፡፡ አንድ ሐኪም፥ ሐኪም የሚባለው ታካሚውን ገላዉን ሲያጥበውና ሲመግበው እንዲሁም ደስ ወደሚያሰኝ ስፍራ ሲወስደው ብቻ አይደለም፤ በእርሱ (በታማሚው) ሰውነት ላይ የቀዶ ጥገና ምላጭና ቢላ ሲያሳርፍም ጭምር ሐኪም ነው፡፡ አባትም አባት የሚባለው ልጁን ሲንከባከብ ብቻ አይደለም፤ የገዛ ልጁን ከቤት ሲያስወጣው፣ ሲገሥጸው፣ ሲገርፈውም ያው አባት ነው፡፡ ስለዚህ እኛም እግዚአብሔር ከሐኪሞችም በላይ ሰውን ወዳጅ እንደ ኾነ በማወቅ፥ ምን ዓይነት የሕክምና ዓይነት እንደሚሰጠን በጥልቀት አንጠይቅ፤ ወይም ደግሞ ለደረሰብን መከራ እርሱን ተጠያቂ አናድርግ፡፡ ከዚህ ይልቅ እርሱ የወደደውን ነገር  ቅጣትም ይኹን ቅጣት የሌለው ነገር ብቻ ምንም ይኹን ምን በአኰቴት ልንቀበል ይገባናል፡፡ በየትኛውም መንገድም ቢኾን የእርሱ ፈቃድ እኛ እንድንድንና ከእርሱ ጋር አንድ እንድንኾን ነውና፡፡ የትኛው መንገድ ለእኛ እንደሚጠቅምም እርሱ ያውቋል፡፡ እያንዳንዱ ሰው የትኛው መንገድ ወደ እርሱ እንደሚመልሰው ያውቃል፡፡ ኹላችንም እንዴትና በምን ዓይነት መንገድ ልንድን እንደምንችል ያውቃል፡፡ በመኾኑም የሚመራን በዚህ እኛ በምንድንበት መንገድ ነው፡፡ ስለዚህ ወደየትኛውም መንገድ ቢወስደንም ልክ እንደ መጻጉዑ እርሱ እንደሚያዘ’ን ተከትለን መሔድ እንጂ ትልቁ ጉዳያችን በለስላሳና በቀላል አልያም ደግሞ በከባድና በሸካራ ጎዳና እንድንሔድ የሚያዘ’ንን ትእዛዝ መኾን የለበትም (ልንሔድበት የሚገባ’ው መንገድ እርሱ ስለሚያውቀው እንዲሁ መታዘዝ እንጂ የመንገዱን ከባድነት ወይም ቀላልነት የእኛ አጀንዳ ሊኾን አይገባውም፡፡) (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ወደ ኦሎምፒያስ የተላኩ መልእክታት - በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ)

"መላው ዓለምን ያስደነገጡ ታላላቅ መከራዎች ኹሉ መነሻቸው ትዕቢት ነው፡፡" #ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ

"ከራሳቸው ውጪ ደስታን የሚፈልጉ እንደምን ምስኪኖች ናቸው? ደስታን በባእድ ምድር በጉዞ የሚፈልጉ አሉ። በሀብትና በዝና መካከል የሚፈልጉ ወገኖች አሉ፤ በታላቅ ይዞታና በንብረት መካከል የሚፈልጉ አሉ፤ መራራ ፍፃሜ ባላቸው በውበትና በተቃራኒ ፆታ መካከል የሚፈልጉ አሉ። በተመሳሳይ ሁኔታ ደስታን ከራሳችን ውጪ ለመገንባት መሞከር በተደጋጋሚ በመሬት ርእደት በሚናወጥ ሥፍራ ላይ እንደ መገንባት ነው። ደስታ የሚገኘው በእኛው ውስጥ እንጂ ከእኛ ውጪ አይደለም። ምስጉን ማለት ይህን ሁኔታ የተገነዘበ ሰው ነው። ደስታ ማለት የልብ ንፅህና ነው፤ እንዲህ አይነቱን ልብ እግዚአብሔር ማደሪያ ያደርገዋልና። ስለዚህ ንፁህ ልብ ያላቸው ወገኖች ክርስቶስ እንዲህ ይላቸዋል፦ በእነሱ እኖራለሁ፣ በመካከላቸውም እመላለሳለሁ፥ አምላካቸው እሆናለሁ እነሱም ሕዝቤ ይሆናሉ። 2ኛ ቆሮ. 6፥16 እንዲህ አይነት ወገኖች ምን ይጎድልባቸዋል? ምንም። " (አባ ሳራባሙን - የበረሃ ፈርጦች መጽሐፍ ገጽ 14 በመምህር ምትኩ አበራ)

