ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
Channel ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (@beteafework) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 54 333 subscribers, ranking 982 in the Religion & Spirituality category and 583 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 54 333 subscribers.
According to the latest data from 10 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 707 over the last 30 days and by 6 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 18.94%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.44% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 10 288 views. Within the first day, a publication typically gains 4 585 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 172.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 11 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 11 July | +12 | |||
| 10 July | +12 | |||
| 09 July | +15 | |||
| 08 July | +27 | |||
| 07 July | +24 | |||
| 06 July | +21 | |||
| 05 July | +39 | |||
| 04 July | +32 | |||
| 03 July | +31 | |||
| 02 July | +18 | |||
| 01 July | +31 |
| 2 | ቅዱሳን አባቶቻችን "ሁል ጊዜ ከወደቃችሁ በኋላ ወዲያውኑ መነሳትና ወደ እግዚአብሔር መመለስ አስፈላጊ ነው" ይሉናል፡፡ ሁላችንም ያለማቋረጥ ኃጢአትን እንሠራለን፤ ተንሸራተንም እንወድቃለን፡፡ ምንም እንኳን በቀን መቶ ጊዜ ብንወድቅም ወደ ኋላ ዞር ብለን ሳናይ ተነስተን ወደ እግዚአብሔር መመለስ አለብን የሆነው ሆኗል፤ ያ ጊዜም አልፎአል፡፡ ከእግዚአብሔር እርዳታ እንጠይቅ፤ ተስፋችንን ከውስጣችን ሊያጠፋ ለሚፈልገው ዲያብሎስ፤ "እግዚአብሔር ከእኔ በላይ እኔን ይወደኛል ይቅርም ይለኛል" እንበለው፡፡
(አረጋዊ ታዴዎስ) | 3 112 |
| 3 | ለሥልጣነ ክህነቱ የማይገባ' ካህን ብትመለከት፥ [በደፈናው] ክህነትን አትንቀፍ፡፡ ደገኛ የኾነውን የክህነት ሥልጣን ይዞ ያልተገባ ሥራን ሲሠራ በማየቱ ምክንያት፥ ከዚህ ተነሥቶ ሥልጣነ ክህነትን የሚነቅፍ አንድ ሰውስ እንኳን አይኑር፡፡
የአስቆሮቱ ይሁዳ ጌታችንን አሳልፎ ሰጥቷል፡፡ ይሁዳ እንዲህ በማድረጉ ግን ሐዋርያነት የሚነቀፍ ስለ ኾነ አይደለም፤ የይሁዳ የገዛ ነጻ ፈቃድ ችግር ነው እንጂ፡፡ የሚተቸውም ክህነቱ አይደለም፤ ጠማማው ነጻ ፈቃዱ ነው እንጂ፡፡
ስለዚህ አንተም ክህነትን አትንቀፍ፤ ክህነቱን ላልተገባ ሥራ የሚያውለውን ካህኑን እንጂ፡፡ ...
