ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
Channel ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (@beteafework) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 53 729 subscribers, ranking 1 006 in the Religion & Spirituality category and 591 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 53 729 subscribers.
According to the latest data from 14 June, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 621 over the last 30 days and by 41 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 21.24%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 8.61% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 11 409 views. Within the first day, a publication typically gains 4 624 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 167.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“በዚህ ቻናል የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ትምህርቶች እና የአበው ቀደምት የተናገሯቸው መንፈሳዊ ንግግሮች እንዲሁም ልዩ ልዩ ሐይማኖታዊ ትምህርቶችና መልዕክቶች ይተላለፉበታል፡፡”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 15 June, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 15 June | +7 | |||
| 14 June | +48 | |||
| 13 June | +38 | |||
| 12 June | +27 | |||
| 11 June | +22 | |||
| 10 June | +28 | |||
| 09 June | +31 | |||
| 08 June | +22 | |||
| 07 June | +21 | |||
| 06 June | +16 | |||
| 05 June | +26 | |||
| 04 June | +26 | |||
| 03 June | +24 | |||
| 02 June | +48 | |||
| 01 June | +15 |
“መጽሐፍ ቅዱስን አለማወቅ የእግዚአብሔርን ፍቅር ችላ ማለት ነው።ክፍል 5 ተለቋል👇 የሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ መልእክት ወደ ዕብራውያን ሰዎች ሐተታ ተከታታይ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት ትምህርት። https://youtu.be/7OVxHVyN6Kw?si=wmJ0Z_tGNoMpvK7S
| 2 | "የተወደድክ ወንድሜ ሆይ ይህቺን ዓለም መውደድ ልብን ታውካለች መንፈሳዊ ዓይንን ታጨልማለች ከልዑል እግዚአብሔር ታርቃለችና ይህንን እወቅ ወንድሜ ሆይ ፍቅረ ዓለምን ከአንተ ቆርጠህ ጣል።
ለክፉ ምኞትህ ባርያ አትሁን፤ ሥጋን ለመብላት ወይንን ለመጠጣት አትሳሳ። በባሕርይህ ጾር ተቃጥለህ ድል እንዳትነሳና የፈጣሪህ የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ እንዳትረሳ ለረኃብና ለጽም ተገዛ እንጂ።
በጠላቶችህ እጅ እንዳትወድቅ በየጊዜውና በየሰዓቱ ወደ እርሱ ጸልይ። ከስስትና ከንፍገት ራቅ ስማያዊ ዐይን ይገልጥልህ ዘንድ ለሰማያዊ ነጽሮት ትበቃ ዘንድ ተጋድሎና ትጋትህን አስተውለህ ያዝ።
ለኃጢአትህ ሥርየትን ይሰጥህ ዘንድ በመኮንነ ጽድቅ በኢየሱስ ክርስቶስ ፊት እንባህን አፍስስ። ከቅዱሳን ጋር ዘለዓለማዊ ዕረፍትን ገንዘብ ታደርግ ዘንድ በአጭር ዘመንህ ዕረፍትን አትውደድ። ክፉዎች መናፍስት ከአንተ እንዲርቁ የምትሻ ከሆነ መዝሙራትን ከመጸለይ አትስነፍ።
የጨለማው አበጋዞች ምሕረት የሌላቸው አጋንንት ከአንተ ይርቁ ዘንድ ለፈጠረህ እግዚአብሔር ጸልይ፡፡ በአልአዛር ማዕድ እንድትቀመጥ ራስህን ድኻ አድርግ፡፡ ለአንተ ሲል ራሱን ለሠዋ አምላክ ራስህን ሠዋ። በግርምት ዕለት ወደ ሰርጉ ጠርቶ ያደርስሃልና፡፡"
(አባ ገብረ ኪዳን - መጽሐፈ ወግሪስ ገጽ 30-31) | 3 724 |
| 3 | "ትልቁን በትንሹ አትጋርድ!"
በእውቀታቸው የተከበሩትና በትህትናቸው የሚወደዱት መንፈሳዊው መምህር የማለዳውን ትምህርት ለተማሪዎቻቸው ሰጥተው እንደጨረሱ ተማሪዎቻቸውን አሰናብተው በጥሞና ቆመው አድማሱን አሻግረው በሃሳብ እያስተዋሉ ሳለ ከተማሪዎቻቸው አንዱ "መምህር አንድ ጉዳይ አስጨንቆኝ ልጠይቅ ነው የመጣሁ" በማለት ከሄዱበት የሃሳብ አለም መለሳቸው መምህሩም ወደ ተማሪያቸው ዞር ብለው እያዩት "ጉዳዩ አስጨንቆህ ሳይሆን በጉዳዩ አንተ ተጨንቀህ ነው ፡፡ የሆነስ ሆነና ምን እንደሆነ ንገረኝ" ተማሪውም "እንዴት መሰሎዎ መምህር የቅዱስ ቃሉ ምስጢር እንዲገለጥልኝ እሻለሁ ይሁን እንጂ እለት በእለት እንዳላጠና እንቅፋት ገጥሞኛል ..."