ሦስቱ ጠቢባን ልጄ ሆይ እነርሱ ይጠብቁህ ዘንድ፤ ሕግጋትን ጠብቅ፡፡ ልጄ ሆይ በኃያላንና በጠቢባን ዘንድ ክብር ይሆንልህ ዘንድ በወጣትነት ዘመንህ ታገሥ፡፡ ልጄ ሆይ ሞገስን ይሆንህ ዘንድ የሰማኸውን ነገር ጠብቅ፡፡ ልጄ ሆይ መንፈሳዊ አባትህን ጠይቀው፡፡ እርሱም ጽድቅንና እውነትን ይነግርሃል። ልጄ ሆይ በተሾምክበት ወራት ለድኾች ፍርድ አታጉድል፤ ሰውን ባለጸጋ ነው ብለህ አትፍራው ለዘመዶችህም ፍርድ አታድላ፡፡ ለባለጸጎችም ቢሆን የሰው ሀብቱ ንብረቱ መብዛቱ እያስፈራህ፡፡ እሰከ ዕለተ ሞትህ ድረስ እውነትን ተናገር ጠቢብ ሲራክ እንዲህ አለ፦ ለሰነፍ ራስህን ዝቅ አታድርግ፡፡ እንደ ሀብቱ ብዛት ኃጢአቱም ብዙ ነው፤ በንግግሩ ብዛት ሐሰቱ ይበዛልና፡፡ ከእግዚአብሔር እንዳትለይ ድኻውን አትግፋው፡፡ ሦስት ጠበብቶች አሉ፥ አንዱ እንደተቻለው የሚተው የሚታገሥ ነገር ኃላፊ ልበ ሰፊ ነው፡፡ ሁለተኛው እያወቀ ዝም የሚል ሦስተኛው ጠቢብ ሲሆን የዋህ ነው፡፡ ልጄ ሆይ ቸኩለህ አትናገር። ነቢይ "ቀባጣሪ አንደበት ሞትን ትጠራለች" ብሏልና፡፡ ወንድሜ ሆይ በአንደበትህ በነገር እንዳትሰናከል ተጠንቀቅ፡፡ በአንደበትህ ከምትወድቅ ወደ ገደል ብትወድቅ ይሻልሃልና፡፡ ቀባጣሪ አንደበት ብዙዎችን አወከቻቸው ከትዳራቸውም ለየቻቸው፡፡ ብዙዎችም ከቤታቸው ወጡ፤ ከሀገራቸው ተሰደዱ ከክብራቸው አነሱ፡፡ (አባ ገብረ ኪዳን - መጽሐፈ ወግሪስ ገጽ 86-84)

በቤትህ ያለው ዳቦ ለተራበው ሰው የሚውል(ንብረቱ) ነው፥ በልብስ ማስቀመጫህ ውስጥ ያለው የማትጠቀመው ኮት የችግረኛው ገንዘቡ ነው፥ በጫማ ማስቀመጫህ ውስጥ አልፈልገውም ብለህ ሊበላሽብህ የሆነው ጫማ የደሃው ጫማ (ጫማ ለሌለው ገንዘቡ) ነው ፥ ያከማቸኸው ገንዘብ ለድሃው የሚገባው ነው.... ዛፍ በፍሬው ይታወቃል፥ ሰውም በድርጊቱ፡፡ መልካም ስራ መቼም አይጠፋም፡፡ መልካም እርዳታን የሚዘራ፥ ወዳጅነትን ያጭዳል፡፡ ደግነትን የሚተክል ፍቅርን ይሰበስባል፡፡ "ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ ብቻ የለብንም፥ ነገር ግን ካነበብነው ተምረን ማደግ አለብን፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ ምንም የማይጠቅም ነገር እንዳልተጻፈ ተገንዘብ፡፡ አሁንም ለጥንካሬ፣ ለመታገስ፣ለመዳን፣ለመለወጥ ጊዜ አለህ! ተኝተሃልን? ንቃ! ኃጢአት ሰርተሃልን? እንግዲያውስ  መስራቱን አቁም፡፡ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ

እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ ከሁለቱ እህትና ወንድም ውጭ እስከ አሁን ሌላ በጎ አድራጊ አልተገኘም።

“​​​​የምትበላውን ምግብ እንደምትመርጥ ሁሉ፣ የምትናገረውንም ቃል ምረጥ፤ መጥፎ ምግብ ሥጋን እንደሚመርዝ፣ መጥፎ ቃልም ነፍስን ይመርዛል።’ አባ ጴሜን