ሐኪም ሳይኾኑ ሐኪም ነን ያሉት ስንት ናቸው? በዚሁ ምክንያት በመድኃኒት ፈንታ መርዝ የሰጡትስ ስንት ናቸው? እየነቀፍኩ ያለሁት ሙያውን አይደለም፤ ሙያውን በአግባቡ የማይተገብሩትን ነው እንጂ፡፡
መርከቦች እንዲሰምጡ ያደረጉ መርከበኞችስ ስንት ናቸው? ነገር ግን ችግሩ የባሕር ላይ ጉዞ አይደለም፤ ሙያውን እንደሚገባ የማይተገብሩት ሰዎች ችግር ነው እንጂ፡፡
ስለዚህ አንተም አንድ ክፉ ክርስቲያን ብትመለከት በደፈናው የክርስትና ትምህርትን ወይም ሥልጣነ ክህነትን አትንቀፍ፤ ደገኛውን ሥልጣን ላልተገባ ሥራ የሚያውለውን ነው እንጂ፡፡"
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፥ ትንቢተ ኢሳይያስን በተረጎመበት ፬ኛ ድርሳን ላይ ከተናገረው የተወሰደ) | 4 878 |
| 4 | ፮ (መጨረሻ)
በእንተ ንስሐ በቅዱስ አፍርሐት ዘሶርያ
ዳግመኛም እናንተ ተነሳሕያን ሆይ ስሙ! በኃጢአት የወደቀ ሰው ምክሩን ሰምቶ ቢመለስ እግዚአብሔርም ሊያመጣበት ካሰበው ቅጣት ይቅር እንደሚለው፣ ከኃጢአቱም ፊቱን እንደሚመልስ ‹‹አጠፋቸውና እደመስሳቸው ዘንድ በሕዝብ ላይና በመንግሥት ላይ ቁርጥ ነገርን ተናገርሁ፤ ስለ እነርሱ የተናገርሁባቸው ሕዝብ ከክፋታቸው ቢመለሱ፣ እኔ አደርግባቸው ዘንድ ካሰብሁት ክፉ ነገር እጸጸታለሁ›› (ኤር ፲፰፥፯፦ ፲) በማለት ተናገረን፡፡
እናንተ የገነት በር መክፈቻ የያዛችሁ” ሆይ ስሙ! በንስሐ ለመጣ ሰው በያዛችሁት ቁልፍ የመንግሥተ ሰማያትን በር ክፈቱለት፡፡ ስለዚህ የተመሰገነው ሐዋርያ ‹‹ወንድሞቻችን ሆይ ከእናንተ ወገን የተሳሳተ ሰው ቢኖር በመንፈስ ቅዱስ የጸናችሁ እናንተ እንዳትሳሳቱ ለራሳችሁ እየተጠበቃችሁ እንደዚህ ያለውን ሰው ቅንነት ባለው ልቡና አጽኑት›› (ገላ 6፥1) በማለት ይመክራል፡፡
በዚህ ምክሩ ላይም መንጋውን የምትጠብቁ ካህናት ስለ ራሳችሁም መጠንቀቅ እንዳለባችሁ እያስጠነቀቀ ነው፡፡
ሐዋርያው ስለ እራሱ ሲናገርም ‹‹ነገር ግን ለሌላ ሳስተምር እኔ እራሴ የተናቅሁ እንዳልሆን ሰውነቴን አስጨንቃለሁ፣ ሥጋዬንም አስገዛለሁ›› (1ቆሮ 9፡27) በማለት መምህራንም ለሌላው አርአያ መሆን እንጂ መሠናክል መሆን እንደሌለባቸው ይመክራል፡፡ ከእናንተ አንዱ በኃጢአት ቢወድቅ እንደ ጠላት አትዩት፡፡ ነገር ግን እናንተ በወንድማዊ ፍቅር ቀርባችሁ በመምከርና በመገሰጽ ወደ መንገድ መልሱት እንጂ (2ተሰ 3፥15)፡፡
(ቅዱስ አፍርሐት ዘሶርያ - በእንተ ንስሐ ከገጽ 49 ጀምሮ) | 5 480 |
| 5 | መማር ለምትችሉና ፍላጎቱ ላላችሁ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ
በበይነ መረብ (በኦንላይን) የነገረ መለኮት ትምህርት ማስታወቂያ ከሰኔ 1 እስከ 30 2018ዓ.ም ምዝገባ ሲያካሂድ መቆየቱ ይታወቃል፤ ይሁን እንጂ ብዛት ያላቸው አመልካቾች በቀረቡት ጥያቄ መሠረት ከሰበካ ጉባኤ ማቅረብ የሚገባቸውን የድጋፍ ደብዳቤ በወቅቱ ማግኘት ባለመቻላቸው፣ እና ማስታወቂያውን ዘግይቶ የደረሳቸው በመሆኑ ተጨማሪ የምዝገባ ጊዜ እንዲራዘምላቸው ጥያቄ አቅርበዋል።