መንፈሳዊው መምህር በጣቶቻቸው ጢማቸውን ሳብ ሳብ እያደረጉ "እንቅፋት እንደገጠመህ አመንክ፡፡ መልካም እንቅፋቱ ምንድነው?" ተማሪው ቀጠለ "የምኖረው ከወንድም እህቶቼ ጋር እናትና አባቴን ጨምሮ በአንድ ትንሽ ጎጆ ቤት ውስጥ ነው እናም ቃሉን ለማጥናት ጥሞናና ጸጥታ የማገኝበት የአፍታ ጊዜ ስለሌለ ተቸግሬያለሁ፡፡ ምን ባደርግ ይሻላል?" ችግሩን በደንብ አድምጠው የተረዱ መምህርም የተማሪያቸውን ትከሻ በፍቅር አሸት አሸት እያደረጉ "እስቲ አንድ አፍታ ወደጓሮ ዞር ዞር እንበል ምናልባት አንዳች ነገር ይገለጥልን ይሆናል" ብለው ወደ ውጭ አብረው ወጡ፡፡ "እስቲ ቀና ብለህ ወደ ሰማይ ተመልከት" አሉት "ምን ይታይሃል? " "ወሰን የሌለው ሰፊ ሰማይ" ተማሪው መለሰ "አሁን ደሞ እጅህን አይኖችህ ፊት ጋርደህ ወደላይ ተመልከት፡፡ ምንድነው የሚታይህ?" "እጄ ብቻ" "በደንብ አይተህ ንገረኝ" ብለው በቆመበት ትተውት ጥቂት እርምጃ እንደተራመዱ "መምህር ከእጄ መዳፍ እና ጣት ውጭ ምንም አይታየኝም" እርምጃቸውን ሳያቋርጡ "አየህ ልጄ ወሰን አልባውን ትልቁን ሰማይ ማየት ያልቻልከው በትንሿ እጅህ አይንህን ስለሸፈንክ ነው። ልክ እንደዚሁ ከቤተሰቦችህ ጋር በትንሽ ጎጆ መኖርህን መንፈሳዊውን እውቀት ልብህ እንዳትረዳ ጋረድክ፥ በነሱ ጨዋታና አንድ ላይ አብሮ በመኖር ፍቅር ውስጥ የቅዱስ ቃሉን ፍቺ መገለጥ ፈልግ . . ."ትልቁን በትንሹ አትጋርድ"
(ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ሲዘዋወር የተገኘ)
እኔም አልኩኝ « …ወሰን አልባውን የልባችን ቁልፍ ያላገኘነው የሌሎችን በመናፈቅ ነው»
እውነተኛ መንፈሳዊነትና የቅዱስ ቃሉ ምስጢር የሚገለጠው ፍጹም ምቾትና ጸጥታ በመፈለግ ሳይሆን፣ ባለንበት ነባራዊ ሕይወትና በቤተሰብ ፍቅር ውስጥ የእግዚአብሔርን እጅ ማየት ሲቻል ነው።
ብዙ ጊዜ በትናንሽ ምድራዊ ጭንቀቶችና "ይህ የለኝም" በሚሉ ሰበቦች ተጋርደን፣ እግዚአብሔር በውስጣችን ያስቀመጠውን ታላቅ ሰማያዊ ጸጋና ሰላም ሳናይ እንቀራለን። ስለዚህ፣ ልባችንን ከምድራዊ ጉድለቶች በላይ ከፍ በማድረግ "ትልቁን መለኮታዊ በረከት በትንሿ ምድራዊ ሰበብ አትጋርደው!" | 5 270 |
| 4 | "በልብህ ውስጥ ቂም አትያዝ። ቂም መያዝ በልብህ ውስጥ መርዝ እንደመያዝ ነው። ያ መርዝ ሌላውን ሳይሆን አንተን ይገድልሃል። ጠላትህ ቢበድልህ እርሱ ታሟል፤ አንተ ግን ይቅር ባለማለት በሽታው እንዳይጋባብህ ተጠንቀቅ።"
"የእግዚአብሔር ምሕረት ልክ እንደ ሰፊ ባሕር ነው። ወደዚህ ባሕር ውስጥ ለመግባት የምትችልበት ብቸኛው በር ግን 'ይቅርታ' ነው። አንተ ለሌሎች ይቅርታን ስትነፍግ፣ ያን በር በራስህ ላይ እየቆለፍክ ነው። እግዚአብሔር ሊምርህ ዝግጁ ነው፤ አንተ ግን ይቅር ለማለት ዝግጁ አይደለህም። ምክንያቱም ይቅር ማለት የሚችለው ይቅር ማለትን የሚያውቅ ልብ ያለው ብቻ ነውና።"
(ሊቁ አውግስጢኖስ "አባታችን ሆይ"ን ባስተማረበት ስብከቱ) | 5 895 |
| 5 | ለጤናዎ ጠቃሚ የሆነ ቻናል
የቤተሳይዳ ኬር ስፔሻሊቲ ክሊኒክ የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ በመሆን የራስዎንና የቤተሰብዎን ጤና ይጠብቁ።
ቻናሉን በመቀላቀል፦
➛ታማኝ የጤና ምክሮችንና መረጃዎችን በየቀኑ ያገኛሉ።
➛ከስፔሻሊስት ሐኪሞቻችን የተመረጡ ጠቃሚ የጤና ግንዛቤዎችን ያገኛሉ።
➛በክሊኒካችን የሚሰጡ ልዩ ልዩ የህክምና አገልግሎቶችን በቀላሉ ያውቃሉ።
አሁኑኑ ሊንኩን ተጭነው ይቀላቀሉንና የጤናዎ ባለቤት ይሁኑ👇
🔗 https://t.me/betesayda24
🔗 https://t.me/betesayda24
🔗 https://t.me/betesayda24 | 6 477 |
| 6 | ጸሎት ኃይል አላት። ጸሎት የነቢዩ ኤልያስን ቃል ሰምታ ሰማይን ዘግታለች፣ ደግሞም ከፍታለች። ጸሎት አንበሶችን አፍ ዘግታለች፣ እሳትንም አቀዝቅዛለች። በአንተም ሕይወት ውስጥ የኃጢአትን እሳት የምታጠፋው ጸሎት ናት። ተስፋ በቆረጥክ ጊዜ ጸልይ፤ ብርሃን ታገኛለህ። በኃጢአት በወደቅህ ጊዜ ጸልይ፤ መነሳትን ታገኛለህ። እግዚአብሔር 'ለምኑ ይሰጣችኋል፣ አንኳኩ ይከፈትላችኋል' ብሏል። እርሱ መስጠት ሰልችቶት አያውቅም፤ እኛ ግን መለመን እንሰለቻለን።