ሰላም ​አንዲት እህት እና አንድ ወንድም ለደብረ ዘመዳ (ጀመዶ ማርያም) ገዳም መነኮሳት የሚሆን የልብስ ንጽህና መጠበቂያ ሳሙና የሚገዛ ገንዘብ አስረክበውኛል። ​ይሁን እንጂ የገዳሙን መነኮሳት ግምት ውስጥ በማስገባት የተላከውን መጠን ጨምረን መላክ ብንችል መልካም በመሆኑ፣ እንደተለመደው የበረከቱ ተካፋይ በመሆን የበኩላችሁን እንድታበረክቱ እጠይቃለሁ። ለበለጠ በውስጥ መስመር @natansolo ማናገር ይቻላል

"ዛሬን ለሰይጣን ነገን ደግሞ ለእግዚአብሔር አትስጡ!" ታላቁ ቅዱስ ጎርጎርዮስ

ሰላም እንደምን ዋላችሁ/አደራችሁ? ​አንዲት እህት እና አንድ ወንድም ለደብረ ዘመዳ (ጀመዶ ማርያም) ገዳም መነኮሳት የሚሆን የልብስ ንጽህና መጠበቂያ ሳሙና የሚገዛ ገንዘብ አስረክበውኛል። ​ይሁን እንጂ የገዳሙን መነኮሳት ግምት ውስጥ በማስገባት የተላከውን መጠን ጨምረን መላክ ብንችል መልካም በመሆኑ፣ እንደተለመደው የበረከቱ ተካፋይ በመሆን የበኩላችሁን እንድታበረክቱ እጠይቃለሁ።

ይህ እንዴት ይሆናል https://youtu.be/1Su_MUsFCZU?si=Zqj_WiKqwraTbrT2

"ለበጎ ነው" "አንድ ንጉስ ከአጃቢው ጋር በመሆን ለአደን ይወጣል። ለአደን ሲወጡ ንጉሱ ወጥመድ እያጠመደ እያለ ወጥመዱ አምልጦት እጁን ቆረጠው። በዚህም አጃቢው በማዘን "አይዞህ ንጉስ ሆይ ሁሉ ነገር ለበጎ ነው!" ይለዋል። በዚህም ንጉሱ በንዴት እየጦፈ "የኔ እጅ መቆረጥ ነው ለበጎ?" ይለውና እስር ቤት አሳሰረው። ከብዙ ጊዜ በኋላ ንጉሱ ብቻውን ሀገሩን ሲዞር ሰው አርደው ለጣዖት መሰዋት የሚያደርጉ ጨካኝ ሰዎች ያዙትና አርደው መሰዋት ሊያደርጉት ሲሉ ቆራጣ እጁን አዩት። በእነሱ ህግ መሰዋት የሚያደርጉት ሰዉ ሙሉ ጤነኛ መሆን ስላለበት ለቀቁት። ንጉሱ አጃቢው 'ሁሉ ነገር ለበጎ ነው!' ያለው ትዝ አለውና እስር ቤት ሄዶ ስላሰርኩህ ይቅርታ አርግልኝ! ብሎ ታሪኩን አጫወተው። አጃቢውም "ማሰርህ ለበጎ ነበር! እኔም መታሰሬ ጠቅሞኛል።" አለው። ንጉሱ "እንዴት?" አለው አጃቢውም "ባልታሰር ኖሮ ከአንተ ጋር እሄድና አንተ ቆራጣ መሆንህን ሲያውቁ ይለቁህና አኔን ይገሉኝ ነበር" አለው። ስለዚህ ሁላችንም ስለተደረገልንም ሆነ ስላልተደረገልን እንዲሁም ስለሆነውም ሆነ ስላልሆነው ነገር ሁሉ "ለበጎ ነው" ማለት ይልመድብን፡፡