ኮሌጁም ይህን ጥያቄያቸው ተቀብሎ እስከ ሐምሌ 6 ቀን 2018ዓ.ም ያራዘመ ስለሆነ አመልካቾችም በተሰጣችሁ ጊዜ ተጠቅማችሁ መረጃችሁን በማሟላት ምዝገባውን ማከናወን የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
ኮሌጁ
የምዝገባ የማመልከቻውን ቅጽ ለመሙላት
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://forms.gle/bHGroCYF5a3MDxV19 | 5 058 |
| 6 | ሰዎችን ልታሸንፉ የምትችሉበት የመጀመሪያ መንገድ ፍቅር ነው፡፡ እነርሱን ካልወደዳችሁና በእነርሱ እስካልተወደዳቹ ድረስ ሰዎችን ወደ እግዚአብሔር ልትመሩ አትችሉም ፤ ምክንያቱም ሰዎች ሊሰሙ የሚፈልጉት የሚወዱትን ሰው ነውና። አንድ ሰው የሚርቅህ ከሆነ ከእርሱ ጋር ያለህን ግንኙነት ስለምታጣ እርሱን ወደ እግዚአብሔር መሳብ አትችልም ፤ እርሱ የምትለውን አይሰማህምና። ከዚህ በተቃራኒ አንተ የምትወደው ሰው እግዚአብሔርን በአንተ አማካይነት ሊወድ ይችላል ፤ አንተም በፍቅር ውስጥ ሆነህ እግዚአብሔርን ከእርሱ ጋር ልታስተዋውቅ ትችላለህ፡፡"
(አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ) | 4 501 |
| 7 | በዙሪያህ ያሉትን ሰዎችና ዓለምን ለመለወጥ ከመልፋትህ በፊት የራስህን ሕይወት ለማቅናት ትጋ። አንተ ራስህ በሰላምና በፍቅር ስትሞላ፣ በአጠገብህ ያሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ያንተን መንፈሳዊ ብርሃን አይተው በራሳቸው ይለወጣሉ። ሰውን መለወጥ የሚቻለው በነቀፋ ሳይሆን በራስ ሕይወት ምሳሌነት ነው።"
(ቅዱስ ሴራፊም) | 4 440 |
| 8 | ፭
በእንተ ንስሐ በቅዱስ አፍርሐት ዘሶርያ
እንግዲህ ወዳጆች ሆይ ሰው ኃጢአቱን ተናዝዞ ሲተዋት ምንኛ መልካም እንደሆነ ተመልከቱ! አምላካችን ንስሓን የሚንቅ አይደለምና፡፡ የነነዌ ሰዎች በደላቸው በበዛች ጊዜ እግዚአብሔር ነቢዩ ዮናስን ልኮ እንደሚያጠፋቸው ነገራቸው፤ እነርሱም የነቢዩን ስብከት ሰምተው ንስሐ ገቡ፡፡ እግዚአብሔርም ጥፋታቸውን ትቶ በምሕረት ዓይኖቹ ተመለከታቸው (ዮና 1፥2 ፣ 3፥1-6)፡፡
የእስራኤል ልጆችም ኃጢአትን ባበዙ ጊዜ ወደ ንስሐ ይመለሱ ዘንድ ተናግሯቸዋል፡፡ እነርሱ ግን አልተቀበሉትም፡፡ ስለዚህም በነቢዩ በኤርምያስ ‹‹ክዳተኞች ልጆች ሆይ! ተመለሱ፤ ቁስላችሁንም እፈውሳለሁ» (ኤር. 3፥22) አለ፡፡ ዳግመኛም በኢየሩሳሌም ጆሮ ‹‹ከዳተኛይቱ እስራኤል ወደ እኔ ተመለሽ›› (ኤር.3 ፥12) አለን፡፡
የእስራኤል ልጆችን ‹‹ልባችሁን አድሱ በእሾህም ላይ አትዝሩ። እናንተም የይሁዳ ሰዎች በኢየሩሳሌም የምትኖሩ ሆይ ስለ ሥራችሁ ክፋት ቁጣዬ እንደ እሳት እንዳይወጣ የሚያጠፋውም ሳይኖር እንዳይነድ ለአምላካችሁ ተገረዙ፤ የልባችሁንም ሸለፈት አስወግዱ›› አለ (ኤር.4፥3-4)፡፡
እነርሱ አልመለስ ስላሉም ባሏን ትታ በሔደች ሴት ምሳሌነት ‹‹ሰው ሚስቱን ቢፈታ ከእርሱም ዘንድ ሔዳ ሌላ ወንድ ብታገባ በውኑ ደግሞ ወደ እርሱ ትመለሳለችን? ያቺ ሴት እጅግ የረከሰች አይደለችምን? አሁንም እንደ ጌታሽና እንደ አባትሽ፤ እንደ ልጅነት ባልሽም አልጠራሽምን? ቁጣው ለዘለዓለም ይኖራልን? እስከ ፍጻሜስ ድረስ ይጠብቀዋልን?... ከዳተኛይቱ እስራኤል ያደረገችውን አየህን? ወደ ረዘመው ተራራ ሁሉ ወደ ለመለመ ዛፍም ሁሉ በታች ሔደች፤ በዚያም አመነዘረች፡፡ ይህንም ሁሉ ካደረገች በኋላ ወደ እኔ ተመለሽ አልኳት፤ ነገር ግን አልተመለሰችም›› (ኤር ፫፥፮፦ ፯) በማለት ወደ እርሱ ይመለሱ ዘንድ ወቀሳቸው፡፡