ወንድሞቼ ሆይ! በቤተክርስቲያንም ሆነ በቤታችሁ፣ በመንገድም ሆነ በሥራ ቦታችሁ ልባችሁ ወደ እግዚአብሔር ይጸልይ። ጸሎት ዘወትር በእጃችሁ ያለች መሣሪያ ናት። ንስሐ የገባች ነፍስ በጸሎት ካልታጠበች እድፏ አይለቅም። ስለዚህ ጸሎታችሁ ከምጽዋት ጋር ይሁን። ጸሎትና ምጽዋት በአንድነት ሆነው ወደ እግዚአብሔር ሲወጡ በፊቱ እንደ ጣፋጭ ዕጣን ይሆናሉ። በጸሎት መለመንን፣ በንስሐ መመለስን፣ በምጽዋት ማረጋገጥን አታቋርጡ።"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ንስሐ ባስተማረበት ድርሳኑ) | 6 345 |
| 7 | አስታግስልን
በዘማሪት ፋሲካ ድንቁ
መታሰቢያነቱ
በሃይማኖታቸው ምክንያት ለተገደሉ እና ከቤት ንብረታቸው ለተፈናቀሉ ወገኖች
https://youtu.be/KzVtmmpqekY?si=ZBSs1swJJZGhEvH6 | 6 269 |
| 8 | ለወላጆች የተሰጠ ትምህርት
ልጅህን ጾም አስለምደው፡፡ ኹልጊዜ ሳይኾን በሳምንት ኹለት ቀን ይኸውም ረቡዕና ዓርብ መጾምን አስለምደው፡፡ ቤተ ክርስቲያን እንዲሳለምም አድርገው፡፡
ተውኔት በሚያልቅበት በማታው ክፍለ ጊዜም ልጅህን ከተውኔት ቤት የሚወጡ ሰዎችን አሳየው፡፡ ትልልቅ ሰዎች እንደ ምን በዋዛና በፈዛዛ እንደ ተጠመዱ፣ ወጣቶችም እንደ ምን በምኞት ተቃጥለው እየወጡ እንደ ኾነ አሳየው፡፡ ልጅህንም እንዲህ ብለህ ጠይቀው፡- “እነዚህ ሰዎች ተውኔት በማየታቸው ምን ጥቅም አገኙ? ከሐፍረት፣ ከሕሊና ወቀሳና ኵነኔ ውጭ ምንም አላገኙም፡፡” ከእንደዚህ ዓይነት ትርኢቶችና ጭፈራዎች መራቅና ራስን መጠበቅ በጎ ምኞት ብሎም ሌላ በጎ ምግባር እንዲኖር የሚያደርጉት አስተዋጽኦ እንዲሁ ቀላል እንዳልኾነ ንገረው፡፡
ዳግመኛም ከፍ ባለ ፍርሐትና መንቀጥቀጥ መጸለይን አስተምረው፡፡ እንዲህ እንድታደርግ ስነግርህም ልጅ እንደዚህ ማድረግ እንደማይችል በፍጹም አትንገረኝ፡፡ ልጅ አስተዋይና ንቁ ከኾነ እነዚህን በእውነት ያለ ሐሰት ያደርጋቸዋልና፡፡ እንደ እነ ዳንኤልና ዮሴፍ የመሳሰሉ ለዚህ ማሳያ የሚኾኑን የጥንት ሰዎችም አሉ፡፡ ከዚያ በፊት ከሌሎች ከታላላቅ ወንድሞቹ ይልቅ በአባቱ ዘንድ ተወዳጅ ያደረገው ምን እንደ ኾነ አስብ አሰላስልም እንጂ ዮሴፍ ዐሥራ ሰባት ዓመቱ እንደ ነበረ አትንገረኝ፡፡
“ዮሴፍ እንዲህ ያደረገው በዐሥራ ሰባት ዓመቱ ስለ ኾነ ትልቅ ነው” ብለህ ካልከኝም እኔም እንዲህ ብዬ እጠይቅሃለሁ፡- ያዕቆብ ከእርሱ ያነሰ አልነበረምን? ኤርምያስስ? ዳንኤልስ ቢኾን [በባዕድ አገር ኾኖ ፊቱን ወደ ኢየሩሳሌም አዙሮ ሲጸልይ] ገና ዐሥራ ኹለት ዓመቱ አልነበረምን? ሰሎሞንስ፡- “እርሱ በፊትህ በእውነትና በጽድቅ፣ በልብም ቅንነት ከአንተ ጋር እንደ ኼደ፥ ከአባቴ ከባሪያህ ከዳዊት ጋር ታላቅ ቸርነትን አድርገሃል፡፡ ዛሬ እንደ ኾነም በዙፋኑ ላይ የሚቀመጥ ልጅ ሰጥተህ ታላቁን ቸርነትህን አቆይተህለታል፡፡ አሁንም አቤቱ አምላኬ ሆይ! እኔን ባሪያህን በአባቴ በዳዊት ፋንታ አንግሠኸኛል፡፡ እኔም መውጫዬንና መግቢያዬን የማላውቅ ታናሽ ብላቴና ነኝ፡፡ ባሪያህም ያለው አንተ በመረጥኸው ሕዝብህ ስለ ብዛቱም ይቈጠር ዘንድ በማይቻል በታላቅ ሕዝብ መካከል ነው፡፡ ስለዚህም ሰምቶ በሕዝብ ላይ መፍረድ ይችል ዘንድ መልካሙንና ክፉውንም ይለይ ዘንድ ለባሪያህ አስተዋይ ልቡና ስጠው፤ አለዚያ’ማ በዚህ በታላቅ ሕዝብ ላይ ይፈርድ ዘንድ ማን ይችላል?” በማለት ዕፁብ ድንቅ የኾነ ጸሎትን የጸለየው በዐሥራ ኹለት ዓመቱ አይደለምን? (1ኛ ነገ.3፡6-9)፡፡ ሳሙኤልስ የገዛ መምህሩን ራእይ በማየት የነገረው ገና በሕፃንነቱ ሳለ አይደለምን? (1ኛ ሳሙ.3፡17)፡፡ ስለዚህ “ልጅ ስለ ኾነ መጸለይ አይችልም” አትበል፡፡ በነፍሱ ሕፃን የኾነ ሰው አድጎም ቢኾን እነዚህን ነገሮች አያደርጋቸውምና፡፡