"ከሐዋርያት ጋር ሆኜ የእመቤታችንን የዕረፍቷንና የክብሯን ነገር በተመለከትኩ ጊዜ፡ ከሰው ህሊና በላይ የሆነ ታላቅ የብርሃንና የመላእክት ምስጋና አየሁ። ሥጋዋም በክብር ወደ ሰማይ ተወሰደ።" (ቅዱስ
"ከሐዋርያት ጋር ሆኜ የእመቤታችንን የዕረፍቷንና የክብሯን ነገር በተመለከትኩ ጊዜ፡ ከሰው ህሊና በላይ የሆነ ታላቅ የብርሃንና የመላእክት ምስጋና አየሁ። ሥጋዋም በክብር ወደ ሰማይ ተወሰደ።" (ቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘአርዮስፋጎስ)

photo content

እኔን ያስደነቀኝ... እመቤቴ ሆይ! እኔን ያስደነቀኝ ከሙታን መካከል ተለይተሽ መነሣትሽ አይደለም፤ ትንሣኤና ሕይወትን በመውለድሽ ነው እንጅ። ሞት በሠለጠነበት ማኅፀን የሕይወት መገኘት እንደምን ይደንቃል?! ድንግል ሆይ! ወደ ሰማይ ከመውጣትሽ ይልቅ የሰማይ ሁለተኛ ተብለሽ መጠራትሽ ይደንቀኛል። ማሕደረ መለኮት በመሆኑ ምድርን ሰማይ ሰማይን ምድር ያደረገ ሰውነትሽ በምድር ተወስኖ ሊኖር እንደምን ይቻላል?! እመብርሃን ሆይ! ልጅሽ የጽድቅ ብርሃን ነው አንች ደግሞ የብርሃኑ መገኛ የፀሐይ ክበብ ነሽ፤ የፀሐይ ክበብ ለጊዜው በተራሮች ራስ ቢጋረድ መልሶ ላይወጣ ኖሯልን? ያንችም ትንሣኤ እንደዚያ ነው። ለጊዜው ሰውነትሽ በመቃብር ውስጥ አደረ ነገር ግን በምሽት የጠለቀችው ፀሐይ በማለዳ እንድትወጣ ያንችም ሰውነት ከመቃብር ወጣ። እመ አምላክ ሆይ! አምላክን የዳሰሱ እጆች፣ መለኮት የተቀመጠባቸው ጉልበቶችሽ፣ ጌታዬ የጠባቸው ጡቶችሽ በመግነዝ እንደታሰሩ ሊቀር ይገባልን? ገፀ መለኮቱን ያዩ ዐይኖች በሞት እንደተከደኑ ትንሣኤ ዘጉባኤን ይጠብቃሉን? ይህስ አይደለም እመቤቴ በሞት ሥልጣን ሥር አይደለችም። የጌታዬ እናት ሆይ! ጥንቱንስ ቢሆን የታቦት ማደሪያው በመቃብር ውስጥ ነውን? ቃሉ የተጻፈባትን የሙሴ ጽላት በመቃብር ውስጥ አለች ብሎ የሚያምን የተረገመ ነው። የአሮን በትር የዘለዓለም የክህነቱ ምልክት ሆና በመቅደስ ልትኖር ከተገባት የሐዲስ ኪዳኑ ሊቀ ካህናት የ ኢየሱስ ክርስቶስ ሊቀ ካህናት ንጉሠ ነገሥት ተብሎ የተሾመባት አማናዊቷ በትረ አሮን በሰማዩ መቅደስ በሕይወት ልትኖር አይገባምን? በነገራችን ላይ ይህንን ታሪክ አምኖ ለመቀበል ከሐዋርያት በጥምቀት መወለድና የሰማዩ የቅዱሳን ኅብረት አባል መሆን ግድ ይላል። ቤተ ክርስቲያናችን የሰማዩ የቅዱሳን ጉባኤ አባል ስለሆነች እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ተነሥታለች፣ ወደ ሰማይ ዐርጋለች ብላ ታምናለች። በሰማይ ያሉ ቅዱሳን እያሸበሸቡ እየዘመሩ ተቀብለዋታል። ይህ በዓል በታቦተ ጽዮን ፊት ሲዘምር ያየነው ዳዊት የዘመረበት ዕለት ነው። ያኔ የበፍታ ኤፉድ ለብሶ የዘመረውን መዝሙር 2 ሳሙ. 6፥14ዛሬ የጽድቅ ካባ ደርቦ ዘመረው። ያኔ የድንግል ማርያም ምሳሌ ለነበረችው ታቦት የዘመረውን መዝሙር ዛሬ በአማናዊቷ ታቦት ፊት አቀረበው። እኔን የሚያስደንቀኝ የእመቤታችን ምሳሌ በነበረችው መቅደስ ሲያገለግሉ የነበሩ ካህናት ሁሉ ዛሬ በአማናዊቷ መቅደስ ፊት ለፊት ቆመው ለማገልገል መብቃታቸው ነው። ሊያዩአት ይመኙ ለነበሩ ሁሉ ዛሬ ተነሥታ በግልጥ አዩአት። ለ እመቤታችን ከተደረገው ይልቅ ለቅዱሳን የተደረገላቸው ብዙ ነው። የእናቱን ትንሣኤ እንደ ልጇ ትንሣኤ አድርጋችሁ የምታከብሩ የጥምቀት ልጆች ሁላችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ወላዲተ አምላክ ማርያም ዐርጋለች። ሊቀ ሊቃውንት ስምዓኮነ መልአክ!