ሆኖም አሁንም ቢሆን እንደማይተዋቸው ሲነግራቸው ‹‹ወደኔ ተመለሱ እኔም ወደ እናንተ እመለሳለሁ›› (ሚል ፫ ፥፯፤ ኤር ፫ ፥ ፲፪) በማለት እንደጠራቸው፣ ንስሐቸውንም ተቀብሎ እንደሚምራቸው ነገራቸው። ዳግመኛም በእናንተ ላይ ያወጣሁትን ህግ እሽራለሁ። አለ።
እናንተም ተነሳሕያን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ በነቢዩ አድሮ ሁሉም በሥርዓት እንዲኖሩ ‹‹ዳድቅ ከጽድቁ ተመልሶ ኃጢአት ቢሠራ ይሞትበታል፡፡ ኃጢአተኛውም ከኃጢአቱ ተመልሶ ፍርድንና ጽድቅን ቢያደርግ በሕይወት ይኖርበታል›› (ሕዝ ፴፫ ፥ ፲፰) በማለት ጻድቁ ከጽድቅ ሥራው ተመልሶ ኃጢአት እንዳይሠራ ሲያስጠነቅቅ ለኃጢአተኞች ደግሞ የንስሐን ተስፋ ሰጠ፡፡
ዳግመኛም በነቢዩ ሕዝቅኤል ‹‹ከአፌ ቃሌን ስማ፤ ከእኔም ዘንድ አስጠንቅቃቸው፡፡ ኃጢአተኛውን ኃጢአተኛ ሆይ በእርግጥ ትሞታለህ ባልሁ ጊዜ ኃጢአተኛውን ከክፉ መንገዱ ታስጠነቅቅ ዘንድ ባትናገር፤ ያ ኃጢአተኛ በኃጢአቱ ይሞታል፤ ደሙን ግን ከእጅህ እፈልጋለሁ›› (ሕዝ ፫፥፲፯) ምክንያቱም አላስጠነቀቅኸውምና፡፡ ‹‹ነገር ግን ከመንገዱ ይመለስ ዘንድ ኃጢአተኛውን ብታስጠነቅቀው እርሱም ከመንገዱ ባይመለስ በኃጢአቱ ይሞታል፤ አንተ ግን ነፍስህን ታድናለህ›› (ሕዝ ˚ ፫ ፥፲፯-፳፩) በማለት ሁሉም ሰው ኃጢአተኛውን ከኃጢአቱ እንዲመለስ መምከር እንዳለበት ተናገረ፡፡
ይቀጥላል.....
(ቅዱስ አፍርሐት ዘሶርያ - በእንተ ንስሐ ከገጽ 49 ጀምሮ) | 4 901 |
| 9 | ፬
በእንተ ንስሐ በቅዱስ አፍርሐት ዘሶርያ
ታክሞ ከበሽታው የዳነ ወታደር ግን ቀድሞ የቆሰለበት ቦታ ላይ ዳግመኛ እንዳይወጋ ይጠነቀቃል፡፡ ምክንያቱም ቀድሞ የተወጋበት ቦታ ላይ ዳግመኛ ከተወጋ ለባለ መድኃኒቱ ቁስሉን ማዳን አዳጋች ይሆንበታልና፡፡ ቁስሉ እንኳ ቢድን ጠባሳው ይቀራል፡፡ በዚህ ጊዜ ታማሚው ከቁስሉ ቢንድን እንኳ ዳግመኛ የጦሩን ልብስ መልበስ አይችልም፡፡ ደፍሮ የጦሩን ልብስ ከለበሰ ደግሞ እራሱን ለወቀሳ አሳልፎ እንደሰጠ ሁሉ ይጸጸታል፡፡
እናንተ የክርስቶስን የጦር ዕቃ የለበሳችሁ ሆይ እንግዲህ ተሸንፋችሁ በጦርነቱ ውስጥ እንዳትወድቁ የጦርነትን ጥበብ ተማሩ! ጠላታችን ተንኮለኛና ጥበበኛ ነውና፡፡ ነገር ግን ክንዱ ከክንዳችን የደከመ ነው፡፡
ስለዚህ ከእሱ ጋር ወደ ጦርነት እንገባ ዘንድ ይገባናል፡፡ ለማሸነፍ ግን ሁል ጊዜ ዝግጁዎች ሆነን መጠበቅ አለብን፡፡ ጠላታችን ከእኛ ጋር ሲዋጋ ለእኛ አይታየንምና፡፡ ውጊያችን እንደ እኛ ሥጋና ደም ካለው ጋር አይደለም፡፡ ስለዚህ ጠላታችንን ወደሚያየው እንጠጋ፡፡ እርሱ ከእኛ ያርቀዋል፡፡
እንግዲህ እናንተ በጦርነት ውስጥ የተወጋችሁ ሆይ አጥብቄ እመክራችኋለሁ፡- ‹‹በጦርነቱ ውስጥ ወደቅን›› ማለትን አትፈሩ! መድኃኒቱን በነፃ ውሰዱ፡፡ ንስሓ ግቡ፤ ክፉ ሳያገኛችሁ በፊት በሕይወት ኑሩ፡፡ እናንተ ባለ መድኃኒቶች (ካህናት) ሆይ በጥበበኛው ሐኪማችን መጽሐፍ" ላይ ጥበበኛው ባለ መድኃኒት ኃጢአተኞችን እንደማይተዋቸው እንደ ተናገረ ላስታውሳችሁ!