በመኾኑም ልጃችን በታላቅ ፍርሐትና መንቀጥቀጥ ኾኖ መጸለይን ይልመድ፡፡ የዓቅሙን ያህል ትግሃ ሌሊትን ይልመድ፡፡ የቅድስና አኗኗር በኹለንተናው ላይ ይታተምበት፡፡ ከመሐላ፣ ከሚሰድቡት ሰዎች፣ የሌሎችን ስም ከማጥፋትና ከጥላቻ ከራቀ፣ ጎን ለጎንም ጾምንና ጸሎትን ገንዘብ ካደረገ እነዚህ ኹሉ ወደ ምግባር ወደ ትሩፋት ያደርሱት ዘንድ በቂ ናቸው፡፡
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ኦርቶዶክሳዊ ቤተሰብ መጽሐፍ፣ ገጽ 122-124) | 7 086 |
| 9 | ሰላም ተወዳጆች
የቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቻናልን እስከአሁን በግል የኢንተርኔት ወጭዎችን በመሸፈን ጠቃሚ ይሆናሉ ያልናቸውን መንፈሳዊ መልዕክቶችና የቅዱሱን ትምህርቶች ስናስተላልፍ መቆየታችን ይታወቃል።
አሁን ላይ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ አንጻር የዳታ (የኢንተርኔት) ወጪ መሸፈን የሚቻልበት ሁኔታ ከባድ እየሆነ መጥቷል፤ ስለሆነም የኢንተርኔት ወጪ ለመሸፈን ያስችለን ዘንድ ከቻናሉ ጋር ተስማሚ የሆኑ ማስታወቂያዎችን ለመስራት ስላሰብን ማንኛውም ምርትና አገልግሎቱ እንዲተዋወቅለት የሚፈልግ ግለሰብ በተመጣጣኝ ክፍያ የምናስተናግድ መሆናችንን ለማሳወቅ እንወዳለን።
ከቻናሉ ጋር ተስማሚ የሆነ ማስታወቂያ ማሠራት የሚፈልግ ካለ በውስጥ መስመር @natansolo ማናገር ይችላል። | 6 691 |
| 10 | አንድ ሰው ነበር ሁሌም ሥራ ውሎ ወደ ቤቱ ሲገባ በቅድሚያ የሚያየው ነገር ከቤቱ ግድግዳ ላይ ያለውን የክርስቶስን ቅዱስ ሥዕል ነው። ሥራው አድካሚ ነው። "ይበቃኛል" የሚለውን ዓይነት ገንዘብ አያገኝበትም። ስለዚህ ሁል ጊዜ እንደ ተነጫነጨና እንዳማረረ ነው።
ከሥራ ደክሞት ቤት ሲገባ በመጀመሪያ የሚያገኘው ደግሞ ሥዕለ ክርስቶስን በመሆኑ፣ የመጀመሪያውን ምሬቱን በጸሎት የሚገልጸው በርሱ ፊት ነው።
"ተው ግን ተው ጌታዬ ሎተሪ እንዲደርሰኝ አድርግ" ይላል ዘወትር ወደ ሥዕሉ ዞሮ።
ከሥራ ወደ ቤቱ ሲገባ ሥዕሉ ፊት የሚያቀርበው የሁልጊዜ ልመናው/ንጭንጩ/ምሬቱ ይህ ነው:-
ከዕለታት በአንዱ ታዲያ ሥራ ውሎ ደክሞት ወደ ቤቱ ሲገባ እንደለመደው "ጌታ ሆይ ምናለ ግን ሎተሪ ቢደርሰኝ?" ሲል
የጌታ ሥዕልም በሰው አንደበት "ልጄ እባክህ እስኪ መጀመሪያ ትኬት ቁረጥ" አለው። ለካንስ "ሎተሪ ካልደረሰኝ" ሲል የነበረው ትኬት እንኳን ሳይቆርጥ ነበር።
እንደዚህ ሰውዬ የድርሻችንን ሳንወጣ ዱብ የሚል ስኬትን የምንጠብቅ ብዙዎች እንኖራለን፤ እንዲሁ ቁጭ ብለን ፈጣሪን "ካልሰጠኸኝ" ብለን የምናማርር።
በቅድሚያ እስኪ ትኬቱን እንቁረጥ፤ የድርሻችንን እንወጣ።
(ከመምህር ህሊና በለጠ) | 7 556 |
| 11 | የእውነተኛ ክርስትያን መግለጫው ምንድን ነው?
ፀሐይ ብርሃን ካልሰጠች ፀሐይ አትባልም፤ ብርሃን አለመስጠት ተፈጥሮዋ አይደለምና፡፡ እንስሳት ካልተነፈሱ እንስሳት አይባሉም፤ መተንፈስ ተፈጥሮአቸው ነውና፡፡ ዓሣ ከውኃ ከወጣ ሕይወት ያለው ዓሣ መኾኑ ይቀርና ይሞታል፡፡ አንድ ክርስቲያንም እውነተኛ ክርስቲያን የሚባለው፡-
ሲጸልይ ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት በወልድ ውሉድ በክርስቶስ ክርስቲያን በመንፈስ ቅዱስም መንፈሳዊ መባል ነውና፡፡ ልጅ ከኾኑ ደግሞ አባትን ማናገር ክርስቲያናዊ ተፈጥሮ ነውና፡፡
ሲያመሰግን ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት እግዚአብሔር ፈጣሬ ዓለማት ነው ብሎ ማመን ነውና፡፡ ስለዚህ ለአንድ ክርስቲያን የሰማይና የምድር ውበት እየተመለከተ እግዚአብሔርን ማመስገኑ ክርስቲያናዊ ተፈጥሮው ነው፡፡
ሲመጸውት ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት ሀብት ኹሉ ከእግዚአብሔር እንደ ኾነ መመስከር ነውና፡፡ ስለዚህ ራስን እንደ መልእክተኛ አድርጎ በመቁጠር ያለውን ለሌላው ማካፈል ክርስቲያናዊ ተፈጥሮው ነውና፡፡
ቅዱሳት መጻሕፍትን ሲያነብ ነው፡፡ ክርስቲያን ማለት በመንፈስ ቅዱስ ሀብት ደስ የሚሰኝ ነውና፡፡ይህን ለማድረግ ደግሞ መንፈስ ቅዱስ በቅዱሳት መጻሕፍት በኩል ሲናገር መስማት ለአንድ ክርስቲያን ክርስቲያናዊ ተፈጥሮው ነውና፡፡