photo content

#ድንግል_ሆይ የአንቺ ሥጋ ይገርመኛል ከሔዋን ተገኝቶ ከመላእክት ይልቅ ንፁህ ሆኗአልና፣ አፈር ነህ ከተባለው ከአዳም ተወልደሽ በሰማይ በአባቱ ቀኝ በተቀመጠው ንጉሥ በክርስቶስ ክቡር ሰውነት ላይ በተለየ ክብር ሆኖ በሰማያት ታይቷልና። ባለ ራዕይው ዮሐንስ ከአንቺ በነሳው ሥጋ ከተወጋው ቁስለቱ ጋር ወደ ሰማይ እንደወጣ ቢያየው እንዲሁ ይመጣል ብሎ በመጽሐፍ ነገረን። የወጉትም ሁሉ ያዩታል ተብሎ ተጻፈ። የታናሿ የአንቺ ገላ ሰማይ ለሚጠበው አምላክ ልብስ ሆነ። መሰወሪያው ከዚህ ነው የማይባለው ልዑል ሥጋሽን ለብሷልና ሥጋ ሆነ ተባለለት። ከባሕሪው እሳት የሆነውን እርሱን ሁሉ ዳሰሰው ሁሉ አቀፈው። መለኮታዊ ክብሩን በአንቺ ሥጋ ውስጥ ቢሰውረው የወደቀው ሰውም አምላክ ሆነ ተባለ። ይደንቃል። #ደንግል_ሆይ መላእክት በቤተልሔም በአንቺ ላይ የሆነውን ቢመለከቱ ስብሐት ለእግዚአብሔር አሉ። ሌላ ምን ይባላል? የማይወርደው ከከፍታው ወርዶ ሲታይ በአድናቆት ስብሐት ነው እንጂ። ሰማይ ከክብሩ የተነሳ የምትጠበውን በአንቺ ክንድ ላይ ሲያዩት ምን ይበሉ? ኦ ማርያም በአንቺ የሆነውን ለመጻፍ የሚያስብ ቃለ ጸሐፊ ከፍቅሩ የተነሣ ብዕሩ በእንባ ስለሚርስ ስለ አንቺ እንዲህ ነው ለማለት ቃልና እቅም በማጣት ሠአሊ ለነ ብሎ ጽሑፉን ይዘጋዋል። አይችልምና። #ልዑሉን_የወለድሽ_ልዕልት_ሆይ የአንቺ ሥጋ ከአቤል ይልቅ ተወደደ፤ ከደገኛው አብርሐም ይልቅ ከፍ አለ፤ ከንጉሡ ከዳዊት ይልቅ ሥጋሽ የተለየና የተመረጠ ሆነ ...ዳዊትም፦ ንጉሥ ደም ግባትሽን ወደደ ብሎ ጻፈልሽ። ከእስራኤላውያን አባት ከያዕቆብ ድንኳን ይልቅ የአንቺ ሥጋ ተመረጠ። ሎጥ፦ መላእክትን ወደ ቤቴ ግቡ ቢላቸው በአደባባይህ እንሆናለን እንጂ አንገባም አሉት። ድንግል ሆይ የአንቺ ሥጋ ግን መላእክትን ለፈጠረ ጌታ ማደሪያ ሆነ። ለዚህ ቃል የለም ዝምታና አንክሮ እንጂ። #ድንግል_ሆይ የአንቺን ሥጋ በመቃብር የለም በአብ ቀኝ እንጂ። አንዳንዶች #ተነሥታለች ለማለት ከበዳቸው። ለመሆኑ ልጅሽ አልዓዛርን ከመቃብር ያስነሣ መሆኑን አላነበቡ ይሆንን? የኢያዒሮስ ልጅን ታሪክ አልተመለከቱ ይሆን አንቺ ግን ወደ ሰማያት ከተነጠቁት ከሄኖክና ከኤልያስ ትበልጫለሽ። #ትንሣኤሽን_የሚያምን_ሁሉ_አሜን_ይበል። #ምልጃሽ #ኢትዮጵያን #ይታደግ። ለዓለም ምሕረት ይሁን ። (Memher abunu mamo መ/ር አቡኑ ማሞ )