አዳም በበደለ ጊዜ ‹‹አዳም ወዴት አለህ?›› ብሎ ወደ ንስሓ ጠራው (ዘፍ 3፥8)፡፡ አዳም ግን ልቡናን ከሚመረምር ከእርሱ ኃጢአቱን ሰወራት፡፡ ስለዚህ ባሳሳተችው ሔዋን ላይ እርግማን ወረደባት፡፡ አዳምም ኃጢአቱን ባለመናዘዙ በእርሱ እና በልጆቹ ሁሉ ላይ ሞት ተፈረባቸው (ዘፍ 3፥10-19)፡፡
ቃየል በተንኮል የተሞላ ነውና ያቀረበው መስዋዕት በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነትን አላገኘም፡፡ እግዚአብሔርም የንስሓ ጊዜን ሰጠው፡፡ እርሱ ግን አልተቀበለም፡፡ እግዚአብሔርም “መልካም ብታደርግ ፊትህ የሚበራ አይደለምን? መልካም ባታደርግ ግን ኃጢአት በደጅ ታደባለች።” አለው (ዘፍ 4፥7)፡፡
ቃየልም በልቡናው ክፋት ተነሳስቶ ወንድሙ አቤልን ገደለውና ‹‹በምድር ላይ የተረገምህ ነህ፣ ምድርን ባረስህ ጊዜ እንግዲህ ኃይሏን አትሰጥህም፤ በምድር ላይ ኮብላይና ተቅበዝባዥ ትሆናለህ›› (ዘፍ 4፥11-12) ተብሎ ተረገመ፡፡ በኖኅ ጊዜ ለነበሩ ሰዎችም ንስሓ ይገቡ ዘንድ መቶ ሃያ ዓመታትን ሰጣቸው (ዘፍ 6፥3)፡፡ እነርሱ ግን ንስሓ አልገቡም፡፡ መቶው ዓመት ሲጠናቀቅም አጠፋቸው (ዘፍ 7፥23)፡፡
ይቀጥላል.....
(ቅዱስ አፍርሐት ዘሶርያ - በእንተ ንስሐ ከገጽ 49 ጀምሮ) | 5 704 |
| 10 | ሰኔ ሠላሳ በዛሬዋ ዕለት፦ ገና በእናቱ ማኅፀን ሳለ ለጌታ የሰገደ፣ በኋላም በዮርዳኖስ ጌታን ያጠመቀ፣ በመወለዱ ብዙዎች የተደሰቱበት፤ አባቱ ስሙን ሲያወጣ አንደበቱ የተከፈተለት፣ ከሄሮድስ እጅ ነጥቆ የእግዚአብሔር መልአክ ወደ በረሃ የወሰደውና በበረሃ ያደገው፤
በነቢዩ ኢሳይያስ "በምድረ በዳ የሚጮኽ ድምፅ"፣ በነቢዩ ሚልክያስም "መንገድህን የሚጠርግ መልእክተኛ" ተብሎ ትንቢት የተነገረለት፣ በጌታችንና በመድኃኒታችንም "ሴቶች ከወለዱአቸው ከእርሱ የሚበልጥ የለም" ብሎ የተመሰከረለት፤
የማይዳሰሰውን ሲዳስስ "በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው" የሚለውን የአብን ድምፅ የሰማ፣ መንፈስ ቅዱስም በክርስቶስ ራስ ላይ ሲወርድ ያየ፣ ኋላም በሰማዕትነት ያረፈው እርሱ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የተወለደበት ቀን ነው።
የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ በረከቱ ለዘላለሙ ከእኛ ጋር ትኑር፣ አሜን። | 7 648 |
| 11 | ፫
በእንተ ንስሐ በቅዱስ አፍርሐት ዘሶርያ
እናንተ የጥበበኛው ባለ መድኃኒት ተከታዮች የሆናችሁ ሐኪሞች ሆይ መዳን ለሚገባው መድኃኒት ትሰጡ ዘንድ ይገባችኋል፡፡ ቁስሉን ለሚያሳያችሁ ሁሉ የንስሓን መድኃኒት ስጡት፡፡በሽታውን ለመናገር ለሚያፍርም ቢሆን ሕመሙን ተናግሮ ድንኅነትን እንዲያገኝ እርዱት፤ ምከሩት፡፡