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - ከአምስቱ የንስሐ መንገዶች መጽሐፍ ገጽ 49) | 7 729 |
| 12 | ሰላም ተወዳጆች
የቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቻናልን እስከአሁን በግል የኢንተርኔት ወጭዎችን በመሸፈን ጠቃሚ ይሆናሉ ያልናቸውን መንፈሳዊ መልዕክቶችና የቅዱሱን ትምህርቶች ስናስተላልፍ መቆየታችን ይታወቃል።
አሁን ላይ ካለው ወቅታዊ ሁኔታ አንጻር የዳታ (የኢንተርኔት) ወጪ መሸፈን የሚቻልበት ሁኔታ ከባድ እየሆነ መጥቷል፤ ስለሆነም የኢንተርኔት ወጪ ለመሸፈን ያስችለን ዘንድ ከቻናሉ ጋር ተስማሚ የሆኑ ማስታወቂያዎችን ለመስራት ስላሰብን ማንኛውም ምርትና አገልግሎቱ እንዲተዋወቅለት የሚፈልግ ግለሰብ በተመጣጣኝ ክፍያ የምናስተናግድ መሆናችንን ለማሳወቅ እንወዳለን።
ከቻናሉ ጋር ተስማሚ የሆነ ማስታወቂያ ማሠራት የሚፈልግ ካለ በውስጥ መስመር @natansolo ማናገር ይችላል። | 6 754 |
| 13 | "በአርምሞና በመንፈስ እርጋታ ውስጥ ናችሁን? ከሆናችሁ እግዚአብሔር ይህን ቋሚ ያደርግላችሁ ዘንድ ለምኑት። በመከራዎችና በችግሮች ከፍተኛ ጥቃት ትታወካላችሁን? እግዚአብሔር በሕይወታችሁ ውስጥ ያለውን ማዕበል ፀጥ እንዲያደርግላችሁ ለምኑት። ጸሎታችሁ ተሰምቷልን? እግዚአብሔርን አመስግኑ። አልተደመጣችሁምን? እስከምትደመጡ ድረስ በጸሎታችሁ በጽናት ቆዩ።
እግዚአብሔር ልመናችሁን ባይመልስላችሁ እንኳ፣ በጸሎት በመጽናታችሁ ብቻ ትልቅ ዋጋን ታገኛላችሁ። ምክንያቱም ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገርና ከእርሱ ጋር መቆየት ከሁሉ በላይ የሆነ ታላቅ ደስታና ረብሕ (ትርፍ) ነውና።"
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ ጸሎት በተናገረበት ድርሳኑ) | 8 593 |
| 14 | ድርሳን 9 (የመጨረሻ)
ድርሳነ ንስሐ ዘቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
"ወንድሞቼ ሆይ! ስለ ንስሐ ስናገር ዘጠነኛውና የመጨረሻው ድርሳኔ ነው። ዛሬም ዳግመኛ ልመክራችሁ እወዳለሁ፤ የንስሐን በር ዛሬውኑ አንኳኩ። ይህቺ ዓለም እንደ ጥላ የምታልፍ ናት፤ ሞት ደግሞ ሳናስበው እንደ ሌባ በድንገት ይመጣል። ብዙዎች 'ነገ ንስሐ እገባለሁ' ይላሉ፤ ነገር ግን ያቺ 'ነገ' ሳትመጣ ሞት ይቀድማቸዋል። እግዚአብሔር ዛሬን እንድንመለስ ሰጠን እንጂ ነገን ለኛ እንደሚሆን ቃል አልገባልንም። ስለዚህ ዕድሉ በእጃችሁ ሳለ ንስሐ ግቡ።
ሞትን ማሰብ ለነፍስ ትልቅ ጥበብ ነው። ሞትን የሚያስብ ሰው ኃጢአት ለመሥራት አይቸኩልም፤ ንስሐ ለመግባት ግን ይተጋል።
እስኪ አስተውሉ፤ በዚያ በሚያስፈራ የፍርድ ቀን በእግዚአብሔር ፊት ስንቆም ምን እንመልሳለን? በዚያ ቀን መላእክት ይንቀጠቀጣሉ፤ መጻሕፍት ይገለጣሉ፤ የተሰወረውም ሁሉ ግልጽ ይሆናል። ያን ጊዜ ሀብታችሁ፣ ሥልጣናችሁ ወይም ወዳጆቻችሁ ሊረዷችሁ አይችሉም። የሚረዳችሁ በምድር ላይ የሠራችሁት ንስሐና ምግባር ብቻ ነው።
በዚህ ዓለም ላይ ሳለን ንስሐ መድኃኒት ናት፤ ከሞት በኋላ ግን ንስሐ ለቅሶ ብቻ ናት። እዚህ ዓለም ላይ እያለህ 'በድያለሁ' ብትል እግዚአብሔር ይቅር ይልሃል፤ በዚያ ግን ብትጮኽ የሚሰማህ የለም። እዚህ ንስሐ ሰማይን ትከፍታለች፤ በዚያ ግን የንስሐ በር ዝግ ነው። ነፍስ ከሥጋ ከመለየቷ በፊት ዕድሉን ተጠቀሙበት። የታመመ ሰው ሕይወቱ ስላለች ሐኪም ዘንድ ይሄዳል፤ ከሞተ በኋላ ግን ሐኪሙ ምን ሊያደርግለት ይችላል? የእኛም ነፍስ በሕይወት ሳለን በንስሐ ትፈወስ ዘንድ ይገባታል።
ወንድሞቼ ሆይ! ተስፋ አትቁረጡ፣ ነገር ግን አትዘናጉም። እግዚአብሔር መሐሪ መሆኑ ንስሐችሁን እንድታዘገዩ አያድርጋችሁ። ይልቁንም መሐሪ ስለሆነ 'እንዲህ ያለውን አምላክ እንዴት በደልኩ?' ብላችሁ በፍቅር ተመለሱ። ሰይጣን 'ገና ወጣት ነህ፣ በኋላ ትጸልያለህ' እያለ የንስሐን ጊዜ ይሻማችኋል። አንተ ግን 'ዛሬውኑ የጌታዬን ፊት እፈልጋለሁ' በለው። ኃጢአት የሠራኸው ትናንት ቢሆንም፣ ንስሐ የምትገባው ዛሬ ቢሆንም፣ እግዚአብሔር ግን የቀድሞውን በደልህን አይቆጥርብህም። እርሱ የሚመለከተው የአሁኑን መመለስህን ነው።
መጨረሻው ሲደርስ ንጹሐን በክብር ወደ መንግሥተ ሰማያት ይገባሉ፤ ንስሐ ያልገቡ ግን ወደ ዘላለም ጨለማ ይጣላሉ። ያን ጊዜ የጥርስ ማፋጨትና ዋይታ ይሆናል። ያን ጊዜ ከማልቀስ ይልቅ ዛሬ ማልቀስ ይሻላል። ዛሬ የምታፈሰው ጥቂት እንባ የገሃነምን እሳት ታጠፋለች። ዛሬ የምትሰግደው ስግደት ነገ ከፍ ያደርግሃል።
ወንድሞቼ ሆይ! ራሳችሁን አዘጋጁ። ልባችሁን ከዓለም ፍቅር አጽዱ፤ ለሰማያዊው ቤት ተዘጋጁ።
ለማጠቃለል ያህል፤ በነዚህ ዘጠኝ ድርሳናት ውስጥ የነገርኳችሁን ሁሉ በልባችሁ አኑሩ። ኃጢአት ቍስል እንደሆነ፣ ንስሐ መድኃኒት እንደሆነች፣ ጸሎትና ምጽዋት ደግሞ የንስሐ ክንፎች መሆናቸውን አትርሱ። በትሕትና ኑሩ፣ ቂምን አስወግዱ፣ በቃለ እግዚአብሔር ታነጹ፣ በቅዱስ ቍርባንም ከጌታችሁ ጋር ተዋሃዱ። በምድር ላይ በንስሐ የኖረ በሰማይ ከቅዱሳን ጋር ይነግሣል።
እግዚአብሔር ሁላችንንም በንስሐ አጽንቶ ለመንግሥቱ ያብቃን። አሜን።" | 9 379 |
| 15 | https://youtu.be/KzVtmmpqekY?si=ZBSs1swJJZGhEvH6 | 8 737 |
| 16 | ድርሳን 8
ድርሳነ ንስሐ ዘቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
"ወንድሞቼ ሆይ! ዛሬ ስለ ንስሐ ልናገር ስነሳ ስምንተኛ ጊዜዬ ነው። ዛሬ ደግሞ ንስሐን ስለሚያጸናው የሕይወት ምግብ ስለሆነው ስለ ቅዱስ ቍርባን አስተምራችኋለሁ።
ንስሐ የገባ ሰው እንደ ተጋዳይ ወታደር ዘወትር ንቁ መሆን አለበት። ኃጢአትን ትተሃልና 'አሁን ሰላም አግኝቻለሁ' ብለህ አትዘናጋ፤ ይልቁንም ጠላት ሰይጣን ያመለጠውን በግ ለመመለስ በበለጠ ቁጣ ይነሳብሃልና። ንስሐ የገባ ሰው በተጋድሎ ካልጸና፣ የኋላኛው ውድቀቱ ከቀድሞው ይከፋል።
መንፈሳዊ ተጋድሎ ማለት ምን ማለት ነው? ተጋድሎ ማለት ፈቃደ ሥጋን ለፈቃደ ነፍስ ማስገዛት ነው። ዐይንህ ክፉ እንዳያይ፣ ጆሮህ ሐሜት እንዳይሰማ፣ ልብህም ወደ ክፉ ምኞት እንዳያዘነብል መጠበቅ ትልቅ ተጋድሎ ነው።
ንስሐ የገባህ ሰው ሆይ! ከቀድሞ ከኃጢአት ቦታዎች ራቅ። የታመመ ሰው ከበሽታው ካገገመ በኋላ ጤናውን ለመጠበቅ እንደሚጠነቀቅ፣ አንተም የነፍስህን ጤና ለመጠበቅ ከፈተናዎች ሽሽ። መጾም፣ መጸለይና በትጋት መቆም ነፍስን የሚያጠነክሩ የተጋድሎ መሣሪያዎች ናቸው።
ነገር ግን የዚህ ሁሉ ተጋድሎና የንስሐችን ፍጻሜውና ማረፊያው ወደ ጌታ ማዕድ መቅረብ ነው። ቅዱስ ቍርባን ለተነስሕያን የተዘጋጀ የሕይወት መድኃኒት ነው። ኃጢአት ነፍስን ይገድላታል፤ የክርስቶስ ሥጋና ደም ግን ሕይወትን ይሰጣታል። በንስሐ ታጥበህ፣ በልቅሶ ነጽተህ ስትመጣ ይህ ምስጢር ላንተ ብርሃን ይሆንልሃል። 'ይህንን የሚበላ ለዘላለም ይኖራል' ተብሏልና። ነገር ግን ወንድሞቼ ሆይ! ወደዚህ ምስጢር ስትቀርቡ በታላቅ ፍርሃትና በመንቀጥቀጥ ይሁን። ይህ ተራ ምግብ አይደለም፤ ይህ የመላእክት ንጉሥ ሥጋና ደም ነውና።
ብዙዎች በበዓላት ቀን ብቻ ለመቁረብ ይጣደፋሉ። እኔ ግን እላችኋለሁ፦ በዓል ስለሆነ ሳይሆን ንጹሕ ሕሊና ሲኖራችሁ ቅረቡ። በዓል መሆኑ ኃጢአተኛን ጻድቅ አያደርገውም፤ ንስሐ ግን ማንኛውንም ቀን በዓል ታደርገዋለች።
በልብህ ክፋትን፣ በቀልንና ዝሙትን ይዘህ ብትቆርብ፣ ቍርባኑ ይፈርድብሃል እንጂ አይቀድስህም። ይሁዳ ጌታ የሰጠውን ኅብስት በበላ ጊዜ፣ በልቡ ክፋት ስለነበረ ሰይጣን ገባበት። አንተም እንደ ይሁዳ ጌታን በመሳም አሳልፈህ አትስጠው። በንስሐ ሳትታጠብ፣ ከባልንጀራህ ጋር ሳትታረቅ ብትቆርብ ጌታን ዳግመኛ እየሰቀልኸው ነው።
ወንድሞቼ ሆይ! ቤተክርስቲያን መድኃኒት ቤት ናት። ንስሐ ፈዋሽ ናት፤ ቅዱስ ቍርባን ደግሞ ኃይል ሰጪ ምግብ ነው። የታመመ ሰው መድኃኒት ወስዶ ካገገመ በኋላ ብርታት እንዲሆነው ምግብ እንደሚበላ፣ አንተም በንስሐ ከዳንህ በኋላ ለነፍስህ ብርታት የክርስቶስን ሥጋና ደም ተቀበል። ይህንን ስታደርግ ሰይጣን ካንተ ይሸሻል፤ መላእክትም ባንተ ዙሪያ ይሰበሰባሉ። የክርስቶስ ደም በከንፈሮችህ ላይ ሲታይ ጠላት ይደነግጣል፤ ሞትም ካንተ ይርቃል።