እርሱ 'ሲነግራችሁም ለሌላው አሳልፋችሁ አታጋልጡ፡፡ ምክንያቱም በጠላትና በሚጠሏቸው ዘንድ በዚህ ሰው ምክንያት ደኅና የሆነው ሁሉ የቆሰለ መስሎ እንዳይታይ ነው፡፡ ጠላት ወታደሮቹ እየወደቁ መሆኑን ባየበት አቅጣጫ በዚያ ያለ የጦር መስመር ከሁሉም መስመሮች ደካማ መስሎ ይታየዋል።
ስለዚህ በጦርነት ውስጥ የጠላት ቀስት አግኝቷቸው የጣላቸውን የጠላት ቀስት ያላገኛቸው ወታደሮች የወደቁትን ቁስለኞች ቁስል እያሰሩ ጠላት እንዳያያቸው ማድረግ ይገባቸዋል፡፡
ነገር ግን በጠላት ቀስት የተመቱ ቁስለኞች እንዳሉ ከተጋለጠ ለሁሉም ሰራዊት መጥፎ ስም ይሰጠዋል፤ የጦሩ መሪ የሆነው ንጉሡም ሰራዊቱን አጋልጦ በሰጠው ሰው ይናደዳል፡፡ ስለዚህም በጠላት ጦር ተመትተው ከወደቁት ይልቅ በሚከፋ ቁስል ይመታዋል፡፡
የጠላት ፍላጻ ያገኛቸው ሰዎች ደዌአቸውን ለባለ መድኃኒቶች ለማሳየት ፈቃደኞች ካልሆኑ ግን ባለ መድኃኒቶቹ ‹በቁስላቸው የደከሙትን አላዳናችሁም› የሚል ወቀሳ የለባቸውም፡፡ የቆሰሉትም ቢሆኑ ቁስላቸውን ደብቀው የጦሩን ልብስ መልበስ አይችሉም። ምክንያቱም የቁስላቸው ደዌ መላ ሰውነታቸውን መርዟልና፡፡
ሰውነታቸው ተመርዞ እያለ የጦሩን ልብስ ለብሰው ወደ ውጊያው ቢገቡም ቁስላቸው አመርቅዞ ክንዳቸው ይዝልና በውጊያው ውስጥ ይገደላሉ፡፡ በአስከሬናቸው ላይም የቀደመ ቁስል በተገኘባቸው ጊዜ ሁሉም ይሳለቅባቸዋል፡፡ ‹‹በደለኛና አታላይ›› ናቸው በመባልም አስከሬናቸው ወደ ውጭ ይጣላል፡፡
ይቀጥላል.....
(ቅዱስ አፍርሐት ዘሶርያ - በእንተ ንስሐ ከገጽ 49 ጀምሮ) | 6 572 |
| 12 | ሰላም ቤተሰቦች
➛ 1 ተአምረ ማርያም ባለ 366ቱ ተአምር
➛ 1 ተአምረ ኢየሱስ
➛ 1 ስንክሳር የዓመቱ
➛ 1 ሃይማኖተ አበው
➛ አጣን
➛ ዘቢብ
➛ የሰም ጧፍ
ለእመቤታችን ቤተክርስቲያን ያስፈልጋል!
ፈቃደኛ የሆናችሁ በውስጥ መስመር @natansolo ኑ።
እስከ አሁን 12,712 ብር ደርሶልናል። | 5 858 |
| 13 | የከዳህን ሰው በተንኮል ለመበቀል አትጣጣር። በቀልን ለእግዚአብሔር ተወው። አንተ ክፋትን በክፋት ለመመለስ ስትነሣ፣ የጠላትን መንገድ እየተከተልክ ነው ማለት ነው። ክርስቲያን ግን ክፉ ላደረጉበት እንኳ መልካም ምኞትንና ጸሎትን በመስጠት ክፋትን በጥሩነት የሚያሸንፍ የብርሃን ልጅ ነው።"
ቅዱስ እንጦንስ | 7 094 |
| 14 | ሰላም ቤተሰቦች
➛ 1 ተአምረ ማርያም ባለ 366ቱ ተአምር
➛ 1 ተአምረ ኢየሱስ
➛ 1 ስንክሳር የዓመቱ
➛ 1 ሃይማኖተ አበው
➛ አጣን
➛ ዘቢብ
➛ የሰም ጧፍ
ለእመቤታችን ቤተክርስቲያን ያስፈልጋል!
ፈቃደኛ የሆናችሁ በውስጥ መስመር @natansolo ኑ።
እስከ አሁን 12,712 ብር ደርሶልናል። | 6 800 |
| 15 | ፪
በእንተ ንስሐ ➛ በቅዱስ አፍርሐት ዘሶርያ
በጦር ሜዳ ተሰልፈው የሚዋጉ ወታደሮች ከጠላታቸው የተወረወረ ቀስት ባገኛቸው ጊዜ፣ ባቆሰላቸውም ጊዜ ድኅነት ለማግኘት ብለው ፈውስ ሊሰጥ ለሚችል ባለ መድኃኒት እራሳቸውን ያሳያሉ፡፡ በጦር ሜዳ የቆሰለውን ወታደር ከቁስሉ ያዳነው ባለ መድኃኒትም ከንጉሡ ሽልማትን ያገኛል፡፡
ወዳጆች ሆይ በተጋድሎው ውስጥ ጠላት መጥቶ ያገኘው፤ የነደፈውም ቢኖር የንስሐ መድኃኒት ሊወስድ ይገባዋል፡፡ በጠላት የተመታ ሰውም በንስሓ ታላቅ ይሆናል፡፡ ምክንያቱም እግዚአብሔር የተጸጸተውን፣ እራሱንም ያዋረደውን አይተውምና።
ስለዚህ በነብዩ ሕዝቅኤል ‹‹እኔ ሕያው ነኝና ኃጢአተኛው ከመንገዱ ተመልሶ በሕይወት ይኖር ዘንድ እንጂ ኃጢአተኛው ይሞት ዘንድ አልፈቅድም›› (ሕዝ ፴፩፥፲፩) በማለት ተናገረ፡፡
በውጊያ ላይ የቆሰለ ወታደር ቁስሉ ይድንለት ዘንድ ለሐኪም ማሳየትን አያፍርም፡፡ ንጉሡም ቢሆን ከቁስሉ የዳነን ወታደር ወደ ሰራዊቱ መልሶ ይቆጥረዋል እንጂ አይተወውም፡፡ እንደዚሁ ሁሉ ጠላታችን ሰይጣን ያገኘው፣ በኃጢአት የጣለው ሰውም ኃጢአቱን በመናዘዝ የንስሐን መድኃኒት ተቀብሎ መዳንን ማፈር የለበትም፡፡
ቆስሎ ቁስሉን መናገር ያፈረና በቶሎ መድኃኒት ያልተደረገለት ወታደር ቁስሉ ወደ ካንሰር ይለወጥና አመርቅዞ መላ ሰውነቱን በመምታት ይጎዳዋል፡፡ ጉዳቱን ቶሎ የተናገረ ታማሚ ግን ታክሞ በመዳን ወደ ጦር ሜዳው ይመለሳል፡፡ ቁስሉን ባለመታከሙ ወደ ካንሰር የተለወጠበትና ያመረቀዘበት ሰው ግን ሊድን አይችልምና ወደ ጦር ሜዳው ሊመለስ አይችልም፡፡
እንደዚሁ ሁሉ በተጋድሎ ውስጥ ያለ ሰው እንደ ወታደር ነው። በተጋድሎ ውስጥ ያለ ሰው በኃጢአት ወድቆ "በኃጢአት ወድቄአለሁ" ብሎ የተናዘዘ የንስሓን መድኃኒት ያገኛል፡፡ ኃጢአቱን የደበቀ ግን ሊድን አይችልም፡፡ ምክንያቱም ታማሚው መድኃኒት አግኝቶ ከቍስሉ ሁሉ ይድን ዘንድ በሽታውን ሁለት ዲናር ወስዶ ለሚያክመው ባለ መድኃኒት አልተናገረምና።"
ይቀጥላል.....
(ቅዱስ አፍርሐት ዘሶርያ - በእንተ ንስሐ ከገጽ 49 ጀምሮ) | 7 857 |
| 16 | ሰላም ቤተሰቦች
➛ 1 ተአምረ ማርያም ባለ 366ቱ ተአምር
➛ 1 ተአምረ ኢየሱስ
➛ 1 ስንክሳር የዓመቱ
➛ 1 ሃይማኖተ አበው
➛ አጣን
➛ ዘቢብ
➛ የሰም ጧፍ
ለእመቤታችን ቤተክርስቲያን ያስፈልጋል!
ፈቃደኛ የሆናችሁ በውስጥ መስመር @natansolo ኑ።
እስከ አሁን 12,712 ብር ደርሶልናል። | 6 472 |
| 17 | ፩
በእንተ ንስሐ ➛ በቅዱስ አፍርሐት ዘሶርያ
ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማያት ወርዶ ሥጋችንን በመዋሐድ እንደ እኛ ሰው ቢሆንም ፍጹም ኃጢአት የሌለበት ነው። እርሱ እራሱን አስመልክቶ ‹‹እኔ ዓለሙን ድል ነስቼዋለሁ›› (ዮሐ ፲፮፥፴፫ ) በማለት ኃጢአት የሌለበት እንደ ሆነ ተናገረ፡፡
ጌታችን ፍጹም ኃጢአት የሌለበት መሆኑን ነብዩ ‹‹የእውነት ሕግ አፉ ውስጥ ነበረች፤ በከንፈሩም ውስጥ በደል አልተገኘበትም›› (ሚል ፮፥፪) በማለት ተናገረ፡፡ የተመሰገነው ሐዋርያም ‹‹ኃጢአት የሌለበት እርሱ እኛን ለእግዚአብሔር ያጸድቀን ዘንድ ስለ እኛ ራሱን እንደ ኃጥእ አድርጓልና›› (፪ቆሮ ፭፥፳፩) አለ፡፡
እንግዲህ ኃጢአትን አንስቶ በመስቀሉ ላይ ሊቸነክር እንጂ እርሱ ኃጢአት ያልሠራ እንዴት ራሱን እንደ ኃጥእ አደረገ?