ስለዚህ ንስሐችሁ በተጋድሎ የታጀበ፣ በተግባር የተገለጠ ይሁን። ዘወትር በጸሎት ትጉ፤ በጾም ሰውነታችሁን ግሩ፤ በምጽዋት ነፍሳችሁን አስውቡ። ከዚህ ሁሉ በኋላ ደግሞ በንጹሕ ልብ ሆናችሁ ወደ ቅዱስ ቍርባን ቅረቡ። በምድር ላይ የክርስቶስን ሥጋና ደም በንጽሕና የተቀበለ፣ በሰማይም ከእርሱ ጋር በማዕዱ ይቀመጣል። እግዚአብሔር ለዚህ ክብር ያብቃን።" | 9 487 |
| 17 | ድርሳን 7
ድርሳነ ንስሐ ዘቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
"ወንድሞቼ ሆይ! ዛሬ ስለ ንስሐ ልናገር ስነሳ ሰባተኛ ጊዜዬ ነው። ዛሬ ደግሞ የንስሐን በር በኃይል ስለሚዘጋውና ጸሎታችን ወደ ሰማይ እንዳይወጣ ስለሚከለክለው ስለ ቂም በቀል አስተምራችኋለሁ።
ንስሐ ማለት ከእግዚአብሔር ጋር መታረቅ ነው፤ አንተ ግን ከባልንጀራህ ጋር ሳትታረቅ እንዴት ከፈጣሪህ ጋር ልትታረቅ ትችላለህ? በልቡ ቂም ይዞ ንስሐ የሚገባ ሰው በውኃ ላይ ቤት እንደሚሠራ ሰው ነው።
እስኪ ጌታችን በወንጌል ያስተማረውን አስተውሉ። 'መባህን በመሠዊያው ፊት አቅርበህ ሳለህ፣ ወንድምህ አንዳች ነገር በአንተ ላይ እንዳለው ብታስብ፣ መባህን በመሠዊያው ፊት ትተህ ሂድ፤ አስቀድመህም ከወንድምህ ጋር ታረቅ' ይላል (ማቴ 5፥23)። ጌታችን 'መባህን አቅርብና በኋላ ታረቅ' አላለም። 'አምልኮህን አቁምና ሂድና ታረቅ' አለ እንጂ። እግዚአብሔር የእርሱን ክብርና አምልኮ ትተህ ወደ ወንድምህ እንድትሄድ ማዘዙ፣ እርቅ በፊቱ ምን ያህል የከበረ መሆኑን ለማሳየት ነው። ሰላም ከሌለ አምልኮ የለም፤ ፍቅር ከሌለ ንስሐ የለም።
ወንድሞቼ ሆይ! ቂም በልብ ውስጥ እንዳለ መርዝ ነው። መርዝ በሰውነት ውስጥ ካለ ምግብ ለሰውነቱ እንደማይጠቅም ሁሉ፣ ቂም በልብ ውስጥ ካለ ጾምና ጸሎት ለነፍስ አይጠቅሙም። ሰይጣን ሌላውን ኃጢአትህን ልትተወው ስትል ቂምን በልብህ ይተክላል፤ ምክንያቱም ቂም በልብህ ካለ እግዚአብሔር ጸሎትህን እንደማይሰማው ያውቃልና። 'እኛ የበደሉንን ይቅር እንደምንል በደላችንን ይቅር በለን' ብለን ስንጸልይ፣ እግዚአብሔር እኛን ይቅር የሚልበትን መስፈርት በእጃችን ሰጥቶናል። አንተ ይቅር ካላልህ 'ይቅር አትበለኝ' ብለህ በራስህ ላይ እየፈረድክ ነው።
ብዙዎች 'እርሱ ነው የበደለኝ፣ እኔ እንዴት መጀመሪያ ልታረቅ እሄዳለሁ?' ይላሉ። አንተ ክርስቲያን ከሆንክ መጀመሪያ ሂድ፤ ክርስቶስ እኛ በበደልነው ጊዜ እርሱ መጀመሪያ ወደ እኛ መጥቶ ታረቀን እንጂ እኛ አልሄድንም። ጠላትን ይቅር ማለት ታላቅ ተጋድሎ ነው፤ የንስሐም ትልቁ ማረጋገጫ ነው። ጠላትህን ይቅር ስትል ለእርሱ ውለታ እየዋልክለት እንዳይመስልህ፤ አንተ ራስህን ከገሃነም እስራት እየፈታህ ነው እንጂ። ቂም የያዘ ሰው ራሱን በጨለማ ቤት ውስጥ የቆለፈ እስረኛ ነውና።
ወንድሞቼ ሆይ! ወደ ቤተክርስቲያን ስትመጡና በቅዱስ ቍርባን ለመሳተፍ ስትዘጋጁ ልባችሁን መርምሩ። ያንን የሚያስፈራና የከበረ ምስጢር ለመቀበል ስትመጡ በልባችሁ ቂም ካለ፣ ያ ቍርባን ለእናንተ መድኃኒት ሳይሆን እሳት ይሆንባችኋል። ይሁዳ በልቡ ክህደትንና ክፋትን ይዞ በጌታ ማዕድ ስለተካፈለ ሰይጣን ሰለጠነበት። አንተም በልብህ ቂም ይዘህ ወደ ጌታ ማዕድ አትቅረብ። መጀመሪያ ከባልንጀራህ ጋር ታረቅ፤ ከዚያም በንጹሕ ልብ ሆናችሁ ጌታህን ተቀበል።
ንስሐ የገባ ሰው ምላሱ ከሐሜት፣ ልቡም ከቂም የራቀ መሆን አለበት። ወንድምህን በምላስህ እያማህ እግዚአብሔርን በምላስህ ብታመሰግነው ምስጋናህ አይሰማም። ባልንጀራህን በልብህ እየጠላህ እግዚአብሔርን ብትወደው ውሸታም ነህ። ስለዚህ ንስሐችሁ ፍጹም ይሆን ዘንድ ቂምን አስወግዱ። እንደ ጌታችን በትሕትና ሆናችሁ 'አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው' በማለት ስለሚጠሉአችሁ ጸልዩ። ያን ጊዜ እውነተኛ የሰላም ልጆች ትሆናላችሁ፤ ንስሐችሁም በሰማይ መላእክት ዘንድ ደስታን ያመጣል።" | 10 491 |