ዳግመኛም ሐዋርያው ‹‹በእሽቅድምድም ስፍራ የሚሽቀዳደሙ ሁሉ እንደሚፋጠኑ አታውቁምን? ለቀደመው የሚደረግለት ዋጋ አለ፤ እንዲሁ እናንተም እንድታገኙ ፈጽማችሁ ሩጡ›› አለ (፩ቆሮ ፱፥ ፳፬) አለን፡፡
ከአዳም ጀምሮ ኃጢአት በሰው ልጆች ላይ ሠልጥኖ ነበር፡፡ ምክንያቱም ሕግን ከተላለፈ የመጀመሪያው ሰው ከአዳም ጀምሮ ኃጢአት ያልገዛው የለምና፡፡ ብዙዎቹን ነድፏል፣ ብዙዎቹንም አግኝቷቸዋል፣ ብዙዎቹንም ገድሏል፡፡ መድኃኒታችን የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሞቱ ሞትን እስኪደመስሰው ድረስ፣ ኃጢአት ያላጠፋው የሰው ልጅ አልነበረም (1ቆሮ.15፥55-57)። በመስቀል ላይ በተቸነከረበት ጊዜም ክንዱ እስኪሰበር፣ እስከ መጨረሻው ሰዓት ድረስ ብዙዎቹን ሲገርፍ ነበር፡፡
ለሁሉም በሽታ መድኃኒት አለ፤ ጥበበኛ ሐኪም ያየው ቁስልም ይድናል፡፡ እንግዲህ በተጋድሎአችን ውስጥ ጠላት ያገኘው ቢኖር የንስሐ መድኃኒት አለለት፡፡ እሱን መድኃኒት ቁስላቸው ላይ ያፈሰሱ ሰዎች ድኅነትን ያገኛሉ፡፡ እናንተ የጥበበኛው ሐኪማችን ተከታዮች የሆናችሁ ባለ መድኃኒቶች ሆይ ይህንን መድኃኒት ውሰዱ፡፡ በዚህ መድኃኒትም በቍስል የተመታውን ታድናላችሁና፡፡
ይቀጥላል.....
(ቅዱስ አፍርሐት ዘሶርያ - በእንተ ንስሐ ከገጽ 49 ጀምሮ) | 7 603 |
| 18 | ሰላም ቤተሰቦች
➛ 1 ተአምረ ማርያም ባለ 366ቱ ተአምር
➛ 1 ተአምረ ኢየሱስ እና
➛ 1 ስንክሳር የዓመቱ
➛ 1 ሃይማኖተ አበው
➛ አጣን
➛ ዘቢብ
➛ የሰም ጧፍ
ለእመቤታችን ቤተክርስቲያን ያስፈልጋል!
ፈቃደኛ የሆናችሁ በውስጥ መስመር @natansolo ኑ።
እስከ አሁን 12,712 ብር ደርሶልናል። | 6 103 |
| 19 | "እውነተኛ ደስታ ከውጫዊ ነገሮች መብዛት አይገኝም። ዓለም በሚሰጥህ ማዕረግ፣ ሀብትና ዝና ውስጥ ሰላምን ብትፈልግ ድካምህ ከንቱ ይሆናል። እውነተኛ ደስታ የሚገኘው ከኃጢአት በነጻች፣ እግዚአብሔርን በማመስገን በምትኖር ትሑት ልብ ውስጥ ብቻ ነው።"
(ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ) | 7 826 |
| 20 | "በወንድምህ ላይ ክፉ በምታስብበት ጊዜ የራስህን የውስጥ ሰላም እያጣህ መሆንህን እወቅ። የጥላቻ እሳት መጀመሪያ የሚያቃጥለው የያዘውን ዕቃ (ልብህን) ነው፤ ከዚያ በኋላ ነው ወደ ሌላው የሚሻገረው። ሰላም እንዲኖርህ ከፈለግህ ለሁሉም ሰው መልካም አስብ፤ ለሚበድሉህም ጭምር ጸልይ።"
(ቅዱስ መቃርስ) | 8 459 |