| 18 | ጸሎት ክፋ ሀሳብ ከውስጣችን የሚወገድበት መንገድ ነው። ከጨለማ ኃይላት ርቆ ወደ መንፈሳዊ ሕይወት መግባት የሚቻለውም በጸሎት ነው።
አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ | 9 456 |
| 19 | በልጅ የተፈተነ ትዳር
https://youtu.be/oupApApPwuE?si=Nyy95RAQ5UH9ul-I | 10 871 |
| 20 | ድርሳን 6
ድርሳነ ንስሐ ዘቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
"ወንድሞቼ ሆይ! ስለ ንስሐ ልናገር ስነሳ ስድስተኛ ጊዜዬ ነው። ዛሬ ደግሞ ንስሐ ፍሬ እንድታፈራና በመንገዷም እንድንጸና ስለምታደርገው ስለ ቅዱሳን መጻሕፍት ንባብ አስተምራችኋለሁ።
የእግዚአብሔር ቃል ለነፍስ እንደ መስታወት ነው። አንድ ሰው ፊቱ ላይ እድፍ ቢኖር መስታወት ዓይቶ ካላወቀው በስተቀር ሊታጠብ አይችልም። እኛም በነፍሳችን ላይ ያለውን የኃጢአት እድፍ ማወቅ የምንችለው በመለኮታዊ መጻሕፍት መስታወትነት ነው። መጽሐፍ ቅዱስን ስናነብ ኃጢአታችንን እናያለን፤ ስናይም እንጸጸታለን፤ ስንጸጸት ደግሞ ንስሐ እንገባለን።
ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ ለነፍስ እንደ ሰማያዊ ገነት ነው። በገነት ውስጥ ጥሩ መዓዛ ያላቸው አበቦች እንደሚገኙ ሁሉ፣ በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥም ነፍስን የሚያድሱ የአባቶች ሕይወት፣ የነቢያት ትንቢትና የሐዋርያት ትምህርት ይገኛሉ።
የዓለምን ወሬና ከንቱ ንግግር ከመስማት ይልቅ የእግዚአብሔርን ቃል መስማት ምንኛ ታላቅ ዕድል ነው! ብዙ ሰዎች 'እኔ ዓለማዊ ሰው ነኝ፣ ሥራ አለብኝ፣ መጽሐፍ ቅዱስን ማንበብ የባሕታውያንና የካህናት ሥራ ነው' ይላሉ። ይህ ትልቅ ስህተት ነው! ይልቁንም በዓለም ግርግርና ውጥረት ውስጥ ለምትኖሩት ለእናንተ የእግዚአብሔር ቃል መድኃኒት ሆኖ ያስፈልጋችኋል። በባሕር ላይ የሚጓዝ መርከበኛ መሪ እንደሚያስፈልገው፣ እናንተም በዚህ ዓለም ማዕበል ውስጥ ስትጓዙ መሪያችሁ የእግዚአብሔር ቃል ሊሆን ይገባል።
ቅዱሳት መጻሕፍት የሰይጣንን ውጊያ ድል ማድረጊያ መሣሪያዎች ናቸው። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገዳመ ቆሮንቶስ በሰይጣን በተፈተነ ጊዜ ድል ያደረገው 'ተብሎ ተጽፏል' በማለት በመጻሕፍት ቃል ነበር። እኛም የሰይጣንን ክፉ ሐሳብና ፈተና ድል የምናደርገው በቃሉ ኃይል ነው። መጽሐፍ ቅዱስ የሚነበብበት ቤት ሰይጣን ሊገባ አይደፍርም፤ የእግዚአብሔር ጸጋ ግን በዚያ ቤት ላይ ያድራል።
ወንድሞቼ ሆይ! ቃሉን ስታነቡ ዝም ብላችሁ ቃላትን ለመቁጠር ብቻ አይሁን። ነገር ግን በቃሉ ውስጥ ያለውን መንፈሳዊ ጣዕም ለማግኘት ጸልዩ። የምታነቡትን በተግባር ለመተርጎም ትጉ። 'ቃሉን የሚሰሙ ብቻ ሳይሆኑ የሚያደርጉት ይጸድቃሉ' ተብሏልና። አንድ ምዕራፍ እንኳ ብታነቡ ያቺ ለአንድ ቀን ስንቅ ትሆናችኋለች። ንስሐ የገባ ሰው ልቡ በቃለ እግዚአብሔር ካልታጠበ ዳግመኛ ወደ ኃጢአት ጭቃ መመለሱ አይቀርም። ቃሉ ግን ልባችሁን ይጠብቃል፤ አእምሮአችሁንም ያበራል።
ሰዎች ሆይ! መጻሕፍትን አትናቁ። እነርሱ ከሰማይ ወደ እኛ የተላኩ ደብዳቤዎች ናቸው። የሰማዩ ንጉሥ የላከልህን ደብዳቤ ችላ ብለህ እንዴት ሰላምን ታገኛለህ? በመጻሕፍት ውስጥ የታመሙት ፈውስን፣ ያዘኑት መጽናናትን፣ የወደቁት መነሳትን፣ ንስሐ የገቡት ደግሞ የተስፋን ብርሃን ያገኛሉ። በቃለ እግዚአብሔር የምትታጠብ ነፍስ ዘወትር ለምለም ትሆናለች።
ስለዚህ በቤታችሁ መጻሕፍትን ለማንበብ ጊዜ መድቡ። ልጆቻችሁንም በቃለ እግዚአብሔር ኮትኩቱ። ዓለማዊ እውቀት ለሥጋዊ ሕይወት ይጠቅም ይሆናል፤ መንፈሳዊ እውቀት ግን ለዘላለም ሕይወት ያበቃል። ንስሐችሁ ፍጹም ይሆን ዘንድ፣ ሕሊናችሁም ከክፉ ሐሳብ ይነጻ ዘንድ ዘወትር በመለኮታዊ መጻሕፍት ንባብ ተጉ። እግዚአብሔር ቃሉን በልባችን ይጻፍልን።" | 11 195 |
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
